Professional Documents
Culture Documents
+++
+++
/ /
ይድረስ ለፈጣሪ መንበረ ጸባዖት
ከትልቁ ሥፍራ ከሰማዩ መንግሥት
ፍርድ ሳይዛነፍ ከሚፈጸምበት፡፡
ላኪው በምድር ላይ ግፍ የደረሰብኝ
ጐስቋላ አገልጋይህ ደካማው ባሪያህ ነኝ፡፡
ሳጥናኤል የሚሉት የቀድሞ ጠላቴ
ቂሙን ሳይዘነጋ እንደ አዳም አባቴ
ከገነት ሊያስቀረኝ ቀጥቅጦ ጥሎኛል
በአፍና አፍንጫዬ ደግሞም በጆሮቼ
መርዙ ተጠቅጥቆ በየብልቶቼ
አውጣኝ እያልኩህ ነው እባሕር ገብቼ፡፡
ደካማ ነኝና ራሴን አልቻልኩም
ለመታገል ሞከርኩ ከእጁም አልወጣሁም
ፍርድ ሰጭው ዳኛ ችግሬን ቃኝተኸው
መፍትሔ እንድትሰጠኝ ወዳንተ እጮኻለሁ፡፡
ኧረ ማን ነው
የበደለውን አስታውሶ
ያጠፋውን ክሶ
ያለውን ለግሦ
ታዛዥ ለፈጣሪ
እውነትን መስካሪ
የእምነትን ፋና አብሪ
ማነው እውነተኛ;
ከኃጢአት ፆመኛ
ኑ ወደ ሕይወት ምንጭ
ምንድን ነው ድርሻዬ
ሰው ሆይ እስቲ ዕወቅ
ዐዋቂውን ጠይቅ
ምንድን ነው ድርሻዬ
ንገረኝ ጌታዬ;
በማለት ጠይቀው
ድርሻህን ሳትለየው
ጉዞ አትጀምር
እንዲያው በግርግር
ምንድን ነው ሥራዬ
ንገረኝ ጌታዬ
በልና ጠይቀው
በጸሎት አሳስበው
ሥራህን ዕወቀው
ድረሻህን ተረዳው
ልከተል ጊዮርጊስን
ቅድስት ኢየሉጣን
ሕፃኑ ቂርቆስን
ሠለስቱ ደቂቅን
የሰማዕቱን ሕይወት
ዋጋ እንዳገኝበት
በኃይልህ በረከት
ወይስ በዓለም ልዙር
ወንጌልን ላስተምር
ላልሰሙት ልናገር
የለደትህን ምሥጢር
ለልምድ ተመላላሽ
በአካል ብቻ ገሥጋሽ
በማያውቁት መኻል
ልናገር ያንተን ኃይል
ላስተምር ጥምቀትን
እንዲሁም ስቅለትን
ልናገር ስለዕርገት
ስለ ዳግም ምፅዓት
ወይንስ ጌታዬ
መካሪ አለኝታዬ
በበአት ልወሰን
በጸሎት ልለምን
ያልተከተለህን
ያላወቀ ሕግህን
እንድታሳውቀው
በፍቅር እንድትቀርበው
ከገባበት ዓለም
እንዲድን በአንተ ደም
አሁንም ጌታዬ
መካሪ አለኝታዬ
የሆነውን ለእኔ
ባለችኝ ዘመኔ
በልና ጠይቀው
ድርሻህን ዕወቀው
ለእኛ የሆነውን
ባለ ዘመናችን
የምንፈጽመውን
እንድታሳውቀን
ቸር ፈቃድህ ይሁን
ማለቱ ይሻላል
እርሱም ይመራናል፡፡
አደራ እልሻለሁ
አደራ እልሻለሁ