Professional Documents
Culture Documents
Education Sector Five Year Growth and Transformation Plan Updated 8september 2010
Education Sector Five Year Growth and Transformation Plan Updated 8september 2010
ትምህርት ሚኒስቴር
2002 ዓ.ም.
1
ማ ው ጫ
ተ/ቁ ርዕስ ገጽ
1 መግቢያ .................................................................................................... 3
2 ያለፈው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም አፈጻጸም ግምገማ
/1998-2002 ዓ/ም/ ..................................................................................... 4
3 የትምህርት ዘርፍ የአምስት ዓመት /2003-2007/ ዕቅድ ................................... 29
2
1.መግቢያ
መንግሥት ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ልማትን በሃገር አቀፍ ደረጃ በማረጋገጥ ድህነትን ለመቀነስና
ለማስወገድ ግልፅ የሆነ ራዕይ አስቀምጧል።ይህም በ2017 ዓ.ም ኢትዮጵያን መካከለኛ ገቢ
ካላቸው ዲሞክራሲያዊ አገሮች ተርታ ተሰልፋ ማየት ነው። ይህን ታላቅ ራዕይ ዕውን ለማድረግ
ደግሞ የትምህርት ዘርፍ ልማት ታላቅ የማስፈጸም አቅም ግንባታ ሚና አለው።
ከዚህ አኳያ ለሃገር አቀፉ ዘላቂ ልማትና የድህነት ቅነሣ ፕሮግራም በግብዓትነት የሚያገለግል
የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም የመካከለኛ ጊዜ ዕቅድ በፌዴራል የትምህርት ሚኒስቴርና
በክልል መንግስታት ሰፊና ንቁ ተሳትፎ ተዘጋጅቷል ፡፡ ዝግጅቱ በፌዴራል የትምህርት
ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር የቅርብ ክትትልና ድጋፍ የተደረገለት ሲሆን በሚኒስቴር መ/ቤቱ
የዕቅድ ዝግጅትና ሐብት ማፈላለግ ማኔጅመንት የሥራ ሂደት አስተባባሪነት ከሁሉም የሚኒስቴር
መ/ቤቱ የሥራ ሂደቶች ፣ከክልል መንግስታት ት/ቢሮዎችና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና
ኤጀንሲዎችና ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ ባለሙያዎችን ያሳተፈ ነበር፡፡
የዕቅድ ዝግጅቱ ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የተላከውን የመካከለኛ ዘመን ዕቅድ
ዝግጅት ጥቅል መመሪያ (Generic Guideline) እና የዕቅድ መነሻ ሐሳቦች መሰረት ያደረገ ነው፡፡
በውስጡም የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ (ቅድመ-መደበኛ ትምህርት፣ የመጀመሪያና የሁለተኛ
ደረጃ ትምህርት፣አማራጭ መሰረታዊ ትምህርትና የጎልማሶች መሰረተ-ትምህርት) ፣የቴክኒክና
ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍና የባለ ብዙ ጉዳዮች (Cross
Cutting Issues) ዘርፍ ተካተዋል፡፡
ዕቅዱ ያለፈውን የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም የአፈጻጸም ሁኔታ በመዳሰስ በልማት ዕቅዱ
የትግበራ ወቅት የተገኙ ውጤቶችንና ያጋጠሙ ችግሮችን፣ በ2ኛው ሃገር አቀፍ ዘላቂ የልማትና
ድህነት ቅነሣ ፕሮግራምና በአራተኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም የትግበራ ወቅት
መወሰድ የሚገባቸውን ርምጃዎችና የአተገባበር ስትራቴጅዎችን፡ዝርዝር አመልካቾችንና ግቦችን
፣የፋይናንስና የሰው ኃይል ፍላጎትን ፣ በልማት ዕቅዱ ዘመን ሊኖሩ የሚችሉ ዕድሎችና ሥጋቶችን
እንዲሁም ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችንና ማጠቃለያን አካቷል።
3
ክፍል አንድ
ሀ. ቅድመ-መደበኛ ትምህርት
የቅድመ-መደበኛ ትምህርት ጥቅል ተሣትፎ በ1997 ዓ.ም ከነበረበት 2.2% በ2001 ዓ.ም ወደ
4.2% አድጓል። የሴት ህጻናት ተሣትፎም ከ2.1% ወደ 4.2% ከፍ ብሏል። በ1997 ዓ.ም 32:1
የነበረው የተማሪ-መምህር ጥምርታ በ2001 ዓ.ም ወደ 21:1 ተሻሽሏል፡፡ እንደዚሁም በ1997 ዓ.ም
1,497 የነበረው የቅድመ-መደበኛ ት/ቤቶች ቁጥርም በ2001 ዓ.ም ወደ 2,904 አድጓል፡፡
የአንደኛደረጃ ትምህርት ተሣትፎ ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ ፈጣን ዕድገት አሣይቷል፡፡
በከተማውም የማስፋፋቱ ሥራ እንደተጠበቀ ሆኖ ገጠሩን ማዕከል ያደረገ የትምህርት ቤቶች
የማስፋፋት ሥራ በመሰራቱ በ1997 ዓ.ም 16,513 የነበረው የአንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች ቁጥር
በ2001 ዓ.ም ወደ 25,212 አድጓል፡፡ በትምህርት ቤቶች ግንባታ ላይ ከፍተኛ የሆነ
የማኅበረሰብ ተሣትፎ ታይቷል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘም የመማሪያ ክፍሎች ቁጥር ከ161,795 ወደ
247,698 ሲጨምር የትምህርት ቤቶች ቁጥር ዓመታዊ ዕድገት ምጣኔ በ2001 ዓ.ም 11.2%
ደርሷል፡፡
4
ህብረተሰቡ በተለይም የገጠሩና አርብቶ አደሩ ህብረተሰብ ለትምህርት ያለው አመለካከት
አዎንታዊ በሆነ መልክ እንዲቀየር በመንግስት በኩል በተደረጉ ጥረቶች ለትምህርት የሚሰጠው
ትኩረት ከፍ እያለ በመምጣቱ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት
እንዲገቡ ለማድረግ የራሱ ከፍተኛ ድርሻ ነበረው፡፡
በመሆኑም ከ1ኛ-8ኛ ክፍል በ1997 ዓ.ም የነበረው 79.8% ጥቅል ተሣትፎ በ2001 ዓ.ም 105.5%
ለማድረስ ታቅዶ 94.2% ውጤት ተገኝቷል። ዓመታዊ የዕድገት ምጣኔውም 8.0% እንደነበረ
ታውቋል። የንጥር ተሣትፎን በተመለከተም በ1997 ዓ.ም 68.5%( ወንድ 73.2 %፣ ሴት 63.6%)
የነበረው በ2001 ዓ.ም 87.8% ለማድረስ ታቅዶ 83.0% ( ወንድ 84.6%፣ሴት 81.3%) ሆኗል።
በሴቶችና በወንዶች መካከል የነበረው የጥቅል ተሣትፎ ልዩነትም እየጠበበ መጥቷል። በ1997
ዓ.ም የነበረው የወንዶች ጥቅል ተሣትፎ 88% ሲሆን የሴቶች ደግሞ 71.5% ሆኖ ልዩነቱ የ16.5%
ነበር። በ2001 ዓ.ም የወንዶች ወደ 91.2%፣ የሴቶች ወደ 87.5% አድጎ ልዩነቱ ወደ 3.7%
ተሻሽሏል። በንጥር ተሣትፎም በ1997 ዓ.ም የነበረው የ 9.6 % ልዩነት በ2001 ዓ.ም ወደ 3.3 %
ዝቅ ብሏል።
5
በክልሎች የሴትና ወንድ ተማሪዎች ተሣትፎ በተመለከተም ልዩነቱ በአብዛኞቹ ክልሎች እየጠበበ
የመጣ ሲሆን በ2001 ዓ.ም መረጃ መሠረት በተወሰኑ ክልሎች ልዩነቱን ለማጥበብ አሁንም ጥረት
መደረግ እንዳለበት ታውቋል።
ባለፈው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም ወቅት የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ትኩረት ተሰጥቶት
ሲሰራበት ቆይቷል።የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ተሣትፎን ለማሳደግ ግብዓት ከማሟላት አኳያ
በሦስተኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም ወቅት በገጠሩም በርካታ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች
ተከፍተዋል ፡፡
በመሆኑም በ1997 ዓ.ም 706 የነበሩት የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች (9-12) በ2001 ዓ.ም 1,197
ደርሰዋል፡፡ ስለሆነም ባለፉት አራት ዓመታት የ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች እድገት በመቶኛ ሲሰላ በ70%
አድጓል፡፡ በከተማና ገጠር መካከል የነበረው የተሣትፎ መጠን ልዩነት የከተማውን የተሣትፎ
ዕደገት ሣይገድብ ዝቅ ብሏል፡፡
የ2ኛ ደረጃ ትምህርትን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ የሚያግዝ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ስትራቴጂም
ተዘጋጅቷል። በስትራቴጂው መሠረት የአጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርትን (9-10) በ2012 ዓ.ም
ዕድሜያቸው ለደረጃው ለሚመጥኑ ዜጎች የማዳረስ ግብ ተቀምጧል። ይህ ግብ ተገቢ ግን ደግሞ
ፈታኝ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል። ተገቢ የሚሆንበት ምክንያት ኢትዮጵያን መካከለኛ ገቢ
ያላት አገር ከማድረግ ራዕይ እና ውጤት ጋር የተገናዘበ በመሆኑ ነው።
በዚህ መሠረት በ1997 ዓ.ም 27.3% የነበረው የአጠቃላይ 2ኛ ደረጃ (9-10) ትምህርት ጥቅል
ተሣትፎ በ2001 ዓ.ም ወደ 38.1% አድጓል። ይህ ውጤት በ2002 ዓ.ም. ሊደረስበት ከተጣለው
የ39.0 % ግብ አንጻር ሲታይ ጥሩ ነው። እንደዚሁም በ2ኛ ደረጃ የመሰናዶ ትምህርት (11-12)
በ1997 ዓ.ም 92,483 የነበረው የተማሪ ቁጥር በ2001 ዓ.ም 110,165 ለማድረስ ታቅዶ ወደ
205,260 አድጓል።
6
በሴቶችና ወንዶች መካከል የነበረውን ተሣትፎ በተመለከተም በ1997 ዓ.ም ከ9-10ኛ ክፍል
21.6% የነበረው የሴቶች ተሣትፎ በ2001 ዓ.ም ወደ 32.4% ከፍ ሲል 36.6% የነበረው የወንዶች
ተሣትፎ ደግሞ ወደ 43.7% አድጓል ፡፡ይህም በ2002 ሊደረስበት ከተቀመጠው 36.8% ግብ
አንጻር በ5.1% ብልጫ አሣይቷል። እንደዚሁም ከ11-12ኛ ክፍል በ1997 ዓ.ም 25,070 የነበረው
የሴት ተማሪዎች ቁጥር በ2001 ዓ.ም ሊደረስበት ከተጣለው 89,299 ግብ አንጻር ወደ 35,032
ሲያድግ 67,413 የነበረው የወንድ ተማሪዎች ቁጥር ደግሞ ወደ 83,257 ከፍ ብሏል።
የአጠቃላይ 2ኛ ደረጃ (9-10) ትምህርት ንጥር ተሣትፎን በተመለከተም በ1997 ዓ.ም ከነበረው
11.8% በ2001 ዓ.ም ወደ 12.6% ከፍ ብሏል። በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት የሚታየው የሥርዓተ-
ፆታ ፍትሐዊነት ጉድለት በአንደኛ ደረጃ የትምህርት ዕርከን ባለው ፍትሐዊነት መሰረት መሻሻሉ
የሚቀጥል ይሆናል።
በገጠርና በከተማ እንዲሁም በክልሎች መካከል ያለው የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ተሣትፎ ልዩነቱ
መጠነኛ መሻሻል አሣይቷል።ሆኖም ግን የአጠቃላይ የ2ኛ ደረጃ ትምህርትን (9-10) በ2012 ዓ.ም
ዕድሜያቸው ለደረሱ ሁሉ ለማዳረስ ከተጣለው ግብ አኳያ ያለው ክፍተት ከፍተኛ ሥራ
መሥራት እንደሚጠይቅ ያመላክታል።
መ. የጎልማሶች ትምህርት
በ3ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም ወቅት የጎልማሶች ትምህርት ስትራቴጂ፣ የጎልማሶች
መሠረተ ትምህርት ሥርዓተ ትምህርት ማዕቀፍና የትግበራ መመሪያ፣ የአመቻቾች መጽሐፈ-ዕድ
ተዘጋጅተዋል። በተጨማሪም በትምህርት ሚኒስቴርና ሌሎች የዘርፍ መስሪያ ቤቶች (ግብርና፣
ጤና፣ ወጣቶችና ስፖርት፣ ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ፣ ሴቶች ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች)
መካከል በጎልማሶች ትምህርት ፕሮግራም አተገባበር ላይ የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈርሟል።
የጎልማሶች ተግባር ተኮር ትምህርት የአተገባበር መመሪያ ተዘጋጅቶ ወደ ትግበራ ለመግባት
በየክልሎቹ አውደ ጥናት ተካሂዷል፡፡ክልሎቹም መመሪያውን ወደየራሳቸው ተጨባጭ ሁኔታ
እንዲተረጉሙትና ተግባራዊ እንዲያደርጉት ተደርጓል፡፡ ስትራቴጂውን ለመተግበርም ብሔራዊ
7
ግብረ-ኃይል ተቋቁሟል። በዚህ መሰረት የጎልማሶች ትምህርት በተግባር ከሚገኝ ልምድና
በመንግስትና በህዝብ ትብብር እንዲሁም በልማት አጋሮች ተሣትፎ ይበልጥ የተቀናጀና የጎለበተ
እንዲሆን በስትራቴጅው መሰረት ያላሰለሰ ጥረት ይጠይቃል።
8
2.2.2.የትምህርት ጥራትና ብቃትን በተመለከተ
በመሆኑም በ2001 ዓ.ም መረጃ መሰረት በ1997 ዓ.ም 188,720 የነበረው የ1ኛና 2ኛ ደረጃ
ትምህርት መምህራን ቁጥር በ2001ዓ.ም ወደ 307,927 አድጓል፡፡ለደረጃው የሰለጠኑ መምህራንን
በተመለከተም በአንደኛ ደረጃ ትምህርት የመጀመሪያ ዕርከን በ2001 ዓ.ም ሊደረስበት ከታቀደው
99.8% አንጻር በመማር ላይ ያሉትን ጨምሮ 90.0%፣ በ2ኛው ዕርከን ለ2001 ዓ.ም ከታቀደው
87% አኳያ ደግሞ 71.6% ደርሷል፡፡ እንደዚሁም በ1997 ዓ.ም 41% የነበረው የ2ኛ ደረጃ
ትምህርት የሰለጠኑ መምህራን ለ2001 ዓ.ም ከታቀደው 71% ወደ 75.2% አድጓል፡፡ በ1997
ዓ.ም 66 የነበረው የአንደኛ ደረጃ ትምህርት (1-8) የተማሪ-መምህር ጥምርታ በ2001 ዓ.ም
ሊደረስበት ከታቀደው 1:53 ግብ አንጻር 1:54 ሲሆን በ2ኛ ደረጃ (9-12) ደግሞ በ1997 51
የነበረው ለ2001 ዓ.ም ከተቀመጠው ግብ አንጻር 41 መድረሱ ታውቋል፡፡
9
ጥምርታው በየክልሎች የተለያየ ገጽታ እንዳለው መረጃዎች ያመላከቱ ሲሆን በሁሉም ደረጃ
ጥምርታውን አንድ አንድ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ ነው፡፡
በሌላ በኩል በአንደኛ ደረጃ ትምህርት የማቋረጥና መድገም ሁኔታዎች ገና ተገቢውን መሻሻል
አላሳዩም። በ1997 ዓ.ም የ1ኛ ክፍል የማቋረጥ መጠን 22.4% የነበረ ሲሆን ይህን መጠን በ2001
ዓ.ም ወደ 9.5% ለማውረድ ታቅዶ በተገኘው መረጃ መሰረት ግን 22.9% ሆኖ በመገኘቱ መጠኑ
አልቀነሰም። በተመሣሣይ መልኩ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት(4-8) የተማሪ የመድገም መጠን
በ1997 ዓ.ም 5.30% ከነበረበት በ2001ዓ.ም ወደ 2.93% ለማውረድ ታቅዶ የነበረ ሲሆን መጠኑ
ወደ 7.3% ከፍ ያለበት ሁኔታ ታይቷል። የትምህርት ማቋረጥና መድገም ምክንያቶች አያሌ
ናቸው። የእስካሁኑ ተሞክሮን መነሻ በማድረግ በትምህርት ቤት ደረጃና ከባቢው ምክንያቶቹን
በተጨባጭ መለየት እንደሚያስፈልግ ታምኖበታል።
ሥርዓተ ትምህርቱን መሰረት አድርገው ከሚሰሩ መደበኛ የትምህርት ተግባራት አንዱ ምዘናና
ፈተና ነው፡፡ ከዚህ አንጻር በቂ የማቴሪያል፣ የገንዘብና የሰው ኃይል በመመደብ በ12ኛ ና
10ኛ ክፍል ደረጃ የሚሰጡ ብሔራዊ ፈተናዎችን በጊዜው በመስጠት፣ በማረምና የተማሪ
ውጤትን በወቅቱ በማሳወቅ፣ ፍትሐዊ የሆነ የተማሪዎች የምደባ ሥርዓትን በመከተልና የከፍተኛ
10
ትምህርት ተቋማት መምረጫ መረጃን በመጠቀም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን በከፍተኛ ትምህርት
ተቋማት ፣ የ10ኛ ክፍል ተማሪዎችን ደግሞ ወደ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና እንዲሁም
ወደ 11ኛ (2ኛ ደረጃ መሰናዶ ትምህርት) በመመደብ ተማሪዎች ትምህርታቸውን በጊዜ
እንዲጀምሩ ተደርጓል፡፡
በተጨማሪም በሦስተኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም ትግበራ ወቅት በ4ኛና 8ኛ ክፍል
ደረጃ ሃገር አቀፍ የትምህርት ቅበላ ጥናት ሁለት ጊዜ በማካሄድ የተገኘውን ውጤት ለባለ
ድርሻ አካላት እንዲደርስ የተደረገ ሲሆን በ10ኛና 12ኛ ክፍልም ለመጀመሪያ ጊዜ ሃገር አቀፍ
የትምህርት ቅበላ ጥናት ተካሂዷል፡፡ ይህን ጥናት ክልሎች በራሳቸው አቅም እንዲያካሂዱ
ከማስቻል አኳያም ለሁለት ክልሎች ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ እንደዚሁም ልዩ ድጋፍ ለሚሹ ክልሎች
የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ፈተናዎች ምዝገባና የግል ተመዝጋቢዎችን ዶክመንት የማጣራት ሥራ
ላይ እገዛ ተደርጓል፡፡ፈተና በማዘጋጀትና በማሳተም እራሳቸውን እንዲችሉ ለክልሎች የአቅም
ግንባታ ስልጠናም ተሰጥቷል፡፡ የፈተና ውጤት መግለጫ መረጃ ለጠፋባቸው ተገልጋዮች የ12ኛ፣
የ10ኛ፣8ኛና 6ኛ ክፍል ድጋሚ የምስክር ወረቀት ተዘጋጅቶ ተሰጥቷል፡፡ የትምህርት መረጃ
ትክክለኛነት እንዲረጋገጥላቸው ለሚጠይቁ የግል አመልካቾች፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ
የመምህራን ልማትን በተመለከተ በ3ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት መርሓ ግብር ወቅት በርካታ
አበረታች ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ በመሆኑም የመምህራንን ሙያዊና አካዳሚያዊ ብቃት
ለማሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽፆ ያለው የመምህራን ልማት መርሓ ግብር ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ
በመካሄድ ላይ ሲሆን መርሓ ግብሩን ለመተግበርም የመምህራን ልማት ገዥ መመሪያ ተዘጋጅቶ
እየተሰራበት ይገኛል፡፡ ከላይ እንደተገለጸው የአጠቃላይ ትምህርት መምህራን ብዛትም በ1997
ዓ.ም
ከነበረው 188,720 በ2001 ዓ.ም 307,050 ደርሷል፡፡ ይህም በ1ኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርት የተማሪ-
መምህር ጥምርታውን እንዲሻሻል አድርጎታል፡፡ ከዚህ አንጻር በ1997 ዓ.ም 66 የነበረው የአንደኛ
11
ደረጃ ትምህርት የተማሪ-መምህር ጥምርታ በ2001 ዓ.ም ወደ 57 እንዲሁም በ2ኛ ደረጃ ትምህርት
ደግሞ 51 የነበረው ወደ 43 ተሻሽሏል። የመምህራንና የትምህርት አመራሮች የትምህርትና
ሥልጠና መመሪያም ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እየተደረገ ነው፡፡ በመሆኑም ሁሉም የቅድመ-መደበኛ
ትምህርት መምህራን በሰርቲፊኬት፣ የአንደኛ ደረጃ የመጀመሪያ ዕርከን መምህራን በጥምር
የትምህርት መስክ ሥልጠና ዲፕሎማ፣ የአንደኛ ደረጃ 2ኛ ዕርከን መምህራን በአብይ እና ንዑስ
ትምህርት መስክ ሥልጠና ዲፕሎማ፣ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት መምህራን በሙሉ ደግሞ
የመጀመሪያ ዲግሪ እንዲኖራቸው እየተደረገ ሲሆን የትምህርት አመራሮችን ልማት በተመለከተም
የአንደኛ ደረጃ የመጀመሪያ ዕርከን ትምህርት ርዕሣነ መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች በዲፕሎማ፣
የአንደኛ ደረጃ 2ኛ ዕርከን ትምህርት ርዕሣነ መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች በመጀመሪያ ዲግሪ፣
የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ርዕሣነ መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች ደግሞ በማስሬት ዲግሪ የትምህርት
ደረጃቸው እንዲያድግ እየተደረገ ይገኛል።
በአገር አቀፍ ደረጃ ከ150,000 በላይ የአንደኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርት መምህራንን ተጠቃሚ
ያደረገ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ማሻሻያ ፕሮግራም ተግባራዊ የተደረገ ሲሆን በመምራን ማሰልጠኛ
ተቋማትም የእንግሊዝኛ ቋንቋ ማሻሻያ ማዕከላት ተቋቁመዋል፡፡ የመምህራን አሰልጣኞችን ብቃት
ለማሳደግም የከፍተኛ ዲፕሎማ መርሓ ግብር ተግባራዊ እየተደረገ ሲሆን የመምህራንን
አካዳሚያዊና ሙያዊ ብቃት እንዲሁም ሙያዊ ሥነ-ምግባር ለማሻሻል የሚረዳ የመምህራን
የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ የሥራ ላይ ስልጠና በገዢ መመሪያውና በተዘጋጀው የስልጠና
ስትራቴጂ መሰረት በትምህርት ቤትና በጉድኝት ማዕከላት ደረጃ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ
12
እየተደረገ ይገኛል፡፡ የመምህራንን የሙያ ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳት አሰራርን ተግባራዊ ለማድረግ
የሚያስችል ሥርዓት ለመዘርጋትም ቅድመ-ሁኔታዎች እየተመቻቹ ነው፡፡
በመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማት ፕሮግራም ዙሪያ ከታዩ ተግዳሮቶች መካከል ቀጥሎ
የተመለከቱት በዋነኝነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ የት/ቤት አመራሮችና ተቋማት አሁንም ቢሆን
የማስፈጸም አቅም ክፍተት ይታይባቸዋል፡፡ የመምህርነት ሙያ ተወዳጅነቱ እያደገ መምጣቱን
ብንገነዘብም አሁንም ገና ከፍ ያለ አቅም ያላቸውን ዕጩዎች መሳብ ላይ ገና አልደረሰም።የሴቶች
ተሣትፎም ገና ማደግ አለበት። የታዳጊ ክልሎች ብሔረሰቦች በመምህርነት ያለው ተሳትፎም ገና
ማደግ አለበት። የዕጩ መምህራን ሥልጠና ጥራትና ለሥልጠናው የሚያስፈልግ ግብዓት
በማሟላትና የተከታታይ ሙያዊ ስልጠናዎች አፈጻጸም ማጠናከርን ይጠይቃሉ።
13
ሥልጠና ተሰጥቶ ወደ ትግበራ ተገብቷል፡፡ ት/ቤቶች ችግሮቻቸውን ለመለየትና የትምህርት
ቤቶቻቸውን የማሻሻያ ፕሮግራም ለመንደፍ የሚያግዛቸው የትምህርት ቤቶች የግምገማ ቅፅ
ተዘጋጅቶ ተግባራዊ ሆኗል፡፡ በመሆኑም በአብዛኞቹ ክልሎች ያሉ 80% ያህል የአንደኛ ደረጃና
60% ያህል 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የሦስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድና ዝርዝር ዓመታዊ ዕቅድ
አዘጋጅተዋል፡፡የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፓኬጁን በብቃት ለመፈፀም እንዲቻል
አንዱ ስልት በፓኬጁ አተገባበር ሂደት የተሻሉ አፈጻጸሞችና የተገኙ ውጤቶችን በመቀመር
ለሌሎች ተቋማት በማስፋፋት መተግበር ነው፡፡ በዚህም መሠረት በትምህርት ሚኒስቴር ደረጃ
ምርጥ ተሞክሮዎች ተቀምረው ለሁሉም ክልሎች ተሠራጭተዋል፡፡ ተጨማሪ ተሞክሮዎችን
ከተመረጡ ትምህርት ቤቶች አሰባስቦ የመቀመርና የማሰራጨት ተግባር እየተከናወነ ሲሆን
ቀሪው ጉዳይ እነዚህን የተቀመሩ ተሞክሮዎች ለሁሉም ክልሎች የማሠራጨት ሥራ ይሆናል፡፡
ከትምህርት ቤቶች ማሻሻያ ርዕሰ ጉዳዮች አንዱ የሆነው ከወላጆች ጋር አብሮ መሥራት ሲሆን
ለተማሪዎች ውጤት የራሱ ድርሻ ስላለው በዚሁ መሰረት ወላጆች በልጆቻቸው ትምህርት ተገቢውን
ተሣትፎ እንዲያደርጉ፣ ልጆቻቸውን እንዲያበረታቱና በትምህርት ቤቶች ላይ የባለቤትነት ስሜት
ኖሯቸው እንዲሳተፉ የሚያስችል ሰነድ ተዘጋጅቷል፡፡ በሁሉም ክልሎች በመገኘት ድጋፍና
ክትትል ተደርጓል፡፡ ይህን መነሻ በማድረግም ለሞዴል የትምህርት ተቋማት፣ የርዕሳነ መምህራን፣
መምህራን፣ ሱፐርቫይዘሮች፣ የተማሪዎች፣ ወላጆችና ማህበረሰብ መለያ ተግባራት ባለድርሻ
አካላትን ባካተተ መልክ ሰነድ ተዘጋጅቶ ለሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ተሰራጭቶ
የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፓኬጅ የህዝብ ንቅናቄ መፍጠሪያ አካል ሆኗል፡፡
በተጨማሪም የትምህርት ቤት ማሻሻያ ፕሮግራሙን በተጨባጭ ለመተግበር የሚረዳ የቅድመ
መደበኛ፣ የአንደኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ስታንደርድ ተዘጋጅቶ ከየክልሎች በተውጣጡ
ባለሙያዎች ዳብሮ ክልሎች ተግባራዊ እንዲያደርጉት ተሰራጭቷል፡፡
14
ሥነ- ዜጋና ሥነ- ምግባርን በተመለከተ የየክፍል ደረጃው አጥጋቢ የችሎታ መለኪያ ተዘጋጅቶ
በዚሁ መሠረት መርሀ ትምህርቶችን በማሻሻል፣ በተዘጋጁት አጥጋቢ የችሎታ መለኪያዎችና
በተሻሻሉት መርሀ ትምህርቶች ላይ በመመሥረት ከ5ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ እያገለገሉ
የሚገኙት የመማሪያ ማስተማሪያ መጽሐፍት ጥራታቸውን ጠብቀው እንዲዘጋጁ ተደርገዋል፡፡
የሥነዜጋና ሥነምግባር ትምህርት በሥርዓተ ትምህርቱ ተካቶ መሠጠት ከተጀመረበት ጊዜ
ጀምሮ በትምህርቱ መማር ማስተማር ዙሪያ ያጋጠሙ ችግሮችን በተመለከተ ሁሉንም ክልሎች
የዳሰሰ ጥናት ተደርጎ የጥናቱን ውጤት መሠረት በማድረግ ችግሩን ለማስወገድ ሥልጠና
መስጠት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ለርእሳነ መምህራን፣ ለመምህራን፣ ለወላጅ መምህራን ህብረት፣
ለወረዳ ትምህርትና
15
በኢትዮጵያ በተለያዩ ወቅቶች የወጡ ሕገመንግሥቶችን አንድ ላይ በማስባሰብና በአንድ ጥራዝ
አዘጋጅቶ በማሳተም በሁሉም ክልሎች እና ለሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች በሚገኙ ትምህርት
ቤቶች እንዲሰራጭ ተደርጓል፡፡ እንደዚሁም በኢትዩጵያ በተለያዩ ወቅቶች የተዘጋጁትን ህገ
መንግሥቶች ዋና ዋና የሆኑ አንቀጾችን የሚያነፃፅር የማብራሪያ ጽሁፍ ተዘጋጅቶ ለፌዴሬሽን
ምክር ቤት ለአስተያየት እንዲቀርብ ተደርጓል፡፡
16
የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ በመካከለኛ ደረጃ የሚፈልገውን
የሰለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራት ቁልፍ ሚና የሚጫወት ዘርፍ ነው። ከዚህ አንጻር በ3ኛው
የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም ትግበራ ወቅት በዚህ ዘርፍ በተሣትፎና በማስፋፋት ዙሪያ
በርካታ ተግባራት ተከናወነዋል።በመሆኑም በ1997 ዓ.ም 106,336 የነበረው የቴ/ሙ/ትምህርትና
ሥልጠና ተሣትፎ በ2002 ዓ.ም ወደ 312,826 ለማድረስ ታቅዶ 615,913 ያደገ ሲሆን ከዚህ
ውስጥ
17
የቴክኖሎጂ ክምችትና ሽግግር የሥራ ሂደት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ጋር በተደረሰ ስምምነት
መሰረት ማንዋሉ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡
መምህራን ሥርዓተ ትምህርት ዝግጅት የሚረዳ የሞጅዩል ዝርዝር የተዘጋጀ ሲሆን ነባር የ B
ደረጃ መምህራንን ከማብቃት አንጻርም በአገሪቱ ውስጥ በመንግስት ተቋማት ውስጥ በ B እና C
ደረጃ ካሉ ነባር መምህራን ውስጥ ምዘናውን ወስደው ላለፉ መምህራን ተግባር ተኮር የማስተማር
ሥነ ዘዴ ሥለጠና ተሰጥቷል፡፡
በየጊዜው የሚኖረውን የሥራ ገበያ ፍላጎት መረጃ ለመለየትና ለማወቅ የሚያስችል መነሻ ሰነድ
እና የሰልጣኞች የሙያ ምክርና ድጋፍ እንዲሁም ተቋምን ከኢንዱስትሪው ጋር ለማስተሳሰር
የሚረዳ የሙያ ምክር ድጋፍ አገልግሎት መመሪያ ተዘጋጅተው ለተጠቃሚዎች ተሰራጭተዋል፡፡
በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት የሚሰጠው ስልጠናም የሙያ ደረጃንና የገበያ
ፍላጎትን መሰረት ያደረገ በመሆኑ ሠልጣኞች በሥራው ዓለም ውስጥ ያላቸው ተፈላጊነት
በከፍተኛ ሁኔታ ተሻሽሏል፡፡ በአዲሱ የመካከለኛ ደረጃ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና
ፕሮግራም ሰልጣኞች ከኢንዱስትሪ ጋር የሚተዋወቁበት ስልት በተለይ በመደበኛው ፕሮግራም
ውስጥ ተካቷል፡፡ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ጥራትን ለማሳደግና ምሩቃኑም የሥራ
18
ዕድል እንዲያገኙ ለማድረግ በተቋማቱና በአሰሪ ድርጅቶች ጠንካራና በመተጋገዝ ላይ የተመሰረተ
የትብብር ሥልጠና እና የሥራ ላይ ልምምድ አሰጣጥ ሥርዓት ተዘርግቷል፡፡
የተቋማትን አሰራር ለማሻሻልና ለጥራት ማረጋገጫ የዓለም አቀፍ ደረጃች ድርጅት/ISO 9001
ሥርዓት ብቁ ለማድረግ 10 የሙከራ ተቋማት ተመርጠዋል፡፡ በዚህ መሰረት ከአዲስ አበባ 5 እና
ከክልሎች 5 ተቋማት የተመረጡ ሲሆን የመጀመሪያ ዙር ከአዲስ አበባ የእንጦጦ፣ ተግባረ ዕድ ፣
ዊንጌት፣ ሠላምና ኤስ ኦ ኤስ (SOS) ኮሌጆች የሦስተኛ አካል የዶክዩመንቴሽንና አደረጃጀት
ኦዲት አልፈው ለመጨረሻ ኦዲት ዝግጁ ሆነዋል፡፡ እስካሁን በተከናወነው ሥራ በተለይ የወርክ
ሾፕ አደረጃጀትና አሰራርን ቀልጣፋ በማድረግ ጥሩ ውጤት የታየ ሲሆን በቀጣይነት በጉድኝት
ደረጃ ወደ ተደራጁ ተቋማት የማስፋት ሥራ ይከናወናል፡፡
19
ማድረግ ተችሏል፡፡ የኩባንያ ውስጥ ሥልጠና በተጀመረባቸው ኩባንያዎችም አመርቂ ውጤቶች
እየተመዘገቡ መሆኑም ታውቋል፡፡
20
በሕብረተሰቡ፣ በባለድርሻ አካላት፣ ባስፈፃሚና በፈፃሚ አካላት እና በሰልጣኞች ዘንድ
ስለውጤት ተኮር ቴ/ሙ/ት/ስ/ ስርዓት ያለው ግንዛቤ አናሳ መሆንና ሰልጣኞች የቴ/ሙ/ት/ስ
ፕሮግራምን ወደ ከፍተኛ ትምህርት መሸጋገሪያ አድርገው ማሰባቸው፡፡
የቴ/ሙ/ት/ሥ/ ተቋማት ቴክኖሎጂን ለማሸጋገርና ለማስረጽ ብቁ ሆነው አለመገኘት፣
ህጋዊ መሠረት ያለውና ባለድርሻ አካላትን ያሣተፈ አደረጃጀት አለመኖር፣
የሥራ ፍላጎት ጥናት ሥርዓት አለመኖር፣
በየደረጃው ያሉ ባለሙያዎች ብቃት ስርዓቱን በአግባቡ ለመተግበር ያለማስቻሉ፣
ተከታታይ የሆነ ክትትልና ግምገማ የማካሄድ ብቃት አለመኖር፣
የተሟሉ የቴ/ሙ/ት/ስ/ስትራቴጂ ማስፈፀሚያ ሰነዶች አለመኖር፣
የተሟላ የመረጃ አያያዝ፣ አደረጃጀትና ልውውጥ ስርዓት አለመኖር፣
ከፍተኛ ትምህርት በ1997 ዓ.ም ከነበረበት ሁኔታ አበረታች ዕድገት አሳይቷል፡፡ በመንግስት
ተቋማት ብቻ በ1997 ዓ.ም ከነበረው 78,232 ጠቅላላ የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ተማሪ ብዛት
በ2002 ወደ 185,788 (በ137.5 መቶኛ) አድጓል፡፡ በ1997 ዓ.ም 24% የነበረው የሴት ተማሪዎች
ድርሻ በ2002 ዓ.ም 29% ሆኗል፡፡ የድሕረ ምረቃ ትምህርት ተሳትፎም በ1997 ከነበረው 3,604
ተማሪዎች በ2001 ወደ 9,761 አድጓል፡፡ የሴት ተማሪዎች ድርሻ ከ9% ወደ 11.3% አድጓል፡፡
በዚያው ዘመን የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ብዛት በ13 ጨምሮ 22 ደርሷል፡፡
የዓመታዊ ቅበላን ዕድገት በሚመለከት በመርሃ ግብሩ ሰነድ ሰፍሮ የነበረው ዕቅድ 150,000
ተማሪዎች አካባቢ ነበር፡፡ ይህ መጠን ከመጀመሪያው ስህተት እንደነበረበት በመታወቁ 110,000
እንዲሆን ተስተካክሏል፡፡ ይህም ቢሆን ግን ሊደረስበት አልተቻለም፡፡ በዕቅዱ ዘመን የተደረሰበት
ከፍተኛው ዓመታዊ የቅበላ መጠን 79,500 ተማሪዎች ብቻ ነበር፡፡ ይህ መጠን የ2001 ዓመታዊ
ቅበላ ሲሆን በ2002 ወደ 77,182 ዝቅ ብሏል፡፡ ለተስተካከለው ዕቅድ አለመሳካት ዋነኛው
ምክንያት የህንጻ ግንባታዎች በታሰበው አለመፋጠን ነበር፡፡
21
በመርሃ ግብሩ ዘመን የከፍተኛ ትምህርት ስርዓቱን ወደ ዓይነታዊ ለውጥ ሊያደርሱ የሚችሉ
በርካታ መሰረታዊ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ተልዕኮአቸውን ለማሳካት
የሚያስችላቸውን የማስፈጸም ዓቅም ለመገንባት በተቋማዊ ለውጥ ሂደት ውስጥ ገብተዋል፡፡ ይህን
ሂደት የሚያጠናክርና የውጤቱን ዘላቂነት የሚያስጠብቅ ሕጋዊ ማዕቀፍም ተዘርግቷል፡፡
በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የቅድመ ምረቃ ትምህርት ተሳትፎ ዕድገት በሳይንስና ቴክኖሎጂ
መሪነት (በ70:30) እንዲቃኝ አቅጣጫ ተቀምጦ በ2002 ዓ.ም የሳይንስና ቴክኖሎጂ ድርሻ
ከጠቅላላው 185,788 ተማሪዎች 55.7% ሲሆን ከዓመታዊ ቅበላው (77,182) ደግሞ 58% ላይ
ደርሷል፡፡ በ2002 በኤንጅኔሪንግና ኮምፕዩቲንግ በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በመማር ላይ ያሉ
ተማሪዎች 31,373 ነው።
የአገሪቱ ልማትና ዕድገት አስተማማኝ የፍትህ ስርዓትን መገንባት ስለሚጠይቅ የሕግ ስርዓተ
ትምህርቱ በዚሁ ቅኝት ተለውጦ መተግበር ተጀምሯል፡፡ የቢዝነስና ኤኮኖሚክስ፣ የህክምናና ጤና
ሳይንስ፣ የግብርናና የማሕበራዊ ሳይንስ ስርዓተ ትምህርቶችም ተለውጠው ወደ ትግበራ
ተሸጋግረዋል፡፡ የህክምና አዲስ ስርዓተ ትምህርት ቀረጻም የማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ ነው፡፡
22
የተለወጡት ስርዓተ ትምህርቶች ተግባሪ ብቁ መምህራንን ይጠይቃሉ፡፡ በዚህ ረገድም
የመምህራን ልማት ስትራቴጂን በመቅረጽ የተለያዩ ጥረቶች ተደርገዋል፡፡ በመሆኑም በ1997
ዓ.ም 4,847 የነበረው የዩኒቨርስቲ መምህራን ብዛት በ2002 ዓ.ም ወደ 11,238 አድጓል፡፡ ከነዚህ
መምህራን መካከል ገና የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው 5,706 (50.8%)፣ በሁለተኛ ዲግሪ ደረጃ
4,528 (40.3%) እና ፒኤች ዲና አቻ ዲግሪ ያላቸው 1,004 (8.9%) ናቸው፡፡ የድሕረ ምረቃ
ትምህርት በመከታተል ላይ የሚገኙት 5,826 (4,681 የ2ኛ ዲግሪ እና1,145 የፒ ኤች ዲ ዲግሪ)
ሲታከልበት የዩኒቨርሲቲ መምህራን ብዛት 17,064 ይሆናል፡፡ ይህ ገና በመጀመሪያ ዲግሪ ክልል
ያሉትን መምህራን ምጣኔን ወደ 33.4% ዝቅ ያደርገዋል፡፡ ይሁንና በማስተማር ስራ ላይ ያሉትን
ብቻ ግምት ውስጥ በማስገባት በ2002 ዓ.ም የተማሪ/መምህር ጥምርታ ባጠቃላይ 1፡16 ሲሆን
ሁለተኛ ዲግሪና ከዚያ በላይ ካላቸው መምህራን አንጻር ግን 1፡34 ነው፡፡
የትምህርት አግባብነትና ጥራትን ለማሳካት የተደራጀ ሙያዊ ሃገራዊ አመራርን ለማረጋገጥ ሲባል
የስትራቴጂ ማዕከልና የትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጄንሲ ተቋቁመዋል፡፡ እነዚህ አካላት
በዋናነት ኃላፊነታቸውን ለመወጣት የሚያስችላቸውን የማስፈጸም ዓቅም በመገንባት ሂደት ላይ
የሚገኙ ናቸው፡፡ ባጠቃላይ የመንግስቱ ዘርፍ የከፍተኛ ትምህርት የትምህርት አግባብነትና
ጥራትን ባማከለ የለውጥና ዕድገት አቅጣጫ ላይ ይገኛል፡፡ ይሁንና አሁንም ዓይነታዊ ለውጥን
ለማረጋገጥ በሚያስችለው የለውጥ ሂደት ውስጥ እንጂ ማረጋገጥ ካለበት ዓይነታዊ ለውጥ ላይ ገና
አልደረሰም፡፡ የግሉን ዘርፍ በተመሳሳይ አቅጣጫ እንዲመራ የማብቃቱ ተግባር ባጠቃላይ ገና
መሰራት ያለበት ትልቅ ጉዳይ ነው ለማለት ይቻላል፡፡
23
በአብዛኞቹ ዩኒቨርሲቲዎች የሥርዓተ ጾታ ጽ/ቤት ተቋቁሞ ለሴት ተማሪዎች የተለያዩ የድጋፍ
ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡ በተለይም ሴት ተማሪዎችን ውጤታማ ለማድረግና ትምህርታቸውን
አቋርጠው እንዳይወጡ በዩኒቨርሲቲዎች የተለያዩ የማብቃት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
በዩኒቨርሲቲዎች በመከናወን ላይ ከሚገኙ የማብቃት ሥራዎች መካከል ነባር ሴት ተማሪዎች
አዲስ ለሚገቡ ሴት ተማሪዎች ልምዳቸውን የሚያካፍሉበት ሥርዓት ተዘርግቷል፡፡ በአንዳንድ
ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሴት ተማሪዎች ማህበር ተቋቁመዋል፡፡ ከየክፍሉ የተመረጡ ምርጥ
አምስት ሴት ተማሪዎች ለክፍል ጓደኞቻቸው ደጋፊ ትምህርት መስጠት ጀምረዋል፣ ውጤታማ
ለሆኑ ሴት ተማሪዎች ሽልማት የመሰጠትና ማበረታታት ሥርዓት ተጀምሯል፡፡ ከፍተኛ ልምድ
ያላቸውን ሴት ምሁራንና ኃላፊዎች በመጋበዝ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሴትነታቸው
የሚያጋጥሟቸውን አሉታዊ ተፅእኖዎች ተቋቁመው ውጤታማ እንዲሆኑ በተከታታይ የኦረንቴሽን
ኘሮግራም ተካሂዷል፡፡ዩኒቨርሲቲዎች ሴት ተማሪዎችን በትምህርታቸው እኩል ተወዳዳሪ
ለማድረግ የጀመሩዋቸው መልካም ጅምሮችን አጠናክረው እንሚቀጥሉባቸው እናምናለን። በሴት
ተማሪዎች የሚደርሱ ማንኛውም ዓይነት ተፅዕኖ፣ ትንኮሳና ጥቃትን ለማስወገድ በመዘርጋት ላይ
ያሉትን ሥርዓትም አጠናከረው ይቀጥሉበታል።
24
የከፍተኛ ትምህርት አመራርና አስተዳደር ስርዓቱ በሚፈለገው የብቃት ደረጃ ላይ
አልደረሰም፡፡
የመምህራን ልማትን ሁሉም ገጽታዎች አስተሳስሮ መፈጸም ገና ስርዓት አልሆነም፡፡
ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት መምህራን የትምህርት ደረጃ ቢያንስ 2ኛ ዲግሪ የሆነበት ደረጃ
ገና አልደረሰም
የኢንዱስትሪውን ፍላጎት መሰረት ያደረገ የቴክኖሎጅ ሽግግር ሥርዓት አለመኖር፣ በተለይ
በሳይንስና ቴክኖሎጂ መስኮች የንዱስትሪ ልማት የሰው ኃይልና የቴክኖሎጂ ሽግግር ፍልጎትን
ለመመለስ የሚያስችል የማስፈጸም ዓቅም ግንባታው ገና ሂደት ላይ ያለ ነው፡፡ መረጋገጥ
የሚገባው የተሳትፎ ደረጃም ገና አልተደረሰበትም፡፡
በ70፡30 የመስኮች ምጣኔ ክልል የቴክኖሎጂ ድርሻ ከሆነው 40% ግብ ላይ ገና አልደረሰም።
የቅድመ ምረቃና ድሕረ ምረቃ የቅበላ ዓቅሞች ገና በግንባታ ሂደት ላይ ናቸው፡፡
የሴት ተማሪዎች ድርሻ በቅድመ ምረቃውና በድሕረ ምረቃው ፕሮግራም ገና አነስተኛ ነው።
የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ገቢን የማመንጨትና የማሳደግ ዓቅም ገና ውሱን ነው፡፡
የግሉ ዘርፍ የትምህርት አግባብነትና ጥራት ገና ፈር እንዲይዝ አልተደረገም፡፡
25
ድጋፍ በመሰጠቱ በከፍተኛ ተቋማት የሴቶች ተሣትፎ እያደገ መጥቷል፡፡ በመሆኑም በተለይ
በመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት በሴቶችና በወንዶች መካከል የነበረው የጥቅል ተሣትፎ ልዩነት
እየጠበበ መጥቷል። በመሆኑም በመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ተሣትፎ ዙሪያ የሥርዓተ- ፆታ
ልዩነት ምጣኔው በ1997 ከነበረበት የወንዶች 0.87 እና የሴቶች 0.69 በ2001 ዓ.ም ወደ 0.93
እና 0.92 መጥቷል፡፡
በሦስተኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም ትምህርትን ለሁሉም ማዳረስን ታሳቢ በማድረግ
ለልዩ ፍላጐትና አካቶ ትምህርት ትኩረት ተሰጥቶ ሲሰራ ቆይቷል፡፡ በመሆኑም የልዩ ፍላጎት
ትምህርት ስትራቴጅ ተዘጋጅቶ በመተግበር ላይ ነው፡፡ የልዩ ፍላጎት ትምህርት የመተዋወቂያ
ኮርስ በሁሉም የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡ በአራት
ዩኒቨርሲቲዎች
26
በመጀመሪያ ዲግሪ ደረጃ፣በአምስት የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች በዲፕሎማ እንዲሁም በአዲስ
አበባ ዩኒቨርሲቲ በማስትሬት ዲግሪ ደረጃ የልዩ ትምህርትና አካቶ ትምህርት ፕሮግራም
በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡ እንደዚሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሥነ ልሣን የትምህርት ክፍል
የምልክት ቋንቋ በመጀመሪያ ዲግሪ ደረጃ በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡ በዘጠኝ ክልሎችና ሁለቱ
የከተማ አስተዳደሮች ለትምህርት ቢሮ የትምህርት ባለሙያዎችና ለሁሉም የወረዳ ትምህርት
ጽ/ቤት ኃላፊዎች በልዩ ድጋፍና አካቶ ትምህርት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ አውደ ጥናት
ተካሂዷል፡፡
ልዩ ድጋፍ ለሚሹ ክልሎችም ተጨማሪ ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ በተፈጠረው ግንዛቤ የተነሣ ከ1999
በፊት ከ33,000 በታች የነበረው የአካል ጉዳተኛ ህጻናት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ተሣትፎ
በ2001 ዓ ም በተገኘው መረጃ መሰረት ወደ 41,300 ደርሷል፡፡ የልዩ ፍላጎትና አካቶ ትምህርት
በዋና ዋና የትምህርት ዓይነቶች ሥርዓተ ትምህርት የተካተተ ሲሆን ልዩ ፍላጎት ያላቸውን
ተማሪዎች እንደየፍላጎታቸው ለመርዳት የሚያስችሉ በሃገር አቀፍ ደረጃ የተመረጡ ሦስት ልዩና
ስድስት ክላስተር ትምህርት ቤቶች በድጋፍ መስጫ ማዕከልነት ተዋቅረዋል፡፡ ለልዩ ፍላጎትና
አካቶ ትምህርት ተንቀሳቃሽ መምህራን ተቀጥረው በመሥራት ላይ ናቸው፡፡ በተጨማሪም የዋና
ዋና ትምህርቶች ሥርዓተ ትምህርት የአካል ጉዳተኛ ሕጻናት ትምህርትን እንዲያካትት የተደረገ
ሲሆን
ለአካል ጉዳተኛ ህጻናት የተለየ ሥርዓተ ትምህርት ለማዘጋጀት የሚያስችል መመሪያም
እየተዘጋጀ ነው።
ከህብረተሰብ ተሳትፎ አኳያ ያለፈው የትምህርት ዘርፍ መርሐ ግብር ትግበራ ከፍተኛ
የማህበረሰብ ንቅናቄና ተሣትፎ የታየበት ነበር፡፡ በመሆኑም በርካታ የአንደኛና 2ኛ ደረጃ
ትምህርት ቤቶች በማህበረሰብ ተሣትፎ በመሰራታቸው የተማሪ ጥቅልና ንጥር ተሳትፎ
ጨምሯል፡፡ ይህንም ከላይ ከቀረበው ሪፖርት መመልከት ይቻላል፡፡ የማህበረሰቡ ተሣትፎ
ጉልበቱን፣ ገንዘቡን፣ ማቴሪያልና ዕውቀቱን በመለገስ ብቻ ሳይሆን ልጆቹን በእድሚያቸው ወደ
ት/ቤት በመላክና በመርዳት ጭምር የተንጸባረቀ እንደነበር የተለያዩ ዓመታዊ ሪፖርቶች
ያመለክታሉ፡፡ ለምሣሌ በኦሮሚያ ክልል ሁሉም የመጀመሪያ ደረጃና ሦስት- አራተኛ ያህሉ የ2ኛ
ደረጃ ት/ቤቶች የተገነቡት ፣የታደሱትና የተስፋፉት በማህበረሰብ ተሣትፎ እንደነበር ተውቋል፡፡
በአማራ ክልልም በማህበረሰቡና በክልሉ መንግስት መካካል የትምህርት ቤት ግንባታ ወጭ
27
መጋራት ሥርዓት ተዘርግቷል፡፡ በሌሎችም ክልሎች በተመሣሣይ ሁኔታ የማህበረሰብ ተሳትፎ
በከፍተኛ ደረጃ በመቀጠሉና ት/ቤቶች ወደ ሕጻናት መኖሪያ አካባቢዎች በመቅረባቸው ሕጻናት
ወደ ት/ቤት ለመሄድ የሚፈጅባቸው ጊዜና ድካም በተወሰነ ደረጃ ቀንሷል፡፡ ይህም በተለይ የሴት
ሕጻናትን የትምህርት ተሣትፎ አሳድጋል፡፡
በወረዳ ደረጃ ከፍተኛ የሆነ የአቅም ክፍተት በአንድ በኩል የሰለጠነ የሰው ኃይል መልቀቅና
እጥረት ደግሞ በሌላ በኩል የሚታዩ ትላልቅ ችግሮች እንደሚታዩ ለመረዳት ተችሏል።
ማጠቃለያ
28
በሦስተኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት መርሐ ግብር የትግበራ ወቅት በአጠቃላይ ውጤታማና
አበረታች ሥራዎች ቢከናወኑም አሁንም በቀጣይ መሰራት ያለባቸው ስራዎች አሉ። በመሆኑም
የአራተኛውን የትምህርት ዘርፍ ልማት መርሐ ግብር ቀልጣፋና ውጤታማ በሆነ መልኩ
ለመተግበር የትምህርት ጥራትና አግባብነት፣ የትምህርት ፍትሃዊነትና ተደራሽነት እንዲሁም
በትምህርት ዘርፉ በየደረጃው የመልካም አሰተዳደር ሙሉ በሙሉ ማስፈን ዋና ዋና የትኩረት
መስኮቻችን ይሆናሉ፡፡ ይሀንንም ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ለቀጣዩ አምስት ዓመት
ጠንክሮ መስራትን ይጠይቀናል።
ክፍል ሁለት
የትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ልማት ዕቅድ ዝግጅት መሰረት ያደረገው ሃገራችንን መካከለኛ ገቢ
ካላቸው ሀገሮች ተርታ ለማሰለፍ የተቀመጠውን ራዕይ ሲሆን ከዚሁ ጋር በተያያዘ ራዕዩን
ለማሳካት ኢንዱስትሪው (በተለይም በማደግ ላይ ያለው የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ) በየደረጃው
የሚፈልገውን የሰለጠነ የሰው ኃይል ማፍራት ነው። ዕቅዱ ያለፈውን የትምህርት ዘርፍ ልማት
ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መነሻ በማድረግ የአጠቃላይ ትምህርትን፣ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና
ስልጠናንና የከፍተኛ ትምህርትን በተመጋጋቢነት በማስፋፋት በሚቀጥሉት አምስት አመታት
ጥራቱንና ፍትሃዊነቱን የጠበቀ ትምህርትና ስልጠና ለማረጋገጥ የተዘጋጀ ነው። በዚህም መሰረት
የልማት ዕቅዱ የትኩረት አቅጣጫዎች፣ ዓላማዎች፣ ዋናዋና ግቦችና የማስፈጸሚያ ስልቶች
ፖሊሲውን መሰረት በማድረግ እንደሚከተለው በየዘርፉ ቀርበዋል፡፡
1. የትኩረት አቅጣጫዎች
29
1.1. አጠቃላይ ትምህርት
በሌላም በኩል ተግባር ተኮር የሆነ የጎልማሶች ትምህርት በሁሉም አካባቢዎች ሊሳተፉ ለሚችሉ
ሁሉ እንዲዳረስ ይደረጋል። ከዚህ አንጻር ተግባር ተኮር የጎልማሶች ትምህርት ስትራቴጂን
በመተግበር ሁሉም ዕድሜያቸው ከ15-60 የሆኑ ሁሉ በዚህ ፕሮግራም ይታቀፋሉ።
30
የተቀየሰውን የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ስትራቴጂ በተሟላ አኳኋን ተግባራዊ በማድረግ
ጥራቱን የጠበቀና ውጤታማ ስርዓት ይረጋገጣል። በዚህ መሰረት የመንግሥት ኢንቨስትመንትን
በማጠናከርና የትብብር ስልጠናን በተሟላ መልኩ ተግባራዊ በማድረግ የሀገራችን የሰለጠነ የሰው
ሀይል ፍላጎት በአጥጋቢ ሁኔታ እንዲሟላ ይደረጋል። የሙያ ምደባ፣ የሙያ ደረጃ ዝግጅት፣
የብቃት ማረጋገጫ፣ የሙያ ምዘና የምስክር ወረቀት አሰጣጥና የስርዓተ ትምህርት ቀረጻ ስርዓትን
በመፍጠርና በማጠናከር ስርዓቱ ቀጣይ የቴክኖሎጂ ሽግግር መሣሪያ ሆኖ ያገለግላል። የቴክኒክና
ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማቱም ለአነስተኛና ጥቃቅን ተቋሞች የቴክኖሎጂ ማዕከላት ሆነው
እንዲያገለግሉ ይደረጋል።
በቀጣዩ አምስት አመታት የከፍተኛ ትምህርት ዋነኛ ትኩረት የትምህርት ጥራትና አግባብነትን
ማረጋገጥ ነው፡፡ በዚሀም መሰረት የዩኒቨርሲቲ የአመራርና የአስተዳደር ስርዓት ይደረጋል፣
የስትራቴጂ ማዕከልና የትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጄንሲ ሚናቸውን እንዲወጡ
ይጠናከራል፡፡ የቴክኖሎጂ ኢንስቲቱዩቶችም የማስፈጸም ዓቅም ይገነባል። በሌላ በኩል
ሁለንተናዊ የዩኒቨርሲቲ መምህራን ልማትን በመተግበር ብቁ የመምህራን አቅርቦት
ይረጋገጣል።የተለወጡ ስርዓተ ትምህርቶች ትግበራን በትምህርቱ አሰጣጥ፣ በተማሪዎች ምዘናና
ፈተና እና በውጤት አሰጣጥ ገጽታዎቹ ተጠናክሮ ይፈጸማል፡፡
በከፍተኛ ትምህርት ደረጃ የሚሰጠው ትምህርት ኢኮኖሚው በሚፈልገው የሰው ሃይል ብዛት፣
ዓይነትና ጥራት ይቃኛል፡፡ በዚህ መሰረት በቅድመ ምረቃና ድሕረ ምረቃ የሚሰጠው ትምህርት
የተሳትፎ ዕድገቱ በመስኮች ምጣኔ መሠረትና ፍትሃዊነትን በጠበቀ ሁኔታ እንዲሳካ ይደረጋል።
ዩኒቨርስቲዎች ገቢን የማመንጨትና የማሳደግ ዓቅማቸውን እንዲገነቡና ለትምህርቱ አግባብነትና
31
ጥራት ማጠናከሪያ እንዲያውሉት የሚያስችል ስራ ይሰራል፡፡ (ጥራትና አግባብነትበሚል
ቢስተካከለ)
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የጥናትና ምርምር ስርዓት የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማዕከል ያደረገ
እንዲሆንና በተለይ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ተቋማትና የትምህርት ክፍሎች ተቋማዊ የማስፈጸም
አቅማቸውን በመገንባት በቴክኖሎጂ ሽግግር የኢኮኖሚ ልማቱን እንዲደግፉ ይደረጋል። ባጠቃላይ
የከፍተኛ ትምህርት የጥናትና ምርምር ስርዓት ለአገሪቱ ልማትና ዕድገት ባላቸው ፋይዳ
ይመራሉ።
የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የትምህርት ጥራትና አግባብነትን ማረጋግጥ ዋነኛ የትኩረት
አቅጣጫ ይሆናል፡፡ተቋማቱም የከፍተኛ ትምህርት አዋጁንና ስትራቴጂውን መሰረት አድርገው
መደራጀታቸው ይረጋገጣል፡፡ ይህም ተገቢው ክትትል እየተደረገበትና የድጋፍና የማስተካከያ
እርምጃዎች በመውሰድ እድገቱ በትምህርት አግባብነትና ጥራት መረጋገጥ ላይ እንዲመሰረት
ይደረጋል።
32
ጥራቱን የጠበቀ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ዕድሜያቸው ለደረሰ ሁሉ ማዳረስ፤
ገበያው የሚፈልገውን በመካከለኛና ከፍተኛ ደረጃ የሰለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራት ጥራት
ያለው የ2ኛ ደረጃ ትምህርትን ተሳትፎ ማሳደግ፤
33
ከኢኮኖሚው ፍላጎት አኳያ የከፍተኛ ትምህርትን ጥራትና አግባብነትን ያማከሉ ተቋማትን
ማረጋገጥ፤
3. ግቦች
34
የአንደኛ ደረጃ (ከ1ኛ-8ኛ ክፍሎች) ንጥር ተሳትፎን አሁን ካለበት 87.9% ወደ 97% ማድረስ፤
የሴቶችንና የወንዶችን የትምህርት ተሳትፎ ምጣኔ ልዩነትን ለማጥፋት የአንደኛ ደረጃ
ትምህርት አሁን ካለበት 0.93 ወደ 1 ማድረስ፤
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት የመጀመሪያ ሣይክል (9-10) ጥቅል ተሳትፎን አሁን ካለበት 41%
ወደ 62% ማድረስ፤
ተግባር ተኮር የጎልማሶች ትምህርትን አሁን ካለበት 36% ወደ 95% ማሳደግ፤
35
መምህራን ብዛት 25% በማሳደግ አጠቃላይ የመምህር/ተማሪ ጥምርታ 1፡20 እንዲሆን
ማድረግ፤
አጠቃላይ ተሳትፎን (Enrollment) በ70፡30 ቀመርና በሳይንስና ቴክኖሎጂ መሪነት ላይ
በመመስረት በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም የተማሪ ብዛት አሁን ካለበት 185,788 ወደ 467,000
ማሳደግ፤
በድሕረ ምረቃ ፕሮግራም የሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ዓመታዊ የቅበላ ዓቅምን በተለይ
ሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ ማኔጅመንት እና ኢኮኖሚክስን ማዕከል በማድረግ ወደ 20,100 ማሳደግ፤
በቅድመ ምረቃው ፕሮግራም የሴቶች ተሳትፎ ድርሻ አሁን ካለው 29% ወደ 40% ማሳደግ፣
በድሕረ ምረቃ ፕሮግራምም ድርሻቸውን ከ10% ወደ 25% ማድረስ፤
በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም የመመረቅ ስኬት የወንዶች 95% የሴቶች 90% ባጠቃላይ 93%
ማድረስ፤
በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በቤተ መጻህፍትና በቤተ ሙከራ አገልግሎት ደረጃውን
የጠበቀ አቅርቦትን ማረጋገጥ፤
4. የማስፈጸሚያ ስልቶች
36
ሁሉም ትምህርት ቤቶች በትምህርት ቤት ማሻሻያ ገዥ መመሪያና መጽሐፈ ዕድ መሠረት
የትምህርት ቤት መሻሻያ ስትራቴጂክ እቅድ በማዘጋጀት መተግበራቸውን ማረጋገጥ፤
ህብረተሰቡ ትምህርት ቤቶችን በሙሉ ባለቤትነት መምራት የሚችልበት ደረጃ ላይ ማድረስ፤
በመምህራን ልማት ገዢ መመሪያ መሠረት የቅድመ እና ድህረ ሥልጠና ትምህርት
እንዲሁም ተከታታይ የሙያ ማሻሻያ ሥልጠና በመስጠት መምህራን የየትምህርት እርከኑ
የሚጠይቀውን የትምህርት ደረጃ እንዲያሟሉ በበቂ ዝግጅት መተግበር፤
ድጋፍ የሚሹ አካባቢዎችና የታዳጊ ክልሎች ነባር ብሔረሰብ ልጆች በመምህርነት ሙያ
እንዲሣተፉና ቁጥራቸውም እንዲጨምር በማድረግ በአካባቢው የመምህራን እጥረትን
በመቅረፍ የትምህርት ጥራትን ማሻሻል፤
የእንግሊዝኛ ቋንቋ መምህራንን በተዘጋጀው ስታንደርድና የመመዘኛ መሣሪያ መሠረት
የክህሎት ክፍተቶችን በመለየት ለደረጃው ብቁ የሚያደርጋቸው ስልጠና መሰጠት፤
በአፍ መፍቻ ቋንቋ ለሚያስተምሩ መምህራን የቋንቋ ክህሎት ማሻሻያ ሥልጠና መስጠት
የሒሳብና የሳይንስ ትምህርቶችን ተማሪዎች በፍላጎትና በአግባቡ እንዲማሩ ለማስቻል
የተዘጋጀውን ስትራቴጂ ሙሉ በሙሉ በመተግበር ተማሪዎች በትምህርት ዓይነቶቹ የተሻለ
ውጤት እንዲያገኙና በቀጣይ የትምህርት ደረጃም በፍላጎት እንዲማሩት ማድረግ፤
የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ሥርዓተ ትምህርትና በመምህራን ትምህርት ተቋማት
የትምህርትና ሥልጠና ሥርዓተ ትምህርት የተሳሰሩና የሚናበቡ እንዲሆኑ መስራት፤
በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የ2ኛ ደረጃን የፕላዝማ ፕሮግራም ሥርጭት
ዲጂታይዝድ ማድረግና ለብሮድካስት በሚመች መልኩ አዘጋጅቶ በመተግበር የትምህርት
ጥራትን ማረጋገጥ፤
ፓኬጁን በውጤታማነት ለመፈፀም እንዲቻል ሦስቱን መስተጋብሮች ማለትም አመለካከት፣
ክህሎትና ግብዓትን መሠረት ያደረገ ቼክሊስት በማዘጋጀት፣ የክትትልና ድጋፍ ሥርዓት
በመዘርጋት፣ በተማሪዎች ተጨባጭ ውጤት ላይ ያመጣውን ለውጥ መገምገምና የፓኬጁን
ብቃት በተሻለ ይዘትና ደረጃ በማሳደግ ተግባራዊ ማድረግ፤
37
ህዝቡን ባሳተፈ መልኩ የት/ቤቶችን ቅርበትና የርስ በርስ ትስስር ማጠናከርና በት/ቤቶችና
በተማሪዎች መኖሪያ አካባቢ መካከል ያለውን ርቀት መቀነስ፤
በሥራ ላይ የሚገኙትን የአማራጭ መሰረታዊ ትምህርት ማዕከላት ወደ መደበኛ የ1ኛ ደረጃ
ት/ቤቶች ማሳደግና አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ብቻ በተለይ ልዩ ድጋፍ በሚሹ ክልሎች ተጨማሪ
ማዕከላትን መክፈትና ማጠናከር፤
በአማራጭ መሰረታዊ ትምህርት ማዕከላትና በመደበኛ ትምህርት ቤቶች መካከል ጠንካራ
የሽግግርና ትስስር ሥርዓት መመስረት፤
ባለ ብዙ ደረጃ (Multigrade) ክፍሎችን በመክፈት ቁጥራቸው አነስተኛ ለሆኑ ማህበረሰቦች
ህጻናት የትምህርት ተሣትፎን ማሳደግ፤
የአርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር ህጻናት ትምህርት ተሣትፎን ለማሳደግ በወጣው
ስትራቴጂ መሠረት አማራጭ የአገልግልት አሰጣጥ ስልቶችን ማለትም የምገባ ፕሮግራም፣
የተንቀሳቃሽ ት/ቤቶች አገልግሎት ወዘተ. ማስፋፋት፤
የተጋላጭ ህጻናትና የታዳጊ ክልሎች ነባር ብሔረሰቦች ህጻናትን የትምህርት ተሣትፎ
ለማሳደግ ልዩ ድጋፍ መስጠት፤
የአጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርትን ለማሳደግ የሚያስችል የማስፋፋት ስራ በስፋት መስራት፣
እንዲሁም ኢኮኖሚው የሚፈልገውን የሰለጠነ የሰው ኃይል ፍላጎትና የከፍተኛ ትምህርት
ተቋማት የቅበላ አቅም መሰረት ያደረገ የ2ኛ ደረጃ የመሰናዶ ትምህርትን ማስፋፋት፤
የግል ባለሃብቶች፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና ማህበረሰቡ የ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶችን
እንዲከፍቱ ማበረታታት፣ ድጋፍ መስጠትና ስታንዳርዱን የጠበቀ ለመሆኑ ተገቢውን ክትትል
ማድረግ፤
የ2ኛ ደረጃ መሰናዶ ትምህርት(11-12) የዋጋ መጋራት ሥርዓትን አጠናክሮ መቀጠል፤
ተግባር ተኮር የጎልማሶች ትምህርትን በስትራትጂው፣ በስርዓተ ትምህርቱና በመመሪያው
መሰረት መተግበር፤
በየደረጃው ያለ የፖለቲካና የትምህርት ዘርፉ አመራር የተግባር ተኮር ጎልማሶች ትምህርትን
የወቅቱ ቁልፍ የልማትና የፖለቲካ ጉዳይ መሆኑን በውል ማስገንዘብና በእውቀት ላይ
ተመሥርቶ በባለቤትነት እንዲመሩት ማስቻል፤
ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነትና ድርሻ እንዲወጡና በተቀናጀና ቀጣይነት ባለው
መልኩ እንዲንቀሳቀሱ በማድረግ መርሀ-ግብሩ ውጤታማ እንዲሆን የበኩላቸውን አስተዋጽኦ
እንዲያበረክቱ መድረግ፤
38
የአመቻቾችን ሥልጠና በብቃት ለመስጠት በመምህራን ትምህርት ኮሌጆች ተቋማዊ ሥርዓት
ዘርግቶ መተግበር፤
የልዩ ፍላጎት ትምህርት ስትራቴጂን ተግባራዊ በማድረግ የትምህርቱን ተደራሸነት ማረጋገጥ፤
በየደረጃው የተጠናከረ የክትትልና ድጋፍ ሥርዓት በመዘርጋት በወቅቱ አስፈላጊውን
የማስተካከያ እርምጃዎችን መውሰድ፤
39
በሁሉም ተፈላጊ ሙያዎች ከኢንዱስትሪው ተመጣጣኝ ወይንም ከፍ ያለ አቅም ያለው
አሰልጣኝ እንዲኖራቸው ማድረግ፤
ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን በመስጠትና የቴክኖሎጂ
ሽግግር ማዕከል በማድረግ ማጠናከር፤
የሴቶችንና የገጠሩን ነዋሪ ህዝብ ማዕከል ያደረጉና ተፈላጊ የሆኑ ሙያዎችን በመለየት
ስልጠና የሚያገኙበትን ሁኔታ በማመቻቸት የሴቶችን አቅም ገንብቶ በቴክኒክና ሙያ
አሰልጣኝነትና ማኔጅመንት ላይ ያላቸውን ድርሻ ማሳደግ፤
በሃገሪቷ ያልተማከለና የተቀናጀ ውጤት ላይ የተመሰረተ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና
ሥልጠና ስርዓትን ለመተግበር በየደረጃው ተፈላጊውን ብቃት ማምጣትና አደረጃጀቱን
በመፈተሽ ማጠናከር፤
የቴክኖሎጂ አቅም ክምችትና ሽግግርን በሚመለከት መልካም ተሞክሮዎችን በመዳሰስ
መጠቀምና የልምድ ልውውጥ ማካሄድ፤
ባለድርሻ አካላትን ከሙያ ደረጃ ምደባ ጀምሮ በስርዓተ ትምህርት ቀረጻ፣ በስልጠናና በምዘና
ተግባራት ላይ ማሳተፍ፤
የስልጠና ገበያ ፍላጎት ጥናት ስርዓት መዘርጋትና በየጊዜው የሙያ ደረጃዎችን ማሻሻልና
ስልጠናዎች እንዲካሄዱ ማድረግ፤
ከፍተኛ ትምህርት
40
ተቋማትና መምህራን በምርምርና ቴክኖሎጂን በማላመድ ልምድ የሚያካብቱበትን ሥርዓት
መዘርጋትና ተግባራዊ ማድረግ፤
የከፍተኛ ትምህርት መምህራን የድኅረ ምረቃ ትምህርት የሚያገኙበትን ዕድል በማስፋት
በቁጥርና በብቃት ከፍ እንዲሉ ማድረግ፣
ሀገር ዓቀፍ የሙያና የትምህርት ብቃት ማዕቀፍ (National Qulifications Framework)
ማዘጋጀትና ተግባራዊ ማድረግ፤
ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተደራጀና በፖሊሲ የሚመራ የውስጥ የጥራት ማረጋገጫ
ሥርዓት አንዲዘረጉ ድጋፍ ማድረግና ማበረታታት፤
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምሩቃኖቻቸውን መዳረሻና የቀጣሪዎቻቸውን እርካታ በማጥናት
(graduate tracer study and employer satisfaction) ከጥናቱ ያገኙትን ግብረ-መልስ እንደ
ግብዓት በመጠቀም ሥርዓተ ትምህርታቸውን የሚያጎለብቱበትንና የሚያሻሽሉበትን ስርዓት
መዘርጋት፤
ልዩ ድጋፍና ትኩረት የሚሹ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ማለትም ሴቶች፣ አካል ጉዳተኞች፣
ታዳጊ ክልሎች፣ ወዘተ.የከፍተኛ ትምህርት ተሳትፎ ለማሳደግ የተለያዩ የአዎንታዊ
እርምጃዎችን (affirmative action) (የተለየ የመግቢያ መስፈርት፣ ልዩ የቲቶሪያል ድጋፍና፣
የስኮላርሺፕ ዕድል፣ ወዘተ) ማመቻቸት
በዚህ ክፍል ስምንት ያህል ጉዳዮች ተካተዋል። እነርሱም ሥርዓተ-ጾታና ትምህርት፣ የልዩ
ፍላጎትና አካቶ ትምህርት፣ ኤች አይቪ ኤድስና ትምህርት፣ የህብረተሰብ ተሣትፎ፣ የአካባቢ
ጥበቃ፣ ያልተማከለ የትምህርት ሥርዓትና የአቅም ግንባታ፣ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች
ለተጎዱ አካባቢዎች ህጻናት መደበኛ ትምህርት (Education in Emergencies) እና
የትምህርት ቤት ጤና እና ምገባ (School Health and Nutrition) ናቸው።
1.ሥርዓተ ፆታ
41
የድህነት ቅነሳና የልማት ስትራቴጂ ውስጥ ትኩረት አግኝቶ እና ተካቶ እንዲተገበር ቀጥሎ
የተዘረዘሩት አቅጣጫዎችና ግቦች ተለይተው ተቀምጠዋል፡፡
42
የትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲው በፈጠረው አመቺ ሁኔታ ከትምህርት የተገለሉትንና ልዩ
ፍላጎት ያላቸውን ህፃናት የትምህርት እድል ለመስጠትና ከዚህም አኳያ የትምህርት ለሁሉም
ግቦችን ለማሳካት የልዩ ፍላጎት ትምህርት ስትራቴጂ ተቀርፆ ሥራ ላይ ውሏል፡፡
ይህ ስትራቴጂ በሁለተኛው የድህነት ቅነሳና የልማት ዕቅድ ውስጥ ትኩረት ተሰጥቶት
በይበልጥ እንዲተገበር ቀጥሎ የተዘረዘሩት የትኩረት አቅጣጫዎችና ግቦች ተቀምጠዋል፡፡
43
የድህነት ቅነሳና የዘላቂ ልማት ፕሮግራም ቀጥሎ በተመለከቱት አንኳር ጉዳዮች ዙሪያ
የተቀናጀና የተጠናከረ እንቅስቃሴ ይደረጋል፡፡
4.የህብረተሰብ ተሳትፎ
44
የተማሪዎችን የትምህርት አለማቋረጥ መደበኛ በሆነ መልኩ መከታተል፣
ትምህርትን በማዳረስና ጥራቱን በመጠበቅ ረገድ ህብረተሰቡ በጉልበት፣ በገንዘብ እና
በእውቀቱ እንዲሳተፍ ማድረግ፣
በትምህርት ሥርዓቱ አመራር ውስጥ ህብረተሰቡ በንቃት እንዲሳተፍ ማድረግ፣
6.የአካባቢ ጥበቃ
45
በአሁኑ ወቅት አካባቢ ጥበቃ የሀገራችንና ብሎም የአለማችን አንገብጋቢ ጉዳይ መሆኑ
አያጠያይቅም፡፡ በመሆኑም ይህንን ሀገራዊና አለም አቀፋዊ ጉዳይ ከዳር ለማድረስና ለመጠበቅ
ዋነኛውና ትክክለኛው አማራጭ የጉዳዩን አሳሳቢነት በትምህርት ዘርፉ በማካተት ለተማሪዎች
ተደራሽ ማድረግ ነው፡፡ በመሆኑም በቀጣይነት በሁለተኛው የዘላቂ ልማትና የድህነት ቅነሳ
ፕሮግራም ሊተገበሩ የሚገባቸውን የትኩረት አቅጣጫዎችና አመላካቾች ተለይተው
ተቀምጠዋል፡፡
ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች /ዋና ዋና ሥራዎች/
46
ለአደጋ ጊዜ ትምህርት ፕሮግራም የቅድመ ዝግጅትና አፋጣኝ ምላሽ መስጫ ሥርዓት
መዘርጋት
እ.ኤ.አ በ1995 በኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ ሃያ ከተሞችና በተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች የተደረገ
ጥናት እንደሚያመለክተው ጫት ፣አልኮል፣ቶባኮ፣ሀሺሽ፣ካናቢስና ሌሎች ሱስ የሚያስይዙ አደገኛ
47
ዕፆችንና መድሀኒቶችን የመጠቀም ሁኔታ በተለይ በወጣቶችና ተማሪዎች ዘንድ እየተባበሰ
መምጣቱ ታውቋል።
ይህ አሳሳቢ ችግር በተለይ በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ደረጃ
በፍጥነት እየተዛመተ እንደሆነ ተጠቅሷል።ችግሩ የተማሪዎችን ጤንነት፣ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ
ህይወት ከማወኩ ሌላ መጠነ ማቋረጥን፣መድገምና የትምህርት ብክነትን እንደሚያባብስ በጥናቱ
ተመላክቷል።
48
ዝርዝር አመልካቾችና ግቦች
ሀ.አጠቃላይ ትምህርት
መነሻ
ግ ቦ ች
አመላካቾች ዓመት
2002 2003 2004 2005 2006 2007
የትምህርት ተሳትፎ አመላካቾች (Access Indicators)
የቅድመ- መደበኛ ወንድ 6.9% 9.5% 12.1% 14.8% 17.4% 20.0%
ትምህርት ጥቅል ሴት 6.9% 9.5% 12.1% 14.7% 17.4% 20.0%
ተሳትፎ አማካይ 6.9% 9.5% 12.1% 14.7% 17.4% 20.0%
ወንድ 136% 133% 130% 126% 123% 120%
የአንደኛ ክልፍ
ሴት 126% 123% 121% 118% 116% 113%
ጥቅል ቅበላ
አማካይ 131% 128% 125% 122% 119% 116%
ወንድ 86.2% 88.3% 90.4% 92.5% 94.6% 100.0%
የአንደኛ ክፍል
ሴት 82.7% 85.5% 88.3% 91.1% 93.9% 100.0%
ንጥር ቅበላ
አማካይ 84.5% 87.0% 89.5% 92.0% 94.5% 100%
የ1ኛ ደረጃ ወንድ 92.9% 93.3% 93.7% 94.1% 94.6% 95.0%
ትምህርት ሴት 90.1% 91.0% 92.0% 93.0% 94.0% 95.0%
የመጀመሪያ
ዕርከን(1-4) ንጥር አማካይ 91.5% 92.2% 92.9% 93.6% 94.3% 95.0%
ተሳትፎ በመቶኛ
የአንደኛ ደረጃ ወንድ 51.9% 57.5% 63.1% 68.8% 74.4% 80.0%
ትምህርት 2ኛ ሴት 52.0% 57.6% 63.2% 68.8% 74.4% 80.0%
ዕርከን ( 5-8) ንጥር
ተሳትፎ አማካይ 52.0% 57.6% 63.2% 68.8% 74.4% 80.0%
49
መነሻ
ግ ቦ ች
አመላካቾች ዓመት
2002 2003 2004 2005 2006 2007
የ1ኛ ደረጃ ወንድ 133.4% 134.9% 133.1% 132.0% 130.8% 129.5%
ትምህርት ሴት 124.5% 126.2% 124.6% 123.9% 123.0% 122.1%
(1-4) /አማራጭ
መሰረታዊ
ትምህርትን ጨምሮ) አማካይ 129.1% 130.7% 128.9% 128.0% 127.0% 125.9%
ጥቅል ተሳትፎ
የአንደኛ ደረጃ ወንድ 67.1% 68.5% 73.3% 80.7% 89.9% 100.4%
ትምህርት 2ኛ ሴት 68.3% 69.0% 73.5% 81.3% 91.0% 102.3%
ዕርከን (5-8) ጥቅል
ተሳትፎ
አማካይ 67.1% 68.5% 73.3% 80.7% 89.9% 100.4%
የአንደኛ ደረጃ (1-8 ወንድ 98.7% 99.4% 102.5% 105.8% 110.0% 114.9%
) ሴት 93.0% 94.4% 98.0% 101.1% 104.9% 109.2%
ትምህርት(አማራጭ 95.9% 96.9% 100.3% 103.5% 107.5% 112.1%
መሰረታዊ
አማካይ
ትምህርትን ጨምሮ)
ጥቅል ተሳትፎ
50
መነሻ
ግ ቦ ች
አመላካቾች ዓመት
2002 2003 2004 2005 2006 2007
መምህራን(9-12)
ክፍል 1-2 4 (1:1) 4 (1:1) 4 (1:1) 4 (1:1)
ክፍል 3-4 5 (1:1) 5 (1:1) 5 (1:1) 5 (1:1)
የ1ኛ ደረጃ
ክፍል 5-
ትምህርት የተማሪ 7 (1:1) 7 (1:1) 7 (1:1) 7 (1:1)
-መጽሐፍ ጥምርታ 6
ክፍል 7-
8 (1:1) 8 (1:1) 8 (1:1) 8 (1:1)
8
ክፍል 9-
የ2ኛ ደረጃ 10 (1:1) 10 (1:1) 10 (1:1) 10 (1:1) 10 (1:1)
10
ትምህርት የተማሪ
-መጽሐፍ ጥምርታ ክፍል 11-
10 (1:1) 10 (1:1) 10 (1:1) 10 (1:1) 10 (1:1)
12
ክፍል 1-
የ1ኛ ደረጃ 56.9 55.1 53.2 51.4 49.6 47.8
4
ትምህርት የተማሪ
-መምህር ጥምርታ ክፍል 5-
45.7 44.4 43.1 41.8 40.5 39.2
8
ክፍል 9-
የ2ኛ ደረጃ 40.2 39.0 37.7 36.3 34.9 33.3
10
ትምህርት የተማሪ
-መምህር ጥምርታ ክፍል 11-
25.3 24.8 24.2 23.6 23.0 22.2
12
በ4ኛ ክፍል
በሚደረግ
ሃገር አቀፍ
የትምህርት 1 1
ቅበላ
40.9% 65% 75%
ጥናት
የትምህርት ቅበላ
ጥናት በዋና ዋና
የትምህርት
ዓይነቶች ቢያንስ
50 % ውጤት ያገኙ
ተማሪዎች
በ8ኛ ክፍል
በሚደረግ
የትምህርት ቅበላ ሃገር አቀፍ
ጥናት በዋና ዋና የትምህርት
35.6% 60% 70%
የትምህርት ቅበላ
ዓይነቶች ቢያንስ ጥናት
50 % ውጤት ያገኙ
ተማሪዎች
በ10ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ
በሚደረግ የትምህርት 13.8% 50% 70%
የትምህርት ቅበላ ቅበላ
1
2004 እና 2005 የተዘለሉበት ምክንያት የትምህርት ቅበላ ጥናት ምዘና የሚካሔድ በየሁለት ዓመት በመሆኑ ነው፡፡
51
መነሻ
ግ ቦ ች
አመላካቾች ዓመት
2002 2003 2004 2005 2006 2007
ጥናት በዋና ዋና ጥናት
የትምህርት
ዓይነቶች ቢያንስ
50 % ውጤት ያገኙ
ተማሪዎች
በ12ኛ ክፍል
በሚደረግ
የትምህርት ቅበላ ሃገር አቀፍ
ጥናት በዋና ዋና የትምህርት
34.9% 60% 70%
የትምህርት ቅበላ
ዓይነቶች ቢያንስ ጥናት
50 % ውጤት ያገኙ
ተማሪዎች
በ4ኛ ክፍል
በሚደረግ
የትምህርት ቅበላ ሃገር አቀፍ
ጥናት በዋና ዋና የትምህርት
1.7% 20% 25%
የትምህርት ቅበላ
ዓይነቶች ቢያንስ ጥናት
75 % ውጤት ያገኙ
ተማሪዎች
በ8ኛ ክፍል
በሚደረግ
የትምህርት ቅበላ ሃገር አቀፍ
ጥናት በዋና ዋና የትምህርት
የትምህርት ቅበላ
0.7 20% 25%
ዓይነቶች ቢያንስ ጥናት
75 % ውጤት ያገኙ
ተማሪዎች
በ10ኛ ክፍል
በሚደረግ
የትምህርት ቅበላ ሃገር አቀፍ
ጥናት በዋና ዋና የትምህርት
1.3% 20% 25%
የትምህርት ቅበላ
ዓይነቶች ቢያንስ ጥናት
75 % ውጤት ያገኙ
ተማሪዎች
በ12ኛ ክፍል
በሚደረግ
የትምህርት ቅበላ ሃገር አቀፍ
ጥናት በዋና ዋና የትምህርት
12.4% 20% 25%
የትምህርት ቅበላ
ዓይነቶች ቢያንስ ጥናት
75 % ውጤት ያገኙ
ተማሪዎች
በ1ኛ ደረጃ ወንድ 75% 76% 89% 98% 107% 116%
ትምህርት (1-
4)ትምህርትን ሴት 73% 74% 86% 95% 102% 109%
ተከታትሎ
የማጠናቀቅ ምጣኔ አማካይ 74% 75% 88% 97% 104% 112%
በመቶኛ
በ1ኛ ደረጃ ወንድ 47% 49% 57% 58% 63% 79%
52
መነሻ
ግ ቦ ች
አመላካቾች ዓመት
2002 2003 2004 2005 2006 2007
ትምህርት (5- ሴት 44% 49% 59% 60% 64% 79%
8)ትምህርትን
ተከታትሎ
የማጠናቀቅ ምጣኔ አማካይ 46% 49% 58% 59% 64% 79%
በመቶኛ
የብቃት አመላካቾች( Efficiency indicators)
ወንድ 17.3% 14.1% 10.8% 7.5% 4.3% 1.0%
የ1ኛ ክፍል መጠነ
ሴት 16.0% 13.0% 10.0% 7.0% 4.0% 1.0%
ማቋረጥ
ድምር 16.7% 13.6% 10.4% 7.3% 4.1% 1.0%
የ1ኛ ደረጃ ወንድ 11.5% 9.2% 7.1% 4.9% 2.8% 1.0%
ትምህርት(1-8) ሴት 10.0% 8.0% 6.1% 4.3% 2.4% 1.0%
የመጠነ ማቋረጥ
ድምር 10.8% 8.7% 6.6% 4.6% 2.6% 1.0%
አማካይ ምጣኔ
የ1ኛ ደረጃ ወንድ 6.1% 5.2% 4.2% 3.1% 2.1% 1.0%
ትምህርት ሴት 5.4% 4.6% 3.7% 2.8% 1.9% 1.0%
(4-8) የመጠነ
መድገም አማካይ ድምር 5.8% 4.9% 3.9% 3.0% 2.0% 1.0%
ምጣኔ
53
ክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጥና
54
መነሻ ግቦች
አመላካቾች መለኪያ ዓመት
2002 2003 2004 2005 2006 2007
የደረጃ 3 እና 4 መዛኝነት ዕውቅና የተሰጣቸው
ቁጥር 469 781 1,198 1,719 2,448
የኢንዱስትሪ መዛኞች
1,324
የደረጃ 1 እና 2 መዛኝነት ዕውቅና የተሰጣቸው
ቁጥር 3,281 5,469 8,385 12,031 17,135
የኢንዱስትሪ መዛኞች
አጠቃላይ የኢንዱስትሪ መዛኝ ድምር 1,324 3,750 6,250 9,583 13,750 19,583
የምዘና መሣሪያ የተዘጋጀላቸው ሙያዎች ቁጥር 211 300 330 350 370 390
ዕውቅና የተሰጣቸው የምዘና ማዕከላት ቁጥር 174 250 250 334 417 500
575,0
የተመዘኑ ዕጩዎች ቁጥር 75,000 225,000 375,000 825,000 1,175,000
00
የሙያ ብቃት ምዘና ያለፉ ተመዛኞች መጠን መቶኛ 20 28 36 44 52 60
የሙያ ደረጃ የወጣላቸው ሙያዎች ቁጥር 250 300 330 350 370 390
55
መነሻ
መነሻ
አመላካቾ ዓመ
አመላካቾች መለኪያ ዓመት ግቦች መለኪያ ግቦች አመላካቾች
ች ት
2002
2002
ድምር ቁጥር 815 888 956 1,029 1,102 1,147
ወደ ጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት የተሸጋገሩ ቴከኖሎጅዎች ቁጥር 100 200 400 600 800 1,000
56
ሐ. ከፍተኛ ትምህርት
መነሻው
ክንውን የዕቅዱ ዘመን የተሳትፎ ዒላማዎች
የመስኮች
ምድብ
2002 2003 2004 2005 2006 2007
57
2. የልዩ ልዩ ዒላማዎች ዕቅድ
58
5. የትምህርትና ስልጠና ዘርፍ የፋይናንስ ፍላጎት
የልማት ዕቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ የፋይናንስ ፍላጎትን ማየት የግድ ነው። ስለሆነም
ለአምስት አመቱ የልማት ዕቅድ ለትምህርት ዘርፍ የሚያስፈልገው የመደበኛና የካፒታል
ፋይናንስ ፍላጎት እንደሚከተለው የተቀመጠ ሲሆን ይህ የፋይናንስ ፍላጎት ግምት ጊዚያዊ
ግምት እንደ መሆኑ መጠን የሚለወጥ ይሆናል ።
ሀ.አጠቃላይ ትምህርት
መደበኛ ፦62.787 ቢሊየን ብር
ካፒታል ፦12.973 ቢሊየን ብር
ድምር፦75.700.000.000 (ሰባ አምስት ነጥብ ሰባት ቢሊየን ብር)
59
ሀ. አጠቃላይ ትምህርት (ዋጋ በቢሊየን ብር)
60
ለ. ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና
Machinery &
equipment 405,080,960 632,939,000 253,175,600 227,858,040 202,540,480 75,952,680 1,392,465,800
61
ሐ. ከፍተኛ ትምህርት
y¦gR WS_
mMH‰N dmwZ 485,441,859 626,755,382 764,472,768 784,948,734 796,324,271 3,457,943,016
yW+ ¦gR
mMH‰N dmwZ 22,471,280 25,985,440 28,016,560 25,018,240 21,794,240 123,285,760
kdmwZ l@§
wÀãC 1,088,073,000.00 1,478,477,000 1,858,825,500 1,945,692,000 1,991,612,000 8,362,679,500
yመdb¾ bjT
DMR 1,702,119,401 2,263,703,999 2,722,663,321 2,828,195,821 2,862,142,008 12,378,824,552
2.yµpE¬L bjT
yµpE¬L bjT
DMR 3,904,967,306 2,947,852,949 2,266,849,460 2,146,734,347 2,032,029,118 13,298,433,180
yመdb¾Â µpE¬L
bjT DMR 5,607,086,706.6 5,211,556,948.1 4,989,512,781.1 4,974,930,168.9 4,894,171,126.6 25,677,257,731.2
62
በትምህርት ዘርፍ በቀጣዩ አምስት ዓመታት ሊተገበሩ የታቀዱ የልማት ፕሮጀክቶች
በሚቀጥሉት አምስት አመታት ሊተገበሩ ከታቀዱ የትምህርት ዘርፍ ፕሮግራሞች/ፕሮጀክቶች መካከል የሚከተሉት ዋና
ዋናዎቹ ናቸው
63
የዩኒቨርሲቲዎች ግንባታ
የትምህርት
3 668,193,441.00 379,497,742.00 106,993,215.00 41,094,107.00
መሳሪያዎች
ግዥ
3,064,400,037.00 1,720,168,073.00 752,120,298.00 410,717,008.00
ድምር
64
በሚቀጥሉት አምስት አመታት ሊተገበሩ ከታቀዱ የትምህርት ዘርፍ ፕሮግራሞች/ፕሮጀክቶች መካከል የሚከተሉት ዋና
ዋናዎቹ ናቸው
65
2.የ10 ዩኒቨርሲቲዎች ግንባታ
5. ጠቅላላ ድምር
3,290,878,037.00 2,173,131,073.00 1,431,547,298.00 1,261,217,008.00
8,156,773,416.00
66
6. የልማት ዕቅዱ ዘመን ዕድሎችና ሥጋቶች
6.1. ዕድሎች
በተከታታይ በሃገሪቱ የሚታየው የኢኮኖሚ ዕድገት የትምህርት ዘርፉን በበጀት
ለመደገፍ አስተማማኝ መሆኑ
mNGST የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርትን በ2008 ዓ.ም ፣ የአጠቃላይ 2ኛ ደረጃ
ትምህርትን ደግሞ በ2017 ዓ.ም ለሁሉም ለማዳረስና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና
ሥልጠና ykFt¾ TMHRTN l¥SÍÍT l¥ššL¼l¥údG ys-W Tk#rT q$R-
"nT½
የመንግስትንና የልማት አጋሮችን ተሣትፎ በማጠናከር የትምህርት ጥራትን
ለማሻሻል መንግስት የሚያሳየው ተግባራዊ እንቅስቃሴና ትኩረት
በሥርዓተ-ፆታ፣ በክልሎች፣ በከተማና በገጠር መካከል የሚታየውን የትምህርት ተሣትፎ
ፍትሐዊነት ለማረጋገጥ በመንግስት በኩል የተለያዩ ስትራቴጅዎች መነደፋቸው
የትምህርት ብክነትን ለመቀነስ እስከ ትምህርት ተቋማት ድረስ የተፈጠረው ግንዛቤና
እየተወሰደ ያለው ርምጃ
bmNGST tÌ¥T ytÌ¥êE lW_ GNƬ XNÄ!h#M ymMH‰N L¥TÂ
y|R›t(TMHRT lW_ tGƉêE mçN½
ykFt¾ TMHRT tÌ¥T xm‰éCN yxm‰R xQM B”T l¥údG ytjm„
yxQM GNƬ PéËKèC mñ‰cW½
yTMHRT SL- _‰T ¥rUgÅ x@jNs! mf-R btšl mLk# md‰jTÂ
m-ÂkR የትምህርትና ስልጠናና የቴ/ሙ/ት/ስለጠና ፖሊሲና እስትራቴጂ መነደፉና
የተመቻቸ የኢንቨስትመንት ፖሊሲ መኖር፣
የቴ/ሙ/ት/ስልጠና ላይ የህብረተሰቡ ተሳትፎ እየተሻሻለ መምጣቱናከአነስተኛና
ጥቃቅን ኢንተፕራይዞች ጋር በትስስር መስራት መቻሉ፣
የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ መስፋፋት
6.2. ስጋቶች
ymMH‰N bbqE q$_RÂ ldr©W b¸m_N yTMHRT ZGJTÂ B”T xlmgßT
Ãl#TNM l¥öyT xlmÒl#½
yb@t(Ñk‰ :”ãC ym¥¶Ã q$œq$îC bbqE m-N½ _‰T½ bwQt$ xlmQrB
67
እየተገኘ ያለው የትምህርት መስፋፋት ውጤት አበራታች ቢሆንም የትምህርት ጥራት
በተፈለገው መልኩ ላይገኝ ይችላል
የሀብት ውስንነት ሊያጋጥም ይችላል
ከተቋማት ቁጥርና አቅም በላይ የሰልጣኞች ፍላጎት ሊጨምር ይችላል
ለሙያ ምዘና የሚቀመጡ ሰልጣኞች ቁጥር በመብዛቱ በወቅቱ ለማስተናገድ ያለመቻል
ችግር ሊያጋጥም ይችላል
የግል ኢንተርፕራይዞች ለትብብርና ለኩባንያ ውስጥ ስልጠና ያላቸው ተሳትፎ አጥጋቢ
ላይሆን ይችላል
yMRMR |‰ãCN k¦g¶t$ yL¥T FላጎT UR y¸ÃStœSR -Nµ‰ |r›T
xlmñ„½
y†n!vRs!tE kFt¾ xm‰éC mlêw_ xm‰„ bqE LMD bl@§cW xÄÄ!S
ሃ§ðãC mÃZ½
yMRMR |‰ãCN k¦g¶t$ yL¥T FላጎT UR y¸ÃStœSR -Nµ‰ |r›T
xlmñ„½
y†n!vRs!tE kFt¾ xm‰éC mlêw_ xm‰„ bqE LMD bl@§cW xÄÄ!S
ሃ§ðãC mÃZ½
lkFt¾ TMHRT xê°Â TMHRT ¸n!St&R¼yTMHRT xGÆBnTÂ _‰T
¥rUgÅ x@jNs! l¸ÃwÈcW y_‰T mSfRèC ytlÆ mm¶ÃãC y¥Ygz#
tÌ¥TN btmlkt xSgÄJnT ÃlW |R›T xlmzRUT ናቸው።
TMHRT xê°Â TMHRT ¸n!St&R¼yTMHRT xGÆBnTÂ _‰T ¥rUgÅ x@jNs!
l¸ÃwÈcW y_‰T mSfRèC ytlÆ mm¶ÃãC y¥Ygz# tÌ¥TN
btmlkt xSgÄJnT ÃlW |R›T xlmzRUT ናቸው።
7.ክትትልና ግምገማ
ዓመታዊ የትምህርትዘርፍ ልማት ፕሮግራም የአፈጻጸምና የጋራ ግምገማ፣
ዓመታዊ የትምህርት ጉባኤ፣
ወቅታዊ የፋይናንስና ፊዚካል አፈጻጻም ሪፖርት፣
አመታዊ የትምህርት ስታስቲካዊ መረጃ ሪፖርት፣
ከክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊዎች ጋር በየሁለት ወሩ የሚካሄድ ቋሚ የጋራ ስብሰባ፣
68
ከዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች ጋር በየሶስት ወሩ በቋሚነት የሚደረግ የሩብ ዓመት
ግምገማ፣
የትምህርት ዘርፉን የሚደግፉ አጋሮች፣ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴርና ክልሎች
የተሳተፉበት በትምህርት ተቋማት፣ በወረዳና ክልል ትምህርት ቢሮዎች በመገኘት
በየዓመቱ የሚደረግ የጋራ ግምገማ፣
በ4ኛ፣ በ8ኛ፣ በ10ኛና በ12ኛ ክፍል ደረጃዎች በየሶስት ዓመቱ የሚካሄድ የተማሪዎች
የትምህርት ቅበላ ጥናት፣
ለ. ማጠቃለያ
69
ጥራት ያለው ትምሀርት ለሁሉም!
70