Download as pdf or txt
Download as pdf or txt
You are on page 1of 70

የትምህርትና ስልጠና ዘርፍ

የቀጣዩ አምስት ዓመታት የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ


(2003-2007)

ትምህርት ሚኒስቴር

2002 ዓ.ም.

1
ማ ው ጫ

ተ/ቁ ርዕስ ገጽ

1 መግቢያ .................................................................................................... 3
2 ያለፈው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም አፈጻጸም ግምገማ
/1998-2002 ዓ/ም/ ..................................................................................... 4
3 የትምህርት ዘርፍ የአምስት ዓመት /2003-2007/ ዕቅድ ................................... 29

4 ዓላማዎች፣ ግቦችና የማስፈጸሚያ ስልቶች................................................... 33


5 የባለ ብዙ ዘርፍ ጉዳዮች ............................................................................ 34
6 ዝርዝር አመልካቾችና ግቦች ...................................................................... 41
7 የትምህርት ዘርፍ የፋይናንሰ ፍላጎት.......................................................... 56
8 በትምህርት ዘርፍ በቀጣዩ አምስት ዓመታት ሊተገበሩ የታቀዱ የልማት
ፕሮጀክቶች ........................................................................................... 60
9 የልማት ዕቅድ ዘመን ዕድሎችና ሥጋቶች.................................................. 64
10 ክትትልና ግምገማ ..................................................................................... 65
11 ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችና ማጠቃለያ .......................................................... 66

2
1.መግቢያ

መንግሥት ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ልማትን በሃገር አቀፍ ደረጃ በማረጋገጥ ድህነትን ለመቀነስና
ለማስወገድ ግልፅ የሆነ ራዕይ አስቀምጧል።ይህም በ2017 ዓ.ም ኢትዮጵያን መካከለኛ ገቢ
ካላቸው ዲሞክራሲያዊ አገሮች ተርታ ተሰልፋ ማየት ነው። ይህን ታላቅ ራዕይ ዕውን ለማድረግ
ደግሞ የትምህርት ዘርፍ ልማት ታላቅ የማስፈጸም አቅም ግንባታ ሚና አለው።

ከዚህ አኳያ ለሃገር አቀፉ ዘላቂ ልማትና የድህነት ቅነሣ ፕሮግራም በግብዓትነት የሚያገለግል
የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም የመካከለኛ ጊዜ ዕቅድ በፌዴራል የትምህርት ሚኒስቴርና
በክልል መንግስታት ሰፊና ንቁ ተሳትፎ ተዘጋጅቷል ፡፡ ዝግጅቱ በፌዴራል የትምህርት
ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራር የቅርብ ክትትልና ድጋፍ የተደረገለት ሲሆን በሚኒስቴር መ/ቤቱ
የዕቅድ ዝግጅትና ሐብት ማፈላለግ ማኔጅመንት የሥራ ሂደት አስተባባሪነት ከሁሉም የሚኒስቴር
መ/ቤቱ የሥራ ሂደቶች ፣ከክልል መንግስታት ት/ቢሮዎችና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና
ኤጀንሲዎችና ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ ባለሙያዎችን ያሳተፈ ነበር፡፡

የዕቅድ ዝግጅቱ ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የተላከውን የመካከለኛ ዘመን ዕቅድ
ዝግጅት ጥቅል መመሪያ (Generic Guideline) እና የዕቅድ መነሻ ሐሳቦች መሰረት ያደረገ ነው፡፡
በውስጡም የአጠቃላይ ትምህርት ዘርፍ (ቅድመ-መደበኛ ትምህርት፣ የመጀመሪያና የሁለተኛ
ደረጃ ትምህርት፣አማራጭ መሰረታዊ ትምህርትና የጎልማሶች መሰረተ-ትምህርት) ፣የቴክኒክና
ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ፣ የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍና የባለ ብዙ ጉዳዮች (Cross
Cutting Issues) ዘርፍ ተካተዋል፡፡

ዕቅዱ ያለፈውን የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም የአፈጻጸም ሁኔታ በመዳሰስ በልማት ዕቅዱ
የትግበራ ወቅት የተገኙ ውጤቶችንና ያጋጠሙ ችግሮችን፣ በ2ኛው ሃገር አቀፍ ዘላቂ የልማትና
ድህነት ቅነሣ ፕሮግራምና በአራተኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም የትግበራ ወቅት
መወሰድ የሚገባቸውን ርምጃዎችና የአተገባበር ስትራቴጅዎችን፡ዝርዝር አመልካቾችንና ግቦችን
፣የፋይናንስና የሰው ኃይል ፍላጎትን ፣ በልማት ዕቅዱ ዘመን ሊኖሩ የሚችሉ ዕድሎችና ሥጋቶችን
እንዲሁም ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችንና ማጠቃለያን አካቷል።

3
ክፍል አንድ

2. ያለፈው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም አፈጻጸም ግምገማ (1998-2002ዓ.ም)

2.2. አጠቃላይ ትምህርት

2.2.1. የትምህርት ተሣትፎና ፍትሐዊነትን በተመለከተ

ሀ. ቅድመ-መደበኛ ትምህርት

የቅድመ-መደበኛ ትምህርት ጥቅል ተሣትፎ በ1997 ዓ.ም ከነበረበት 2.2% በ2001 ዓ.ም ወደ
4.2% አድጓል። የሴት ህጻናት ተሣትፎም ከ2.1% ወደ 4.2% ከፍ ብሏል። በ1997 ዓ.ም 32:1
የነበረው የተማሪ-መምህር ጥምርታ በ2001 ዓ.ም ወደ 21:1 ተሻሽሏል፡፡ እንደዚሁም በ1997 ዓ.ም
1,497 የነበረው የቅድመ-መደበኛ ት/ቤቶች ቁጥርም በ2001 ዓ.ም ወደ 2,904 አድጓል፡፡

ሆኖም ግን የሰለጠኑ መምህራን ቁጥር ማነስ፣ በቅድመ-መደበኛ ትምህርት ተሣትፎ ላይ የመረጃ


እጥረት፣ በገጠርና በአርብቶ አደር አካባቢዎች የመዋዕለ-ህጻናት አለመስፋፋት ዋና ዋና ችግሮች
እንደነበሩ የታወቀ ሲሆን ችግሮቹን ለመፍታትም የቅድመ-መደበኛ ትምህርት ሥርዓተ-ትምህርት፣
ፖሊሲ፣ ስትራቴጅና የአተገባበር መመሪያ ተዘጋጅተዋል፡፡

ለ. የአንደኛ ደረጃ ትምህርት/ ከ1ኛ-8ኛ (አማራጭ መሠረታዊ ትምህርትን ጨምሮ)

የአንደኛደረጃ ትምህርት ተሣትፎ ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ ፈጣን ዕድገት አሣይቷል፡፡
በከተማውም የማስፋፋቱ ሥራ እንደተጠበቀ ሆኖ ገጠሩን ማዕከል ያደረገ የትምህርት ቤቶች
የማስፋፋት ሥራ በመሰራቱ በ1997 ዓ.ም 16,513 የነበረው የአንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች ቁጥር
በ2001 ዓ.ም ወደ 25,212 አድጓል፡፡ በትምህርት ቤቶች ግንባታ ላይ ከፍተኛ የሆነ
የማኅበረሰብ ተሣትፎ ታይቷል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘም የመማሪያ ክፍሎች ቁጥር ከ161,795 ወደ
247,698 ሲጨምር የትምህርት ቤቶች ቁጥር ዓመታዊ ዕድገት ምጣኔ በ2001 ዓ.ም 11.2%
ደርሷል፡፡

4
ህብረተሰቡ በተለይም የገጠሩና አርብቶ አደሩ ህብረተሰብ ለትምህርት ያለው አመለካከት
አዎንታዊ በሆነ መልክ እንዲቀየር በመንግስት በኩል በተደረጉ ጥረቶች ለትምህርት የሚሰጠው
ትኩረት ከፍ እያለ በመምጣቱ ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት
እንዲገቡ ለማድረግ የራሱ ከፍተኛ ድርሻ ነበረው፡፡

በመሆኑም ከ1ኛ-8ኛ ክፍል በ1997 ዓ.ም የነበረው 79.8% ጥቅል ተሣትፎ በ2001 ዓ.ም 105.5%
ለማድረስ ታቅዶ 94.2% ውጤት ተገኝቷል። ዓመታዊ የዕድገት ምጣኔውም 8.0% እንደነበረ
ታውቋል። የንጥር ተሣትፎን በተመለከተም በ1997 ዓ.ም 68.5%( ወንድ 73.2 %፣ ሴት 63.6%)
የነበረው በ2001 ዓ.ም 87.8% ለማድረስ ታቅዶ 83.0% ( ወንድ 84.6%፣ሴት 81.3%) ሆኗል።

በሴቶችና በወንዶች መካከል የነበረው የጥቅል ተሣትፎ ልዩነትም እየጠበበ መጥቷል። በ1997
ዓ.ም የነበረው የወንዶች ጥቅል ተሣትፎ 88% ሲሆን የሴቶች ደግሞ 71.5% ሆኖ ልዩነቱ የ16.5%
ነበር። በ2001 ዓ.ም የወንዶች ወደ 91.2%፣ የሴቶች ወደ 87.5% አድጎ ልዩነቱ ወደ 3.7%
ተሻሽሏል። በንጥር ተሣትፎም በ1997 ዓ.ም የነበረው የ 9.6 % ልዩነት በ2001 ዓ.ም ወደ 3.3 %
ዝቅ ብሏል።

በክልሎች መካከል ስለተመዘገበው የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ተሣትፎ በተመለከተም አብዛኞቹ


ክልሎች ከተቀመጠላቸው የጥቅል ተሣትፎ ግብ አኳያ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንዳሉ ታውቋል።
በተለይ በአፋርና በሶማሌ ክልሎች በሦስተኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም የመጨረሻ
ዓመታት የተመዘገበው ተሣትፎ አበረታች ሲሆን ሃገራችን የሚሊኒየም ግቡን ማሣካት
እንደምትችል አመላካች ነው። በ2002 ዓ.ም የአፋርና ሶማሌን ጥቅል የትምህርት ተሣትፎ
90% ለማድረስ ታቅዶ በ1997 ዓ.ም በአፋር ክልል የነበረው 20.9% ጥቅል ተሣትፎ በ2002
ዓ.ም በተገኘው መረጃ መሰረት 58.2%፣ የሶማሌ ደግሞ በ1997 ዓ.ም ከነበረበት 23.3%
በ2002 ዓ.ም 70% መድረሱ ታውቋል።

5
በክልሎች የሴትና ወንድ ተማሪዎች ተሣትፎ በተመለከተም ልዩነቱ በአብዛኞቹ ክልሎች እየጠበበ
የመጣ ሲሆን በ2001 ዓ.ም መረጃ መሠረት በተወሰኑ ክልሎች ልዩነቱን ለማጥበብ አሁንም ጥረት
መደረግ እንዳለበት ታውቋል።

ሐ.የ2ኛ ደረጃ ትምህርት (9-12)

ባለፈው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም ወቅት የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ትኩረት ተሰጥቶት
ሲሰራበት ቆይቷል።የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ተሣትፎን ለማሳደግ ግብዓት ከማሟላት አኳያ
በሦስተኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም ወቅት በገጠሩም በርካታ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች
ተከፍተዋል ፡፡

በመሆኑም በ1997 ዓ.ም 706 የነበሩት የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች (9-12) በ2001 ዓ.ም 1,197
ደርሰዋል፡፡ ስለሆነም ባለፉት አራት ዓመታት የ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች እድገት በመቶኛ ሲሰላ በ70%
አድጓል፡፡ በከተማና ገጠር መካከል የነበረው የተሣትፎ መጠን ልዩነት የከተማውን የተሣትፎ
ዕደገት ሣይገድብ ዝቅ ብሏል፡፡

የ2ኛ ደረጃ ትምህርትን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ የሚያግዝ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ስትራቴጂም
ተዘጋጅቷል። በስትራቴጂው መሠረት የአጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርትን (9-10) በ2012 ዓ.ም
ዕድሜያቸው ለደረጃው ለሚመጥኑ ዜጎች የማዳረስ ግብ ተቀምጧል። ይህ ግብ ተገቢ ግን ደግሞ
ፈታኝ መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል። ተገቢ የሚሆንበት ምክንያት ኢትዮጵያን መካከለኛ ገቢ
ያላት አገር ከማድረግ ራዕይ እና ውጤት ጋር የተገናዘበ በመሆኑ ነው።

በዚህ መሠረት በ1997 ዓ.ም 27.3% የነበረው የአጠቃላይ 2ኛ ደረጃ (9-10) ትምህርት ጥቅል
ተሣትፎ በ2001 ዓ.ም ወደ 38.1% አድጓል። ይህ ውጤት በ2002 ዓ.ም. ሊደረስበት ከተጣለው
የ39.0 % ግብ አንጻር ሲታይ ጥሩ ነው። እንደዚሁም በ2ኛ ደረጃ የመሰናዶ ትምህርት (11-12)
በ1997 ዓ.ም 92,483 የነበረው የተማሪ ቁጥር በ2001 ዓ.ም 110,165 ለማድረስ ታቅዶ ወደ
205,260 አድጓል።

6
በሴቶችና ወንዶች መካከል የነበረውን ተሣትፎ በተመለከተም በ1997 ዓ.ም ከ9-10ኛ ክፍል
21.6% የነበረው የሴቶች ተሣትፎ በ2001 ዓ.ም ወደ 32.4% ከፍ ሲል 36.6% የነበረው የወንዶች
ተሣትፎ ደግሞ ወደ 43.7% አድጓል ፡፡ይህም በ2002 ሊደረስበት ከተቀመጠው 36.8% ግብ
አንጻር በ5.1% ብልጫ አሣይቷል። እንደዚሁም ከ11-12ኛ ክፍል በ1997 ዓ.ም 25,070 የነበረው
የሴት ተማሪዎች ቁጥር በ2001 ዓ.ም ሊደረስበት ከተጣለው 89,299 ግብ አንጻር ወደ 35,032
ሲያድግ 67,413 የነበረው የወንድ ተማሪዎች ቁጥር ደግሞ ወደ 83,257 ከፍ ብሏል።

የአጠቃላይ 2ኛ ደረጃ (9-10) ትምህርት ንጥር ተሣትፎን በተመለከተም በ1997 ዓ.ም ከነበረው
11.8% በ2001 ዓ.ም ወደ 12.6% ከፍ ብሏል። በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት የሚታየው የሥርዓተ-
ፆታ ፍትሐዊነት ጉድለት በአንደኛ ደረጃ የትምህርት ዕርከን ባለው ፍትሐዊነት መሰረት መሻሻሉ
የሚቀጥል ይሆናል።

በገጠርና በከተማ እንዲሁም በክልሎች መካከል ያለው የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ተሣትፎ ልዩነቱ
መጠነኛ መሻሻል አሣይቷል።ሆኖም ግን የአጠቃላይ የ2ኛ ደረጃ ትምህርትን (9-10) በ2012 ዓ.ም
ዕድሜያቸው ለደረሱ ሁሉ ለማዳረስ ከተጣለው ግብ አኳያ ያለው ክፍተት ከፍተኛ ሥራ
መሥራት እንደሚጠይቅ ያመላክታል።

መ. የጎልማሶች ትምህርት

በ3ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም ወቅት የጎልማሶች ትምህርት ስትራቴጂ፣ የጎልማሶች
መሠረተ ትምህርት ሥርዓተ ትምህርት ማዕቀፍና የትግበራ መመሪያ፣ የአመቻቾች መጽሐፈ-ዕድ
ተዘጋጅተዋል። በተጨማሪም በትምህርት ሚኒስቴርና ሌሎች የዘርፍ መስሪያ ቤቶች (ግብርና፣
ጤና፣ ወጣቶችና ስፖርት፣ ሠራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ፣ ሴቶች ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች)
መካከል በጎልማሶች ትምህርት ፕሮግራም አተገባበር ላይ የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈርሟል።
የጎልማሶች ተግባር ተኮር ትምህርት የአተገባበር መመሪያ ተዘጋጅቶ ወደ ትግበራ ለመግባት
በየክልሎቹ አውደ ጥናት ተካሂዷል፡፡ክልሎቹም መመሪያውን ወደየራሳቸው ተጨባጭ ሁኔታ
እንዲተረጉሙትና ተግባራዊ እንዲያደርጉት ተደርጓል፡፡ ስትራቴጂውን ለመተግበርም ብሔራዊ

7
ግብረ-ኃይል ተቋቁሟል። በዚህ መሰረት የጎልማሶች ትምህርት በተግባር ከሚገኝ ልምድና
በመንግስትና በህዝብ ትብብር እንዲሁም በልማት አጋሮች ተሣትፎ ይበልጥ የተቀናጀና የጎለበተ
እንዲሆን በስትራቴጅው መሰረት ያላሰለሰ ጥረት ይጠይቃል።

ሠ.ልዩ ድጋፍ የሚሹ ክልሎች

ልዩ ድጋፍ ለሚሹ ክልሎች ትምህርትን በፍትሐዊነት ማዳረስ በተመለከተ ከመደበኛ ትምህርት


አቅርቦት በተጨማሪ በቋሚነትና በኮንትራት የሚሰሩ የትምህርት ባለሙያዎችን ከማዕከል ቀጥሮ
በመመደብ በትምህርት ዕቅድ ዝግጅትና አተገባበር፣አፈጻጸምና ግምገማ ላይ ቴክኒካዊና ሙያዊ
እገዛ ተደርጓል፡፡በእነኚህ ክልሎች ስለ አጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፓኬጅ ምንነትና
አተገባበር በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫና ልዩ ዕገዛ በመደረጉና ክልሎችና ህብረተሰቡ
ባደረጉት ንቁ ተሣትፎና ርብርቦሽ በትምህርት ተሣትፎ ላይ ከፍተኛ ዕድገት ታይቷል፡፡ በተለይ
በአፋርና ሱማሌ ክልሎች ከ50% በታች የነበረው (በ1997 ዓ.ም አፋር 20.9% ፣ ሶማሌ 23.3%)
የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ተሣትፎ በ2002 ዓ.ም የአፋር ክልል 58.2%፣የሱማሌ ክልል ደግሞ
70% ሊደርስ ችሏል፡፡በእርግጥ ይህ ውጤት ሁለቱ ክልሎች በ2002 ዓ.ም እንዲደርሱበት
ከታቀደው የ90% ግብ አኳያ ሲታይ አሁንም ብዙ መሰራት እንዳለበት መረዳት ይቻላል። ልዩ
ድጋፍ ለሚሹ አራቱ ክልሎች (አፋር ፣ሶማሌ፣ጋምቤላና ቤኒሻንጉል ጉምዝ) የ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶችን
የቴሌቪዥን ትምህርት ፕሮግራም ተጠቃሚ ለማድረግ የ100 ቴሌቪዥኖች ድጋፍ ከማዕከል
የተሰጠ ሲሆን ስለ ቴሌቪዥን ትምህርት ፕሮግራም ትግበራና ስለመሣሪያዎቹ አያያዝና
አጠቃቀም ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ የብሔረሰቦቹ ልጆች የትምህርት ተሣትፎ በተለይም የልጃገረዶች
ተሣትፎ እንዲጨምር ከፍተኛ የሆነ የህዝብ ንቅናቄ ሥራ ተካሂዷል፡፡ የከፍተኛ ትምህርት
ተሣትፏቸው እንዲያድግም ልዩ ድጋፍ ተሰጥቷል፡፡

8
2.2.2.የትምህርት ጥራትና ብቃትን በተመለከተ

ስለ አጠቃላይ ትምህርት (1-12ኛ) ጥራት በተመለከተ የ3ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት


ፕሮግራም አካል የሆነና ዘላቂ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የሚያስችል የአጠቃላይ ትምህርት
ጥራት ማሻሻያ ፓኬጅ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ ሆኗል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የአጠቃላይ ትምህርት
ስታንዳርድ፣ የሣይንስና ሒሣብ ትምህርት እንዲሁም የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ስትራቴጅዎች
ተዘጋጅተዋል፡፡ የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፓኬጅ ስድስት ዋናዋና ፕሮግራሞችን
የሚያካትት ሲሆን እነርሱም የመምህራን ልማት ፕሮግራም ፣የሥርዓተ-ትምህርትና መጻህፍት
ዝግጅት፣ አቅርቦትና ትግበራ እንዲሁም የግምገማና ፈተናዎች ዝግጅትና አስተዳደር ፕሮግራም፣
የሥነ-ዜጋና ሥነ-ምግባር ፕሮግራም፣ የት/ቤቶች ማሻሻያ ፕሮግራም፣ የአመራርና አስተዳደር
ፕሮግራም፣ የኢንፎርሜሽን ኮምዩኒኬሽን ቴክኖሎጅ እና እነኚህን ፕሮግራሞች የማስተባበር፣
ክትትልና ግምገማ ፕሮግራም ሲሆኑ ሁሉም ከጥራት ጋር የተያያዙ ግብዓቶችን፣ ሂደቶችንና
ውጤቶችን ማሻሻል ታሳቢ አድርገው የሚተገበሩ ናቸው።

በመሆኑም በ2001 ዓ.ም መረጃ መሰረት በ1997 ዓ.ም 188,720 የነበረው የ1ኛና 2ኛ ደረጃ
ትምህርት መምህራን ቁጥር በ2001ዓ.ም ወደ 307,927 አድጓል፡፡ለደረጃው የሰለጠኑ መምህራንን
በተመለከተም በአንደኛ ደረጃ ትምህርት የመጀመሪያ ዕርከን በ2001 ዓ.ም ሊደረስበት ከታቀደው
99.8% አንጻር በመማር ላይ ያሉትን ጨምሮ 90.0%፣ በ2ኛው ዕርከን ለ2001 ዓ.ም ከታቀደው
87% አኳያ ደግሞ 71.6% ደርሷል፡፡ እንደዚሁም በ1997 ዓ.ም 41% የነበረው የ2ኛ ደረጃ
ትምህርት የሰለጠኑ መምህራን ለ2001 ዓ.ም ከታቀደው 71% ወደ 75.2% አድጓል፡፡ በ1997
ዓ.ም 66 የነበረው የአንደኛ ደረጃ ትምህርት (1-8) የተማሪ-መምህር ጥምርታ በ2001 ዓ.ም
ሊደረስበት ከታቀደው 1:53 ግብ አንጻር 1:54 ሲሆን በ2ኛ ደረጃ (9-12) ደግሞ በ1997 51
የነበረው ለ2001 ዓ.ም ከተቀመጠው ግብ አንጻር 41 መድረሱ ታውቋል፡፡

የተማሪ-ክፍል ጥምርታን በተመለከተም በአንደኛ ደረጃ ትምህርት(1-8) በ1997 ዓ.ም 69 የነበረው


በ2001 ዓ.ም ሊደረስበት ከታቀደው የ54 ግብ አንጻር 59 ሲሆን በ2ኛ ደረጃ (9-12) ደግሞ 78
የነበረውን በ2001 ዓም ወደ 56.0 ለማሻሻል ታቅዶ ውጤቱ 68 ሆኗል። የተማሪ-መጽሐፍ

9
ጥምርታው በየክልሎች የተለያየ ገጽታ እንዳለው መረጃዎች ያመላከቱ ሲሆን በሁሉም ደረጃ
ጥምርታውን አንድ አንድ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ ነው፡፡

በሌላ በኩል በአንደኛ ደረጃ ትምህርት የማቋረጥና መድገም ሁኔታዎች ገና ተገቢውን መሻሻል
አላሳዩም። በ1997 ዓ.ም የ1ኛ ክፍል የማቋረጥ መጠን 22.4% የነበረ ሲሆን ይህን መጠን በ2001
ዓ.ም ወደ 9.5% ለማውረድ ታቅዶ በተገኘው መረጃ መሰረት ግን 22.9% ሆኖ በመገኘቱ መጠኑ
አልቀነሰም። በተመሣሣይ መልኩ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት(4-8) የተማሪ የመድገም መጠን
በ1997 ዓ.ም 5.30% ከነበረበት በ2001ዓ.ም ወደ 2.93% ለማውረድ ታቅዶ የነበረ ሲሆን መጠኑ
ወደ 7.3% ከፍ ያለበት ሁኔታ ታይቷል። የትምህርት ማቋረጥና መድገም ምክንያቶች አያሌ
ናቸው። የእስካሁኑ ተሞክሮን መነሻ በማድረግ በትምህርት ቤት ደረጃና ከባቢው ምክንያቶቹን
በተጨባጭ መለየት እንደሚያስፈልግ ታምኖበታል።

የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማሻያ ፓኬጅን አተገባበር በተመለከተ በእያንዳንዱ የፓኬጁ


አበይት ጉዳዮች አፈጻጸም ዙሪያ ቀጥሎ የተመለከቱት ዋና ዋና ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡

ሥርዓተ-ትምህርትን በተመለከተ (የኢንፎርሜሽን ኮምዩኒኬሽን ቴክኖሎጅን ጨምሮ) ችሎታንና


ብቃትን መሰረት ያደረገ የሥርዓተ-ትምህርት ለውጥ ተደርጓል፡፡ ይህን መሰረት በማድረግ
ከቅድመ መደበኛ እስከ 12ኛ ክፍል የሥርዓተ ትምህርት ማዕቀፎች፣ የሁሉም ትምህርት ዓይነቶች
የአጥጋቢ ችሎታ መለኪያዎች፣ የፍሰት ሰንጠረዥ፣ መርሓ ትምህርቶች እና የተማሪና መምህር
መጻሕፍት ተዘጋጅተዋል፡፡የሒሣብና የሣይንስ ትምህርቶች ስትራቴጅ ተዘጋጂቶ ተግባራዊ
እየተደረገ ነው፡፡ በተጨማሪም የቅድመ መደበኛ ትምህርት ፖሊሲ፣ ስትራቴጅና መመሪያ
ተዘጋጅተዋል፡፡

ሥርዓተ ትምህርቱን መሰረት አድርገው ከሚሰሩ መደበኛ የትምህርት ተግባራት አንዱ ምዘናና
ፈተና ነው፡፡ ከዚህ አንጻር በቂ የማቴሪያል፣ የገንዘብና የሰው ኃይል በመመደብ በ12ኛ ና
10ኛ ክፍል ደረጃ የሚሰጡ ብሔራዊ ፈተናዎችን በጊዜው በመስጠት፣ በማረምና የተማሪ
ውጤትን በወቅቱ በማሳወቅ፣ ፍትሐዊ የሆነ የተማሪዎች የምደባ ሥርዓትን በመከተልና የከፍተኛ

10
ትምህርት ተቋማት መምረጫ መረጃን በመጠቀም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን በከፍተኛ ትምህርት
ተቋማት ፣ የ10ኛ ክፍል ተማሪዎችን ደግሞ ወደ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና እንዲሁም
ወደ 11ኛ (2ኛ ደረጃ መሰናዶ ትምህርት) በመመደብ ተማሪዎች ትምህርታቸውን በጊዜ
እንዲጀምሩ ተደርጓል፡፡

በተጨማሪም በሦስተኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም ትግበራ ወቅት በ4ኛና 8ኛ ክፍል
ደረጃ ሃገር አቀፍ የትምህርት ቅበላ ጥናት ሁለት ጊዜ በማካሄድ የተገኘውን ውጤት ለባለ
ድርሻ አካላት እንዲደርስ የተደረገ ሲሆን በ10ኛና 12ኛ ክፍልም ለመጀመሪያ ጊዜ ሃገር አቀፍ
የትምህርት ቅበላ ጥናት ተካሂዷል፡፡ ይህን ጥናት ክልሎች በራሳቸው አቅም እንዲያካሂዱ
ከማስቻል አኳያም ለሁለት ክልሎች ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ እንደዚሁም ልዩ ድጋፍ ለሚሹ ክልሎች
የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ፈተናዎች ምዝገባና የግል ተመዝጋቢዎችን ዶክመንት የማጣራት ሥራ
ላይ እገዛ ተደርጓል፡፡ፈተና በማዘጋጀትና በማሳተም እራሳቸውን እንዲችሉ ለክልሎች የአቅም
ግንባታ ስልጠናም ተሰጥቷል፡፡ የፈተና ውጤት መግለጫ መረጃ ለጠፋባቸው ተገልጋዮች የ12ኛ፣
የ10ኛ፣8ኛና 6ኛ ክፍል ድጋሚ የምስክር ወረቀት ተዘጋጅቶ ተሰጥቷል፡፡ የትምህርት መረጃ
ትክክለኛነት እንዲረጋገጥላቸው ለሚጠይቁ የግል አመልካቾች፣ መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ

የትምህርት ተቋማት፣ መስሪያ ቤቶች፣ ኤምባሲዎች፣ ወዘተ አግባብነት ያለው የማረጋገጥ


አገልግሎት በየዓመቱ በተከታታይ ተሰጥቷል፡፡

የመምህራን ልማትን በተመለከተ በ3ኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት መርሓ ግብር ወቅት በርካታ
አበረታች ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ በመሆኑም የመምህራንን ሙያዊና አካዳሚያዊ ብቃት
ለማሻሻል ከፍተኛ አስተዋጽፆ ያለው የመምህራን ልማት መርሓ ግብር ከ1999 ዓ.ም ጀምሮ
በመካሄድ ላይ ሲሆን መርሓ ግብሩን ለመተግበርም የመምህራን ልማት ገዥ መመሪያ ተዘጋጅቶ
እየተሰራበት ይገኛል፡፡ ከላይ እንደተገለጸው የአጠቃላይ ትምህርት መምህራን ብዛትም በ1997
ዓ.ም

ከነበረው 188,720 በ2001 ዓ.ም 307,050 ደርሷል፡፡ ይህም በ1ኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርት የተማሪ-
መምህር ጥምርታውን እንዲሻሻል አድርጎታል፡፡ ከዚህ አንጻር በ1997 ዓ.ም 66 የነበረው የአንደኛ

11
ደረጃ ትምህርት የተማሪ-መምህር ጥምርታ በ2001 ዓ.ም ወደ 57 እንዲሁም በ2ኛ ደረጃ ትምህርት
ደግሞ 51 የነበረው ወደ 43 ተሻሽሏል። የመምህራንና የትምህርት አመራሮች የትምህርትና
ሥልጠና መመሪያም ተዘጋጅቶ ተግባራዊ እየተደረገ ነው፡፡ በመሆኑም ሁሉም የቅድመ-መደበኛ
ትምህርት መምህራን በሰርቲፊኬት፣ የአንደኛ ደረጃ የመጀመሪያ ዕርከን መምህራን በጥምር
የትምህርት መስክ ሥልጠና ዲፕሎማ፣ የአንደኛ ደረጃ 2ኛ ዕርከን መምህራን በአብይ እና ንዑስ
ትምህርት መስክ ሥልጠና ዲፕሎማ፣ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት መምህራን በሙሉ ደግሞ
የመጀመሪያ ዲግሪ እንዲኖራቸው እየተደረገ ሲሆን የትምህርት አመራሮችን ልማት በተመለከተም
የአንደኛ ደረጃ የመጀመሪያ ዕርከን ትምህርት ርዕሣነ መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች በዲፕሎማ፣
የአንደኛ ደረጃ 2ኛ ዕርከን ትምህርት ርዕሣነ መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች በመጀመሪያ ዲግሪ፣
የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ርዕሣነ መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች ደግሞ በማስሬት ዲግሪ የትምህርት
ደረጃቸው እንዲያድግ እየተደረገ ይገኛል።

በቅድመ-አገልግሎት ለመምህርነት ሙያ ስልጠና የሚመለመሉ ዕጩ መምህራን የአመራረጥ


መመሪያም ተዘጋጀቷል፡፡ ስለሆነም በችሎታቸው፣ ለመምህርነት ሙያ ባላቸው ፍላጎትና
ተነሳሽነት እንዲሁም ያላቸው መልካም ሥነ-ምግባር እየተረጋገጠ እንዲመለመሉና የአንደኛ ደረጃ
ትምህርት ዕጩ መምህራን በተግባራዊ ልምምድ የታገዘ ሥልጠና ተከታትለው እንዲያጠናቅቁ
እየተደረገ ነው።የ2ኛ ደረጃ ትምህርት መምህራን ደግሞ በመረጡት የትምህርት መስክ እንደ
አቻዎቻቸው ሁሉ ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ ችሎታቸው፣ ፈቃደኝነታቸውና ለሙያው
ተገቢው ሥነ-ምግባር ያላቸውን በመመልመል በመምህርነት ሙያ እንዲሰለጥኑ ለማድረግ
የሚያስችል ሥርዓት ተዘርግቷል።የመምህራን ትምህርታና ሥልጠና ሥርዓተ- ትምህርትም
አዲሱን/የተሻሻለውን/ የአጠቃላይ ትምህርት ሥርዓተ-ትምህርት የተከተለ እንዲሆን ተደርጓል፡፡

በአገር አቀፍ ደረጃ ከ150,000 በላይ የአንደኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርት መምህራንን ተጠቃሚ
ያደረገ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ማሻሻያ ፕሮግራም ተግባራዊ የተደረገ ሲሆን በመምራን ማሰልጠኛ
ተቋማትም የእንግሊዝኛ ቋንቋ ማሻሻያ ማዕከላት ተቋቁመዋል፡፡ የመምህራን አሰልጣኞችን ብቃት
ለማሳደግም የከፍተኛ ዲፕሎማ መርሓ ግብር ተግባራዊ እየተደረገ ሲሆን የመምህራንን
አካዳሚያዊና ሙያዊ ብቃት እንዲሁም ሙያዊ ሥነ-ምግባር ለማሻሻል የሚረዳ የመምህራን
የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ የሥራ ላይ ስልጠና በገዢ መመሪያውና በተዘጋጀው የስልጠና
ስትራቴጂ መሰረት በትምህርት ቤትና በጉድኝት ማዕከላት ደረጃ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ

12
እየተደረገ ይገኛል፡፡ የመምህራንን የሙያ ፈቃድ አሰጣጥና ዕድሳት አሰራርን ተግባራዊ ለማድረግ
የሚያስችል ሥርዓት ለመዘርጋትም ቅድመ-ሁኔታዎች እየተመቻቹ ነው፡፡

የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ርዕሣነ-መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች ብቃት ለማሳደግ የአመራርና ሥራ


አመራር መርሓ ግብር ተግባራዊ የተደረገ ሲሆን ይህን መርሓ ግብር በይበልጥ አጠናክሮ
ለመቀጠልና እስካሁን ድረስ በትምህርት ዘርፍ በአገር አቀፍ ደረጃ በመንግስትና በልማት አጋሮች
የተደረጉ የአቅም ግንባታ ሥራዎች ያስገኙትን ውጤት ፣አሁን ያሉ የአቅም ክፍተቶችና የስልጠና

ፍላጎቶች እንዲሁም ለወደፊቱ መደረግ የሚገባውን የማስፈጸም አቅም ግንባታ ሥራ የሚያሳይ


የትምህርት ሥራ አመራርና አስተዳደር መርሐ ግብር ጥናትና ዲዛይን አዘጋጅቶ የሚያቀርብ
ዓለም አቀፍ አጥኝ ቡድን ተቀጥሮ በመስራት ላይ ይገኛል። ይህ የሥራ አመራርና አስተዳደር
መርሐ ግብር በትምህርት ዘርፍ ሥራ አመራርና አስተቃቀድ፣ በት/ቤት ዕቅድና ሥራ አመራር
እንዲሁም በትምህርት ሥራ አመራር መረጃ ሥርዓት የማስፈጸም አቅም ግንባታ ሥራ
ለመስራትና በሥራ አመራርና አስተዳደር ዙሪያ ዓይነታዊ ለውጥ በማምጣት የትምህርት ጥራትን
ለማሻሻል ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ታምኖበት የፓኬጁ አንድ ዋና አካል የሆነ መርሐ ግብር
ነው፡፡

በመምህራንና የትምህርት አመራሮች ልማት ፕሮግራም ዙሪያ ከታዩ ተግዳሮቶች መካከል ቀጥሎ
የተመለከቱት በዋነኝነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ የት/ቤት አመራሮችና ተቋማት አሁንም ቢሆን
የማስፈጸም አቅም ክፍተት ይታይባቸዋል፡፡ የመምህርነት ሙያ ተወዳጅነቱ እያደገ መምጣቱን
ብንገነዘብም አሁንም ገና ከፍ ያለ አቅም ያላቸውን ዕጩዎች መሳብ ላይ ገና አልደረሰም።የሴቶች
ተሣትፎም ገና ማደግ አለበት። የታዳጊ ክልሎች ብሔረሰቦች በመምህርነት ያለው ተሳትፎም ገና
ማደግ አለበት። የዕጩ መምህራን ሥልጠና ጥራትና ለሥልጠናው የሚያስፈልግ ግብዓት
በማሟላትና የተከታታይ ሙያዊ ስልጠናዎች አፈጻጸም ማጠናከርን ይጠይቃሉ።

የትምህርት ቤቶች ማሻሻያ ፕሮግራምን በተመለከተ ከ1999 ዓ .ም ጀምሮ የትምህርት ቤቶች


ማሻሻያ ገዥ መመሪያ ተዘጋጅቷል፡፡ በየደረጃው ለሚገኙ አካላትም ስለ ፕሮግራሙ አተገባበር

13
ሥልጠና ተሰጥቶ ወደ ትግበራ ተገብቷል፡፡ ት/ቤቶች ችግሮቻቸውን ለመለየትና የትምህርት
ቤቶቻቸውን የማሻሻያ ፕሮግራም ለመንደፍ የሚያግዛቸው የትምህርት ቤቶች የግምገማ ቅፅ
ተዘጋጅቶ ተግባራዊ ሆኗል፡፡ በመሆኑም በአብዛኞቹ ክልሎች ያሉ 80% ያህል የአንደኛ ደረጃና
60% ያህል 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የሦስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድና ዝርዝር ዓመታዊ ዕቅድ
አዘጋጅተዋል፡፡የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፓኬጁን በብቃት ለመፈፀም እንዲቻል
አንዱ ስልት በፓኬጁ አተገባበር ሂደት የተሻሉ አፈጻጸሞችና የተገኙ ውጤቶችን በመቀመር
ለሌሎች ተቋማት በማስፋፋት መተግበር ነው፡፡ በዚህም መሠረት በትምህርት ሚኒስቴር ደረጃ
ምርጥ ተሞክሮዎች ተቀምረው ለሁሉም ክልሎች ተሠራጭተዋል፡፡ ተጨማሪ ተሞክሮዎችን
ከተመረጡ ትምህርት ቤቶች አሰባስቦ የመቀመርና የማሰራጨት ተግባር እየተከናወነ ሲሆን
ቀሪው ጉዳይ እነዚህን የተቀመሩ ተሞክሮዎች ለሁሉም ክልሎች የማሠራጨት ሥራ ይሆናል፡፡

ከትምህርት ቤቶች ማሻሻያ ርዕሰ ጉዳዮች አንዱ የሆነው ከወላጆች ጋር አብሮ መሥራት ሲሆን
ለተማሪዎች ውጤት የራሱ ድርሻ ስላለው በዚሁ መሰረት ወላጆች በልጆቻቸው ትምህርት ተገቢውን
ተሣትፎ እንዲያደርጉ፣ ልጆቻቸውን እንዲያበረታቱና በትምህርት ቤቶች ላይ የባለቤትነት ስሜት
ኖሯቸው እንዲሳተፉ የሚያስችል ሰነድ ተዘጋጅቷል፡፡ በሁሉም ክልሎች በመገኘት ድጋፍና
ክትትል ተደርጓል፡፡ ይህን መነሻ በማድረግም ለሞዴል የትምህርት ተቋማት፣ የርዕሳነ መምህራን፣
መምህራን፣ ሱፐርቫይዘሮች፣ የተማሪዎች፣ ወላጆችና ማህበረሰብ መለያ ተግባራት ባለድርሻ
አካላትን ባካተተ መልክ ሰነድ ተዘጋጅቶ ለሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ተሰራጭቶ
የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፓኬጅ የህዝብ ንቅናቄ መፍጠሪያ አካል ሆኗል፡፡
በተጨማሪም የትምህርት ቤት ማሻሻያ ፕሮግራሙን በተጨባጭ ለመተግበር የሚረዳ የቅድመ
መደበኛ፣ የአንደኛና 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ስታንደርድ ተዘጋጅቶ ከየክልሎች በተውጣጡ
ባለሙያዎች ዳብሮ ክልሎች ተግባራዊ እንዲያደርጉት ተሰራጭቷል፡፡

ትምህርት ቤቶችን መሰረት ያደረገ አመራርና አደረጃጀት ለማጎልበትና ህብረተሰቡንና


የትምህርት ቤቶችን ሁሉም አካላት በማሳተፍ ውጤታማ፣ ዲሞክራሲያዊና ትምህርት ቤት ተኮር
የሆነ አመራር ለማስፈን የሚያስችል መመሪያ ተዘጋጅቷል፡፡ በመሆኑም በአንዳንድ ት/ቤቶች
የተማሪዎች ዲሲፕሊንና ውጤት የመሻሻል አዝማሚያ አሳይቷል፡፡እንደዚሁም የተማሪዎች
በወቅቱ ትምህርት ቤት ተገኝተው ትምህርታቸውን የመከታተል ሁኔታ ተሻሽሏል፡፡

14
ሥነ- ዜጋና ሥነ- ምግባርን በተመለከተ የየክፍል ደረጃው አጥጋቢ የችሎታ መለኪያ ተዘጋጅቶ
በዚሁ መሠረት መርሀ ትምህርቶችን በማሻሻል፣ በተዘጋጁት አጥጋቢ የችሎታ መለኪያዎችና
በተሻሻሉት መርሀ ትምህርቶች ላይ በመመሥረት ከ5ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ እያገለገሉ
የሚገኙት የመማሪያ ማስተማሪያ መጽሐፍት ጥራታቸውን ጠብቀው እንዲዘጋጁ ተደርገዋል፡፡
የሥነዜጋና ሥነምግባር ትምህርት በሥርዓተ ትምህርቱ ተካቶ መሠጠት ከተጀመረበት ጊዜ
ጀምሮ በትምህርቱ መማር ማስተማር ዙሪያ ያጋጠሙ ችግሮችን በተመለከተ ሁሉንም ክልሎች
የዳሰሰ ጥናት ተደርጎ የጥናቱን ውጤት መሠረት በማድረግ ችግሩን ለማስወገድ ሥልጠና
መስጠት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ለርእሳነ መምህራን፣ ለመምህራን፣ ለወላጅ መምህራን ህብረት፣
ለወረዳ ትምህርትና

ሥልጠና ኃላፊዎች እና ለሱፐርቫይዘሮች ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ለሥነዜጋና ሥነምግባር ትምህርት


አተገባበር በመመሪያነት የሚያገለግል ገዥሰነድ ተዘጋጅቶ፣ በባለሙያዎችና በባለድርሻ አካላት
ተተችቶ ሰነዱ በሥራ ላይ እንዲውል ተደርጓል፡፡

የሥነ-ዜጋና ሥነ-ምግባር ትምህርት እሴቶች በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ላይ እየተሰጡ በሚገኙ


የታሪክና የጂኦግራፊ ትምህርቶች ውስጥ እንዲካተቱ ተደርጓል፡፡የሥነዜጋና ሥነምግባር ትምህርት
መምህራንን አቅም ለመገንባትና በትምህርቱ ላይ ያለውን የተዛባ አመለካከት ለማስተካከል
እንዲያስችል ለመምህራን፣ ለሱፐርቫይዘሮችና ለሌሎችም ባለድርሻ አካላት በፕላዝማ ቴሌቪዥን
የተደገፈ ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እየተሰጠ ለሚገኘው የሥነዜጋና ሥነምግባር ትምህርት ለዲግሪ፣


ለዲፕሎማና ለጋራ ትምህርት የሚያገለግሉ ሥርዓተ ትምህርቶች ከሁሉም ዩኒቨርስቲዎችና
የመምህራን ማሰልጠኛ ተቋማት ከተውጣጡ ባለሙያዎች ጋር በመሆን ተዘጋጅቶ ሥራ ላይ
እንዲውል ተደርጓል፡፡ የሥነ-ዜጋና ሥነ-ምግባር ትምህርትን በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት
ለማስረጽ የሚያስችል መመሪያም ተዘጋጅቷል፡፡

15
በኢትዮጵያ በተለያዩ ወቅቶች የወጡ ሕገመንግሥቶችን አንድ ላይ በማስባሰብና በአንድ ጥራዝ
አዘጋጅቶ በማሳተም በሁሉም ክልሎች እና ለሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች በሚገኙ ትምህርት
ቤቶች እንዲሰራጭ ተደርጓል፡፡ እንደዚሁም በኢትዩጵያ በተለያዩ ወቅቶች የተዘጋጁትን ህገ
መንግሥቶች ዋና ዋና የሆኑ አንቀጾችን የሚያነፃፅር የማብራሪያ ጽሁፍ ተዘጋጅቶ ለፌዴሬሽን
ምክር ቤት ለአስተያየት እንዲቀርብ ተደርጓል፡፡

የኢንፎርሜሽን ኮምዩኒኬሽን ቴክኖሎጅን በተመለከተም ለክልሎች የፕላዝማ ቴሌቪዥን ግዥ


ተከናውኗል፡፡በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት በዘጠኝ የትምህት ዓይነቶች ላይ የተዘጋጁት
የቴሌቪዥን ኘሮግራሞች በ12 የሣተላይት ቴሌቪዥን ቻናሎች እየተሰራጩ ሲሆን፣ ለት/ቤቶችና
ለህብረተሰቡ ትምህርት ሰጪና አዝናኝ የሆኑ ኘሮግራሞችም ከሰኞ እስከ ቅዳሜ
ተሰራጭተዋል፡፡ ይህንኑ የሥርጭት ተግባር በተጠናከረ እና በተሻሻለ ሁኔታ ለማከናወን
የሚያስችል አዲስ በተዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት መሠረት በ12 የትምህርት ዓይነቶች (አማርኛ፣
እንግሊዝኛ፣ ፊዚክስ፣ ኬሚስትሪ፣ ባዮሎጂ፣ ሂሣብ፣ ጂኦግራፊ፣ ታሪክ፣ ሲቪክስ፣ ኢኮኖሚክስ፣
ጀኔራል ቢዝነስና እና ቴክኒካል ድሮዊንግ) የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቴሌቪዥን ኘሮግራሞችን
ለማዘጋጀት እንዲቻል የሣተላይት ቴሌቪዥን ፕሮግራሞች ግምገማ ተካሂዷል፡፡ ይህን መሰረት
በማድረግም የይዘት ስፔስፊኬሽን ተዘጋጅቶ ከሁሉም ክልሎች በተውጣጡ የ2ኛ ደረጃ መምህራን
በማስተቸት እንዲስተካከል ተደርጓል፡፡

ስለ ቴሌቪዥን ትምህርት ፕሮግራሞች አጠቃቀም የአሰልጣኞች ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ በፕላዝማ


ቴሌቪዥን ጥገና እና ኔትዎርኪንግ ላይ ለክልሎች የአቅም ግንባታ ተሰጥቷል፡፡የዲጂታይዜሽን

የሙከራ ፕሮጀክት በባህርዳርና ሀዋሣ መሰናዶ ትምህርት ቤቶች ተሞክሮ ውጤታማ ሆኖ


በመገኘቱ ወደ ሙሉ ዲጂታይዜሽን ትግበራ ለመግባት በማዕከል የዲጂታይዜሽን መሣሪያዎች
ተተክለዋል፡፡

2.3.ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና

16
የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ በመካከለኛ ደረጃ የሚፈልገውን
የሰለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራት ቁልፍ ሚና የሚጫወት ዘርፍ ነው። ከዚህ አንጻር በ3ኛው
የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም ትግበራ ወቅት በዚህ ዘርፍ በተሣትፎና በማስፋፋት ዙሪያ
በርካታ ተግባራት ተከናወነዋል።በመሆኑም በ1997 ዓ.ም 106,336 የነበረው የቴ/ሙ/ትምህርትና
ሥልጠና ተሣትፎ በ2002 ዓ.ም ወደ 312,826 ለማድረስ ታቅዶ 615,913 ያደገ ሲሆን ከዚህ
ውስጥ

ከ50% በላይ የሚሆኑት ሴቶች ናቸው፡፡ የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና


ተቋማትም ወደ 253 ደርሰዋል።

በኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂ ተመርኩዞ ጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማትን በቴክኖሎጂ አቅማቸውን


ከማሳደግ አንፃር በአገር አቀፍ ደረጃ ትኩረት በተሰጣቸው 7 ኢንዱስትሪዎች /ጨርቃጨርቅ፣
ቆዳ፣ አግሮ ፕሮሰሲንግ፣ ግብርና፣ ኮንስትራክሽን፣ ሜታል ማኑፋክቸሪንግና ሆቴል ቱሪዝምና
ቢዝነስ/ የአመራረትና የአሰራር እሴት ሰንሰለት ትንተና በማካሄድ 200 የሚደርሱ የቴክኖሎጂ
ክፍተቶች የተለዩ ሲሆን 137ቱ ቴክኖሎጂዎች ከተለያዩ አማራጮች ተገኝተዋል፡፡ ቴክኖሎጂ
ለመምረጥ በተቀመጡት መስፈርቶች ማለትም ምርታማነት፣ የምርት ጥራት፣ ጉልበት በስፋት
መጠቀምና የዋጋ አዋጭነት በመጠቀም 126 ቴክኖሎጂዎች ተመርጠው የ99ኙ ንድፍና ናሙና
ተዘጋጅቶ የፍተሻ ሥራ ተከናውኗል፡፡ ከነዚህ ውስጥ 44ቱ ቴክኖሎጂዎች ተባዝተው ለተለያዩ
ጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት የተሰራጩ ሲሆን ተጨማሪ 29 የሚሆኑ ቴክኖሎጂዎች ለማሰራጨት
ተጠቃሚዎችን የማብቃት ስራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም አጠቃላይ ሀገር አቀፍ የቴክኖሎጂ ክምችትና ሽግግር ሥራ ውጤቶችን


ሥርዓት ባለው መልክ ለማደራጀትና መረጃውን ለተጠቃሚዎች በቀላሉ ለማድረስ የሚያስችል
የመረጃ ቋት ከክልሎች ጋር በመሆን ተዘጋጅቷል፡፡ የቴክኖሎጂ አቅም የማከማቸትና የማሸጋገር
ዝርዝር የስራ ፍሰትን የያዙ የአሰራር ሥርዓት ሰነዶችን ተመርኩዞ የትምህርትና ሥልጠና
ተቋማትን ስራ የሚያግዙ የማስፈፀሚያ ማንዋሎች ማዘጋጀትን በተመለከተ የእሴት ሰንስለት ማፕ
የማዘጋጀትና ችግሮችን ተንትኖ በቅድም ተከተል ለማስቀመጥ የሚረዳ ማንዋል ተዘጋጅቶ ሥራ
ላይ ውሏል፡፡በቴክኖሎጂ አቅም ክምችትና ሽግግር ሥራ የተገኙ ልምዶችንና ጥሩ ተሞክሮዎችን
በመመርኮዝ ሁሉንም ስራዎች ያካተተ አንድ ወጥ ማኑዋል ለማዘጋጀት ከክልሎች ከተውጣጡ

17
የቴክኖሎጂ ክምችትና ሽግግር የሥራ ሂደት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ጋር በተደረሰ ስምምነት
መሰረት ማንዋሉ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡

በተጨማሪም በክልሎች እየተከናወነ ያለውን የቴክኖሎጂ ሽግግር ሂደት ለመደገፍ ከ8 ክልሎች


ለተውጣጡ የቴክኖሎጂ ሽግግር ሥራ ሂደት ቡድን አባላት ተፈላጊ ቴክኖሎጂዎችን እንዴት
ማፈላለግ፣ መለየት፣ ማቀብና ማሸጋገር እንደሚቻል ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ ቴክኖሎጂዎችን
ከማከማቸት አኳያ በርካታ ቴክኖሎጂዎች ተባዝተው ለትግራይ፣ አማራ፣ ኦሮሚያ፣ ደቡብና አዲስ
አበባ የተሰራጩ ሲሆን በቴክኖሎጂ ክምችትና ሽግግር ስራው ላይ እየተጠቀሙበት መሆኑን
ማረጋገጥ ተችሏል፡፡

የመምህራንን የማሰልጠን ብቃት ለማጎልበት የመምህራንን የክህሎት ክፍተት ከሙያ ደረጃዎች


አንጻር በመለየት የማብቃት ሥራ ተጀምሯል፡፡ የክህሎት ብቃታቸውም በምዘና ተረጋግጧል፡፡
ለቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና መምህራን የማብቃት ማዕቀፍ ተጠናቆ በ A ደረጃ
ለሚገኙ

መምህራን ሥርዓተ ትምህርት ዝግጅት የሚረዳ የሞጅዩል ዝርዝር የተዘጋጀ ሲሆን ነባር የ B
ደረጃ መምህራንን ከማብቃት አንጻርም በአገሪቱ ውስጥ በመንግስት ተቋማት ውስጥ በ B እና C
ደረጃ ካሉ ነባር መምህራን ውስጥ ምዘናውን ወስደው ላለፉ መምህራን ተግባር ተኮር የማስተማር
ሥነ ዘዴ ሥለጠና ተሰጥቷል፡፡

በየጊዜው የሚኖረውን የሥራ ገበያ ፍላጎት መረጃ ለመለየትና ለማወቅ የሚያስችል መነሻ ሰነድ
እና የሰልጣኞች የሙያ ምክርና ድጋፍ እንዲሁም ተቋምን ከኢንዱስትሪው ጋር ለማስተሳሰር
የሚረዳ የሙያ ምክር ድጋፍ አገልግሎት መመሪያ ተዘጋጅተው ለተጠቃሚዎች ተሰራጭተዋል፡፡
በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት የሚሰጠው ስልጠናም የሙያ ደረጃንና የገበያ
ፍላጎትን መሰረት ያደረገ በመሆኑ ሠልጣኞች በሥራው ዓለም ውስጥ ያላቸው ተፈላጊነት
በከፍተኛ ሁኔታ ተሻሽሏል፡፡ በአዲሱ የመካከለኛ ደረጃ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና
ፕሮግራም ሰልጣኞች ከኢንዱስትሪ ጋር የሚተዋወቁበት ስልት በተለይ በመደበኛው ፕሮግራም
ውስጥ ተካቷል፡፡ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ጥራትን ለማሳደግና ምሩቃኑም የሥራ

18
ዕድል እንዲያገኙ ለማድረግ በተቋማቱና በአሰሪ ድርጅቶች ጠንካራና በመተጋገዝ ላይ የተመሰረተ
የትብብር ሥልጠና እና የሥራ ላይ ልምምድ አሰጣጥ ሥርዓት ተዘርግቷል፡፡

የተቋማትን አሰራር ለማሻሻልና ለጥራት ማረጋገጫ የዓለም አቀፍ ደረጃች ድርጅት/ISO 9001
ሥርዓት ብቁ ለማድረግ 10 የሙከራ ተቋማት ተመርጠዋል፡፡ በዚህ መሰረት ከአዲስ አበባ 5 እና
ከክልሎች 5 ተቋማት የተመረጡ ሲሆን የመጀመሪያ ዙር ከአዲስ አበባ የእንጦጦ፣ ተግባረ ዕድ ፣
ዊንጌት፣ ሠላምና ኤስ ኦ ኤስ (SOS) ኮሌጆች የሦስተኛ አካል የዶክዩመንቴሽንና አደረጃጀት
ኦዲት አልፈው ለመጨረሻ ኦዲት ዝግጁ ሆነዋል፡፡ እስካሁን በተከናወነው ሥራ በተለይ የወርክ
ሾፕ አደረጃጀትና አሰራርን ቀልጣፋ በማድረግ ጥሩ ውጤት የታየ ሲሆን በቀጣይነት በጉድኝት
ደረጃ ወደ ተደራጁ ተቋማት የማስፋት ሥራ ይከናወናል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ በአብዛኞቹ ክልሎች የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ፕሮግራም በኤጀንሲ


ደረጃ ራሱን ችሎ የሚሰራበት አደረጃጀት ተዋቀሯል፡፡ የመንግስት የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና
ሥልጠና ተቋማትም በቦርድ የሚመሩበት አደረጃጀት ተፈጥሯል፡፡ የትብብር ስልጠና ስርዓት
ማሻሻልን በተመለከተም ቀደም ሲል ሲሰራበት የነበረውን የትብብር ስልጠና ስርዓት ማንዋል
አዳዲስ ልምዶችና ተሞክሮዎችን በማካተት ለተጠቃሚው የተሻለ መረጃ መስጠት በሚችል መልኩ
ተዘጋጅቶ ለተጠቃሚዎች ተሰራጭቷል፡፡

የትብብር ስልጠና ማስፋፋትን በተመለከተም በሁሉም የሙያ ዓይነቶች የሚሰጡ ስልጠናዎች


በሁሉም የመንግስት የልማት ድርጅቶችና በግሉ ዘርፍ ተሳታፊነት በትብብር ስልጠና ዘዴ እንዲሆን
ከክልሎች ጋር ስምምነት ላይ የተደረሰ ሲሆን ለዚህ የሚያግዝ መመሪያም ለክልል አስፈጻሚዎች
እንዲደርስ ተደርጓል፡፡በዚህ መሰረት በአሁኑ ወቅት 163,509 ሰልጣኞች በመላው አገሪቱ የትብብር
ሥልጠና እየተከታተሉ ሲሆን የኩባንያ ውስጥ ስልጠናን ከሙያ ደረጃ ፣ምዘናና ቴክኖሎጅ ሽግግር
ጋር በማስተሳሰር ኢንዱስትሪውን በብቁ የሰው ኃይልና ቴክኖሎጅ ለመመገብ የሚያስችል ፍሬም
ወርክ ተቀርጿል፡፡የኩባንያ ውስጥ ሥልጠናን በፍጥነት በኩባንያዎች ውስጥ ለማስረፅ በላቀ ደረጃ
በመተግበር ላይ ያሉ ኩባንያዎችን ሌሎች ኩባንያዎች እንዲጎበኙ በማድረግና ደከም ያለ አፈጻጸም
ላሳዩ ኩባንያዎች የልምድ ልውውጥ እንዲያደርጉ በማገዝ የኩባንያ ሥርዓቱ በፍጥነት እንዲዘረጋ

19
ማድረግ ተችሏል፡፡ የኩባንያ ውስጥ ሥልጠና በተጀመረባቸው ኩባንያዎችም አመርቂ ውጤቶች
እየተመዘገቡ መሆኑም ታውቋል፡፡

በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ደረጃ የሚሰጡ ሥልጠናዎች ከመነሻቸው የየኢንዱስትሪ


ዘርፉን የሰለጠነ የሰው ኃይል ፍላጎት ያማከሉ መሆን እንዳለባቸው ካለው አጠቃላይ ግንዛቤ
በመነሳት በ18 ዘርፎች 249 በሥራ ገበያ ላይ ተፈላጊ የሆኑ ሙያዎች የተለዩ ሲሆን ከእነዚህ
ውስጥ 232ቱ የሙያ ደረጃ ተዘጋጅቶላቸዋል፡፡ በተለይም በኮንስትራክሽን፣ በኤሌክትሪሲቲና
ኤሌክትሮኒክስ፣ በሜታል ማኑፋክቸሪንግ፣ በአውቶሞቲቭ፣ በቴክስታይልና ጋርሜንት፣ በውሃ
ሥራዎች፣ በግብርናና ሆቴልና ቱሪዝም ዘርፎች ለተለዩ ሙያዎች በሙሉ በተለያዩ የሙያ
ደረጃዎች ሊቀጠሩና በራሳቸው በጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ተደራጅተው ሥራ
የሚፈጥሩ በርካታ

ሙያተኞችን ማፍራት እንዲቻል ለየሙያዎቹ ከዝቅተኛው ጀምሮ ደረጃዎች ተለይተው የሙያ


ደረጃ ሰነዶች ተዘጋጅተውላቸዋል፡፡

ቀደም ሲል የነበሩ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ፕሮግራሞችን ተከታትለውም ይሁን


በተላያዩ መንገዶች ሰልጥነውና በየመስኩ ተሰማርተው የሚገኙትን እንደዚሁም በቀጣይ የቴክኒክና
ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ሥርዓታችን በሚያበረታታቸው የተለያዩ አካሄዶች ሰልጥነው ወይም
ራሳቸውን አብቅተው በዕጩነት የሚቀርቡ ዜጎችን ከሙያ ደረጃዎችና ከኢንዱስትሪው ፍላጎት
አኳያ መመዘን እንዲቻል ከሁሉም ዘርፎች ቅድሚያ ለተሰጣቸው 84 ሙያዎች የምዘና
መሳሪያዎች ተዘጋጅተው በአገሪቱ በሚገኙ 6 የልህቀት ማዕከላት በሙያዎቹ ላይ የብቃት ምዘና
መስጠት ተጀምሯል፡፡ የብቃት ምዘና መስጠት ከተጀመረ ወዲህ በ6ቱም የልህቀት ማዕከላት
በኩል ለ39,510 ዕጩዎች የብቃት ምዘና ተሰጥቶ 9,643 (24.41%) ዕጩዎች ብቁ መሆናቸው
ተረጋግጧል፡፡

ሆኖም ግን በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና አተገባበር ወቅት የተከሰቱ ችግሮች ነበሩ፡፡


ከእነሱም በዋኛነት የሚጠቀሱት ቀጥሎ የተመለከቱት ናቸው፡፡

20
 በሕብረተሰቡ፣ በባለድርሻ አካላት፣ ባስፈፃሚና በፈፃሚ አካላት እና በሰልጣኞች ዘንድ
ስለውጤት ተኮር ቴ/ሙ/ት/ስ/ ስርዓት ያለው ግንዛቤ አናሳ መሆንና ሰልጣኞች የቴ/ሙ/ት/ስ
ፕሮግራምን ወደ ከፍተኛ ትምህርት መሸጋገሪያ አድርገው ማሰባቸው፡፡
 የቴ/ሙ/ት/ሥ/ ተቋማት ቴክኖሎጂን ለማሸጋገርና ለማስረጽ ብቁ ሆነው አለመገኘት፣
 ህጋዊ መሠረት ያለውና ባለድርሻ አካላትን ያሣተፈ አደረጃጀት አለመኖር፣
 የሥራ ፍላጎት ጥናት ሥርዓት አለመኖር፣
 በየደረጃው ያሉ ባለሙያዎች ብቃት ስርዓቱን በአግባቡ ለመተግበር ያለማስቻሉ፣
 ተከታታይ የሆነ ክትትልና ግምገማ የማካሄድ ብቃት አለመኖር፣
 የተሟሉ የቴ/ሙ/ት/ስ/ስትራቴጂ ማስፈፀሚያ ሰነዶች አለመኖር፣
 የተሟላ የመረጃ አያያዝ፣ አደረጃጀትና ልውውጥ ስርዓት አለመኖር፣

2.4. ከፍተኛ ትምህርት

ከፍተኛ ትምህርት በ1997 ዓ.ም ከነበረበት ሁኔታ አበረታች ዕድገት አሳይቷል፡፡ በመንግስት
ተቋማት ብቻ በ1997 ዓ.ም ከነበረው 78,232 ጠቅላላ የመጀመሪያ ዲግሪ መደበኛ ተማሪ ብዛት
በ2002 ወደ 185,788 (በ137.5 መቶኛ) አድጓል፡፡ በ1997 ዓ.ም 24% የነበረው የሴት ተማሪዎች
ድርሻ በ2002 ዓ.ም 29% ሆኗል፡፡ የድሕረ ምረቃ ትምህርት ተሳትፎም በ1997 ከነበረው 3,604
ተማሪዎች በ2001 ወደ 9,761 አድጓል፡፡ የሴት ተማሪዎች ድርሻ ከ9% ወደ 11.3% አድጓል፡፡
በዚያው ዘመን የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ብዛት በ13 ጨምሮ 22 ደርሷል፡፡

የዓመታዊ ቅበላን ዕድገት በሚመለከት በመርሃ ግብሩ ሰነድ ሰፍሮ የነበረው ዕቅድ 150,000
ተማሪዎች አካባቢ ነበር፡፡ ይህ መጠን ከመጀመሪያው ስህተት እንደነበረበት በመታወቁ 110,000
እንዲሆን ተስተካክሏል፡፡ ይህም ቢሆን ግን ሊደረስበት አልተቻለም፡፡ በዕቅዱ ዘመን የተደረሰበት
ከፍተኛው ዓመታዊ የቅበላ መጠን 79,500 ተማሪዎች ብቻ ነበር፡፡ ይህ መጠን የ2001 ዓመታዊ
ቅበላ ሲሆን በ2002 ወደ 77,182 ዝቅ ብሏል፡፡ ለተስተካከለው ዕቅድ አለመሳካት ዋነኛው
ምክንያት የህንጻ ግንባታዎች በታሰበው አለመፋጠን ነበር፡፡

21
በመርሃ ግብሩ ዘመን የከፍተኛ ትምህርት ስርዓቱን ወደ ዓይነታዊ ለውጥ ሊያደርሱ የሚችሉ
በርካታ መሰረታዊ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ተልዕኮአቸውን ለማሳካት
የሚያስችላቸውን የማስፈጸም ዓቅም ለመገንባት በተቋማዊ ለውጥ ሂደት ውስጥ ገብተዋል፡፡ ይህን
ሂደት የሚያጠናክርና የውጤቱን ዘላቂነት የሚያስጠብቅ ሕጋዊ ማዕቀፍም ተዘርግቷል፡፡
በመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የቅድመ ምረቃ ትምህርት ተሳትፎ ዕድገት በሳይንስና ቴክኖሎጂ
መሪነት (በ70:30) እንዲቃኝ አቅጣጫ ተቀምጦ በ2002 ዓ.ም የሳይንስና ቴክኖሎጂ ድርሻ
ከጠቅላላው 185,788 ተማሪዎች 55.7% ሲሆን ከዓመታዊ ቅበላው (77,182) ደግሞ 58% ላይ
ደርሷል፡፡ በ2002 በኤንጅኔሪንግና ኮምፕዩቲንግ በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በመማር ላይ ያሉ
ተማሪዎች 31,373 ነው።

መረጋገጥ የሚገባው የተሳትፎ ዕድገት እንደተጠበቀ ሆኖ የኤንጅኔሪንግና የኮምፕዩቲንግ መስኮች


ምድብ የተቀመጠለት የ40% ግብ ላይ ለመድረስ በነባር ዩኒቨርስቲዎች የማስፋፋት ግንባታን
ማከናወንና በትምህርት መሣሪያዎች የማደረጀት እንዲሁም አዲስ ዩኒቨርስቲዎችን መገንባትና
ማደራጀት ይጠይቃል፡፡ የተጠቀሰውን ተልዕኮ ለማሳካት የሚያስችል የአመራርና የአስተዳደር
ስርዓት የመገንባትና የቅድመ ምረቃ ትምህርትን አግባብነት በኢንዱስትሪ ልማት የሰው ኃይል
ፍላጎትና የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲመራ የማድረግ መልካም እርምጃዎች ጋር በማስተሳሰር
የትምህርት ጥራቱን ለማረጋገጥ በሚያስችሉ የስርዓተ ትምህርትና የመምህራን ልማት ቁልፍ
ጎዳዮች ላይ የተቀመጡ አቅጣጫዎችና የተከናወኑ ስራዎች አሉ፡፡ የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ
ዕድገትን በሰው ኃይልና በቴክኖሎጂ ሽግግር ለማሳለጥ የኤንጂኔሪንግ እና የተፈጥሮ ሳይንስ
ስርዓተ ትምህርቶች ለውጥ ተጠናቆ ወደ ትግበራ ተገብቷል፡፡ አዳማ ዩኒቨርስቲን የቴክኒካል
ዩኒቨርስቲ ሆኖ እንዲገነባና የዘጠኝ ዩኒቨርስቲዎች የቴክኖሎጂ ፋክልቲዎችን የአስተዳደር ነጻነት
ባላቸው የቴክኖሎጂ ኢንስቲቱዩቶች እንዲደራጁ እርምጃዎች ተወስደዋል፡፡

የአገሪቱ ልማትና ዕድገት አስተማማኝ የፍትህ ስርዓትን መገንባት ስለሚጠይቅ የሕግ ስርዓተ
ትምህርቱ በዚሁ ቅኝት ተለውጦ መተግበር ተጀምሯል፡፡ የቢዝነስና ኤኮኖሚክስ፣ የህክምናና ጤና
ሳይንስ፣ የግብርናና የማሕበራዊ ሳይንስ ስርዓተ ትምህርቶችም ተለውጠው ወደ ትግበራ
ተሸጋግረዋል፡፡ የህክምና አዲስ ስርዓተ ትምህርት ቀረጻም የማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ ነው፡፡

22
የተለወጡት ስርዓተ ትምህርቶች ተግባሪ ብቁ መምህራንን ይጠይቃሉ፡፡ በዚህ ረገድም
የመምህራን ልማት ስትራቴጂን በመቅረጽ የተለያዩ ጥረቶች ተደርገዋል፡፡ በመሆኑም በ1997
ዓ.ም 4,847 የነበረው የዩኒቨርስቲ መምህራን ብዛት በ2002 ዓ.ም ወደ 11,238 አድጓል፡፡ ከነዚህ
መምህራን መካከል ገና የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው 5,706 (50.8%)፣ በሁለተኛ ዲግሪ ደረጃ
4,528 (40.3%) እና ፒኤች ዲና አቻ ዲግሪ ያላቸው 1,004 (8.9%) ናቸው፡፡ የድሕረ ምረቃ
ትምህርት በመከታተል ላይ የሚገኙት 5,826 (4,681 የ2ኛ ዲግሪ እና1,145 የፒ ኤች ዲ ዲግሪ)
ሲታከልበት የዩኒቨርሲቲ መምህራን ብዛት 17,064 ይሆናል፡፡ ይህ ገና በመጀመሪያ ዲግሪ ክልል
ያሉትን መምህራን ምጣኔን ወደ 33.4% ዝቅ ያደርገዋል፡፡ ይሁንና በማስተማር ስራ ላይ ያሉትን
ብቻ ግምት ውስጥ በማስገባት በ2002 ዓ.ም የተማሪ/መምህር ጥምርታ ባጠቃላይ 1፡16 ሲሆን
ሁለተኛ ዲግሪና ከዚያ በላይ ካላቸው መምህራን አንጻር ግን 1፡34 ነው፡፡

የትምህርት አግባብነትና ጥራት የትምህርት መርጃ መሣሪያዎችንም ይጠይቃሉ፡፡ ነባር


ዩኒቨርስቲዎች የካፒታል በጀትን ለማስተዳደር በተሰጣቸው ውክልና መሠረት በጀታቸውን
በራሳቸው እያስተዳደሩ ሲሆን ለአዲሶቹ ዩኒቨርስቲዎች ግን ከማዕከል ይቀርብላቸዋል፡፡
ይሁንና በነባሮቹም ይሁን በአዲሶቹ አቅርቦቱ ፍላጎትን ያለማርካትና ያለውን አቅርቦት ደግሞ
በሚገባ ያለመጠቀም ክፍተቶች ገና ያልተወገዱ ችግሮች ናቸው፡፡

የትምህርት አግባብነትና ጥራትን ለማሳካት የተደራጀ ሙያዊ ሃገራዊ አመራርን ለማረጋገጥ ሲባል
የስትራቴጂ ማዕከልና የትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጄንሲ ተቋቁመዋል፡፡ እነዚህ አካላት
በዋናነት ኃላፊነታቸውን ለመወጣት የሚያስችላቸውን የማስፈጸም ዓቅም በመገንባት ሂደት ላይ
የሚገኙ ናቸው፡፡ ባጠቃላይ የመንግስቱ ዘርፍ የከፍተኛ ትምህርት የትምህርት አግባብነትና
ጥራትን ባማከለ የለውጥና ዕድገት አቅጣጫ ላይ ይገኛል፡፡ ይሁንና አሁንም ዓይነታዊ ለውጥን
ለማረጋገጥ በሚያስችለው የለውጥ ሂደት ውስጥ እንጂ ማረጋገጥ ካለበት ዓይነታዊ ለውጥ ላይ ገና
አልደረሰም፡፡ የግሉን ዘርፍ በተመሳሳይ አቅጣጫ እንዲመራ የማብቃቱ ተግባር ባጠቃላይ ገና
መሰራት ያለበት ትልቅ ጉዳይ ነው ለማለት ይቻላል፡፡

23
በአብዛኞቹ ዩኒቨርሲቲዎች የሥርዓተ ጾታ ጽ/ቤት ተቋቁሞ ለሴት ተማሪዎች የተለያዩ የድጋፍ
ሥራዎች ተከናውነዋል፡፡ በተለይም ሴት ተማሪዎችን ውጤታማ ለማድረግና ትምህርታቸውን
አቋርጠው እንዳይወጡ በዩኒቨርሲቲዎች የተለያዩ የማብቃት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
በዩኒቨርሲቲዎች በመከናወን ላይ ከሚገኙ የማብቃት ሥራዎች መካከል ነባር ሴት ተማሪዎች
አዲስ ለሚገቡ ሴት ተማሪዎች ልምዳቸውን የሚያካፍሉበት ሥርዓት ተዘርግቷል፡፡ በአንዳንድ
ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሴት ተማሪዎች ማህበር ተቋቁመዋል፡፡ ከየክፍሉ የተመረጡ ምርጥ
አምስት ሴት ተማሪዎች ለክፍል ጓደኞቻቸው ደጋፊ ትምህርት መስጠት ጀምረዋል፣ ውጤታማ
ለሆኑ ሴት ተማሪዎች ሽልማት የመሰጠትና ማበረታታት ሥርዓት ተጀምሯል፡፡ ከፍተኛ ልምድ
ያላቸውን ሴት ምሁራንና ኃላፊዎች በመጋበዝ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሴትነታቸው
የሚያጋጥሟቸውን አሉታዊ ተፅእኖዎች ተቋቁመው ውጤታማ እንዲሆኑ በተከታታይ የኦረንቴሽን
ኘሮግራም ተካሂዷል፡፡ዩኒቨርሲቲዎች ሴት ተማሪዎችን በትምህርታቸው እኩል ተወዳዳሪ
ለማድረግ የጀመሩዋቸው መልካም ጅምሮችን አጠናክረው እንሚቀጥሉባቸው እናምናለን። በሴት
ተማሪዎች የሚደርሱ ማንኛውም ዓይነት ተፅዕኖ፣ ትንኮሳና ጥቃትን ለማስወገድ በመዘርጋት ላይ
ያሉትን ሥርዓትም አጠናከረው ይቀጥሉበታል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተቋማዊ ለውጥን በተመለከተም ዩኒቨርስቲዎችን በቦርዶች


የማደራጀትና በተለይ ለውጡን በመምራት ላይ ከኃላፊነታቸው ጋር የማስተዋወቅ ስራ
ተሰርቷል፡፡ ዝርዝር የመከታተያ ነጥቦችም እንዲደርሳቸው ተደርጓል፡፡ የዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች
ሹመት በቦርዶች ተደግፎ እየቀረበ በወሳኝነት ተፈጽሟል፡፡ የምክትል ፕሬዚዳንቶች ሹመትም
በቦርዶች በወሳኝነት ተፈጽሟል፡፡ የአስተዳደር ካውንስሎች ተደራጅተው ስራ ጀምረዋል፡፡
ሰኔቱን ዳግም የማደራጀቱ ጉዳይ የማቋቋሚያ ደንቦችን መጽደቅ ስለሚጠይቅ ገና ነው፡፡ በነባር
ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ የቴክኖሎጂ ኢኒስቲቱዩቶችን የማደራጀቱ ስራ በመከናወን ላይ ነው፡፡
እስካሁን ለአምስት ኢኒስቲቱዩቶች የሚመጥኑ የውጭ ምሁራን ለመመልመልና ለመመደብ
ተችሏል፡፡ የራሳቸው ቦርዶች የማደራጀቱም ሥራ ተፈጽሟል፡፡የዩኒቨርስቲዎች ማቋቋሚያ
ደንቦችን ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ለማቅረብ በሚቻልበት ደረጃ በሁለት ናሙናዎች መልክ
ተዘጋጅተዋል፡፡ ዓዋጁን በሚመለከት ደግሞ ለዩኒቨርስቲ ቦርዶችና ከፍተኛ መሪዎች በተለያዩ
የጥልቀት ደረጃዎች ማስተዋወቅ ተደርጓል፡፡ በዚህ አጠቃላይ ዕይታ ክልል የከፍተኛ ትምህርት
ዘርፍ የሚከተሉት ድክመቶች ያሉበት መሆኑን መገንዘብ ይገባል።

24
 የከፍተኛ ትምህርት አመራርና አስተዳደር ስርዓቱ በሚፈለገው የብቃት ደረጃ ላይ
አልደረሰም፡፡
 የመምህራን ልማትን ሁሉም ገጽታዎች አስተሳስሮ መፈጸም ገና ስርዓት አልሆነም፡፡
 ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት መምህራን የትምህርት ደረጃ ቢያንስ 2ኛ ዲግሪ የሆነበት ደረጃ
ገና አልደረሰም
 የኢንዱስትሪውን ፍላጎት መሰረት ያደረገ የቴክኖሎጅ ሽግግር ሥርዓት አለመኖር፣ በተለይ
በሳይንስና ቴክኖሎጂ መስኮች የንዱስትሪ ልማት የሰው ኃይልና የቴክኖሎጂ ሽግግር ፍልጎትን
ለመመለስ የሚያስችል የማስፈጸም ዓቅም ግንባታው ገና ሂደት ላይ ያለ ነው፡፡ መረጋገጥ
የሚገባው የተሳትፎ ደረጃም ገና አልተደረሰበትም፡፡
 በ70፡30 የመስኮች ምጣኔ ክልል የቴክኖሎጂ ድርሻ ከሆነው 40% ግብ ላይ ገና አልደረሰም።
 የቅድመ ምረቃና ድሕረ ምረቃ የቅበላ ዓቅሞች ገና በግንባታ ሂደት ላይ ናቸው፡፡
 የሴት ተማሪዎች ድርሻ በቅድመ ምረቃውና በድሕረ ምረቃው ፕሮግራም ገና አነስተኛ ነው።
 የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ገቢን የማመንጨትና የማሳደግ ዓቅም ገና ውሱን ነው፡፡
 የግሉ ዘርፍ የትምህርት አግባብነትና ጥራት ገና ፈር እንዲይዝ አልተደረገም፡፡

2.5.የባለ ብዙ ዘርፍ ጉዳዮች

ባለፉት አምስት ዓመታት በሁሉም የትምህርት ዘርፍ እንቅስቃሴዎች ተካተው ሲሰራባቸው


የነበሩ የባለ ብዙ ዘርፍ ጉዳዮች ሥርዓተፆታ፣ ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ፣ ልዩፍላጐትና አካቶ ትምህርት፣
የህብረተሰብ ተሳትፎናያልተማከለ የትምህርት ሥርዓትና የአቅም ግንባታ ፕሮግራም ናቸው ፡፡

ሥርዓተ -ፆታን በተመለከተ በወንድና ሴት ተማሪዎች መካከል ያለውን የትምህርት ተሣትፎ


ልዩነት ለማጥበብ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ ብሔራዊ የልጃ ገረዶች
ትምህርት ስትራቴጅና ሥርዓተ-ፆታን በሁሉም ተግባራት የማካተት መመሪያ
ተዘጋጅተዋል፡፡ከዚህ ጋር በተያያዘ በርካታ የሥርዓተ-ፆታ ግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችና
ሥልጠናዎች ተካሂደዋል፡፡ በየትምህርት ተቋማቱ የሥርዓተ -ፆታ ማዕከላትና ክበባት
ተቋቁመዋል፡፡ ሥርዓተ-ትምህርቱና የሥልጠና ሂደቱ ሥርዓተ- ፆታን ያካተተ እንዲሆን
ተደርጓል፡፡ የተለያዩ የሥርዓተ-ፆታ ጥሰቶችን ለመከታተልና ለመከላከል ከየሴክተር መስሪያ
ቤቶች ከተቋቋመው የጋራ ኮሚቴ ጋር በመሆን በሥርዓተ ፆታ ጉዳዮች ላይ የመከታተልና
የመከላከል ሥራዎች ተሰርተዋል፡፡ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሚገቡ ሴት ተማሪዎች ልዩ

25
ድጋፍ በመሰጠቱ በከፍተኛ ተቋማት የሴቶች ተሣትፎ እያደገ መጥቷል፡፡ በመሆኑም በተለይ
በመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት በሴቶችና በወንዶች መካከል የነበረው የጥቅል ተሣትፎ ልዩነት
እየጠበበ መጥቷል። በመሆኑም በመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ተሣትፎ ዙሪያ የሥርዓተ- ፆታ
ልዩነት ምጣኔው በ1997 ከነበረበት የወንዶች 0.87 እና የሴቶች 0.69 በ2001 ዓ.ም ወደ 0.93
እና 0.92 መጥቷል፡፡

ይሁን እንጅ በተለይ በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስለጠና እና በከፍተኛ ትምህርት፣


በማስተማርና በትምህርት አመራር ደረጃ የሴቶች ተሣትፎ አነስተኛ በመሆኑ በዚህ ረገድ
ልዩነቱን ለማጥበብ ከፍተኛ ሥራ መስራት ይጠይቃል፡፡

ኤች አይ ቪ ኤድስን መከላከልን በተመለከተ በሦስተኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም


ከ3ኛ ክፍል ጀምሮ ባሉት ሥርዓተ ትምህርቶች ኤች አይ ቪ ኤድስን በማካተት ሰለ ኤች አይቪ
ምንነት፣ስለመተላለፊያው ሁኔታና እንዴት መከላከል እንደሚቻል ለህጻናትና ወጣቶች ትምህርትና
ግንዛቤ በመሰጠት ላይ ነው፡፡ በቅርቡ በተለወጠውና ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ በሚተገበረው ሥርዓተ
ትምህርት ደግሞ ኤች አይ ቪ ኤድስ ከ1ኛ ክፍል ጀምሮ ባሉት ሥርዓተ ትምህርቶች ውስጥ
ተካቷል፡፡ እንደዚሁም ጉዳዩ በመምህራን ትምህርት ሥርዓተ ትምህርት የተካተተ ሲሆን ጉዳዩን
የሚከታተሉ ተጠሪዎች በፌዴራል ትምህርት ሚኒስቴር፣ በክልልና ወረዳ ደረጃ ተመድበው
በመስራት ላይ ይገኛሉ፡፡ በሁሉም የትምህርት ተቋማትና የትምህርት ዕርከኖች ደረጃ የፀረ-ኤች
አይቪ /ኤድስ ክበባት ተዋቀረዋል፡፡ የትምህርት ዘርፍ በኤች አይቪ /ኤድስ መከላከል ላይ
የሚያካሂደውን ሥራ ይበልጥ ውጤታማ ለማድርግም የትምህርት ዘርፍ የኤች አይ ቪ/ኤድስ
ፖሊሲና ስትራቴጅ ተዘጋጅቶ ፀድቋል፡፡

በሦስተኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም ትምህርትን ለሁሉም ማዳረስን ታሳቢ በማድረግ
ለልዩ ፍላጐትና አካቶ ትምህርት ትኩረት ተሰጥቶ ሲሰራ ቆይቷል፡፡ በመሆኑም የልዩ ፍላጎት
ትምህርት ስትራቴጅ ተዘጋጅቶ በመተግበር ላይ ነው፡፡ የልዩ ፍላጎት ትምህርት የመተዋወቂያ
ኮርስ በሁሉም የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡ በአራት
ዩኒቨርሲቲዎች

26
በመጀመሪያ ዲግሪ ደረጃ፣በአምስት የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች በዲፕሎማ እንዲሁም በአዲስ
አበባ ዩኒቨርሲቲ በማስትሬት ዲግሪ ደረጃ የልዩ ትምህርትና አካቶ ትምህርት ፕሮግራም
በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡ እንደዚሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሥነ ልሣን የትምህርት ክፍል
የምልክት ቋንቋ በመጀመሪያ ዲግሪ ደረጃ በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡ በዘጠኝ ክልሎችና ሁለቱ
የከተማ አስተዳደሮች ለትምህርት ቢሮ የትምህርት ባለሙያዎችና ለሁሉም የወረዳ ትምህርት
ጽ/ቤት ኃላፊዎች በልዩ ድጋፍና አካቶ ትምህርት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ አውደ ጥናት
ተካሂዷል፡፡

ልዩ ድጋፍ ለሚሹ ክልሎችም ተጨማሪ ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡ በተፈጠረው ግንዛቤ የተነሣ ከ1999
በፊት ከ33,000 በታች የነበረው የአካል ጉዳተኛ ህጻናት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ተሣትፎ
በ2001 ዓ ም በተገኘው መረጃ መሰረት ወደ 41,300 ደርሷል፡፡ የልዩ ፍላጎትና አካቶ ትምህርት
በዋና ዋና የትምህርት ዓይነቶች ሥርዓተ ትምህርት የተካተተ ሲሆን ልዩ ፍላጎት ያላቸውን
ተማሪዎች እንደየፍላጎታቸው ለመርዳት የሚያስችሉ በሃገር አቀፍ ደረጃ የተመረጡ ሦስት ልዩና
ስድስት ክላስተር ትምህርት ቤቶች በድጋፍ መስጫ ማዕከልነት ተዋቅረዋል፡፡ ለልዩ ፍላጎትና
አካቶ ትምህርት ተንቀሳቃሽ መምህራን ተቀጥረው በመሥራት ላይ ናቸው፡፡ በተጨማሪም የዋና
ዋና ትምህርቶች ሥርዓተ ትምህርት የአካል ጉዳተኛ ሕጻናት ትምህርትን እንዲያካትት የተደረገ
ሲሆን
ለአካል ጉዳተኛ ህጻናት የተለየ ሥርዓተ ትምህርት ለማዘጋጀት የሚያስችል መመሪያም
እየተዘጋጀ ነው።

ከህብረተሰብ ተሳትፎ አኳያ ያለፈው የትምህርት ዘርፍ መርሐ ግብር ትግበራ ከፍተኛ
የማህበረሰብ ንቅናቄና ተሣትፎ የታየበት ነበር፡፡ በመሆኑም በርካታ የአንደኛና 2ኛ ደረጃ
ትምህርት ቤቶች በማህበረሰብ ተሣትፎ በመሰራታቸው የተማሪ ጥቅልና ንጥር ተሳትፎ
ጨምሯል፡፡ ይህንም ከላይ ከቀረበው ሪፖርት መመልከት ይቻላል፡፡ የማህበረሰቡ ተሣትፎ
ጉልበቱን፣ ገንዘቡን፣ ማቴሪያልና ዕውቀቱን በመለገስ ብቻ ሳይሆን ልጆቹን በእድሚያቸው ወደ
ት/ቤት በመላክና በመርዳት ጭምር የተንጸባረቀ እንደነበር የተለያዩ ዓመታዊ ሪፖርቶች
ያመለክታሉ፡፡ ለምሣሌ በኦሮሚያ ክልል ሁሉም የመጀመሪያ ደረጃና ሦስት- አራተኛ ያህሉ የ2ኛ
ደረጃ ት/ቤቶች የተገነቡት ፣የታደሱትና የተስፋፉት በማህበረሰብ ተሣትፎ እንደነበር ተውቋል፡፡
በአማራ ክልልም በማህበረሰቡና በክልሉ መንግስት መካካል የትምህርት ቤት ግንባታ ወጭ

27
መጋራት ሥርዓት ተዘርግቷል፡፡ በሌሎችም ክልሎች በተመሣሣይ ሁኔታ የማህበረሰብ ተሳትፎ
በከፍተኛ ደረጃ በመቀጠሉና ት/ቤቶች ወደ ሕጻናት መኖሪያ አካባቢዎች በመቅረባቸው ሕጻናት
ወደ ት/ቤት ለመሄድ የሚፈጅባቸው ጊዜና ድካም በተወሰነ ደረጃ ቀንሷል፡፡ ይህም በተለይ የሴት
ሕጻናትን የትምህርት ተሣትፎ አሳድጋል፡፡

ይሁን እንጅ ማህበረሰቡ በትምህርት ላይ ሊኖረው የሚገባውን ያህል ተሣትፎ እንዲያደርግ


የሚያስችሉ ደንቦችና መመሪያዎች ላይ ተጨማሪ የግንዛቤ ሥራ አጠናክሮ መስራት
እንደሚያስፈልግ፣ በማህበረ-ሰብ ተሣትፎ የሚገነቡ ት/ቤቶችን የጥራት ደረጃ ማስጠበቅ
እንደሚገባና በተሣትፎው ላይ ወቅታዊና ተጨባጭ መረጃ መሰብሰብና ማደራጀት
እንደሚያስፈልግ ታውቋል።

ያልተማከለ የትምህርት ሥርዓትና የአቅም ግንባታ ፕሮግራምን በተመለከተ በትምህርት ዋና


ዋና ጉዳዮች ላይ የማህበረ ሰቡን ውሣኔ ሰጭነትና ተሣታፊነት በማሳደግ ረገድ ያልተማከለ
የትምህርት ሥርዓት ባለፈው የትምህርት ዘርፍ ልማት ፕሮግራም አተገባበር ላይ ከፍተኛ ድርሻ
ነበረው፡፡ በመሆኑም የትምህርት የማቴሪል፣ የፋይናንስና የሰው፣ ኃይል አመራርና አስተዳደር
ባልተማከለ ሥርዓት በወረዳ ደረጃ እንዲመራ ለወረዳዎች ብሎም ለቀበሌና ት/ቤቶች ከፍተኛ
የአመራርና አስተዳደር ነጻነት ተሰጥቷል፡፡ መምህራንን፣ ርዕሣነ መምህራንንና ድጋፍ ሰጭ
ሠራተኞችን ከመቅጠርና ከመምራት አንስቶ በጀትን የማስተዳደር ሥልጣንና ኃላፊነት
ለታችኛው የስልጣን እርከን በመሰጠቱ የትምህርት አገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱን ቀልጣፋ
አድርጎታል፡ የማህበረሰቡን ተሳትፎና የባለቤትነት ስሜትም አሳድጎታል፣ ይህንንም ያልተማከለ
ሥርዓት ተግባራዊ ለማድረግ እስከ ት/ቤቶች ድረስ በርካታ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች
ተሰጥተዋል፡፡ ሆኖም ግን የትምህርት ዘርፉን የልማት ፐሮግራሞች በተገቢው ሁኔታ ከማስፈጸም
አንጻር በተለይ

በወረዳ ደረጃ ከፍተኛ የሆነ የአቅም ክፍተት በአንድ በኩል የሰለጠነ የሰው ኃይል መልቀቅና
እጥረት ደግሞ በሌላ በኩል የሚታዩ ትላልቅ ችግሮች እንደሚታዩ ለመረዳት ተችሏል።

ማጠቃለያ

28
በሦስተኛው የትምህርት ዘርፍ ልማት መርሐ ግብር የትግበራ ወቅት በአጠቃላይ ውጤታማና
አበረታች ሥራዎች ቢከናወኑም አሁንም በቀጣይ መሰራት ያለባቸው ስራዎች አሉ። በመሆኑም
የአራተኛውን የትምህርት ዘርፍ ልማት መርሐ ግብር ቀልጣፋና ውጤታማ በሆነ መልኩ
ለመተግበር የትምህርት ጥራትና አግባብነት፣ የትምህርት ፍትሃዊነትና ተደራሽነት እንዲሁም
በትምህርት ዘርፉ በየደረጃው የመልካም አሰተዳደር ሙሉ በሙሉ ማስፈን ዋና ዋና የትኩረት
መስኮቻችን ይሆናሉ፡፡ ይሀንንም ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ለቀጣዩ አምስት ዓመት
ጠንክሮ መስራትን ይጠይቀናል።

ክፍል ሁለት

የትምህርትና ስልጠና ዘርፍ


የቀጣዩ አምስት ዓመታት (2003-2007) የዕድገትና የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ
የትኩረት አቅጣጫዎች

የትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ልማት ዕቅድ ዝግጅት መሰረት ያደረገው ሃገራችንን መካከለኛ ገቢ
ካላቸው ሀገሮች ተርታ ለማሰለፍ የተቀመጠውን ራዕይ ሲሆን ከዚሁ ጋር በተያያዘ ራዕዩን
ለማሳካት ኢንዱስትሪው (በተለይም በማደግ ላይ ያለው የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ) በየደረጃው
የሚፈልገውን የሰለጠነ የሰው ኃይል ማፍራት ነው። ዕቅዱ ያለፈውን የትምህርት ዘርፍ ልማት
ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መነሻ በማድረግ የአጠቃላይ ትምህርትን፣ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና
ስልጠናንና የከፍተኛ ትምህርትን በተመጋጋቢነት በማስፋፋት በሚቀጥሉት አምስት አመታት
ጥራቱንና ፍትሃዊነቱን የጠበቀ ትምህርትና ስልጠና ለማረጋገጥ የተዘጋጀ ነው። በዚህም መሰረት
የልማት ዕቅዱ የትኩረት አቅጣጫዎች፣ ዓላማዎች፣ ዋናዋና ግቦችና የማስፈጸሚያ ስልቶች
ፖሊሲውን መሰረት በማድረግ እንደሚከተለው በየዘርፉ ቀርበዋል፡፡

1. የትኩረት አቅጣጫዎች

29
1.1. አጠቃላይ ትምህርት

የመሰረታዊ ትምህርት አገልግሎትን ለሁሉም ለማዳረስና በትምህርት መስክ የተቀመጡ


የሚሊኒየም የልማት ግቦችን ለማሳካት የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥልና ግቦቹም
እንዲሣኩ ይደረጋል። በትምህርት መስክ የሚሊኒየም የልማት ግቦችን ከማሳካት አኳያ ወጪ
ቆጣቢና በህብረተሰቡ ሙሉ ተሳትፎ መደበኛና መደበኛ ባልሆነ ስልት የቅድመ መደበኛ
ትምህርት ይስፋፋል። ከዚህ አኳያ የመንግስት ሚና ፖሊሲውን መሰረት በማድረግ ሁኔታዎችን
ማመቻቸት፣ የትምህርት ጥራትን ማስጠበቅና ለዚህም የሚረዱ ግብዓቶችንና ስታንዳርዶችን
ማውጣት እንደዚሁም መከታተል ይሆናል።

መደበኛ ትምህርትን በሚመለከት ጥራቱን የጠበቀ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ለሁሉም


ይዳረሳል። በዚህ መሠረት የተጀመረው ፍትሐዊነትና ተደራሽነት ያለው መደበኛ ትምህርት
ተጠናክሮ እንዲቀጥል ይደረጋል፡፡ በሴትና ወንድ ተማሪዎች መካከል ያለው የትምህርት ተሣትፎ
ልዩነት ጠፍቶ የሥርዓተ-ፆታ እኩልነት ይረጋገጣል። ልዩ የትምህርት ፍላጎት ያላቸው
የህብረተሰብ ክፍሎች በትምህርት ስርዓቱ ውስጥ ተጠቃሚ እንዲሆኑ የተቀመጠው ስትራቴጂ
ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ይደረጋል፡፡ ይህ ሁሉ እንደ ተጠበቀ ሆኖ ዋናው ትኩረት በሁሉም ደረጃ
የትምህርት ጥራትና አግባብነትን ማሻሻልና ማስጠበቅ ይሆናል። ይህንኑ ለማሳካትም የትምህርት
ጥራት ማሻሻያ ፓኬጁን ሙሉ በሙሉ በመተግበር በፓኬጁ ሊመጣ የሚችል በተማሪዎች ውጤት
ማለትም ዕውቀት፣ ክህሎትና ባህርይ ላይ መሰረታዊ ለውጥ ይረጋገጣል፡፡ ይህም በትምህርት
ዘርፉና ሌሎች አግባብነት ያላቸው አካላት ቀጣይነት ያለው ወቅታዊ ክትትሎችና የትምህርት
ቅበላ ጥናቶች ቁጥጥር በማድረግና ውጤቱን የእንቅስቃሴው ግብዓት በማድረግ የሚጠናከር
ይሆናል፡፡ በዚህ ሂደት ፓኬጁን በማዳበር የላቀ የትምህርት ጥራትን የምናረጋግጥበት ሁኔታ
ይፈጠራል።

በሌላም በኩል ተግባር ተኮር የሆነ የጎልማሶች ትምህርት በሁሉም አካባቢዎች ሊሳተፉ ለሚችሉ
ሁሉ እንዲዳረስ ይደረጋል። ከዚህ አንጻር ተግባር ተኮር የጎልማሶች ትምህርት ስትራቴጂን
በመተግበር ሁሉም ዕድሜያቸው ከ15-60 የሆኑ ሁሉ በዚህ ፕሮግራም ይታቀፋሉ።

1.2. የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና

30
የተቀየሰውን የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ስትራቴጂ በተሟላ አኳኋን ተግባራዊ በማድረግ
ጥራቱን የጠበቀና ውጤታማ ስርዓት ይረጋገጣል። በዚህ መሰረት የመንግሥት ኢንቨስትመንትን
በማጠናከርና የትብብር ስልጠናን በተሟላ መልኩ ተግባራዊ በማድረግ የሀገራችን የሰለጠነ የሰው
ሀይል ፍላጎት በአጥጋቢ ሁኔታ እንዲሟላ ይደረጋል። የሙያ ምደባ፣ የሙያ ደረጃ ዝግጅት፣
የብቃት ማረጋገጫ፣ የሙያ ምዘና የምስክር ወረቀት አሰጣጥና የስርዓተ ትምህርት ቀረጻ ስርዓትን
በመፍጠርና በማጠናከር ስርዓቱ ቀጣይ የቴክኖሎጂ ሽግግር መሣሪያ ሆኖ ያገለግላል። የቴክኒክና
ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማቱም ለአነስተኛና ጥቃቅን ተቋሞች የቴክኖሎጂ ማዕከላት ሆነው
እንዲያገለግሉ ይደረጋል።

የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማት (የመንግስትም የግልም) ከትምህርት ጥራትና


አግባብነት አኳያ የሚጠበቅባቸውን የብቃት ደረጃ እንዲያረጋግጡ ተገቢው ክትትልና ድጋፍ
ይደረጋል። የክትትልና ድጋፉ መነሻም በኢኮኖሚው ፍላጎት መሰረት ስልጠና መከናወኑ፣
አሰልጣኞች የአሰልጣኖች ብቃት ማዕቀፍ መስፈርቶችን ያሟሉ መሆናቸው፣ ሰልጣኞች
ለተፈላጊው ሙያ ብቁና ስራ ፈጣሪ መሆናቸው በአጠቃላይ ተቋማቱ በተቀመጠው ስትራቴጂ
በትክክል እየሰሩ መሆኑን፣ ይህ ባልሆነበት ሁኔታ አስፈላጊው የማስተካከያ ርምጃ የሚወሰድበት
ሥርዓት ተጠናክሮ ይቀጥላል።

1.3. ከፍተኛ ትምህርት

በቀጣዩ አምስት አመታት የከፍተኛ ትምህርት ዋነኛ ትኩረት የትምህርት ጥራትና አግባብነትን
ማረጋገጥ ነው፡፡ በዚሀም መሰረት የዩኒቨርሲቲ የአመራርና የአስተዳደር ስርዓት ይደረጋል፣
የስትራቴጂ ማዕከልና የትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጄንሲ ሚናቸውን እንዲወጡ
ይጠናከራል፡፡ የቴክኖሎጂ ኢንስቲቱዩቶችም የማስፈጸም ዓቅም ይገነባል። በሌላ በኩል
ሁለንተናዊ የዩኒቨርሲቲ መምህራን ልማትን በመተግበር ብቁ የመምህራን አቅርቦት
ይረጋገጣል።የተለወጡ ስርዓተ ትምህርቶች ትግበራን በትምህርቱ አሰጣጥ፣ በተማሪዎች ምዘናና
ፈተና እና በውጤት አሰጣጥ ገጽታዎቹ ተጠናክሮ ይፈጸማል፡፡

በከፍተኛ ትምህርት ደረጃ የሚሰጠው ትምህርት ኢኮኖሚው በሚፈልገው የሰው ሃይል ብዛት፣
ዓይነትና ጥራት ይቃኛል፡፡ በዚህ መሰረት በቅድመ ምረቃና ድሕረ ምረቃ የሚሰጠው ትምህርት
የተሳትፎ ዕድገቱ በመስኮች ምጣኔ መሠረትና ፍትሃዊነትን በጠበቀ ሁኔታ እንዲሳካ ይደረጋል።
ዩኒቨርስቲዎች ገቢን የማመንጨትና የማሳደግ ዓቅማቸውን እንዲገነቡና ለትምህርቱ አግባብነትና

31
ጥራት ማጠናከሪያ እንዲያውሉት የሚያስችል ስራ ይሰራል፡፡ (ጥራትና አግባብነትበሚል
ቢስተካከለ)

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የጥናትና ምርምር ስርዓት የቴክኖሎጂ ሽግግርን ማዕከል ያደረገ
እንዲሆንና በተለይ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ተቋማትና የትምህርት ክፍሎች ተቋማዊ የማስፈጸም
አቅማቸውን በመገንባት በቴክኖሎጂ ሽግግር የኢኮኖሚ ልማቱን እንዲደግፉ ይደረጋል። ባጠቃላይ
የከፍተኛ ትምህርት የጥናትና ምርምር ስርዓት ለአገሪቱ ልማትና ዕድገት ባላቸው ፋይዳ
ይመራሉ።

የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የትምህርት ጥራትና አግባብነትን ማረጋግጥ ዋነኛ የትኩረት
አቅጣጫ ይሆናል፡፡ተቋማቱም የከፍተኛ ትምህርት አዋጁንና ስትራቴጂውን መሰረት አድርገው
መደራጀታቸው ይረጋገጣል፡፡ ይህም ተገቢው ክትትል እየተደረገበትና የድጋፍና የማስተካከያ
እርምጃዎች በመውሰድ እድገቱ በትምህርት አግባብነትና ጥራት መረጋገጥ ላይ እንዲመሰረት
ይደረጋል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሁሉም ተማሪዎች ምቹ እንዲሆኑና በተለይ ደግሞ ለሴት


ተማሪዎችና ልዩ ትኩረትና ድጋፍ ለሚሹ ተገቢውን ትኩረትና ድጋፍ በመስጠት ውጤታማ
እንዲሆኑ ይደረጋል።

2. የትምህርት ስልጠና ዘርፍ ዓላማዎች

2.1. የትምህርት ዘርፉ አጠቃላይ ዓላማ

የትምህርት ዘርፉን የማስፈጸም አቅም በመገንባት፣ የብቃት መለኪያዎችን በማውጣትና


በማስጠበቅ፣ የትምህርት ጥራትና አግባብነትን፣ ፍትሃዊነትና ተደራሽነትን በየደረጃው ያረጋገጠ፣
ውጤታማ የትምህርትና ስልጠና ስርዓትን ዕውን ማድረግ።

2.2. የአጠቃላይ ትምህርት ዓላማ

 የቅድመ መደበኛ ትምህርት ተሳትፎን ማሳደግና አግባብነትና ጥራቱን ማስጠበቅ፤

32
 ጥራቱን የጠበቀ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ዕድሜያቸው ለደረሰ ሁሉ ማዳረስ፤

 ገበያው የሚፈልገውን በመካከለኛና ከፍተኛ ደረጃ የሰለጠነ የሰው ኃይል ለማፍራት ጥራት
ያለው የ2ኛ ደረጃ ትምህርትን ተሳትፎ ማሳደግ፤

 በሴቶችና ወንዶች፤ በክልሎች፣ በገጠርና በከተማ መካከል ያለውን የትምህርት ተሣትፎ


ልዩነት በማጥበብ ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ፤

 ተግባር ተኮር የጎልማሶች ትምህርትን በማስፋፋት የሃገሪቱን ሁለንተናዊ የልማት እንቅስቃሴ


ማጠናከር፤

2.3. የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ዓላማ

 ውጤትን ማዕከል ያደረገ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠናን በገጠርና በከተማ በጥራትና


በፍትሀዊነት ከስራ ገበያው ፍላጎት ጋር በማጣጣም ማቅረብና ተቋማት የቴክኖሎጂ ሽግግር
ማዕከል የሚሆኑበትን አሰራር ማጠናከር፤

 የቴክኖሎጂ አቅም በማከማቸት፣ በመገንባትና በማሸጋገር ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንዱስትሪ


ተጨባጭ አቅም መሆን፤

 በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ለሁሉም ተዋናዮችና ባለድርሻዎች የተቀናጀ የአሰራር


ማዕቀፍ መፍጠርና በተለይም ኢንዱስትሪው የሙያ ደረጃ ምደባንና የብቃት ምዘናን
በባለቤትነት እንዲመራውና በስልጠናው ላይ በሰፊው እንዲሳተፍ ማድረግ፤

 ለሴቶችና ለወጣቶች ልዩ ትኩረት በመስጠትና የሙያ ክህሎት ባለቤት በማድረግ የኢኮኖሚ


ተጠቃሚነታቸውን ማረጋገጥ፤

2.4. የከፍተኛ ትምህርት ዓላማ

 ውጤታማነትን ያማከለ የአመራር፣ የአስተዳደርና የአፈጻጸም እንዲሁም ለአብነታዊ አፈጻጸም


እውቅና የሚሰጠና የሚያተጋ ተቋማዊ ስርዓትን መገንባት፤

 በከፍተኛ ባለሙያ ደረጃ ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ልማት በተለይም ለማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ


እድገት የሚፈለጉ ብቁ ዜጎችን ማፍራት፤

 የሳይንስና ቴክኖሎጂ መሪነትን ያረጋገጠ የከፍተኛ ትምህርት የተሳትፎ ዕድገትን ማሳካት፤

33
 ከኢኮኖሚው ፍላጎት አኳያ የከፍተኛ ትምህርትን ጥራትና አግባብነትን ያማከሉ ተቋማትን
ማረጋገጥ፤

 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሴት ተማሪዎችን ተወዳዳሪና ውጤታማ እንዲሆኑ በማስቻል


የተሳትፎ ፍትሃዊነትን በትምህርት ስኬትም እንዲገለጽ ማብቃት፤

3. ግቦች

የተጠቀሱትን የትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ዓላማዎች ለማሳካት በትምህርት ተደራሽነት/ተሣትፎ


(access) ፣ በትምህርት ፍትሐዊነት (equity) እና ጥራትና አግባብነት እንዲሁም ብቃት (quality,
relevance & efficiency) አመላካቾች ላይ የተመሰረቱ ቀጥሎ የተመለከቱት ዋናዋና ግቦች
ተጥለዋል።

3.1. አጠቃላይ ትምህርት

የትምህርት ጥራትና አግባብነት


 በየእርከኑ የሚገኙ ሁሉም ትምህርት ቤቶችና የጉድኝት ማዕከላት በስታንዳርዱ መሠረት
ደረጃውን ባሟሉ ርዕሳነ መምህራንና ሱፐርቫይዘሮች እንዲመሩ በማድረግ የትምህርቱን ጥራት
የሚያረጋግጥ የአመራር ስርዓት መገንባት፤
 ሁሉም የየእርከኑን ትምህርት ያጠናቀቁ ተማሪዎች ከየእርከኑ የሚጠበቀውን የስነ ዜጋና የስነ
ምግባር ባህሪያትን ያረጋገጡ ይሆናሉ፤
 በሁሉም የክፍል ደረጃ በያንዳንዱ የትምህርት ዓይነት ቢያንስ 50% አማካይ ውጤት
የሚያገኙ ተማሪዎችን ወደ 90% ማሳደግ፤
 በሁሉም እርከን የሚገኙ መምህራን ጥራት ያለው የመማር ማስተማር ሂደትን ተግባራዊ
ለማድረግ የሚያስችላቸውን የትምህርት የብቃት ደረጃ ያላቸው ይሆናሉ፤
 የሁሉም ዕርከን ስርዓተ ትምህርቶች የየትምህርቱን ተፈላጊውን የትምህርት ጥራትና
አግባብነትን ያረጋገጡ እንዲሆኑ ማድረግ፤

የትምህርት ፍትሐዊነትና ተደራሽነት

 የቅድመ መደበኛ ትምህርት አሁን ካለበት 4.2% ወደ 20% ማሳደግ፤

34
 የአንደኛ ደረጃ (ከ1ኛ-8ኛ ክፍሎች) ንጥር ተሳትፎን አሁን ካለበት 87.9% ወደ 97% ማድረስ፤
 የሴቶችንና የወንዶችን የትምህርት ተሳትፎ ምጣኔ ልዩነትን ለማጥፋት የአንደኛ ደረጃ
ትምህርት አሁን ካለበት 0.93 ወደ 1 ማድረስ፤
 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት የመጀመሪያ ሣይክል (9-10) ጥቅል ተሳትፎን አሁን ካለበት 41%
ወደ 62% ማድረስ፤
 ተግባር ተኮር የጎልማሶች ትምህርትን አሁን ካለበት 36% ወደ 95% ማሳደግ፤

3.2. ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና

 ኢንዱስትሪው የሚፈልገውን የብቃት ደረጃ በምዘና አረጋግጦ ወደ Mራ የተሰማራ የቴክኒክና


ሙያ ባለሙያ ብዛት አሁን ካለው 23% ወደ በ60% ማሳደግ፤

 በተቀመጠው ስትራቴጂ መሰረት ሃብት መፍጠር ያስቻሉ ቴክኖሎጂዎችን 3000 ማድረስ፤

 በቴክኒክና ሙያ ሰልጥኖ ከሚወጣው ባለሙያ 90% የሚሆነውን ከስራ ጋር በማስተሳሰር ወደ


ስራ እንዲገባ ማድረግ፤

 በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ለመሳተፍ ፍላጎትና ዝግጁነት ያለውንና ለየደረጃው የሚጠየቀውን


መስፈርት ማሟላት የሚችለውን ዜጋ ሁሉ ለማሳተፍ የሚያስችል አቅም መፍጠር፤

3.3. ከፍተኛ ትምህርት

 ዩኒቨርሲቲዎች የትምሀርት ጥራትና አግባብነትን ያማከለ ተልዕኮአቸውን ብበቃት የሚያራምድ


የአመራርና አስተዳደር ስርዓትን የገነቡና የትምህርት አግባብነትና ጥራት እና የልማት
ማነቆዎችን መፍታት ላይ ባተኮረ ጥናትና ምርምር እንዲሁም በህብረተሰብ አገልግሎት
ዓይነታዊ ዕድገት ያረጋገጡ ይሆናሉ፤
 የዩኒቨርሲቲ መምህራን ብዛት አስከ 23000 ይደርሳል፣ ከነዚህም መካከል ሁለተኛ ዲግሪ
ያላቸው የብቁ መምህራን ብዛት 75% ሶስተኛ ዲግሪ ያላቸው በመማር ላይ ያሉና ያጠናቀቁ

35
መምህራን ብዛት 25% በማሳደግ አጠቃላይ የመምህር/ተማሪ ጥምርታ 1፡20 እንዲሆን
ማድረግ፤
 አጠቃላይ ተሳትፎን (Enrollment) በ70፡30 ቀመርና በሳይንስና ቴክኖሎጂ መሪነት ላይ
በመመስረት በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም የተማሪ ብዛት አሁን ካለበት 185,788 ወደ 467,000
ማሳደግ፤
 በድሕረ ምረቃ ፕሮግራም የሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ ዓመታዊ የቅበላ ዓቅምን በተለይ
ሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ ማኔጅመንት እና ኢኮኖሚክስን ማዕከል በማድረግ ወደ 20,100 ማሳደግ፤
 በቅድመ ምረቃው ፕሮግራም የሴቶች ተሳትፎ ድርሻ አሁን ካለው 29% ወደ 40% ማሳደግ፣
በድሕረ ምረቃ ፕሮግራምም ድርሻቸውን ከ10% ወደ 25% ማድረስ፤
 በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም የመመረቅ ስኬት የወንዶች 95% የሴቶች 90% ባጠቃላይ 93%
ማድረስ፤
 በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በቤተ መጻህፍትና በቤተ ሙከራ አገልግሎት ደረጃውን
የጠበቀ አቅርቦትን ማረጋገጥ፤

4. የማስፈጸሚያ ስልቶች

4.1. አጠቃላይ ትምህርት

የትምህርት ጥራትና ተገቢነት


 የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማረጋገጫ ፓኬጅ በሚጠይቀው ስታንደርድ መሠረት
ለመተግበር በየደረጃው ያለውን ፈጻሚና አስፈጻሚ አካላትን አቅም ማሳደግ፤
 በፓኬጁ ስታንደርድ መሠረት በላቀ ሁኔታ የተተገበሩ ምርጥ ተሞክሮዎችን በመለየትና
በመቀመር በሁሉም ትምህርት ቤቶች ደረጃ እንደ አግባቡ ተግባራዊ እንዲሆን ማድረግ፤
 ሁሉንም ሚዲያዎች በመጠቀም መላው ሕብረተሰቡ በትምህርት ጥራት ላይ በተነቃቃና
ተነሳሽነት ባለው መልኩ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያደርግ የሚያስችል የአህዝቦት ሥራ
በተቀናጀ መልኩ በየደረጃው መሥራት፤
 የትምህርት ሥርዓቱን አመራርና አደረጃጀት በመሠረታዊ የሥራ ሂደት ለውጥ ትግበራና
ምዘና በማቀናጀትና በቂ ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ዘመናዊ፣ ቀልጣፋ፣ ወጪ ቆጣቢና
ውጤታማ እንዲሆን ማስቻል፤

36
 ሁሉም ትምህርት ቤቶች በትምህርት ቤት ማሻሻያ ገዥ መመሪያና መጽሐፈ ዕድ መሠረት
የትምህርት ቤት መሻሻያ ስትራቴጂክ እቅድ በማዘጋጀት መተግበራቸውን ማረጋገጥ፤
 ህብረተሰቡ ትምህርት ቤቶችን በሙሉ ባለቤትነት መምራት የሚችልበት ደረጃ ላይ ማድረስ፤
 በመምህራን ልማት ገዢ መመሪያ መሠረት የቅድመ እና ድህረ ሥልጠና ትምህርት
እንዲሁም ተከታታይ የሙያ ማሻሻያ ሥልጠና በመስጠት መምህራን የየትምህርት እርከኑ
የሚጠይቀውን የትምህርት ደረጃ እንዲያሟሉ በበቂ ዝግጅት መተግበር፤
 ድጋፍ የሚሹ አካባቢዎችና የታዳጊ ክልሎች ነባር ብሔረሰብ ልጆች በመምህርነት ሙያ
እንዲሣተፉና ቁጥራቸውም እንዲጨምር በማድረግ በአካባቢው የመምህራን እጥረትን
በመቅረፍ የትምህርት ጥራትን ማሻሻል፤
 የእንግሊዝኛ ቋንቋ መምህራንን በተዘጋጀው ስታንደርድና የመመዘኛ መሣሪያ መሠረት
የክህሎት ክፍተቶችን በመለየት ለደረጃው ብቁ የሚያደርጋቸው ስልጠና መሰጠት፤
 በአፍ መፍቻ ቋንቋ ለሚያስተምሩ መምህራን የቋንቋ ክህሎት ማሻሻያ ሥልጠና መስጠት
 የሒሳብና የሳይንስ ትምህርቶችን ተማሪዎች በፍላጎትና በአግባቡ እንዲማሩ ለማስቻል
የተዘጋጀውን ስትራቴጂ ሙሉ በሙሉ በመተግበር ተማሪዎች በትምህርት ዓይነቶቹ የተሻለ
ውጤት እንዲያገኙና በቀጣይ የትምህርት ደረጃም በፍላጎት እንዲማሩት ማድረግ፤
 የመጀመሪያና የሁለተኛ ደረጃ ሥርዓተ ትምህርትና በመምህራን ትምህርት ተቋማት
የትምህርትና ሥልጠና ሥርዓተ ትምህርት የተሳሰሩና የሚናበቡ እንዲሆኑ መስራት፤
 በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የ2ኛ ደረጃን የፕላዝማ ፕሮግራም ሥርጭት
ዲጂታይዝድ ማድረግና ለብሮድካስት በሚመች መልኩ አዘጋጅቶ በመተግበር የትምህርት
ጥራትን ማረጋገጥ፤
 ፓኬጁን በውጤታማነት ለመፈፀም እንዲቻል ሦስቱን መስተጋብሮች ማለትም አመለካከት፣
ክህሎትና ግብዓትን መሠረት ያደረገ ቼክሊስት በማዘጋጀት፣ የክትትልና ድጋፍ ሥርዓት
በመዘርጋት፣ በተማሪዎች ተጨባጭ ውጤት ላይ ያመጣውን ለውጥ መገምገምና የፓኬጁን
ብቃት በተሻለ ይዘትና ደረጃ በማሳደግ ተግባራዊ ማድረግ፤

የትምህርት ፍትሐዊነትና ተደራሽነት

 የቅድመ መደበኛ ትምህርት የፖሊሲ ማዕቀፉንና ስትራቴጅውን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ


ማድረግ፤

37
 ህዝቡን ባሳተፈ መልኩ የት/ቤቶችን ቅርበትና የርስ በርስ ትስስር ማጠናከርና በት/ቤቶችና
በተማሪዎች መኖሪያ አካባቢ መካከል ያለውን ርቀት መቀነስ፤
 በሥራ ላይ የሚገኙትን የአማራጭ መሰረታዊ ትምህርት ማዕከላት ወደ መደበኛ የ1ኛ ደረጃ
ት/ቤቶች ማሳደግና አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ብቻ በተለይ ልዩ ድጋፍ በሚሹ ክልሎች ተጨማሪ
ማዕከላትን መክፈትና ማጠናከር፤
 በአማራጭ መሰረታዊ ትምህርት ማዕከላትና በመደበኛ ትምህርት ቤቶች መካከል ጠንካራ
የሽግግርና ትስስር ሥርዓት መመስረት፤
 ባለ ብዙ ደረጃ (Multigrade) ክፍሎችን በመክፈት ቁጥራቸው አነስተኛ ለሆኑ ማህበረሰቦች
ህጻናት የትምህርት ተሣትፎን ማሳደግ፤
 የአርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር ህጻናት ትምህርት ተሣትፎን ለማሳደግ በወጣው
ስትራቴጂ መሠረት አማራጭ የአገልግልት አሰጣጥ ስልቶችን ማለትም የምገባ ፕሮግራም፣
የተንቀሳቃሽ ት/ቤቶች አገልግሎት ወዘተ. ማስፋፋት፤
 የተጋላጭ ህጻናትና የታዳጊ ክልሎች ነባር ብሔረሰቦች ህጻናትን የትምህርት ተሣትፎ
ለማሳደግ ልዩ ድጋፍ መስጠት፤
 የአጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርትን ለማሳደግ የሚያስችል የማስፋፋት ስራ በስፋት መስራት፣
እንዲሁም ኢኮኖሚው የሚፈልገውን የሰለጠነ የሰው ኃይል ፍላጎትና የከፍተኛ ትምህርት
ተቋማት የቅበላ አቅም መሰረት ያደረገ የ2ኛ ደረጃ የመሰናዶ ትምህርትን ማስፋፋት፤
 የግል ባለሃብቶች፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችና ማህበረሰቡ የ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶችን
እንዲከፍቱ ማበረታታት፣ ድጋፍ መስጠትና ስታንዳርዱን የጠበቀ ለመሆኑ ተገቢውን ክትትል
ማድረግ፤
 የ2ኛ ደረጃ መሰናዶ ትምህርት(11-12) የዋጋ መጋራት ሥርዓትን አጠናክሮ መቀጠል፤
 ተግባር ተኮር የጎልማሶች ትምህርትን በስትራትጂው፣ በስርዓተ ትምህርቱና በመመሪያው
መሰረት መተግበር፤
 በየደረጃው ያለ የፖለቲካና የትምህርት ዘርፉ አመራር የተግባር ተኮር ጎልማሶች ትምህርትን
የወቅቱ ቁልፍ የልማትና የፖለቲካ ጉዳይ መሆኑን በውል ማስገንዘብና በእውቀት ላይ
ተመሥርቶ በባለቤትነት እንዲመሩት ማስቻል፤
 ባለድርሻ አካላት የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነትና ድርሻ እንዲወጡና በተቀናጀና ቀጣይነት ባለው
መልኩ እንዲንቀሳቀሱ በማድረግ መርሀ-ግብሩ ውጤታማ እንዲሆን የበኩላቸውን አስተዋጽኦ
እንዲያበረክቱ መድረግ፤

38
 የአመቻቾችን ሥልጠና በብቃት ለመስጠት በመምህራን ትምህርት ኮሌጆች ተቋማዊ ሥርዓት
ዘርግቶ መተግበር፤
 የልዩ ፍላጎት ትምህርት ስትራቴጂን ተግባራዊ በማድረግ የትምህርቱን ተደራሸነት ማረጋገጥ፤
 በየደረጃው የተጠናከረ የክትትልና ድጋፍ ሥርዓት በመዘርጋት በወቅቱ አስፈላጊውን
የማስተካከያ እርምጃዎችን መውሰድ፤

ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና

 ለብቃት ማረጋገጡ ስራ በትላልቅ የልማት ፕሮግራሞቻችንና በተወሰነ ደረጃ በዘርፉ ያለውን


የውጭ ሙያተኛ በብቃት መዛኝነት መጠቀምና በዚህ ሁኔታ ብቃቱ የተረጋገጠው
የኢንዱስትሪ ሙያተኛ በቀጣይነት የስርዓቱን ቁልፍ ተግባራት እንዲመራ ማድረግ፤
 የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ስርዓቱ በተቻለ መጠን የአለም አቀፍ ሙያተኛ
አቅምን፤ በዋነኛነት ግን የሀገሪቱን ኢንዱስትሪ ሙያተኛ አቅም መጠቀም በሚችልበት መልኩ
በመቃኘት በቅድሚያ ከኢንዱስትሪ ሙያተኛው ውስጥ የተሻለ ብቃት ያለውን በብቃት ምዘና
መለየት፤
 በምዘና ብቁ ሆነውን በኢንዱስትሪው ውስጥ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ያለ ባለሙያን በመጠቀም
የሙያ ምደባ ስራን በስፋት በማከናወንናሌላውን የኢንዱስትሪ ባለሞያ እንዲመዝን በማድረግ
ብቁ የሆኑትን ብቻ በመዛኝነት ስራ ላይ እንዲሳተፉ ማድረግ፤
 የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ዕድገት አቅጣጫ በመከተልና የገበያ ፍላጎትን መሰረት በማድረግ
ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ሙያዎች መለየትና ስልጠና የሚዳረስበትን ሁኔታ ማመቻቸት፣
የትብብር ስልጠና በስፋት የሚዳረስበትትን ሁኔታ ማመቻቸት፣እየሰለጠነ ከሚወጣውም ብቃቱ
ከፍተኛ የሆነውን ሰልጣኝ ወደ ተቋም አሰልጣኝነት መመልመል፤
 በተከታታይ በሚደረግ ምልመላና ቀድሞ የተመለመለውንና ልምድ እያገኘ ያለውን ወደ
ከፍተኛ አሰልጣኝና የአመራር ዕርከን እንዲያድግ በማድረግ የበቃው አሰልጣኝና መምህር
በተለያዩ መንገዶች የሚሰጡ ስልጠናዎችንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ተግባራትን እንዲመራ
ማድረግ፤
 የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ስርዓቱን የማይቀለበስበት ደረጃ ላይ ለማድረስ
የኢንዱስትሪውን ሙያተኛ በየጊዜው ራሱን በአለም አቀፍ ደረጃ ማስተካከል እንዲችል
ማድረግ፣ ኢንዱስትሪው ተቋማዊ ባለቤትነትን እንዲያረጋግጥ ማስቻል፣ የስልጠና ተቋማት

39
በሁሉም ተፈላጊ ሙያዎች ከኢንዱስትሪው ተመጣጣኝ ወይንም ከፍ ያለ አቅም ያለው
አሰልጣኝ እንዲኖራቸው ማድረግ፤
 ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን በመስጠትና የቴክኖሎጂ
ሽግግር ማዕከል በማድረግ ማጠናከር፤
 የሴቶችንና የገጠሩን ነዋሪ ህዝብ ማዕከል ያደረጉና ተፈላጊ የሆኑ ሙያዎችን በመለየት
ስልጠና የሚያገኙበትን ሁኔታ በማመቻቸት የሴቶችን አቅም ገንብቶ በቴክኒክና ሙያ
አሰልጣኝነትና ማኔጅመንት ላይ ያላቸውን ድርሻ ማሳደግ፤
 በሃገሪቷ ያልተማከለና የተቀናጀ ውጤት ላይ የተመሰረተ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና
ሥልጠና ስርዓትን ለመተግበር በየደረጃው ተፈላጊውን ብቃት ማምጣትና አደረጃጀቱን
በመፈተሽ ማጠናከር፤
 የቴክኖሎጂ አቅም ክምችትና ሽግግርን በሚመለከት መልካም ተሞክሮዎችን በመዳሰስ
መጠቀምና የልምድ ልውውጥ ማካሄድ፤
 ባለድርሻ አካላትን ከሙያ ደረጃ ምደባ ጀምሮ በስርዓተ ትምህርት ቀረጻ፣ በስልጠናና በምዘና
ተግባራት ላይ ማሳተፍ፤
 የስልጠና ገበያ ፍላጎት ጥናት ስርዓት መዘርጋትና በየጊዜው የሙያ ደረጃዎችን ማሻሻልና
ስልጠናዎች እንዲካሄዱ ማድረግ፤

ከፍተኛ ትምህርት

 የዩኒቨርሲቲ አመራርን ማጠናከር፣ አዳዲስ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ሥራ


ከመጀመራቸው በፊት ለዚሁ ዓላማ የተዘጋጀ የማብቂያ ስልጠና እንዲያገኙ ማድረግ፤
 የሁሉም ዩኒቨርስቲዎችን የቅበላ አቅም በተለይም በሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም በመምህራን
ትምህርት መርሐ ግብሮች ማሳደግ፤
 ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን ፕሮፌሽናል መምህራን እንዲሆኑ የሚያስችሉ
(የማስተማር ስነ-ዘዴ፣ የተማሪ ምዘና፣ የአክሽን ሪሰርችና የመሳሰሉትን) ስልጠናዎችን
በመስጠት የመምህርነት ብቃታቸውን ማሳደግ፣
 በመገንባት ላይ ያሉትን ዩኒቨርሲቲዎች በማጠናቀቅና በአስፈላጊ ቁሳቁሶች በማሟላት በተለይ
ለሳይንስና ቴክኖሎጂ እና መምህራን ትምህርት መርሐ ግብሮች ትኩረት እንዲሰጡ ማድረግ፤

40
 ተቋማትና መምህራን በምርምርና ቴክኖሎጂን በማላመድ ልምድ የሚያካብቱበትን ሥርዓት
መዘርጋትና ተግባራዊ ማድረግ፤
 የከፍተኛ ትምህርት መምህራን የድኅረ ምረቃ ትምህርት የሚያገኙበትን ዕድል በማስፋት
በቁጥርና በብቃት ከፍ እንዲሉ ማድረግ፣
 ሀገር ዓቀፍ የሙያና የትምህርት ብቃት ማዕቀፍ (National Qulifications Framework)
ማዘጋጀትና ተግባራዊ ማድረግ፤
 ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተደራጀና በፖሊሲ የሚመራ የውስጥ የጥራት ማረጋገጫ
ሥርዓት አንዲዘረጉ ድጋፍ ማድረግና ማበረታታት፤
 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የምሩቃኖቻቸውን መዳረሻና የቀጣሪዎቻቸውን እርካታ በማጥናት
(graduate tracer study and employer satisfaction) ከጥናቱ ያገኙትን ግብረ-መልስ እንደ
ግብዓት በመጠቀም ሥርዓተ ትምህርታቸውን የሚያጎለብቱበትንና የሚያሻሽሉበትን ስርዓት
መዘርጋት፤
 ልዩ ድጋፍና ትኩረት የሚሹ የኅብረተሰብ ክፍሎችን ማለትም ሴቶች፣ አካል ጉዳተኞች፣
ታዳጊ ክልሎች፣ ወዘተ.የከፍተኛ ትምህርት ተሳትፎ ለማሳደግ የተለያዩ የአዎንታዊ
እርምጃዎችን (affirmative action) (የተለየ የመግቢያ መስፈርት፣ ልዩ የቲቶሪያል ድጋፍና፣
የስኮላርሺፕ ዕድል፣ ወዘተ) ማመቻቸት

5. የባለ ብዙ ዘርፍ ጉዳዮች

በዚህ ክፍል ስምንት ያህል ጉዳዮች ተካተዋል። እነርሱም ሥርዓተ-ጾታና ትምህርት፣ የልዩ
ፍላጎትና አካቶ ትምህርት፣ ኤች አይቪ ኤድስና ትምህርት፣ የህብረተሰብ ተሣትፎ፣ የአካባቢ
ጥበቃ፣ ያልተማከለ የትምህርት ሥርዓትና የአቅም ግንባታ፣ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች
ለተጎዱ አካባቢዎች ህጻናት መደበኛ ትምህርት (Education in Emergencies) እና
የትምህርት ቤት ጤና እና ምገባ (School Health and Nutrition) ናቸው።
1.ሥርዓተ ፆታ

የትምህርት ፍትሐዊነትን ለማረጋገጥ የሴቶች ትምህርት በሁሉም የትምህርት ዘርፍ


እንቅስቃሴ ውስጥ ተካቶና ትኩረት አግኝቶ መተግበር ይኖርበታል፡፡በዚህ መስክ የተጀመረው
እንቅስቃሴና የተገኙ ውጤቶች ይበልጥ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ለማድረግ በሁለተኛው

41
የድህነት ቅነሳና የልማት ስትራቴጂ ውስጥ ትኩረት አግኝቶ እና ተካቶ እንዲተገበር ቀጥሎ
የተዘረዘሩት አቅጣጫዎችና ግቦች ተለይተው ተቀምጠዋል፡፡

ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች /ዋና ዋና ሥራዎች/

 በአንደኛና ስምንተኛ ክፍሎች ያለውን ከፍተኛ የሴቶች የትምህርት መጠነ ማቋረጥ


መቀነስ፣
 በምሳሌና በአርአያነት ሊጠቀሱ የሚችሉ ሴቶችን በመማሪያና በማጣቀሻ መጽሐፍ ውስጥ
ማካተት፣
 ለህብረተሰቡ ስለሴቶች ትምህርት ጥቅም ግንዛቤ እንዲኖረው ማለትም(እንደ ጠለፋ፣ ፆታዊ
ትንኮሳ እና ያለዕድሜ ጋብቻን) ለማስቀረት የሚያስችለ ተከታታይ ሥራ እንዲሰራ
ማድረግ፣
 ሴት ተማሪዎችን በሁሉም የትምህርት እርከን ተሣታፊና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማድረግ፣
 የሴት ተማሪዎች የምክር አገልግሎት ከአንደኛ ደረጃ 2ኛ ሳይክል ጀምሮ እንዲሰጥ
ማድረግ፣
 በሁሉም የትምህርት ሥርዓት ውስጥ የሥርዓተ ፆታ ጉዳዮች ተካተው እንዲተገበሩ
ማድረግ፣
 በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሴት ተማሪዎችን ክበብ ማጠናከርና ማስፋፋት፣
 የሴቶች ትምህርት መድረክ /ፎረም / በሁሉም የትምህርት ሥርዓቱ ደረጃዎች ማጠናከር፣
 በአመራር ላይ ለሚገኙ ሴቶችና ለሥርዓተ ፆታ ትምህርት ተጠሪዎች ተከታታይ የአቅም
ግንባታ ስልጠና መስጠት፣
 ለሴቶች ትምህርት የድጋፍ አሰጣጥ (Affirmative action) ሂደትና ትግበራን መከታተል
እና መገምገም፣
 በሴት ተማሪዎች ትምህርት ዙሪያ የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን ማስፋት፣
 አርብቶ አደር አካባቢ የሚገኙ ሴት ተማሪዎችን የትምህርት ተሳትፎ ማሳደግ፣
 ልዩ ፍላጎት ያላቸውን ሴት ተማሪዎች በሁሉም ደረጃ ለትምህርታቸው ምቹ ሁኔታ
መፍጠር፣

2.ልዩ ፍላጐት ትምህርት

42
የትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲው በፈጠረው አመቺ ሁኔታ ከትምህርት የተገለሉትንና ልዩ
ፍላጎት ያላቸውን ህፃናት የትምህርት እድል ለመስጠትና ከዚህም አኳያ የትምህርት ለሁሉም
ግቦችን ለማሳካት የልዩ ፍላጎት ትምህርት ስትራቴጂ ተቀርፆ ሥራ ላይ ውሏል፡፡
ይህ ስትራቴጂ በሁለተኛው የድህነት ቅነሳና የልማት ዕቅድ ውስጥ ትኩረት ተሰጥቶት
በይበልጥ እንዲተገበር ቀጥሎ የተዘረዘሩት የትኩረት አቅጣጫዎችና ግቦች ተቀምጠዋል፡፡

ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች /ዋና ዋና ሥራዎች/

 የፌዴራል የልዩ ፍላጐት ትምህርት ስትራቴጂን ማሻሻል፣ ስትራቴጂውን ለመተግበር


የሚያስችል የአፈጻጸም መመሪያ ማዘጋጀት
 ለመምህራን ትምህርት ፕሮግራሞች በልዩ ፍላጐት ትምህርት ላይ ሙያዊ ድጋፍ
መስጠት፣
 ልዩ ፍላጐት ያላቸውና ከትምህርት የተገለሉ ሕፃናትን የትምህርት ተደራሽነት ማሳደግ፣
 በልዩ ፍላጐት ትምህርት ላይ ያለውን አመለካከት ለመቀየር የህብረተሰቡን ግንዛቤ
ማሳደግ፣
 የድጋፍ መስጫ ማዕከላትን (Resource center) በክልሎች ማቋቋም ፣
 የዳሰሳና የመለያ መሳሪያ (Educational assessment & Screening tools) ማዘጋጀት፣
 በልዩ ፍላጐት ትምህርት መምህራንን በተጠናከረ ሁኔታ ማሰልጠን፣
 የልዩ ፍላጎት ትምህርትን በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ስትራቴጂ ውስጥ አካቶ
ለመስጠት የሚያስችል መመሪያ ማዘጋጀት፣

3.ኤች. አይ.ቪ/ኤድስና ትምህርት

በመካሄድ ላይ ያለውን ዘርፈ ብዙ ፀረ-ኤድስ እንቅስቃሴ ውጤታማ ከማድረግ አኳያ


የትምህርት ሚና የጎላ ነው፡፡ ስለሆነም በሁሉም ደረጃ በሚካሄደው የሥርዓተ ትምህርት
ማዕቀፍ ውስጥ ስለ ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ እንዲካተት ከመደረጉም በላይ በትምህርት ስርዓቱ
ውስጥ ሚና ያላቸው ባለድርሻ አካላትም የችግሩን አሳሳቢነት ተገንዝበው በባለቤትነት
እንዲይዙና እንዲያግዙ ቀጣይነት ያለው ሥርዓት ተዘርግቷል፡፡ በዚሁ መሠረት በሁለተኛው

43
የድህነት ቅነሳና የዘላቂ ልማት ፕሮግራም ቀጥሎ በተመለከቱት አንኳር ጉዳዮች ዙሪያ
የተቀናጀና የተጠናከረ እንቅስቃሴ ይደረጋል፡፡

ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች /ዋና ዋና ሥራዎች/

 በሥርዓተ ትምህርት ውሰጥ ስለኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ትምህርት ተጠናክሮ እንዲቀጥል


ማድረግ፣
 የአቻ ለአቻ ትምህርት ማስፋፋት፣
 በትምህርት ሥርዓቱ በየደረጃው(በፌዴራል፣በክልል፣በወረዳ እና በቀበሌ) ቋሚ
 የኤች .አይ.ቪ /ኤድስ ተጠሪ አካል መመደብ፣
 የተጠናከረ እና ቀጣይነት ያለው የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር
በፕላዝማ፣ በሬዲዮ፣ ቴሌቪዥንና በት/ቤት ሚኒሚዲያዎች አጠናክሮ መቀጠል፣
 በየት/ቤቱ የፀረ-ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ክበባትን ማጠናከር፣

4.የህብረተሰብ ተሳትፎ

መንግስት በሚሰራው ሥራ ብቻ የታለመውን የትምህርት ግብ ለማሳካት ስለማይቻል የሕብረተሰቡ


ተሳትፎ እጅግ ወሳኝ ነው፡፡ለትምህርት ሂደት ስኬት እንቅፋት እየሆነ ያለውን የተማሪ
ትምህርት ማቋረጥ ምጣኔን ለመቀነስ፣ የትምህርት ተሳትፎን ለመጨመር፣ የትምህርቱን
ጥራት ለመጠበቅ፣ ፍትሐዊነቱን ለማረጋገጥ እና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ለሁሉም
የሚለውን አለምአቀፋዊ ግብ ለማሳካት የሕብረተሰቡ ተሳትፎ ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል
ማድረግ እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡
ስለሆነም በሚቀጥሉት አምስት አመታት (2003-2007) በሁለተኛው ዙር የድህነት ቅነሳና
የልማት ዕቅድ ውስጥ የሕብረተሰብ ተሳትፎ ትኩረት እንዲያገኝ ቀጥሎ የተዘረዘሩት
የትኩረት አቅጣጫን የሚያመላክቱ ግቦችን አካቶ እንዲዘጋጅ ተደርጓል፡፡

ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች /ዋና ዋና ሥራዎች/

 ህብረተሰቡ ስለትምህርት ጥቅም አውቆ ልጆቹን ወደ ትምህርት ቤት እንዲልክ መቀስቀስ፣

44
 የተማሪዎችን የትምህርት አለማቋረጥ መደበኛ በሆነ መልኩ መከታተል፣
 ትምህርትን በማዳረስና ጥራቱን በመጠበቅ ረገድ ህብረተሰቡ በጉልበት፣ በገንዘብ እና
በእውቀቱ እንዲሳተፍ ማድረግ፣
 በትምህርት ሥርዓቱ አመራር ውስጥ ህብረተሰቡ በንቃት እንዲሳተፍ ማድረግ፣

5.ያልተማከለ የትምህርት ሥርዓትና የአቅም ግንባታ ፕሮግራም

በህገ-መንግስቱ በተደነገገው መሠረት የት/ት አመራርና ፈፃሚ አካላት ያልተማከለ የትምህርት


ሥርዓትን በመከተል እና በእያንዳንዱ የሥልጣን ተዋረድ(ፌደራል፣ ክልል፣ ዞን፣ ወረዳ፣
ቀበሌና ት/ቤቶች) ኃላፊነትና ተጠያቂነቱን በብቃትና በትጋት ለመወጣት እንዲችሉ የድህነት
ቅነሳና የልማት ስትራቴጂ ተግባራዊ ለማድረግ ሁሉም በትምህርት ዘርፉ አወቃቀርና
አደረጃጀት ውስጥ የድርሻቸውን እንዲወጡ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት የትኩረት አቅጣጫና
ግቦች ተለይተው ተቀምጠዋል፡፡

ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች /ዋና ዋና ሥራዎች/

 የክልል፣ የወረዳ፣ የቀበሌ እና የት/ቤት የትምህርት አመራሮችንና ባለሙያዎችን አቅም


መገንባት፣
 በየደረጃው ያሉ የትምህርት ሥርዓቱ አካላት እና ህብረተሰቡ በጋራ በመሆን የትምህርት
ቤት የውስጥ ገቢ እንዲዳብር ማድረግ፣
 የት/ሚኒስቴር እና የልማት አጋሮች በጋራ የሚሰሩት የአቅም ግንባታ ሥራ ተጠናክሮ
እንዲቀጥል ማድረግ፣

6.የአካባቢ ጥበቃ

45
በአሁኑ ወቅት አካባቢ ጥበቃ የሀገራችንና ብሎም የአለማችን አንገብጋቢ ጉዳይ መሆኑ
አያጠያይቅም፡፡ በመሆኑም ይህንን ሀገራዊና አለም አቀፋዊ ጉዳይ ከዳር ለማድረስና ለመጠበቅ
ዋነኛውና ትክክለኛው አማራጭ የጉዳዩን አሳሳቢነት በትምህርት ዘርፉ በማካተት ለተማሪዎች
ተደራሽ ማድረግ ነው፡፡ በመሆኑም በቀጣይነት በሁለተኛው የዘላቂ ልማትና የድህነት ቅነሳ
ፕሮግራም ሊተገበሩ የሚገባቸውን የትኩረት አቅጣጫዎችና አመላካቾች ተለይተው
ተቀምጠዋል፡፡
ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች /ዋና ዋና ሥራዎች/

 የአካባቢ ጥበቃ ክበባትን በት/ቤቶች ውስጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ማድረግ፣


 ለህብረተሰቡ ስለ አካባቢ ጥበቃ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን መስራት፣
 በሥርዓተ ትምህርት ውስጥ የገቡ አካባቢ ጥበቃን የሚመለከቱ ይዘቶችን ተጠናክረው
እንዲቀጥሉ ማድረግ፣

7.በአደጋ ጊዜ ትምህርት (Education in Emergencies)

የትምህርት ለሁሉም መርሓ ግብርን ለማሣካትና ትምህርትን በፍትሐዊነት ለሁሉም ለማዳረስ


በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ለተጋለጡ አካባቢዎች ህጻናት መደበኛ ትምህርትን ማዳረስ
ወሳኝ ተግባር ነው።ከዚህ አንጻር በአገራችን ውስጥ በድርቅ፣በጎርፍ፣ በጎሳ ግጭትና በመሳሰሉ
ችግሮች ተደጋጋሚ ተጋላጭነት በሚገጥማቸው አካባቢዎች የመደበኛ ትምህርት መቋረጥና
የህጻናትን ከትምህርት ገበታቸው መፈናቀል ለማስቀረት በአደጋ ጊዜ መደበኛ የትምህርት
ፕሮግራምን ለማሰቀጠል የሚያስችሉ ሁኔታዎችን ማመቻቸት አስፈላጊ ነው።

ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች /ዋና ዋና ሥራዎች/

 የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራሞችን ማካሄድ


 ስለ አደጋ ጊዜ ትምህርት የአቅም ግንበታ ስልጠና መስጠት
 በትምህርት ሥራ አመራር መረጃ ሥርዓት አማካይነት ስለ አደጋ ጊዜ ትምህርት መረጃ
መሰብሰብ

46
 ለአደጋ ጊዜ ትምህርት ፕሮግራም የቅድመ ዝግጅትና አፋጣኝ ምላሽ መስጫ ሥርዓት
መዘርጋት

8.የትምህርት ቤት ጤናና ምገባ ፕሮገራም (School Health and Nutrition)

ጤናማነትና ጥሩ የአመጋገብ ሁኔታ የትምህርት አቀባበልና የመማር ችሎታን በማዳበር ረገድ


ከፍተኛ አስተዋጽፆ እንዳላቸው ይታወቃል።ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ህጻናት ወደ
ትምህርት ቤት እንዲመጡና ከትምህርት ገበታቸው ሳይለዩ ትምህርታቸውን በሚገባ
ተከታትለው እንዲያጠናቅቁና ችሎታቸውም እንዲሻሻል ለማድረግ የህጻናቱን ጤናማነትና
የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ ወሳኝ ነው። የትምህርት ቤት ጤናና ምገባ ለትምህርት ጥራት
መሻሻል ከሚኖረው ጉልህ ድርሻ በተጨማሪ ትምህርትን በፍትሐዊነት ለሁሉም ለማዳረስ
ከፍተኛ ሚና ይጫወታል ። ይህም በተለይ የጤናና የምግብ ችግር ያለባቸውና ከድሃ ቤተሰብ
የሚመጡ የትምህርት ቤት ህጻናት ጤናቸውና የምግብ ዋስትናቸው እንዲጠበቅና የትምህርት
አቀባበል ችሎታቸው እንዲሻሻል ያደርጋል ። የህጻናትን የትምህርት መጠነ መድገማና ማቋረጥ
በመቀነስ ትምህርታቸውን የማጠናቀቅ ዕድላቸውን ያሳድጋል ። የዚህ ድምር ውጤት ደግሞ
ትምህርት ለሁሉምን ለማሳካት ያስችላል።

ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች (ዋና ዋና ሥራዎች)


 ስለ ትምህርት ቤት ጤናና ምገባ የግንዛቤ ማስጨበጫ መስጠት
 በየት/ቤቶች አካባቢ ከሚገኙ የጤና ተቋማት ጋር በመቀናጀት የጤና አጠባበቅ ትምህርትና
አገልግሎት ሥርዓት መዘርጋት
 በትምህርት ሥራ አመራር መረጃ ሥርዓት አማካይነት ስለ ትምህርት ቤት ጤናና ምገባ
መረጃመሰብሰብ

9.የአደገኛ ዕፆችና መድኃኒቶች ተጠቃሚነትን መከላከልና ትምህርት


(Drug and Substance Abuse Prevention in Education)

እ.ኤ.አ በ1995 በኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ ሃያ ከተሞችና በተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች የተደረገ
ጥናት እንደሚያመለክተው ጫት ፣አልኮል፣ቶባኮ፣ሀሺሽ፣ካናቢስና ሌሎች ሱስ የሚያስይዙ አደገኛ

47
ዕፆችንና መድሀኒቶችን የመጠቀም ሁኔታ በተለይ በወጣቶችና ተማሪዎች ዘንድ እየተባበሰ
መምጣቱ ታውቋል።

የአደገኛ ዕፅ ወይም መድሀኒት ሱሰኞች አንድን ዕፅ ወይም መድሀኒት በመጠቀም ብቻ


እንደማይወሰኑና ሌሎችን ሱስ አስያዥ ነገሮችን ወደ መጠቀም እንደሚሄዱ ፣ችግሩም
ኢኮኖሚያዊ፣ማህበራዊና ፖለቲካዊ ይዘት እንደሚኖረውና ውስብስብ እንደሆነና አፋጣኝ ርምጃ
እንደሚያስፈልገው በጥናቱ ተመልከቷል። ችግሩ በተለይ ከኤች አይ ቪ ኤድስ ወረርሺኝ ጋር
ያለው ቀጥተኛ ቁርኝትም ተገልጿል።

ይህ አሳሳቢ ችግር በተለይ በ2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ደረጃ
በፍጥነት እየተዛመተ እንደሆነ ተጠቅሷል።ችግሩ የተማሪዎችን ጤንነት፣ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ
ህይወት ከማወኩ ሌላ መጠነ ማቋረጥን፣መድገምና የትምህርት ብክነትን እንደሚያባብስ በጥናቱ
ተመላክቷል።

ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች (ዋና ዋና ሥራዎች)


 በሁሉም ደረጃ የፀረ አደገኛ ዕፆችና መድሀኒቶች መከላከል ተቋማትን ማቋቋም
 የአደገኛዕፆችና መድሀኒቶች ተጠቃሚነትን ለመከላከል የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨበጫ
መድረኮችን ማካሄድና የማህበረሰብ ንቅናቄ መፍጠር
 ሁሉም የትምህርት ተቋማት የአደገኛ ዕፆችና መድሀኒቶች መከላከልን የእቅዳቸው ዋና
አካል እንዲያደርጉት ግንዛቤ መስጠት
 ተከታታይ የሆነና ጠንካራ የክትትልና ግምገማ ሥርዓት መዘርጋት

48
ዝርዝር አመልካቾችና ግቦች
ሀ.አጠቃላይ ትምህርት
መነሻ
ግ ቦ ች
አመላካቾች ዓመት
2002 2003 2004 2005 2006 2007
የትምህርት ተሳትፎ አመላካቾች (Access Indicators)
የቅድመ- መደበኛ ወንድ 6.9% 9.5% 12.1% 14.8% 17.4% 20.0%
ትምህርት ጥቅል ሴት 6.9% 9.5% 12.1% 14.7% 17.4% 20.0%
ተሳትፎ አማካይ 6.9% 9.5% 12.1% 14.7% 17.4% 20.0%
ወንድ 136% 133% 130% 126% 123% 120%
የአንደኛ ክልፍ
ሴት 126% 123% 121% 118% 116% 113%
ጥቅል ቅበላ
አማካይ 131% 128% 125% 122% 119% 116%
ወንድ 86.2% 88.3% 90.4% 92.5% 94.6% 100.0%
የአንደኛ ክፍል
ሴት 82.7% 85.5% 88.3% 91.1% 93.9% 100.0%
ንጥር ቅበላ
አማካይ 84.5% 87.0% 89.5% 92.0% 94.5% 100%
የ1ኛ ደረጃ ወንድ 92.9% 93.3% 93.7% 94.1% 94.6% 95.0%
ትምህርት ሴት 90.1% 91.0% 92.0% 93.0% 94.0% 95.0%
የመጀመሪያ
ዕርከን(1-4) ንጥር አማካይ 91.5% 92.2% 92.9% 93.6% 94.3% 95.0%
ተሳትፎ በመቶኛ
የአንደኛ ደረጃ ወንድ 51.9% 57.5% 63.1% 68.8% 74.4% 80.0%
ትምህርት 2ኛ ሴት 52.0% 57.6% 63.2% 68.8% 74.4% 80.0%
ዕርከን ( 5-8) ንጥር
ተሳትፎ አማካይ 52.0% 57.6% 63.2% 68.8% 74.4% 80.0%

የአንደኛ ደረጃ ወንድ 89.3% 90.8% 92.4% 93.9% 95.5% 97.0%


ትምህርት (1-8) ሴት 86.5% 88.6% 90.7% 92.8% 94.9% 97.0%
ንጥር ተሳትፎ አማካይ 87.9% 89.7% 91.5% 93.4% 95.2% 97.0%

49
መነሻ
ግ ቦ ች
አመላካቾች ዓመት
2002 2003 2004 2005 2006 2007
የ1ኛ ደረጃ ወንድ 133.4% 134.9% 133.1% 132.0% 130.8% 129.5%
ትምህርት ሴት 124.5% 126.2% 124.6% 123.9% 123.0% 122.1%
(1-4) /አማራጭ
መሰረታዊ
ትምህርትን ጨምሮ) አማካይ 129.1% 130.7% 128.9% 128.0% 127.0% 125.9%
ጥቅል ተሳትፎ
የአንደኛ ደረጃ ወንድ 67.1% 68.5% 73.3% 80.7% 89.9% 100.4%
ትምህርት 2ኛ ሴት 68.3% 69.0% 73.5% 81.3% 91.0% 102.3%
ዕርከን (5-8) ጥቅል
ተሳትፎ
አማካይ 67.1% 68.5% 73.3% 80.7% 89.9% 100.4%
የአንደኛ ደረጃ (1-8 ወንድ 98.7% 99.4% 102.5% 105.8% 110.0% 114.9%
) ሴት 93.0% 94.4% 98.0% 101.1% 104.9% 109.2%
ትምህርት(አማራጭ 95.9% 96.9% 100.3% 103.5% 107.5% 112.1%
መሰረታዊ
አማካይ
ትምህርትን ጨምሮ)
ጥቅል ተሳትፎ

የ2ኛ ደረጃ ወንድ 44.0% 44.5% 47.2% 52.8% 57.8% 61.8%


ትምህርት ሴት 35.2% 38.5% 44.1% 52.6% 58.9% 62.3%
የመጀመሪያ ዕርከን
ጥቅል ተሳትፎ(9-
10)
አማካይ 39.7% 41.6% 45.7% 52.7% 58.4% 62.0%

የ2ኛ ደረጃ ወንድ 8.2% 8.0% 8.5% 8.4% 8.8% 9.7%


ትምህርት ሁለተኛ ሴት 3.8% 4.3% 5.3% 6.1% 7.3% 9.2%
ዕርከን /መሰናዶ
ትምህርት(11-12) አማካይ 6.0% 6.2% 6.9% 7.3% 8.0% 9.5%
ጥቅል ተሳትፎ
የ2ኛ ደረጃ ሁለተኛ ጠቅላላ
ተሳትፎ
204,000 209,000 231,000 254,000 293,000 360,000
ዕርከን /መሰናዶ
ትምህርት (11-12) ሴቶች
ጠቅላላ ተሳትፎ
31% 35% 38% 42% 45% 48%
9,100,00 18,200,00
ድምር 18,200,000 18,200,000 9,100,000
0 0
ጥቅል
ተሳትፎ
የጎልማሶች 36% 47.8 59.6 71.4 83.2 95.0
በመቶኛ
ትምህርት ተሳትፎ
(%)
ወንድ 50% 59 68 77 86
95.0
ሴት 23% 37.4 51.8 66.2 80.6 95.0
የጥራት አመላካቾች (Quality Indicators)
ዲፕሎማ ያላቸው
የ1ኛ ደረጃ በመቶኛ 38.4% 49.7% 61.0% 72.3% 83.3% 94.6%
መምህራን(1-8)
ዲግሪ ያላቸው
በመቶኛ 79.4% 83.6% 87.8% 90.2% 96.2% 98.2%
የ2ኛ ደረጃ

50
መነሻ
ግ ቦ ች
አመላካቾች ዓመት
2002 2003 2004 2005 2006 2007
መምህራን(9-12)
ክፍል 1-2 4 (1:1) 4 (1:1) 4 (1:1) 4 (1:1)
ክፍል 3-4 5 (1:1) 5 (1:1) 5 (1:1) 5 (1:1)
የ1ኛ ደረጃ
ክፍል 5-
ትምህርት የተማሪ 7 (1:1) 7 (1:1) 7 (1:1) 7 (1:1)
-መጽሐፍ ጥምርታ 6
ክፍል 7-
8 (1:1) 8 (1:1) 8 (1:1) 8 (1:1)
8
ክፍል 9-
የ2ኛ ደረጃ 10 (1:1) 10 (1:1) 10 (1:1) 10 (1:1) 10 (1:1)
10
ትምህርት የተማሪ
-መጽሐፍ ጥምርታ ክፍል 11-
10 (1:1) 10 (1:1) 10 (1:1) 10 (1:1) 10 (1:1)
12
ክፍል 1-
የ1ኛ ደረጃ 56.9 55.1 53.2 51.4 49.6 47.8
4
ትምህርት የተማሪ
-መምህር ጥምርታ ክፍል 5-
45.7 44.4 43.1 41.8 40.5 39.2
8
ክፍል 9-
የ2ኛ ደረጃ 40.2 39.0 37.7 36.3 34.9 33.3
10
ትምህርት የተማሪ
-መምህር ጥምርታ ክፍል 11-
25.3 24.8 24.2 23.6 23.0 22.2
12
በ4ኛ ክፍል
በሚደረግ

ሃገር አቀፍ
የትምህርት 1 1
ቅበላ
40.9% 65% 75%
ጥናት

የትምህርት ቅበላ
ጥናት በዋና ዋና
የትምህርት
ዓይነቶች ቢያንስ
50 % ውጤት ያገኙ
ተማሪዎች
በ8ኛ ክፍል
በሚደረግ
የትምህርት ቅበላ ሃገር አቀፍ
ጥናት በዋና ዋና የትምህርት
35.6% 60% 70%
የትምህርት ቅበላ
ዓይነቶች ቢያንስ ጥናት
50 % ውጤት ያገኙ
ተማሪዎች
በ10ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ
በሚደረግ የትምህርት 13.8% 50% 70%
የትምህርት ቅበላ ቅበላ

1
2004 እና 2005 የተዘለሉበት ምክንያት የትምህርት ቅበላ ጥናት ምዘና የሚካሔድ በየሁለት ዓመት በመሆኑ ነው፡፡

51
መነሻ
ግ ቦ ች
አመላካቾች ዓመት
2002 2003 2004 2005 2006 2007
ጥናት በዋና ዋና ጥናት
የትምህርት
ዓይነቶች ቢያንስ
50 % ውጤት ያገኙ
ተማሪዎች
በ12ኛ ክፍል
በሚደረግ
የትምህርት ቅበላ ሃገር አቀፍ
ጥናት በዋና ዋና የትምህርት
34.9% 60% 70%
የትምህርት ቅበላ
ዓይነቶች ቢያንስ ጥናት
50 % ውጤት ያገኙ
ተማሪዎች
በ4ኛ ክፍል
በሚደረግ
የትምህርት ቅበላ ሃገር አቀፍ
ጥናት በዋና ዋና የትምህርት
1.7% 20% 25%
የትምህርት ቅበላ
ዓይነቶች ቢያንስ ጥናት
75 % ውጤት ያገኙ
ተማሪዎች
በ8ኛ ክፍል
በሚደረግ
የትምህርት ቅበላ ሃገር አቀፍ
ጥናት በዋና ዋና የትምህርት
የትምህርት ቅበላ
0.7 20% 25%
ዓይነቶች ቢያንስ ጥናት
75 % ውጤት ያገኙ
ተማሪዎች
በ10ኛ ክፍል
በሚደረግ
የትምህርት ቅበላ ሃገር አቀፍ
ጥናት በዋና ዋና የትምህርት
1.3% 20% 25%
የትምህርት ቅበላ
ዓይነቶች ቢያንስ ጥናት
75 % ውጤት ያገኙ
ተማሪዎች
በ12ኛ ክፍል
በሚደረግ
የትምህርት ቅበላ ሃገር አቀፍ
ጥናት በዋና ዋና የትምህርት
12.4% 20% 25%
የትምህርት ቅበላ
ዓይነቶች ቢያንስ ጥናት
75 % ውጤት ያገኙ
ተማሪዎች
በ1ኛ ደረጃ ወንድ 75% 76% 89% 98% 107% 116%
ትምህርት (1-
4)ትምህርትን ሴት 73% 74% 86% 95% 102% 109%
ተከታትሎ
የማጠናቀቅ ምጣኔ አማካይ 74% 75% 88% 97% 104% 112%
በመቶኛ
በ1ኛ ደረጃ ወንድ 47% 49% 57% 58% 63% 79%

52
መነሻ
ግ ቦ ች
አመላካቾች ዓመት
2002 2003 2004 2005 2006 2007
ትምህርት (5- ሴት 44% 49% 59% 60% 64% 79%
8)ትምህርትን
ተከታትሎ
የማጠናቀቅ ምጣኔ አማካይ 46% 49% 58% 59% 64% 79%
በመቶኛ
የብቃት አመላካቾች( Efficiency indicators)
ወንድ 17.3% 14.1% 10.8% 7.5% 4.3% 1.0%
የ1ኛ ክፍል መጠነ
ሴት 16.0% 13.0% 10.0% 7.0% 4.0% 1.0%
ማቋረጥ
ድምር 16.7% 13.6% 10.4% 7.3% 4.1% 1.0%
የ1ኛ ደረጃ ወንድ 11.5% 9.2% 7.1% 4.9% 2.8% 1.0%
ትምህርት(1-8) ሴት 10.0% 8.0% 6.1% 4.3% 2.4% 1.0%
የመጠነ ማቋረጥ
ድምር 10.8% 8.7% 6.6% 4.6% 2.6% 1.0%
አማካይ ምጣኔ
የ1ኛ ደረጃ ወንድ 6.1% 5.2% 4.2% 3.1% 2.1% 1.0%
ትምህርት ሴት 5.4% 4.6% 3.7% 2.8% 1.9% 1.0%
(4-8) የመጠነ
መድገም አማካይ ድምር 5.8% 4.9% 3.9% 3.0% 2.0% 1.0%
ምጣኔ

የፍትሓዊነት አመላካቾች(Equity indicators)


1ኛ ደረጃ
0.93 0.94 0.94 0.94 0.94 1.00
1-4
2ኛ ደረጃ
የሥርዓተ -ፆታ 0.97 0.99 0.99 0.99 0.97 1.00
5-8
ልዩነት ከጥቅል
2ኛደረጃ 9-
ተሳትፎ አኳያ 0.80 0.87 0.93 1.00 1.00 1.00
10
2ኛደረጃ11-
0.46 0.54 0.63 0.72 0.83 1.00
12
የአፋር
1ኛ ደረጃ ትምህርት 58.0% 66.0% 74.0% 82.0% 90.0% 98%
ክልል
ጥቅል ተሳትፎ (1-
የሶማሌ
8) 63.8% 71.0% 78.2% 85.4% 92.6% 100%
ክልል

53
ክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጥና

54
መነሻ ግቦች
አመላካቾች መለኪያ ዓመት
2002 2003 2004 2005 2006 2007
የደረጃ 3 እና 4 መዛኝነት ዕውቅና የተሰጣቸው
ቁጥር 469 781 1,198 1,719 2,448
የኢንዱስትሪ መዛኞች
1,324
የደረጃ 1 እና 2 መዛኝነት ዕውቅና የተሰጣቸው
ቁጥር 3,281 5,469 8,385 12,031 17,135
የኢንዱስትሪ መዛኞች
አጠቃላይ የኢንዱስትሪ መዛኝ ድምር 1,324 3,750 6,250 9,583 13,750 19,583

የምዘና መሣሪያ የተዘጋጀላቸው ሙያዎች ቁጥር 211 300 330 350 370 390

ዕውቅና የተሰጣቸው የምዘና ማዕከላት ቁጥር 174 250 250 334 417 500
575,0
የተመዘኑ ዕጩዎች ቁጥር 75,000 225,000 375,000 825,000 1,175,000
00
የሙያ ብቃት ምዘና ያለፉ ተመዛኞች መጠን መቶኛ 20 28 36 44 52 60

የሙያ ደረጃ የወጣላቸው ሙያዎች ቁጥር 250 300 330 350 370 390

በትብብር ስልጠና የታቀፉ ሰልጣኞች መጠን መቶኛ 23 50 65 70 75 80


22,48
የትብብር ስልጠናን የተገበሩ ኢንተርፕራይዞች ቁጥር 1,208 13,326 19,099 26,135 30,062
0
የካምፓኒ ውስጥ ስልጠናን የሚያካሂዱ ካምፓኒዎች ቁጥር 15 45 85 135 195 295
በየዐመቱ ሥልጠና አጠናቀው ወደ ሥራ የተሰማሩ
በመቶኛ 45 70 75 80 85 90
ሰልጣኞች መጠን
963,4
ድምር ቁጥር 717,603 799,548 881,494 1,045,385 1,127,330
39
578,0
ሠልጣኞች የመንግስት ቁጥር 430,562 479,729 528,896 627,231 676,398
64
385,3
መንግስታዊ ያልሆኑ ቁጥር 287,041 319,819 352,597 418,154 450,932
76
በሶስቱ ደረጃዎች የፈሩ ድምር 19,36
ቁጥር 14,596 16,186 17,776 20,956 22,547
መምህራን 6
የመንግስት 11,92
ቁጥር 9,514 10,317 11,120 12,726 13,528
3

መንግስታዊ ያልሆኑ ቁጥር 5,082 5,869 6,656 7,443 8,230 9,019

55
መነሻ
መነሻ
አመላካቾ ዓመ
አመላካቾች መለኪያ ዓመት ግቦች መለኪያ ግቦች አመላካቾች
ች ት
2002
2002
ድምር ቁጥር 815 888 956 1,029 1,102 1,147

የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ቁጥር 257 287 317 347 377 407


ተቋማት
የመንግሥት ፖሊ ቴክኒክ ቁጥር 1 11 16 26 36 40

መንግስታዊ ያልሆኑ ቁጥር 557 592 627 662 697 730


ተሸጋግረው ኃብት የፈጠሩ ቴክኖሎጂዎች ቁጥር - 600 1,200 1,800 2,400 3,000
ቅድሚያ ትኩረት ለተሰጣቸው ዘርፎች የተዘጋጁ የዕሴት
ቁጥር - 60 120 180 240 300
ሰንሰለቶች
ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች አስፈላጊ ሆነው
ቁጥር - 300 600 900 1,200 1,500
የተመረጡ ቴክኖሎጅዎች
ተፈትሸው የተረጋገጡ የቴክኖሎጅ ፕሮቶታይፖች ቁጥር 99 216 432 648 896 1,080
ቴክኖሎጅን ለማባዛት የበቁ ጥቃቅንና አነስተኛ
ቁጥር - 150 300 450 600 750
ኢንተርፕራይዞች

ወደ ጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት የተሸጋገሩ ቴከኖሎጅዎች ቁጥር 100 200 400 600 800 1,000

የተቀዱ ቴከኖሎጅዎች ቁጥር - 190 380 570 760 950

የተሻሻሉ ቴከኖሎጅዎች ቁጥር - 10 20 30 40 50

56
ሐ. ከፍተኛ ትምህርት

1.የተማሪዎች አጠቃላይ ተሳትፎ ዒላማዎች

መነሻው
ክንውን የዕቅዱ ዘመን የተሳትፎ ዒላማዎች
የመስኮች
ምድብ
2002 2003 2004 2005 2006 2007

1.ኢንጅኔሪንግና ኮምፕዩቲንግ 31373 41000 67000 120000 160000 186978


2.ተፈጥሮ ሣይንስ 36035 62400 83500 88000 90000 93489
3.የህክምና ሣይንስ 17026 19900 20000 20000 22570 23372
4.ግብርናና የእንስሳት ህክምና 19070 19900 20000 20000 22570 23372
5.ቢዚነስና ኢኮኖሚክስ 37767 50679 67824 81445 91649 93489
6.ማህበራዊ ሣይንስ 44517 49900 50000 38900 43793 46745
የሣይንስና ቴክኖሎጂ መስክ ዓመታዊ ቅበላ ድርሻ
61:39 63:37 65:35 67:33 69:31 70:30
ምጣኔ
የቅድመ ምረቃ ትምህርት ጥቅል ተሳትፎ 185788 196893 310120 368345 430582 467445
የሴቶች ተማሪዎች በመቶኛ 29 30.2 31.8 34.4 37.6 40
ዓመታዊ ዕድገት በመቶኛ 0.0 31.2 26.5 19.5 16.9 7.9

57
2. የልዩ ልዩ ዒላማዎች ዕቅድ

መነሻው ክንውን የዕቅድ ዘመኑ ግብ


ሀ. የመስኮች ምጣኔ (%)
2002 2007
1.ኢንጅኔሪንግና ኮምፕዩቲንግ 16.9 40.0
2.ተፈጥሮ ሣይንስ 19.4 20.0
3.የህክምና ሣይንስ 9.2 5.0
4.ግብርናና የእንስሳት ህክምና 10.3 5.0
5.ቢዚነስና ኢኮኖሚክስ 20.3 20.0
6.ማህበራዊ ሣይንስ 24.0 10.0
የሳይንስና ቴክኖሎጂ ድርሻ 55.7 70.0
የቢዝንስና ማሕበራዊ ሣይንስ ድርሻ 44.3 30.0
ለ. ሌሎች ዒላማዎች
በቅድመ ምረቃ ፕሮግራም አጠቃላይ ተሳትፎ (ብዛት) 185788 467445
የሴት ተማሪዎች ድርሻ (%) 29.0 40.0
አጠቃላይ የመመረቅ ስኬት (%) 93.0
በድሕረ ምረቃ ፕሮግራም የሴቶች ድርሻ (%) 11.3 25.0
ለደረጃው የሚመጥኑ የመምህራን ብዛት 5532 23000
የመምህር/ተማሪ አጠቃላይ ጥምርታ 1፡34 1፡20
ጠቅላላ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች ብዛት 22 31
ከ31ዱ ውስጥ አዲስ ቅርንጫፍ የከፈቱ ዩኒቨርቲዎች ብዛት 1 6
የሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲዎች ብዛት 1 2
የቴክኖሎጂ ኢንስቲቱዩቶች ብዛት 5 10
ብቁ የአመራርና አስተዳደር ስርዓት የገነቡ ተቋማት ብዛት 31
አስተማማኝ ገቢን ማመንጨት የቻሉ ተቋማት 22

58
5. የትምህርትና ስልጠና ዘርፍ የፋይናንስ ፍላጎት

የልማት ዕቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ የፋይናንስ ፍላጎትን ማየት የግድ ነው። ስለሆነም
ለአምስት አመቱ የልማት ዕቅድ ለትምህርት ዘርፍ የሚያስፈልገው የመደበኛና የካፒታል
ፋይናንስ ፍላጎት እንደሚከተለው የተቀመጠ ሲሆን ይህ የፋይናንስ ፍላጎት ግምት ጊዚያዊ
ግምት እንደ መሆኑ መጠን የሚለወጥ ይሆናል ።

በመሆኑም የአምስት ዓመቱ የትምህርት ዘርፍ አጠቃላይ የፋይናንስ ፍላጎት በሚከተለው


ሁኔታ ተቀምጧል::

ሀ.አጠቃላይ ትምህርት
መደበኛ ፦62.787 ቢሊየን ብር
ካፒታል ፦12.973 ቢሊየን ብር
ድምር፦75.700.000.000 (ሰባ አምስት ነጥብ ሰባት ቢሊየን ብር)

ለ.ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና

መደበኛ፦ 4,438,108,354 ቢሊየን ብር


ካፒታል፦ 3,350,321,433 ቢሊየን ብር
ድምር፦7,788,429,787 (ሰባት ቢሊየን ሰባት መቶ ሰማንያ ስምንት ሚሊየን አራት መቶ
ሃያ ዘጠኝ ሺህ ሰባት መቶ ሰማንያ ሰባት ብር)

ሐ.ከፍተኛ ትምህርትመደበኛ፦ 12,378,824,552ቢሊየን ብር

ካፒታል፦ 13,298,433,180 ቢሊየን ብር


ድምር፦ 25,677,257,731 (ሃያ አምስት ቢሊየን ስድስት መቶ ሰባ ሰባት ሚሊየን ሁለት
መቶ ሃምሳ ሰባት ሺህ ሰባት መቶ ሠላሳ አንድ ብር)
የፋይናንስ ምንጭ፦ መደበኛ የመንግስት በጀት፣ የተቋማት የውስጥ ገቢ፣ የተማሪ ወጭ
መጋራት፣ ከልማት አጋሮች

59
ሀ. አጠቃላይ ትምህርት (ዋጋ በቢሊየን ብር)

2003 2004 2005 2006 2007 Total

የተመደበ መደበኛ/Recurrent 7,662 7,478 8,611 9,957 11,423 45,131


የመጀመሪያ
በጀት
ደረጃትምህርት/
/Program ካፒታል /Capital 1,010 1,050 1,230 1,389 787 5,466
Primary
Costs
ድምር/Total 8,672 8,528 9,841 11,347 12,209 50,597

የተመደበ መደበኛ/Recurrent 2,172 2,456 3,351 4,271 5,406 17,656


2ኛ ደረጃ
በጀት/
ትምህርት/
Program ካፒታል /Capital 759 1,378 1,639 1,931 1,801 7,507
Secondary
Costs
ድምር/Total 2,931 3,834 4,990 6,202 7,207 25,163

የተመደበ መደበኛ/Recurrent 9,834 9,934 11,962 14,228 16,829 62,787


በጀት
ጠቅላላ/Total
/Program ካፒታል /Capital 1,769 2,428 2,869 3,320 2,588 12,973
Costs
ጠቅላላ ደምር/Total 11,603 12,362 14,830 17,548 19,417 75,760

60
ለ. ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና

Year 2002 2003 2004 2005 2006 2007 Total


Recurrent total
finance 560,645,790 793,186,444 834,225,982 884,803,210 936,952,795 988,939,924 4,438,108,354
Financial
requirement
for the
construction of
Poly-technical
college No data 256,250,000 256,250,000 205,000,000 153,750,000 51,250,000 922,500,000
Financial
requirement
for the
construction of
TVET college 314,944,260 419,925,680 104,981,420 104,981,420 104,981,420 41,992,568 776,862,508

Machinery &
equipment 405,080,960 632,939,000 253,175,600 227,858,040 202,540,480 75,952,680 1,392,465,800

Furniture 75,198,000 117,496,875 46,998,750 42,298,875 37,599,000 14,099,625 258,493,125


Capital total
finance 795223220 1,426,611,555 661405770 580138335 498870900 183294873 3,350,321,433

Total finance 1,355,869,010 2,219,797,999 1,495,631,752 1,464,941,545 1,435,823,695 1,172,234,797 7,788,429,787

61
ሐ. ከፍተኛ ትምህርት

mdb¾ bjT 2003 2004 2005 2006 2007 Total

y¦gR WS_
mMH‰N dmwZ 485,441,859 626,755,382 764,472,768 784,948,734 796,324,271 3,457,943,016

yW+ ¦gR
mMH‰N dmwZ 22,471,280 25,985,440 28,016,560 25,018,240 21,794,240 123,285,760

kdmwZ l@§
wÀãC 1,088,073,000.00 1,478,477,000 1,858,825,500 1,945,692,000 1,991,612,000 8,362,679,500

ymMH‰N SL-Â 106,133,262 132,486,177 71,348,493 72,536,847 52,411,497 434,916,276

yመdb¾ bjT
DMR 1,702,119,401 2,263,703,999 2,722,663,321 2,828,195,821 2,862,142,008 12,378,824,552

2.yµpE¬L bjT

lGNƬ 2,121,390,530.0 1,341,433,538.7 810,242,410.1 621,064,022.2 357,902,271.3 5,252,032,772.2


lx!k#PmNT½
fRn!cR½ l@lÖC
yTMHRT mR©
mϦ̋C 1,783,576,776 1,606,419,410 1,456,607,050 1,525,670,325 1,674,126,847 8,046,400,407

yµpE¬L bjT
DMR 3,904,967,306 2,947,852,949 2,266,849,460 2,146,734,347 2,032,029,118 13,298,433,180

yመdb¾Â µpE¬L
bjT DMR 5,607,086,706.6 5,211,556,948.1 4,989,512,781.1 4,974,930,168.9 4,894,171,126.6 25,677,257,731.2

62
በትምህርት ዘርፍ በቀጣዩ አምስት ዓመታት ሊተገበሩ የታቀዱ የልማት ፕሮጀክቶች

በሚቀጥሉት አምስት አመታት ሊተገበሩ ከታቀዱ የትምህርት ዘርፍ ፕሮግራሞች/ፕሮጀክቶች መካከል የሚከተሉት ዋና
ዋናዎቹ ናቸው

የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፕሮገራም

የያንዳንዱ ንኡስ ፕሮግራም በጀት / Program


Cost By Component 2008/09 2009/10 2010/11 2011/12 2012/13 Total
1. ሥርዓተ-ትምህርት፣መጻሕፍትና ግምገማ/
Curriculum, Textbooks & Assessment 7.3 76.2 37.6 25.6 146.7
2. የመምህርን ልማት ፕሮግራም / Teacher
Development Program 10.4 25.7 26.1 0.0 62.2
3.የት/ቤት ማሻሻያ ፕሮግራም / School
Improvement Program 30.9 35.6 40.5 44.7 151.7
4. የአመራርና አስተዳደር ፕሮግራም
/Management & Administration Program 1.6 9.4 10.4 0.0 21.4
5. ማስተባበር፣ክትትልና ግምገማ /Program
Coordination, M & E 1.7 3.7 2.8 1.2 1.0 10.4
ድምር/Sub-Total 51.9 150.6 117.4 71.5 1.0 392.4

መጠባበቂያ/Price/Physical Contingency 3.3 6.6 0.0 0.0 15.0 24.9


417.3
ጠቅላላ ድምር/Grand Total 55.2 157.2 117.4 71.5 16.0 million
USD

63
የዩኒቨርሲቲዎች ግንባታ

በትምህርት ዘርፍ በቀጣዩ አምስት ዓመታት ሊተገበሩ የታቀዱ የልማት ፕሮጀክቶች


ተ.ቁ ተግባራት 2003 2004 2005 2006

1 1,876,938,463.00 1,072,536,265.00 514,455,409.00 295,698,321.00


የህንፃ ግንባታ

2 መሰረተ ልማት 519,268,133.00 268,134,066.00 130,671,674.00 73,924,580.00


ግንባታ

የትምህርት
3 668,193,441.00 379,497,742.00 106,993,215.00 41,094,107.00
መሳሪያዎች
ግዥ
3,064,400,037.00 1,720,168,073.00 752,120,298.00 410,717,008.00
ድምር

4 226,478,000.00 452,963,000.00 679,427,000.00 850,500,000.00


መደበኛ በጀት

5 3,290,878,037.00 2,173,131,073.00 1,431,547,298.00 1,261,217,008.00


ድምር

ጠቅላላ ድምር 8,156,773,416.00

64
በሚቀጥሉት አምስት አመታት ሊተገበሩ ከታቀዱ የትምህርት ዘርፍ ፕሮግራሞች/ፕሮጀክቶች መካከል የሚከተሉት ዋና
ዋናዎቹ ናቸው

1.የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፕሮገራም

የያንዳንዱ ንኡስ ፕሮግራም በጀት / Program Cost By


Component 2008/09 2009/10 2010/11 2011/12 2012/13 Total
1. ሥርዓተ-ትምህርት፣መጻሕፍትና ግምገማ/ Curriculum,
Textbooks & Assessment 7.3 76.2 37.6 25.6 146.7
2. የመምህርን ልማት ፕሮግራም / Teacher
Development Program 10.4 25.7 26.1 0.0 62.2
3.የት/ቤት ማሻሻያ ፕሮግራም / School Improvement
Program 30.9 35.6 40.5 44.7 151.7
4. የአመራርና አስተዳደር ፕሮግራም /Management &
Administration Program 1.6 9.4 10.4 0.0 21.4
5. ማስተባበር፣ክትትልና ግምገማ /Program
Coordination, M & E 1.7 3.7 2.8 1.2 1.0 10.4
ድምር/Sub-Total 51.9 150.6 117.4 71.5 1.0 392.4
መጠባበቂያ/Price/Physical Contingency 3.3 6.6 0.0 0.0 15.0 24.9
417.3
ጠቅላላ ድምር/Grand Total 55.2 157.2 117.4 71.5 16.0 million USD

65
2.የ10 ዩኒቨርሲቲዎች ግንባታ

ተ.ቁ ተግባራት 2003 2004 2005 2006

1 የህንፃ ግንባታ 1,876,938,463.00 1,072,536,265.00 514,455,409.00 295,698,321.00

2. መሰረተ ልማት ግንባታ 519,268,133.00 268,134,066.00 130,671,674.00 73,924,580.00

3. የትምህርት መሳሪያዎች ግዥ 668,193,441.00 379,497,742.00 106,993,215.00 41,094,107.00

ድምር 3,064,400,037.00 1,720,168,073.00 752,120,298.00 410,717,008.00

4. መደበኛ በጀት 226,478,000.00 452,963,000.00 679,427,000.00 850,500,000.00

5. ጠቅላላ ድምር
3,290,878,037.00 2,173,131,073.00 1,431,547,298.00 1,261,217,008.00

8,156,773,416.00

66
6. የልማት ዕቅዱ ዘመን ዕድሎችና ሥጋቶች

6.1. ዕድሎች
 በተከታታይ በሃገሪቱ የሚታየው የኢኮኖሚ ዕድገት የትምህርት ዘርፉን በበጀት
ለመደገፍ አስተማማኝ መሆኑ
 mNGST የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርትን በ2008 ዓ.ም ፣ የአጠቃላይ 2ኛ ደረጃ
ትምህርትን ደግሞ በ2017 ዓ.ም ለሁሉም ለማዳረስና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና
ሥልጠና ykFt¾ TMHRTN l¥SÍÍT l¥ššL¼l¥údG ys-W Tk#rT q$R-
"nT½
 የመንግስትንና የልማት አጋሮችን ተሣትፎ በማጠናከር የትምህርት ጥራትን
ለማሻሻል መንግስት የሚያሳየው ተግባራዊ እንቅስቃሴና ትኩረት
 በሥርዓተ-ፆታ፣ በክልሎች፣ በከተማና በገጠር መካከል የሚታየውን የትምህርት ተሣትፎ
ፍትሐዊነት ለማረጋገጥ በመንግስት በኩል የተለያዩ ስትራቴጅዎች መነደፋቸው
 የትምህርት ብክነትን ለመቀነስ እስከ ትምህርት ተቋማት ድረስ የተፈጠረው ግንዛቤና
እየተወሰደ ያለው ርምጃ
 bmNGST tÌ¥T ytÌ¥êE lW_ GNƬ XNÄ!h#M ymMH‰N L¥TÂ
y|R›t(TMHRT lW_ tGƉêE mçN½
 ykFt¾ TMHRT tÌ¥T xm‰éCN yxm‰R xQM B”T l¥údG ytjm„
yxQM GNƬ PéËKèC mñ‰cW½
 yTMHRT SL- _‰T ¥rUgÅ x@jNs! mf-R btšl mLk# md‰jTÂ
m-ÂkR የትምህርትና ስልጠናና የቴ/ሙ/ት/ስለጠና ፖሊሲና እስትራቴጂ መነደፉና
የተመቻቸ የኢንቨስትመንት ፖሊሲ መኖር፣
 የቴ/ሙ/ት/ስልጠና ላይ የህብረተሰቡ ተሳትፎ እየተሻሻለ መምጣቱናከአነስተኛና
ጥቃቅን ኢንተፕራይዞች ጋር በትስስር መስራት መቻሉ፣
 የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ መስፋፋት

6.2. ስጋቶች
 ymMH‰N bbqE q$_RÂ ldr©W b¸m_N yTMHRT ZGJTÂ B”T xlmgßT
Ãl#TNM l¥öyT xlmÒl#½
 yb@t(Ñk‰ :”ãC ym¥¶Ã q$œq$îC bbqE m-N½ _‰T½ bwQt$ xlmQrB

67
 እየተገኘ ያለው የትምህርት መስፋፋት ውጤት አበራታች ቢሆንም የትምህርት ጥራት
በተፈለገው መልኩ ላይገኝ ይችላል
 የሀብት ውስንነት ሊያጋጥም ይችላል
 ከተቋማት ቁጥርና አቅም በላይ የሰልጣኞች ፍላጎት ሊጨምር ይችላል
 ለሙያ ምዘና የሚቀመጡ ሰልጣኞች ቁጥር በመብዛቱ በወቅቱ ለማስተናገድ ያለመቻል
ችግር ሊያጋጥም ይችላል
 የግል ኢንተርፕራይዞች ለትብብርና ለኩባንያ ውስጥ ስልጠና ያላቸው ተሳትፎ አጥጋቢ
ላይሆን ይችላል
 yMRMR |‰ãCN k¦g¶t$ yL¥T FላጎT UR y¸ÃStœSR -Nµ‰ |r›T
xlmñ„½
 y†n!vRs!tE kFt¾ xm‰éC mlêw_ xm‰„ bqE LMD bl@§cW xÄÄ!S
ሃ§ðãC mÃZ½
 yMRMR |‰ãCN k¦g¶t$ yL¥T FላጎT UR y¸ÃStœSR -Nµ‰ |r›T
xlmñ„½
 y†n!vRs!tE kFt¾ xm‰éC mlêw_ xm‰„ bqE LMD bl@§cW xÄÄ!S
ሃ§ðãC mÃZ½
 lkFt¾ TMHRT xê°Â TMHRT ¸n!St&R¼yTMHRT xGÆBnTÂ _‰T
¥rUgÅ x@jNs! l¸ÃwÈcW y_‰T mSfRèC ytlÆ mm¶ÃãC y¥Ygz#
tÌ¥TN btmlkt xSgÄJnT ÃlW |R›T xlmzRUT ናቸው።
 TMHRT xê°Â TMHRT ¸n!St&R¼yTMHRT xGÆBnTÂ _‰T ¥rUgÅ x@jNs!
l¸ÃwÈcW y_‰T mSfRèC ytlÆ mm¶ÃãC y¥Ygz# tÌ¥TN
btmlkt xSgÄJnT ÃlW |R›T xlmzRUT ናቸው።

7.ክትትልና ግምገማ
 ዓመታዊ የትምህርትዘርፍ ልማት ፕሮግራም የአፈጻጸምና የጋራ ግምገማ፣
 ዓመታዊ የትምህርት ጉባኤ፣
 ወቅታዊ የፋይናንስና ፊዚካል አፈጻጻም ሪፖርት፣
 አመታዊ የትምህርት ስታስቲካዊ መረጃ ሪፖርት፣
 ከክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊዎች ጋር በየሁለት ወሩ የሚካሄድ ቋሚ የጋራ ስብሰባ፣

68
 ከዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች ጋር በየሶስት ወሩ በቋሚነት የሚደረግ የሩብ ዓመት
ግምገማ፣
 የትምህርት ዘርፉን የሚደግፉ አጋሮች፣ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴርና ክልሎች
የተሳተፉበት በትምህርት ተቋማት፣ በወረዳና ክልል ትምህርት ቢሮዎች በመገኘት
በየዓመቱ የሚደረግ የጋራ ግምገማ፣
 በ4ኛ፣ በ8ኛ፣ በ10ኛና በ12ኛ ክፍል ደረጃዎች በየሶስት ዓመቱ የሚካሄድ የተማሪዎች
የትምህርት ቅበላ ጥናት፣

8. ትኩረት የሚሹ ጉዳዮችና ማጠቃለያ

ሀ. ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች


 የቅድመ-መደበኛ ትምህርት ተሣትፎን ማሳደግ
 የአጠቃላይ ትምህርት ጥራት ማሻሻያ ፓኬጁን መተግበር
 የትምህርት ተደራሽነትንና ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ
 የጎልማሶች ትምህርትን ማስፋፋት
 የሣይንስና ሒሣብ ትምህርት ስትራቴጅን ተግባራዊ ማድረግ
 የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ስትራቴጅን መተግበር
 y†n!vRs!tE xm‰R yLMD X_rTN lmQrF wd xm‰R kmMȬcW bðT
bqE yxStÄdRÂ xm‰R SL-Â XNÄ!Ãgß# ማድረግ፣
 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማዊ ለውጥን ማረጋገጥ
 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማዊ ለውጥን ማረጋገጥ

ለ. ማጠቃለያ

በአጠቃላይ በዕቅዱ ውስጥ የተቀመጡት ዓላማዎችና ግቦች ትኩረት ያደረጉት በየደረጃው


ጥራት ያለው ትምህርትን ማረጋገጥ ነው፡፡ በመንግሥትም ይሁን በግል የሚካሄዱ
የትምሀርት ፕሮግራም ጥራትን ማዕከል አድርገው የሚጠበቀውን ደረጃ እስካላሟሉ ድረስ
በዘርፉ ሊቀጥሉ አይገባም። ከዚህ አኳያ የመንግስት አካላት፣ የትምህርት ፈጻሚ አካላትና
ህብረተሰቡ በአጠቃላይ ጥራት ያለው ትምህርትን የማረጋገጥ አጀንዳ ቁልፍ አጀንዳቸው
አድርገው ሊረባረቡ ይገባል። ይህ ዕውን ካልሆነ ግን ሁሉም ነገር ዋጋ አልባ ይሆናል።

69
ጥራት ያለው ትምሀርት ለሁሉም!

70

You might also like