Recomendation For Shewa

You might also like

Download as doc, pdf, or txt
Download as doc, pdf, or txt
You are on page 1of 3

ለ፡ ሸዋ ጥጥ መፊልፈያ ኃ.የተ.

ግ/ማህበር

ጉዳዩ፡ የጥጥ መዳመጫ ፋብሪካዎች ክፍተትና መስተካከል የሚኖርባቸውን ጉዳዮችን


ይመለከታል፡፡

የጨርቃጨርቅና አልባሳት ኢንዱስትሪ ዘርፍ በኢንዱስትሪ ልማት ስትራቴጂው ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት


የዘርፉን ልማት ሊያጐለብቱ ይችላሉ ተብለው የታመነባቸው የተለያዩ የፖሊሲ፣ የአደረጃጀትና የድጋፍ
ፕሮግራሞች ተነድፈው ተግባራዊ በመደረግ ላይ ይገኛሉ፡፡ ከሚሠጡት ድጋፎች አንዱ የዘርፉ የምርት
እሴት ስንሰለቶች እርስ በእርሳቸው በግብአት ብዛትና ጥራት ተደጋግፈውና ተመጋግበው የመራመድ አቅም
እንዲኖራቸው ማድረግ ነው፡፡ ለጨርቃጨርቅ ኢንዱስትሪ ግብዓትነት ከሚያገለግሉ ምርቶች ውስጥ ጥጥ
ዋነኛውና አንደኛው እንደመሆኑ መጠን የጥጥ አቅርቦትን አስተማማኝ ከማድረግ በተጓዳኝ የሚቀርበው
ጥጥ ጥራቱን የጠበቀ እንዲሆን የማድረግ ስራ ልዩ ትኩረት ሊሠጠው የሚገባ ተግባር ነው፡፡

የጥጥ መዳመጫ ፋብሪካዎች የጥጥ ጥራትን ከመጠበቅ አንጻር ያላቸው ሚና ከፍተኛ በመሆኑ አስፈላጊው
ጥንቃቄ ተደርጎ መመረት እንዳለበት ይታወቃል፡፡ ሆኖም ግን የሀገራችን ጥጥ መዳመጫ ፋብሪካዎች ምርት
አያያዝና አሰራር ስርዓት ሲታይ ለምርቱ ጥራት የሚሰጠው ትኩረት አነስተኛ መሆኑ ነው፡፡ በአብዛኞቹ ጥጥ
መዳመጫ ፋብሪካዎች ጎልተው ከሚታዩ ችግሮች ውስጥ ወቅቱን ጠብቆ አለመዳመጥና ለረጅም ጊዜ
ማቆየት፣ በቂ የማከማቻ መጋዘን ባለመኖሩ ለዝናብና አቧራ ተጋላጭ መሆኑ፣ አስፈላጊ ማሽነሪዎች
ተሟልተው አለመገኘት፣ ዘመናዊ የአመራረት ሂደት አለመከተል እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡ ይህ ሂደትን
የጥጥ ጥራትን የሚቀንስ በመሆኑ የጨርቃጨርቅ ፋብሪካዎችን ገዥ ከማሳጣቱ በተጨማሪ አገሪቱ
ከዘርፉ ልታገኝ በምትችለው የውጭ ምንዛሬ ገቢ ላይ ተጽዕኖ እያሳደረ ይገኛል፡፡

የጨርቃጨርቅ ፋብሪካዎች ጥራት ያለው ምርት ለገበያ አቅርበው ተወዳዳሪ መሆን ካልቻሉ የጥጥ
መዳመጫ ፋብሪካዎች የገበያ ድርሻም አብሮ የሚቀንስ መሆኑ አያጠራጥርም፡፡ አጠቃላይ እሴት
ሰንሰለቱን ውጤታማ ከማድረግ አንጻር ዘመናዊ የአመራረት ሂደት የሚከተልና አስፈላጊው መሰረተ
ልማት የተሟላለት የጥጥ መዳመጫ ፋብሪካ ሊኖር ይገባል፡፡ በመሆኑም የሀገራችን የጥጥ መዳመጫ
ፋብሪካዎች ከመሰረተ ልማትና አመራረት ሂደት አንጻር ያሉበትን ወቅታዊ ሁኔታ ለመረዳት
በ 16(አስራ ስድስት ) ፋብሪካውች የዳሰሳ ጥናት በማድረግ ለመዳመጫ ፋብሪካ ባለ ሀብቶች እና
ሌሎች ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለ ድርሻ አካላት እንዲቀርብ ተደርጓል፡፡

የጥናቱ ዋነኛ ዓላማ እያንዳንዱ ፋብሪካ ካለው የመሰረተ ልማትና አመራረት ሂደት በመነሳት
ደረጃውን በኮከብ መለየትና በቀጣይ መወሰድ ስላለባቸው እርምጃዎች መፍትሄ መጠቆም ነው፡፡
ስለሆነም ከአንድ ኮከብ (ዝቅተኛ ደረጃ ) እስከ አምስት ኮከብ (በጣም ጥሩ ደረጃ ) ደረጃዎች
በመስጠት የእያንዳንዱን ፋብሪካ ወቅታዊ ሁኔታ ለማመላከት ተሞክሯል፡፡ አንድ ኮከብ ደረጃ ውስጥ
ለመግባት በተቀመጡ መስፈርቶች ሲመዘን አማካይ ውጤቱ 50 በመቶ መምጣት ያለበት ሲሆን
አምስት ኮከብ ለመግባት ደግሞ አማካይ ውጤቱ ከ 90 በመቶ በላይ መሆን ይኖርበታል፡፡

የሸዋ ጥጥ መዳመጫ ፋብሪካ ጥናቱ ከተካሄደባቸው ፋብሪካዎች ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ከላይ
በተቀመጠው የኮከብ ደረጃ መሰረት የፋብሪካው አማካይ ውጤት 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ
ሊሆን ባለመቻሉ ከደረጃ በታች በሚል ተይዟል፡፡ ፋብሪካው ዝቅተኛ ደረጃ ላይ እንዲወድቅ ካደረጉ
ምክንያቶች ውስጥ ዋና ዋናዎቹ ቀጥሎ የተዘረዘሩት ናቸው፡፡

 የቅድመ ማጣሪያ (pre cleaner) ማሽን አለመኖር


 የድህረ ማጣሪያ (lint cleaner) ማሽን አለመኖር
 በጣም ያረጀ እና በመለዋወጫ እጥረት የተጎዳ ጂን ስታንድ (Gin stand) ማሽን እንዲሁም
የማሽኑ ሞዴል ገበያ የሌለ መሆኑ
 የማሽኖች ተሽከርካሪ አካላት (ፑሊዎች ) ያለመሸፈን እና ለሰራተኞች ደህንነት አስጊ መሆኑ
 በመዳመጫ ደረጃ ሊኖሩ የሚገባቸው የርዝመት መለኪያ፣ንጣት ደረጃ (grading charts)
የእርጥበት መጠን መለኪያ፣አነስተኛ ሚዛን አለመኖር
 ጥጥ በጣም ደረቅ በሚሆንበት ወቅት ውሃ ለመርጨት የሚያስችል (moisturizer)
አለመኖር
 የስራ ቦታ ጽዳት አጠባበቅ ደካማነት
 የጥገና ፕሮግራም አለመዘጋጀቱ ( maintenance plan for daily, weekly, monthly
and yearly activities)
 የጥጥ ጥራትን የሚያሳዩ መረጃዎች አለመኖር እና ቁጥጥር አለመደረጉ
 የብናኝ ማስወገጃ መስመር (Cyclone disposal line) የተበላሸ በመሆኑ የስራ ቦታ
በአቧራ መታፈንና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡
ስለሆነም ከጥጥ ግብአት አቅርቦት አንጻር እያጋጠመ ያለውን የጥራት ችግር ለመቅረፍ በጥናቱ በተቀመጡ
የመፍትሄ ሀሳቦች መሰረት የጥጥ መዳመጫ ዘርፉን በአ ጭርና የረጅም ጊዜ ዕቅድ ለመደገፍ አስፈላጊው
ድጋፍና ክትትል እንዲደረግ በመንግስት በኩል እንደ አቅጣጫ ተይዟል፡፡ ለዚህ ዓላማ መሳካት ባለሀብቶች
የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ትልቅ ድርሻ ይኖረዋል፡፡ በመሆኑም ባለሀብቶቹ በአጭር ጊዜና በራሳቸው አቅም
ሊፈቷቸው የሚችሉ ተግባራትን ቅድሚያ በመስጠት ለጥጥ ጥራቱ መጠበቅ የበኩላቸውን ሚና ማበርከት
እንደሚጀምሩ ይጠበቃል፡፡ ስለሆነም ሸዋ ጥጥ መዳመጫ ፋብሪካ በአጭር ጊዜ ትኩረት ሰጥቶ ሊፈታቸው
ከሚገቡ ተግባራት ውስጥ፤

 ፋብሪካው በአሁኑ የጥጥ ማስቀመጫ መጋዘን ያስገነባ ቢሆንም በተያዘው የምርት ዘመን
በስፋት ሊመጣ የሚችል በቂ የማከማቻ ቦታ ማዘጋጀት
 ጥጥን ከዝናብና እርጥበት ሊከላከል የሚችል በቂ መሸፈኛ እና የሲሚንቶ ወለል /ርብራብ
ማዘጋጀት
 የጥገና ፕሮግራም ማዘጋጀት ( maintenance plan for daily, weekly, monthly
and yearly activities)
 በቂ መለዋወጫ መያዝ
 የማሽኖች ተሽከርካሪ አካላትን (ፑሊዎች ) መሸፈን እንዲሁም ለሰራተኞች ደህንነት
አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ
 የስራ ቦታ ጽዳት አጠባበቅን ማሻሻል
 የፋብሪካውን የጥጥ ብናኝ ማስወገጃ መስመር እና ፋን ማስተካከል
 በመዳመጫ ደረጃ ሊኖሩ የሚገባቸው የርዝመት መለኪያ፣ንጣት ደረጃ (grading charts)
የእርጥበት መጠን መለኪያ፣አነስተኛ ሚዛን አለመኖር
 ጥጥ በጣም ደረቅ በሚሆንበት ወቅት ውሃ ለመርጨት የሚያስችል (moisturizer)
አለመኖር
 ከጥጥ ጋር የተቀላቀሉ በዕድ ነገሮችን ቀጣይነት ባለው መልኩ የመለየት ስራ በመስራት
ዘርፉን ለማሻሻል ጥረት ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
በሌላ በኩል በመካከለኛ ጊዜ መፈታት ያለባቸውን ቴክኖሎጂ የማዘመንና መሰረተ ልማት የሟሟላት
ስራዎች ከመንግስት ጋር በመቀናጀት ለማከናወን አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እና ፕሮፖዛል እንድታዘጋጁ
እየገለጽን ለመነሻ የሚሆኑ ዝርዝር የመፍትሄ ሀሳቦችን ከዚህ ደብዳቤ ጋር - ገጽ አባሪ አድርገንላችኋል፡፡

You might also like