Professional Documents
Culture Documents
Islamic Sci
Islamic Sci
Islamic Sci
ጃቢር ኢብኑ ሀያን የመካከለኛው ዘመን የኬሚስት ሊቁ ጀብር የሚባል ሲሆን “የኬሚስትሪ አባት” በመባል
በስፋት ይታወቃል።
ጃቢር በኢማም ጃዕፈር አስ ሣዲቅ እና የኦማያድ ሠርወ መንግስት ልዑል በሆነው ኻሊድ ኢብኑ የዚድ ሥር
ሆኖ ነው ትምህርቱን የተከታተለው። ህክምናን የተማረው ገና በልጅነቱ በባርማኪ ወዚር ቤት ሆኖ በአባሲድ
አገዛዝ ኸሊፋ ሃሩን አር ረሺድ ዘመን ነበር። ለባርማኪስ መውደቅ የተወሰነ ሚና የነበረው ሲሆን በወቅቱም
ምድር ቤት ውስጥ ታስሮ ነበር። ጃቢር የሞተው እ.ኤ.አ. በ803 ነው።
ማክስ ሜየርሃፍ (Max Mayerhaff) እንዳለውም በአውሮፓ የኬሚስትሪ እድገት በቀጥታ መመለሻው ጃቢር ኢብኑ ሀያን ነው
ብሏል።
ጃቢር በኬሚስትሪ ዘርፍ ትልቅ አስተዋፅኦ ነበረው። ወደ ዘመናዊው ኬሚስትሪ ለማደግ መሠረት የሆነውን
ተግባር ተኮር (experimental investigation) የኬሚስትሪ ምርምርን ለዓለም ያሣወቀው እርሱ ነበር።
እጅግ የታወቀው ላቦራቶሪው ፍርስራሹ ለዘመናት የቆየ ቢሆንም ነገር ግን ጃቢር እውቅናን የተጎናፀፈው
በመቶ ትላልቅ ድርሰቶቹ ምክኒያት ነበር። ከነኚህም መካከል ሀያ ሁለቱ ከኬሚስትሪ ጋር የተያያዙ ናቸው።
የጃቢር ተግባር ተኮር ምርምር ከፍተኛ ስኬት የነበሩት የተለያዩ ማዕድናትን እና ሌሎችን አሲዶችን ማግኘቱ
ላይ ነበር። እነኚህም ለመጀመሪያ ጊዜ በርሱ አለምቢክ (አለንቢቅ/alembic) የማጣሪያ መሣሪያ ውስጥ
የተዘጋጁ ነበሩ። ለኬሚስትሪ መሠረታዊ ባህሪ በርካታ አስተዋፅኦዎችን ከማድረጉም በላይ አዳዲስ ውህዶችን
(compounds) እና የኬሚካል አሠራር ዘዴዎችን እንዲሁም በርካታ ተግባር ተኮር የሆኑ ኬሚካላዊ
ሂደቶችን (applied chemical processes) አጎልብቷል። በዚህም ሰፊ ሥራው የተነሣ በተግባር ተኮር
ሣይንስ ዘረፍ መሪና ሞዴል ተጠቃሽ ለመሆን ችሏል። በዚሁ ዘርፍ ካስመዘገባቸው ስኬቶች መካከል የተለያዩ
ብረታ ብረቶች ስለሚዘጋጁበት ሁኔታ፣ የሽቦ (steel) አሠራር፣ የልብስ አነካከር፣ የቆዳ አዘገጃጀት፣ ውሃ
የማያስገቡ ልብሦችን ስለ መቀባት፣ በመስታወት ሥራ ማንጋኒዝ ዳይ ኦክሣይድን መጠቀም፣ ዝገትን
መከላከል፣ በወርቅ መሙላት፣ ቀለማትን መለየት፣ ቅባቶች እና የመሣሰሉት ይጠቀሳሉ። በዚህ ረጅምና እልህ
አስጨራሽ የተግባር ምርምር ወቅት ወርቅን ለማሟሟት የሚያስችል አኳራጂያ ማግኘት ችሏል። አለምቢክ
የሱ ትልቅ ፈጠራ ሲሆን ይህም የማጣራትን ሥራ ቀላልና ስልታዊ በሆነ መልኩ እንዲሆን አድርጎታል። ጃቢር
ከዚህም በላይ በተግባር ምርምሮችና በትክክለኛነታቸው (experimentation and accuracy) ላይ
ትልቅ ትኩረት የመስጠትን መሠረት ጥሏል።
ጃቢር ከባህሪያቸው በመነሣት ንጥረ ነገሮችን (substances) በሦስት የተለያዩ አይነቶች ይከፍላቸዋል።
የመጀመሪያው ሰፒሪት/መንፈስ ማለትም በሚሞቁበት ጊዜ የሚተኑት ሲሆኑ እነኚህም ካምፎር፣ አርሰኒክና
አሞኒየም ክሎራይድን የመሣሰሉትን ይይዛል። ሁለተኛው ብረት ነኬ ሲሆን ይህም ወርቅን፣ ብርን፣ መዳብን፣
ሊድ እና ብረትን ያጠቃልላል። በሦስተኛው ምድብ ውስጥ ደግሞ ወደ ዱቄትነት/ብናኝነት የሚለወጡ
ነገሮችን አስቀምጧል። ይህም ክፍፍል ኋላ ላይ ነገሮችን ብረት ነኬ (metals)፣ ብረት ነኬ ያልሆኑ (non-
metals) እና በቀላሉ የሚተኑ (volatile) ተብለው ለተከፈሉበት ሁኔታ መሠረትን ጥሏል።
ጃቢር ምንም እንኳ በኬሚስትነቱ ቢታወቅም እንደ አልኬሚያ ባለሙያ ግን ምናባዊ የተከበሩ ማእድናት
አዘጋጃጀት ለይ ትኩረት አድርጎ የተንቀሣቀሠ አይመስልም። ባይሆን ትልቁን ጉልበቱንና ጊዜውን የጨረሠው
መሠረታዊ የሆኑ ኬሚካለዊ አሠራሮች አንዴት እንደሚያድጉና በኬሚካል ፅግበራ (chemical
reactions) ዙሪያ ነበር። በዚህም የኬሚስትሪ ሣይንስ ከአልኬሚ ምናባዊ እንቆቅልሽ ጎልብቶ ይወጣ ዘንድ
ረድቷል። በኬሚካላዊ ፅግበራ በርካታ የተለያዩ ውጤቶች ሊገኙ እንደሚችሉ አፅንኦት ሠጥቷል። በዚህም
የተነሣ የኮንስታንት ፕሮፖርሽን ህግ (the law of constant proportions) የማግኘቱ መንገድ ቀላል
ሊሆን ችሏል።
ጃቢር ኢብኑ ሀያን
በጃቢር የፅሁፍ ክምችት ውስጥ በርካታ የመፅሃፍ ቅጂዎች ተካተዋል። ከኬሚስትሪ በተጨማሪ ለህክምና እና
ለሥነ ከዋክብት ጥናትም የጃቢር አስተዋፅኦ ከፍተኛ ነው። በኬሚስትሪ ዙሪያ ከሚጠቀሱ መፅሃፎች መካከል
“ኪታብ አል-ኪሚያ” እና “ኪታብ አስ-ሰቢኢን” ይጠቀሳሉ። መፅሃፎቹም ወደ ላቲን እና በርካታ የአውሮፓ
ቋንቋዎች ተተርጉመዋል። እነኚህም ትርጉሞች በአውሮፓ ውስጥ ለክፍለ ዘመናት ገነው የቆዩ ሲሆን
ዘመናዊዉ ኬሚስትሪ መከሠትም አቢይ ምክኒያት ነበሩ። ጃቢር ይጠቀምባቸው የነበሩና የዛሬው
የአውሮፓውያኑ ቋንቋዎች የሚጠቀሙባቸው አልካሊ (alkali) እና የመሣሠሉት በርካታ ከምርምሩ ጋር
የተያያዙ ቃላት የሳይንስ መዝገበ ቃላት ክፍል ሊሆኑ ችለዋል። ከመፅሃፎቹ ታርመው ለህትመት የበቁት
የተወሰኑት ብቻ ሲሆኑ በርከት ያሉትና በዐረቢኛ ቋንቋ የተፃፉት ግን ዛሬም ድረስ ትኩረት ተነፍጎአቸው
ሣይታተሙ ተቀምጠዋል።
በርካታ ግኝቶቹ ለምሣሌ አሲድ ለመጀመሪያ ጊዜ ማግኘቱ በተለይ ናይትሪክ፣ ሃይድሮ ክሎሪክ፣ ሲትሪክ፣ እና
ታርታሪክ አሲድ እና ስልታዊ ሙከራዎቹ እጅግ የተዋጣላቸው ነበሩ። ይህም በመሆኑ ነው ይህ ሰው
የዘመናዊው ኬሚስትሪ አባት (father of modern chemistry) ተብሎ ሊታይ የቻለው። ማክስ
ሜየርሃፍ (Max Mayerhaff) እንዳለውም በአውሮፓ የኬሚስትሪ እድገት በቀጥታ መመለሻው ጃቢር
ኢብኑ ሀያን ነው ብሏል።
Share on Facebook
ጃቢር ኢብኑ ሀያን
በፊቅሂ እውቀትም በሻፊዒይ መዝሀብ እውቀቱ የበቃ (ኤክስፐርት) ሲሆን የታወቀ ሃኪምም ነበር፡፡
በህክምናና በህግ እውቀት ከፍተኛ ትምህርት ካገኘ በኋላ ወደ ካይሮ በመጓዝ በታዋቂው ናስሪ ሆስፒታል
በዋና ሥራ አስኪያጅነት የተሾመ ሲሆን እዚያም ሣለ ለታዋቂው የቀዶ ጥገና ባለሙያ ኢብኑ አል ቁፍ አል
መሲሂን ጨምሮ ለበርካታ የህክምና ጠበብቶች ሥልጠና ሠጥቷል። ከዚህም ሌላ በካይሮ በሚገኘው
መንሱሪያ ትምህርት ቤት ግልጋሎት ሠጥቷል፡፡ የሞተውም እ.ኤ.አ በ678 ሲሆን የግል ቤቱን፣ ቤተ-
መፅሃፍቱንና ክሊኒኩን ለመንሱሪያ ሆስፒታል በስጦታነት አበርክቷል፡፡
ጃቢር ኢብኑ ሀያን
የኢብኑ አን-ነፊስ ዋነኛ አስተዋፅኦዎቹ በህክምና ዙሪያ ያተኮሩ ናቸው፡፡ አቀራረቦቹም በቀደሙት ሥራዎች
ላይ ዝርዝር አስተያየቶች መፃፍን፣ እነሱን በጥልቀት መመርመርንና የራሱን ወጥ የሆኑ አስተዋፅኦዎች
መጨመርን ያካትታሉ፡፡ ጉልህ ተፅእኖ ከነበራቸው ትላልቅ ወጥ ሥራዎቹ መካከል ከሦስት ምእተ አመታት
በኋላ በዘመናዊው ሣይንስ እንደገና የተደረሠበት የደም ዝውውርን ማግኘቱ ይጠቀሳል፡፡ ሣንባ ውስጥ
የሚገኙትን ነገሮች በትክክል ለመግለፅ የመጀመሪያው ሰው ሲሆን ስለ ብሮንካይ ምንነት፣ በሰው ልጅ የደም
ቱቦዎችና በአየርና በደም መካከል ስለሚከሠተው አጠቃላይ ሁኔታ በዝርዝር አስፍሯል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ
ልብ ላይ የሚገኘውን የኮሮናሪ አርተሪን (ልብ ላይ የሚገኝ የደም ሥር) ጥቅም በመግለፅ የልብ ጡንቻዎችን
የሚመግብበትን ሁኔታ ተንትኗል፡፡
ሁሉም ልጆች በዚያ የልጅነት ዕድሜ ከጎናቸው ሊያጧት የማይፈልጉትንና የሚወደውን ምግብ
የምታዘጋጅለት፣ የምታጫውት፣ በደስታም ሆነ በሐዘን ወቅት ከጎን የምትሆን እናት ከአጠገባቸው ባለመኖሯ
ምክንያት በዉስጣቸው አስከፊ እና ትልቅ የብቸኝነት ስሜት ተሰምቷቸው አድገዋል… አሕመድ። አባታቸው
የቤተሰቡን የዕለት ወጭ ለመሸፈንና የአባትነት ኃለፊነታቸውን ለመወጣት ሌት ተቀን ይታትሩ ነበር።
ታሪካቸውን የምናወሳላቸው አሕመድ ዲዳት፣ ምንም እንኳ በርካታ ችግሮች የተጋረጡባቸው ቢሆንም
በልጅነታቸው ከትምህርት ባልንጀሮቻቸው መካከል እጅግ ጎበዝ እና ቀዳሚ፣ ብልህ ልጅ ነበሩ። ዕድሜያቸው
ጃቢር ኢብኑ ሀያን
አሥራ ስድስት ዓመት ሲሆን እርሣቸውንና ቤተሰባቸውን የከበበውን የድህነት ማቅ ለመግፈፍ ሲሉ
በራሣቸው ሥራ ጀመሩ። ሱቅ ዉስጥ ሰዎች ዘንድ ተቀጥረው ሻጭ ሆኑ።
ዛሬ ላይ ሆነን ከተወለዱና ወደዚህች ምድር ከመጡ ድፍን መቶ ዓመት ሊሞላቸው አንድ ዓመት ብቻ
የቀራቸውንና በሕይወት ካለፉ ደግሞ 12 ዓመት የሆናቸው ታላቁን የኢስላም ፈርጥ አሕመድ ዲዳትን
ስናስብ ትክክለኛውን የእስልምናን ጥሪና አስተምህሮ ለማድረስ የተጉ ጎበዝ ፈረሠኛ ብቻ ሆነው አይደሉም
የምናገኛቸው። በምላስም ሆነ በብዕራቸው እስልምናን ከምዕራባውያን ጥቃትና የሥም ማጥፋት ዘመቻ
በመከላከል ከፍተኛ አስተዋጽኦ ካበረከቱ የሙስሊም ዓለማቀፍ ስብእናዎች መካከል አንዱ መሆናቸውን
እንረዳለን።
ዲዳት የጽሑፍም የመድረክም አንበሳ ናቸው። መድረክ አያያዛቸው፣ ሞገሳቸውና የንግግራቸው ሁኔታ ሁሉ
ሀሳብን ይሰርቃል፣ ልብን ይገዛል። መድረክ ላይ የትኛውም ርቱዕ ተናጋሪ አይረታቸውም። በንግግራቸውና
በክርክራቸውም የገጠሟቸውን ብዙዎችን መሳቂያ መሳለቂያ አድርገዋል። አንዲት ቃል የተናገሩ እንደሆን ያች
ቃል በዓለም ዙሪያ አሉ በተባሉ ጳጳሶች ጉያ በመግባት ታሸብራቸዋለች፣ ዕረፍትም ትነሳቸዋለች።
አሕመድ ሑሴን ቃሲም ዲዳት የተወለዱት በ1918 ዓ.ል በህንድ ሱራት ነው። አባታቸው ሑሴን ቃሲም
ዲዳት በደቡብ አፍሪካ ዉስጥ በልብስ ሰፊነት ይሠሩ ነበር።
አሕመድ ዲዳት በ1927 ዓ.ል አባታቸው ወደሚገኙበት ። በወቅቱ የዘጠኝ ዓመት ዕድሜ ታዳጊ ነበሩ።
ህንድን ከለቀቁ በኋላ እናታቸው ሞተች። አላህ ይዘንላት። አሕመድ እስከ ስድስተኛ ክፍል ድረስ
ትምህርታቸውን ቀጠሉ። ከዚያ በኋላ ድህነት አላፈናፍን አላቸው። የትምህርት ክፍያቸውን እንኳን መክፈል
እስኪሳናቸው ሲደርሱ ትምህርታቸውን ለማቋረጥ ተገደዱ።
ጃቢር ኢብኑ ሀያን
አባታቸው ልጃቸው ያቋረጠውን ትምህርቱን ይቀጥል ዘንድ ከብዙ ነጋዴዎች ጋር ቢነጋገሩም ምንም መፍትሄ
ሊያገኙ አልቻሉም። ስለዚህም ሌላ አማራጭ መፈለግ ያዙ።
አሕመድ ዲዳት በተለያዩ ሙያዎች ላይ በመሥራት ዕድላቸውን ሞክረዋል። በብዙ የንግድ ቦታዎች ላይ
ሠርተዋል። ከዚያም ቤተሰባቸው የሚኖርበትን ደርባን ከተማን በመልቀቅ ከአንድ የተከበረ ሙስሊም ሱቅ
ዉስጥ ለመሥራት ከደርባን ሀያ አምስት ማይል ርቀው ተጓዙ። እዚያም ተቀጥረው ሻጭ ሆነው ቆዩ።
ቀጥሎም ትላልቅ መኪናዎችን ከሚያመርት አንድ ፋብሪካ ዉስጥ ሹፌር ሆነው ተቀጠሩ። ቀጥሎም የገቢና
ወጭ ምርቶች መዝጋቢ ሆነው ሠሩ። ከዚያም የፋብሪካው ኃላፊ ሆኑ።
በ1936 በናታል ደቡባዊ ዳርቻ በቢሮ ዕቃዎች ሻጭነት ተቀጥረው በመሥራት ላይ እያሉ በክርስቲያኖች
ሴሚናር ላይ ሙስሊሞችን ወደ ክርስትና ለመለወጥ የተሰማሩ የተወሰኑ ሚሽነሪዎችን አገኙ። ሰዎቹ
የእስልምና ሃይማኖት መልዕክተኛ ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) እስልምናን ያስፋፉት በሰይፍ ኃይል እንደሆነም
ይናገሩ ነበር። የዚህ ዓይነቱ ውንጀላ ሸይኽ አሕመድ ዲዳትን ይበልጥ እንዲነሳሱና ወደሃይማኖት ንፅፅር
ጥናት እንዲገቡ አድርጓቸዋል።
በ1949 ዓ.ል ወደ ፓኪስታን በመጓዝ በአንድ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ዉስጥ ለሦስት ዓመታት ያህል
አገልግለዋል።
በ1996 ዓ.ል እዚያ ከሚገኙ ትላልቅ ጳጳሶች ጋር የተሳካ ክርክር አድርገው ከአውስትራሊያ ሲመለሱ
አንገታቸው ሥር ባገኛቸው ድንገተኛ ህመም ምክንያት ሙሉ በሙሉ ፓራላይዝድ በመሆን ለዘጠኝ ዓመታት
ያህል ፍራሽ ላይ ወድቀው ቆዩ።
አሕመድ ዲዳት በመጨረሻም ወደማይቀረው ሞት እና ወደ አላህ ጉርብትና የሄዱት በ2005 ዓ.ል በሰማኒያ
ሰባት ዓመት ዕድሜአቸው በእጅጉ የሚወዱትን የአላህን (ሱ.ወ) ቃል ቁርኣንን በማዳመጥ ላይ እያሉ ነበር።
በአሕመድ ዲዳት ሕይወት ዉስጥ ያልተጠበቁ የአላህ ጥበቃዎችና እንክብካቤዎች ታይተዋል። አላህ (ሱ.ወ.)
ነገሮችን አስተካክሎላቸዋል፣ ሰበቦችንም አሟልቶላቸዋል። የመጀመሪያው – ለንባብ ያላቸው ጉጉት እጅግ
ከፍተኛ መሆኑ ነው። በብቸኝነታቸው ጊዜያት ሁሉ መጽሐፎች መልካም ወዳጆቻቸው ነበሩ። በዚህም
የመጽሐፎች ጥብቅ ጓደኛ ሆነው ኖሩ። መጽሐፍ፣ መጽሄት ይሁን ጋዜጣ አሊያም ሌላ ነገር በእጃቸው
የገባውን ሁሉ በጥልቅ የመረዳት ስሜት ሳያነቡ አያልፉም ነበር። በቤተመጽሐፋቸው ዉስጥ ያላነበቧቸው
አንድም መጽሐፍ የለም። ከዚህም ጎን ለጎን አላህ ጥልቅ የመረዳት ተሰጥኦ እና የመጠቀ እይታን፣ አንደበተ
ርቱእነትን፣ በነገሮች ስኬትና ድልን፣ ትግልና ብርታትን አላህ ለግሷቸዋል።
ጃቢር ኢብኑ ሀያን
ለማንበብ ያላቸው ከፍተኛ ጉጉት ከባበድ መሠናክሎች ሁሉ እንዲገሩላቸው እገዛ አድርጎላቸዋል። ከእስልምና
መከላከል እና ጠበቃው መሆን ትልቁ ዓላማቸውና ጭንቀታቸው ነበር። እስልምና የሚነካውን ሰው ሁሉ
ባገኙበት በተለያዩ ጉዳዩች ላይ ይከራከሩ ነበር። በዚህም በአዕምሮ ምጥቀትም ሆነ በክርክር ችሎታ ዘወትር
ይረቷቸው ነበር። ከዚህም ባለፈ ከፍተኛ የሆነ የቋንቋ ንግግር ችሎታ ነበራቸው።
ረሕመቱላህ ይህንን መጽሐፍ ያዘጋጁት ለክርስቲያኖች መልስ እንዲሆናቸው ነበር። በዋናነትም በመበረዝና
መከለስ፣ በሥላሴ ምንነት፣ በቁርኣን እውነትነትና በነቢይነት ዙሪያ አምስት ጥናቶች የተካተቱበት ነበር።
በወቅቱ የክርስትና ሚሽነሪዎች በሙስሊም ህንዶች መካከል ገብተው በሰፊው ይንቀሳቀሱ ነበር።
አሕመድ ዲዳት ሃይማኖታዊ ንጽጽር ጉዳዮች በሚገባ ካነበቡና በጥልቀት ከተረዱ በኋላ በማስረጃዎች እና
መረጃዎች በእጅጉ ታጥቀው በአዳራሽ ዉስጥ ትምህርት መስጠት ጀመሩ። ትምህርቱንም የሚሠጡት በጉዳዩ
ዙሪያ በቂ ዕውቀት ላላቸውና ለሌሎችም ወገኖች ነበር። ትምህርታቸው እጅግ ሳቢ እና ፋይዳውም የጎላ
ነበር። የአዳራሹን ኪራይም ሆነ የተለያዩ ወጭዎችንም የሚችሉት ራሣቸው ነበሩ።
አሕመድ ዲዳት የደዕዋ ትምህርት መስጠቱን በጆሃንስበርግ ቢጀምሩ ትልቅ አቀባበል ሊኖረው እንደሚችል
አሰቡና በ1958 ዓ.ል በደርባን ከተማ አዳራሽ የደዕዋ ትምህርታቸውን መስጠት ጀመሩ። እዚያ የሚገኘውን
ትልቁን መስጂድም ለደዕዋ ሥራው ማዕከል አደረጉት። እጅግ ጠንካራ እንቅስቃሴዎች በማድረጋቸውም
ሰዎች በብዛት እስልምናን መቀበል ጀመሩ። አሕመድ ዲዳት በእውነት መንገድ ላይ አንዳችም ነገር አይፈሩም
ነበር። በፓኪስታን ያሉበት ድረስ ሄደው ሦስት ቄሶችን በመከራከር አጣብቂኝ ዉስጥ ሲያስገቧቸው
ከርሣቸው የሚወጡ ቃላቶች በሙሉ በጀግንነትና በወኔ የተሞሉ ነበሩ።
የመድረክ ላይ አንበሳ
ልጃቸው ዩሱፍ ዲዳት አባታቸውን “የመድረክ አንበሳ’ ሲሉ ይገልጿቸዋል። በርግጥም ሸይኽ አሕመድ ዲዳት
በዋናነት በክርክር ስልታቸውና በማራኪ የመድረክ አቀራረባቸው ነው የሚታወቁት። ከዚህም በተጨማሪ
የተዋጣለት ፀሐፊም ናቸው። ከሀያ በላይ መጽሐፎችን የፃፉ ሲሆን በርካታ በራሪ ወረቀቶችንም አዘጋጅተው
በሚሊዮን የሚቆጠሩ ቅጂዎች በዓለም ዙሪያ ተበትነዋል። እነኚህ የህትመት ዉጤቶችም ብዙዎቹ ወደ
ልጃቸው ዩሱፍ ዲዳት የቀድሞው የደቡብ አፍረካ ፕሬዚዳንት ኔልሰን ማንዴላ ሥልጣን ላይ በነበሩበት ወቅት
በ1994 ዓ.ል ሳውዲ ዐረቢያን ሲጎበኙ ያሉትን ያስታውሳሉ። ማንዴላ እንዳሉት በሄዱበት ሁሉ ሰዎች
በተለይም ወጣቶች ስለታላቁ የሙስሊም ምሁር ስለ ዲዳት ሁኔታ ይጠይቋቸዋል። ለቴሌቭዥን ቃለምልልስ
ሲቀርቡም የጋዜጠኛው ቀዳሚ ጥያቄ ደቡብ አፍሪካ የሚገኙት ሸይኽ ዲዳት እንዴት ናቸው የሚል ነው።
ሸይኽ አሕመድ ዲዳት በዓለማቀፍ ደረጃ ከታዋቂ ሰዎች ጋር ያደረጓቸው በርካታ ክርክሮችን አድርገዋል።
ጎልተው ከሚጠቀሱት መካከል፡-
ጃቢር ኢብኑ ሀያን
1. ከጆን ጊልኽረስት ጋር ያደረጉት ክርክር – ጊልኽረስት ከቤኖኒ ደቡብ አፍሪካ ሲሆን በሃይማኖቱ
ክርስቲያን የሆነ ጠበቃ ነው። በ1975 ዓ.ል በኢየሱስ ክርስቶስ ስቅላት ዙሪያ ከዲዳት ጋር ክርክር
አድርገዋል።
2. ከጆሽ ማክዶዌል ጋር ያደረጉት ክርክር – አሕመድ ዲዳት በዓለማቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ
ያደረጉትና ሰፊ እውቅናም ያስገኘላቸው ክርክር ሲሆን በኦገስት 1981 በደርባን ደቡብ አፍሪካ
ነበር ያደረጉት። ጆሽ ማክዶዌል ታዋቂ የክርስቲያን ሰባኪ ነው።
የሮማው የካቶሊክ ጳጳስ ጆን ፖል በሙስሊሞች ጋር የጋራ ግንዛቤ መፍጠር፣ መከባበርና መነጋገር እንዲኖር
ጥሪ ካደረጉ በኋላ በ1984 ዓ.ል ዲዳት በቫቲካን አደባባይ ለህዝብ ክፍት በሆነ መልኩ ከጳጳሱ ጋር
ለመከራከር ሀሳብ አቀረቡ። ሆኖምግን ጳጳሱ ሀሳቡን አልተቀበሉም። የጳጳሱ ቢሮ መልስ ሊሠጣቸው
ባለመቻሉም በጥር ወር 1985 ዓ.ል አሕመድ ዲዳት ብፁዕነታቸው ከሙስሊሞች ጋር ድርድር ይደረግ
የሚል የድብብቆሽ ጨዋታ ይዘዋል የሚል አርዕስት የያዘ በራሪ ወረቀት አሠራጩ።
መጽሐፎቻቸው እና ንግግሮቻቸው
አሕመድ ዲዳት ከደርዘን በላይ የሆኑና በብዛት የተሠራጩ አነስተኛ መጠን ያላቸው መጽሐፎችን አዘጋጅተው
አሳትመዋል። ዲዳት የሠጧቸው ትምህርቶችና ያደረጓቸው ንግግሮችም በዋናነት የሚያተኩሩት በኢስላም
ክርስቲያን ሃይማኖት ንጽጽር ዙሪያ ነው። መጽሐፎቻቸውም የተዘጋጁት በመድረክ ላይ ያቀረቧቸውን
ትምህርቶችና ንግግሮች መሠረት አድርገው ነው። ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ያህል-
ዲዳት አራት አነስተኛ እውቅ መጽሐፎቻቸውን በአንድ ላይ በመጠረዝ ያሳተሙ ሲሆን 10,000 ኮፒ
የሚሆኑ መጽሐፎችን “The Choice” በሚል ስያሜ ነበር የታተሙት። የመጀመሪያው መጽሐፋቸው
በአፕሪል 1993 ዓ.ል የታተመው Islam and Christianity የተሠኘው ነው። ይህ መጽሐፍ በ1990ዎቹ
ዉስጥ ከፍተኛ እውቅናን የተጎናፀፈ ነበር። በሰሜን አሜሪካ በሚገኙ በርካታ ሚሽነሪዎችም በነፃ ታድሏል።
ጃቢር ኢብኑ ሀያን
መጽሐፉን በርካታ ማተሚያ ቤቶች በተደጋጋሚ ያሳተሙት ሲሆን በሁለት ዓመት ዉስጥ ብቻ 250ሺህ
ቀጥሎ ደግሞ ሁለተኛው ጥራዝ “The Choice” ስድስት አነስተኛ መጽሐፎችን በማካተት ታተመ። ዲዳት
በዐብደላህ ዩሱፍ ዐሊ ወደ እንግሊዝኛ ቋንቋ የተተረጎመው የቅዱስ ቁርኣን በሰፊው እንዲተዋወቅና
እንዲሠራጭ እገዛ አድርገዋል። በንግግራቸውም ዉስጥ በተደጋጋሚ ይጠቅሱት ነበር።
አሕመድ ዲዳት አላህ ይዘንላቸውና በደዕዋው ዘርፍ ለሙስሊሞች አዲስ መንገድ ያሳዩ ታላቅ ሰው ነበሩ።
ሕይወታቸውን በሙሉ በእስልምና እና በቁርኣን ላይ አንፀው ኖረዋል። በአላህ እና በመልዕክተኛው ማመን
ብቻውን በቂ እንዳልሆነና መልዕክታቸውን ትክክለኛው ጥሪ ካልደረሣቸው ሙስሊም ባልሆኑ ሰዎች መካከል
በማሠራጨትና በማስተማር ስለዚህች ዓለምም ሆነ ስለመጨረሻው ዓለም እንዲሁም ለዘመናት ስለ
እስልምና እና ቁርኣን የተሳሳተ ግንዛቤ የያዙ ሰዎችን አመለካከት አደገኛነት በማስተማር የሚገባቸውን ሐቅ
በእንግሊዝኛ ቋንቋ በጻፏቸው መጽሐፎችና ባሰሟቸው ዲስኩሮችና ክርክሮች ዓለማቀፍ ዝናን ያተረፉት
ሸይኽ አሕመድ ዲዳት በ1986 ዓ.ል ሃምሳ ዓመት ሙሉ እስልምናን ለማገልገል ስላበረከቱት አስተዋጽኦ
የንጉስ ፈሀድን ዓለማቀፍ ሽልማት አግኝተዋል።
አላህ አሕመድ ዲዳትን ይዘንላቸው። ከሰፊው የእዝነት ጀነቱም ያስገባቸው። ስለ ኢስላም ላደረጉት አስተዋጽኦ
ሁሉ መልካሙን ይመንዳቸው።
ኢማም አን-ነወዊ
0
5267
Share on Facebook
Tweet on Twitter
ጃቢር ኢብኑ ሀያን
አቡ ዘከሪያ ሙሕይዲን ኢብኑ ሸረፍ አን-ነወዊ ይባላሉ። የተወለዱት በሶሪያ ከሐውራን መንደር አንዷ
በሆነችው በነዋ ነው። ጊዜውም በ631 ዓ.ሂ ሲሆን ከደጋግ ወላጆች ነው የተወለዱት። ዕድሜአቸው አሥር
ዓመት ገደማ ሲሆን ቁርኣንን በቃላቸው ማጥናት እና ፊቅሂን በአንዳንድ ዑለማኦች እጅ መማር ጀመሩ።
በ649 ዓ.ሂ ትምህርታቸውን ለመቀጠል ብለው ከአባታቸው ጋር በመሆን ደማስቆ ወደሚገኘው የሐዲሥ
ማዕከል አቀኑ። እዚያም የረዋሒያ መድረሳን ተቀላቀሉ። መድረሳው ከታላቁ የኡመዉያ መስጂድ ጋር ተያይዞ
የተሠራ ነበር። በ651 ዓ.ሂ ከአባታቸው ጋር በመሆን ሐጅ አደረጉ። ከዚያም ወደ ዲመሽቅ (ደማስቆ)
ተመለሱ። እዚያም ሆነው ሙሉ ሀሳባቸውንና ፊታቸውን ወደ ዑለማኦች ማዕድ በማዞር ዕውቀት መቅሰም
ጀመሩ።
ኢማም ነው ለአላህ ያላቸው ፍራቻ በእጅጉ ይለያል። ለመሪዎችና አስተዳዳሪዎች መልካም ምክራቸውን
ያቀብላሉ። በጥሩ ያዛሉ፣ ከመጥፎ ነገርም ይከለክላሉ። ለኢማም አንነወዊ አላህ ይዘንላቸው – በሀያ አራት
ሰዓታት ዉስጥ አንድ ጊዙ ብቻ ማለትም ከዒሻ በኋላ ነበር የሚመገቡት። ከማንም ምንም ፈልገው
አያውቁም። ብዙን ጊዜ ለመሪዎች እና ለሚኒስቴሮቻቸው ይጽፉ፤ ለህዝቡም ሆነ ለሀገራቸው በሚጠቅም
ነገር ላይ ያመላክቱና ይመክሩ ነበር።
የዕውቀት ሕይወታቸው
ዲመሽቅ ከደረሱ በኋላ ያለው የዕውቀት ሕይወታቸው ሶስት የተለያየ ክፍል ነበረው።
ሁለተኛው – ዕውቀታቸውን የበለጠ ለማስፋት፣ በጥልቀትም ለማወቅ የጣሩበት ነው። በዚህም የተለያዩ
ዕውቀቶችን ፍለጋ አብዝተው ደክመዋል። በየቀኑ በተለያዩ ሸይኾች ላይ አሥራ ሁለት ያህል ትምህርቶችን
ይማሩ ነበር።
ሦስተኛው – ዕውቀትን መጠቀም፣ ማስተማርና ማሠራጨት። ይህንን የጀመሩት በ660 ዓ.ሂ ገና በሰላሳ
ዓመታቸው ነበር። አላህም (ሱ.ወ) ጊዜያቸውን ባርኮላቸዋል። በርግጥም ረድቷቸዋል። ጊዜያቸውን እጅግ
የሚገራርሙና የማይታመኑ ትላልቅ የሆኑ መጽሐፍት በመፃፍ ተጠቅመውበታል። በመጽሐፍቶቻቸው ዉስጥ
የሚጠቀሙት ገለፃ የለሰለሰና ገር፣ ማስረጃቸው ግልጽ፣ እይታቸው የተብራራ ነበር። ድርሰቶቻቸው
ዘመናትን ተሻግረው ዛሬም ድረስ በያንዳንዱ ሙስሊም ቤት ዉስጥ ይገኛሉ።
ኢማም ነወወዊ ጊዜያቸውን በሙሉ በዕውቀትና በትግበራው ላይ ያዋሉ ታላቅ ዓሊም ናቸው። ከፊሉን
ድርሰት ያዘጋጁበታል፣ ከፊሉን ይማሩበታል፣ ከፊሉን ደግሞ ይሰግዱበታል፣ ሌላውን ቁርኣን ለማንበብ፣
በጥሩ ነገር ለማዘዝና ከመጥፎ ለመከልከል ይጠቀሙበታል።
በቃል በማጥናት ሁኔታቸው (በሒፍዛቸው) ሲበዛ ፈጣን ናቸው። በአጭር ጊዜ ዉስጥ በርካታ መጽሐፎችን
ሐፍዘዋል። በዚህም የኡስታዛቸውን አቢ ኢብራሂም ኢስሓቅ ኢብኑ አሕመድ አልመግሪቢን ዉዴታና
አድናቆት ማትረፍ ችለዋል። በትምህርት ማዕዳቸውም ላይ የየዕለቱን ትምህርት መልሰው ለታዳሚዎች
እንዲያስተምሩ አድርገዋቸው ነበር። ከዚያም በአል-አሽረፊያ የሐዲሥ ማዕከል እና በሌሎችም ተምረዋል።
ተማሪያቸው የነበረው ዐላአዲን ኢብኑ አልዐጣር ስለ ትምህርት አቀሳሰማቸው ኢማም ነወዊ የነገሩትን ሲናገር
– በየቀኑ በተለያዩ ሸይኾች እጅ አሥራ ሁለት ትምህርቶችን ከነማብራሪያውና ትክክለኛ መልዕክቱ ይማሩ
ነበር። በአል-ወሲጥ ዙሪያ ሁለት ትምህርት፣ በሙሀዘብ አንድ ትምህርት፣ በአል-ጀምዕ በይነ ሶሒሐይን ዙሪያ
አንድ ትምህርት፣ በሶሒሕ ሙስሊም ዙሪያ አምስት ትምህርት፣ በለምዕ ኢብኑ ጀኒይ ነሕው ዙሪያ አንድ
ትምህርት፣ በኢብኑ ሰኪት ኢስጢላሕ አልመንጢቅ የቋንቋ ትምህርት ዙሪያ አንድ ትምህርት፣ በሶርፍ ዙሪያ
አንድ ትምህርት፣ በኡሱል አልፊቅህ ዙሪያ አንድ ትምህርት፣ በአስማእ ሪጃል ዙሪያ አንድ ትምህርት፣
በኡሱለዲን ዙሪያ አንድ ትምህርት፣ የሚማሩ ሲሆን ከነኚህ ትምህርቶች ጋር የተያያዘውን ሁሉ
ከነማብራሪያው፣ ጥያቄ ከሚያስነሳው ጉዳይና ከቋንቋ አንጻር እና ከመሳሰሉት ሁሉ አስፈላጊውን ነገር ይፅፉ
ነበር።
ኢማም ነወዊ በአባ አልፈረጅ ዐብዱረሕማን ኢብኑ አቢ ዑመር እና በዋና ሸይኻቸው ሙሐመድ ኢብኑ
አሕመድ አልመቅዲሲ እጅ ተምረዋል። ከዚህም በተጨማሪ ከአባ ኢስማዒል ኢብን አቢ አስሓቅ ኢብራሂም
ኢብኑ አቢ አልዩስር፣ ከአባል ዐባስ አሕመድ ኢብኑ ዐብዱ ዳኢም፣ ከአቡልበቃእ ኻሊድ አንናቡሊሲ ፣ ከአባ
ሙሐመድ ዐብዱልዐዚዝ ኢብኑ ዐብደላህ ሙሐመድ ኢብኑ ዐብዱልሙሕሲን አልአንሷሪይ፣ ከዲያእ ኢብኑ
ቲማም አልሒሲ፣ ከአልሓፊዝ አባልፈድል ሙሐመድ ኢብኑ ሙሐመድ አልበክሪይ፣ ከአባልፈዳኢል
ዐብዱልከሪም ኢብኑ ዐብዱሶመድ (የዳመስቆ ኸጢብ)፣ ከአባ ሙሐመድ ዐብዱረሕማን ኢብኑ ሳሊም ኢብኑ
የሕያ አልአብናሪ፣ ከአባ ዘከሪያ የሕያ ኢብኑ አልፈትሕ አሲራፊ አልሐራኒ፣ ከአባ ኢስሐቅ ኢብራሂም ኢብኑ
ዐሊ ኢብኑ አሕመድ ኢብኑ ፋዲል አልዋሲጢ እና ከሌሎችም እጅ ተምረዋል።
በፊቅሂ ዙሪያ
ኢብኑ አልዐጣር እንዲህ ይላል – “ነወዊ የሻፊዒ መዝሀብ ጥልቅ አዋቂ ናቸው። መርሆቹን፣ መሠረቶቹን እና
ቅርንጫፎቹን ሁሉ አሳምረው ያውቃሉ። እንዲሁም ስለ ሶሓቦች እና ታቢዒዮች መዝሀብም፣ ሙስሊም
ዑለማኦች ስለተለያዩባቸውና ስለተስማሙባቸው ነጥቦች፣ ይበልጥ ዕውቅና ስላገኘውና ስለተተወው እይታ
ሁሉ ያውቃሉ። በዚህ ሁሉ አቋማቸው ቀደምት ደጋግ ሙስሊሞችን መንገድ ይከተሉ ነበር።›
በሐዲሥ ዙሪያ
አንድ ዘመን በመጣ ቁጥር በዚያ ዘመን ዉስጥ አላህ የሐዲሥ ሰዎችን ያስነሳል። እነርሱም በሐዲሥ ዕውቀት
ዙሪያ በማብራራት፣ አዲስ አቅጣጫ በማሳየትም ሆነ በማረም በኩል ሌላ አብዮት ያስነሳሉ። በመካከለኛው
ዘመን ከተነሱ ትላልቅ ስብእናዎች መካከል ኢብኑ ሶላሕ፣ ኢማም ነወዊ፣ አልሚዚይ እንዲሁም ኢማም ዘሀቢ
ይጠቀሳሉ። ኢማም ነወዊ ከነርሱ ባላቸው የጠለቀ ዕውቀት ይለያሉ። በፊቅሂም ሆነ በሐዲሥ ዕውቀት
እርሣቸውን የሚስተካከል አልነበረም ማለት ይቻላል።[1]
ኢብኑ አልዐጣር እንደዘገቡት ኢማም ነወዊ ቡኻሪና ሙስሊምን፣ የአቢ ዳዉድን፣ የቲርሚዚን እና የነሳኢን
የሒዲሥ ጥንቅሮችን፣ የኢማም ማሊክን አልሙወጦእ፣ የሻፊዒን እና የኢማም አሕመድን ሙስነድ፣
የዳሪሚን፣ የአቢ ዐዋናን፣ የአቢ የዕላ አልመውሱሊን፣ የኢብኑ ማጀህ ሱነንን፣ የዳር ቁጥኒን፣ የበይሀቂን፣
የበገዊ ሸርሑ ሱናን እና የተፍሲር ኪታባቸውን መዓሊሙ ተንዚልን፣ የዙበይር ኢብኑ በካር አልአንሳብን፣
ጃቢር ኢብኑ ሀያን
የነባቲያ አልኹጠብን፣ የአልቁሸይሪ ሪሳላን፣ የኢብኑ ሱንኒን ዐመል አልየውም ወልለይላን፣ የአልኸጢብን
ኣዳቡ ሳሚዕ ወርራዊን እና ሌሎችንም በርካቶችን ተምረዋል። እነኚህ ሁሉ በሸይኹ የእጅ ጽሑፍ የተጠቀሱ
ናቸው።
ኢማም ነወዊ እንደ በርካታ ሙሐዲሶች ጥረታቸውን በሐዲሱ ዘገባ ሰንሰለት (ሰነድ) ዙሪያ ብቻ ትኩረት
አያደርጉም ነበር። የሐዲሡን መልዕክት ለማወቅ ትልቅ ጥረት ያደርጉ ነበር። ይህንኑ በሶሒሕ ሙስሊም
ማብራሪያቸው መቅድም ላይ ጠቅሰውታል። ከዚያም ወደዕውቀታዊ ጭብጡ ያተኩራሉ። ከርሣቸውም
በርካታ ሰዎች ተምረዋል። አቡልፈትሕ፣ አልሚዚይ እና ኢብኑል ዐጣር ጥቂቶቹ ናቸው።
ሌሎች ሁለቱ የነወዊ መጽሐፎች “ተሕሪር አት-ተንቢህ” እና “ተህዚብ አልአስማእ ወልሉጋት” ኢማም ነወዊ
በቋንቋ ዕውቀት ዙሪያ በዘመናቸው አቻ እንዳልነበራቸው የሚያመላክቱ ናቸው።
ኢማም ነወዊ እንዲህ ይላሉ – “በሕክምና ሥራ ለመሠማራት በዉስጤ አስቤ ነበር። ለዚህም ሲባል የኢብኑ
ሲናን ‘አልቃኑን’ መጽሐፍ ገዛሁኝ። በዚሁ ዙሪያ ለመሥራትም ቆርጬና አቋም ይዤ ተነሳሁኝ። ሆኖምግን
ልቤ ላይ ተጋረደ። ለበርካታ ቀናትም ምንም ሳልሠራ ቆየሁኝ። ጉዳዩን መልሼ አሰብኩበት። እንዴት ነው ይህን
ነገር ላስብ የቻልኩት አልኩኝ። ስለህክምና አብዝቼ ማሰቤ እንደሆነ አላህም ሰበቡን አሳወቀኝ። ወዲያውኑ
ጃቢር ኢብኑ ሀያን
የገዛሁትን የኢብኑ ሲናን መጽሐፍ አውጥቼ ሸጥኩኝ። ከህክምና ጋር የተያያዙ ነገሮችንም ከቤቴ አስወጣሁኝ።
ቀልቤ እንደገና ሲበራ ታወቀኝ። መጀመሪያ ወደነበርኩበት ሁኔታ ተመለስኩኝ።”[3]
ምናልባት ያ ኢማሙን ያገኛቸው የቀልብ ጨለማ በሕክምና ዙሪያ እንዳይጽፉ አግዷቸው ይሆናል። ስለ
ሕክምናም ነገሮች እንዲከብዱ አድርጎባቸው ይሆናል። ኢማም ነወዊ ወደ ሕክምና ትምህርት ሊያዘነብሉ
የቻሉት ምናልባት “ከሐላል እና ከሐራም ዕውቀት ቀጥሎ ከሕክምና ትምህርት በላይ ምርጥ የሆነ ትምህርት
አላውቅም” ያሉትን የኢማማቸውን የኢማም አሽ-ሻፊዒን አባባል ተከትለው ሊሆን ይችላል።[4]
ኢማም ነወዊ የኢብኑ ኸልካን ምክትል በመሆን በኢቅባሊያ መድረሳ እስከ 669 ዓ.ሂ መጨረሻ ድረስ
ሠርተዋል።[5] እንዲሁም በአል-ፈለኪያ እና ሩክኒያ መድረሳዎችም ምክትል ሆነው አገልግለዋል።[6]
ኢማም ነወዊ ከ665-676 ዓ.ሂ ባለው ጊዜ ዉስጥ የአል-አሽረፊያን ሐዲሥ ማዕከል በዋና ኃላፊነት
መርተዋል። በወቅቱ ይህ ማዕከል በሐዲሥ ትምህርት በሻም ምድር እጅግ ይታወቅ ነበር። እዚያ የገባ ሰው
ሙሉ ጊዜውን ዕውቀት በመቅሰም ላይ ነው የሚያሳልፈው። በተለይ የሐዲሥ ዕውቀትን። “የሐዲሥ ማዕከሉ
ሸይኽ” የተባለ ሰው በዕውቀት ደረጃ ከፍተኛውን ማዕረግ እንደተጎናፀፈ ነው የሚቆጠረው። ከኢማም ነወዊ
በፊት የማዕከሉ ኃላፊ የነበሩት ተቂየዲን ኢብኑ ሶላሕ እና ሺሃቡዲን አቡ ሻማህ አልመቅዲሲ ነበሩ።
ታጅ አስ-ሱብኪ እንዲህ ይላል “አባቴ እንዲህ አሉኝ .. ከኢማም ነወዊ እና ኢብኑ ሶላሕ በላይ ሓፊዝ እና
አላህን ፈሪ የሆነ ከአል-አሽረፊያ የሐዲሥ ማዕከል አንድም ሰው አልገባም።”[7]
ኢማም ነወዊ በዚህች ምድር ላይ የኖሩት ለ46 ዓመታት ብቻ ነበር። ይህ ከመሆኑ ጋር ትተው ያለፉት
የድርሰት ክምችት ለዕድሜያቸው ቢካፈል በየቀኑ ሁለት ቀለል ያሉ መጽሐፍትን የመፃፍ ያህል ነው።[8] ወደ
ዕውቀቱ ዓለም የገቡት በ18 ዓመታቸው መሆኑን ስናስተውል ደግሞ በርግጥም አላህ ዕድሜያቸውን
እንደባረከላቸውና እርሣቸውም የቱን ያህል ብርቱ ጥረት ያደርጉ እንደነበር እንረዳለን።
ሌሎች መጽሐፎች
ህልፈታቸው
ኢማም ነወዊ የሞቱት በ676 ዓ.ሂ ወደ ነዋ ከተመለሱ በኋላ ነበር። ከዚያ ቀደም ብሎ ለወቅፍ የተሠጡና
የተዋሷቸውን መጽሐፎችን ለየባለቤቶቻቸው መልሰዋል። የሸይኾቻቸውን መቃብሮች ጎብኝተውም
አልቅሰዋል። እንዲሁም በሕይወት ያሉትን ወዳጆቻቸውን ጎብኝተው ተሰናብተዋልም። አባታቸውንም
ጃቢር ኢብኑ ሀያን
እንዲሁም በይት አልመቅዲስ (ኢየሩሳሌምን) እና አልኸሊልን (ቤተልሄምን) ጎብኝተዋል። ከዚያም ወደ ነዋ
ተመለሱ። እዚያም ታመሙ። በረጀብ 24 ቀን እዚያው ሞቱ።
አላህ ኢማም ነወዊን በሰፊ እዝነቱ ዉስጥ ያስገባቸው። ለኢስላምና ለሙስሊሞች ላበረከቱት አስተዋጽኦ ሁሉ
በመልካም ይመንዳቸው።
4/1470والتذكرة 6- 7،ص ،الحديث ألفية شرح المغيث فتح :السخاوي ][3
، 6/ 36م 1990بيروت – العلمية الكتب دار ،المدارس تاريخ في الدارس :القادر عبد ،النعيمي ][7