Professional Documents
Culture Documents
Memehir Henok Weldemariam
Memehir Henok Weldemariam
4 mins ·
ንስሐ መግባት የመረረው መነኩሴና የአባ ሲሶይ ምክር!
በቀሲስ መ/ር ሄኖክ ወ/ማርያም
ተወዳጆች ሆይ በመጽሐፈ ፊሊክስዮስ በገጽ 178 ላይ ያለውን ታሪክ እንይ፡፡ አንድ መነኩሴ አባ ሲሶይን ‹‹አባቴ በኃጢአት
ተነሰካከያለሁና ምን ላድርግ›› አላቸው፡፡ አባ ሲሶይም ‹‹ንስሐ ግባ›› አለው፡፡ መነኩሴውም ‹‹ብዙ ግዜ እየተሰነካከልኩ
በንስሐ ስመላለስ ኖርኩ እስከ መቼ ስወድቅ ስነሳ እኖራለሁ?›› አላቸው፡፡ አባ ሲሶይም ‹‹እስክትሞት ድረስ፡፡ አንድም
ሞትህን በንስሐ፣ኃጢአትህን በንስሐ፣ወይም በሞት እስክትቀደም ድረስ›› አሉት፡፡
ደግ ሰው ከበጎ ሥረው በሚመለስበት፣ኃጢአቱ በሚሰረየይበት ቀን ቢሞት የቀድሞ ኃጢአቱ አይታሰብበትም ኃላ በሠረው
ኃጢአት ይሞታል እንጂ፡፡ ኃጥእ ከኃጢአቱ ተመልሶ በጎ ሥራ ቢሠራ የቀድሞ ኃጢአቱ አይታሰብበትም፡፡ ጻድቅም ኃጢአት
ቢሠራ በቀደመው በጎ ሥራው አይድንም በመጨረሻ በሠራው ኃጢአት ይኮነናል፡፡ ምክንያቱም ሰው በጊዜው ግብሩ ነው
የሚሄደውና፡፡ ስለዚህ በኃጢአት ስንወድቅ በቶሎ ንስሐ ልንገባ ይገባል፡፡
አንዳንድ ሰነፎች ቀድሞ የጽድቅ ሥራ ሲሠሩ ይኖሩና በኃላ በኃጢአት ይወድቃሉ፡፡ ንስሐ ግቡ ሲባሉ ልባቸውን
የሚያደነድኑት የቀድሞ በጎ ሥራቸውን በማሰብ በዛ ሥራ የሚድኑ፣ከፈጣሪም ሰማያዊ ዋጋ የሚቀበሉ ይመስላቸዋል፡፡ ይህ
ስህተት ነው፡፡ በሕይወታችን መጨረሻ የምንሠራው ሥራ ለገነቱም ሲዖሉም ሕይወት ይወስናሉ፡፡ ለዚህም ነው አባቶች
‹‹ፍጻሜዬን ያሳምርልኝ›› የሚሉት፡፡
የመንፈሳዊ ሕይወታችን የጽድቅና የኃጢአት ፍጻሜ ነው ለሰማያዊ ሽልማት እና ቅጣት የሚዳርገን፡፡ ለዚህም ነው
እግዚአብሔር ለነብዩ ሕዝቅኤል ለሰው ልጅ ንገርልኝ ብሎ ‹‹በበደለበት ቀን የጻድቅ ጽድቁ አያድነውም፣ኃጢአተኛም
ከኃጢአቱ በተመለሰበት ቀን በኃጢአቱ አይሰናከልም፤ጻድቁም ኃጢአት በሠራበት ቀን በጽድቁ በሕይወት አይኖርም፡፡ እኔ
ጻድቁን በእርግጥ በሕይወት ትኖራለህ ባልሁ ጊዜ፣እርሱ በጽድቁ ታምኖ ኃጢአት ቢሠራ በሠራው ኃጢአት ይሞታል እንጂ
ጽድቁ አይታሰብለትም፡፡ እኔም ኃጢአተኛውን በእርግጥ ትሞታለህ ባልሁ ጊዜ፣እርሱ ከኃጢአት ተመልሶ ፍርድንና ቅን
ንገርን ቢያደርግ፣ኃጢአተኛው መያዣን ቢመልስ የነጠቀውንም ቢመልስ በሕይወት ትእዛዝ ቢሄድ ኃጢአትም
ባይሠራ፣በሕይወት ይኖራል እንጂ አይሞትም፡፡ የሠራው ኃጢአት ሁሉ አይታሰብበትም፤ፍርድንና ቅን ነገርን
አድርጎአል፤በእርግጥ በሕይወት ይኖራል›› በማለት ዘርዝሮ ቋጥሮ አስቀምጦልናል፡፡ /ት.ሕዝቅ 33÷12-16/
ስለዚህ ያለማነውና ያጠፋነው በእግዚአብሔር ዘንድ ይመዘናል፡፡ ሰው ከዚህ ዓለም በሚለይበት ጊዜ በፈጣሪው ፊት
የሠራው ጽድቅ እና ኃጢአት ያመዘናል፡፡ ያለማነው ካጠፋነው ጋር ይመዘናል፡፡ ያለማነው በልጦ ቢገኝ ይፈረድልናል፡፡
ያጠፋነው በልጦ ቢገኝ ይፈረድብናል፡፡ ወዳጆቼ በፍቃደ ሥጋ ተስበን የሠራነውን ኃጢአት ንስሐ ልንገባበት ይገባል፡፡ በኃላ
በሚያስፈራው ዙፋን ፊት የኃጢአታችን ሒሳብ ሲወራረድ፣ለሲኦል እሳት እንዳንማገድ በንስሐ መንገድ እንጓዝ ጽድቁንም
እንያዝ፡፡
ቸር ዋሉልኝ!
ጥር 2/5/11 ዓ.ም
አዲስ አበባ