Professional Documents
Culture Documents
2007
2007
2007
ማውጫ
መግቢያ ............................................................................................................................ 2
ክፍል አንድ....................................................................................................................... 4
ክፍል ሶስት..................................................................................................................... 35
ማጠቃለያ ....................................................................................................................... 41
መግቢያ
በፌዴራል ፍ/ቤቶች ደረጃ አዲስ የተዘረጋውን ሚዛናዊ የሥራ አፈጻጸም ምዘና ሥርዓት ተከትሎና
ከስትራቴጂክ ዕቅድተነስቶ የተዘጋጀው የተቋም ዓመታዊ ዕቅድ ከሁሉም ዕይታዎች (የተገልጋይ እርካታ
ማሳደግ፣ የውስጥ አሠራር ማሻሻል፣ የፋይናንስ/በጀት አጠቃቀም፣ መማማርና ዕድገት) የተወሰዱ አስራ
አንድ ግቦች እና ሰባት ፕሮጀክቶችን የያዘ ሲሆን በመጀመሪያው ሩብ ዓመት የአፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ
ከሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት በተገኙ ግብዓቶች መሰረት በመጋቢ ግቦች ላይ የተወሰኑ ማስተካከያዎች
ተደርገዋል፡፡ የዚህን ዕቅድ አፈጻጸም ውጤታማ ለማድረግ በየደረጃው በሚገኙ ኃላፊዎች፣ ዳኞችና ድጋፍ
ሰጪ ሠራተኞችን አስተያየቶች በማሰባሰብ ተቀባይነት ያገኙ ማስተካከያዎች ተደርገዋል፡፡
በተቋሙ የዕቅድ ዝግጅት ምዕራፍ የተቋሙን ዓመታዊ ዕቅድ ለሚመለከታቸው ክፍሎች በማስተዋወቅ
እስከ ፈጻሚዎች አውርዶ ለማቀድ የሚያስችሉ የኦረንቴሽንና የውይይት መድረኮች የተካሄዱ ሲሆን
ለዳኝነት ዘርፉ በተዘጋጀው የአገልግሎት አሰጣጥ ስታንደርድ እና በተቋሙ ዓመታዊ ዕቅድ ላይ ተወያይቶ
ስምምነት ላይ ለመድረስ ተችሏል፡፡ በዚህ ስምምነት መሰረት በሁሉም ፍ/ቤቶች የሚገኙ የዳኝነት ዘርፎች
እና የሲቪል ሰርቪስ ሥራ ክፍሎች ከተቋም ዓመታዊ ዕቅድ የሚመለከቱዋቸውን ግቦችና ፕሮጀክቶች
በመውሰድ የየራሳቸውን ዓመታዊ ዕቅድ ከማዘጋጀታቸውም ሌላ የችሎቶችን ዕቅድ እስከ ዳኞች እና የሥራ
ክፍሎችን ዕቅድ እስከ ፈጻሚ ግለሰቦች በማውረድ የተሟላም ባይሆን ዝርዝር ተግባራትን የያዙ ዓመታዊ
ዕቅዶች በየደረጃው ተዘጋጅተዋል፡፡
የተቋሙን የትግበራ ምዕራፍ አጠናክሮ በመቀጠል የዕቅድ አፈጻጸም ውጤታማነትን ማሳደግ የሚያስችል
የክትትልና ግምገማ ሥርዓት ተዘርግቶ የተተገበረ ሲሆን የተቋሙ የበላይ አመራር፣ የችሎት/ምድብ ችሎት
አስተባባሪዎች፣ የችሎት ሰብሳቢዎችና የሲቪል ሰርቪስ ሥራ ክፍል ኃላፊዎች በየደረጃው ተገቢውን
ክትትል፣ ድጋፍና ግምገማ በማድረግ በዕቅድ የተያዙ ግብች እና ፕሮጀክቶች ለበጀት ዓመቱ
ከተቀመጠላቸው ዒላማ አኳያ እንዲከናወኑ ለማድረግ ያገዙ ጥረቶችን አድርገዋል፡፡ ከበጀት ዓመቱ
የመጀመሪያ ሩብ ዓመት(ነሐሴና መስከረም) የዳኞች የዕረፍት ጊዜ በመሆኑ እና ዕቅዶችን በየደረጃው
አውርዶ የማዘጋጀቱ ሥራ የተወሰነ ጊዜ በመውሰዱ በእነዚህ ወራት በፍ/ቤቶች ዕልባት ያገኙ መዛግብት
መጠን ከሌላው ጊዜ አኳያ ሲታይ ዝቅ ብሎ ታይቷል፡፡ ይሁን እንጂ ለዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ
ውጤታማነት የሚያግዙ ቅድመ ሁኔታዎችን ለማሟላት የተሻለ ጥረት የተደረገበት፣ በጥናት ላይ የቆየው
የዕቅድ አፈጻጸም ምዘና ሥርዓት ወደ ትግበራ የተሻገረበትና በሥራ የደከሙ ዳኞች ተገቢውን ዕረፍት
አግኝተው በአዲስ ኃይል ወደ ሥራ እንዲመለሱ የተደረገበት ወቅት በመሆኑ የበጀት ዓመቱን የዳኝነት
አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል መሰረት የተጣለበት ነበር ለማለት ይቻላል፡፡
የዕቅድ አፈጻጸም ክትትልል፣ ድጋፍና ግምገማ ምዕራፍ በዕቅድ አፈጻጸም ሂደት ከዓመቱ ዕቅድ
እየተመነዘሩና ዳኞች ወርሃዊ፣ የአስተዳደር ክፍሎች ደግሞ ሳምንታዊ ዕቅድ እያዘጋጁ በዕቅዳቸው መሰረት
መፈጸምና የአፈጻጸም መረጃ መያዛቸውን፣ የሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች የዕቅድ ዝግጅቶችንም ሆነ
የአፈጻጸም መረጃዎችን አግባብነት ተከታትለው ማስተካከያ ድጋፎችን ማድረጋቸውንና የአፈጻጸም ግምገማ
መድረኮችን በተገቢው ጊዜ ማካሄዳቸውን፣ በጋራ ግምገማ የተለዩ ክፍተቶች እና ከበላይ አመራር የሚሰጡ
ግብረመልሶች በአግባቡ መፈጻማቸውንና ከፍተቶች እንዲሞሉ መደረጋቸውን፣ እንዲሁም ወቅታዊ
የአፈጻጸም ሪፖርቶች ተዘጋጅተው ለሚመለከታቸው አካላት መድረሳቸውን ማረጋገጥ ያስቻሉ ተግባራት
ተከናውነዋል፡፡ በዚህ ምዕራፍ መከናወን የሚገባቸው እነዚህ የክትትል፣ ድጋፍና ግምገማ ተግባራት
በሁሉም ፍ/ቤቶች በተሟላ ሁኔታ ተፈጽመዋል ለማለት ባይቻልም በተወሰነ ደረጃም ቢሆን አበረታች
የለውጥ ጅምሮች ነበሩ ለማለት የሚያስችሉ አፈጻጸሞች ታይተዋል፡፡ በተለይ በሁለተኛው መንፈቅ ዓመት
በየፍ/ቤቶች በተናጥል እና ሶስቱም ፍ/ቤቶች በጋራ ባካሄዱዱዋቸው የበጀት ዓመቱ የዕቅድ አፈጻጸም
ግምገማዎች ለምዘና ሥርዓቱን ትግበራ እንቅፋት የፈጠሩ ችግሮች ተለይተው ከመውጣታቸውም ሌላ
በአመራር፣ በዳኛ፣ በድጋፍ ሰጪ ሥራ ክፍል ኃላፊዎችና ፈጻሚዎች ዘንድ የነበሩ ጥንካሬ እና
ክፍተቶች/ድክመቶች በግልጽ እንዲወጡ ተደርገዋል፡፡ ክፍተቶችን ለመሙላት የሚያስችሉ የመፍትሔ
አቅጣጫዎችንም በማመላከት በቀጣዩን በጀት ዓመት የምዘና ሥርዓቱን ትግበራ አጠናክሮ ለመቀጠል
ስምምነት ተደርጓል፡፡
የምዘና ምዕራፍን በተመለከተ የመጀመሪያው መንፈቅ ዓመት በሁሉም ፍ/ቤቶች የተሟላ ምዘና ተካሂዷል
ማለት አይቻልም፡፡ በተወሰነ መልኩ የግቦች አፈጻጸም የሚገኙበትን ደረጃ መለየት ያስቻሉ መረጃዎችን
ለማግኘት ቢቻልም በየደረጃው ወርዶ በተዘጋጀው ዕቅድ መሰረት የዳኞችን፣ ችሎቶችንና ፍ/ቤቶች
እንዲሁም የደጋፍ ሰጪ ሠራተኞችን፣ ቡድኖችን፣ የሥራ ክፍሎችንና ፍ/ቤቶችን አፈጻጸም በየደረጃው
ገምግሞ የተገኙ ውጤቶችን በመለየት የተቋሙን የመንፈቅ ዓመት አፈጻጸም የመመዘን ተግባር
አልተከናወነም፡፡ ለዚህም ዓይነተኛ ምክንያት ሆኖ የሚጠቀሰው አዲስ የተጀመረውን የምዘና ሥርዓቱን
ለመተግበር የሚያስችል አቅም በቀላሉ መፍጠር አለመቻልና የምዘና ሥርዓቱ የሚጠይቀውን ሂደት
ተከትሎ መተግበር የሚያስችል አመለካከት አለመዳበር ነው፡፡ የሁተኛውን መንፈቅ ዓመት ትግበራ
ክትትል፣ ድጋፍና ግምገማ ተጠናክሮ የቀጠለ በመሆኑ የምዘና ሥርዓቱ ትግበራ የተሻለ ደረጃ ላይ
ከመድረሱም በላይ አፈጻጸምን በየደረጃው ለመመዘን የተጠናከረ ጥረት ተደርጓል፡፡
በዚህ ሪፖርት ሶስት ክፍሎች የተካተቱ ሲሆን የመጀመሪያው ክፍል በዕቅድ ዝግጅት ምዕራፍ ከተቋማዊ
እስከ ግለሰብ የዘለቀውን የዕቅድ ዝግጀት ሂደት እና በአፈጻጸም/ትግበራ ምዕራፍ የግቦችን አፈጻጸም
እንዲያሳይ ተደርጓል፡፡ ሁለተኛው ክፍል ለበጀት ዓመቱ የተያዙ ፕሮጀክቶችን አፈጻጸም የሚያሳይ ሲሆን
ሶስተኛው ክፍል በክትትልና ግምገማ ምዕራፍ ዕቅዱን ለማሳካት በዕቅድ ዝግጅት እና በትግበራ ሂደት
የተደረጉ ክትትልና ድጋፎች በማሳየት በግምገማ የተለዩ ጥንካሬና ድክመቶችን፣ በአፈጻጸም ያጋጠሙ
ችግሮችንና የተወሰዱ የመፍትሔ እርምጃዎችን፣ በዕቅድ ተይዘው በተለያዩ ምክንያቶች ያልተከናወኑ
ተግባራትን እንዲሁም የቀጣዩን በጀት ዓመት አፈጻጸም ውጠየታማነት ለማጎልበት የተቋሙ የበላይ
አመራር ትኩረት ሊሰጥባቸው የሚገው ጉዳዮችን አመላክቷል፡፡
ክፍል አንድ
የፍ/ቤቶች ማህበረሰብ የተቋሙን ስትራቴጂያዊ አቅጣጫ፣ ራዕይ፣ ተልዕኮ፣ እሴቶችና ግቦች በአግባቡ
ተረድቶና ኃላፊነቱን ለመወጣት የሚችልበትን አመለካከትና ብቃት አጎልብቶ በየደረጃው ያዘጋጃቸውን
ዕቅዶች እንዲፈጸም ለማድረግ፡-
የለውጥ አመለካከት እና የመፈጸም ብቃት የሚያጎለብቱ የተለያዩ የስልጠና እና የውይይት መድረኮች
መዘጋጀታቸውን፣
ተቋማዊ ይዘት ያላቸው የለውጥ ኮሚኒኬሽን ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን፣
በዚህም በተቋም ደረጃ በዕቅድ የተያዙ ግቦችን/መጋቢ ግቦችን ለማሳካት የሚከተሉት ዝርዝር ተግባራት
ተከናውነዋል፡፡
በፌዴራል ጠቅላይ፣ ከፍተኛ እና መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት፣ በፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ጽ/ቤት
እና ሸሪዓ ፍርድ ቤት የሚገኙ ዳኞች፣ የሲቪል ሰርቪስ ኃላፊዎችና ሠራተኞችን የመፈጸም አቅም፣
የአመለካከት፣ የዕውቀትና ክህሎት ስልጠና ፍላጎቶችና ክፍተቶች መለየት ያስቻለ ጥናት ተካሂዶ
የተቋሙ የበጀት ዓመት የሥልጠና ዕቅድ ተዘጋጅቷል፣
በስልጠና ዕቅዱ የተካተቱ ርዕሰ ጉዳዮች የሴቶችን የመሪነትና የመፈጸም አቅም ለማጎልበት፣
የብሔራዊ የሰብዓዊ መብት ድርጊት መርሃግብር ድንጋጌዎችን ግንዛቤ ለማዳበር፣ የመልካም
አስተዳደርና የሥነ መግባር መርሆችን የዕለት ተዕለት ተግባር ለማድረግ፣ ለባለብዙ ዘርፍ ጉዳዮች ልዩ
ትኩረት ሰጥቶ ለማስተናገድ፣ በአጠቃላይ የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥን የሚያሻሽሉ የለውጥ
አተገባበሮችን ለማጠናከር የሚያስችሉ መሆናቸውን ማረጋገጥ ያስቻለ ክትትል፣ ድጋፍና ግምገማ
ተደርጓል፣
በዚህ ዕቅድ መሰረት 14 የስልጠና ርዕሰ ጉዳዮችን ለማሰልጠን ከኢትዮጵያ ስራ አመራር ኢንስቲትዩት
እና በሾፌር መካኒክነት ለማሰልጠን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምርታማነት ማሻሻያ ማዕከል ጋር
ስምምነት ተደርጓል፣
በሲቪል ሰርቪስ ሕጎች ላይ የሠራተኞችን ግንዛቤ ለማዳበር የሲቪል ሰርቪስ ባለሙያዎችን በሥነ
ምግባር መርሆች ላይ ተገቢው ግንዛቤ እንዲያገኙ ለማድረግ የፌዴራል የሥነ ምግባርና ጸረ ሙስና
ኮሚሽን ባለሙያዎችን በመጋበዝ የተለያዩ የስልጠና መድረኮች ተዘጋጅተዋል፣
በወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ አተገባበር ዙሪያ ተገቢው ግንዛቤ እንዲጨበጥ በመመሪያው
አዘጋጅ ኮሚቴ አማካኝት ለተለያዩ ጉዳዩ ለሚመለከታቸው ክፍሎች (ለምሳሌ ተከላካይ ጠበቆች፣ የህግ
ጥናትና ድጋፍ ባለሙያዎች ወዘተ…) ስልጠናዎች ተሰጥተዋል፣
የዩንቨርስቲ መምህራንን በመጋበዝ የሕግ ጥናት እና የፕሮጀክት ዝግጅት ጉዳዮችን የሚመለከቱ
ስልጠናዎችን ለመስጠት ያስቻሉ መድረኮች የተዘጋጁ ሲሆን በአጠቃላይ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ
በተዘጋጁ ከ15 በላይ በሆኑ ስልጠናዎችና የተለያዩ የውይይት መድረኮች ላይ 1‚910 ተሳታፊዎችን
ማስተናገድ ተችሏል፡፡
የድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች የትምህርትና ስልጠና አፈጻጸም መመሪያም ተዘጋጅቷል፣
የሴት ሠራተኞችን አቅም በሥልጠናና ትምህርት ማጐልበትን አስመልክቶ ከተለያዩ የግል ኮሌጆት
በተገኘ ድጋፍ ሁለት ሴት ሠራተኞች ነጻ ሁለት ደግሞ 5ዐ በመቶ ቅናሽ የትምህርት እድል
አግኝተዋል፡፡
ሥርዓተ ጾታን በየሥራ ዘርፉ ማካተትና የሥርዓተ ጾታ መረጃን አስመልክቶ ከፌደራል ፍ/ቤቶች እና
ከፌ/ጠ/ ሸሪዓ ፍ/ቤት ለተውጣጡ 24 ሴት 32 ወንድ በጠቅላላው ለ56 የሥራ ክፍል ኃላፊዎችና
ባለሙያዎች የአንድ ቀን ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡
የሴቶችን ኢኮኖሚያዊ አቅም ለማጐለበት እንዲቻል በተጨማሪ የገቢ ማስገኛ ዘዴ ላይ ለ33 ሴቶች
ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡
ራስ አገዝ የሴቶች ድርጅት ከሚባል ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር በተደረገው የባለሙያና
የቁሳቁስ ድጋፍ ለ22 ሴት የጽዳት ሠራተኞች መሠረታዊ የንግድ ክህሎት በሚል ርእስ የ5 ቀን
ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡
ዓለም አቀፍ የጸረ ጾታዊ ጥቃትና የኤች አይ ቪ ኤድስ ቀን ከፌደራል ፍ/ቤቶችና ከፌ/ጠ/ሸሪዓ ፍ/ቤት
ከተውጣጡ 200 ሠራተኞችና /115 ሴት 85 ወንድ/ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ተያያዥ በሆኑ
ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ሥልጠና በመስጠትና ሰፋ ያለ ውይይት በማድግ ቀኑ ተከብሯል፡፡
የፌ/ፍ/ቤቶች ወጣት ሠራተኞች በኤች አይ ቪ ኤድስ ላይ ያላቸውን ግንዛቤ ለማዳበር ይቻል ዘንድ
በአቻ-ለአቻ ውይይትና በሥነ ተዋልዶ ጤና ዙሪያ ለ5ዐ/ 33 ሴት 17ወንድ/ ወጣቶች የአንድ ቀን
ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡
ለዳታ ቤዝ ባለሙያዎች ከአዲሱ መረጃ ስርዓት ጋር ተስማምተው ለመስራት እንዲችሉ በሶስት ዙር
የተከፈለ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷል፣
በፌዴራል እና በክልል ፍርድ ቤቶች በህጻናት ችሎቶች ላይ ለሚሰሩ የማህበራዊ ሳይንስ ባለሙያዎች
የረጅም ጊዜ በዘርፉ ላይ እውቀትና ክህሎት የሚያስጨብጥ ለሁለት ዓመታት የሚቆይ የዲፕሎማ
ስልጠና ለመስጠት የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት ተጠናቅቋል፣ ስልጠናውን ለመስጠት በተዘጋጁት
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሶሻል ወርክ ትምህርት ክፍል የቀረቡ የብቃት ምዘና ፈተናዎች ተሰጥተዋል፡፡
ለኦዲዮቪዥዋል ሁለት ባለሙያዎች ከሙያቸው በተያያዘ ያለባቸውን የክህሎት ክፍተት ግምት ውስጥ
ያስገባ የሦስት ወር ሥልጠና በቪዲዮ ቀረፃ እና በቪዲዮ ኤዲቲንግ፣ በፎቶ አነሳስ እና በፎቶ ኤዲቲንግ
ሥልጠና ወስደዋል፣
በአዲስ ቅጥር ፍ/ቤቱን ለተቀላቀሉ 101 ባለሙያዎችና ሠራተኞች በተቋሙ ሥራ ባህልና የለውጥ
እንቅስቃሴዎች ላይ ያተኮሩ የማስተዋወቂያ ስልጠናዎች ተዘጋጅተዋል፣
በተሰጡ ስልጠናዎች የተገኘውን የመፈጸም አቅም ዕድገትና የአመለካት ለውጥ መኖሩን ማረጋገጥ
የሚያስችሉ ግምገማዎች በየሥራ ክፍሎች እንዲከሄዱ ተደርጓል፣
የተለያዩ መገናኛ ብዙሐንን (ሬዲዮ፣ ቴሌቪዥን፣ ጋዜጣ፣ መጽሔት፣ ብሮሽር፣ ጋዜጣዊ መግለጫ
ወዘተ…) በመጠቀም የሰብዓዊ መብት የደርጊት መርሃግብር ድንጋጌዎችን አፈጻጸም ጨምሮ
የፌዴራል ፍ/ቤቶችን የዕቅድ አፈጻጸም ለሕዝብ በማስተዋወቅ የተቋሙን ገጽታ የሚገነቡ የተለያዩ
መልዕክቶች እንዲተላለፉ ተደርጓል፣
ተቋሙ ያዘጋጃቸውን የተለያዩ የውይይትና የስልጠና መድረኮች የመንግሥት የኤሌክትሮኒክስና
የህትመት ሚዲያ ጋዜጠኞች ተገኝተው እንዲዘግቡ በማድረግ የዜናና የዘገባ ሽፋን አንዲሰጡ
ተደርጓል፤
አገር አቀፍ የፍትህ አካላት የበላይ አመራሮች የተሳተፉበትን የአቅም ግንባታ ስልጠና የኢትዮጵያ
ቴሌቪዥን፣ አ.አ መገናኛ ብዙኃን ቴሌቪዥንና ሬዲዮ፣ ኦሮሚያ ቴሌቪዥን፣ ኢትዮጵያ ኘሬስ
(አማርኛ፣ እንግሊዘኛና አረብኛ) ዛሚ፣ ሸገር፣ ሬዲዮ ፋና ተገኝተው በመዘገብ ለሕዝብ እንዲያስተላልፉ
ተደርጓል፣
የዳኝነት ነፃነት፣ ተጠያቂነት፣ ግልፅነት በኢትዮጽያ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ፅሁፍ ለኢትዮጵያ ኘሬስ
ድርጅት በመላክ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዲወጣ ተደርጓል፡፡
አገር አቀፍ ነፃ የህግ ድጋፍ ቅንጅት ለመመስረት በተዘጋጀ መድረክ የአትዮጵያ ዜና አገልግሎት፣
የኢትዮጵያ ኘሬስ ድርጅት ዛሚ እና ሸገር ተገኝተው እንዲዘግቡ ተደርጓል፣
የፌ/ጠ/ፍ/ቤት እና የፌ/ጠ/ሸሪዓ ፍ/ቤት ዳኞችና ሠራተኞች ለሕዳሴ ግድብ ማጠናከሪያ የሚሆን
ለሁለተኛ ዙር የቦንድ ግዥ ለመፈፀም በተካሄደ ስብሰባ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን፣ የአዲስ አበባ መገናኛ
ብዙኃን /ሬዲዮ/ የኢትዮጵያ ኘሬስ ድርጅት/ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዛሚ ኤፍ ኤም ተገኝተው
እንዲዘግቡ ተደርጓል፣
አገር ዓቀፍ የሕፃናት የፍትህ አስተዳደር ያለበትን ሁኔታ በሚያሳይ አገር ዓቀፍ ጥናት ላይ ለመነጋገር
በተዘጋጀ የምክክር መድረክ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን፣ የኦሮሚያ ቴሌቪዥን፣ የአ.አበባ ቴሌቪዥንና
ሬዲዮ፣ ኢትዮጵያ ኘሬስ /ሄራልድዘመን/ ፋና፣ ዛሚ፣ ሸገር ተገኝተው ዘግበዋል፣
የፌዴራል ፍ/ቤቶች የኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት የፀደቀበትን 2ዐኛ ዓመት ለማክበር በተዘጋጀ መድረክ
የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን፣ ኦሮሚያ ቴሌቪዥን፣ የአ.አበባ ኤፍ ኤም ሬዲዮ፣ዜና አገልግሎት ፣
የኢትዮጵያ ኘሬስ ድርጅት ተገኝተው እንዲዘግቡ ተደርጓል፣
የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 2 ለተከላካይ ጠበቆችና ሰሌሎች የፌ/ፍ/ቤቶች የሕግ
ባለሙያዎች በተሰጠ ሥልጠና ላይ የተገኘው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎ ሆኖ ዘገባው ግን በኢትዮጵያ
ቴሌቪዥን፣ በኢትዮጵያ ሬዲዮ፣ ኤፍ ኤም 97.1 እና በአ.አ ኤፍ ኤም ሬዲዮ እንዲሁም በፋና
ተላልፏል፣
የፌ/ፍ/ቤቶች የፍርድ አፈፃፀም ዳይሬክቶሬት እና የሕፃናት ፍትህ ኘሮጀክት የ2ዐዐ6 ዓ.ም. የሥራ
አፈፃፀም በሸገር ሬዲዮ ጣቢያ ከአድማጮች ጋር በመገናኘት የ4 ሰዓት ሽፋን እንዲሰጣቸው ተደርጓል፣
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ድርጅት የተቋሙ የአይሲቲ አጠቃቀም በተመለከተ ሁለቴ የዜና ዘገባ
እንዲሰራ ተደርጎ በቴዤቪዥንና በሬዲዮ ተላልፋል፤
የ2ዐዐ7 የኢኮቴ፣ የሕፃናት ፍትህ ኘሮጀክት የፍርድ አፈፃፀም እና የተከላካይ ጠበቆች የሥራ
አፈፃፀምና ዋና ዋና ተግባራት እንዲሁም ያመጣቸው ለውጦች በተመለከተ በኢትዮጵያ ሬዲዮ በኩል፣
የፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ዋና ተግባርና ወቅታዊ የሥራ አፈፃፀም በሸገር ሬዲዮ ጣቢያ
በሁለት ዘገባ ሽፋን ተሰጥቶታል፣
የተቋም ገፅታ ግንባታ ሥራ ለማከናወን በአጀንዳ እና በካላንደር መልክ የሚተላለፉ መልክዕክቶች
ዓይነተኛ መሳሪያዎች በመሆናቸው የ2007 አጀንዳና ካሌንደሩ ለማዘጋጀት የሚሰፍሩ መረጃዎች፣
መልዕክቶች፣ ፎቶግራፎችና ጠቃሚ አድራሻዎች የማሰባሰብና የማደራጀት ሥራ ቢከናወንም በግዥ
ሂደት መጓተት ምክንያት ሥራው ባለመጠናቀቁ የተሰባሰቡ መረጃዎች ወደ 2008 በጀት ዓመት
እንዲሸጋገሩ ተደርጓል፣
ችሎት ቁጥር 3 መፅሔት ባለ 70 ገፅ መፅሄት ሚያዚያ 2007 ታትሞ ለባለድርሻ አካላት፣ ለክልል
የፍትህ አካላት፣ ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት፣ ለፍ/ቤቱ ተገልጋዮች፣ በአጠቃላይ ከ 320 በላይ
ለሚሆኑ መንግታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት እንዲሁም ለፍ/ቤቱ ማህበረሰብ እንዲሰራጭ
ተደርጓል፣
የመፅሔቱ የፅሁፍ ይዘት ጥራት ብስለትና ክብደት በተመለከተ የአንባቢው ግብረመልስ የሚሻ ቢሆንም
መፅሔቱ ሌሎች የመንግስት ተቋማት ከሚያሳትሟቸው ዓመታዊ ህትመቶች አንፃር ሲገመገም
ደረጃውን የጠበቀ ነው ማለት ይቻላል፣
በመሰለ መልቲ ሚዲያ በሚዘጋጀው ሽግግር መፅሄት ጋር በመተባበር (ስፖንሰር በማድረግ)
የፍርድቤቱን የእድገትና ትራንስፎረምሽን ዕቅድ አፈፃፀም፡ ስለዳኞች የስራ ሸክምና ከባድ ሃላፊነት
በተመለከተ በመፅሄቱ 12 ገጥ ላይ ሽፋን አግኝቷል፡፡ መፅሄቱ በተለይ በአስፈፃሚ ተቋማት ሰፊ
ስርጭት ያለው ስለሆነ የዳኝነት አካሉ የስራ ሸክም ትክክለኛ ግንዛቤ እንዲኖረው በማድረግ በኩል
የራሱ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል፣
በበጀት ዓመቱ ስድስት ብሮሸሮችን ለማሳተም ታቅዶ ስድስቱንም ብሮሸሮች ማዘጋጀትና ማሰራጨት
የተቻለ ሲሆን የሁለት ተጨማሪ ብሮሸሮች ዝግጅት በሂደት ላይ ይገኛል፣
ቡክሌት ማዘጋጀት በበጀት ዓመቱ ዕቅድ የተካተተ ባይሆንም በበርካታ ፎቶግራፎች የተደገፉ አንድ
የአማረኛ እና አንድ የእንግሊዘኛ ቡክሌቶች ተዘጋጅተው ለህትመት በቅተዋል፡፡
የህጻናት የህግ ከለላ ማዕከል አገልግሎቶችን የሚያሳይና ለማህበረሰቡ ግንዛቤ የሚሰጥ በራሪ ጽሁፍ
በ5,000 ኮፒ ለህትመት በማብቃት እንዲሰራጭ ተደርጓል፣
የህጻናት ፍትህ አስተዳደሩን በሐገር አቀፍ ደረጃ ለማሻሻል የሚደረጉት ዓመታዊ የምክክር መድረኮች
ውጤት የሆነውና ሁሉም ክልል ግብዓት ሰጥቶበት በጋራ የጸደቀው በዳኝነት ስርአት ውስጥ ለሕፃናት
ምቹ እና ወጥ የሆነ አሰራር ለመዘርጋት የሚያግዝ መለኪያ/መመሪያ በፕሮጀክት ጽ/ቤቱ ተዘጋጅቶ
ለዳኝነት አካሉ ባለሙያዎች ተደራሽ እንዲሆን በ3,000 ኮፒ ታትሞ ተሰራጭቷል፣
የፕሮጀክት ጽ/ቤቱን ዋና ዋና ተግባራት እና ሌሎች ግንዛቤ ማስጨበጫ ጽሁፎችን የያዘ ዓመታዊ
መጽሄት ዝግጅት ተጠናቅቆ በ 2000 ኮፒ ተሠራጭቷል፣
የፌዴራል ፍ/ቤቶች የ2007 ዕቅድ እና የዳኝነትን አገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርድ ለማስተዋወቅ
በተዘጋጀ የምክክር መድረክ የኢትዮጵያ ቴሌቪዢን ፣ አ.አ መገናኛ ብዙኃን / ቴሌቪዥን፣ ሬዲዮ/
ሬዲዮ ፋና፣ ዛሚ፣ ሸገር ኢትዮጵያ ኘሬስ/ አዲስ ዘመን፣ ሄራልድና በሪሳ ተገኝተው በመዘገብ ሕዝብ
እንዲያውቅ አድርገዋል፣
የፌ/ፍ/ቤቶች በኢኮቴ አጠቃቀም ያስመዘገቡት ለውጥ በተመለከተ ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የዜናና
የኘሮግራም ሥራ ለመስራት የሁለት ቀናት ቀረፃ ሥራና ቃለ- መጠይቅ ተደርጓል፡፡ ሰፋ ያለ ዜና
ተሰርቶ ተሰራጭቷል፣
የፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ገለልተኛነት ዋና ተግባርና ወቅታዊ የሥራ አፈፃፀም እንዲሁም
የ2007 የዕጩ ዳኞች ምልመላ ለማካሄድ የወጣው የተወዳዳሪዎች የምዝገባ ስርዓት በተመለከተ በሸገር
ሬዲዮ ጣቢያ በተደጋጋሚ የዜናና የዘገባ ሽፋን እንዲሰጠው ተደርጓል.
በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት አሰጣጥ የሰባት ወርና የዘጠኝ ወር አፈፃፀም የተመለከተ ዘገባ
በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን፡ በሬደዮ ፋና፤ በሸገርና በዛሚ የኤፍኤም ሬድዮ ጣቢያዎች ተላልፏል፣
የፌ/ፍ/ቤቶች የ10 ወር የስራ አፈፃፀምና የዳኝነት አካሉ የአይሲቲ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም
በተደራሽነት፤ በቅልጥፍናና የተገልጋዮችን ወጪ ከመቀነስ ጊዜ ከመቆጠብ ያሰገኛቸው ለውጦች
በተመለከተ በአዲስ አበባ ቴሌቪዥን በተደጋጋሚ ተላልፏል፣
ስለ ሐሰት ምስክርነት፣ ስለይግባኝ፣ ስለችሎት መድፈር፣ ስለ ዳኝነት ሥልጣን በተመለከተ የሕግ
የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት በኢትዮጵያ ሬዲዮ፣ በአዲስ ዘመን ጋዜጣና በአዲስ አበባ መገናኛ
ብዙኃን በዳኞች መግለጫ እንዲሰጥ ተደርጓል፡፡
የተቋሙ ዳኞችና የሲቪል ሠራተኞች ከጥር 29 እስከ የካቲት 1/2007 የህዳሴ ግድብ ጉብኝት
በማድረግ ስራው ያለበትን ደረጃ ለማየት እንዲችሉ ተደርጓ፣
የፌደራልና የክልሎች የፍትህ አካላት አስተባበሪ ባዘጋጀውና ከመጋቢት 9 እስከ 13/2007 በመቀሌ
ከተማ በተካሄደው የምክክር ጉባኤ የሚዲያና የዶክሜንቴሽን እንዲሁም ፕሮግራሙን የማስተባበር ስራ
ተከናውኗል፡፡
የተለያዩ የህፃናት የህግ የማህበራዊና ስነልቦናዊ ጉዳዮችን በመለየትትና የህፃናትን የህግ ከለላ ማዕከል
የሚሰጠውን ድጋፍ ለማህበረሰቡ ግንዛቤ ማስጨበጫ በሚሆን መልኩ በአጫጭር የቪዲዮ ኪሊፖችን
በማዘጋጀት የህፃናት ጉዳዮች በሚታዩባቸው የፌዴራል ፍርድ ቤቶች የባለጉዳይ መጠበቂያዎች
ቦታዎች ላይ እንዲታዩ ለማድረግ ተችሏል፡፡
የፍርድ ቤቱን የአሰራር ስርዓት የሚያስገነዝቡ፣ የፍትህ ተደራሽነትን የሚያጎለብቱ፣ በፍ/ቤቶች
የሚሰጡ ባለብዙ ዘርፍ አገልግሎቶችን የሚያስተዋውቁ፣ የፍ/ቤቱን ማህበረሰብ የለውጥ አመለካከት
የሚያጎለብቱና የመፈጸም አቅምን የሚጨምሩ መልዕክቶችን ለማስተላለፍ ከ3ዐ በላይ የግልና
የመንግሥት ሚዲያ ተቋማት ጋዜጠኞችና ከ2ዐ በላይ የፌዴራል ተቋማት የኮሙኒኬሽን ኃላፊዎች
የተሳተፉበት የጉብኝት ኘሮግራም በማዘጋጀት የሚዲያ ተቋማት እንዲዘግቡት ተደርጓል፣
4.3 የመረጃ ነጻነት ሕጉን ትግበራ በማጠናከር የመረጃ ጠያቂዎችን ፍለጎት ለማሟላት በተያዘው
ዕቅድ፡-
በመረጃ ነጻነት ሕግ እንዳይገለጹ ከተፈረጁት በስተቀር በየፍ/ቤቶች ችሎቶችና ሥራ ክፍሎች የተያዙ
መረጃዎች በሚመለከተው ክፍል አማካኝነት ተሰባስበውና በአግባቡ ተደራጅተው ባለፉት በበጀት ዓመቱ
46 የሚዲያ ተቋማትና 526 መረጃ ፈላጊ ዜጎችና ተቋማት ተስተናግደዋል፣
የመገናኛ ብዙኃን ለፍ/ቤቱ ተገቢው ቦታና ሽፋን እንዲሰጡና በዕቅዳቸው እንዲያካትቱት ለማድረግ
ከኢትዮጵያ ሬዲዮ፣ ከኢትዮጵያ ኘሬስ ድርጅት፣ ከሸገር እና ከዛሚ ጋር ስምምነት ተፈጥሯል፣
ፍ/ቤቶችን የሚያከናውኑዋቸው ተግባራትና ትኩረት የሚሹ የሥራ ዘርፎችን በተመለከተ ለየተቋማቱ
ለዘጋቢ ጋዜጠኞች ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል፡፡
በዚሁ መሠረት በተለይ የኢትዮጵያ ሬዲዮ፣ የኢትዮጵያ ኘሬስ ድርጅት እና ሸገር ኤፍ ኤም ወደ ሥራ
ገብተው ሽፋን እየሰጡ ይገኛሉ፡፡
በፍ/ቤቱ ድረ-ገፅ ባለው ጥቂት የሰው ኃይል ቢያንስ በወር አንድ ዜና መረጃዎችን ለመጫን ታቅዶ
በበጀት ዓመቱ ፍ/ቤቱን የሚመለከት ዘጠኝ ዜናዎች እንዲጫኑ ተደርጓል፡፡
የ132 ሰዓት የቪዲዮ ቀረፃ እና የፎቶግራፍ ማንሳት ሥራ ተከናውኗል፡፡ ከዚህ ውስጥ 680 ፎቶ
ግራፎች ተመርጠው በፎቶ ዜና መልክ ታጥበው የተቋሙ ማህበረሰብ እንዲመለከታቸው ተደርጓል፡፡
ስድስት የሚሆኑ ፎቶግራፎችም በድረ-ገፅ ላይ ተጭነዋል፡፡
ከለጋሽ ድርጅቶች በሚገኘው ድጋፍ ከችሎት ሚዲያ ፕሮግራም ጋር በተገባው ውል መሰረት
ለማህበረሰቡ በህጻናት ጉዳይ ላይ ግንዛቤ ሊያስጨብጡ የሚችሉ የቴሌቪዥን ድራማዎች እየተሰራጩ
የሚገኙ ሲሆን 6 ያህል የሚዲያ ፕሮግራም ለማስተላለፍ ተችሏል፣
ስለችሎት አጋዥ ማህበራዊ ሳይንስ ክፍል አገልግሎት የሚያሳዩ ባነሮች በየምድብ ችሎቶቹ
ለህብረተሰቡ መረጃ መስጠት በሚያስችል መልኩ እንዲቀመጥ ተደርጓል፣
በበጀት ዓመቱ 1200 መዝገቦችን በኢፋይሊንግ ስርዓት ለመክፈት ታቅዶ 1‚508 መዝገቦችን በመክፈት
አፈጻጸሙ 125.6% ደርሷል፣
በቪዲዮ ኮንፍረንስ አማካኝነት በሁሉም ፍ/ቤቶች 3‚100 የዳኝነት አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ
በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በ1‚518፣ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ደግሞ በ 4‚886 መዝገቦች
ላይ አገልግሎቱን መስጠት በመቻሉ አፈጻጸምን 206.5% ለማድረስ ተችሏል፣
የቪዲዮ ኮንፍረንስ ማዕከላት ለማስፋፋት በተደረገ ጥረት በቤኒሻንጉል ጠቅላይ ፍ/ቤት አሶሳ ከተማ እና
በደቡብ ብ/ብ/ህ/ክ/ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት በቦንጋ ከተማ እንዲሁም በፌዴራል ከፍተኛፍ/ቤት
አራዳ ምድብ ችሎት የቪዲዮ ኮንፈረንስ ማዕከል በመክፈት አገልግሎት መስጠት ተጀምሯል፣
የቪዲዮኮንፍረንስ አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓቱን በመከታተልና በመገምገም ለሥርዓቱ እንቅፋት
የሚፈጥሩ የቴክኒክ ችግሮችን በመለየት መፍትሄ እንዲያገኙ ተደርጓል፣
በአጠቃላይ በጠቅላይ እና በከፍተኛ ፍ/ቤት የሚሰጠውን የቪዲዬ ኮንፍርንስ አገልግሎት በማጠናከር
አገልግሎቱ የሚሰጡባቸውን ቦታዎች 32 ለማድረስ ተችሏል፣
5.3 በጉዳዮች አይነትና ይዘት የተከፋፈሉ የችሎት አደረጃጀቶችን ለማጠናከር የተያዘው ዕቅድ፡-
የህዝብ አሰፋፈርና ብዛት መሰረት በማድረግ ምድብ ችሎቶችንና ችሎቶችን ለማስፋፋትና ለማጠናከር
በተደረጉ ጥረቶች ከ 2006 በጀት ዓመት መጨረሻ ጀምሮ በከፍተኛ ፍ/ቤት ደረጃ በአራዳ ክፍለ ከተማ
ሶስት ችሎቶችን የያዘ አንድ ምድብ ችሎት፣ በልደታ ሶስት የወንጀል ችሎቶችን የያዘ አንድ ምድብ
ችሎት እና የተለዩ ጉዳዮች የሚስተናገዱባቸው አምስት የፍትሐብሔር ችሎቶች (Specialized
Bench) እንዲከፈቱ ተደርጓል፡፡
በፌ/መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤትም ድሬድዋን ጨምሮ አስራ አንድ ምድብ ችሎቶች የተደራጁ ሲሆን
ከ2006 በጀት ዓመት ጀምሮ አዲስ አበባ በአሥሩም ክፍለ ከተማ ለሚገኙ ምድብ ችሎቶች 23
ተጨማሪ የወጀንልና የፈትሐብሔር ችሎቶች ተከፍተዋል፡፡
በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከዚህ ቀደም የተሰሩ የተጠቂ ህጻናት ጉዳዮች የሚታይባቸው 4
ምድብ ችሎቶች የሲሲቲቪ ካሜራዎች ከግዜ ብዛት እና በአጠቃቀም ጉድለት የአገልግሎት ጥራት
ደረጃቸው የቀነሰ በመሆኑና ከቀላል እስከ ከፍተኛ ጥገናና ማሻሻያ የሚያስፈልጋቸው በመሆኑ፤ ቀደም
ሲል ስራውን ከሰራም ድርጅት ጋር የእድሳት ውል በመግባት ጥገና ተካሂዷል፣
ችሎቶችን በጉዳዩ ዓይነት በማደራጀት አማራጭ የሙግት መፍቻ ሥርዓትን ለመተግበር የተቋቋሙ
የማስማሚያ ጽ/ቤቶችን ጨምሮ የተለያዩ ችሎቶች በጉዳዮች ዓይነት ለምሳሌ በፍትሐብሔር ችሎቶች
ስር የቤተሰብ ችሎት፣ የንግድና ኢንቨስትመንት ችሎት ወዘተ… ተደራጅተው አገልግሎት በመስጠት
ላይ ይገኛሉ፣
በእነዚህ ችሎቶች አፈጻጸም የሚከሰቱ የአደረጃጀት፣ የአሠራር ሥርዓትና የመፈጸም አቅም ችግሮቹን
ተከታትሎ ለመፍታትና ውጤታማነታቸውን ለማሳደግ እንዲቻል ዕቅዶች በየደረጃው አሳታፊ በሆነ
መልኩ እንዲዘጋጁ ከመደረጋቸውም በላይ ከዓመታዊ ዕቅድ የተመነዘሩ ወቅታዊ ዕቅዶች ተለይተው
እየተፈጸሙ የተከሰቱ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችል ክትትልና ድጋፍ ተደርጓል፣
በፌዴራል መጀመሪያና ከፍተኛ ፍ/ቤት የግልግል ዳኝነት አገልግሎት የሚሰጡ የማስማሚያ ጽ/ቤቶች
ተደራጅተው አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ፣ በዚህም የፍ/ቤቶች ጫና በመቀነስ ረገድ ብዙ
የሚቀር ቢሆንም ተከራካሪዎች ጉዳያቸውን በስምምነት ለመፍታት የሚችሉባቸው ምቹ ሁኔታዎችን
ተፈጠርዋል፣
በአማራጭ የሙግት መፍቻ ሥርዓት የሚሳተፉ የህግ ባለሙያዎች (ረዳት ዳኞች) ተመድበው
አመለካከትና የመፈጸም አቅም የሚያጎለብቱ ስልጠናዎችን በመውሰድ አገልግሎቶችን በመስጠት ላይ
ይገኛሉ፣
በጥናት ላይ ተመስርቶ የተዘረጋውን ተከራካሪዎችን የማስማማት ሥርዓት አፈጻጸም በመከታተል፣
በመደገፍና በመገምገም ክፍተቶችን እየለዩ ማስተካከያዎችን ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት
በመከናወን ላይ ይገኛሉ፣
የሥርዓቱን ውጤታማነት ቀጣይነት ባለው ሁኔታ ለማጎልበት የሚያስችሉ ድጋፎች በመደረግ ላይ
ሲሆኑ በየፍ/ቤቶች ለተደራጁ ጽ/ቤቶች የሚያስፈልጉ አቅርቦቶች በመሟላት ላይ ናቸው፤
የሥርዓቱን አፈጻጸምና ጥቅሞች ለሕብረተሰቡ ማስተዋወቅና ተደራሽ የሆነ ፍትህ የማግኘት መብት
ተጠቃሚነቱን አጎልብቱ የፍ/ቤቶች ጫና እንዲቀንስ ለማድረግ የሚያስችሉ የማስተዋወቅ ሥራዎች
በተፈለገው ፍጥነትና መጠን ባይፈጸሙም የተወሰኑ ጅምሮች ታይተዋል፣
በ 2‚6ዐዐ መዛግበት ለተከሰሱ 3‚15ዐ ተጠርጣሪዎች የጥብቅና አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ በ 7‚201
መዛግብት ለተከሰሱ 9‚585 ተጠርጣሪዎች የጥብቅና አገልግሎት በመሰጠቱ አፈጻጸሙን 243%
ለማድረስ ተችሏል፣
ለ 9‚600 ተገልጋዮች የምክር አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ ለ 8‚078 ተገልጋዮች የምክር አገልግሎት
በመስጠትና ሙያዊ ድጋፍ በማድረግ የተገልጋዮችን እርካታ 72% ደርሷል፣
ፈጻሚዎች የተጠቀሙባቸውን መረጃዎች በጥራት በመያዝ ለሌሎች እንዲያስተላልፉ በዕቅድ ከተያዙ
378 መዛግብት 117 ጠብቆ ማስተላለፍ በመቻሉ አፈጻጸሚን 33.3% ደርሷል፣
የተከላካይ ጠበቆችን አቅም የሚገነቡ ሁለት ስልጠናዎችን ለመስጠት ቢታቀድም አንድ ስልጠና ብቻ
በመሰጠቱ አፈጻጸሙ 50% ደርሷል፣
ውጤት ተኮር የዳሰሳ ጥናት ተካሂዷል፣ አስፈላጊ የሆኑ የክትትል፣ ድጋፍና ግምገማ ሥራዎችም
ተሰርተዋል፣
በህጻናት የሕግ ከለላ ማዕከል አማካኝነት ወደ ፍርድ ቤት የሚመጡ በርካታ ህጻናት የህግ፣
የማህበራዊና ስነልቦናዊ ድጋፍ እንዲያገኙ በማድረግ በተቻለ መጠን አማራጭ የግጭት መፍቻ
ሥርዓትን ተጠቅመው ጉዳያቸውን እንዲጨርሱ ተደርጓል፡፡
በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ስር የሚገኙ የአራት ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያዎች የህጻናት ጥበቃና
ማቆያ ክፍሎችን በማደራጀት የቁሳቁስ ግዢው ተጠናቆ ክፍሎቹን በፓርቲሽን የመለየት ስራ
ተጠናቅቋል፣
በፌደራል ፍርድ ቤቶች የሚገኘው የችሎት አጋዥና አገናኝ የማህበራዊ ሳይንስ ክፍል አሰራር
ለህጻናት ምቹ እንዲሆን የሚያደርጉ ድጋፎችን በማድረግ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶች ተለይተው የግዢ
ሂደቱ ተፈጽሟል፣
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በህጻናት ፍትህ አስተዳደር ዙሪያ ያለውን ሚና እና ያሉትን ክፍተቶች
የሚያሳይ ጥናት ተጠናቆ በጥናቱ ግኝቶችና የመፍትሄ አቅጣጫዎች መሰረት በቀጣይነት መወሰድ
በሚገባቸው እርምጃዎች ላይ ያተኮሩ ተግባራት ተከናውነዋል፣
በፌደራል ፍርድ ቤቶች (ድሬዳዋን ጨምሮ) የሚሰሩ ሬጅስትራሮች፣ የዳታ ቤዝ ሰራተኞችና ፋይል
ከፋቾች በአጠቃላይ 112 ተሳታፊዎች የተካፈሉበትና በህጻናት የተሟላ መረጃ አያያዝ ስርአት ላይ
ያተኮረ የውይይት መድረክ የተዘጋጀ ሲሆን በዚህ የውይይት ከመረጃ ቋት የማሻሻያ ስራ በተጨማሪ
የዘርፉ ባለሙያዎች በመረጃ ቋቱ በሚገቡ መረጃዎች ምሉዕነትና ጥራት ዙሪያ ግንዛቤ እንዲኖራቸው
ተደርጓል፣
ከአዲስ አበባ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የአእምሮ ህክምና ትምህርት ክፍል ጋር በመተባበር በፌደራል ፍርድ
ቤቶች ለሚሰሩ የማህበራዊ ሳይንስ ባለሙያዎች ከሱስ ጉዳይ ጋር በተያያዘ የሚያጋጥሙ ችግሮችን
ማሳወቅ ያስቻለ የ2 ቀን ስልጠና የተሰጠ ሲሆን በስልጠናው 24 ባለሙያዎች (8 ሴቶች) ተሳታፊ
ሆነዋል፣
ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ፣ ከህጻናት ጉዳይ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ካላቸው የክልልና
የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አመራሮች፣ ከዩኒቨርሲቲና ኮሌጅ መምህራንና ተማሪዎችን ለተውጣጡ እና
101 ለሚሆኑ ባለሙያዎች በፍትህ ስርዓት ስለሚያልፉ ሕፃናት፣ በሴቶች ላይ ስለሚፈፀሙ የቤት
ውስጥ ጥቃቶች ተፈጻሚ ስለሚሆኑ የሕግ ማዕቀፎች እና ስለምርመራ አካሄድ፣ በወንጀል ለተሳተፉ
ሕፃናት ተፈጻሚ ስለሚሆኑ የወንጀል ሕግ ስነስርዓት እና ከሕፃናት ሕግ ከለላ ማዕከል ጋር በቅርበት
እና በተጠናከረ መልኩ አብሮ መስራት ስለሚቻልበት ሁኔታ ሁለት ዙር የአቅም ግንባታ ስልጠና
ተሰጥቷል፣
በአጠቃላይ በ 2007 በጀት ዓመት ለ 687 የፍትህ ስርዓቱ ባለሙያዎች በህጻናት ፍትህ አስተዳደርና
ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን በማዘጋጀት 275 ሴቶችን ማሳተፍ
ያስቻሉ በርካታ በስልጠናዎች ተሰጥተዋል፣ በፍትህ ስርአት ለሚያልፉ ሕጻናት ሁሉን አቀፍ ድጋፍ
ለመስጠት በተቋቋመው የቅብብሎሽ ስርዓት ላይ ያተኮሩ በርካታ የውይይት መድረኮችም
ተዘጋጅተዋል፣
አለም አቀፍ የሴቶች ቀን በተለያዩ ዝግጅቶች የጥያቄና መልስ ውድድር፣ ዕለቱን አስመልክቶ
አስተማሪ ብሮሸሮችን በማዘጋጀትና የስነ ጽሑፍ ዝግጅት በማቅረብ አስተማሪና አሳታፊ በሆነ መልኩ
ተከብሯል፣
5.8 የሰበር ውሳኔዎችንና ሌሎች የህትመት ውጤቶችን ዝግጅትና ሥርጨት ለማሻሻል በተያዘው
ዕቅድ፡-
የሠበር ውሣኔዎችን የያዙ ሕትመቶች በጥራት እንዲዘጋጁና በበቂ ቅጅ ታትመው የተገልጋዮችን
ፍላጎት ባገናዘበ መልኩ እንዲሰራጩ ለማድረግ የቅጽ 14፣ 15 እና 16 ህትመትና ስርጭት
የተጠናቀቀ ሲሆን ቅጽ 17 ለማሳተም የሚያስችሉ ዝግጅቶችን በማጠናቀቅ Soft copy በፌ/ጠ/ፍ/ቤት
ድረ ገጽ ተጭኖ ለሕዝብ እንዲደርስ ተደርጓል፣
ከዚህ በፊት ለህትመት ያልበቁና እስከ በጀት ዓመቱ መጨረሻ አስገዳጅ የህግ ትርጉም የተሰጠባቸውን
የሰበር ችሎት ውሳኔዎች በማሰባሰብና ተገቢውን ጭብጥ በመለየት ለሕትመት የሚበቁበትን ሁኔታ
የማመቻቸት ተግበር ተከናውኗል፣ ፣
ቀደም ሲል የታተሙ ቅጽ 6-13 የሰበር ውሳኔዎችን ድጋሚ ሕትመት ለመስራት የሚያስችሉ
ዝግጅቶች ተጠናቅቀዋል፣
በቅፅ መልክ የተዘጋጁ የሰበር ውሳኔዎችን ማውጫ ሰንጠረዥ በማሻሻል በተቋሙ ድረ-ገፅ
ተጭነዋል፣
የፌዴራልና የክልል አዋጆችን፣ ደንቦችንና መመሪያዎችን አሰባስቦ ለተጠቃሚው ለማድረስ በተደረገ
ጥረት የተለያዩ ክልሎች አዋጆች፣ ደንቦችና መመሪያዎችን አሰባስቦ ለዳኞች ማሰራጨት ተችሏል፣
የፌዴራል ፈ/ቤቶችን ቤተመጻሕፍት ለተጠቃሚዎች ምቹ እንዲሆን ለማድረግ የሚያስችሉ
ተግባራትን በማከናወን የተቋሙን ቤተ-መጽሐፍት ለማጠናከር ብዛታቸው 288 የሆነ 108 ዓይነት
መጻህፍት በብር 38‚534.50 ተገዝተው አገልግሎት ላይ ወለዋል፣
በአጠቃላይ የጥናትና ሕግ ድጋፍ አገልግሎቶችን በማጠናከር የሰበር ውሳኔዎችን የያዙ ቅጾችን ማሳተምን
ጨምሮ የሕግ ጥናቶችን ለማካሄድና የተለያዩ የሕግ ጆርናሎችን አዘጋጅቶ ለማውጣት የሚደረጉ ጥረቶች
ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ተደርጓል፡፡
የሲቪል ሰርቪስ ሥራ ክፍሎች ለዳኝነት ዘርፉ የሚያደርጉትን የድጋፍ አገልግሎት በተሟላ መልኩ
ለመስጠት የሚያስችል የአሠራር ግልጽነት እንዲኖራቸው ለማድረግ የሚረዱ ክትትልና ድጋፎች
የተደረጉ ሲሆን አፈጻጸማቸውን እየገመገሙ ችግሮቻቸውን መፍታት የሚያስችል አሠራር መተግበር
እየተለመደ መጥቷል፣
በዚህም እያንዳንዱ የሲቪል ሰርቪስ ሥራ ክፍል የሳምንት ዕቅድ አፈጻጸሙን በመገምገም ጠንካራ
አፈጻጸሞችን ማበረታታትና ክፍተቶችን መሙላት የሚያስችሉ አሠራሮችን በማጠናክ ለይ ይገኛል፣
ወርሃዊ የግምገማ ሪፖርቶችን ማዘጋጀትና ለሚመለከታቸው ክፍሎች አድርሶ በመረጃ ምንጭነት
እንዲያገለግሉ የማድረጉ ሥራም ተጠናክሮ ቀጥሏል፣
በዳኝነት ዘርፉ የሚቀርቡ ቅሬታና አቤቱታዎች በፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ በኩል በመስተናገድ
ላይ ሲሆኑ የሲቪል ሰርቪስ ሥራ ክፍሎችን በተመለከተ የሚቀርቡት በሥነ ምግባር ክፍል እና
በዲስፕሊን ኮሚቴ አማካኝነት በመስተናገድ ላይ ይገኛሉ፣
በዚህም ሰብዓዊ መብቶች እንዲከበሩና የመልክም አስተዳደርና የሥነ ምግባር መርሆች እንዲተገበሩ
በማድረግ የፍ/ቤት ተገልጋዮችን እርካታ ለማሳደግ በአፈጻጸም ለሚከሰቱ ችግሮች የሚቀርቡ
አቤቱታዎችና ቅሬታዎች የሚስተናገዱበት ሥርዓት ተዘርግቶ በመተግበር ላይ ይገኛል፣
በበጀት ዓመቱ በፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ጽ/ቤቱ በኩል ዳኞችን የሚመለከቱ 72 የዲሲፕሊን
አቤቱታዎች የቀረቡ ሲሆን በፍርድ ምርመራ ተጣርተው ለጉባዔው ከቀረቡ 21 የዲሲፕሊን
ቅሬታዎች ውስጥ 15 ቱ በዲሲፕሊን የማያስጠይቁ በመሆናቸው ተዘግተዋል፣
በ 6 ዳኞች ከቀረቡ አቤቱታዎች 3ቱ ዳኞች የጽሁፍ መልስ እንዲሠጡ፣ 1 ዳኛ ጉባዔው ፊት
ቀርበው የቀረበባቸውን ቅሬታ እንዲያስተባብሉ፣ 2 ዳኞች ከስራቸው ታግደው ለጉባዔው የጽሁፍ
መልስ እንዲሠጡና በአካል ቀርበውም እንዲያስረዱ ተደርጓል፣
ጉባዔው በ 6 የዲሲፕሊን ጉዳዮች ላይ ከዳኞች የተሠጡ መልሶችን መርምሮ፤ 2 ዳኞች የጽሁፍ
ማስጠንቀቂያ፣ 1 ዳኛ የቃል ማስጠንቀቂያ፣ 1 ዳኛ የቀረበባቸውን ቅሬታ በአግባቡ አስተባብለዋል
በሚል ነጻ እንዲሆኑ የወሠነ ሲሆን፤ 1 ዳኛ የዲሲፕሊን ጥፋት መፈጸማቸውን በማረጋገጥ ውሳኔ
ለመስጠት እንዲቻል ዳኛው በአካል ተገኝተው እንዲያስረዱ ትዕዛዝ ተሰጥቷል፣
በሙስና ወንጀል ጥፋተኛ መሆናቸው የተረጋገጠ ሁለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች
በህገመንግስቱ አንቀጽ 79/4//ሀ/ መሠረት ከዳኝነት ሥራቸው እንዲነሱ በጉባዔው የተሠጠ ውሳኔ
ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተላልፏል ሹመታቸው ተነስቷል፤
በሲቪል ሰርቪስ ሠራተኞች አገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ የሚቀርቡ የሥነ ምግባር ጥሰትና የዲሲኘሊን
ግድፈት ጥቆማዎች፣ ቅሬታዎችና የዲስፕሊን ግድፈቶችን በማስተናገድ 40 የሚሆኑ የሥነ ምግባር
ጥቆማዎችን በማስተናገድ የማጣራትና ተገቢው እርምጃ እንዲወሰድ የሚያደርጉ ተግባራት
ተከናውነዋል፣
በአምስት ሠራተኞች በፈጸሙት የዲስፕሊን ግድፈት ለዲስፕሊን ኮሚቴ ክስ ቀርቦ ሁለቱ
ጥፋተኛነታቸው በመረጋገጡ ከሥራ እንዲሰናበቱ ውሳኔ ተሰጥቶባቸዋል፣ የቀሪዎቹ ጉዳይ በመታየት
ላይ ይገኛል፣
ዳኝነት የተጠየቀባቸው ጉዳዮች ከጅምሩ እስከ ፍጻሜው በህግ የተቀመጡ የሥነ ሥርዓት ድንጋጌዎችን
ተከትለው እየተፈጸመ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ከችሎቶችና ከመዝገቦች መረጃ በማሰባሰብ
ለኢንስፔክሽን በተዘጋጀው ቼክ ሊስት መሰረት ችግሮችን የለየና ተግባራዊ ሊሆኑ የሚችሉ አማራጭ
መፍትሄዎችን የያዘ ሪፖርት ተዘጋጅቷል፣
በዳኞች አስተዳደር ጉባዔ በኩል የቀረቡ 72 የተገልጋይ ቅሬታ/አቤቱታዎችን በመመርመር የውሳኔ
መነሻ ሀሳቦች ተዘጋጅተው ለጉባዔው ቀርበዋል፣
ዳኞችም ሆኑ ድጋፍ ሰጪ የሲቪል ሰርቪስ ሥራ ክፍሎች በለውጥ ሥርዓቱ አተገባበር ንቁ ተሳታፊ
መሆናቸውንና ችግሮቻቸውን ለይተው መፍትሄ እንዲያገኙ በማድረግ አገልግሎት አሰጣጣቸውን
ማሻሻላቸውን በመከታተል፣ በመደገፍና በመገምገም ወርሐዊ የአፈጻጸም ሂደታቸውን በሪፖርት
እንዲገልጹ ተደርጓል፣
በሁለም የፌዴራል ፍ/ቤቶች የችሎት ቦታዎች በመገኘት የኢንስፔክሽን ተግባር ተከናውኖ 3 የተሟላ
ኢንሰፔክሽን ሪፖርት እና አንድ ረቂቅ የቅኝት ሪፖርት ማዘጋጀት ተችሎአል፡፡
በሁሉም የፌ/ፍ/ቤቶች የድሬዳዋም/ችሎቶችን እና የፌ/ሸሪዓ ፍ/ቤቶችን ጨምሮ የናሙና ቅኝት ስራ
ተከናወኖ በ 828 መዝገቦች ላይ በ109 የችሎት ቦታዎች ላይ ቅኝት የተደረገ ሲሆን ከችሎቶችና
ከፍርድ ሥራ መዝገቦች መረጃ በማሰባሰብ 3 የተሟላ የኢንስፔክሽን ሪፖርቶችና አንድ ረቂቅ የቅኝት
ሪፖርት ማዘጋጀት ተችሏል፤
በዚህም በውስጥ አሰራር በፍርድ ቤቶቹ የታዩ የአሰራር ክፍተቶች በመለየትና ማመላከት ተችሎአል፡፡
የፌደራል ፍ/ቤቶችን የአገልግሎት አሰጣጥ አስመልክቶ የባለድርሻ አካትን አስተያየት ማሰባሰብ ያስቻለ
የዳሰሳ ጥናት ተካሂዶ ረቂቅ የጥናት ሪፖርት ተዘጋጅቷል፣
በአማራጭ የሙግት መፍቻ ሥርዓት የተከፈቱ የማስማሚያ ጽ/ቤቶችን ጨምሮ በሁሉም ችሎቶች
እና የሲቪል ሰርቪስ ሥራ ክፍሎች የሚሰጡ አገልግሎቶች በተለወጡ አሠራሮች የተቃኙና የሰብዓዊ
መብት ድርጊት መርሃግብር ድንጋጌዎችን ያስከበሩ መሆናቸውን ለማረጋገጥ የሚያግዙ ክትትል፣
ድጋፍና ግምገማዎች ተካሂደዋል፣
የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ የመልካም አስተዳደርና የሥነ ምግባር መርሆችን የተከተሉ መሆናቸውን
ለማረጋገጥ በተካሄዱ ክትትል፣ ድጋፍና ግምገማዎች አንጻራዊ በሆነ መልኩ ነጻ፣ ግልጽ፣ ገለልተኛ፣
ኪራይ ሰብሳቢነትን የሚታገል፣ ተገልጋዮችን በአግባቡ ማስተናገድ ያስቻለ አገልግሎት ለመስጠት
የሚያስችሉ ጅምሮች መኖራቸውን ማረጋገጥ ተችሏል፣
በፍ/ቤቶች ውስጥ የሴቶችን ተሳታፊነት ለማሳደግ በሁሉም የሥራ ክፍል ዕቅዶች የሥርዓተ ጾታ
ጉዳዮች መካተታቸውን ለማረጋገጥና የሥርዓተ ጾታ ጉዳይ በየሥራ ዘርፉ ትኩረት እንዲሰጠው
(Gender Mainstreaming) ለማድረግ የሰው ኃይል አደረጃጀትን፤ ሥልጠናና የአቅም ግንባታን፤
የመረጃ አደረጃጀትና አሰባሰብን፤ ተቋማዊ አደረጃጀትን፤ የሥራ መመሪያዎችና ደንቦች ዝግጅትን፣
የዕቅድ ዝግጅት፤ ክትትልና ግምገማ አካሄድን ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብን በሚመለከቱ ነጥቦች
ላይ ያተኮሩ ክትትሎች፣ ድጋፎችና ግምገማዎች ተደርገዋል፣
መሆናቸውን ያመላክታል፡፡
ካለፈው በጀት ዓመት የተላለፉ 9,798 መዛግብትን መነሻ በማድረግ በበጀት ዓመቱ 16,883 አዲስ
መዛግብት እንደሚከፈቱ አቅዶ በበጀት ዓመቱ 15,830 በመከፈታቸው አፈጻጸሙ 94 %፣ በበጀት
ዓመቱ እንደገና ይከፈታሉ ተብለው ከታቀዱት 950 መዛግብት በበጀት ዓመቱ 1,153
በመከፈታቸው አፈጻጸሙ 121%፣ በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ 27,260 መዛግብት ለውሳኔ
እንዲቀርቡ ታቅዶ በበጀት ዓመቱ 26,721 መዛግብት በመቅረባቸው አፈጻጸሙ 98% ደርሷል፣
ዕልባት ያገኛሉ ተብለው ከተያዙት 26,310 መዛግብት ውስጥ 15,413 እልባት በማግኘታቸው
59% መፈጸም ተችሏል፣ ይህም ዳኞች በእረፍት የቆዩባቸውን 2 ወራት ያካተት በመሆኑ የ7 ወር
አፈጻጸም ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፣
በዚህም መሰረት በፌ/ከ/ፍ/ቤት የ2007 በጀት ዓመት አፈጻጸም የማጣራት አቅም 90.75፣
የመጨናነቅ ሁኔታ 1.73 እንዲሁም የመዝገብ ክምችት 0.73 ሆኗል፡፡
ዕልባት ያገኙ መዝገቦችን ጊዜ የሚያመለክተው ዳታቤዝ እልባት ከተሰጠባቸው መዛግብት መካከል፡-
መሆናቸውን ያመላክታል፡፡
በፌ/ጠ/ሸሪዓ/ፍ/ቤት
በበጀት ዓመቱ በቀጥታ እና በይግባኝ ክሶች አዲስ ፋይሎች ይከፈታል ተብሎ በዕቅድ ከተያዘው
7,512 ውስጥ 7,158 ፋይሎች አዲስ ተከፍቷል፡፡ ይህም ከተያዘው ዕቅድ አንፃር 95.28%
ፐርሰንት ተከናውኗል፡፡
በበጀት ዓመቱ በቀጥታና በይግባኝ ፋይሎች ይወሰናሉ ተብሎ በዕቅድ ከተያዘው 7,512 ውስጥ
7,138 ፋይሎች ውሣኔ አግኝተዋል፡፡ ይህም ከተያዘው ዕቅድ አንፃር 95.02% ፐርሰንት
ተከናውኗል፡፡
314 መዝገቦች ወደ ቀጣዩ በጀት ዓመት በቀጠሮ ተላልፏል፡፡
ፌ/ከ/ ፍ/ቤት 9,738 15,830 1,153 26,721 15,413 11,308 90.75 1.73 0.73
መ/ደ/ፍ/ቤት 21,395 99,929 20,808 142,132 112,196 29,936 92.09 1.2 0.2
አጠቃላይ 33,366 128,571 22003 183,940 138,089 45,851 91.70 1.3 0.3
ድምር
ወንጀል 2ኛ 0 0 0 19 57 0 0 76
ከ6
ከ3ዐ ቀን ከ6 ወር ከ1-3 ከ3-6
ከ1-2 ወር ከ2-6 ወር ዓመት ድምር
ችሎት ጉዳይ በታች 1ዓመት ዓመት ዓመት
በላይ
ሰበር አጣሪ 2ኛ 86 105 1118 1898 510 0 0 3392
2 ከ/ሸ/ፍ/ቤት 7 38 45 33 12
ግልጽ ባልሆኑ ወይም በሚቃረኑ 1,050 ውሣኔዎች /ትዕዛዞች/ ላይ የአፈጻጸም ሂደቱ ከመከናወኑ
በፊት ጉዳዩን ለሚመለከተው ፍ/ቤት በማቅረብ መብራሪያ መጠየቅና ግልጽ ማድረግ ተችሏል፣
በ 744 አቤቱታዎች ላይ የማጣራት ሥራ ተሠርቷል፣
ርክክብ የሚደረግባቸውን 885 ንብረቶች ፍርድ ያረፈባቸው መሆናቸው፣ አድራሻቸው መለየቱና
በፍ/ባለዕዳው ስም የተመዘገቡ መሆኑን ከሚመለከተው አካል ጋር በማጣራት የማስፈፀም ተግባር
ተከናውኗል፣
301 በሀራጅ/ጨረታ/ እንዲሸጡ የቀረቡ ንብረቶች በህጉና በመመሪያው መሠረት ተሸጠዋል፣
692 በባለሙያዎች የተገመቱ፣ 105 በመሬት አስተዳደር የተካፈሉ፣ 445 በመሬት አስተዳደር
የተገመቱ፣ 110 ጉዳዮች በግራ ቀኙ ስምምነት ያለቁ፣ 316 መዝገቦች ወደ ሐራጅ የተመሩ እና
7032 እንደፍርድቤቱ ትዕዛዝ ተፈፅመው እንዲዘጉ የተደረጉ ሲሆን በአጠቃላይ 8700 ጉዳዮችን
ለማስተናገድ ተችሏል፡፡
የፍ/ቤት ውሣኔዎች /ትዕዛዞች/ የተሟሉና ግልፅ መሆናቸውን በማረጋገጥ እና በአፈጻጸም ሂደት
መዝገቦችን በማጥራት ተግባር የተከሰቱ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ ጥረቶች
ተከናውነዋል፣
በ 300 ለአፈፃፀም አስቸጋሪ የሆኑ የፍ/ቤት ውሣኔዎችና ትዕዛዞችን በጥራት እና በቅልጥፍና
አጣርቶ ለባለጉዳይ አገልግሎት የሚሰጥበትን ሁኔታ እንዲጎለብት ተደርጓል፣
የህግ ጉዳዮች በተመለከተ ከየሥራ ክፍሎች ለቀረቡ ጥያቄዎች ሙያዊ አስተያቶች ተሰጥተዋል፣
የሲቪል ሰርቪስ ሥራ ክፍሎችን የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት በተመሳሳይ ሁኔታ ለመገምገም የሚያስችል
ሥርዓት ቢዘረጋም የሥራ ክፍሎች የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራታቸውን መለካት የሚያስችሉ መስፈርቶችን
የያዘ የአገልግሎት አሰጣጥ ስታንደርድ ዝግጅት ባለመጠናቀቁ የተገልጋዮችን አስተያየት ማሰባሰብ
አልተቻለም፡፡
ጠቅላይ ፍርድ ቤት
ፌ/ከ/ፍርድ ቤት
ዘመናዊ የኦዲት ስርዓትን ተግባራዊ በማድረግ የበጀትና የንብረት አስተዳደርና አጠቃቀምን ከዕቅድና
አፈጻጸምና ከተጠያቂነት ሥርዓት ጋር እንዲያያዝ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራት፡-
የፋይናንስ ኦዲት፣የጥሬ ገንዘብ እና ሠነድ ቆጠራ በማድረግ የፈሰስ ሪፖርት በማዘጋጀት፣ በደረሰኝ
ላይ ምልክት በማድረግ /Cut off/፣ቋሚና አላቂ ንብረቶች ቆጠራ በማካሄድ፣ በጠቅላይ ፍ/ቤትና
በፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት የግል ማህደር እና ከደመወዝ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮች ላይ ምርመራ
በማድረግ፣ በስጋት ዳሰሳ ላይ ተመስርቶ ለስጋት የተጋለጡ አካባቢዎችን በመለየት፣ በጠቅላይ
ፍ/ቤት የአላቂና የቋሚ እቃዎች እንዲሁም የገቢ እና የወጭ ሂሣብ ምርመራ ሪፖርት በማዘጋጀት
ለገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚ/ር ተልኳል፣
በጠ/ፍ/ቤት እና በመ/ደረጃ ፍ/ቤት የተሰብሣቢና የተከፋይ ሂሣብ የማጣራት፣ የባንክ ሂሣብ
ማስታረቂያ ትክክለኛነት እና የበጀት ተግባራዊነት የማረጋገጥ ስራ ተከናውኗል፡፡
በፌ/ጠቅላይ ፍ/ቤት፣ በፌ/ከፍተኛ ፍ/ቤት እና በፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት የግዢ ምርመራ ተከናውኖ እና
የመውጫው ስብሰባ ተደርጐ ሪፖርቱ ተዘጋጅቷል፣
በህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ሂሳብ ስራ ላይ ምርመራ ተደርጓል፣
የበጀት፣ ፋይናንስ ንብረት አስተዳደርና አጠቃቀምን በተመለከተ በሶስቱም ፍ/ቤቶች የአላቂ
ንብረቶች ቆጠራ ተከናውኖ በተገኘው ውጤት መሠረት የፈሰስ ሪፖርት ተዘጋጅቶ ለሚመለከታቸው
ኃላፊዎች እና ባለድርሻ አካላት ቀርቧል፣
የጥሬ ገንዘብ እና የሰነድ ቆጠራ በማድረግ በደረሰኞች መጨረሻ የመለያ ቀን ተወስዷል፣ የቋሚ እና
አላቂ ንብረቶች ቆጠራ ተከናውኗል፣
በአጠቃላይ በኦዲተሮች የተለዩ የበጀት፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደርና አጠቃቀም ክፍተቶች
በአግባቡ ተጣርተው ተገቢውን ምላሽ እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን የክዋኔ ኦዲትን በተመለከተ የግል
ማህደር ላይ ምርመራ እየተደረገ ይገኛል፣ ከደመዝ ጋር ተያያዥነት ያላቸውን ጉዳዮች
የመመርመር ተግባር በመከናወን ላይ ይገኛሉ፣ በስጋት ዳሰሳ ላይ ተመስርቶ ለስጋት የተጋለጡ
አካባቢዎችን የመለየት ተግባር ተከናውኗል፣ የግዥ እቅድ ጸድቆ ስራ ላይ መዋሉን የማረጋገጥ
ሰራ ተሰርቷል፡፡
በዚህም የፋይናንስና ከዋኔ ኦዲት ሪፖርቶች ተዘጋጅተው ለሚመለከታቸው አካላት እንዲደርሱ ለማድረግ
ከተያዘው ዕቅድ 84.97 መፈፀም ተችሏል፡፡
መደበኛ በጀት
በዘጠኝ
ወራት
ለክርክሮች ውሳኔ መስጠት ለሥራ አመራርና አስተዳደር በአጠቃ ላይ በአጠቃ ላይ በስራ
ለበጀት ዓመቱ በዘጠኝ ወራት ላይ
ፍርድ ቤቶች ለበጀት ዓመቱ በዘጠኝ ወራት ለበጀት ዓመቱ በዘጠኝ የተፈቀደ በስራ ላይ የዋለ የዋለ ለበጀት ዓመቱ በዘጠኝ ወራት የዘጠኝ
የተፈቀደ በስራ ላይ የዋለ የተፈቀደ ወራትዓመቱ በ% የተፈቀደ በስራ ላይ የዋለ ወራት በስራ
በስራ ላይ የዋለ ላይ የዋለ
በ%
የፌደራል ጠቅላይ 16,369,502.00 16,121,139.29 28,152,115.00 28,152,115.00 44,521,617.00 44,273,254.29 99.44% 12,000,000.00 16,369,502.00 59.68
ፍርድ ቤት
የፌደራል ከፍተኛ 22,753,793.00 25,305,299.39 10,695,801.00 12,974,369.86 33,449,594.00 38,279,669.25 114.43% 6000000.00 22,753,793.00 87.74
ፍርድ ቤት
የፌደራል 42,398,247.00 40,634,886.43 17,300,534.93 16,712,151.62 59,698,781.93 57,347,038.05 96.06% 25,000,000.00 42,398,247.00 79.35
መጀመሪያ ፍርድ
ቤት
የፌደራል ፍርድ
ቤቶች ጠቅላላ 81,521,542.00 82,061,325.11 56,148,450.93 57,838,636.48 137,669,992.93 139,899,961.59 101.61% 43,000,000.00 81,521,542.00
ድምር 75.03
የፌደራል ሸሪዓ 1,931,900.00 1,623,530.00 5,890,800.00 5,218,803.03 7,822,700.00 6,842,338.03 87.47% 1,931,900.00 -
ፍርድ ቤት
በፌዴራል ጠ/ፍ/ቤት
የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ የሙያ የሥነ ምግባር ብቃት ያላቸው ዕጩ ዳኞችን
አወዳድሮና መልምሎ ለማሾም በአዋጅ ቁጥር 684/2002 በተሠጠው ስልጣን መሠረት
የጠቅላይ፣ የከፍተኛና የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ዳኞችን ለማሾም የሚያስችልና በግልጽ ውድድር
ላይ የተመሠረተ ምልመላ ተካሂዶ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተወዳዳሪዎች ምርጫ
በመጠናቀቁ ሰባት ወንዶች እና አንድ ሴት ዕጩ ዳኞች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲሾሙ
ተደርጓል፡፡
በሚያዝያ ወር መጀመሪያ 2007 ዓ.ም በተጠናቀቀ የዕጩ ዳኞች ምዝገባ ከየክልሉ የተላኩትን
ጨምሮ ለፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት 1243 ወንድና 277 ሴት በአጠቃላይ 1520
አመልካቾች፤ ለፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት 387 ወንድና 68 ሴት በአጠቃላይ 455 አመልካቾች
እጩዎች ለፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት 69 ወንድ እና 10 ሴት በድምሩ 79 አመልካቾች በአጠቃላይ
ለሶስቱም ፍ/ቤቶች 2056 አመልካቾች ለውድድር የተመዘገቡ ሲሆን ከፍተኛ የዳኞች እጥረት
ለሚታይበት የጠቅላይ ፍ/ቤት ተወዳዳሪዎች ቅድሚ በመስጠት መረጃዎቻቸውን አደራጅቶ፣
የጽሁፍእና የቃል ፈተናዎችን እንዲወስዱ አደርጎና የሕዝብ አሰተያየቶችን አሰባስቦ አሸናፊ የሆኑ
ተወዳዳሪዎችን የበጀት ዓመቱ ከመጠናቀቁ በፊት ለማሾም ተችሏል፣
በቀሩት የፌደራል መጀመሪያ ደረጃና የከፍተኛ ፍርድ ቤት ተወዳዳሪዎች ላይ መረጃዎቻቸውን
የማደራጀቱ ሥራ ተጠናቅቆና ቅድመ ሹመት ምልመላዎች ተከናውነው አሸናፊ የሆኑ ዕጩ
ዳኞችን በቀጣዩ በጀት ዓመት እንዲሾሙ ለማድረግ የሚያስችሉ ዝግጅቶች በመደረግ ላይ
ይገኛሉ፡፡
በአጠቃላይ በፌደራል ጠ/ፍ/ቤት አዲስ የተሸሙትን ዳኞች እና ፕሬዝዳንቶች ጨምሮ 2 ሴት እና
30 ወንድ በአጠቃላይ 32 ዳኞች የሚገኙ መሆኑን ማረጋገጥ ተችሏል፣
የጠቅላይ ፍ/ቤት ድጋፍ ሰጪ የሲቪል ሰርቪስ ሥራ ክፍሎች ክፍት የሥራ መደቦች በሰው ኃይል
ለመሙላት በተያዘው ዕቅድ፡-
ለማድረስ ተችሏል፡፡
በአደረጃጀት ለውጥና አዳዲስ የስራ መደቦች በመፈጠራቸው ከሥራ ክፍሎች የቀረቡ ጥያቄዎችን
በማስተናገድ ለድምጽ ቀራጭ 10 የስራ መደብ ተጠይቆ 8 ማስፈቀድና ለሾፌር 29 የሥራ
መደብ ተጠይቆ ሁሉንም ማስፈቀድ በመቻሉ 37 ተጨማሪ የሥራ መደቦችን እንዲፈቀዱ
ተደርጓል፣
ጠቅላይ ፍ/ቤቱ በውክልና የሰው ኃይል በሚያሟላባቸው ከፕሳ 5 በላይ ባሉ የሥራ መደቦች
ለከፍተኛ ፍ/ቤት 7 በቅጥር፣ ለመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት 10 በቅጥር፣ ለሸሪዓ ፍ/ቤቶች 3 በቅጥር
እና 9 በደረጃ ዕድገት ማሟላት ተችሏል፣
አዳዲስ የስራ መደቦች እንዲፈቀዱ ከስራ ክፍሎች የቀረቡ ጥያቄዎችን በማስተናገድ ለድምጽ
ቀራጭ 10 የስራ መደብ ተጠይቆ 8 ተፈቅዷል፤ ለሾፌር 29 መደብ ተጠይቆ ሁሉም ተፈቅዷል፡፡
የሚመለከተው ሥራ ክፍል (የሰው ኃይል አስተዳደር) የተፈቀዱ መደቦችን በሰው ኃይል
ለመሙላት የሚያስችል ቅጥር ለመፈጸም በሂደት ላይ ይገኛል፣
ከተለያዩ ከ5 ያላነሱ የፊደራል ተቋማት የሰው ሃይል አስተዳደር ተሞክሮ ልውውጥ በሠራተኞች
አያያዝ፣ ጥቅማ ጥቅም ወዘተ ጥሩ ተሞክሮ ተሰባስቧል፡፡
በአጠቃላይ ድጋፍ ሰጪዎችን በተመለከተ 244 ሴት እና 178 ወንድ በአጠቃላይ 422 የሲቪል
ሰርቪስ ሠራተኞች በሥራ ላይ የሚገኙ ሲሆን 2 ሠራተኞች በጡረታ(1 ወንድ 1 ሴት)፣ 24 ሴት
እና 22 ወንድ በድምሩ 46 ሠራተኞች ደግሞ በገዛ ፈቃዳቸው ሥራቸውን ለቅቀዋል፣ አንድ ሠራተኛ
በሞት የተለዩ ሲሆን በጥቅሉ 26 ወንድ እና 23 ሴት ሠራተኞች ከመ/ቤቱ ተሰናብተዋል፡፡
የሚለቁበትን ምክንያት እንዲገልጹ በተዘጋጁ መጠይቆች አብዛኞቹ የተሻለ ደመወዝና ጥቅማ ጥቅም
በማግኘታቸው መሆኑን ማረጋገጥ ተችሏል፣
49 ሴት 76 ወንድ በአጠቃላይ 125 ዳኞች እና 988 የሲቪል ሰርቪስ ሠራተኞች የሚገኙ ሲሆን
ክፍት የሥራ መደቦችን በሰው ኃይል ለመሙላት 81 ሠራተኞች ተቀጥረዋል፡፡
48 ሠራተኞች በገዛ ፈቃዳቸው ሥራቸውን ለቀዋል፡፡
ዕድሜያቸው 6ዐ የሞሉ 3 ሠራተኞች እና በ 55 ዓመታቸው ጡረታቸውን የጠየቁ 2 ሠራተኞች
በአጠቃላይ 5 ሰራተኞች በጡረታ ተቋሙን ለቀዋል፡፡
በፌ/ጠ/ሸሪዓ ፍ/ቤት
በሸሪዓ ፍ/ቤት አዳዲስ ዳኞችን ለማሾም ለሚመለከተው አካል ጥያቄ የቀረበ ሲሆን የዳኞችን
የጥቅማጥቅም ጥያቄ ቀርቦ መልስ እየተጠበቀ ይገኛል፣
የሸሪዓ ፍ/ቤት አዲስ መዋቅር እንዲዘጋጅ ለቀረበው ጥያቄ የይሁንታ መልስ በመገኘቱ አዲስ
መዋቅር የሚያዘጋጅ ኮሚቴ ተዋቅሮ እንዲሠራ ተደርጓል፣
ያሉትን ክፍት የሥራ መደቦች በሰው ኃይል ለመሙላት በተያዘው ዕቅድ 13 መደቦች በደረጃ
ዕድገት፣ 15 መደቦችን ደግሞ በቅጥር ለመሙላት ተችሏል፤
የሥራ መልቀቂያ ጥያቄ ያቀረቡ 5 ዳኞች (2 የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ዳኞች፣ 3
የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ዳኞች) ስንብት ተፈቅዷል፣
1 ዳኛ ያለባቸው የዲሲፕሊን ክስ እልባት በማግኘቱ የመልቀቂያ ጥያቄያቸው እንዲስተናገድ
በጉባዔው በመወሠኑ ይኸው እንድፈጠም ተደርጓል፤
8 የህግ ረዳቶች ያቀረቡትን የመልቀቂያ ጥያቄ በመቀበል ስንብቱ ተፈቅዶላቸዋል፣
ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ለሚሾሙዋቸው ዳኞች የጉባዔውን አስተያየት ለማግኘት
የሚልኩዋቸው ጥያቄዎችን በማስተናገድ ከደ/ብ/ብ/ህ/ክልል 32፣ ለሐረሪ 1፣ ከትግራይ 39፣
ከአማራ ክልል 71፣ ከጋምቤላ 13 ዕጩዎች ላይ በህግ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ የጉባዔው
አስተያየት እንዲደርስ ተደርጓል፡፡
9.3 ለዳኝነት አገልግሎት አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶች እንዲሟሉ ለማድረግ በተያዘው ዕቅድ፡-
የሸሪያ ፍ/ቤቶችን ጨምሮ ሁሉም የፊደራል ፍ/ቤት ዳኞች እና ቤተሰቦቻቸው የጤና መድህን
ሽፋን እንዲያገኙ የ225 ዳኞች የኢንሹራንስ መረጃዎች ተደራጅተው ከኢትዮጵያ መድህን ድርጅት
ጋር ውል ተገብቶ ተገብቷል፣
የፌዴራል ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ባካሄዳቸው ስብሰባዎች የጉባኤ ተሿሚዎች የቤት አበል
ጥያቄን ለማስተናገድ በተካሄደው ጥናት መሰረት ከሐምሌ 1/2006 ዓ.ም ጀምሮ እንዲከፈል
ተደርጓል፣ የፌደራል ፍ/ቤት ረዳት ዳኞች ከሐምሌ 1/2006 ዓ.ም ጀምሮ የደመወዝ ጭማሪ
እንዲያገኙ ተፈቅዷል፣ በበጀት ዓመቱ መግቢያ መንግስት ለፌደራል መንግስት ሠራተኞች
ያደረገውን የደሞዝ ጭማሪ መነሻ በማድረግ ጉባዔው የዳኞችንና የተሿሚዎች ደሞዝ በመንግስት
መመሪያ መሠረት ተሠልቶ ተፈጻሚ ሆኗል፣ ድሬዳዋ የሚገኙ የፌዴራል ፍ/ቤት ዳኞችና
ተሿሚዎች ያቀረቡት ጥያቄ መሠረት በማድረግ ከሚያዝያ 1 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም. ጀምሮ የበረሃ
አበል 2ዐ% እንዲከፈላቸው ተፈቅዷል፤
የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ጽ/ቤት ሃላፊ እና የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ስትራቴጂክ
ስራ አመራር ዳይሬክተር ሹመት በጉባዔው በመጽደቁ ሹመቱ በደብዳቤ ለሚመለከታቸው አካላት
እንዲደርስ ተደርጓል፤
ጉባዔው የዳኞችን ደሞዝ ስርዓት ለማሻሻል በጉባዔው አባላት የተከናወነ ጥናት (እንደተሻሻለ)
ተቀብሎ የዳኞችን ደሞዝ ያካተተ የጥቅማጥቅም ፓኬጅ ተዘጋጅቶ ለአስፈጻሚው አካል ተልኳል፡
የዳኞች አስተዳደር ጉባዔ ጽ/ቤት በሰጣቸው አገልግሎቶች 10 ዳኞች የስራ ልምድ ማስረጃ፣ የ 5
ዳኞች እና 8 ረዳት ዳኞች የሥራ መልቀቂያ ተሠጥቷል፣ 380 የተለያዩ ወጪ ደብዳቤዎች
ተልከዋል፣ 75 የተለያዩ ገቢ ደብዳቤዎች ለጽ/ቤቱ ቀርበዋል፣
የፍርድ ቤቶችን የበጀት ነፃነትና የአፈጻጸም ተጠያቂነት በማጠናከር የበጀት ዓመቱ ዕቅድ እና
የበጀት ፍላጎት ተዘጋጅቶ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተልኳል፣ የአፈጻጸም ሪፖርቶችም
በየመንፈቅ ዓመቱ ተዘጋጅተው ቀርበዋል፣
ከሕዝብ ተወካዮች ምክር የሚሰጡ አስተያየቶችን ወይም ግብረመልሶችን በግብዓትነት በመጠቀም
በዓመታዊ ዕቅዱም ሆነ በአፈጻጸም ሪፖርቶች ላይ ማስተካከያዎችን በማደርግ የዳኝነት ነጻነትና
ገለልተንነትን ማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል፣
የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተ በተዘጋጁ መመዘኛ ነጥቦች አኳያ በተገልጋዮች
የተሰጡ የምዘና ነጥቦችን የሚያሳይ ሪፖርት ተዘጋጅቶ ለበላይ አመራር ቀርቧል፣
2 የፕሮጀክቶች አፈጻጸም
1. የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ ጥናት ፕሮጀክት፣
ለውሳኔ ሰጪ(ዳኝነት) ሥራ ዘርፍ የተዘጋጀው የአገልግሎት አሰጣጥ ስታንዳርድ ተገምግሞና ዳብሮ በስራ
ላይ እንዲውል ለማድረግ በተያዘው ዕቅድ፡-
o ረቂቁ በበላይ አመራር ተገምግሞና ለፌዴራል ዳኞች እንዲሁም የሲቪል ሰርቪስ ሥራ ኃላፊዎች
ቀርቦ ውይይት ከተደረገበት በኋላ ጸድቆ በሥራ ላይ እንዲውል ተደርጓል፡፡
o የሲቪል ሰርቪስ ሥራ ክፍሎችን የአገልግሎት አሰጥጥ ስታንደርድ ለማዘጋጀት ኮሚቴ ተቋቁሞ
የመጀመሪያውን ረቂቅ ለበላይ አመራር ያቀረበ ሲሆን በተሰጡ አስተያየቶች መሰረት
ማስተካከያዎችን አደርጎ የመጨረሻ መልኩን የማስያዝ ተግባር በመከናወን ላይ ይገኛል፣
o የዳኝነት ዘርፉንና የሲቪል ሰርቪሱን ሥራ ክፍሎች አገልግሎት አሰጣጥ ስታንደርድ መነሻ
በማድረግ የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ ለሕዝብ ማሳወቅ የሚያስችል የዜጎች ቻርተር
የማዘጋጀቱ ሥራ የአገልግሎት አሰጣጥ ስታንደርዱን መጠናቀቅ በመጠበቅ ላይ ይገኛል፣
o የፌዴራል ፍ/ቤቶችን የሥራ ባህሪና የለውጥ መሳሪዎችን አተገባበር መነሻ በማድረግ ተቋማዊ
የፍትህ ሠራዊት ግንባታ ለማካሄድ የሚያስችል የትግበራ መመሪያ ተዘጋጅቶና የግንዛቤ
ማስጨበጫ ስልጠናዎች ተሰጥተው ተበትግበራ ላይ ይገኛል፣
2. የተቀናጀ የኢኮቴ ኘሮጀክት
የኢሊትጌሽን አገልግሎትን ለማስፋፋት ታቅዶ፡-
ሁሉንም የፌዴራል ፍ/ቤቶች በኔትወርክ በማገናኘት የመረጃ ልውውጥ ሥራን ቀልጣፋ
ለማድረግ የሚያስችል የፕሮጀክት ፕሮፖዛል ሰነድ ዝግጅት ተጠናቅቆ ውሳኔ እንዲሰጥበት ለበላይ
ሃላፊዎች ቢቀርብም ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ እስከ 100 ሚሊዮን ብር የሚፈጅ በመሆኑ
የሚያስፈልገውን በጀት በመጠባበቅ ላይ ይገኛል፣
የአይሲቲና ሴኩሪቲ ፖሊሲዎችን ለማውጣትና ለመተግበር ታቅዶ፡-
ክፍል ሶስት
የክትትልና ግምገማ ምዕራፍ
3.1 በአፈጻጸም ሂደት የተደረጉ ክትትልና ድጋፎች
በሁሉም ፍ/ቤቶች ወጥ የሆነ አተገባበር ባይኖርም በውሳኔ ሰጪ ዘርፍም ሆነ በሲቪል ሰርቪስ
ሥራ ክፍሎች የምዘና ሥርዓቱን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያግዙና በዕቅድ ዝግጅትም ሆነ
በአፈጻጸም ሂደት ተገቢውን አቅጣጫ ለመከተል የሚያግዙ ክትትሎች በማድረግ የለውጡን
ቀጣይነት የሚያጎለብቱ ድጋፎች ተደርገዋል፣
ለለውጥ አተገባበሮች እንቅፋት የሚፈጥሩ አሠራሮችና አደረጃጀቶችነ ተከታትሎ በመለየት
አስፈላጊ ማስተካከያዎች ተደርገዋል፣
በምዘና መመሪያው የተዘጋጁ ቅጾችን በመጠቀም በየደረጃው ከተዘጋጁ ዓመታዊ ዕቅዶች
የተመነዘሩና በዳኝነት ዘርፉ ወርሃዊ፣ በቪል ሰርቪስ ሥራ ክፍሎች ደግሞ ሳምንታዊ ዝርዝር
ተግባራትን የሚያሳዩ ዕቅዶችን አፈጻጸም የሚያሳዩ ሪፖርቶች ተዘጋጅተው የውስጥ እና የጋራ
ግምገማ እንዲከሄድባቸው ተደርጓል፣
በዚህም ዳኞችም ሆነ የሲቪል ሰርቪስ ኃላፊዎች፣ ባለሙያዎችና ሠራተኞች በሰብዓዊ መብት
የድርጊት መርሃግብር፣ በመልካም አስተዳደርና የሥነ ምግባር መርሆች ዙሪያ የአመለካከት
ለውጦችን ማዳበር የሚያስችሉ ተግባራትን ማከናወን ተገቢው ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ
መሆኑን መገንዘብ ተችሏል፣
በምዘና መመሪያው መሰረት የግምገማ ነጥቦችን አሰባስቦ በየመንፈቅ ዓመቱ የምዘና ውጤቶችን
መስጠት ባይቻልም የጠቅላይ ፍ/ቤት ችሎቶችና ዳኞች ዕልባት የሰጡባቸውን መዛግብት መጠን
እና ከድጋፍ ሰጪ ክፍሎች የቀረቡ የአፈጻጸም ሪፖርቶችን መነሻ በማድረግ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት
ዳኞችን፣ ችሎቶችንና ድጋፍ ሰጪ ዘርፎችን የአፈጻጸም ደረጃ ለመለየት ተሞክሯል፣
በዕቅድ ዝግጅት እና የትግበራ ምዕራፎች በየደረጃው የሚገኙ የተቋሙ አመራር አካለት፣ ዳኞች፣ የሲቪል
ሰርቪስ ሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ኃላፊነታቸውን ለመወጣት ያከናወኑዋቸውን ተግባራትና የተገኙትን
ውጤቶች በጋራ በመገምገም ወደ 2008 በጀት ዓመት ለመሻገር የሚረዱ ቅድመ ዝግጅቶችን ተደርገዋል፡፡
በዚህም በየፍ/ቤቶች በተናጥል እና ሶስቱም ፍ/ቤቶች በጋራ የበጀት ዓመቱን የፍ/ቤቶች አፈጻጸም
የገመገሙ ሲሆን በየደረጃው የተለዩ ጥንካሬና ድክመቶችን በማውጣት የጋራ መግባባት እንዲፈጠርበቸው
አድረገዋል፡፡
ግምገማው የተካሄደው የፌዴራል ፍ/ቤቶች የበላይ አመራር አካላት ካዘጋጁዋቸው የመወያያ ነጥቦች
በመነሳት ሲሆን የፍ/ቤቶች የበላይ አመራር አካላት መድረኮችን በባለቤትነት በመምራት የሁሉም
ችሎቶች ዳኞች እና ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች በንቃት እንዲሳተፉ ተደርጓል፡፡ በዚህም በየደረጃው የሚገኙ
ኃላፊዎች፣ ዳኞችና ድጋፍ ሰጪ ሥራ ክፍሎች ድክመቶቻቸውን አሻሽለው የቀጣዩን በጀት ዓመት
ውጤታማነት ለማሳደግ ተስማምተዋል፡፡ እነዚህን በግምገማ የተለዩ ጥንካሬዎች ይበልጥ አጎልብቶ
ክፍተቶችን በመሙላት የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጡን ቅልጥፍና፣ ጥራት፣ ተደራሽነት፣ ፍትሃዊነትና
ተዓማኒነት ለማጠናከር የሚያስችሉ ቀጣይ የአተገባበር አቅጣጫዎችንም ለይተዋል፡፡ በዚህ ግምገማ
በየምዕራፉና በየሥራ ደረጃው ከታዩ ጥንካሬና ድክመቶች መካከል ጎልተው የታዩት በሚከተለው ሁኔታ
እንዲቀርቡ ተደርገዋል፡፡
አሳታፊነትን ተግባራዊ ያደረገ የበጀት ዓመትን ዕቅድ ያለፈውን በጀት ዓመት አፈጻጸም ገምግሞና
የበጀት ዓመቱን የትኩረት አቅጣጫዎችን ለይቶ እንዲያዘጋጅ፣
የዳኝነት አገልግሎት አሰጣጥ ስታንደርድ ተዘጋጅቶና ከሚመለከታቸው አካላት በተገኙ ገንቢ
አስተያየቶች ዳብሮ ወደ ትግበራ እንዲገባ፣
በበጀት ዓመቱ ዕቅድ፣ በተቋሙ ተልዕኮ፣ ራዕይ፣ እሴቶች እና በአጠቃላይ በአፈጻጸም ምዘና
ሥርዓት ላይ ካለፉት ዓመታት በተሻለ ሁኔታ በርካታ የኦረንቴሽን መድረኮች ተዘጋጅተው ግንዛቤ
እንዲኖር፣
የተቋሙን ዓመታዊ ዕቅድ በየደረጃው አውርዶ ከተቋሙ ዕቅድ ጋር የተሳሰረ የችሎቶች እና
የሲቪል ሰርቪስ ሥራ ክፍሎች ዓመታዊ ዕቅድ እንዲዘጋጅ፣
ዳኞች ከችሎቶች እና ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች ከሥራ ክፍሎች ያወረዱዋቸውን መጋቢ ግቦች
መሰረት በማድረግ የየራሳቸውን ዕቅዶች ለማዘጋጀት የሚያስችሉ ድጋፎች እንዲሟሉ፣
ከዓመታዊ ዕቅድ የተመነዘሩ ወቅታዊ ዕቅዶች (ዳኞች ወርሃዊ ለሲቪል ሰርቪስ ሥራ ክፍሎች
ደግሞ ሳምንታዊ) እየተዘጋጁና የአፈጻጸም መረጃዎች እየተያዙ እንዲተገበሩ፣
ዕቅዱን ለመፈጸም የሚያስችል የሰው ኃይል፣ በጀት እና ሌሎች አቅርቦቸቶች እንዲሟሉ፣
የሰብዓዊ መብት ድርጊት መርሃግብር ድንጋጌዎች የተቋሙ ዕቅድ አካል ሆነው እንዲፈጸሙ
ለማድረግ የሚያስችል ሥርዓት እንዲተገበር፣
በየፍርድ ቤቶች ልዩነት ቢኖረውም በተወሰነ መልኩ በችሎቶችነ ሥራ ክፍሎች የተዘጋጁ
ዕቅዶችን አተገባበር ተከታትሎ በመገምገም የሥርዓቱ ትግበራ እንዲጠናከር፣
የፍ/ቤቶቹ ፕረዚደንቶችና ምክትል ፕረዚደንቶች መደበኛ የሆኑ ሳምንታዊ ስብሰባዎችን በማካሄድ
ተቋማዊ የለውጥ አተገባበሩች እንዲሻሻሉ፣
የዳኝነት አካሉ ከሌሎች የፍትህ አካላትና ባለድርሻዎች ጋር የሚያደረጋቸውን ግንኙነቶችና
ተከታታይ ውይይቶች የሚመሩበት ፕሮግራም ተቀርጾ ተግባራዊነታቸው እንዲሻሻል፣
የዳኞችንና የሠራተኞችን የአመለካከትና የአቅም ክፍተቶች የሚሞሉ በርካታ ስልጠናዎች
እንዲዘጋጁ፣
ተገቢው ጥረት መደረጉ የበጀት ዓመቱ የበላይ አመራር አካላት ጥንካሬዎች ተደርገው የተለዩ ነጥቦች
ናቸው፡፡
ክፍተቶች/ድክመቶች
የለውጥ መሳሪያዎችን በዕምነትና በቁርጠኝነት ተቀብሎ አርዕያ መሆን የሚያስችል የለውጥ
አመራር አለመኖር፣
በጊዜው ተገምግሞ የተስተካከለ ቢሆንም ኦሬንቴሽን በሚሰጥበት ወቅት ተናቦ ተገቢውን
አመራር አለመስጠትና የበጀት ዓመቱ ዕቅድ ወቅቱን ጠብቆ እንዲዘጋጅ አለማድረግ፣
የፍርድ ቤቶችን ተልዕኮ ለማሳካትና የአመራሩን ድጋፍ የሚሹ ችግሮችን ለመፍታት
በስትራቴጂያዊ ጉዳዮች ላይ አትኩሮ የቅርብ ክትተልና ድጋፍ ከማድረግ ይልቅ መደበኛ በሆኑ
የዕለት ተዕለት ሥራዎች በመጠመድ የዕቅድ አፈጻጸም ክትትልና ድጋፍ ሥራዎችን በጥብቅ
ዲስፕሊን አለመመራት፣
የተቋሙን ዕቅድ ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት አቅርቦ በማስገምገም ገንቢ አስተያየቶችን
አለማሰባሰብ፣
በመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኞችና ሰራተኞች ዕቅድ እንዲያዘጋጁ ቢደረግም አመራሩ
አግባብነቱን አረጋግጦ አለመፈረም፣
ከፍተኛ ፍርድ ቤት የተወሰኑ ዳኞች አዘጋጅተው ያቀረቦለትን ዕቅድ ፈርሞ አለመመለስና
ያላዘጋጁትን ተከታትሎ ተገቢውን እርምጃ አለመውሰድ፣
በከፍተኛና መጀመሪያ ዳረጃ ፍርድ ቤት የዳኞች ምደባ ላይ አልፎ አልፎ ግልጽነት አለመኖሩ፣
በተቋም ደረጃ በዳኝነት ዘረፉና በድጋፍ ሰጪ ሥራ ክፍሎች መካከል የጋራና ተቀራራቢ
አመለካከትና ግንዛቤ እንዲኖር የሚያደረግ ጥረት አለመዳበር፣
በተለያዩ ምክንያቶች በፍርድ ቤቶች የሚታየውን የሰው ኃይል ፍልሰት ለመግታትም ሆነ ብቃት
ያላቸውን ባለሙያዎች ለመሳብ የሚደረጉ ጥረቶች የሚፈለገውን ውጤት አለማምጣት፣
ከኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር ለመውጣትና የሙስና ምንጮችን ለይቶና የመታገል
ውስንነት መኖር፣
የምዘና ሥርዓቱን ውጤታማነት የሚያጎለብቱ የማበረታቻ ሥርዓቶችን ዘርግቶ አለመተግበር፣
አመራሩ በበጀት ዓመቱ የታዩበት ድክመቶች መሆናቸው ተገልጾ ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡
ክፍተቶች/ድክመቶች
በርካታ ችሎቶችና ዳኞች በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ ዕቅዳቸውን አዘጋጅተው ያለማቅረባቸው፣
አንዳንድ ዳኞች በኦሬንቴሽን ወቅት ባለመገኘትና ችግር የማይፈጥሩ ነጥቦችን በማንሳት ለውጡን
በቁርጠኝነት ተቀብሎ ለማቀድና ለሌሎች ዳኞችም ሆነ ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞች አርዓያ መሆን
አለመቻላቸው፣
የዳኝነት አካሉ በሀገሪቱ አጠቃላይ ኢኮኖሚና ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ውስጥ የማይተካ
ሚና ያለው መሆኑን በአግባቡ አለመረዳት፣
ለተገልጋዬች የሚገባውን ክብር ሰጥቶ አለማስተናገድ፣ የህዝብ አገልጋይነት ስሜት አለመዳበር፣
የመልካም ሥነ ምግባር እና የመልካም አስተዳደር መርሆዎችን በአግባቡ ያለመፈጸም፣
ከነበረው አሰራር ወጣ ያሉ አዳዲስ ለውጦችን ለመቀበል አለመፍጠን ወይም ከልማዳዊ አሰራር
በቀላሉ አመላቀቅ ፣
ችግሮች የታዩባቸው መሆኑ ተገልጾ ማስተካከያዎች ማድረግ የሚያስችሉ አቅጣጫዎች ተይዘዋል፡፡
ክፍተቶች/ድክመቶች
በርካታ የቡድን መሪዎችና ሠራተኞች ዕቅዳቸውን በተቀመጠው ጊዜ አዘጋጅተው
አለማቅረባቸው፣
የለውጥ አመራርንና አሰራርን በቁርጠኝነት ያለመቀበልና የለውጡን ቀጣይነት በጥርጣሪ
የመመልከት ዝንባሌ በማሳየት ለሌሎች ጥሩ ምሳሌ አለመሆናቸው፣
3.4.1 ችግሮች
በሁሉም ፍ/ቤቶች የሚታየውን ከፍተኛ የሠራተኛ ፍልሰት ለመከላከልም ሆነ ባለሙያዎችን
ከውጭ ለመሳብ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ ባለመፈጠሩ የሰው ኃይል እጥረት ችግሮችን መፍታት
አለመቻሉ፣
ተደጋጋሚ የመብራት እና የኔትወርክ መቆራረጥ በመኖሩ በችሎቶችም ሆነ በድጋፍ ሰጪ
ክፍሎች አሠራሮች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ መፈጠሩና በኢኮቴ መሳሪያዎች ላይ ጉዳት እያደረሰ
መሆኑ፣
በድሬዳዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሚገኘው የቪዲዬ ኮንፈረንስ ማዕከል አገልግሎት በኔትወርክ ችግር
ምክንያት መስራት አለመቻሉ፣
የማስችያ፣ የተገልጋይ ማስተናገጃ፣ የሰነድ ማስቀመጫ በአጠቃላይ በፍ/ቤቶች ውስጥ ተገቢውን
አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችልና የሥራ ፍሰትን የተከተለ በቂ የቢሮ አደረጃት አለመኖሩ፤
ከፍርድ አፈፃፀም ጋር በተያያዘ የመሬት አስተዳደር ለሚቀርብለት የአፈጻጸም ጥያቄ የተሟላ
መረጃ አለመስጠት /ማዘግየት/፣ ባለድርሻ አካላት የፍርድ ቤት ትዕዛዝን አክብረዉ ወቅታዊ ምላሽ
አለመስጠት፤ በፍድ አፈፃፀም ሂደት ፖሊስና የቀበሌ መስተዳድር ተገቢውን ዕገዛና ትብብር
አለማድረግ፣ አንዳንድ ባለጉዳዮች ፍ/ቤት ያልተነሳና ውሣኔ ያልተሰጠበትን ጉዳይ በማቅረብ
አፈፃፀሙ በጊዜው እንዳይከናወን ችግር መፍጠር፤ የአፈፃጸም ውሳኔ የተሰጠበትን ንብረት
የፍርድ ባለዕዳዎች ማሸሽ/በሌላ መለወጥ/፤ በፍርድ አፈፃፀም ጉዳዩ የሚመለከታቸዉ ባለመበትም
የቀጣዮን በጀት ዓመት አፈጻጸም የተሳካ ለማድረግ የፍ/ቤቶች የበላይ አመራር አካላት ትኩረት ሰጥተው
መፍትሄ ሊሰጡባቸው ይገባቸዋል ተብለው በአፈጻጸም ሪፖርቶች ከቀረቡ ጉዳዮች መካከል፡-
በችሎቶች እና በቢሮዎች እጥረት ምክንያት የሚታዩ ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ
የመፍትሔ እርምጃዎች እንዲወሰዱ ማድረግ፣
የሰው ኃይል ፍልሰቶችን ለመቀነስና የተሻለ አቅም ያላቸው ባለሙያዎችን ወደ ፍ/ቤቶች ለመሳብ
የሚያስችሉ አሰራሮችንና ጥቅማ ጥቅሞችን ማመቻቸት፣
በአጠቃላይ የአፈጻጸም ምዘና ሥርዓቱን ለመተግበር የሚያስችሉ ሁኔታዎችን በማመቻቸት
ጠንካራ አፈጻጸሞች ይበልጥ የሚጎለብቱበት፣ የአፈጻጸም ክፍተቶች የሚሞሉበትና የተጠያቂነት
ሥርዓት የሚተገበርበትን ሁኔታ መፍጠር፣
የሚሉት ቀዳሚውን ስፍራ የሚይዙት ናቸው፡፡
ማጠቃለያ