Professional Documents
Culture Documents
HOSAENA Ena TEMSALETU
HOSAENA Ena TEMSALETU
ቤተ ሳጌ የድሆች መንደር ናት፡- ጌታ የድሆች መንደር ወደደ፡፡እኛ ድሆቹን ባለ ፀጋ ሊያደርገን ስለኛ ብሎ ራሱን ድሃ ያደረገ አምላክ
ነውና፡፡ቤተ ሳጌ ለእየሩሳሌም በጣም ቅርብ ናት፡፡እኛም ለቤተ ክርስትያን ቅርብ መሆን
አለብን፡፡ እየሩ ሳሌም ቤተ ክርስትያን ናት እንቅረባት ፡፡እየሩ ሳሌም እመቤታችን ናት እንቅረባት ፡፡ጌታ ቤተሳጌ በደረሰ ጊዜ የተመሳቀለ
መንገድ ቁሞ ሁለቱን ደቀ
መዛሙርቱ ላከ *ሁሩ ሃገረ ቅድመክሙ* ወደ ፊታችሁ ላለው ሃገር ሂዱ ወደ መንደሪቱ ግቡ አላቸው፡፡ በተመሳቀለ ቦታ መቆሙ፡- ወደ
ፊት በመስቀል ላይ እሰቀላለሁ ሲል ነው፡፡
ሁለቱ ደቀ መዛሙርቱ ሲልካቸው በፊታችሁ ላለው ሃገር ሂዱ ያን ጊዜ አህያ ከውርንጭላዋ ጋር ታስራ ታገኛላችሁ ፈታችሁ አምጡልኝ
አላቸው፡፡
አህዮቹ የታሰሩት ሌባ ሰርቆ ነው ያሰራቸው፡፡ ወንበዴ ሰርቆ ነው ያሰራቸው አህዮቹ ለጌታ ውለታ ሰርተዋል፡፡ ጌታ ሲወለድ
አሙቀውታልና፡፡ ለጌታ ውለታ ልንመልስ ያልቻልነው እኛ ሰዎች ብቻ ነን፡፡
ወንበዴው አህዮቹን ሰርቆ በመንደር እንዳሰራቸው ዲያብሎስም ለሰው ልጅ በሃጥአት ሰንሰለት ከሲኦል መንደር አስራቸው ነበርና፡፡
ሃዋርያቱ ሲልካቸው ምን ታደርጋላችሁ የሚላችሁ ሰው ቢኖር ጌታቸው ይሻቸዋል በልዋቸው አላቸው፡፡ የፈጠራቸው እሱ ነውና፡፡
ለስላሳ ህግ የሰራህልን አንተ አባት ነህ ሲሉ ነው፡፡ለስላሳ ህግ የተባለው ወንጌል ነው ወንጌል ፍቅር ናት የሚረግማችሁ መርቁ
ትላለችና፡፡ልብስ የሰውነት ነውር
ይሸፍናል፡፡ ነውረ ሃጥአታችን የምትሸፍንልን አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡ እሱ ልብሳችን ነውና፡፡ ነውራችን የሚሸፍንልን እሱ ነውና፡፡ችግሩ
ግን ነውረ ሃጥአታችን የሚሸፍንልን ልብስ እርሱ መሆኑን አለማወቃችን ነው፡፡አብሮን
እንዳለ አለማስተዋላችን ነው፡፡ስለዚ እንደ ሃዋርያት ሃጥአታችንን አስቀድመህም የሸፈንክልን ዛሬም የምትሸፍንልን ወደፊትም
የምትሸፍንልን አምላክ አንተ ነህ ልንለው ይገባል፡፡ጌታችን በሁለቱ አህያዎች በጥበብ
ተቀመጠ፡- በሰው የማይቻል በእግዚአብሔር ዘንድ ግን የሚቻል መሆኑ ጥበበኛ አባት ሁሉን የሚችል አባት መሆኑ የሚገልጽ ነው፡፡
አንድም ወንጌልን ኦሪትና ሃዲስን ሁለቱ አስታርቆ አስማምቶ አንዱን አንዱን እየመገበ የሚሄድ መሆኑ የሚያመለክት ነው፡፡
ጌታ ለምን በፈረስ ላይ አልተቀመጠም?
ትንቢትና ምሳሌውን ለመፈጸም ነው፡፡ ት.ዘካ9፡9 ” አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ፥ እጅግ ደስ ይበልሽ፤ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፥ እልል
በዪ፤ እነሆ፥ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያም፥ በአህያይቱ ግልገል በውርጫይቱ
በአህያ መቀመጡ
•ትህትናን ለማስተማር
•የሰላም ዘመን ነው ሲል
•ለፈለጉኝ ሁሉ የቅርብ አምላክ ነኝ ሲል በንጽህና በየዋህነት ለሚኖሩ ምእመናን አድሬባቸው እኖራለሁ ሲል፡፡
ውርጭላዋ
1.በህገ ወንጌል ትመሰላለች፡-ምክንያቱም ወንጌል ኢየሱስ ክርስቶስ የመሰረታት የሰራት አዲስዋ ህግ ናትና፡፡
2.በአህዛብ ትመሰላለች፡-ትንሽዋ አህያ ሸክም የለመደች አይደለችም እንዲሁም አህዛብም ህግህን የመቀበል የለመደ አይደሉም፡፡ ለህግህ
አዲስ ናቸውና፡፡
3.የእመቤታችን ምሳሌ ናት፡- የዓለም ሸክም አቅልላለችና በእመቤታችን ትመሰለላለች፡፡ እመቤታችን ድህነተ ምክንያታችን ጌታን
የተሸከመች ንጽህት እንከን የሌላት እናት ናትና፡፡
ሌሎችም ቅጠል አነጠፉለት፡ ሰስት አይነት ቅጠል አነጠፉለት ዝንባባ፤የቴመር ዛፍ፤የወይራ ዛፍ አነጠፉለት፡፡
ዘንባባ
4.ዝንባባ የደስታ መግለጫ ነው፡- አንተ ደስ የምታሰኝ ሃዘናችንም የምታርቅልን አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡
6.ዝንባባ እሳት አይበላውም ለብልቦ ይተወዋል እንጂ፡፡ ጌታም አንተ ባህሪህን የማይመረመር ነው ሲሉ ነው፡፡
1.ጌታ ለአዳም የሰጠው ቃል ኪዳን ለማስታወስ፡-ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድነሃለሁ ያለውን የተስፋ ቃል ለማስታወስ፡፡
4.ጌታ ለአዳም ከሰይጣን ግዛት ነጻ እንዳወጣው ሁሉ እኛም ከሰይጣን ግዛት ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ ከክፋት ከሃጥአት አውጣን ማረን
ለንስሃ ሞት አብቃን ከቤትህ አትለየን እንደ ቸርነትህ ይቅር በላን ስንል ከጌታ ደግመን
ስለዚ እንደ ታሰሩ አህዮች መፈታት አለብን፡፡ ሁላችን ታስረናልና ቤተ ክርስትያን በመሄድ እንድንፈታ እናድርግ፡፡ የታሰሩት ሁሉ በካህናት
አባቶቻችን አማካኝነት
እዲፈቱ ልናድርግ ይገባናል፡፡ ለምን ቢባል አምላካችን ይፈልገናል አባታችን አምላካችን ንጉሳችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይፈልገናል፡፡ ጌታ
ጸጋውን አብዝቶ ለዘላለሙ ከቤቱ አይለየን የነጻነት አባት ካለን ሱስና ልማድ ሁሉ ነጻ አድርጎ