Professional Documents
Culture Documents
የአሰሪና ሰራተኛ መተዳደሪያ ደንብ
የአሰሪና ሰራተኛ መተዳደሪያ ደንብ
መግለጫ
አርዕስት ገጽ
የሠራተኛ ግዴታዎች
------------------------------------------------------------------------------------3
የድርጅቱ ግዴታዎች
--------------------------------------------------------------------------------------4
የሠራተኛ አቀጣጠር
---------------------------------------------------------------------------------------5
የሙከራ ጊዜ
------------------------------------------------------------------------------------------------5
የስራው ውል ይዘት
---------------------------------------------------------------------------------------5
የሥራ ሰዓት
-----------------------------------------------------------------------------------------------7
የትርፍ ሰዓት ሥራ
---------------------------------------------------------------------------------------8
ፍቃድ
------------------------------------------------------------------------------------------------------10
የደሞዝ ጭማሪ
-------------------------------------------------------------------------------------------14
የደረጃ እድገት
--------------------------------------------------------------------------------------------16
የዲስፕሊን ስነ-ስርአት------------------------------------------------------------------------------------
17
የስራ ላይ አደጋ/ጉዳት
-----------------------------------------------------------------------------------27
ሌሎች አገልግሎቶች
-------------------------------------------------------------------------------------28
ስምምነት
-------------------------------------------------------------------------------------------------29
1. ሠራተኛው የማንኛውም የሥራ ውጤት ምንጭ መሠረት በመሆኑ ለጉልበቱ ተመጣጣኝ ክፍያ
አግኝቶ የሥራ መብቱ ተከብሮለት የኑሮ ደረጃው እንዲሻሻል የውድድር አቅሙን በማጠናከር
ትርፋማ ሆኖ ለቆየት ሠራተኛው የመሥራት ፍላጎቱንና ችሎታውን አዳብሮ ሙሉ ጉልበቱንና
እውቀቱን በመጠቀም የተሰጠውን የሥራ ሀላፊነት በቅን ልቦና እና በቅልጥፍና እንዲያከናውን
ለማድረግ፡፡
2. በድርጅቱ ሠራተኞችና መካከል ያለውን ግንኙነት ጤናማ በማድረግ የድርጅቱን ራዕይ፣ተልዕኮና
ዓላማ በማሳካትና እንዲሁም የሠራተኛውን ሥራ ዋስትና በማረጋገጥ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን
ማድረግ፣ለሰራተኞች መብትና ግዴታ እውቅና ሰጥቶ አብሮ መስራት፡፡
3. ሠራተኞችም ሆኑ የድርጅቱ የሥራ ግዴታቸውን አክብረውና ተግባራቸውን ተረድተው
በመግባባትና በመተባበር ለአንድ ዓላማ እንዲሰሩ ለማስቻልና ግንኙነታቸውን በትክክል
እንዲመሩ ለማድረግ፡፡
4. የአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 377/96 እና ማሻሻያዎቹን መሰረታዊ ጽንሰ ሐሳብና መርህን
እንዲሁም የድርጅቱን የአመራር ወይንም አሠሪነቱን የማይገታ፣የሰራተኛውን ደህንነትና ጤንነት
ሊንከባከብ፣ሰብአዊ ክብሩን ሊጠብቅ፣ተስማሚ የሥራ ሁኔታዎችን ሊፈጥር የሚችል የጋራ
መተዳደሪያ ደንብ በማስፈለጉ፡፡
የሠራተኛው ግዴታዎች
1. ሠራተኛው የማናቸውም የሥራ ውጤት ምንጭና መሰረት ስለሆነ የድርጅቱን የሥራ እንቅስቃሴ
እንዲፋጠንና ከፍተኛ የሥራ ውጤት እንዲያገኝ ምርትን ለማሳደግ የጉልበትም ሆነ የአእምሮ እርዳታ
የመስጠት ግዴታ አለበት፡፡ እንዲሁም ለተመደበበት ሥራ መላ ችሎታውንና ሀይሉን ያበረክታል፡፡
2. ሠራተኛው የሥራ ውል ለማከናወን የሚገለገልባቸውን የደንብ ልብስ ወይም የሥራ ልብስ በሥራ ላይ
የመልበስ ግዴታ አለበት፤እንዲሁም ማናቸውንም መሣሪያ ወይም ዕቃ በጥሩ ሁኔታ መጠበቅና መያዝ
አለበት፡፡
3. የራሱንና የሥራ ባልደረቦችን ሕይወት እንዲሁም የድርጅቱን ንብረት ሊጎዱ ከሚችሉ አደጋዎችና
አስከፊ ከሆኑ ተግባራት የመጠበቅ ግዴታ አለበት፡፡
4. ያለፍቃድ ወይም ያለበቂ ምክንያት ከሥራ አይቀርም፡፡ የሥራ ሰዓትንም በሚገባ ያከብራል፡፡
5. በድርጅቱ በሥራ ጎደኛውና በእንግዳ ሰው ላይ ጉዳት የሚያስከትል ድንገተኛ አጋጣሚ ሲደርስ
በማንኛውም ጊዜ ዕርዳታውን ያበረክታል፡፡
6. የሥራው ሁኔታ በቡድን የመሥራት ባህልና የቡድን ሃላፊነት ስሜትን ለማጠናከር ሥራው ልዩ የሙያ
ሰልጠና /እውቀት/ የማይጠይቅ እስከሆነ ድረስ በድርጅቱ እምነት ሰራተኛው አቅም ችሎታውና ጊዜው
የሚፈቅድለት መሆኑ ሲታመንበት እንዲሁም ሰራተኛው ሥራውን ለማከናወን ይችላል ተብሎ
ከታመነበት በተመሳሳይ ሥራ ተጨማሪ ሥራ ደርቦ ወይም ተክቶ እንዲሰራ ማድረግ ይችላል፡፡
7. ሠራተኛው የድርጅቱን ንብረት የሆነውን ማንኛውንም የሥራ መሣሪያና ገንዘብ ለግል ጥቅም ወይም
ለ 3 ኛ ወገን ማዋል የለበትም፡፡
የድርጅቱ ግዴታዎች
አንቀጽ 1
የሠራተኛ አቀጣጠር
የሙከራ ጊዜ
የሥራ ውል ይዘት
አንቀጽ 3
የሥራ ሰዓት
1. የማንኛውም ሠራተኛ መደበኛ የሥራ ሰዓት በቀን ከ 8 ሰዓት ወይም በሳምንት ከ 48 ሰዓት
መብለጥ የለበትም፡፡ የሰዓቱ አቆጣጠር ሠራተኛው ሥራውን እንዲጀምር ከተወሰነበት ጊዜ
አንስቶ ይሆናል፡፡ ሆኖም ሽፍት የማዘጋጅቱ ሀላፊነት የድርጅቱ ነው፡፡
2. አንድ ሠራተኛ ከአንድ የሥራ መደብ ወደ ሌላ ሥራ መድብ ሲዛወር አዲስ የተዛወረበት
የሥራ መደብ ላይ ተፈፃሚ በሆነው የሥራ ሰዓት ማለት ነው፡፡
3. በእሁድ እና ከህዝብ በአላት ቀን በስተቀር ዘወትር ከጠዋት 2፡00 ሰአት እስከ ቀኑ 6፡00
ሰአት ከሰአት በኋላ ከ 7 ፡00 ሰአት እስከ ቀኑ 11፡00 ሰአት ያለውን የስራ ሰአት
ማለት ነው ፡፡
የሳምንቱ የእረፍት ቀን
አንቀጽ 4
የትርፍ ሰዓት ሥራ
1. ጠቅላላ
1.1 አንድ ሰራተኛ መደበኛ የስራ ሰአቱና በትርፍ የሚሰራው የስራ ሰአት ተደምሮ በሃያ አራት ሰአቶች
ውስጥ አስራ ሁለት ሰአቶች በላይ እንዲሰራ አይገደድም ፡፡
1.2 በአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጽ 67(2) ስር የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ አንድ ሰራተኛ
ካልተስማማ ወይም ፈቃደኛ ካልሆነ በስተቀር በእረፍት ቀን ከስምምነት ሰአቶች በላይ የትርፍ
ሰአት ስራ እንዲሰራ አይገደድም፡፡
1.3 የትርፍ ሰአት ክፍያ ከደመወዝጋር ይከፈላል፡፡
1.4 በድርጅቱ በተወከለ ሰው በጽሁፍ ያልታዘዘ የትርፍ ሰአት ክፍያ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
ሆኖም ሁኔታው አስቸኳይ ከሆነና እስኪፈቀድ መጠበቅ የማይቻል በሚሆንበት ጊዜ አስቀድሞ
ባይፈቀድም የትርፍ ሰአት ስራ ክፍያ ይኖረዋል ፡፡
1.5 አንድ ትርፍ ሰአት የሚቆጠረው እጅግ ቢያንስ ሩብ ሰአት (15 ደቂቃ) ነው፡፡
3.1 ከጠዋቱ 12 ሰአት እስከ ምሽት 4፡00 ሰአት ባለው ጊዜ የተሰራው ትርፍ
ሰአት ስራ የቀን ትርፍ ሰአት ስራ ይባላል፡፤
3.2 ከምሽቱ 4፡00 ሰአት እስከ ንጋቱ 12፡00 ሰአት ባለው ጊዜ የተሰራ የትርፍ
ሰአት ስራ የማታ ትርፍ ሰአት ይባላል
3.3 በህዝብ በአላት እና የሳምንት የእረፍት ቀን የሚሰራ የትርፍ ሰአት ስራ
የበአል የትርፍ ሰአት ይባላል፡፤
አንቀጽ 5
ፈቃድ
1.1 አንድ አመት ያገለገለ አዲስ ሰራተኛ የፈቃድ መነሻ 14 የስራ ቀናት የዐመት ፈቃድ
ይሰጠዋል፡፡ አንድ ዐመት በላይ ያገለገለ ሰራተኛ ለእንዳንዱ ተጨማሪ ያገለገለበት አመት
አንድ የስራ ቀን ተጨማሪ ፈቃድ ይሰጠዋል፡፡ ከአንድ አመት በታች የገለገለ ሰራተኛ
እንዳገለገለበት ጊዜ መጠን ታስቦ ተመጣጣኝ ፈቃድ ይሰጠዋል፡፡
1.2 የሰራተኛው ፈቃድ አወሳሰድ ድርጅቱ በሚያወጣው የፈቃድ አወሳሰድ ፕሮግራም መሰረት
እንዲሁም ስለ አሰሪ እና ሰራተኛ ጉዳይ በወጣው አዋጅ ቁጥር 377/1996 አንቀጽ 78/79
እና 80 መሰረት ይፈጸማል፡፡ ስለሆነም የአመት ፈቃድ የሚወሰደው ለዚሁ አላማ የተዘጋጀውን
ፎርም በመሙላት ለቅርብ አለቃው ቀርቦ ሲፈቀድ ብቻ ነው፡፡
1.3 በመሰረቱ የአመት ፈቃድ በጊዜው መውሰድ አለበት፡፡ በአዋጁ ላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች
ድርጅቱ በጊዜው ፈቃድ መስጠት ካልቻለና ጊዜው ከተላለፈ ወይም ፍቃዱ ከተቋረጠ
የተቋረጠው ፍቃድ በአዋጁ መሰረት መውሰድ ወይም ፈቃዱን ማስተላለፍ ይኖርበታል፡፡
1.4 እሁድ እና የህዝብ በዓላት ከእረፍት ፈቃድ ውስጥ አይቆጠሩም፡፡
1.5 ሠራተኘው በዓመት ፈቃድ ላይ እያለ ቢታመም፣የሚሰጠው የሕመም ፍቃደ ከዓመት ፈቃዱ
ላይ አይቀነስም፡፡ ያቋረጠውንም የዓመት እርፍት የሕመም ፍቃዱን እንደጨረሰ መቀጠል
ይችላል፡፡
1.6 አንዲት ሠራተኛ የዓመት ፍቃድ ላይ እያለች ብትወልድ፣የወሊድ ፈቃድዋ ከዓመት እረፍት ላይ
አይቀነስም፣የወሊድ ፈቃድዋን ካበቃች በኋላ የተቋረጠውን የዓመት ፈቃድዋን መቀጠል
ትችላለች፡፡
1.7 ከስራ የተሰናበተ ወይም በራሱ ፍቃድ ስራን እንዲለቅ የተፈቀደለት ሰራተኛ ወይም በጡረታ
የተገለለ እስከተሰናበተበት ቀን ድረስ ያልተጠቀመው የእረፍት ግዜ ምትክ በገንዘብ ተለውጦ
ይከፈለዋል፡፡
1.8 የዓመት እረፍት ቀን በገንዘብ ሲተመን እንደሚከተለው ይሰላል፡፡
2 ገ=አ x 12 x ደ ገ=ለቀሪ የዓመት እረፍት የሚከፈል ገንዘብ
3 365 አ=ቀሪ የዓመት እረፍት ቀን
4 ደ = ደመወዝ
2. የሕመም ፈቃድ
4.1 የሰራተኛዋ/ው የትዳር ጉዋደኛ፣ወላጅ፣ተወላጅ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ድረስ የሚቆጠር የሥጋ ወይም
ጋብቻ ዘመድ ሲሞትባት ከክፍያ ጋር የአምስት የስራ ቀናት ፍቃድ ይሰጠዋል፡፡
4.2 የሰራተኛው የባለቤቱ አያት፣የልጅ ልጅ፣የእንጀራ አባት ወይም የእንጀራ እናት የሞተ/ች እንደሆነ
ለሰራተኛው የሶስት (3) ተከታታይ ቀን የሀዘን ፍቃድ ይሰጠዋል፡፡
4.3 የሀዘን ፍቃድ ለማግኘት ከሚመለከተው ህጋዊ እካል የሀዘን ፍቃድ ለማግኘት ከሚመለከተው ህጋዊ
አካል መረጃ ይዞ መገኘት ያስፈልጋል፡፡
5. ልዩ ልዩ ፍቃድ
አንቀጽ 6
የሰራተኛው የስራ ውጤት ምዘና
እያንዳንዱ ቋሚ የድርጅቱ ሰራተኛ በአጠቃላይ ስላከናወናቸውና በተጨባጭ ባስመዘገባቸው ውጤቶች
ላይ ከግዜ ወደ ጊዜ በሚወጡት መመሪያዎች መሰረት ይመዘናል፡፡
ምዘና ወቅት
እያንዳንዱ ሰራተኛ በአመት ሁለት ግዜ የሥራ ውጤቱ መመዘን አለበት፡፡ የምዘና ወቅቶች በሁለት
የተከፈሉ ሲሆን ይኽውም እንደ ኢት.አቆጣጠር ከሀምሌ 1 እስከ ታህሳስ 30 ድረስ ሲሆን ሁለተኛው
ደግሞ እንደ ኢት.አቆጣጠር ከጥር 1 እስከ 30 ድረስ ይሆናል፡፡ ይህንንም የሚያከናውነው የሰራተኞቹ
የቅርብ አለቃ ይሆናል፡፡
አንቀፅ 7
የጭማሪ አሰጣጥ
ጭማሪ በሚሰጥበት በጀት አመት ቢያንስ ስድስት ወር እና ከዚያ በላይ ያገለገለ ሆኖ የስራ ውጤት ነጥቡ በስራ
ውጤት መመዘኛ ቅፅ ላይ ለመካከለኛ ነጥብ በተሰጠው ትርጉም መሰረት መካከለኛ ነጥብና በላይ ያገኘ ሰራተኛ
ለጭማሪ ብቁ ይሆናል፡፡
ከመካከለኛ ነጥብ በታች ያገኘ ሰራተኛ ጭማሪ አያገኝም፡፡ ጭማሪ በተፈቀደበት በጀት አመት ስድስት ውር ያገለገለ
ሰራተኛ ለአመቱ ከተፈቀደው ጭማሪ ግማሹን ያገኛል፡፡
ጭማሪ በተፈቀደበት በጀት አመት ከስድስት ወር በላይ ያገለገለ ሰራተኛ ከስድስት ወር በላይ ለሰራበት ግዜ ታስቦ
ተመጣጣኝ ጭማሪ ያገኛል፡፡
ድርጅቱ በበጀት አመት ያስቀመጣቸው ግቦች ሲያሳካ በሰራተኛው የስራ አፈፃፀም ምዘና ውጤት ላይ በመመርኮዝ
ሰራተኛውን ማበረታቻና የስራ ተነሳሽነትን መፍጠር አስፈላጊነትን ከግምት በማስገባት ለሰራተኞቹ የማበረታቻ
ጉርሻ (ቦነስ) ሊሰጥ ይችላል፡፡ ይህም የሚሆነው ድርጅቱን ምርታማነቱ ሲረጋገጥ ነው፡፡
አንቀፅ 8
የደረጃ እድገት
የደረጃ እድገት ማለት አንድ ሰራተኛ ከዝቅተኛ የስራ ደረጃ ወደ ከፍተኛ የስራ ደረጃ በመሸጋገሩ
ምክንያት የሚያገኛው የደረጃና የደሞዝ ለውጥ ነው፡፡ የኸውም በሁለት አይነት የፈፀማል ፡፡
ለደረጃ እድገት ለመወዳደር የሚያበቃ በስራ ውጤት መመዘኛ ቅፅ አጥጋቢ ውጤት እና ከዚያ በላይ
ያስመዘገበ ነው፡፡
የደረጃ እድገት የተሰጠው ሰራተኛ አዲሱ የሰራ መደብ ወይም ደረጃ ሚያስገኝው ደሞዝ እድገትም
ሆነ ሌሎች ጥቅሞች ሁሉ እድገቱ የፀደቀበት እለት ጀምሮ ያገኛል፡፡
አንቀፅ 9
1. የዲሲፒሊን ስነ - ስርአት
1.1 የዲሲፒሊን እርምጃ ማለት አንድ ሰራተኛ የድርጅቱን እና የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅን በመተላለፍ
ለሚያደርሰው ጥፋት የሚወሰድበት የቅጣት እርምጃ ማለት ነው፡፡
1.2 የቃል ማስጠንቀቂያ ማለት ለአንድ ሰራተኛ የቅርብ ሀላፊው ወይም የስራ ሀላፊው የጥፋቱን
አይነትና አድራጎት የጣሳቸውን ስምምነቶች ጥፋቱን እንዳይደግም በቃል የሚሰጠው ማስጠንቀቂያ
ነው፡፡
1.3 የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ማለት ለአንድ ሰራተኛ የስልጣን ውክልና የተሰጠው ሀላፊው ወይም
የስራ ሀላፊው የጥፋቱን አይነት እና አድራጎቱን የጠሳቸው ሰምምነቶች ጠቅሶ በፅሁፍ የሚሰጠው
ማስጠንቀቂያ ነው፡፡
1.4 የገንዘብ ቅጣት ማለት አንድ ሰራተኛ አሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ወይም የድርጅቱን መተዳደሪያ ደንብ
በመተላለፍ ለሚያደርሰው ጥፋት ከደሞዙ የሚቀነስ መቀጮ ነው፡፡
1.5 ከደረጃ ወይም ዝቅ ማድረጋ ማለት አንድ ሰራተኛ አሰሪና ሰራተኛ ወይም የድርጅቱ መተዳደሪያ
ደንብ በመተላለፍ የሚደርሰውን ጥፋት ካለበት የስራ ደረጃ እና ደሞዝ እንደ ጥፋት ክብደት ዝቅ
ማድረግ ማለት ነው፡፡
1.6 ከስራ እገዳ ማለት አንድ ሰራተኛ በድርጅቱ ስምምነት መሰረት ሁኔታው ተጣርቶ ውሳኔው
እስኪሰጥ ድረስ ከመደበኛ ስራው ላይ እንዲገለል የሚወሰድ እርምጃ ነው፡፡
1.7 ከስራ ማሰናበት ማለት አንድ ሰራተኛ አሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ወይም የድርጅቱን ስምምነት
በመተላለፍ ላደርሰው ጥፋት ድርጅቱ የስራ ውሉን በማቋረጥ ከስራ ሊያስወጣው ነው፡፡
2.5.1 እገዳው የሚፀናው ሰራተኛው የእገዳውን ደብዳቤ ፈርሞ ከተቀለበት ቀን ወይም የእገዳ
ውሳኔ በማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ በተለጠፈ ማግስት ጀምሮ ይሆናል፡፡ ሰራተኛ የታገደበትን
ምክንያት የሚገልጽ ጥፋቱን ዝርዝር የሚያስረዳ ሪፖርት ያገደው ሀላፊ በአራት ቀን ውስጥ
በቅርብ አለቃው ያስተላልፋል፡፡
2.7 በሴቶች ላይ ፆታዊ ትንኮሳ ፤ ፆታዊ ጥቃት እና የሴቶችን ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች
የሚጥስ ድርጊቶችን የፈፀሙ ሰራተኞች በማስረጃ ተረጋግጦ ሲገኝ ተመጣጣኝ የዲሲፒሊን
እርምጃ ይወስዳል፡፡
3. ድርጅቱ በሚከተሉት ጥፋቶች በመጀመሪያ ጥፋት ብቻ አጥፊውን ሰራተኛ ከስራ ማሰናበት ይችላል፡፡
3.4 ዶክመንቶችን ፤መሰረዝ ፤መደለዝ ወይም ትክክል ያልሆነ የምስክር ወረቀት ማቅረብ፤
3.5 ሆን ብሎ ዶክመንት እንዲሳሳት ማድረግ ፤ማስደረግ ወይም የተሳሳተ ምስክር ወረቀት እንዲቀርብ
መተባበር፤መረዳት፤
3.6 እምነት በማጉደል የድርጅቱን ገንዘብ ወይም ንብረት ለግል ጥቅም ወይም ለሌላ ሶስተኛ ወገን
ማዋል
3.7 በስራ ቦታ ከሰራተኛ ላይ ወይም ወደ ድርጅቱ ከመጣ ባለ ጉዳይ ላይ መስረቅ እንዲሁ ከመስሪያ ቤቱ
ስራ ጋር በተያዘ ከመስሪያ ቤቱ ውጭ ስርቆት መፈፀሙ ሲረጋገጥ፤
3.11 በስራ ገበታ ላይ ሌለን ሰራተኛ የሰአት መቆጣጠሪያ ካርድ ላይ ማተም ወይም መፈረም፤
3.13 እንደ ጥፋቱ ክብደት በስራው ቦታ አምባጓሮ ወይም ጠብ አጫሪነት ተጠያቂ መሆን፤
3.15 ህጋዊ ያልሆነ የስራ ማቆም አድማ አድርጎ መገኘት ወይም ሌሎች ስራ ማቆም አድማ እንዲያደርጉ
መቀስቀስ እና ማነሳሳት፤
3.16 የወሲብ ጥያቄን መሰረት በማድረግ የሰራተኞችን የስራ ግምገማ ውጤት፤ እድገት ፤ቅጥርና ዝውውር
--- ወዘተ መፈፀም
3.17 በህግ እና በተቋሙ ውስጥ የጦር መሳሪያ ይዞ መግባት ከተፈቀደላቸውና ከጥበቃ ሰራተኞች በስተቀር
የጦር መሳሪያ ይዞ ድርጅቱ መግባት ፤
3.18 ዘርን ወይም ብሄርን ፤ፆታን ፤ሀይማኖትን፤ቀለምን ወይም ሌሎች መሰል ልዩነቶችን መሰረት ያደረገ
አድልዎ መፈፀም
5. አንድ ሰራተኛ በቸልተኝነት የድርጅቱ ገንዘብ ወይም ንብረት ያጎደለ ዌም ያለአግባብ የተጠቀመ
የድርጅቱን ማሽኖች ሆን ብሎ ያበላሸ በድርጅቱ ላይ ኪሳራ የሚያስከትል ድርጊት የፈፀመ
ወይም በገንዘብ ሊተመን የሚችል ዶክመንት ላየ ጉዳት የደረሰ ወይም ያጠፋ በመተዳደሪያ ው
ደንብ ከተመለከተው የዲሲፕሊን እርምጃ በተጨማሪ ባደረሰው ጉዳት መጠን በድርጅቱ
በሚዘጋጀው ጉዳት ግምት መሰረት ገቢ ያደርጋል፡፡
6. የጥፋትአይነት
6.1 በሰንጠረዡ ላይ ከተዘረዘሩት የጥፋት አይነቶች ዉጪ የሚያጋጥሙ ሌሎች የጠፋት አይነቶች ቢኖሩ
የጥፋቶቹ ከባድነትና ቀላልነት እየታየ ከሰንጠረዡ ዉስጥ ከተዘረዘሩ የቅጣት አይነቶች ዉሰጥ
ተመጣጣኝ ወይም ተቀራራቢ ይሆናሉ ተብለዉ በሚገምቱ የቅጣት አይነቶች መጠቀም ይቻላል ፡፡
6.2 በሚከተለዉ የቅጣት ሰነጠረዥ የቅጣት ደረጃዉ የሚያመለክተዉ የጥፋቱ ክብደትና ቅለት ደረጃ እና
ለደረጃዉም የሚወሰነዉ ቅጣት እንጂ የጥፋት ቅደም ተከተል አይደለም፡፡
4 ኛ ደረጃ
የጥፋት አይነት 1 ኛደረጃ ጥፋት 2 ኛ ደረጃ ጥፋት 3 ኛ ደረጃ ጥፋት 5 ኛ ደረጃ ጥፋት
ጥፋት
1.3 የተመደበበትን ስራ ሆን ብሎ
አለመስራት የ 7 ቀን ደሞዝ የ 15 ቀን ደሞዝ
በቅርብ ሃላፊ የሚሰጡ ከጹሁፍ ከጹሁፍ ከስራ ማሰናበት
አግባብ ያላቸዉ ትዛዞችን ማስጠንቀቂያጋር ማስጠንቀቂያጋር
አለመፈፀም
3. ስለ መኪና መንዳት
የወጣዉን ደንብ መጣስ የ 4 ቀን ደሞዝ የ 15 ቀን ደሞዝ የ 9 ቀን ደሞዝ የ 15 ቀን ደሞዝ
ከጽሁፍ
3.1 የትራፊክ ደንብ መጣስ ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከጽሁፍ
ማስጠንቀቂያ
ከተፈቀደዉ ፍጥነት በላይ ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር
የድርጀቱን ተሸከርካሪ መንዳት
የ 15 ቀን ደሞዝ
3.3 ሰክሮ የድርጀቱን ተሸከርካሪ
ከጽሁፍ ከስራ ማስናበት
መንዳት
ማስጠንቀቂያ ጋር
የ 7 ቀን ደሞዝ የ 15 ቀን ደሞዝ
3.4 የድርጀቱን ተሸከርካሪ
ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከደረጃ ዝቅ ማድረግ ከስራ ማስናበት
ላልተፈቀደ ተግባር ማዋል
ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር
የ 15 ቀን ደሞዝ
3.6 ያለ ህጋዊ መንጃ ፍቃድ
ከጽሁፍ ከደረጃ ዝቅ ማድረግ ከስራ ማስናበት
የድርጀቱን ተሸከርካሪ መንዳት
ማስጠንቀቂያ ጋር
ደንበኙች ማጭበርበር
/ማታለል/ ከጽሁፍ
4.1 በግል ጥቅም በሎ ማስጠንቀቂያ ጋር
ትክክለኛዉን ሁኔታ ማፈለስ
የ 7 ቀን ደሞዝ
የ 7 ቀን ደሞዝ የ 15 ቀን ደሞዝ
4.2 በተሰጡት መብተች ከጽሁፍ
ከጽሁፍ ከጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ከደረጃ ዝቅ ማድረግ ከስራ ማስናበት
አላግባብ መጠቀም ማስጠንቀቂያ
ማስጠንቀቂያ ጋር ጋር
ጋር
የ 15 ቀን ደሞዝ
5. ስለ ስካር የ 4 ቀን ደሞዝ የ 7 ቀን ደሞዝ የ 9 ቀን ደሞዝ
ከጽሁፍ
5.1 ለስራ እንቅፋት በሚሆን ከጽሁፍ ከጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ከጽሁፍ ከስራ ማስናበት
ማስጠንቀቂያ
ሁኔታ መጥቶ ወደ ስራ መግባት ማስጠንቀቂያ ጋር ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር
ጋር
7. ለደንበኞች እና ወደ ድርጀቱ
ለሚመጡ ባለ ጉዳይዎች ተገቢ የ 15 ቀን ደሞዝ
ያልሆነ ጠባይ ማሳየት ከጽሁፍ ከስራ ማስናበት
መጉላላት መሳደብ ወይም ማስጠንቀቂያ ጋር
መዛት ድርጊቶችን የፈጸሙ
7.1 አነድ ሰራተኛ ከስራ ቀሪ ሲሆን የሚወሰንበት ቅጣት ለቀረበት ቀናት ከደሞዝ ላይ ተቀናሽ
የደረጋል፡፡
7.2 በተለያዩ ጊዝያት ዉስጥ በአንድ ዓመትጊዝ አንድ ሰራተኛ ለ 30(ሰላሳ)ቀናት ያለ በቂ ምክኒያት ከስራ
የመጀመርያዉን የጹሁፍ ማስጠንቀቂያ ከ 5-15 ባሉት ቀኖች ሁለተኛዉን የጹሑፍ መስጠንቀቂያ ደግሞ
7.3 በተከታይ 5 ቀናት ያለ በቂ ምክኒያተወ ከስራ የሚቀር ሰራተኛ ከስራ ቀሪ ሲሆን ይሰናበታል፡፡ድርጀቱ
7.4 ሰራተኛዉ የጹሁፍ ማስጠንቀቂያ ለመቀበል ፍቃደኛ ባይሆን ወይም ሠራተኛዉ ባለማግኘቱ ምክኒያት
አስፈርሞ ለመስጠት ባይችል ሰራተኛዉ በሚሰራበት አካባቢ ወይም ክፍል ዉስጥ ግልጽበሆነ ስፍራ ላይ
የተለጠፈዉም የቱፍ ማስጠንቀቂያ ቢያንስ 5 የስራ ቀናት በማስታወቂያ ሰልዳ ወይም በተለጠፈ ስፍራ ላይ
ይኮያል
አንቀጽ 10
የስራ ላይ አደጋ/ጉዳት
ድርጀቱ ሀላፊ ነዉ፡፡ ሆኖም አደጋዉ ወይም በሽታዉ የደረሰበት ሰራተኛዉ አስቦ ያደረገዉ ጥፋተ መሆኑን
ወይም ሰራተኛዉ በግልጽ በጹሁፍ የተሰጠዉን ትእዛዝ በማስተላለፍ ወይም አደጋዉ ከሰራተኛዉ ስራ ጋር
ሌሎች አገልግሎቶች
1. የምስክር ወረቀት
የምስክር ወረቀት ይሰጣል ሆኖም ሰራተኛዉ የስንብት የምስክር ወረቀት ማግኘት የሚችለዉ የንብረት
ማጣሪያ ቅጽ አስሞልቶ የድርጅቱ ንብረት እና ገንዘብ በሙሉ በማስረከብ ማስረጃ ካቀረበ በኃላ ነዉ፡፡
ሀ) የሚሰራዉ ስራ
ለ) ሙያዉ
ሐ) የሰራበት ዘመን
2. ልየ ልዩ ክፍያዎች
2.1 ሰራተኛዉ የስራዉ ዉሉን የሚያቋርጥበት ጊዜ የሰራበት ደሞዝ እና ልዩልዩ አበሎች እንዲሁም
2.2 አንድ ሰራተኛ የመስክ ስራ (ከአዲስ አበባ ከ 20 ኪ.ሜ) ሲታዘዝ በቀን 300 ብር ሂሳብ አበል
ይታሰብበታል፡፡
2.3 አንድ ሰራተኛ የስራ ዉሉን ማቋረጥ ከፈለገ ከአንድ ወር በፊት ማሳወቅ ይጠበቅበታል፡፡ ሆኖም የህ
2.4 አንድ ሰራተኛ ጥቅማ ጥቅም መጠየቅ ካለበት 6 ወር ካለፈ በይርጋ ይታገዳል፡፡
ስምምነት
1. 1.
2. 2.
3. 3.
4. 4.