Download as docx, pdf, or txt
Download as docx, pdf, or txt
You are on page 1of 28

መተዳደሪያ ደንብ

መግለጫ

አርዕስት ገጽ

የመተዳደሪያ ደንብ ዓላማ


---------------------------------------------------------------------------------2

የመተዳደሪያ ደንብ ተፈጻሚነት ወሰን ------------------------------------------------------------------3

የሠራተኛ ግዴታዎች
------------------------------------------------------------------------------------3

የድርጅቱ ግዴታዎች
--------------------------------------------------------------------------------------4

የሠራተኛ አቀጣጠር
---------------------------------------------------------------------------------------5

የሙከራ ጊዜ
------------------------------------------------------------------------------------------------5

የስራው ውል ይዘት
---------------------------------------------------------------------------------------5

ለተወሰነ ጊዜ ወይም ለተወሰነ ስራ የሚደረግ የስራ ውል -------------------------------------------6

የሥራ ሰዓት
-----------------------------------------------------------------------------------------------7

የትርፍ ሰዓት ሥራ
---------------------------------------------------------------------------------------8

ፍቃድ
------------------------------------------------------------------------------------------------------10

የሰራተኛው የስራ ውጤት ምዘና -----------------------------------------------------------------------13

የደሞዝ ጭማሪ
-------------------------------------------------------------------------------------------14

የደረጃ እድገት
--------------------------------------------------------------------------------------------16

የዲስፕሊን ስነ-ስርአት------------------------------------------------------------------------------------
17

አቡበከር ከረሜላ Page 1


መተዳደሪያ ደንብ

የስራ ላይ አደጋ/ጉዳት
-----------------------------------------------------------------------------------27

ሌሎች አገልግሎቶች
-------------------------------------------------------------------------------------28

ስምምነት
-------------------------------------------------------------------------------------------------29

የመተዳደሪያ ደንቡ አላማ

1. ሠራተኛው የማንኛውም የሥራ ውጤት ምንጭ መሠረት በመሆኑ ለጉልበቱ ተመጣጣኝ ክፍያ
አግኝቶ የሥራ መብቱ ተከብሮለት የኑሮ ደረጃው እንዲሻሻል የውድድር አቅሙን በማጠናከር
ትርፋማ ሆኖ ለቆየት ሠራተኛው የመሥራት ፍላጎቱንና ችሎታውን አዳብሮ ሙሉ ጉልበቱንና
እውቀቱን በመጠቀም የተሰጠውን የሥራ ሀላፊነት በቅን ልቦና እና በቅልጥፍና እንዲያከናውን
ለማድረግ፡፡
2. በድርጅቱ ሠራተኞችና መካከል ያለውን ግንኙነት ጤናማ በማድረግ የድርጅቱን ራዕይ፣ተልዕኮና
ዓላማ በማሳካትና እንዲሁም የሠራተኛውን ሥራ ዋስትና በማረጋገጥ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን
ማድረግ፣ለሰራተኞች መብትና ግዴታ እውቅና ሰጥቶ አብሮ መስራት፡፡
3. ሠራተኞችም ሆኑ የድርጅቱ የሥራ ግዴታቸውን አክብረውና ተግባራቸውን ተረድተው
በመግባባትና በመተባበር ለአንድ ዓላማ እንዲሰሩ ለማስቻልና ግንኙነታቸውን በትክክል
እንዲመሩ ለማድረግ፡፡
4. የአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 377/96 እና ማሻሻያዎቹን መሰረታዊ ጽንሰ ሐሳብና መርህን
እንዲሁም የድርጅቱን የአመራር ወይንም አሠሪነቱን የማይገታ፣የሰራተኛውን ደህንነትና ጤንነት
ሊንከባከብ፣ሰብአዊ ክብሩን ሊጠብቅ፣ተስማሚ የሥራ ሁኔታዎችን ሊፈጥር የሚችል የጋራ
መተዳደሪያ ደንብ በማስፈለጉ፡፡

አቡበከር ከረሜላ Page 2


መተዳደሪያ ደንብ

የመተዳደሪያ ደንብ ተፈፃሚነት ወሰን

1. ይህ የመተዳደሪያ ደንብ ተፈጻሚነት የሚኖረው ቋሚ ቅጥር ለሆኑ ሠራተኞች ነው፡፡


2. የሥራው ሁኔታ የማያቋርጥ ሆኖ ሲገኝ እንዲሁም አደጋ እንዳይደርስ ለመከላከልና ጊዜያዊ ችግርን
ለመወጣት ከሥራ ውሉ ውጪ ማሰራት ይቻላል፡፡
3. ይህ የመተዳደርያ ደንብ በማኔጅመንት ደረጃ ያለን የስራ መደብ አይመለከትም፡፡

የሠራተኛው ግዴታዎች

1. ሠራተኛው የማናቸውም የሥራ ውጤት ምንጭና መሰረት ስለሆነ የድርጅቱን የሥራ እንቅስቃሴ
እንዲፋጠንና ከፍተኛ የሥራ ውጤት እንዲያገኝ ምርትን ለማሳደግ የጉልበትም ሆነ የአእምሮ እርዳታ
የመስጠት ግዴታ አለበት፡፡ እንዲሁም ለተመደበበት ሥራ መላ ችሎታውንና ሀይሉን ያበረክታል፡፡
2. ሠራተኛው የሥራ ውል ለማከናወን የሚገለገልባቸውን የደንብ ልብስ ወይም የሥራ ልብስ በሥራ ላይ
የመልበስ ግዴታ አለበት፤እንዲሁም ማናቸውንም መሣሪያ ወይም ዕቃ በጥሩ ሁኔታ መጠበቅና መያዝ
አለበት፡፡
3. የራሱንና የሥራ ባልደረቦችን ሕይወት እንዲሁም የድርጅቱን ንብረት ሊጎዱ ከሚችሉ አደጋዎችና
አስከፊ ከሆኑ ተግባራት የመጠበቅ ግዴታ አለበት፡፡
4. ያለፍቃድ ወይም ያለበቂ ምክንያት ከሥራ አይቀርም፡፡ የሥራ ሰዓትንም በሚገባ ያከብራል፡፡
5. በድርጅቱ በሥራ ጎደኛውና በእንግዳ ሰው ላይ ጉዳት የሚያስከትል ድንገተኛ አጋጣሚ ሲደርስ
በማንኛውም ጊዜ ዕርዳታውን ያበረክታል፡፡
6. የሥራው ሁኔታ በቡድን የመሥራት ባህልና የቡድን ሃላፊነት ስሜትን ለማጠናከር ሥራው ልዩ የሙያ
ሰልጠና /እውቀት/ የማይጠይቅ እስከሆነ ድረስ በድርጅቱ እምነት ሰራተኛው አቅም ችሎታውና ጊዜው
የሚፈቅድለት መሆኑ ሲታመንበት እንዲሁም ሰራተኛው ሥራውን ለማከናወን ይችላል ተብሎ
ከታመነበት በተመሳሳይ ሥራ ተጨማሪ ሥራ ደርቦ ወይም ተክቶ እንዲሰራ ማድረግ ይችላል፡፡
7. ሠራተኛው የድርጅቱን ንብረት የሆነውን ማንኛውንም የሥራ መሣሪያና ገንዘብ ለግል ጥቅም ወይም
ለ 3 ኛ ወገን ማዋል የለበትም፡፡

አቡበከር ከረሜላ Page 3


መተዳደሪያ ደንብ

8. በስካር፣አእምሮን በሚያደነዝዝ ዕፅ ወይንም ሥራውን ለማከናወን በማያስችል ሁኔታ ላይ ሆኖ ሥራ ላይ


መገኘት የለበትም፡፡
9. ሠራተኛው የራሱንና የድርጅቱን ስም በመጠበቅ መልካም ጠባይ ይዞ መገኘት አለበት፡፡
10. ሠራተኛው ከሥራ ጋር በተያየዘ መንገድ ስለደረሰ ጉዳቴ ወይም ስለተፈጸመ ጥፋት የምስክርነት ቃል
እንዲሰጥ ወይም የሚያውቀውን እንዲያስረዳ ወይም በእጅ የሚገኘ መረጃ እንዲሰጥ አግባብ ባለው
ባለስልጣን ወይም የዲሲፕሊን ኮሚቴ ወይም በድርጅቱ በተሰየመ አጣሪ ሲጠየቅ የመተባበር ግዴታ አለበት፡፡
11. ሠራተኛው የድርጅቱን ንብረት ሲባክን ወይም ስርቆት ሲፈጽም ካየ ለሚመለከተው የድርጅቱ አካል ወይም
አግባብ ላለው ሕጋዊ ተቋም የማሳወቅ ግዴታ አለበት፡፡
12. የድርጅቱን ሚስጥር የመጠበቅ ግዴታ አለበት፡፡

የድርጅቱ ግዴታዎች

1. ስለ አሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ የወጡትን አዋጆች እና ወደ ፊት የሚወጡትን ደንቦች፤መመሪያዎች፤ስርአቶችና


ማሻሻያዎች በሚገባ ያከብራል፡፡
2. ጤናማ የሆነ የስራ ሁኔታዎችን ለማምጣት የሚያስችሉ እና ሰራተኛውም ድርጅቱ ያወጣቸውን ወይም
የሚያወጣቸውን ፖሊሲዎች ተግባራዊ ማድረግ እንዲችል እንዲሁም ሰራተኛው የሚጠበቅበትን ተግባር
በተገቢው መልኩ መወጣት የሚያስችለውን የስራ ጸባይ ባገናዘበ መልኩ ለስራ የሚያስፈልገውን የስራ
ዕቃዎች ያሟላል እንዲሁም ንብረቶች የሚጠበቁበትን ንብረቶች ተገቢ የሆነ ቦታ (ያዘጋጃል የስራ ላይ
ደህንነትንም ይጠብቃል፡፡
3. ለሠራተኛው ጤና ጥበቃና ለአደጋ መከላከያ የሚያገለግሉ መሣሪያዎችን እንዲሁም መጸዳጃ ዝግጅቶችን
የሥራው ሁኔታዎች በሚጠይቀው መሠረት ያዘጋጃል፡፡
4. ሠራተኞች በሙያቸውና በእውቀታቸው እንዲሻሻሉ ያደርጋል፡፡
5. ድርጅቱ ለሥራ አስፈላጊ የሆኑትን ዕቃዎችና መሣሪያዎች አሟልቶ ያቀርባል ያለቁ እቃዎችንም በየጊዜው
ይተካል፡፡
6. ድርጅቱ ማንኛውም የድርጅቱ ሠራተኛ የድርጅቱ ንብረት ሲባክን አይቶ ላሳወቀ ምንም ዓይነት የአስተዳደር
በደል ወይም ተጽዕኖ እንዳይደርስበት ዋስትና ይሰጣል፡፡
7. ድርጅቱ ከማናቸውም የሠራተኞውን ሕጋዊ መብቶችና ጥቅሞች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ
የሚጫን ወይም የሚገታ ተግባር አይፈጸምም፡፡
8. በማንኛም ምክንያት የሥራ ውሎ ለተቋረጠ ሠራተኛ ሥራውን ሙያውን የሰራበትን ዘመን ደመወዙን
ሰራተኛው ሲያገኛቸው የነበሩትን ሌሎች ክፍያዎችንና ከሥራ የለቀቀበትን ምክንያት ገልፆ ፎቶግራፍ ያለበት
የምስክር ወረቀት ሠራተኛው ክሊራንስ ከጨረሰበት ቀን ጀምሮ በ 15 ቀናት ውስጥ ድርጅቱ ይሰጣል፡፡

አንቀጽ 1

አቡበከር ከረሜላ Page 4


መተዳደሪያ ደንብ

የሠራተኛ አቀጣጠር

1. ላልተወሰነ ጊዜ ሰራተኛ ሲቀጠር መመሪያና ደንብ መሰረት የሚከናውነውን የስራ፣የደሞዝ


ልክ፣መብቶቹ፣ሃላፊነቱና ግዴታዎች ተዘርዝረው ይሰጡታል፡፡
2. አዲስ ሠራተኛ ሥራውን ከመጀመሩ በፊት ስለሚያከናውነው የሥራ አስፈላጊው ገለጻና
ማብራሪያ በማኔጅመንቱ ይደረግለታል፡፡

የሙከራ ጊዜ

1. የአንድ ሠራተኛ የሙከራ ጊዜ ከ 45 ተከታታይ ቀናት አይበልጥም፡፡


2. የሙከራ ጊዜውን የፈጸመ ሠራተኛ በውሉ መሠረት ሠራተኛ መሆኑን የሚያረጋግጥ የጽሁፍ
ማስረጃ ወዲያውኑ ይሰጠዋል፡፡ ሆኖም የጽሑፍ መረጋገጫ ሳይሰጠው ቢቀር በውሉ መሰረት
እንደተቀጠረ ይቆጠራል፡፡
3. ሰራተኛው በሙከራ ጊዜ ለሥራው ብቁ ካልሆነ ወይንም ሠራተኛው በድርጅቱ ውስጥ መስራት
ካልፈለገ በተባለው የሙከራ ጊዜ ውስጥ ድርጅቱ ወይንም ሠራተኛው በአዋጅ ቁጥር
377/1996 አንቀጽ 11 ተራ ቁጥር 5 እና 6 በተመለከተው መሠረት የሥራ ስንብት ክፍያ
ካሳ መክፈል ሳይገደድ የሥራ ውሉን ያለማስጠንቀቂያ ሊያቋርጥ ይችላል፡፡

የሥራ ውል ይዘት

1. ማንኛውም ሰው ደመወዝ እየተከፈለው፣በአሰሪ መሪነት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ


ለተወሰነ ወይም ላልተወሰነ ጊዜ ወይም የተወሰነ ሥራ ለአሰሪው ለመሥራት ቢስማማ በሁለት
መካከል የሥራ ውል ይመሰረታል፡፡
2. ማንኛውም የሥራ ውል ተዋዋይ ወገኖች በውሉ መሠረት የሚኖራቸውን መብትና ግዴታ
በማያጠራጥር አኳኋን በሚያውቁበት ሁኔታ በግልጽ መደረግ ይኖርበታል፡፡
3. ማንኛውም የሥራ ውል የሥራውን ዓይነትና ቦታ፣ለሥራ የሚከፈለውን ደመወዝ
መጠን፣የስሌቱን ዘዴ፣የአከፋፈሉን ሁኔታንና ጊዜ፣እና ውሉ ፀንቶ የሚቆይበትን ጊዜ መያዝ
ይኖርበታል፡፡
4. የሥራ ውል ሕግን ወይም ሞራልን ተቃራኒ ለሆኑ ሥራ አይደረግም፡፡
5. የሥራ ውል በሕግ፣ስምምነት ወይም በስራ ደንብ ለሠራተኛው ከተሰጡት ጥቅሞች ያነሰ
ጥቅም የሚሰጥ መሆን የለበትም፡፡
አንቀጽ 2
ለተወሰነ ጊዜ ወይም ለተወሰነ ሥራ የሚደረግ የሥራ ውል
ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ሁኔታዎች የሥራ ውል ለተወሰነ ጊዜ ወይም ለተወሰነ ሥራ
ሊደረግ ይችላል፤

አቡበከር ከረሜላ Page 5


መተዳደሪያ ደንብ

1. ሠራተኛው የተቀጠረበት የተወሰነ ሥራ እስከሚያልቅበት ጊዜ ድረስ


2. በፍቃዱ፣በሕመም ወይም በሌላ ማናቸውም ምክንያት ለጊዜው ቀሪ የሆነ ሠራተኛ
ለመተካት
3. የሥራ መብዛት በሚኖርበት ጊዜ ሥራን ለማቃለል፡፡
4. በሕይወት ላይ አደጋ ወይም በንብረት ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ለመከላከል አጣዳፊ
ሥራዎችን ለመሥራት በድርጅቱ ሥራ፣ዕቃ፣ሕንፃ ወይም ፋብሪካ ላይ የደረሰውን
ጉድለትና ብልሽት ለማድረስ
5. አልፎ አልፎ የሚሰራ ሥራ ማለትም ቋሚ ሥራ ያልሆነ ለመሥራት በሚያስፈልግበት
ጊዜ ብቻ የሚሠራ ሥራ ለመሥራት በሚያስፈልግበት ጊዜ ብቻ የሚሠራ ሥራ
ለመሥራት
6. ላልተወሰነ ጊዜ የሥራ ውል በተደረገበት የሥራ መደብ ላይ ሠራተኛ በድንገት
ለዘለቄታው በመለየቱ ለጊዜው ሥራ ለማሰራት
7. በድርጅት መዋቅር ጥናትና በጥናቱ አፈጻጸም መካከል ባለው ጊዜ የሚፈጠርን ክፍት
የሥራ መደብ ለማሟላት ለጊዜው የሚፈጸም ቅጥር

አንቀጽ 3

የሥራ ሰዓት

አቡበከር ከረሜላ Page 6


መተዳደሪያ ደንብ

1. የማንኛውም ሠራተኛ መደበኛ የሥራ ሰዓት በቀን ከ 8 ሰዓት ወይም በሳምንት ከ 48 ሰዓት
መብለጥ የለበትም፡፡ የሰዓቱ አቆጣጠር ሠራተኛው ሥራውን እንዲጀምር ከተወሰነበት ጊዜ
አንስቶ ይሆናል፡፡ ሆኖም ሽፍት የማዘጋጅቱ ሀላፊነት የድርጅቱ ነው፡፡
2. አንድ ሠራተኛ ከአንድ የሥራ መደብ ወደ ሌላ ሥራ መድብ ሲዛወር አዲስ የተዛወረበት
የሥራ መደብ ላይ ተፈፃሚ በሆነው የሥራ ሰዓት ማለት ነው፡፡
3. በእሁድ እና ከህዝብ በአላት ቀን በስተቀር ዘወትር ከጠዋት 2፡00 ሰአት እስከ ቀኑ 6፡00
ሰአት ከሰአት በኋላ ከ 7 ፡00 ሰአት እስከ ቀኑ 11፡00 ሰአት ያለውን የስራ ሰአት
ማለት ነው ፡፡

የሳምንቱ የእረፍት ቀን

ማንኛውም ሰራተኛ ቢያንስ በሳምንት 24/ ሃያ አራት/ ሰአት በተከታታይ ያርፋል፡፡

አንቀጽ 4
የትርፍ ሰዓት ሥራ
1. ጠቅላላ

1.1 አንድ ሰራተኛ መደበኛ የስራ ሰአቱና በትርፍ የሚሰራው የስራ ሰአት ተደምሮ በሃያ አራት ሰአቶች
ውስጥ አስራ ሁለት ሰአቶች በላይ እንዲሰራ አይገደድም ፡፡

አቡበከር ከረሜላ Page 7


መተዳደሪያ ደንብ

1.2 በአዋጅ ቁጥር 377/96 አንቀጽ 67(2) ስር የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ አንድ ሰራተኛ
ካልተስማማ ወይም ፈቃደኛ ካልሆነ በስተቀር በእረፍት ቀን ከስምምነት ሰአቶች በላይ የትርፍ
ሰአት ስራ እንዲሰራ አይገደድም፡፡
1.3 የትርፍ ሰአት ክፍያ ከደመወዝጋር ይከፈላል፡፡
1.4 በድርጅቱ በተወከለ ሰው በጽሁፍ ያልታዘዘ የትርፍ ሰአት ክፍያ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
ሆኖም ሁኔታው አስቸኳይ ከሆነና እስኪፈቀድ መጠበቅ የማይቻል በሚሆንበት ጊዜ አስቀድሞ
ባይፈቀድም የትርፍ ሰአት ስራ ክፍያ ይኖረዋል ፡፡
1.5 አንድ ትርፍ ሰአት የሚቆጠረው እጅግ ቢያንስ ሩብ ሰአት (15 ደቂቃ) ነው፡፡

የትርፍ ሰአት ስራ የሚሰራባቸው ሁኔታዎች ፡-

በአዋጅ ቁጥር 377/1999 አንቀጽ 67 ተራ ቁጥር 2 ያለው እንደተጠበቀ ሆኖ የትርፍ ሰአት ስራ


በሚከተሉት ምክንያቶች ሊሰራ ይችላል፡፤

2.1 የተፈጥሮ አደጋን እና እሳትን ለመቆጣጠር ወይም ለመከላከል፡፤


2.2 ሊቋረጡ በማይችሉ ስራዎችን ለመቀጠል እና እንዲሁም በአጋጣሚ የሚደርሱ ችግሮችን
ለመቅረፍ እና የተቋረጠ ስራን ለማስተካከል፡፤
2.3 በስራው ጸባይ ምክንያት በመደበኛ የስራ ሰአት ጊዜ ሊሰሩ የማችሉትን ስራዎች ለማከናወን
ወይም በመደበኛ የስራ ሰአት ጊዜ ሊሰሩ የማይችሉትን ስራዎች ለማከናወን ወይም በመደበኛ
ስራ ጊዜ ስራው ቢከናወን አገልግሎቱን የሚያቋርጥ ወይም የሚያቃውስ ሆኖ ሲገኝ፡፤
2.4 ሰራተኛው የጉዞ አበል እያገኘ ለሚጓዝበት ጊዜ የትርፍ ሰአት ክፍያ አይደረግም፡፤ሆኖም
ከመደበኛ የስራ ሰአት ውጪና በበአላት ቀን ለሚሰራው ትርፍ ሰአት ክፍያ ይደረግለታል፡፤
2.5 ሰራተኛው በህዝብ በአላት ቀን በስራ ላይ የሚገኙ ከሆነ የትርፍ ሰአት ክፍያ ይከፈላቸዋል፡፡

3 የትርፍ ሰአት ስራ አይነቶች ፡

3.1 ከጠዋቱ 12 ሰአት እስከ ምሽት 4፡00 ሰአት ባለው ጊዜ የተሰራው ትርፍ
ሰአት ስራ የቀን ትርፍ ሰአት ስራ ይባላል፡፤
3.2 ከምሽቱ 4፡00 ሰአት እስከ ንጋቱ 12፡00 ሰአት ባለው ጊዜ የተሰራ የትርፍ
ሰአት ስራ የማታ ትርፍ ሰአት ይባላል
3.3 በህዝብ በአላት እና የሳምንት የእረፍት ቀን የሚሰራ የትርፍ ሰአት ስራ
የበአል የትርፍ ሰአት ይባላል፡፤

አቡበከር ከረሜላ Page 8


መተዳደሪያ ደንብ

4 የትርፍ ሰአት ስራ ክፍያ ስሌት

4.1የቀን ትርፍ ሰአት

ደመወዝ x 1.25x የተሰራባቸው የትርፍ ሰአት 208

4.2የማታ ትርፍ ሰአት


ደመወዝ x 1.5x የተሰራባቸው የትርፍ ሰአት 208
4.3የበአል ትርፍ ሰአት

ደመወዝ x 2.5 x የተሰራባቸው የትርፍ ሰአት

አንቀጽ 5

ፈቃድ

1. የአመት እረፍት ፈቃድ

1.1 አንድ አመት ያገለገለ አዲስ ሰራተኛ የፈቃድ መነሻ 14 የስራ ቀናት የዐመት ፈቃድ
ይሰጠዋል፡፡ አንድ ዐመት በላይ ያገለገለ ሰራተኛ ለእንዳንዱ ተጨማሪ ያገለገለበት አመት
አንድ የስራ ቀን ተጨማሪ ፈቃድ ይሰጠዋል፡፡ ከአንድ አመት በታች የገለገለ ሰራተኛ
እንዳገለገለበት ጊዜ መጠን ታስቦ ተመጣጣኝ ፈቃድ ይሰጠዋል፡፡

አቡበከር ከረሜላ Page 9


መተዳደሪያ ደንብ

1.2 የሰራተኛው ፈቃድ አወሳሰድ ድርጅቱ በሚያወጣው የፈቃድ አወሳሰድ ፕሮግራም መሰረት
እንዲሁም ስለ አሰሪ እና ሰራተኛ ጉዳይ በወጣው አዋጅ ቁጥር 377/1996 አንቀጽ 78/79
እና 80 መሰረት ይፈጸማል፡፡ ስለሆነም የአመት ፈቃድ የሚወሰደው ለዚሁ አላማ የተዘጋጀውን
ፎርም በመሙላት ለቅርብ አለቃው ቀርቦ ሲፈቀድ ብቻ ነው፡፡
1.3 በመሰረቱ የአመት ፈቃድ በጊዜው መውሰድ አለበት፡፡ በአዋጁ ላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች
ድርጅቱ በጊዜው ፈቃድ መስጠት ካልቻለና ጊዜው ከተላለፈ ወይም ፍቃዱ ከተቋረጠ
የተቋረጠው ፍቃድ በአዋጁ መሰረት መውሰድ ወይም ፈቃዱን ማስተላለፍ ይኖርበታል፡፡
1.4 እሁድ እና የህዝብ በዓላት ከእረፍት ፈቃድ ውስጥ አይቆጠሩም፡፡
1.5 ሠራተኘው በዓመት ፈቃድ ላይ እያለ ቢታመም፣የሚሰጠው የሕመም ፍቃደ ከዓመት ፈቃዱ
ላይ አይቀነስም፡፡ ያቋረጠውንም የዓመት እርፍት የሕመም ፍቃዱን እንደጨረሰ መቀጠል
ይችላል፡፡
1.6 አንዲት ሠራተኛ የዓመት ፍቃድ ላይ እያለች ብትወልድ፣የወሊድ ፈቃድዋ ከዓመት እረፍት ላይ
አይቀነስም፣የወሊድ ፈቃድዋን ካበቃች በኋላ የተቋረጠውን የዓመት ፈቃድዋን መቀጠል
ትችላለች፡፡
1.7 ከስራ የተሰናበተ ወይም በራሱ ፍቃድ ስራን እንዲለቅ የተፈቀደለት ሰራተኛ ወይም በጡረታ
የተገለለ እስከተሰናበተበት ቀን ድረስ ያልተጠቀመው የእረፍት ግዜ ምትክ በገንዘብ ተለውጦ
ይከፈለዋል፡፡
1.8 የዓመት እረፍት ቀን በገንዘብ ሲተመን እንደሚከተለው ይሰላል፡፡
2 ገ=አ x 12 x ደ ገ=ለቀሪ የዓመት እረፍት የሚከፈል ገንዘብ
3 365 አ=ቀሪ የዓመት እረፍት ቀን
4 ደ = ደመወዝ

1.9 አንድ ሰራተኛ በፍቃድ ላይ እያለ ቀደም ብሎ በማይታወቅ ምክንያት ስራ ላይ እንዲገኝ


የሚያስገድድ ምክንያት ሲፈጠር ሰራተኛው ፍቃዱን አቆርጦ ስራው ላይ እንዲገኝ ድርጅቱ
ሊጠራው ይችላል፡፡

2. የሕመም ፈቃድ

የሙከራ ጊዜውን የጨረሰ ማንኛውም ሠራተኛ ሕመም ቢደርስበት የሕመም ፍቃድ


ይሰጠዋል፡፡ ሆኖም ሠራተኛው/ዋ ህጋዊ የሆነ የህመም ፍቃድ ማቅረብ አለበት አለባት፡፡
3. የወሊድ ፈቃድ

አቡበከር ከረሜላ Page 10


መተዳደሪያ ደንብ

3.1 ነፍሰጡር የሆነች ሠራተኛ ከእርግዝና ጋር የተያያዘ ምርመራ ለማድረግ ከደመወዝ ጋር


ፈቃድ ይሰጣታል፡፡ ሆኖም ሠራተኛዋ ከምርመራ በኋላ የሐኪም ማረጃ ማቅረብ
አለባት፡፡
3.2 ነፍሰጡር የሆነች ሰራተኛ ከመውለዶ በፊት ሀኪም እንድታርፍ ካዘዘ ከደሞዝ ጋር
እርፈት ይሰጣታል፡፡
3.3 ነፍሰጡር የሆነች ሰራተኛ እወልዳለሁ ብላ ከገመተችበት ቀን በፊት መውለጃዋ
ሲደርስ የ 30 ተከታታይ ቀናት የወሊድ ፈቃድ እንዲሁም ስትወልድ ከወለደችበት ቀን
ጀምሮ 60 ተከታታይ ቀናት የወሊድ ፍቃድ ከደመወዝ ጋር ይሰጣታል፡፡
3.4 ነፍሰጡር ሠራተኛ በእርግዝናዋ ጊዜ ጀምራ እስከወለደች ድረስ ከምሽቱ ሁለት ሰዓት
በኋላና የትርፍ ሰአት ስራ ለመስራት አትገደድም፡፡ ከወለደችና ሥራ ከጀመረች በኋላም
ለአንድ አመት ከምሽቱ ሁለት ሰዓት በኋላና የትርፍ ሰዓት ስራ ለመስራት
አትገደድም፡፡
3.5 ሽፍት የሚሰሩ የሚያጠቡ እናቶች /ሴቶች /ከወለዱ በኋላ ልጆቻቸውን ለማጥባት
እንዲመቻቸው ለአንድ ዓመት የማታ ሽፍት እንዲገቡ አይገደዱም፡፡
3.6 አንዲት ሴት ከወለደችበት ጊዜ ጀምሮ ህጻኑ ተጨማሪ ምግብ እስከሚጀምርበት ጊዜ
ለስድስት ወር ጡት ማጥባት እንዲችሉ በሥራ ሰዓት እንድትወጣ ይደረጋል፡፡
4. የሀዘን ፍቃድ

4.1 የሰራተኛዋ/ው የትዳር ጉዋደኛ፣ወላጅ፣ተወላጅ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ድረስ የሚቆጠር የሥጋ ወይም
ጋብቻ ዘመድ ሲሞትባት ከክፍያ ጋር የአምስት የስራ ቀናት ፍቃድ ይሰጠዋል፡፡
4.2 የሰራተኛው የባለቤቱ አያት፣የልጅ ልጅ፣የእንጀራ አባት ወይም የእንጀራ እናት የሞተ/ች እንደሆነ
ለሰራተኛው የሶስት (3) ተከታታይ ቀን የሀዘን ፍቃድ ይሰጠዋል፡፡
4.3 የሀዘን ፍቃድ ለማግኘት ከሚመለከተው ህጋዊ እካል የሀዘን ፍቃድ ለማግኘት ከሚመለከተው ህጋዊ
አካል መረጃ ይዞ መገኘት ያስፈልጋል፡፡
5. ልዩ ልዩ ፍቃድ

5.1 የትምህርትና የፈተና ፍቃድ


ሠራተኛው ብሔራ ፈተና ሲወስድ የፈተና ፈቃድ ይሰጠዋል፡፡
5.2 ሕጋዊ ግዳጅ ለመፈጸም የሚሰጥ ፈቃድ
ሠራተኛው ሕጋዊ ግዳጅ ለመፈጸም ከፍርድ ቤት ወይም ከፖሊስ ጣቢያ በሚያቀርበው መጥሪያ
መሠረት ፈቃድ ይሰጠዋል፡፡

አቡበከር ከረሜላ Page 11


መተዳደሪያ ደንብ

5.3 የጋብቻ ፍቃድ


ሠራተኛው በድርጅቱ ውስጥ ባለበት ዘመን ብቻ ደመወዝ የሚከፍልበት አምስት የሥራ ቀናት
የጋብቻ ፍቃድ ያገኛል፡፡
6. የፈረቃ ስራ

ማንኛውም ሰራተኛ በቀን በማታ ወይም በሌሊት የመስራት ግዴታ አለበት፡፡

አንቀጽ 6
የሰራተኛው የስራ ውጤት ምዘና
እያንዳንዱ ቋሚ የድርጅቱ ሰራተኛ በአጠቃላይ ስላከናወናቸውና በተጨባጭ ባስመዘገባቸው ውጤቶች
ላይ ከግዜ ወደ ጊዜ በሚወጡት መመሪያዎች መሰረት ይመዘናል፡፡
ምዘና ወቅት
እያንዳንዱ ሰራተኛ በአመት ሁለት ግዜ የሥራ ውጤቱ መመዘን አለበት፡፡ የምዘና ወቅቶች በሁለት
የተከፈሉ ሲሆን ይኽውም እንደ ኢት.አቆጣጠር ከሀምሌ 1 እስከ ታህሳስ 30 ድረስ ሲሆን ሁለተኛው
ደግሞ እንደ ኢት.አቆጣጠር ከጥር 1 እስከ 30 ድረስ ይሆናል፡፡ ይህንንም የሚያከናውነው የሰራተኞቹ
የቅርብ አለቃ ይሆናል፡፡

አቡበከር ከረሜላ Page 12


መተዳደሪያ ደንብ

አንቀፅ 7

የደሞዝ ጭማሪ ቦነስ

1. የደሞዝ ጭማሪ የሚሰጥበት መሰረተ ሀሳብ


ሰራተኛው ጉልበቱን እና እውቀቱን በስራ ላይ በማዋል ድርጅቱ በያዘው አመት የስራ እቅድና ግብ መሰረት
ተፈላጊውን የስራ ውጤት ካስገኘ በተገኘው የስራ ውጤታማነትና ለእቅዱ ግብ መምታት ላበረከተው
አስተዋፅኦ የደሞዝ ጭማሪ ይደረግለታል፡፡
1.1 ድርጅቱ በተጠናቀቀው የበጀት አመት ያቀደው የአገልግሎት ጥራት እድገት እና አመታዊ
1.2 ትርፍ ግብ ከተገኘው የደሞዝ ጭማሪው የኑሮ ውድነትን ፤ ያለፈው አመት የደሞዝ ጭማሪን በማየት
እና በሌሎች መነሻ ሀሳቦች መነሻ ሀሳቦች ላይ ተመስርቶ በየአመቱ የደሞዝ ችማሪ ይሰጣል፡፡
1.3 የደሞዝ ጭማሪ በድርጅቱ እስኬል መሰረት በእርከን ወይም ኮፍሸንት (አባዥ)ይሆናል፡፡
1.4 በስራ ውጤት መመዘኛ ቅፅ ላይ ለመካከለኛ ነጥብ በተሰጠው ትርጉዋሜ መሰርተ ከመካከለኛ በታጭ
የስራ ውጤት ነጥብ ያገኘ ሰራተኛ የደሞዝ ጭማሪ አይደረግለትም ፡፡
1.5 የደሞዘ ጭማ ተፈፃሚነት የሚኖረው ከበጀት አመት የመጀመሪያው ቀን አንስቶ ሲሆን ድርጅቱም
ያተረፈ መሆኑ ሲረጋገጥ ነው፡፡

የጭማሪ አሰጣጥ

አቡበከር ከረሜላ Page 13


መተዳደሪያ ደንብ

ጭማሪ በሚሰጥበት በጀት አመት ቢያንስ ስድስት ወር እና ከዚያ በላይ ያገለገለ ሆኖ የስራ ውጤት ነጥቡ በስራ
ውጤት መመዘኛ ቅፅ ላይ ለመካከለኛ ነጥብ በተሰጠው ትርጉም መሰረት መካከለኛ ነጥብና በላይ ያገኘ ሰራተኛ
ለጭማሪ ብቁ ይሆናል፡፡

ከመካከለኛ ነጥብ በታች ያገኘ ሰራተኛ ጭማሪ አያገኝም፡፡ ጭማሪ በተፈቀደበት በጀት አመት ስድስት ውር ያገለገለ
ሰራተኛ ለአመቱ ከተፈቀደው ጭማሪ ግማሹን ያገኛል፡፡

ጭማሪ በተፈቀደበት በጀት አመት ከስድስት ወር በላይ ያገለገለ ሰራተኛ ከስድስት ወር በላይ ለሰራበት ግዜ ታስቦ
ተመጣጣኝ ጭማሪ ያገኛል፡፡

ቦነስ የሚሰጥበት መሰረተ ሀሳብ

ድርጅቱ በበጀት አመት ያስቀመጣቸው ግቦች ሲያሳካ በሰራተኛው የስራ አፈፃፀም ምዘና ውጤት ላይ በመመርኮዝ
ሰራተኛውን ማበረታቻና የስራ ተነሳሽነትን መፍጠር አስፈላጊነትን ከግምት በማስገባት ለሰራተኞቹ የማበረታቻ
ጉርሻ (ቦነስ) ሊሰጥ ይችላል፡፡ ይህም የሚሆነው ድርጅቱን ምርታማነቱ ሲረጋገጥ ነው፡፡

አቡበከር ከረሜላ Page 14


መተዳደሪያ ደንብ

አንቀፅ 8

የደረጃ እድገት

የደረጃ እድገት ማለት አንድ ሰራተኛ ከዝቅተኛ የስራ ደረጃ ወደ ከፍተኛ የስራ ደረጃ በመሸጋገሩ
ምክንያት የሚያገኛው የደረጃና የደሞዝ ለውጥ ነው፡፡ የኸውም በሁለት አይነት የፈፀማል ፡፡

1. ግልፅ የሆነ ማስታወቂያ አውጥቶ በማወዳደር


2. በስራ አፈፃፀም ላይ ተመስርቶ በስራ ሀላፊው ሰራተኛው እንዲያድግ በሚቀርብ የውሳኔ
ሀሳብ (Recommendation)

ለደረጃ እድገት ለመወዳደር የሚያበቃ በስራ ውጤት መመዘኛ ቅፅ አጥጋቢ ውጤት እና ከዚያ በላይ
ያስመዘገበ ነው፡፡

የደረጃ እድገት የተሰጠው ሰራተኛ አዲሱ የሰራ መደብ ወይም ደረጃ ሚያስገኝው ደሞዝ እድገትም
ሆነ ሌሎች ጥቅሞች ሁሉ እድገቱ የፀደቀበት እለት ጀምሮ ያገኛል፡፡

አቡበከር ከረሜላ Page 15


መተዳደሪያ ደንብ

አንቀፅ 9

1. የዲሲፒሊን ስነ - ስርአት
1.1 የዲሲፒሊን እርምጃ ማለት አንድ ሰራተኛ የድርጅቱን እና የአሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ አዋጅን በመተላለፍ
ለሚያደርሰው ጥፋት የሚወሰድበት የቅጣት እርምጃ ማለት ነው፡፡

1.2 የቃል ማስጠንቀቂያ ማለት ለአንድ ሰራተኛ የቅርብ ሀላፊው ወይም የስራ ሀላፊው የጥፋቱን
አይነትና አድራጎት የጣሳቸውን ስምምነቶች ጥፋቱን እንዳይደግም በቃል የሚሰጠው ማስጠንቀቂያ
ነው፡፡

1.3 የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ ማለት ለአንድ ሰራተኛ የስልጣን ውክልና የተሰጠው ሀላፊው ወይም
የስራ ሀላፊው የጥፋቱን አይነት እና አድራጎቱን የጠሳቸው ሰምምነቶች ጠቅሶ በፅሁፍ የሚሰጠው
ማስጠንቀቂያ ነው፡፡
1.4 የገንዘብ ቅጣት ማለት አንድ ሰራተኛ አሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ወይም የድርጅቱን መተዳደሪያ ደንብ
በመተላለፍ ለሚያደርሰው ጥፋት ከደሞዙ የሚቀነስ መቀጮ ነው፡፡
1.5 ከደረጃ ወይም ዝቅ ማድረጋ ማለት አንድ ሰራተኛ አሰሪና ሰራተኛ ወይም የድርጅቱ መተዳደሪያ
ደንብ በመተላለፍ የሚደርሰውን ጥፋት ካለበት የስራ ደረጃ እና ደሞዝ እንደ ጥፋት ክብደት ዝቅ
ማድረግ ማለት ነው፡፡
1.6 ከስራ እገዳ ማለት አንድ ሰራተኛ በድርጅቱ ስምምነት መሰረት ሁኔታው ተጣርቶ ውሳኔው
እስኪሰጥ ድረስ ከመደበኛ ስራው ላይ እንዲገለል የሚወሰድ እርምጃ ነው፡፡
1.7 ከስራ ማሰናበት ማለት አንድ ሰራተኛ አሰሪና ሰራተኛ ጉዳይ ወይም የድርጅቱን ስምምነት
በመተላለፍ ላደርሰው ጥፋት ድርጅቱ የስራ ውሉን በማቋረጥ ከስራ ሊያስወጣው ነው፡፡

አቡበከር ከረሜላ Page 16


መተዳደሪያ ደንብ

2. ዲስፒሊን እርምጃ አወሳሰድ ሂደት


2.1 የዲሲፒሊን እርምጃ የሚወስደው ድርጅቱ ባለው የስልጣና ውክልና መሰረት ሲሆን ከደረጃ ዝቅ
የሚያስደርግ ወይም ከስራ የሚያስወጣ ጥፋት ሲፈጸም ከታየ በዋና ስራ አሲኪያጅ የመጨረሻ ውሳኔ
ይሰጣል፡፡
2.2 በአንድ ሰራተኛ ላይ የዲስፕሊን እርምጃ የሚወሰደው ሰራተኛውን ከጥፋት ለማረም፤ ስራው
እንዳይበደል ለመቆጣጠር እና ሌሎች ሰራተኞች ተመሳሳይ ጥፋት ከማድረግ እንዲቆጠቡ ነው፡፡ ስለዚህ
ሰራተኞች ወደ ጥፋት እንዳያመሩ ጥፋት ከመፈፀማቸው በፊት መምከርና ማስተማር ይገባል ይሁን እንጂ
በሰራተኛው ላይ የበቀል እርምጃ ለመውሰድ አይደለም፡፡
2.3 በማንኛውም ሰራተኛ ጥፋት በሚፈፀምበት ግዜ እርምጃ ከመውሰዱ በፊት አስፈላጊ መረጃ
መቅረብ አለበት፡፡እንዲሁም ቅጣት ከመውሰዱ በፊት የጥፋቱ ክብደት ፤ሰራተኛው ከጥፋት በፊት
የነበረው ፀባይ ፤ያለፈው መልካም አገልግሎቱና ለጥፋቱ መንስኤ የሆኑት ተጨባጭ ሁኔታዎች
በጥንቃቄ መመርመር አለባቸው፡፡
2.4 ከቃል ማስጠንቀቂያ በስተቀር ማንኛውም .ዲስፒሊን እርምጃ በሚወሰድበት ወቅት ሰራተኛው
ዝርዝር ሁኔታውን በፅሁፍ እንዲያውቀው ና በግልባጩ ላይ ፈርሞ እንዲቀበል ይደረጋል፡፡ ሰራተኛው
ፈርሞ ለመቀበል ፈቃደኛ ባለመሆኑ በመጥፋቱ ምክንያት አስፈርሞ ለመስጠት ባይቻል የቅጣቱ
ማስታወቂያ ሰራተኛው በሚሰራበት ክፍል ወይም አካባቢ ግልፅ በሆነ ቦታ ላይ ቢያንስ ለአስር
ተከታታይ ቀናት እንዲለጠፍ ይደረጋል፡፡
2.5 ከደረጃ ዝቅ የሚያስደርግ ወይም ከስራ የሚያስወጣ ከባድ ጥፋት በሚፈፅም ሰራተኛ ላይ ድርጅቱ
ስልጣን የሰጠው ሀላፊ ወዲያው እገዳ ውሳኔ ሊሰጥ ይችላል፡፡ሆኖም እንደዚህ አይነት እገዳ ሊፈፀም
የሚችለው የሰራተኛው በአስቸኳይ አለመታገድ በድርጅቱ ንብረት ላይ ጉዳት የሚያደርስ
አድራጎት፤የድርጅቱ ስራ እንዳይሰራ የሚያደርግ መሆኑ ሲረጋገጥ እና ምድብ ስራውን የሚመለከት
የበላይ ትእዛዝ አለመቀበል ወይም ተመሳሳይ ጥፋቶች ሲፈፀሙ ነው፡፡ የእገዳው ውሳኔ አፈጻጸም
እንደሚከተለው ይሆናል፡፡፡

አቡበከር ከረሜላ Page 17


መተዳደሪያ ደንብ

2.5.1 እገዳው የሚፀናው ሰራተኛው የእገዳውን ደብዳቤ ፈርሞ ከተቀለበት ቀን ወይም የእገዳ
ውሳኔ በማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ በተለጠፈ ማግስት ጀምሮ ይሆናል፡፡ ሰራተኛ የታገደበትን
ምክንያት የሚገልጽ ጥፋቱን ዝርዝር የሚያስረዳ ሪፖርት ያገደው ሀላፊ በአራት ቀን ውስጥ
በቅርብ አለቃው ያስተላልፋል፡፡

2.6 ከስራው የታገደ ሰራተኛ ጥፋተኛ አለመሆኑ ከተረጋገጠ በታገደበት ጊዜ ሙሉ ደሞዙ


ይከፈለዋል፡፡

2.7 በሴቶች ላይ ፆታዊ ትንኮሳ ፤ ፆታዊ ጥቃት እና የሴቶችን ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶች
የሚጥስ ድርጊቶችን የፈፀሙ ሰራተኞች በማስረጃ ተረጋግጦ ሲገኝ ተመጣጣኝ የዲሲፒሊን
እርምጃ ይወስዳል፡፡

3. ድርጅቱ በሚከተሉት ጥፋቶች በመጀመሪያ ጥፋት ብቻ አጥፊውን ሰራተኛ ከስራ ማሰናበት ይችላል፡፡

3.1 የድርጅቱን ሚስጥር ማባከን

3.2 ማሽኖችና የስራ መሳሪያዎችን ሆን ብሎ ማበላሽት ወይም እንዳይሰሩ ማድረግ ፤

3.3 በድጅቱ ንብረት ወይም ዶክመንቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሆን ብሎ ማድረስ፤

3.4 ዶክመንቶችን ፤መሰረዝ ፤መደለዝ ወይም ትክክል ያልሆነ የምስክር ወረቀት ማቅረብ፤

3.5 ሆን ብሎ ዶክመንት እንዲሳሳት ማድረግ ፤ማስደረግ ወይም የተሳሳተ ምስክር ወረቀት እንዲቀርብ
መተባበር፤መረዳት፤

3.6 እምነት በማጉደል የድርጅቱን ገንዘብ ወይም ንብረት ለግል ጥቅም ወይም ለሌላ ሶስተኛ ወገን
ማዋል

3.7 በስራ ቦታ ከሰራተኛ ላይ ወይም ወደ ድርጅቱ ከመጣ ባለ ጉዳይ ላይ መስረቅ እንዲሁ ከመስሪያ ቤቱ
ስራ ጋር በተያዘ ከመስሪያ ቤቱ ውጭ ስርቆት መፈፀሙ ሲረጋገጥ፤

3.8 ከስራ ጋር በተያዘ ሁኔታ ከደንበኞች ላይጉቦ/መደለያ/መቀበል/

3.9 በስራ ላይ ሆኖ አእምሮ የሚያስት /ጫት/መጠጥ/እና ሀሺሽ//ወስዶ መገኘት

3.10 ደንበኞችን ማታለል ወይም ማጭበርበር

3.11 በስራ ገበታ ላይ ሌለን ሰራተኛ የሰአት መቆጣጠሪያ ካርድ ላይ ማተም ወይም መፈረም፤

3.12 የድርጅቱን መታወቂያ ካርድ ሆነ ብሎ ለሌላ ሰው አሳልፎ መስጠት ፤

3.13 እንደ ጥፋቱ ክብደት በስራው ቦታ አምባጓሮ ወይም ጠብ አጫሪነት ተጠያቂ መሆን፤

3.14 በድርጅቱ ተሽከርካሪ የኮንትሮባንድ እቃ መጫን እና ማስተላለፍ

አቡበከር ከረሜላ Page 18


መተዳደሪያ ደንብ

3.15 ህጋዊ ያልሆነ የስራ ማቆም አድማ አድርጎ መገኘት ወይም ሌሎች ስራ ማቆም አድማ እንዲያደርጉ
መቀስቀስ እና ማነሳሳት፤

3.16 የወሲብ ጥያቄን መሰረት በማድረግ የሰራተኞችን የስራ ግምገማ ውጤት፤ እድገት ፤ቅጥርና ዝውውር
--- ወዘተ መፈፀም

3.17 በህግ እና በተቋሙ ውስጥ የጦር መሳሪያ ይዞ መግባት ከተፈቀደላቸውና ከጥበቃ ሰራተኞች በስተቀር
የጦር መሳሪያ ይዞ ድርጅቱ መግባት ፤

3.18 ዘርን ወይም ብሄርን ፤ፆታን ፤ሀይማኖትን፤ቀለምን ወይም ሌሎች መሰል ልዩነቶችን መሰረት ያደረገ
አድልዎ መፈፀም

4. በአንድ ሰራተኛ ላይ የዲሲፒሊን እርምጃ ሲወሰድ የሚወሰነው ቅጣት ስለጥፋት እና ስለቅጣት


ሰንጠረዥ መሠረት ሆኖ ይጥፋቱን ክብደት ከሚያሳዩት ደረጃዎች ለጥፋቱ ተመጣጣኛ በሆነ
የቅጣት ደረጃ ሊቀጣ ይችላል፡፡

5. አንድ ሰራተኛ በቸልተኝነት የድርጅቱ ገንዘብ ወይም ንብረት ያጎደለ ዌም ያለአግባብ የተጠቀመ
የድርጅቱን ማሽኖች ሆን ብሎ ያበላሸ በድርጅቱ ላይ ኪሳራ የሚያስከትል ድርጊት የፈፀመ
ወይም በገንዘብ ሊተመን የሚችል ዶክመንት ላየ ጉዳት የደረሰ ወይም ያጠፋ በመተዳደሪያ ው
ደንብ ከተመለከተው የዲሲፕሊን እርምጃ በተጨማሪ ባደረሰው ጉዳት መጠን በድርጅቱ
በሚዘጋጀው ጉዳት ግምት መሰረት ገቢ ያደርጋል፡፡

6. የጥፋትአይነት

6.1 በሰንጠረዡ ላይ ከተዘረዘሩት የጥፋት አይነቶች ዉጪ የሚያጋጥሙ ሌሎች የጠፋት አይነቶች ቢኖሩ
የጥፋቶቹ ከባድነትና ቀላልነት እየታየ ከሰንጠረዡ ዉስጥ ከተዘረዘሩ የቅጣት አይነቶች ዉሰጥ
ተመጣጣኝ ወይም ተቀራራቢ ይሆናሉ ተብለዉ በሚገምቱ የቅጣት አይነቶች መጠቀም ይቻላል ፡፡

አቡበከር ከረሜላ Page 19


መተዳደሪያ ደንብ

6.2 በሚከተለዉ የቅጣት ሰነጠረዥ የቅጣት ደረጃዉ የሚያመለክተዉ የጥፋቱ ክብደትና ቅለት ደረጃ እና
ለደረጃዉም የሚወሰነዉ ቅጣት እንጂ የጥፋት ቅደም ተከተል አይደለም፡፡

አቡበከር ከረሜላ Page 20


መተዳደሪያ ደንብ

የጥፋት አይነት እና የቅጣት ሰንጠረዥ

4 ኛ ደረጃ
የጥፋት አይነት 1 ኛደረጃ ጥፋት 2 ኛ ደረጃ ጥፋት 3 ኛ ደረጃ ጥፋት 5 ኛ ደረጃ ጥፋት
ጥፋት

1.በስራ ላይ ሁከት መፍተር


1.1 በስራ ላይ እያሉ እዉከት
ዛቻ እና ማስፈራራት

1.2 አካላዊ ጥቃት መፈጸም የ 7 ቀን ደሞዝ የ 15 ቀን ደሞዝ


ወይም መደባደብ (እራስን ከጽሁፍ ከጹሁፍ ከስራ ማሰናበት
ለመከላከል ካልሆን በስተቀር) ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያጋር

1.3 የተመደበበትን ስራ ሆን ብሎ
አለመስራት የ 7 ቀን ደሞዝ የ 15 ቀን ደሞዝ
በቅርብ ሃላፊ የሚሰጡ ከጹሁፍ ከጹሁፍ ከስራ ማሰናበት
አግባብ ያላቸዉ ትዛዞችን ማስጠንቀቂያጋር ማስጠንቀቂያጋር
አለመፈፀም

1.4 ሌሎች ሰራተኞች


እንዳይሰሩ ማነሳሳት የ 15 ቀንደሞዝ
ወይም የሀሰት ወሬዎችን በመንዛት
ከጹሁፍ ከስራ ማሰናበት
ስራ ማስፈታት በማኔጀመነቱ እና
በሰራተኛዉ መካከል ቅራኔ በመፍጠር ማስጠንቀቂያጋር
የእንዲስተሪ ሰላም ማደፍረስ

1.5 በቁሚነት በዚዜያዊነት ወይም የ 2 ቀን ደሞዝ የ 7 ቀንደሞዝ


የቃል
በትርፍ ሰአት የተመደበበትን ስራ ከጹሁፍ ከጽሁፍ ከስራ ማሰናበት
የተሰተዉን ትእዛዝ አለማከበር ማስጠንቀቂያ
ማስጠንቀቂያጋር ማስጠንቀቂያጋር

2. ጉዳት ስለማድረስ የ 4 ቀንደሞዝ የ 7 ቀንደሞዝ የ 15 ቀንደሞዝ


2.1 በድርጅቱ ንብረት ወይም
ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከስራ ማሰናበት
ዶክመንት ላይ በችልተኝነት
ጉዳት ማድረስ ማስጠንቀቂያጋር ማስጠንቀቂያጋር ማስጠንቀቂያጋር

አቡበከር ከረሜላ Page 21


መተዳደሪያ ደንብ

2.2 ከድርጅቱ ስራ ጋር በተያያዝ


ሁኔታ ሆን
ብሎ በሰራተኞች የ 4 ቀን ደሞዝ የ 7 ቀን ደሞዝ የ 15 ቀን ደሞዝ
ላይ ወይም በግል ንብረታቸዉ ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከደረጃ ዝቅ ማድረግ ከስራ ማስናበት
ላይ ጉዳት ያደረሰ ወይም ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር
በከፍተኛ ቸልተኝነት ይህ
ህንዳይደርስ ያደረገ

የ 1 ቀን ደሞዝ የ 15 ቀን ደሞዝ የ 7 ቀን ደሞዝ


2.3 በንብረት ላይ ጥቃቅን ከጽሁፍ
የቃል ማስጠንቀቂያ ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከጽሁፍ
ጉዳት ማድረስ ማስጠንቀቂያ
ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር

3. ስለ መኪና መንዳት
የወጣዉን ደንብ መጣስ የ 4 ቀን ደሞዝ የ 15 ቀን ደሞዝ የ 9 ቀን ደሞዝ የ 15 ቀን ደሞዝ
ከጽሁፍ
3.1 የትራፊክ ደንብ መጣስ ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከጽሁፍ
ማስጠንቀቂያ
ከተፈቀደዉ ፍጥነት በላይ ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር
የድርጀቱን ተሸከርካሪ መንዳት

3.2 የድርጀቱን ተሸከርካሪ


ያለአግባብ በመንዳት ወይም ከጽሁፍ
ከደረጃ ዝቅ ማድረግ ከስራ ማስናበት
በአጠቃላይ ጉድለት ጉዳት ማስጠንቀቂያ
ማድረስ

የ 15 ቀን ደሞዝ
3.3 ሰክሮ የድርጀቱን ተሸከርካሪ
ከጽሁፍ ከስራ ማስናበት
መንዳት
ማስጠንቀቂያ ጋር

የ 7 ቀን ደሞዝ የ 15 ቀን ደሞዝ
3.4 የድርጀቱን ተሸከርካሪ
ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከደረጃ ዝቅ ማድረግ ከስራ ማስናበት
ላልተፈቀደ ተግባር ማዋል
ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር

3.5 ያልተፈቀደ አወቃ ወይም የ 4 ቀን ደሞዝ የ 7 ቀን ደሞዝ የ 9 ቀን ደሞዝ የ 11 ቀን ደሞዝ


ከጽሁፍ
የድርጅቱ ሰራተኛ ያልሆነ ሰዉ ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከጽሁፍ
ማስጠንቀቂያ
መጫን /ማሳፈር/ ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር

የ 15 ቀን ደሞዝ
3.6 ያለ ህጋዊ መንጃ ፍቃድ
ከጽሁፍ ከደረጃ ዝቅ ማድረግ ከስራ ማስናበት
የድርጀቱን ተሸከርካሪ መንዳት
ማስጠንቀቂያ ጋር

4. ድርጅቱ ወይም የድርጀቱን የ 15 ቀን ደሞዝ ከደረጃ ዝቅ ማድረግ ከስራ ማስናበት

አቡበከር ከረሜላ Page 22


መተዳደሪያ ደንብ

ደንበኙች ማጭበርበር
/ማታለል/ ከጽሁፍ
4.1 በግል ጥቅም በሎ ማስጠንቀቂያ ጋር
ትክክለኛዉን ሁኔታ ማፈለስ
የ 7 ቀን ደሞዝ
የ 7 ቀን ደሞዝ የ 15 ቀን ደሞዝ
4.2 በተሰጡት መብተች ከጽሁፍ
ከጽሁፍ ከጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ከደረጃ ዝቅ ማድረግ ከስራ ማስናበት
አላግባብ መጠቀም ማስጠንቀቂያ
ማስጠንቀቂያ ጋር ጋር
ጋር

የ 15 ቀን ደሞዝ
5. ስለ ስካር የ 4 ቀን ደሞዝ የ 7 ቀን ደሞዝ የ 9 ቀን ደሞዝ
ከጽሁፍ
5.1 ለስራ እንቅፋት በሚሆን ከጽሁፍ ከጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ከጽሁፍ ከስራ ማስናበት
ማስጠንቀቂያ
ሁኔታ መጥቶ ወደ ስራ መግባት ማስጠንቀቂያ ጋር ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር
ጋር

5.2 ከስራ ቦታ ላይ ወይም


የ 7 ቀን ደሞዝ የ 15 ቀን ደሞዝ
በስራ ላይ ሆኖ የሚያሰክር
ከጽሁፍ ከጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ከደረጃ ዝቅ ማድረግ ከስራ ማስናበት
መጠጥ መጠጣት ወይም ጫት
ማስጠንቀቂያ ጋር ጋር
ይዞ መግባት እና መቃም
6.ያለ ፍቃድ የድርጀቱን የሰዉ የ 15 ቀን ደሞዝ
ሐይል እና ንብረት ለግል ጥቅም ከጽሁፍ ከደረጃ ዝቅ ማድረግ
ማዋል ማስጠንቀቂያ ጋር

7. ለደንበኞች እና ወደ ድርጀቱ
ለሚመጡ ባለ ጉዳይዎች ተገቢ የ 15 ቀን ደሞዝ
ያልሆነ ጠባይ ማሳየት ከጽሁፍ ከስራ ማስናበት
መጉላላት መሳደብ ወይም ማስጠንቀቂያ ጋር
መዛት ድርጊቶችን የፈጸሙ

8.በሴቶች ላይ ጾታዊ ትንኮሳ


ጾታዊ ጥቃት እና የሴቶችን የ 15 ቀን ደሞዝ
ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ ከጽሁፍ ከስራ ማስናበት
መብቶች ጥሰት የሚያደረጉ ማስጠንቀቂያ ጋር
ድርጊቶችን የፈጸሙ

አቡበከር ከረሜላ Page 23


መተዳደሪያ ደንብ

9. ከስራ ጋር በተያያዘ ድርጅን


በሚጎዳ ሁኔታ ወይም የዲርጀቱን
የ 15 ቀን ደሞዝ
ስም በሚጎድፍ መንገድ ወይም
ከጽሁፍ ከስራ ማስናበት
የድርጀቱን ጥቅም በሚያስቀር
ማስጠንቀቂያ ጋር
ሁኔታ ከደንበኞች ጋር ተገቢ
ያልሆኑ ግነኙነት መፍጠር

10.በስራ ገበታ ላይ አለመገኘት


የ 2 ቀን ደሞዝ የ 4 ቀን ደሞዝ የ 7 ቀን ደሞዝ
10.1 ከመደበኛ የስራ ሰአት
የቃል ማስጠንቀቅያ የጹሁፍ ማስጠንቀቅያ ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከጽሁፍ
ያለበቂ ምክኒያት ዘግይቶ
ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር
መግባት

10.2 ከመደበኛ የመዉጫ ሰአት የ 2 ቀን ደሞዝ የ 4 ቀን ደሞዝ የ 7 ቀን ደሞዝ


ቀድሞ ብሎ ያለበቂ ምክኒያት የቃል ማስጠንቀቅያ የጹሁፍ ማስጠንቀቅያ ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከጽሁፍ
መዉጣት ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር

የ 1 ቀን ደሞዝ የ 2 ቀን ደሞዝ የ 5 ቀን ደሞዝ የ 7 ቀን ደሞዝ


10.3 ያለ ስራ ፍቃድ ከስረ ቦታ የጹሁፍ
ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከጽሁፍ
መለየት ማስጠንቀቅያ
ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር

የ 2 ቀን ደሞዝ የ 5 ቀን ደሞዝ የ 7 ቀን ደሞዝ የ 9 ቀን ደሞዝ


የጹሁፍ
10.4 በስራ ስአት ተኝቶ መገኘት ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከጽሁፍ
ማስጠንቀቅያ
ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር

11. ልዩ ልዩ ጥፋቶች የ 4 ቀን ደሞዝ የ 7 ቀን ደሞዝ የ 15 ቀን ደሞዝ


11.1 በስራ ላይ የድርጀቱን አባል ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከስራ ማስናበት
በሀሰት ስም መጥፋት ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር

በድርጀቱ ንብረት ላይ ጉዳት


ሲደርስ እና በድርጀቱ ስር ላይ
እያለ በስራ ባልደረባዉን
የ 4 ቀን ደሞዝ የ 7 ቀን ደሞዝ የ 15 ቀን ደሞዝ
በማንኛዉም እንግዳ ሰዉ ላይ
ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከጽሁፍ ከስራ ማስናበት
ጉዳት የሚያስከትል ድንገተኛ
ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር ማስጠንቀቂያ ጋር
አጋጣሚ ሲደርስ እርዳታ
በድርጀቱ ነብረት እና ሰዉ ላይ
አለማድረግ

አቡበከር ከረሜላ Page 24


መተዳደሪያ ደንብ

7. ከስራ ላይ ስለ መጥፋት ከስራ ስለ መቅረት የዲሲፕሊን እርምጃዎች

7.1 አነድ ሰራተኛ ከስራ ቀሪ ሲሆን የሚወሰንበት ቅጣት ለቀረበት ቀናት ከደሞዝ ላይ ተቀናሽ

የደረጋል፡፡

7.2 በተለያዩ ጊዝያት ዉስጥ በአንድ ዓመትጊዝ አንድ ሰራተኛ ለ 30(ሰላሳ)ቀናት ያለ በቂ ምክኒያት ከስራ

ቀሪ ሲሆን የሰናበታል፡፡ ሆኖም የተጠቀሰዉ የ 30(ሰላሳ)ቀን ገደብ ከመድረሱ በፊት ድርጅቱ

የመጀመርያዉን የጹሁፍ ማስጠንቀቂያ ከ 5-15 ባሉት ቀኖች ሁለተኛዉን የጹሑፍ መስጠንቀቂያ ደግሞ

ከ 16-25 ባሉት ቀኖች ዉስጥ አስፈርሞ መስጠት አለበት፡፡

7.3 በተከታይ 5 ቀናት ያለ በቂ ምክኒያተወ ከስራ የሚቀር ሰራተኛ ከስራ ቀሪ ሲሆን ይሰናበታል፡፡ድርጀቱ

የመጀመርያ የጹሁፍ ማስጠንቀቂያ በሰባተኛ ቀን ሲሰጥ ሁለተኛዉ የጹሁፍ

ማስጠንቀቂያ ደግሞ በአስራ ሁለተኛዉ ቀን መስጠት ይኖርበታል ፡፡

7.4 ሰራተኛዉ የጹሁፍ ማስጠንቀቂያ ለመቀበል ፍቃደኛ ባይሆን ወይም ሠራተኛዉ ባለማግኘቱ ምክኒያት

አስፈርሞ ለመስጠት ባይችል ሰራተኛዉ በሚሰራበት አካባቢ ወይም ክፍል ዉስጥ ግልጽበሆነ ስፍራ ላይ

የሰራተኛ የቅርብ አለቃ ወይም ተቆጣጣሪ ባለበት እነዲለጠፍ ይደረጋል፡፡

የተለጠፈዉም የቱፍ ማስጠንቀቂያ ቢያንስ 5 የስራ ቀናት በማስታወቂያ ሰልዳ ወይም በተለጠፈ ስፍራ ላይ

ይኮያል

አቡበከር ከረሜላ Page 25


መተዳደሪያ ደንብ

አንቀጽ 10

የስራ ላይ አደጋ/ጉዳት

በስራዉ ምክኒያት በሰራተኛዉ ላይ የሚደርሱ አደጋዎች አና በስራዉ ምክኒያት ለሚደርሱበት በሽታዎች

ድርጀቱ ሀላፊ ነዉ፡፡ ሆኖም አደጋዉ ወይም በሽታዉ የደረሰበት ሰራተኛዉ አስቦ ያደረገዉ ጥፋተ መሆኑን

ወይም ሰራተኛዉ በግልጽ በጹሁፍ የተሰጠዉን ትእዛዝ በማስተላለፍ ወይም አደጋዉ ከሰራተኛዉ ስራ ጋር

ንነም ግኙነት መሆኑን ካስረዳ አሰሪዉ ሃላፊነት የለበትም፡፡

አቡበከር ከረሜላ Page 26


መተዳደሪያ ደንብ

ሌሎች አገልግሎቶች

1. የምስክር ወረቀት

የአንድ ሰራተኛ የስራ ዉል የሚቋለጥበት ወይም ሠራተኛዉ በሚጠየቅበት በማንኛዉም ጊዜ ድርጀቱ

የምስክር ወረቀት ይሰጣል ሆኖም ሰራተኛዉ የስንብት የምስክር ወረቀት ማግኘት የሚችለዉ የንብረት

ማጣሪያ ቅጽ አስሞልቶ የድርጅቱ ንብረት እና ገንዘብ በሙሉ በማስረከብ ማስረጃ ካቀረበ በኃላ ነዉ፡፡

የምስክር ወረቀት የሰራተኛ ፎቶ ያለዉ ሆኖ፡-

ሀ) የሚሰራዉ ስራ

ለ) ሙያዉ

ሐ) የሰራበት ዘመን

2. ልየ ልዩ ክፍያዎች

2.1 ሰራተኛዉ የስራዉ ዉሉን የሚያቋርጥበት ጊዜ የሰራበት ደሞዝ እና ልዩልዩ አበሎች እንዲሁም

የአመት ፍቃድ ቀኖች በገንዘብ ተተምነዉ ይከፈሉታል፡፡

2.2 አንድ ሰራተኛ የመስክ ስራ (ከአዲስ አበባ ከ 20 ኪ.ሜ) ሲታዘዝ በቀን 300 ብር ሂሳብ አበል

ይታሰብበታል፡፡

2.3 አንድ ሰራተኛ የስራ ዉሉን ማቋረጥ ከፈለገ ከአንድ ወር በፊት ማሳወቅ ይጠበቅበታል፡፡ ሆኖም የህ

ባልሆነበት ሁኔታ ድርጅቱ ሰራተኛዉ አለኝ ለሚለዉ ጥቅም ተጠያቂ አይሆንም፡፡

2.4 አንድ ሰራተኛ ጥቅማ ጥቅም መጠየቅ ካለበት 6 ወር ካለፈ በይርጋ ይታገዳል፡፡

አቡበከር ከረሜላ Page 27


መተዳደሪያ ደንብ

ስምምነት

የድርጅቱን ማኔጅመንት እና የድርጀቱ ሰራተኞች ተወካይ አንድ ኢ .ት. አቆጣተር

ከ---------------------------ጀምሮ በዚ መተዳደርያ ደንብ መሰረት ለመስራት ተስማምተዉ

እነደሚከተለዉ በፊርማቸዉ አጽድቀነዋል፡፡

የሰራተኞች ተወካይ ፊርማ የማኔጅመንቱ ተወካይ ፊርማ

1. 1.

2. 2.

3. 3.

4. 4.

አቡበከር ከረሜላ Page 28

You might also like