Download as docx, pdf, or txt
Download as docx, pdf, or txt
You are on page 1of 4

የቢሮ ኪራይ ውል ስምምነት

ቀን፡- መጋቢት 01/2012


ዓ.ም
አከራይ፡- ኖኅ ሪል እስቴት ኃ/የተ/ግ/ማኅበር አድራሻ፡- አዲስ አበባ ክ/ከተማ፡- ቦሌ ወረዳ፡- _03_ የቤት ቁ.፡-
_አዲስ_ ስልክቁ.፡-_0116674083/0945949872_ኢሜል፡-_info@noahrelestateplc.com_የመ.ሳ.ቁ.፡-33136-
1000
ዋና ስራ አስኪያጅ፡- አቶ ብዙነህ ታደሰ ዜግነት /ኢትዮጲያዊ/ አድራሻ፡- አዲስ አበባ ክ/ከተማ፡- _የካ__ ወረዳ፡-
__09_ የቤት ቁ.፡-_104__
እና
ተከራይ፡-ምትኩ ንጋቱ ሚቲ ኒዉትሪሽን አስመጪ
ዋና ስራ አስኪያጅ፡-አቶ ምትኩ ንጋቱ ዜግነት /ኢትዮጲያዊት/ አድራሻ፡- አዲስ አበባ ክ/ከተማ፡- አቃቂ ወረዳ፡- 07
የቤት ቁ፡- TR 85 ስ.ቁ፡ 0911120446
ህጋዊ ወኪል አቶ መሀመድ አብሬ ሰይድ ዜግነት /ኢትዮጲያዊት/ አድራሻ፡- አዲስ አበባ ክ/ከተማ፡- አቃቂ ቃሊቲ
ወረዳ፡- 07 የቤት ቁ፡-m/1232 ስ.ቁ፡ 0911225447
የዉክልና ቁጥር ፡ ቅ 12/7059/1/09
የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፡ 0004455625

አንቀጽ አንድ፡- የውሉ ዓላማ

አከራይ በስሙ የተመዘገበውና የራሱ ንብረት ከሆነው አዲስ አበባ ከተማ_ቦሌ_ ክፍለ ከተማ ወረዳ_03___
የቤት ቁጥር _አዲስ_ የካርታ ቁጥር AA000060304609 ካርታው የተሰጠበት ቀን 09/10/08 ዓ.ም ተመዝግቦ
በሚገኘው ህንፃ ላይ በ_ ግራዉንድ ወለል _ የቢሮ ቁጥር _ NRE/AP/G05 B_፤ ስፋቱ _28_ካ.ሜ.፤ የሆነ ቦታ
ለማከራየት ፍላጎት ያለው በመሆኑ ሁለቱም ወገኖች ወደውና ፈቅደው ከዚህ እንደሚከተለው ተዋውለዋል፡፡
አንቀጽ ሁለት፡- የኪራይ ተመን እና አከፋፈል
2.1. የቦታው የኪራይ መጠን 15% ተጨማሪ እሴትን ጨምሮ በካሬ ሜትር ብር 522.00 (አምስት መቶ ሃያ
ሁለት ብር ከ 00/100) ነው፡፡
2.2. በወር 15% ተጨማሪ እሴት ታክስ ሳይጨምር ብር 12709.57 ( አስራ ሁለት ሺ ሰባት መቶ ዘጠኝ ብር
ከ 57/100) ብሎም ተጨማሪ እሴት ታክስ 15% ብር 1906.43 (አንድ ሺ ዘጠኝ መቶ ስድስት ብር
ከ 43/100) ሲሆን ይህ ዋጋ ከ የካቲት 20 ቀን 2012 ዓ.ም እስከ የካቲት 19 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ ጸንቶ
ይቆያል፡፡
2.3. የኪራይ አከፋፈል
2.3.1. ተከራይ የ 6 ወር ቅድሚያ ኪራይ ክፍያ 15% ተጨማሪ እሴት ታክስን ጨምሮ ብር 87696.00(ሰማንያ
ሰባት ሺ ስድስት መቶ ዘጠና ስድስት ብር ከ 00/100) ከፍለዋል፤ አከራይም ለተከራይ ተገቢውን ደረሰኝ
ሰጥተዋል፡፡
2.3.2. ቅድሚያ ክፍያ የተከፈለበት የመጀመሪያው የ 6 ወር ጊዜ ካበቃ በኃላ ላሉት ቀሪ የኪራይ ዘመናት
ተከራይ የ 3 ወር ቅድሚያ ኪራይ ክፍያ ለአከራይ ይከፍላል፡፡
2.3.3. ተከራይ ቀድሞ የከፈለው የቅድሚያ ኪራይ ጊዜ ከተጠናቀቀ በኃላ ቀጣይ ክፍያውን በ 10 (አስር) ቀናት
ይከፍላል፡፡
2.3.4. የቅድሚያ ኪራዩን በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 2.3.3. መሰረት ሳይከፍል ከዘገየ የውዝፉን ወይም
ያልተከፈለበትን የቅድሚያ ኪራይ 10% መቀጫ ጋር በ 10 (አስር) ቀናት ውስጥ ይከፍላል፡፡
2.3.5. ተከራይ የቅድሚያ ኪራዩን ከ 10% መቀጫ ጋር በ 10 (አስር) ቀናት ውስጥ ካልከፈለ አከራይ ውሉን
ለመሰረዝና እዳውን ለማስከፈል በህግ አግባብ መብት እንዳለው ሁለቱም ወገኞች ተስማምተዋል፡፡
አንቀጽ ሦስት፡- የኪራይ ንብረት አጠቃቀም
3.1. ተከራይ የተከራየውን ክፍል (ቦታ) ለ ንግድ ቤት አገልግሎት ብቻ ይውላል፡፡
3.2. ተከራይ የኪራይ ንብረቱን ወይንም ማንኛውንም የንብረቱ አካል ከሕግ፣ ከደንብ፣ ከዚህ ውል፣ ከመንግስት
መመሪያና በአብዛኛው ህዝብ ተቀባይነት ካለው ልምድና ባህል ውጪ ለሆኑ ጉዳዮች ወይም ተግባር መጠቀም
ወይንም ማዋል ጨርሶ አይችልም፡፡
3.3. ተከራይ የተከራየውን ንብረት ሲለቅ የተከራየውን ንብረት እንዲሁም በውስጡ የተገጠሙት ልዩ ልዩ
መገልገያ ዕቃዎች ብልሽትና ጉዳት ካላቸው ቀድሞ በተሰራበት ማቴሪያል ዓይነት በራሱ ወጪ በመለወጥና
በማስተካከል በነበሩበት አኳኃን በማድረግ ለአከራዩ መልሶ ያስረክባል፤ ግንባታውም ደረጃውን የጠበቀና በአከራዩ
ተቀባይነት ያለው መሆን ይገባዋል፡፡

አንቀጽ አራት፡- አገልግሎቶች እና ግብር


ተከራይ ለሚጠቀመው የውሃ፣ የመብራት፣ ስልክ እና የመሳሰሉትን ክፍያዎች ንብረቱን ከተከራየበት ጊዜ ጀምሮ
ይከፍላል፤ ተከራይ ለተሰማራበት ወይም ለሚሰማራበት የንግድ ሥራ ዘርፍ ማናቸውም የመንግስት ግብር
የመክፈል ኃላፊነት አለበት፡፡
አንቀጽ አምስት፡- የግንባታ ማሻሻያ ለውጦች፣ ተጨማሪ ሥራዎችና የማስታወቂያ ምልክቶች
5.1. የአከራይ የጽሁፍ ፍቃድ ስለማግኘት
5.1.1. ተከራዩ የአከራዩን የጹሁፍ ፈቃድ ሳያገኝ በሕንፃው ወይም በንብረቱ ላይ የግንባታ ማሻሻያ፣ የቅርጽ
ወይም የይዞታ ለውጥ ማድረግ፣ የማስታወቂያ ምልክት ማድረግ፣ መግጠምም ሆነ መለጠፍ አይችልም፡፡
5.1.2. ተከራይ ከላይ የተጠቀሱትን ማሻሻያ ሥራዎች ለማካሄድ ሲፈልግ አከራዩን የጽሁፍ ፈቃድ ይጠይቃል፤
አከራይ ለተከራይ በዚህ ጉዳይ ለሚቀርብለት የፈቃድ ጥያቄ በ 15 (አስራ አምስት) ቀናት ውስጥ መልስ
ለመስጠት ጥረት ያደረጋል፡፡ ነገር ግን አከራይ በዚህ የግዜ ገደብ ውስጥ በልዩ ልዩ ምክንያቶች መልስ ሳይሰጥ
ቢቀር ፈቃድ እንደሰጠ አይቆጠርም፡፡
5.1.3. የአከራይ ፈቃድ ከተገኘ በኋላ በተከራይ በኩል የሚደረግ የማሻሻያ ግንባታ የህንፃውን የጥራት ደረጃ፣
የኪራይ ንብረቱን ይዞታ ወሰንና ክልል የጠበቀ መሆን ይኖርበታል፡፡
5.1.4. ለማሻሻያ ግንባታም ሆነ ለማፍረሻ የሚያስፈልገውን ወጪ ተከራይ ይከፍላል፡፡
5.1.5. ተከራይ ህንፃውን ለቆ በሚሄድበት ወቅት በህንፃው ላይ ያደረጋቸውን ማሻሻያዎችና ለውጦች
እንዲሁም ያቆማቸውን የማስታወቂያ ምልክቶች በራሱ ወጪ በማፍረስ ንብረቱን ቀድሞ በነበረበት ሁኔታ
ለአከራዩ መልሶ ያስረክባል፡፡
5.1.6. በተከራዩ አጠቃቀምና አያያዝ ጉድለት ወይም ግዴለሽነት በሕንፃው አካል፣ በንብረቱ ወይም በመገልገያ
መሣሪያዎች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ተከራይ በራሱ ወጪ ይጠግናል፤ ያድሳል፡፡
5.1.7. በእርጅና፣ በኮንስትራክሽን ጉድለት እንዲሁም ከአቅም በላይ በሆነ ችግር በሕንፃው ወይም በንብረቱ ላይ
የሚደርሰውን ጉዳት አከራዩ በራሱ ወጪ ይጠግናል፤ ያድሳል፡፡
አንቀጽ ስድስት፡- በአደራ መስጠትና መልሶ ማከራየት
6.1. ተከራይ የአከራዩን የጽሁፍ ፈቃድ ሳያገኝ የተከራየውን ንብረት በሙሉም ሆነ በከፊል ለሉላ ሦስተኛ ወገን
በአደራ መስጠት አይችም፤ ተከራይ የተከራየውን ንብረት በአደራ መስጠት ሲፈልግ አከራይን በጽሁፍ
ይጠይቃል፡፡ አከራይ ለተከራዩ ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ ይሰጣል፡፡
6.2. አከራይ ጥያቄውን ውድቅ የማድረግ ወይም ተገቢ የሚለውን ከፍያ አስከፍሎ ጥያቄውን ለመቀበል ወይም
ተገቢ ነው ብሎ ያመነበትን ክፍያ በመፈጸም ከዋናው ተከራይ ጋር ያለውን ውል ለመሰረዝ ይችላል፡፡
6.3. ተከራይ የተከራየውን ንብረት ለሌላ ሦስተኛ ወገን ማከራየት አይችልም፡፡
አንቀጽ ሰባት፡- የጽሁፍ ልውውጦች
በአከራይና በተከራይ መካከል የሚኖር ማንኛውም የጽሁፍ ልውውጥ፣ ማስጠንቀቂያ፣ ማስታወቂያ ወይንም
ማሳሰቢያ ከላይ በተጠቀሰው የአከራይና የተከራይ አድራሻዎች አማካኝነት ይሆናል፡፡
አንቀጽ ስምንት፡- አለመግባባትን ስለመፍታት
8.1. ሁለቱ ወገኖች በመካከላቸው የሚፈጠረውን አለመግባባት በውይይት ለመፍታት ይጥራሉ፡፡
8.2. የተፈጠረው አለመግባባት በስምምነት የማያልቅ ሆኖ ከተገኘ ውሉን ለማፍረስ የሚሞክረው አካል ለውል
አክባሪው ወገን ብር 5,000.00 (አምስት ሺ ከ 00/100) መቀጫ ከፍሎ ውሉና ገደቡ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1889/1890
መሰረት በህግ ፊት የጸና ይሆናል፡፡
አንቀጽ ዘጠኝ፡- አከራይ ንብረቱን የመቆጣጠር ስልጣን
9.1. አከራይ የኪራይ ንብረቱ በሚገባ መያዙንና ለተፈቀደው አገልግሎት ብቻ መዋሉን ለማረጋገጥ ለተከራይ
ከ 48 (አርባ ስምንት) ሰዓት በፊት ማሳሰቢያ በመስጠት ከተከራይ ተወካይ ጋር በመሆን በሥራ ሰዓት እና ቀን
የመግባትና የመቆጣጠር መብት ይኖረዋል፡፡
9.2. ተከራይ ኪራይ ባለመክፈሉ ወይም በማንኛውም ምክንያት ስራውን መስራት የማያስችለው ሁኔታ
ገጥሞት ቤቱን ያለአከራይ ዕውቅናና ፈቃድ ከ 7(ሰባት) ቀናት በላይ ቢዘጋ ምክንያቱን እንዲያስረዳ
ማስጠንቀቂያ እንዲደርሰው ይደረጋል፤ በተሰጠው የማስጠንቀቂያ ግዜ ውስጥ ካልከፈተ አከራይ ለተከራይ
ቤቱን በሰባት ቀን ውስጥ እንዲከፍት ባይከፍት አከራይ ቤቱን በራሱ የሚከፍት መሆኑን የሚገልጽ ሁለተኛ
ማስጠንቀቂያ ለተከራይ ይሰጠል ፡፡
9.3 የእቃውን ዝርዝር በመመዝገብ እና ከክፍሉ በማውጣት ቢበዛ ለ 1 (አንድ) ወር በመጋዘን ያስቀምጣል፤
ተከራይ ለአከራይ የመጋዘን ኪራይ በወር 5000.00 (አምስት ሺ ከ 00/100) ብር በመክፈል ንብረቱን ይረከባል፡፡
9.4. ከ 1 (አንድ) ወር በኋላ በተከራይ ንብረት ላይ ለሚደርስ ማንኛውም ጉዳት አከራይ ኃላፊነት
እንደማይወስድ እንዲሁም ተከራይ እዳውን ከፍሎ ንብረቱን መውሰድ ካልቻለ አከራይ በራሱ መንገድ ንብረቱን
ሸጦ ለእዳ ማካካሻ እንዲውል አከራይና ተከራይ ተስማምተዋል፡፡ ንብረቶቹ ተሸጠው የሚገኘው ገቢ እዳውን
ለመሸፈን ካልቻለ ቀሪውን እዳ አከራይ በህግ አግባብ የመጠየቅ መብት አለው፡፡

አንቀጽ አስር፡- ተፈጻሚነት ያለው ሕግ እና አለመግባባቶችን ስለመፍታት


ይህ ውል በስራ ላይ ባለው በኢትዮጵያ ሕጎች መሰረት በሚጣጣምና በማይቃረን መልኩ ይተረጎማል፡፡
ተዋዋይ ወገኖች ይሄንን ውል አስመልክቶ በመካከላቸው የሚነሳውን አለመግባባት በስምምነት ለመፍታት
ጥረት ያደርጋሉ፤ አለመግባባታቸውን በስምምነት መፍታት ካልቻሉ ግን ጉዳያቸውን ሥልጣን ላለው ፍርድ
ቤት ሊያቀርቡ ይችላሉ፡፡
አንቀጽ አስራ አንድ፡- ውል የሚቋረጥባቸው ሁኔታዎች
ይህ ውል ከሚከተሉት ሁኔታዎች መካከል በአንዱ ምክንያት ሊቋረጥ ይችላል፡-
11.1. ውሉ እንዲፈርስ ሁለቱ ወገኖች ሲስማሙ፤
11.2. ከዚህ በታች በአንቀጽ 12.1 የተጠቀሰው የኪራይ ውል ዘመኑ ሲያበቃ፤
12.3. በማንኛውም ጊዜ ተከራዩ ወይም አከራዩ ውሉ እንዲቋረጥ የ 3 (ሦስት) ወር የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ
በሚሰጠው ጊዜ፤
11.4. ተዋዋይ ወገኖች በዚህ ውል መሰረት ግዴታቸውን ሳይፈጽሙ ወይም ሳያከብሩ ሲቀሩ፤ ውሉ እንዲከበር
የሚፈልግ ወገን ለሌላኛው ወገን የ 30 (ሰላሳ) ቀናት ማስጠንቀቂያ በመስጠት፤
12.5. ተከራይ የውሉ ዘመን ከማለቁ በፊት የኪራይ ዘመኑን ማቋረጥ ከፈለገ በቅድሚያ የከፈለውን ክፍያ
መጠየቅ አይችልም፡፡
አንቀጽ አስራ ሁለት፡- የኪራይ ዘመን
12.1. ይህ ውል ጸንቶ የሚቆየው ከላይ በ 2.2 ላይ እስከተጠቀሰው ጊዜ ድረስ ነው፡፡ ከዚህ በታች በተገለፀው
መሰረት ውሉ ካልተራዘመ በስተቀር ይህ የውል ጊዜ እንዳበቃ ውሉ ይቋረጣል፡፡
12.2. ተከራይ የኪራይ ዘመኑን ለማራዘም ፍላጎት ሲኖረው በዚህ ውል የተወሰነው የኪራይ ዘመን ከማለቁ ከ 3
(ሦስት) ወር በፊት አከራዩን በጽሁፍ ይጠይቃል፤ አከራይ ከተከራይ ለሚቀርብለት ጥያቄ በ 15 (አስራ አምስት)
ቀናት ውስጥ መልስ ይሰጣል፡፡ የአከራይ መልስ አለመስጠት የኪራይ ዘመኑን የሚያራዝም አይሆንም፡፡
12.3. ውሉ የሚራዘም ከሆነ እንደአስፈላጊነቱ ከወቅቱ የገበያ ዋጋ ጋር በማገናዘብ አከራይ የኪራይ ዋጋ
የመጨመር መብት አለው፤ የኪራይ ተመኑ በድርድር ይወሰናል፡፡ በድርድር የኪራይ ተመኑን መወሰን ካልተቻለ
ውሉን ለማቋረጥ በቂ ምክንያት ይሆናል፡፡

የአከራይ ስምና ፊርማ የተከራይ ስምና ፊርማ

You might also like