Download as pdf or txt
Download as pdf or txt
You are on page 1of 10

አቡነ ጎርጎርዮስ ፩ኛ ደረጃ ት/ቤት

አማርኛ መማሪያ መጽሐፍ ፩ኛ ክፍል


መግቢያ
ቋንቋ መግባቢያ በመሆኑ ለማንኛውም ስው አስፈላጊ ነው፡፡ ሰዎች ስራቸውን ለማከናወን
መግባባት ስለሚያስፈልጋቸው በየዕለቱ በቋንቋ ይገለገላሉ፡፡ ሃሳብ፣ ይለዋወጣሉ፡፡ የሚወዱትንም
ሆነ የሚጠሉትን ይገልፃሉ፡፡ የሌሎችን ሀሳብ፣ አስተያየት፣ በቋንቋ አማካኝነት ይረዳሉ፡፡ ቋንቋ
እነዚህን መሰል አገልግሎቶች ሲኖሩት እነሱን ተግባራዊ ለማድረግ ሥርዓት ባለው መንገድ
ልንጠቀምበት ይገባል፡፡ በመሆኑም ይህንን ዋነኛ የመግባቢያ መንገድ መማር ወይም መልመድ
አስፈላጊነቱ ከፍተኛ ነው፡፡

በክፍል ውስጥ የሚቀርበው የቋንቋ ትምህርት የተማሪዎችን የማዳመጥ፣ የመናገር፣


የማንበብና የመፃፍ ክሂሎት የሚያሳድግ መሆን ይኖርበታል፡፡ እንዲህ ሲሆን በየደረጃው
ያዳመጡትን እንዲረዱ ያስችላቸዋል፡፡ ሃሳባቸውንም በእድሜያቸውና በዕውቀታቸው ደረጃ
ያለችግር እንዲገልፁ ይረዳቸዋል፡፡ ከችሎታቸውና ከአቅማቸው ጋር የሚመጣጠኑ ጽሑፎችን
አንብበው መገንዘብ እንዲችሉ ያግዛቸዋል፡፡ በጽሑፉ ሊያስተላልፍ የፈለጉትንም እንዲያሰፍሩ፡፡

በዚህ መጽሐፍ ሃያ ስምንት ምዕራፎችን የያዘ ሲሆን አስራ አራት ምንባቦች፣ ተረቶችና
ግጥሞችም ተካተዋል፡፡ ምንባቦች ከተማሪዎች ዕድሜና ልምድ ጋር እንዲ መጣጠኑና
ክሂሎቻችውን እንዲያሳድጉ ሆነው ተሰናድተዋል፡፡ ተከታታይነት እንዲኖራቸውም የተቻለውን
ሁሉ ጥረት ተደርጓል፡፡ ከዚህም በላይ ተማሪዎችን የሚስቡ እንዲሆኑ ተሞክሯ፡፡ ተማሪዎች
አስራ አራቱ ምንባቦች ላይ ብቻ ሳይገደቡ ሌሎች ተመጣጣኝ የሆኑ ጽሑፎችን እንዲያነቡ
ይገድፋቸዋል የሚል እምነት አለን፡፡ ከዚህ በላይ የማንበብ ችሎታ፣ ፍጥነትና ልምድ
እንዲያዳብሩም ይጠበቃል፡፡
ክፍል አንድ
የፊደል ገበታ
ፊደል የጽህፈትና የንባብ መጀመሪያ ነው፡፡ ስለሆነም ማንኛውንም ጽሑፍ ለማንበብና ለመፃፍ
ፊደላትን ማወቅ ይጠይቃል፡፡

፩ የአማርኛ የፊደላት አቀማመጥ

ሀ ሁ ሂ ሃ ሄ ህ ሆ
ለ ሉ ሊ ላ ሌ ል ሎ
ሐ ሑ ሒ ሓ ሔ ሕ ሖ
መ ሙ ሚ ማ ሜ ም ሞ
ሠ ሡ ሢ ሣ ሤ ሥ ሦ
ረ ሩ ሪ ራ ሬ ር ሮ
ሰ ሱ ሲ ሳ ሴ ስ ሶ
ሸ ሹ ሺ ሻ ሼ ሽ ሾ
ቀ ቁ ቂ ቃ ቄ ቅ ቆ
በ ቡ ቢ ባ ቤ ብ ቦ
ተ ቱ ቲ ታ ቴ ት ቶ
ቸ ቹ ቺ ቻ ቼ ች ቾ
ነ ኑ ኒ ና ኔ ን ኖ
ኘ ኙ ኚ ኛ ኜ ኝ ኞ
ኀ ኁ ኂ ኃ ኄ ኅ ኆ
አ ኡ ኢ ኣ ኤ እ ኦ
ከ ኩ ኪ ካ ኬ ክ ኮ
ኸ ኹ ኺ ኻ ኼ ኽ ኾ
ዐ ዑ ዒ ዓ ዔ ዕ ዖ
ወ ዉ ዊ ዋ ዌ ው ዎ
ዘ ዙ ዚ ዛ ዜ ዝ ዞ
ዠ ዡ ዢ ዣ ዤ ዥ ዦ
የ ዮ ዪ ያ ዬ ይ ዮ
ደ ዱ ዲ ዳ ዴ ድ ዶ
ጀ ጁ ጂ ጃ ጄ ጅ ጆ
ገ ጉ ጊ ጋ ጌ ግ ጎ
ጠ ጡ ጢ ጣ ጤ ጥ ጦ
ጨ ጩ ጪ ጫ ጬ ጭ ጮ
ፀ ፁ ፂ ፃ ፄ ፅ ፆ
ጸ ጹ ጺ ጻ ጼ ጽ ጾ
ጰ ጱ ጲ ጳ ጴ ጵ ጶ
ፈ ፉ ፊ ፋ ፌ ፍ ፎ
ፐ ፑ ፒ ፓ ፔ ፕ ፖ
ቨ ቩ ቪ ቫ ቬ ቭ ቮ

በአማርኛ ፊደል ገበታ ላይ የሚገኙ ፊደላት እግር አልባ፣ ባለአንድ እግር፣ ባለ ሁለት እግር
እና ባለ ሶስት እግር ተብለው ሊጠኑ ይችላሉ፡፡

፩. እግር አልባ /የለሽ/ፊደላት

ሀ ዐ

መ ወ

ሠ ፀ

ረ ፈ

ከላይ የተዘረዘሩት የአማርኛ ፊደላት እግር የሌላቸው ፊደላት ናቸው፡፡

፪. ባለ አንድ እግር ፊደላት

ተ ኀ ነ ገ

ቸ የ ኘ ፐ

ከላይ የተዘረዘሩት ፊደላት በሙሉ ባለ አንድ እግር የአማርኛ ፊደላት ናቸው፡፡

መልመጃ አንድ

1. የሚከተሉትን ፊደላት ከነቤተሰቦቻቸው ጻፉ፡፡

ቀ _________ _________ _________ _________ _________ _________

ኀ _________ _________ _________ _________ _________ _________


ወ _________ _________ _________ _________ _________ _________

ኘ _________ _________ _________ _________ _________ _________

የ _________ _________ _________ _________ _________ _________

2. እግር አልባ /የለሽ/ ፊደላትን ከነ ቤተሰቦቻቸው ፃፉ፡፡


፩. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______
፪. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______
፫. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______
፬. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______
፭. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______
፮. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______
፯. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______

3. ባለ አንድ እግር የአማርኛ ፊደላትን ከነቤተሰቦቻቸው ጻፉ፡፡

፩. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______


፪. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______
፫. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______
፬. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______
፭. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______
፮. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______
፯. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______

፫. ባለ ሁለት እግር ፊደላት


ባለ ሁለት እግር ፊደላት የሚባሉት የሚከተሉት ፊደላት ናቸው፡፡ ስማቸውንም ያገኙት
ከእግራቸው ብዛት የተነሳ ነው፡፡

ሰ ዘ

ሸ ዠ
በ ደ
አ ጀ
ከ ጸ
ኸ ጰ

፬ ባለ ሦስት እግር ፊደላት

ባለ ሦስት እግር ፊደላት የሚባሉት 3እግሮች ያሏቸው ፊደላት ናቸው፡፡

እነዚህ ፊደላት በቁጥራቸው ከሌሎች አንፃር ውስን ናቸው፡፡

መልመጃ 2(ሁለት)

1. በባለ ሁለት እግር ፊደላት እና ባለ ሦስት እግር ፊደላት መካከል ለው ልዩነት


ምንድን ነው?
2. ባለ ሁለት እግር ፊደላት የሚባሉትን ከነቤተሰቦቻቸው ፃፉ፡፡
፩. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______
፪. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______
፫. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______
፬. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______
፭. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______
፮. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______
፯. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______
፰. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______

3. ባለ ሦስት እግር ፊደላትን ከነቤተሰቦቻቸው ጻፍ


፩. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______
፪. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______
፫. _______ ______ _______ ______ _______ _______ _______

ሁሉም የአማርኛ ፊደላት ሰባት ሰባት ቤተሰቦች አሏቸው፡፡ ሰባቱን የፊደላቱ ቤተሰቦች
የየራሳቸው መጠሪያ ስሞች አሏቸው፡፡
የመጀመሪያዎቹ = ግእዝ
የሁለተኛዎቹ = ካኢብ
ሦስተኛዎቹ = ሣልስ
አራተኛዎቹ = ራብዕ
አምስተኛዎቹ = ሃምስ
ስድሰተኛዎቹ = ሣድስ
ሰባተኛዎቹ = ሳብዕ ይባላሉ፡፡
ለምሳሌ፡-
ሀ = ግዕዝ
ሁ = ካኢብ
ሂ = ሣልስ
ሃ = ራብዕ
ሄ = ሃምስ
ህ = ሳድስ
ሆ = ሳብዕ ማለት ነው፡፡
፪ ቃላት መመስረት
ሀ. በእግር አልባ ፊደላት ቃላት መመስረት
 እግር አልባ ፊደላትን በቃሉ መጀመሪያ ላይ መጠቀም ቃላት እንመሠርታለን፡፡
ለምሣሌ
መሰላል ፈረስ
ወንዝ ዐይን
ፀሐይ ሀገር
 የተመሰረተባቸው ፊደላት ቡሉ እግር አልባ ፊደላት ናቸው፡፡
ለ. ለባለ አንድ እግር ፊደላት ቃላት መመስረት
 ባለ አንድ እግር ፊደላትን የቃሉ መጀመሪያ ላይ በመጠቀም በርካታ ቃላትን
መመስረት ቻላል፡፡
ለምሳሌ፡-
ተማሪ ነብር ቀበሮ
ገመድ ቸርነት የኛ

መልመጃ አንድ
1. በሚከተሉት ቃላት ውስጥ የሚገኙትን እግር አልባ ፊደላት አስምሩባቸው፡፡
ሀ. ወጣት ሠ. ፈሳሽ
ለ. ፀጉር ረ. መኝታ
ሐ. ረጅም ሰ. ዐዞ
መ.ሠማይ ሸ. ሀሰት
2. በሚከተሉት ባለ አንድ እግር ፊደላት ቃላት መስርቱ፡፡
ሀ. ተ _______
ለ. ገ _______
ሐ. ቀ _______
መ. ገ _______
፫. በባለ ሁለት እግር ፊደላት ቃላት መመስረት
ለምሳሌ፡-
ሰው ጀንበር
ሸሚዝ ዘመድ
አበባ በር
ከበሮ ደጀን የመሣሠሉት
 ከላይ በተዘረዘሩት ቃለት ውስጥ መጀመሪያ ፊደላቱ በሙሉ ባለ ሁለት እግር
ናቸው፡፡
ተግባር
 ተማሪዎች እናንተም ከላይ በቀረበው ምሳሌ መሰረት በባለ ሁለት እግር ፊደላት
በርካታ ቃላት መስርቱ፡፡ስትጨርሱም ለመምህራችሁ አንብቡላቸው፡፡
፬. በባለ ሦስት እግር ፊዳላት ቃላት መመስረት

ባለ ሦስት እግር ፊዳላት የሚባሉት ሐ፣ጠ፣ጨ እንደሆኑ ቀደም ባለው ጊዜ ተምራችኋል፡፡


አሁን ደግሞ በነዚህ ፊደላት ቃላትን ትመሠረታላች፡፡

ለምሳሌ ሐብል

ጨጨብሳ

ጠርሙስ

 ተማሪዎች በምሳሌው መሰረት በባለሦስት እግር ፊደላት ቢያንስ ሁለት ሁለት ቃላት
መሰርቱ፡፡
ሀ. _______
ለ. _______
ሐ. _______
መ. _______

You might also like