ወዴት ነህ

You might also like

Download as docx, pdf, or txt
Download as docx, pdf, or txt
You are on page 1of 38

1.

ሳሙና የሚገድለው በሽታ ቤተ ክርስቲያንን አዘጋ


 ሙት ያስነሳው የኤልያስ አምላክ ሆይ ወዴት አለህ?
 ከሞተ በኋላ በአጽሙ ሙት ያስነሰው የኤልሳዕ አምላክ ሆይ ለምን ዝም አልክ?
 ባህር የከፈለው የሙሴ አምላክ ሆይ ወዴት ነህ?
 በእጣኑ በሽታን አርቆ ምሙማንን የፈወሰው የአሮን አምላክ ሆይ ለምን ዝም አልክ?
 ፀሐይን ያቆመው የኢያሱ አምላክ ሆን ለምን ተውከን?
 ጣቢታን ከሞት ያስነሳው የጴጥሮስ አምላክ ሆይ ወዴት ነህ?
 በቤተ መቅደሱ በር ድውያንን የፈወሱ የጴጥሮስ የዮሐንስ አምላክ ሆይ መቅደስህ ሲዘጋ ለምን
ዝም አልክ?
 በልብሳቸው ድውያንን የሚፈውሱ በጥላቸው ምህረትን የሚያመጡ የቅዱሳን አምላካቸው ሆይ
ተለመነን።
 የነቢያት አምላካቸው ምህላችን ስማን።
 የሐዋርያት አምላካቸው ጸሎታችን ከፊትህ ትድረሰን።
 የሰማእታት አምላካቸው ስለእነሱ ብለህ ራራልን።
 በቃል ዐላዛርን ጠርተህ ከሞት ያስነሳሀው የአላዛር አምላክ ሆይ ሞትና ህማም በአንተ ዘንድ
ኢምንት ናቸውና እባክህ እንደክፋታችን አትክፈለን።
 በዘመነ ሰማእታት በከሀድያን ነገስታት ቤተ ክርስቲያን ተዘግታ ነበር።
 ዛሬ ደግሞ ሳሙና በሚገድለው በሽታ ምክንያት በደምህ የዋጀሃት ቤተ ክርስቲያንህ ስትዘጋ ዝም
አትበል።
 በቆሮንቶስ የፈተነህ ሰይጣን ዛሬም በዓለም ዙሪያ በሽታ ዘርቶ ቤተ ክርስቲያንህን ፈትኗታል
በቆሮንቶስ ድል እንደነሳሀው ዛሬም ድል መንሳትህ ከቤተ ክርስቲያንህ አታርቅ።
 አምላክ ሆይ ታረቀን ተለመነን ማረን እዘንልን እንደ ኀጢአታችን አትፍረድብን
ቁጣህን በምረትህ መልስልን።
 አምላክ ሆይ ከአንተ ደጅ ተለይቶ ከመኖር ከባድ ሞት ነው ከጅህን ክፈትልን።
 ሳሙና የሚገድለው በሽታ ሰውን በመግደል ሰውን አስጨንቋልና ለዓለም ፈውስህን ላክላት
እጆችህን ዘርጋላት።
 በዚህ ቤተ ክርስቲያን በምትዘጋበት ዘመን መፈጠሬን አምርሬ ጠላሁት።
 ሞተ ሥጋ የማይቀር ነው ከደጅህ መቅረት ግን ከባድ ሞት ነው።
 መጻጉን የፈወሱ እጆችህ፣
 አላዛርን ያነሳ ድምጽህ፣
 ወለተ ኤያኤሮስን ያነሳ ዝምታህ፣
 አጋንንትን ያወጣ ኀይልህ፣
 ድውያንን የፈወሰ ምህረት አይለየን።

መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ መጋቢት 24/2012


2. #የአንድ_ተነሣሂ_ጸሎት፦
በዲያቆን ብርኃኑ አድማስ።

 ጌታ ሆይ ስንበድልህ ኖረናል፤ አሁንም እየበደልንህ ነው፤ በሚታወቀን በድለንሃል እንላለን


እንጂ፦ በማይታወቀን ደግሞ ምን ያህል እንኳ እንደበደልንህ የምታውቀው አንተ ብቻ ነህ፡፡
አሁን ግን ከሁሉም ጊዜ በላይ እየተፈተንን ነውና መውጫውን ስጠን፡፡ እሥራኤል
በመሥዋዕቱ ሳይቀር ሲበድሉህ በኢሳይያስ አድረህ፦ "የመሥዋዕታችሁ ብዛት ለእኔ ምን
ይጠቅመኛል? ይላል እግዚአብሔር፥ የሚቃጠለውን የአውራ በግ መሥዋዕትን እና የፍሪዳን
ስብ ጠግቤያለሁ፤ የበሬና የበግ ጠቦት፥ የአውራ ፍየልም ደም ደስ አያሰኘኝም፤" ኢሳ፡፩፥፲፩።
ብለሃቸዋል። ዳግመኛም፦ "ዓመት በዓላችሁን ጠልቼዋለሁ፥ ተጸይፌውማለሁ፥
የተቀደሰውም ጉባኤያችሁ ደስ አያሰኘኝም፤" አሞ፡፭፥፳፩። ብለህ ካስነገርህ በኋላ፦
መሥዋዕት ወደማይሠዉበት ግዞት አንደላክሃቸው፤ በእኛስ ላይ ይህን ሁሉ ያመጣህብን፥
በቅዳሴያችን በውዳሴያችን ጊዜ በምንፈጽመው ግድፈትና ኃጢአት ይሆንን? በእውነት እኛ
አንተን ያልበደልንበት ቦታና ጊዜ የት አለ? አንዳንዶቻችን አጸደ መቅደስህን ለሌላ ዓላማ
ተቃጠርንበት፤ አንዳዶቻችን ውሰጥ ድረስ ገብተን ተነታረክንበት፥ ተደባደብንበት፤
አንዳንዶቻችን ከአንተ ከምናገኘው ጸጋ ይልቅ መቅደሱ የእኔ ነው፥ የእኔ ነው በማለት ጠበቃ
ይዘን ለዐመታት ተሟገትንበት፡፡ አንዳንዶቻችን በነጠላችን ውስጥ ሆነን ሰለማዊ ሰልፍ
ወጣንበት፡፡ አንዳዶቻችንም ሰው የማያውቃትን ኃጢአት ሠራንበት፡፡
 አንዳንዶቻችንም ሐፍረት ጥለን ቤተ መቅደስህን የፋሽን ውድድር በሚመስል ሁኔታ
ተኵነሰነስንበት፡፡ መቅደስህ ውስጥ ሳይቀር በስልካችን አሽካካንበት። አንዳንዶቻችንም
የውበት ሳሎን አስመሰለነው፡፡ በዝማሬው፥ በልብሱ፥ በስብከቱና በሌላውም አገ ልግሎት
ከአጥቢያ አጥቢያ ተፎካከርንበት፡፡ አገልጋዮችህም ጸጋ ለማካፈል ከሮጥነው ይልቅ ገንዘብ
ለመሰብሰብ የሮጥነው በለጠ፡፡ ለድኅነታቸው ሳይሆን ለገቢያችን ስንል ምእመናንንም
እንደጠፍ ከብት ነዳናቸው። እንደ ምርኮም ተካፈልናቸው፡፡ በአንድ መቅደስ በአራት
በአምስት ጻድቅ ስም ታቦት የምንደራርበውም፦ ሰዉ ወደ ሌላ ቤተ ክርስቲያን እንዳይሄድና
ለእኛ ደብር ብቻ ገንዘቡን እንዲሰጥ ከመፈለግ እንጂ ለበረከት አይደለም። ይህንንም፦ እንኳን
አንተ ልብንና ኩላሊትን የምትመረምረው ቀርቶ፥ አንዳንድ ምእምናንም ታዝበው
በትዕግሥት ትተውናል፡፡ በዐመት ከዐራት እስከ አምስት ታቦት በየምከንያቱ
የምናነግሥበትንም ምክንያት ዛሬ ሁሉም አውቆታል። እንኳን በሌላው ጊዜ፦ በዐቢይ ጾም
እንኳ የምናደርገው ድለቃና ዳንኪራም አንተን ሳይሆን የእኛኑ ስሜት ለማርካት እንደሆነ
ልባችን ያውቀዋል፡፡ እንዲያውም ዝምካልከን፥ ከኮረና ያለፍንበት ብለን አዲስ ንግሥም
ልንጨምር እንችላለን፡፡ አቤቱ ስንቱን ታገሥከን? በዐውደ ምሕረትህ ቆመን፥ በሌላው
መቅደስ የተሰየመውን ካህን እያሽሟጠጥን ስንቱን ተናገርንበት፡፡ ፖለቲካዊ ስሜቶቻችን
ከሌላ ቦታ ይልቅ በቤተ መቅደስህ ተሰበኩ፡፡ ስለአንተ ድኅነትና ጸጋ ከምንናገር ይልቅ፦ እኛ
በግል የወደድናቸውን ያንተ መልእክተኞች እንደሆኑ፥ በግል የጠላናቸውን ደግሞ አንተ
የረግምሃቸው እንደሆኑ አድርገን ስናቀርብ ስቅቅ አይለንም ነበር። ኧረ እንዲያውም አንተ
በጆሯችን ሹክ እያልከን የምንናገር እንመስል ነበር፡፡ በዚህና በመሳሰለው አዝነህብን ይሆን፥
ከቤተ መቅደስ እንደ ቀድሞው የማንሰበሰብበትን ጊዜ ያመጣኸው? በዚህስ ጉዳይ ማነው
አፉን ሞልቶ ሊናገር የሚችል ጻድቅ? ለዘላለም ያልዘጋህብንም በእውነት ቸር ብትሆን ነው፡፡
አዎን ጌታ ሆይ! እንደ በደላችንማ ከሆነ እንኳን ይህን ሌላስ ብታመጣ ይገባን የለምን?
"የእግዚአብሔርን ልጅ የረገጠ፥ ያንንም የተ ቀደሰበትን የኪዳኑን ደም እንደ ርኵስ ነገር
የቆጠረ፥ የጸጋውንም መንፈስ ያክፋፋ፥ እንዴት ይልቅ የሚብስ ቅጣት የሚገባው
ይመስላችኋል?" ዕብ፡፲፥፳፱። ስትል በቅዱስ ጳውሎስ እንደ ነገርከን፥ ለኦሪቱ መሥዋዕት
መርከስ ቀንተህ፦ በእሥራኤል ላይ፦ ለሰበዓ ዐመት ቤተ መቅደስ የማያዩበት፥ መሥዋዕት
የማይሠዉበት፥ ምስጋና የማያቀርቡበት፥ በዓል የማያከብሩበት ስፍራ ፋርስ ባቢሎን
አውርደህ ከቀጣሃቸው፥ እኛንማ አማናዊው የአንተ ሥጋና ደም በሚፈተትበት ቤተ
መቅደስህ፦ ያን ሁሉ ኃጢአት፥ ፌዝና ግደየለሽነት፥ የታይታ፥ የይስሙላና የግብር ይውጣ
አድርገን በምንፈጽመው ነገር ብትቀጣን፥ እንኳን በዚህች ቁንጥጫ መገሠጽ ቀርቶ፥ እንደ
ዳታን እና እንደ አቤሮን እንዳለ ከነሥጋችን ሲኦል እንኳ ብታ ወርደን ቢያንስብን እንጂ መች
ይበዛብናል፡፡
 ነገር ግን ጌታ ሆይ! አንተ መሐሪና ይቅር ባይ ነህና፥ በድፍረት የምናጠፋውን ሳይሆን በፈሪሃ
እግዚአብሔር ሆነው ርደውና ተንቀጥቅጠው የሚያገለግሉህን ጥቂቶቹን አይተህ አኛን
ብዙዎቹን ጥፋተኞች ይቅር በለን፡፡ አዎን ጌታ ሆይ በየዕለቱ መቀደስህን መወዳደሪያና
መፎካከሪያ አድርገነዋል፡፡ መሥዋዕት ማቅረብ አሰልቺና አድካሚ ሥራ የመሰለን አገልጋዮች
እየበዛን እንደመጣን እንኳን አንተ እኛም የምናወቀው ሐቅ ነው፡፡ አንድ ትልቅ ሆቴል ስንገባ
የምናደርገውን ያህል ክብርና ጥንቃቄ ለቤተ መቅደስህ የማንሰጥ መኖራችንም ከአንተ
የተሠወረ አይደለም፡፡ ከምእመናን ብዙዎቹም ንስሐ፥ ዕርቅ፥ ይቅርታና በፈሪሃ እግዚአብሔር
ሆኖ ሥጋህንና ደምህን መቀበል፥ ወደፊት የሚደረስበትና የማያመልጥ የሚመስለን
ሞልተናል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ከካህናትም ቢሆን ምን አስቸኮለህ አርፈህ ቁጭ በል የሚል
አንታታጣም፡፡ ጌታ ሆይ በዚህና በመሳሰሉት ምክንያቶች ቤተ መቅደስህ ተዘግቶ በጸጋ የከበሩ
ብቻ የሚጠቀሙበት ጊዜ ብታመጣ በእውነት የተገባ ነው፤ ነገር ግን ገሥጸን አንጂ አትጣለን፥
ማረን አንጂ አታጥፋን፡፡ አቤቱ ጌታ ሆይ በተለይ እንደ ራሴ ንዝህላልነት ከሆነ ከቤተ
መቅደስህ እንኳን ሳምንታትን ዐመታትን ብት ቀጣኝ እንደማያንሰኝ አውቃለሁ፡፡ ነገር ግን
ጌታ ሆይ እንደ ቸርነትህ ነው እንጂ እንደ በደላችን አታድርግብን። ይልቁን እኔን ከሁሉም
የማንሰውንና በኃጢአት የምበልጠውን ይቅር በለኝ፡፡
 ጌታ ሆይ! እንኳን የሌላው ጊዜ ኃጢአት የሰሞኑ ብቻ በፊትህ ብዙ እንደሆነ አውቃለሁ፡፡
ንትርካችንም ቢበዛ እንጂ አልቀነሰም፡፡ ነገሩን በመንፈስ ዐይን አይተው ለንስሐቸው
የሚፋጠኑትን ሁልጊዜም አታጣምና ሰለእነርሱ ብለህ ይቅር በለን እንጂ እኔና መሰሎቸማ ገና
አሁንም እንሟገታለን፥ አንነቃቀፋለን፥ እንተቻቻለን፡፡ በተለይ እኔማ ሲመክሩኝ የናቁኝ፥
አሳብ ሲሰጡኝም የጠሉኝ እየመሰለኝ ተቸገሬያለሁ። ከዚህም የተ ነሣ፦ ሌሎች ዘንድ
ስሕተት የመሰለ ነገር ፈልጌ በመተቸት፥ ራሴን ነጻ ለማውጣት ብዙ ጥቅሶችን አማትርና
በኋላ ላይ ግን ለድኅነቴ ሳይሆን ለክብሬ መሆኑን ሳስበው በእውነት አፍራለሁ፡፡ እንዲያውም
በቅቶ በተአምራት ቆቅ እየተያዘለት ይመገብ የነበረውን አባ መቃርስን፦ "እንዴት መነኵሴ
ሆኖ ሥጋ ይበላል?" እያሉ ይንቁት እንደ ነበሩት ወጣንያን መነኮሳት፥ በማውቃት ብቻ
ተነሥቼ በማላውቀው ሁሉ የምተቸውን አስቤ ደንግጫለሁና አትቀየመኝ፡፡ ይልቁንም የአባ
መቃርስን ብቃት ገልጸህ እነዚያን ተመካሂ መነኮሳት እንደ ገሠጽካቸውና እንደ መለስካቸው
እኔን እና መሰሎቼንም አንተን ደስ በሚያሰኝ ለእኛም በሚረዳ ገሥጸህ መልሰን እንጂ
አትዘንብን፡፡
 አዎን ጌታ ሆይ! ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ከገዳሙ የተለካለትን ደብዳቤ መሠረት አድርጎ "አንተ እኮ
አንደ ቀዳማይ ኤልያስ ነህ ሲሉ ገልጸውልኛል፤ "ሲለው፥" ንጉሥ ሆይ! ለኤልያስ ምግቡን
የሚያመጡለት ቁራዎች ነበሩ፥ እኔ ግን ምግቤን ባሰጣው ቁራ ይወስድብኛል፤ "ሲል በትሕትና
እንደተናገረው፥ እንደ ገዳማዊው አባ ኤልያስ ዘገዳመ ሲሐት፦ በትሑታን ትደሰታለህና እንደ
እርሱ ያሉትን አይተህ ባለማወቅና በትንሽ ዕውቀት የምንወዛገበውን ይቅር በለን፡፡ ጌታ ሆይ
እኛም ብንሆን እንጥቀም ብለን እንጂ እንጉዳ ብለን አይደለምና አትቀየመን፡፡
 ጌታ ሆይ! አንተን ከልብ የሚያመልኩትን ባሉበት እንደምታከብር፥ ከልብ የተመለሱትንም
ለንስሐ ጊዜ ሰጥተህ የናቁትን ሲያከብሩ፣ ቸለል ያሉትን ውድነቱን ሲያውቁ፣ በበደሉት
ሲጸጸቱ፣ ከልብ እንዲሹት አድርገህ እንደምታበቃቸው ሰምቻለሁና እኔንም ከእነርሱ
ደምረኝ፡፡ ለበቁትና በእውነት አንተን ለሚያመልኩህ፥ በድፍረት ከሚቆርቡት በዕደ መላእክት
በእሳት ጉጠት እየነጠቅህ በወደቁበት በረሀ እና ዋሻ እንደምታቆርባቸው ሰምቻለሁ፡፡
በመሆኑም በእነርሱ ላይ የተዘጋም የሚዘጋም ቤተ መቅደስ እንደሌለ አውቃለሁ። ለእኔ
ለበደለኛው ግን አስብልኝ፥ እዘንልኝ፡፡
ዳንኤልን አንበሶች እንዳጫወቱት፥ ለአቡነ አረጋዊ ዘንዶው እንደ ታዘዘ፥ ለሌሎቹም ቅዱሳን
ብዙ አራዊት እንደታዘዙ ሰምቼ ራሴን ሳልመረምር በተመካሁበት ይቅር በለኝ እንጂ
አትቀየመኝ፡፡ እኔ እምነት አለኝ በዬ ቤቴን እንኳ ከፍቼ አልተኛም፡፡ እንኳን አንበሳ
ሊያጫውተኝ ያሳደግሁት ውሻም አንዳንድ ቀን ይነክሰኛል፡፡ ይህም ሆኖ ግን በአለማወቅ
ከመናገርና በማደርገው ከመመጻደቅ አልተመለስኩም፡፡ ይህም ሁሉ ወደ ልቡናዬ ባለመመለሴ
ነውና ጥፋቴን ሳይሆን ቅናቴን፥ ስሕተቴን ሳይሆን በመሳትም ቢሆን ከሰማሁት ተነሥቼ
በአቅሜ በጎ ነው ብዬ መመኘቴን አይተህ ይቅር በለኝ እንጂ፦ እንደ ፈሪሳዊው ቀራጩ ከአንተ
ይሻላል ብለህ አታሳፍረኝ፡፡ እንደሚሻል አሁን ስያዝ አስታውሻለሁ፥ ከእኔ ያልተሻለ
እንደሌለም ተረድቻለሁ፥ ስለዚህ ይቅር በለኝ፡፡
 አዎን ጌታ ሆይ! ቤተ መቅደስህን የዘጋሁትም እኔ እንደሆንኩ አውቃለሁ፡፡ ጊዜውም ቀደም
ብሎ እንደሆነ አስታውሳለሁ፡፡ ቤተክርስቲያንህ ግቢ ውስጥ ቁጭ ብዬ በልቤ ከቢሮዬ ስገባ
አስታውሳለሁ፡፡ ሠራዊተ መላአክቲሁ ለመድኃኔ ዓለም፥ ይቀውሙ ቅድሜሁ ለመድኃኔ ዓለም
እየተባለ፥ እኔ ግን በልቤ ከቤትህ ወጥቼ ከጓደኞቼ ጋር ከተማ ካለ ምግብ ቤት ስገባ
አስታውሳለሁ፡፡ አንዳንድ ጊዜም በኅሊናየ ተስቤ ወጥቼ ስከብር ስምነሸነሽ፥ ሌላ ጊዜ ደግሞ
ስሾም ስዘማነን፥ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የተቀየምኩትን ስቀጣ ሳስቀጣ፥ ሌላ ጊዜ ስማር
ስመራመር፥ ስበርና ስከንፍ እውል እንደ ነበር ትዝ ይለኛል፡፡ ስግዱ ላይ ሰግጄ በአሳብ ሌላ ቦታ
ስባክን በሰው ተቀስቅሼ የተነሣሁበትንም አልረሳውም፡፡ ተስጥኦ እየተቀበልኩ ከመወሰዴ
የተነሣ በእግዚኦ ተሣሃለነ ፈንታ ምስለ መንፈስከ እያልኩ እስኪ መልሱልኝ ድረስ
እንደምቸገር አልዘነጋውም፡፡ ስለዚህ ጌታ ሆይ ከቤተ መቅደስ ሥጋየን አቁሜ ስባዝንብህ ጊዜ
ነው መሰል፥ የሥጋየ ማጎሪያ ብቻ ማድረጌን አይተህ በመንፈስ እስክመለስ ድረስ መቅደስህን
ብትዘጋብኝ የሚበዛብኝ አይደለሁም።
 ነገር ግን ጌታ ሆይ! አንደወጣሁ አታስቀረኝ፥ እባክህን ከእነ ጠፋው ልቡናየ መልሰኝ፡፡ ለምን
ተዘጋ? የምለውም ተጨንቄ አንጂ ይገባኛል(ይደልወኒ) ብዬ አይደለምና እባክህን ጌታ ሆይ!
በፈሪሃ እግዚአብሔር እንድመለስበት እርዳኝ፡፡ ያን የጠፋውን በግ እንደተሸከምከው እኔንም
ተሸክመህ መልሰኝ እንጂ አትተወኝ፡፡ ያን ጊዜ በዋዛ በፈዛዛ ማሳለፌን ረስቼው ዛሬ አንደዋዛ
መግባት ሲሳነኝ ፈራሁ፥ ደነገጥሁም፡፡ ትችቴን እና ነቀፋየንም የመጨነቅና ወደ አንተ
የመቅረብ ብቻ አድርገህ ውሰድልኝ እንጂ ጌታ ሆይ አትቀየመኝ፡፡ አቤቱ ወደ ቤተ መቅደስህ
እንደ ዳዊት በደስታ የምመጣበትን ቀን አቅርብልኝ፡፡
 አውቃለሁ ጌታ ሆይ! ቅዳሴውን ረዘመ፥ አገልግሎቱንም በዛ እያልኩ እተች ነበር፡፡
የይስሙላውን ቁመቴን አድርሼ ለሌሎች ጉዳዮች ልቤ ክንፍ አውጥቶ ይበርር ነበር፡፡ ዛሬ ግን
ሁሉንም እንዳቆመውና ወደ አንተ እንዳይ ስትጠራኝ ምን ያህል ጊዜ እንደበደልኩህ ሳስብ
መቁጠር አቃተኝና ደነገጥኩኝ፡፡
 ጌታ ሆይ! በቤት መቅደስህ ውስጥ ቆሜ በዓለም ካሉት ይልቅ መበደሌን አውቄያለሁ። አቤቱ
ጌታ ሆይ! መዓትህን በምሕረትህ፥ ቁጣህንም በትዕግሥትህ መልሰህ፥ ለነፍሴም ትዕግሥትንና
ማስተዋልን ሰጥተህ፥ በማላውቀውና በማይመለከተኝ ሁሉ ከምእመን እስከ ጳጳስ
ከሚያስተቸኝ መንፈስ ነጻ አውጥተህ፥ እንደ መበለቲቱ ሐና ከቤተ መቅደስህ እንዳልለይ
እርዳኝ፡፡
 ጌታ ሆይ! በልቤ የዘጋሁብህን መቅደስ በእርዳታህ ክፈትልኝና ከምሥጢራት ለምካፈልበት
መቅደስህ አብቃኝ፡፡ አቤቱ ጌታ ሆይ! ይህንንም የፈሪሳዊ ጸሎት አድርገህ አትጸየፍብኝ፡፡
ፈሪሳዊ መሆኔን አውቄ ለምኝሃለሁና። ለእኔ ዐይነቱም ቢሆን ምሕረትህ እንደማይከለከል
ሰምቻለሁና። አቤቱ ፈጥነህ ማረን፥ ይቅር በለንም፥ አሜን፡፡
3. #ሆሣዕና

 የሰሞነ ሕማማት የመጀመሪያው ቀን ሆሣዕና ይባላል። ትርጉሙም ‹‹እባክህ አሁን አድን


አንድም መድኃኒት›› ማለት ነው፡፡
 በዚህ ዕለት ጌታችን የማዳን ሥራውን ወደሚፈጽምባት ወደ ኢየሩሳሌም ገባ፡፡ ቤተ ፋጌ
ሲደርስ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከደቀ መዛሙርቱ ሁለቱን ልኮ
‹‹ያስፈልጉኛልና የታሠሩትን አህያና ውርንጫ ይዛችሁልኝ ኑ፡፡›› ብሎ ላካቸው፡፡
በምስጢሩም የአዳምን ልጆች ከዲያብሎስ ቁራኝነት ሊፈታ እንደ መጣ ለማጠየቅ ነው፡፡
እነርሱም እንደታዘዙት መጡ፤ ከኢየሩሳሌም እስከ ቤተ መቅደስ 16 ምዕራፍ ሲሆን 14 ቱን
በእግሩ፣ 2 ቱን በአህያ ሄዶ፣ ቤተ መቅደሱን 3 ጊዜ በውርንጫላዋ ከዞረ በኋላ ወደ ቤተ
መቅደስ ገባ፡፡
 ቀድሞ በነቢያት ዘመን ጸብዕ (ጥል) በሆነ ጊዜ በፈረስ ተቀምጠው የጦር ዕቃ ይዘው ይታዩ
ነበር፤ ዘመነ ሰላም በሆነ ጊዜ ደግሞ በአህያ ተቀምጠው መነሳንስ ይዘው ይታያሉ፤ እርሱም
‹‹ዘመነ ሰላም ይዤላችሁ›› መጣሁ ሲል በአህያ ተቀምጦ መጣ፡፡ (ስለ ሰላምሽ የሚሆነውን
አንቺስ ብታውቂ … /ሉቃ. 19፥24/) ፡፡ ነቢዩ ዘካርያስም በትንቢቱ በአህያ እንደሚመጣ
ተናግሮ ነበር /ዘካ. 9፥9/፡፡
 በግራና በቀኝ የነበሩትም ‹‹እንኳን አንተ የተቀመጥክባትም አህያ መሬት መርገጥ
አይገባትም›› እያሉ ግማሹ ልብሱን ግማሹ የዘንባባ ዝንጣፊ አነጠፉለት፡፡ አብርሃም
ይስሐቅን፣ ይስሐቅ ደግሞ ያዕቆብን በወለዱ ጊዜ፣ እስራኤል ከግብጽ በወጡ ጊዜ፣ ዮዲት
ሆሎፎርኒስን በገደለች ጊዜ ዘንባባ ይዘው አመስግነው ነበር፤ በዚያ ልማድ ጌታችንንም
ዘንባባ ይዘው ‹‹ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ የተባረከ ነው ሆሣዕና
በአርያም›› እያሉ አመሰገኑት፡፡
 ከዚህ በኋላ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ በዚያ ይሸጡ ይለውጡ የነበሩትን ‹‹ቤቴ የጸሎት ቤት
ይባላል፤ እናንተ ግን የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችሁት›› ብሎ በመቆጣት የለዋጮችን ገበታ
እየገለበጠ አስወጣቸው፡፡ አይሁድም ሕፃናት ሲያመሰግኑ ሰምተው በቅንአት በታወረ
ልቦናቸው ‹‹ዝም አስብላቸው እንጂ›› አሉት፡፡ ጌታችንም ‹‹ከሕፃናትና ከሚጠቡ አፍ
ምስጋና ለራስህ አዘጋጀህ›› /መዝ. 8፥2/ የሚለውን የመጽሐፍ ቃል ጠቅሶ አሳፍሯቸዋል፡፡
በሌላም አንቀጽ እነሱ ዝም ቢሉ ድንጋዮች ሲያመሰግኑ አይተው አፍረዋል፡፡ ይህ በዓል
ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘጠኙ ዓበይት በዓላት መካከል አንዱ ነው፡፡
4. #የሰሙነ_ሕማማት_ዕለታት_ስያሜዎች

 እሑድ፦ የሰሞነ ሕማማት የመጀመሪያው ቀን ሆሣዕና ይባላል። ትርጉሙም ‹‹እባክህ አሁን


አድን አንድም መድኃኒት›› ማለት ነው፡፡
 ሰኞ፦ መርገመ በለስ የተፈጸመበት፣ አንጽሖተ ቤተ መቅዳስ የተፈጸመበት
 ማግሰኞ፦ የጥያቄና የትምህርት ቀን::
 ረቡዕ፣- ምክረ አይሁድ፣ የዕንባ ቀን፣ የመልካም መዓዛ ቀን::
 ሐሙስ፦ ጸሎተ ሐሙስ፥ ሕጽበተ ሐሙስ፥ የምሥጢር ሐሙስ፥ የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ፥
የነጻነት ሐሙስ::
 ዐርብ፦ የስቅለት ዐርብ::
 ቅዳሜ፦ ቀዳም ሥዑር (ሹር ቅዳሜ)፤ ለምለሚቱ ቅዳሜ፥ ገብረ ሰላመ በመስቀሉ፥ ሰንበት
ዐባይ፥ ቅዱስ ቅዳሜ፡፡
5. ሥርዐተ_ጸሎት_ወስግደት_ዘሰሙነ_ሕማማት፡፡

 በሰሙነ ሕማማት የሚባሉትን በአጭሩ ስንቃኛቸው፡፡


 የሰሙነ ሕማማት ጸሎት የሚደረገው በ 7 ቱ የጸሎት ጊዜያት መሠረትነት 7 ት ጊዜ ነው፡፡
 ለዚሁ አገልግሎት ታላቁ ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በ 7 ቱ ጊዜያት ከፋፍሎ የደረሰው
መልክአ ሕማማትም አብሮ በዜማ ይደርሳል፡፡
 ደወልና ቃጭል ይመታል፤
 ጸሎታት(ሙሉ ውዳሴ ማርያምና ዳዊት)ና (የኦሪትና የነቢያት) ምንባባት ይደርሳል፤
 የተአምር መቅድምና ምንባብ ይነበባል፤ የተአምራት መርገፍ በዜማ ይባላል፡፡
 የወንጌል አቡን በቅብብሎሽ ይደርሳል፤
 ምስባክ ይሰበካል ፥ ወንጌል ይነበባል፡፡
#1 ኛ_ስግደት፤ ‹‹ጸልዩ በእንተ ጽንዐ ዛቲ›› እያለ ቃጭል ሲያሰማ 22 ት ጊዜ ‹‹እግዚኦ
ተሣሃለነ›› እየተባለ ይሰገዳል፡፡
#2 ኛ_ስግደት፤ ‹‹ለከ ኀይል ክብር ወስብሐት›› የሚለውን በቅብብሎሽ 6 ት ፥ 6 ት ጊዜ
(በድምሩ 12) ፤ 7 ኛውን በኅብረት እየተሰገደ ይባላል፡፡
#3 ኛ_ስግደት፤ ‹‹ለአምላክ ይደሉ›› የሚለውን 1 ኛውን ዙር በቅብሎሽ፤ 2 ኛውን ዙር
እያስተዛዘሉ፤ ከስግደት ጋራ ይባላል፡፡
#4 ኛ_ስግደት፤ ‹‹ክርስቶስ አምላክነ…›› የሚለውን በመሪና ‹‹ንሰብሖ.›› ወናልዕል ስሞ
የሚለውን በቅብብሎሽ ብለው በዚያው ቀጥለው፤ ‹‹ኪራያላይሶን፥ ኪራያላይሶን፥
ኪራያላይሶን›› የሚለውን በመሪ 21 ጊዜ፤ በተመሪ 20 ጊዜ (በድምሩ 41 ጊዜ) እየተሰገደ
ይደርሳል፡፡
 የየሰዓቱን (የሌሊት፣ የነግህ፣ የጠዋት 3 ሰዐት፣ የቀትር/6 ሰዐት/፣ የተሰዐት/9 ኝ ሰዐት/፣
የሰርክ /11 ሰዐት/፣ የንዋም) መልክአ ሕማማት በዜማ ይደርሳል፡፡
 ካህኑ ቡራኬ ሰጥቶ፤ ዲያቆኑ ደግሞ ‹‹ሑር በሰላም›› ብሎ ሕዝቡን ያሰናብታል፡፡
6. #መልክአ_ሕማማት፤

 መልክአ ሕማማት ማለት ስለ ጌታችን መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ሕማም፥ መከራ፥ ስቃይ፥
የሚናገር መጽሐፍ ሲሆን፤ ደራሲው ታላቁ ሊቅና የደብረ ባሕርይ ጋሥጫ
መምህር #አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫ_ ነው፡፡
 መልክአ ሕማማት በባለ 3 ት መስመር አርኬ የተደረሰ ግጥማዊ ድርሰት ሲሆን፤
የተደረሰውም በ 7 ቱ የጸሎት ጊዜያት አንጻር በመሆኑ ‹‹#ጸሎት_ዘሰባዐቱ_ጊዜያት›› በሚል
መጠሪያም ይጠራል፡፡
 የእያንዳንዱ ጊዜ ድርሰትም በዋነኛነት 3 ት ክፍሎችን የያዘ ነው።
እነርሱም፤ 1 ኛ) ስብሐተ እግዝእትነ ማርያም /የእመቤታችን ምስጋና/
2 ኛ) ስበሐተ ኢየሱስ ክርስቶስ /የኢየሱስ ክርስቶስ ምስጋና/
3 ኛ) ስብሐተ ሥሉስ ቅዱስ /የሥሉስ ቅዱስ ምስጋና/
 በ 7 ቱ ጊዜያት ጸሎት ማድረስ እንደሚገባን ቅዱስ ዳዊት በመዝሙር 118 ላይ ‹‹ሰባት ጊዜ
በቀን አመሰግንሃለሁ ይላል››፤ አባቶቻችን ሐዋርያትም ይህንኑ ደንግገዋል፡፡ /ዲድስቅልያ
37፣ ቀሌምንጦስ 1 ና 7፣ አቡሊዲስ 25 ኛና 27 ኛ፣ ባስልዮስ 28 ኛ አንቀጽ፣ ፍትሐ ነገሥት
ገጽ 21/፡፡
 ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ መልክአ ሕማማትን ሲደርስም በ 7 ቱ የጸሎት ጊዜያት
የተፈጸሙትን ድጊቶች ከ 3 ቱ የየጊዜያቱ የድርሰቱ ክፍሎች ምስጋና (የማርያም፣ የጌታ፣
የሥሉስ ቅዱስ ምስጋና) ጋር እያመሠጠረና እያራቀቀ፥ እያስዋበና ምሥጢር እያመጣ፤
እንደ ወርቅ እያንከባለለ፥ እንደ ሸማ እየጠቀለለ፥ በግጥም እያስጌጠ፥ በቃላት እየሰደረ፥
በዜማ እያሸበረቀ፥ መንፈስን እየመሰጠ፤ ነው የደረሰው፡፡
7. #የ 7 ቱ_የጸሎት_ጊዜያት_የሚባሉትም

 1 ኛ) መንፈቀ ሌሊት (ሌሊት 6 ሰዐት)፤ ጌታችን የተወለደበት፥ የተጠመቀበት፥


የተነሣበትና ዳግመኛ የሚመጣበት ፥ … ሰዐት ነው፡፡
 2 ኛ) ነግህ (ማለዳ፥ ጧት)፤ ጨለማን አርቆ ብርሃንን የሚያመጣበት፥ አባታችን ቅዱስ
አዳም የተፈጠረበት፥ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በጲላጦስ አደባባይ ፊት ቁሞ
የተመረመረበት፥ …. ሰዐት ነው፡፡
 3 ኛ) ሠለስት (ጠዋት ሦስት ሰዐት)፤ እናታችን ሔዋን የተፈጠረችበት፥ ነቢዩ ዳንኤል
ጸሎት ያደረሰበት፥ እመቤታችን ከቅዱስ ገብርኤል ብሥራትን ሰምታ የጸነሰችበት፥ መድኀኔ
ዓለም ክርስቶስ ለኛ ሲል በጲላጦስ አደባባይ የተገረፈበት፥ ….. ሰዐት ነው፡፡
 4 ኛ) ቀትር (6 ሰዐት)፤ አጋንንት የሚሰለጥኑበት ሰዐት ስለሆነ እንዳይሰለጥኑብን፥ አዳም
ዕፀ በለስን በልቶ የሳተበት ስለሆነ እንዳንስት እንጸልያለን፡፡ በተጨማሪም ነቢዩ ሄኖክ ቤተ
መቅደስን ያጠነበት፥ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ ለኛ ሲል በመስቀል ላይ የተሰቀለበት፥ …..
ሰዐት ነው፡፡
 5 ኛ) ተስዓት (ዘጠኝ ሰዐት)፤ ቅዱስ ጴጥሮስና ዮሐንስ ለጸሎት ወደ ቤተ መቅደስ
የወጡበት፥ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በፈቃዱ ነፍሱን ከሥጋው የለየበት፥ ….. ሰዐት ነው፡፡
 6 ኛ) ሠርክ (ዐሥራ አንድ ሰዐት)፤ ነቢዩ ኤልያስ መሥዋዕት የሰዋበት፥ ዕዝራ ጸሎትን
ያቀረበበት፥ ሕዝቅያስ ጸልዮ ፀሐይን ወደ ዐሥር ደረጃዎች የመለሰበት፥ መድኀኔ ዓለም
ክርስቶስ ወደ በፈቃዱ ወደ አዲስ መቃብር የወረደበት፥ …… ሰዐት ነው፡፡
 7 ኛ) ንዋም (የመኝታ ሰዐት)፤ መድኀኔ ዓለም ክርስቶስ በጌቴሴማኒ የጸሎትን ሥርዐት
ያስተማረበት ፥ እንዲሁም ሌሊቱን በመላእክት ጥበቃ ከርኵሳን አጋንንት እንዲጠብቀን
የምንጸለይበት …… ሰዐት ነው፡፡
 #ለቡ(ልዩ ማስታወሻ)!! ይህ ታላቅ ጸሎት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
ስር ባሉ በሁሉም ገዳማትና አድባራት በሰሙነ ሕማማት የሚደርስ ሲሆን፤ በአንዳንድ
ትላልቅ ገዳማት (እንደ ዋልድባ፣ ማኅበረ ሥላሴ፣ ደብረ ባሕርይ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ
ወደብረ ጎል አቡነ በጸሎተ ሚካኤል) ያሉ መነኰሳትና መናንያን ግን ከዓመት እስከ ዓመት
ጸሎቱን በዜማ /በንባብ/ ያደርሱታል፡፡

8. ፬ቱ #ስግደታት

(በሰሙነ ሕማማት በ፯ቱ ጊዜያት የሚሰገድባቸው


(#ሥርዐተ_ጸሎት_ወስግደት_ዘሰሙነ_ሕማማት፡፡)

 የሰሙነ ሕማማት ጸሎት የሚደረገው በ 7 ቱ የጸሎት ጊዜያት መሠረትነት 7 ት ጊዜ ነው፤


 በ 7 ቱ ጊዜያትም 4 ት ስገደታት አሉ፡፡ ለዚሁ አገልግሎት ታላቁ ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ
በ 7 ቱ ጊዜያት ከፋፍሎ የደረሰው መልክአ ሕማማትም አብሮ በዜማ ይደርሳል፡፡
 ደወልና ቃጭል ይመታል፤
 ጸሎታት(ሙሉ ውዳሴ ማርያምና ዳዊት)ና (የኦሪትና የነቢያት) ምንባባት ይደርሳል፤
 የተአምር መቅድምና ምንባብ ይነበባል፤ የተአምራት መርገፍ በዜማ ይባላል፡፡
 የወንጌል አቡን በቅብብሎሽ ይደርሳል፤
 ምስባክ ይሰበካል ፥ ወንጌል ይነበባል፡፡
#፬ቱ #ስግደታት የምንላቸውም (እየሰገድን የምንላቸውም) ቃላት፡፡

 ፩ኛ ስግደት፤ የወንጌል ምንባብ እንዳበቃ በማስከተል ተግሣጽ ተነቦ እንደተፈጸመ፤


‹‹ጸልዩ_በእንተ_ጽንዐ_ዛቲ_መካን›› የሚለውን ካህኑ ሲመራና ዲያቆኑ በየምዕራፉ
ቃጭል ሲደውል፤ ሕዝቡ_እየተቀበሉ_እግዚኦ_ተሣሀለነ (አቤቱ ይቅር በለን)
በማለት ፳፪ት ጊዜ በግእዝ፥ በዕዝልና በአራራይ ዜማ እየተዜመ ይሰገዳል፡፡
 ፪ኛ #ስግደት፤ በመቀጠል ‹‹#ለከ_ኃይል_ክብር_ወስብሐት›› የሚለውን ምቅናይ
በመሪና በአንሺ ወገን መቀባበል ፮ት ፮ት ጊዜ (በድምሩ ፲፪ ጊዜ) ይበሉ፤
በመጨረሻም በ፲፫ኛው ከ‹‹ለከ ኃይል›› እስከ ‹‹ዕብል በአኰቴት›› ድረስ አንድ ጊዜ
በኅብረት ይበሉ፡፡ /ከሆሳዕና ሠርክ እስከ ሰኞ ሰርክ መሪ በቀኝ፤ ተመሪ በግራ
ሲሆን፡፡ ከማክሰኞ ሠርክ ጀምሮ ግን መሪ የነበረው ተመሪ፤ ተመሪ የነበረው መሪ
ይሆናል፡፡/እንዲህእያሉይበሉ፤

 ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ለዓለም፤


 አማኑኤል አምላኪየ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፤
 ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለከ ኃይል ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ
ለዓለም፤
 ኃይልየ ወፀወንየ ውእቱ እግዚእየ፤ እስመ ኮንከኒ ረዳእየ እብል በአኰቴት፤
 አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ፥ ትምጻእ መንግሥትከ፥ ወይኩን
ፈቃድከ፥ በከመ በሰማይ ከማሁ በምድር፥ ሲሳየነ ዘለለዕለትነ፥ ሀበነ ዮም፥
ኅድግ ለነ፥ አበሳነ ወጌጋየነ፥ ከመ ንህነኒ ንኅድግ፥ ለዘአበሰ ለነ፥ ኢታብአነ፥
እግዚኦ ውስተ መንሱት፥ አላ አድኅነነ፥ ወባልሐነ፥ እምኵሉ እኩይ፥ እስመ
ዚአከ፥ ይእቲ መንግሥት፥ ኃይል ወስብሐት ለዓለመ ዓለም።
 ፫ኛ  ስግደት፤ በመቀጠል ‹‹ለአምላክ_ይደሉ››ን መጀመሪያ በመሪ እየቀደሙ በአንሺ
እየተከተሉ አንድ ጊዜ ይዝለቁ፤ በ፪ኛው ክፍል ደግሞ እያስተዛዘሉ ፩ድ ጊዜ ይበሉ፡፡
እንዲህ እያሉ ይበሉ፤

 ለአምላክ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡


 ለሥሉስ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
 ለማሕየዊ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
 ለዕበዩ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
 ለዕዘዙ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
 ለመንግሥቱ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
 ለሥልጣኑ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
 ለምኵናኑ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
 ለኢየሱስ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
 ለክርስቶስ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
 ለሕማሙ ይደሉ፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
 ለመስቀሉ ይደሉ (ለዐርብ ብቻ)፤ ክብር ወስብሐት ወዕዘዝ እስከ ዓለም፡፡
ቀጥሎ ያለውን የመዝጊያ ጸሎት እያዜሙና እየሰገዱ ፫ት ጊዜ መላልሰው ይዝለቁት፡፡
 ለከ ይደሉ ኃይል፥ ወለከ ይደሉ ስብሐት፥ ወለከ ይደሉ አኰቴት፥
 ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለመ ዓለም፡፡
 ፬ኛ  ስግደት፤ ዜማው አሁንም በቀኝና በግራ በመቀባበል ነው የሚባለው፡፡ በመሪ ወገን
እየቀደሙ፤ በአንሺ ወገን ደግሞ እየተከተሉ ፩ድ ጊዜ ይዝለቁ፤ ቀጥለውም በመሪና
በተመሪ ወገን እያስተዛዘሉ ፩ድ ጊዜ ይዝለቁ፡፡
 መሪ፤ ክርስቶስ አምላክነ፥ ዘመጽአ ወሐመ በእንቲአነ፥ በሕማማቲሁ
ቤዘወነ፤
 ተመሪ፤ ንሰብሖ፥ ወናልዕል ስሞ ኅቡረ፥ እስመ ውእቱ ገብረ መድኃኒተ
በብዝኀ (በዕበየ) ሣህሉ፡፡ /በዐርብ፤ ዘሐመ ወሞተ በእንቲአነ/
 ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፤ #ኪርያላይሶን; ኪርያላይሶን፥ኪርያላይሶን
 ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፣ #እብኖዲ ናይናን/ናይን/፥ኪርያላይሶን፤
 ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፣ #ታኦስ ናይናን/ናይን/፥ኪርያላይሶን፤
 ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፣ #ማስያስ ናይናን/ናይን/፥ኪርያላይሶን፤
 ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፣ #ኢየሱስ ናይናን/ናይን/፥ኪርያላይሶን፤
 ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፣ #ክርስቶስ ናይናን/ናይን/፥ኪርያላይሶን፤
 ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፣ #አማኑኤል ናይናን/ናይን/፥ኪርያላይሶን
 ኪርያላይሶን፤ኪርያላይሶን፣ #ትስቡጣ  ናይናን/ናይን/፥ ኪርያላይሶን፡፡
ኪርያላይሶን የሚለውን ብቻ በመሪ ፳፩ ጊዜ፥ በተመሪ ወገን ፳ ጊዜ ይበሉ፤ ድምሩ ፵፩ ኪርያላይሶን
ይኾናል::
 የየሰዓቱን (የሌሊት፣ የነግህ፣ የጠዋት 3 ሰዐት፣ የቀትር/6 ሰዐት/፣
የተሰዐት/9 ኝ ሰዐት/፣ የሰርክ /11 ሰዐት/፣ የንዋም) መልክአ ሕማማት
በዜማ ይደርሳል፡፡
 ካህኑ ቡራኬ ሰጥቶ፤ ዲያቆኑ ደግሞ ‹‹ሑሩ በሰላም›› ብሎ ሕዝቡን
ያሰናብታል፡፡
9. #ሰሙነ_ሕማማት

 ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ሰሙነ ሕማማት የጾመ ሁዳዴ የመጨረሻው ሳምንት፤ የጌታችን
የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሕማም የሚታሰብበት፤ ካህናትና ምእመናን በአጸደ
ቤተክርስቲያን ተሰብስበው የሕማሙን ነገር የሚያወሳውን ዜማ የሚያዜሙበት፤ ግብረ
ሕማም በመባል የሚታወቀውን መጽፍ የሚያነቡበትና የሚሰሙበት፤ በነግህ፣ በሠልስት፣
በስድስት፣ በተሰዓት /ዘጠኝ /ሰዓት፣ በሰርክ /በዐስራ አንድ/ ሰዓት እየመላለሱ
የሚሰግዱበትና የሚጸለዩበት ልዩ ሳምንት ነው ከሆሳዕና ማግስት እስከ ትንሳኤ። በዚህ
ሳምንት በተለይ ካህናት ጥቁር ልብስ ይለብሳሉ ምክንያቱም ጌታችን የደረሰበትን መከራና
ስቃይ እንዲሁም የሰው ልጅ ፭ ሺ ፭ መቶ ዘመን በጨለማ ግዞት ይኖር እንደነበር
ለማዘከርም ጭምር ነው። የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መከራና ሕማም
በጽኑ እንድናስበው ያስተማሩን ሐዋርያት ናቸው። ለእነርሱም የነገራቸው ደግሞ ራሱ
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ሰሙነ ሕማማት የጌታችንን ሕማማት
ከማሰብ ጋር በየዕለቱ በርካታ ድርጊቶች መፈጸማቸውን የምናስታውስበት ሳምንት ነው፦
የሰሙነ ሕማማት ሥርዓቶች

 የሰሙነ ሕማማት ዜማ፥ ከሰኞ እስከ ረቡዕ – ግዕዝ፣ ሐሙስ – አራራይ፣ ዓርብና


ቅዳሜ – ዕዝል ነው፡፡
 በእነኚኽ ዕለታት፣ ከኹሉም በፊት የሠዓቱ ተረኛ አገልጋይ ቃጭል እየመታ ሦስት ጊዜ ቤተ
ክርስቲያኑን ይዞራል፡፡
 የሰባት ቀን ውዳሴ ማርያም፣ አንቀጸ ብርሃን፣ መዝሙረ ዳዊት በሙሉ ይጸለያል፤ በዕለቱ
ተረኛ መምህር/መሪጌታ/ የዕለቱ ድጓ ይቃኛል፡፡
 ድጓው ከአራቱ ወንጌላት ምንባብ ጋራ እንዲስማማ ኾኖ ነው የሚቃኘው፡፡ ድጓውን
እየተቀባበሉ እያዜሙ ይሰግዳሉ፡፡
 ድጓው ሦስት ጊዜ ተመላልሶ ከተዘለቀ በኋላ፡–
 ለከ ኀይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም
 ዐማኑኤል አምላኪየ ለከ ኀይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም
 ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ ለከ ኀይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለም፤
 ኀይልየ ወጸወንየ ውእቱ እግዚእየ እስመ ኮንከኒ ረዳዕየ እብል በአኮቴት
 እየተባለ፣ በቀኝ በኩል ስድስት፣ በግራ በኩል ስድስት ጊዜ እየተዜመ ይሰገዳል፡፡ በድምሩ ዐሥራ
ኹለት ጊዜ ማለት ነው፡፡ በዚያው ልክ አቡነ ዘበሰማያት በዜማ /በንባብ/ ይደገማል፡፡
 ከዚያ በመቀጠል፡–
 ለአምላክ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም
 ለሥሉስ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም
 ለእዘዙ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስከ ለዓለመ ዓለም
 ለመንግሥቱ፣ ለሥልጣኑ፣ ለምኩናኑ፣ ለኢየሱስ፣ ለክርስቶስ፣ ለሕማሙ /በዓርብ
ለመስቀሉ/ ይደሉ
 እያሉ በቀኝ በግራ እየተቀባበሉ ይሰግዳሉ።
 በመቀጠል የነግሁ ምንባብ መነበብ ይጀምራል።
 በመጨረሻ ተኣምረ ማርያም እና ተኣምረ ኢየሱስ ይነበባሉ፡፡
 ከዚያ ከዳዊት መዝሙር ምስባክ ተሰብኮ የሰዓቱ ወንጌል ከተነበበ በኋላ፣
 ጸልዩ በእንተ ጽንዓ ዛቲ የተባለው ጸሎት በካህኑ ሲነበብ፣ ምእመናንም፣ አቤቱ ይቅር በለን፤
እያሉ በመስገድ ይጸልያሉ፡፡
 ከዚያም ኹለተኛው ሥርዓተ ስግደት ይጀመራል። ዜማውን በቀኝ በግራ በመቀባበል፣ አንዱ
ይመራል ሌላው ይቀበላል፡፡ እንዲኽ በማለት፡–
 ኪርያላይሶን/አምስት ጊዜ/ በመሪ በኩል
 ኪርያላይሶን/ሁለት ጊዜ/ ዕብኖዲ ናይን በተመሪ በኩል
 ኪርያላይሶን ታኦስ ናይን
 ኪርያላይሶን ማስያስ ናይን
 ኪርያላይሶን ኢየሱስ ናይን
 ኪርያላይሶን ክርስቶስ ናይን
 ኪርያላይሶን ዐማኑኤል ናይን
 ኪርያላይሶን ትስቡጣ ናይን
 በዚኽ መልኩ አንድ ጊዜ ከተዘለቀ በኋላ እንደገና ይደገማል፡፡ በመጨረሻ በግራ በቀኝ
በማስተዛዘል 41 ጊዜ ይደገማል፡፡ ከላይ የተጠቀሱት፣ የጌታችን ኅቡእ ስሞች ናቸው፡፡
ኪርያላይሶን ማለት አቤቱ ይቅር በለን ማለት ነው፡፡ ምንባባቱ ከመለያየታቸው በቀር
በኹሉም ዕለታት ሥርዓቱ ተመሳሳይ ነው፡፡
 በሰሙነ ሕማማት ያለው ዐርብ፣ የስቅለት ዐርብ ይባላል፤ የአዳምን ነጻነት ለመመለስ ዕዳ
በደሉን ተሸክሞ የተንገላታው የዓለሙ ኹሉ መድኃኒት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛ ኾኖ
በመልዕልተ መስቀል ላይ የተሰቀለበት ነው፡፡ ስቅለት፣ ከዘጠኙ የጌታችን ዐበይት በዓላት አንዱ
ሲኾን፣ የጌታን የመከራውንና የሕማሙን ነገር የምናስታውስበት በመኾኑ የሚከበረውም
በስግደት፣ በጾም፣ በጸሎት፣ በንባብና በትምህርት ነው፤ ስግደቱም ከሰሞኑ ኹሉ የበለጠ ነው፡፡
 በመኾኑም በስቅለት ዓርብ፣ መሪው ዕዝል ይመራል፤ ሕዝቡ ይከተላል፤ አራቱ ወንጌላት
ይነበባሉ፡፡ በየመሀሉ፥ “ወጸቢሖ ተማከሩ ሊቃነ ካህናት = ሲነጋም ሊቃነ ካህናት ተማከሩ”
የሚለው ዜማ፣ በመሪ በተመሪ በሕዝብ ተሰጥዎ ይከናወናል። ምንባቡም ስግደቱም
ድጓውም እንዳለፈው ይቀጥላል፡፡ ይህም ቀኑን በሙሉ ሲከናወን ውሎ በአሥራ አንድ ሠዓት፣
ካህናት በዐራት ማዕዝን ቆመው እግዚኦታ ያደርሳሉ፡፡ ዕለቱን የሚመለከቱ መዝሙራት
ተመርጠው ይነበባሉ፡፡ ንሴብሖ እየተባለ ቤተ መቅደሱን በመዞር በከበሮ በጸናጽል በሕማሙ
ያዳነን እግዚአብሔር ይመሰገናል፡፡ ዑደት የሚደረገው ሥነ ስቅለቱን በመያዝ ነው፡፡
 ምእመናንም፣ በሰሙነ ሕማማት የሠሩትን ኃጢአት እየተናዘዙ በካህናት አባቶች ንስሐ
ይቀበላሉ፤ ካህናቱም በወይራ ቅጠል ትከሻቸውን እየጠበጠቡ ቀን ከሰገዱት ስግደት
በተጨማሪ ሌላ ስግደት ያዟቸዋል፡፡ ጥብጣቤ ማለት ቸብ ቸብ ማድረግ ማለት ነው፡፡
ይኸውም፣ በአንድ በኩል የክርስቶስ ግርፋት ተሳታፊዎች መኾናቸውን ለመግለጥ ሲኾን፣
በሌላ በኩል የተግሣጽ ምሳሌ ነው፡፡ ወይራ ጽኑዕ ነው፤ የተቀበልከው መከራም ጽኑዕ ነው፤
እኛም ይህን መከራ ለመቀበል ዝግጁ ነን፤ ለማለት ነው፡፡
 ጥብጣብ የሚደረግለት ሰው፣ በሕማማቱ ወቅት የፈጸመው በደል ወይም ኃጢአት ካለ
ይህንኑ በመናገር፣ አቅሙ ተመዝኖ የስግደቱ ቁጥር ከፍ እንዲል ይደረጋል፤ በታዘዘውም
መሠረት ይፈጽማል፡፡ ሕዝበ ክርስቲያኑ በዕለተ ስቅለት ሲሰግድ፣ ሲጸልይ፣ ሲያነብ ከዋለ
በኋላ፣ በካህኑ ኑዛዜ ወደየቤቱ ይሰናበታል፡፡
 መስቀል መሳለም የለም፤ የወንጀለኞች መቅጫ ምልክት የነበረውን መስቀል፣ ጌታ በደሙ
ቀድሶ፣ የምሕረት ምልክት፣ የሕይወት ዓርማ፣ የዲያብሎስ ድል መንሻ አድርጎ የሰጠበትን
የትንሣኤውን ብርሃን እስክናይ ድረስ፡፡
 ከዓርብ ስግደት መልስ፣ እስከ እሑድ /የትንሣኤው ሌሊት/ ድረስ ኹለት ቀን የሚያከፍሉ
ምእመናን፣ ምንም ሳይቀምሱ ያድራሉ፡፡ ይህም አክፍሎት ይባላል፡፡ የማያከፍሉ ግን
በየቤታቸው ጥቂት ነገር ለቁመተ ሥጋ ቀምሰው ይሰነብታሉ። ብዙ ጊዜ የሚቀመሰውም፣
ከጸሎተ ሐሙስ የተረፈውን ጉልባንና ዳቦ ነው፡፡
 ጉልባን ከባቄላ ክክ፣ ከስንዴ ወይም ከተፈተገ ገብስ ጋር አንድ ላይ ተቀቅሎ የሚዘጋጅና
በጸሎተ ሐሙስ የሚበላ ንፍሮ ነው። እስራኤላውያን፣ ከግብጽ ተሰደው በሚወጡበት ጊዜ
በችኮላ ስለነበር፣ አቡክተው ጋግረው መብላት ያለመቻላቸውን ኹኔታ ያመለክታል፡፡ ይህን
መሠረት አድርጎ የሚዘጋጀው ጉልባን እንዲኹም ቂጣ፣ ጨው በዛ ተደርጎ ይጨመርበታል፡፡
ውኃ የሚያስጠማ በመኾኑ የጌታን መጠማት ያስታውሳል፡፡
 ቅዳሜ ጠዋት፣ ምእመናኑና ካህናቱ ወደ ቤተ ክርስቲያን ይሰበሰባሉ፤ የጠዋቱ ጸሎት
ሲፈጸም፣ “ገብረ ሰላመ በመስቀሉ ትንሣኤሁ አግሀደ = በመስቀሉ ሰላምን መሠረተ፤
ትንሣኤውን ገለጸ፤ የምሥራች” እየተባለ እየተዘመረ ቄጤማው ቤተ መቅደሱን ዞሮ በካህኑ
ተባርኮ ለምእመናን ይታደላል፤ ምእመናኑም እየሠነጠቁ በራሳቸው ያስሩታል፡፡
 ወደ ቤተ ክርስቲያን ላልመጡትም፣ ካህናቱ ልብሰ ተክህኖአቸውን በመልበስ፣ መስቀልና
ቃጭል ይዘው በየሰበካቸው፣ ቄጤማውን የምሥራች እያሉ ያድላሉ፤ ምእመናንም ለቤተ
ክርስቲያን አገልግሎት የሚውል ገጸ በረከት ያቀርባሉ፡፡ ቄጤማው በራስ ላይ መታሰሩ፥
አይሁድ በጌታችን ጭንቅላት ላይ የእሾህ አክሊል ያሰሩበትን ድርጊት የሚያስታውስ ነው፡፡
 ጥንተ አመጣጡና ምስጢሩ ግን፣ ከአባታችን ኖኅ ታሪክ ጋራ የተያያዘ ነው፡፡ ምድር በጥፋት
ውኃ በጠፋችበት ወቅት፣ የኖኅ ታማኝ መልእክተኛ ርግብ የውኃውን መጉደል ያበሠረችው
ቄጤማ ባፏ ይዛለት በመግባት ነው፡፡ ዛሬም ለሐዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች፦ የኃጢአት ውኃ
ጠፋ፤ ኃጢአት – ሞተ ነፍስ ከሰው ልጆች ተወገደ፤ በክርስቶስ ሞት ነጻነት ተሰበከ፤ ታወጀ
በማለት፣ አዳምና ልጆቹ፥ ከለምለሚቱ ሥፍራ ከተድላ ገነት መግባታቸውን ለመግለጽ፥
ምእመናን ቄጤማ ይዘው፣ ቄጤማ አስረው ይታያሉ፤ ትንሣኤውንም ለሚናፍቁ ትልቅ
ብሥራት ነው፡፡
 የሰሙነ ሕማማት ቅዳሜ፣ “ሰንበት ዓባይ” ትባላለች፤ ጌታችን፣ የሦስት ዓመት ከሦስት ወር
የማዳን ሥራውን በመስቀል ላይ ፈጽሞ በከርሠ መቃብር ዐርፎ የዋለባት ዕለት ናት፡፡
ኹለተኛም፣ ይህች ዕለት ሥዑር ቅዳሜ፤ የተሻረች ቀዳሚት ሰንበት ትባላለች፡፡ ሥዑር
መባሏ በዓመት አንድ ቀን ስለምትጾም ነው፤ “ቅዳሜ ሹር” እንዲሉ፤ አንድም፣ በዚኹ ቀን
በሚባለው ዕዝል ውስጥ፥ ስኢሮ ሞተ፤ ሞትን ሽሮ ተነሣ፤ ይላል፤ ሞትም የተባለው
ዲያብሎስ ያመጣው ሞተ ነፍስ ነውና፣ የተሻረ የተባለው ዲያብሎስ ነው፡፡
 በአዳም ከሲኦል መውጣትና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን መነሣት፣ ቤተ ክርስቲያን
የምታሰማን የምሥራች ከደስታ ኹሉ የበለጠ ነው። ምንም እንኳን፣ ጌታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ የተነሣው እሑድ በመንፈቀ ሌሊት ቢኾንም፣ አዳም ከሲኦል
ወጥቶ ወደ ገነት መግባቱ የታወቀው፤ የክርስቶስ ትንሣኤው የተመረመረው በቀዳም ስዑር
ስለኾነ፣ የትንሣኤው ብሥራት በአፈ ካህናት ለሕዝበ ክርስቲያን ይነገርበታል፡፡ የኀዘኑ
ዜማዋና የኀዘኑ ልብሷ ተለውጦ፣ የጸናጽል የከበሮ ድምፅ ታሰማለች፡፡
 ቅዳሜ ምሽት፣ የአብያተ ክርስቲያናቱ ቅጽርና ዙሪያው ነጫጭ በለበሱ ምእመናን መልቶ
ሲታይ ያስደንቃል፡፡ የአብያተ ክርስቲያናቱ ደወሎች ሲደወሉ፣ መዘምራኑ የማሕሌቱን፣
ቀሳውስቱ የሰዓታቱን ሥርዓት ማከናወን ይጀምራሉ፡፡ ማሕሌቱ ተቁሞ ቆይቶ በምልጣኑ
ሠዓት ዲያቆኑ ከዳዊት መዝሙር፣ ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃሕ እምነዋም… ብሎ
በሰበከ ጊዜ፣ የሕዝቡ ደስታ በጣም የበዛ ይኾናል፤ በውስጥም በውጭም ያለው ሕዝብ
በእልልታና በጭብጨባ ተቀባብሎ ያደምቀዋል፡፡
 ከዚኽ በኋላ፣ የትንሣኤውን ነገር የሚያነሣው ወንጌል ተነቦ፣ መሪው መስቀሉን ከዲያቆኑ
ተቀብሎ፦ ዮም ፍሥሓ ኮነ በሰንበተ ክርስቲያን እስመ ተነሥአ ክርስቶስ እሙታን = ክርስቶስ
ከሙታን ተነሥቶአልና ዛሬ በክርስቲያን ሰንበት በዚኽች በእሑድ ፍሥሓ ኾነ፤ ደስታ ተደረገ፤
ብሎ መርቶ መዘምራኑ ይህንኑ ተቀባብለው ይዘሙታል፤ ያሸበሽቡታል፡፡
 ከዚኽ በኋላ፣ ትንሣኤከ ለእለ አመነ ብርሃነከ ፈኑ ዲቤነ = ትንሣኤህን ለምናምን ኹሉ
ብርሃንህን ላክልን፤ የሚለውን እስመ ለዓለም የተባለውን ቀለም አለዝበው በወረቡት ጊዜ፣
ለተሰበሰበው ሕዝበ ክርስቲያን፣ ከሰም የተሠራ የጧፍ መብራት ይታደልና ዑደቱ ሊደረግ
ይጀምራል፤ ከጧፉ ውጋጋን የተነሣም ምሽቱ ሰዓተ መዓልት ኾኖ ይገኛል፡፡ ይህን ተከትሎም፣
ሦስት ጊዜ ከተደወለ በኋላ ቅዳሴ ለመግባት ሲዘጋጁ ይታያል፤ መንፈቀ ሌሊት ሲኾን ቅዳሴ
መቀደስ ይጀመራል፤ ድርገትም በወረዱ ጊዜ በጣም ብዙ ሰው ሥጋወደሙን ለመቀበል
ተዘጋጅቶ ይቀርባል፡፡ከቅዳሴም በኋላ፣ ኹሉም ወደየቤቱ ተመልሶ በትንሣኤው በዓል
ከየቤተሰቡ ጋራ ደስ ብሎት የሚገባውን ያደርሳል፡፡
 በበነጋውም በየቤተ ዘመዱ እየሔደ፣ እንኳን ጾመ ልጓሙን ፈታልህ፤ እንኳን አብሮ ፈታልን፤
እየተባባለ ይጠያየቃል፤ እንኳን ጾመ ልጓሙን ፈታልን፤ ማለት፣ ሁለት ወር ሁዳዴ ሲጾም
ሰንብቶ በጌታ ትንሣኤ ምክንያት ጾሙ ስለቀረለት ነው፡፡በተጨማሪም፣ የአክፋይ
ወይም ገብረ ሰላመ እየተባለ፣ ምእመናን፣ ከማዕዶት እስከ ዳግም ትንሣኤ ያሉትን ዕለታት
ተከፋፍለው ለሰበካቸው ካህናት፥ ጠላ በመንቀል፣ እንጀራ በአገልግል በመውሰድ ያበላሉ፤
በየቤታቸውም እየጠሩ ይጋብዛሉ፤ እንዲኹም ዘመድ ዘመዱንም ሲጠይቅ ይሰነብታል።
ይህም፣ ጌታችን ከተነሣ በኋላ እስኪያርግ ድረስ፣ ለደቀ መዛሙርቱ ሦስት ቀን ግብር አግብቶ
መግቧቸው ነበርና ያንን ያሳስባል፡፡
 ምስጋና ለእግዚአብሔር ይሁን አሜን

የሰሙነ_ሕማማት_ዕለታት_ስያሜዎች;-
1. እሑድ ፦ የሰሞነ ሕማማት የመጀመሪያው ቀን ሆሣዕና ይባላል። ትርጉሙም ‹‹እባክህ አሁን አድን
አንድም መድኃኒት›› ማለት ነው፡፡
2. ሰኞ
ሀ. መርገመ በለስ የተፈጸመበት = በዚህ ዕለት ጌታችን ከቢታኒያ ሲወጣ ተራበ ቅጠል ያለባትን በለስ
ተመልክቶ ወደ በለሲቱ ቢቀርብ ከቅጠል በቀር ምንም ነገር ባለማግኘቱ “ከአሁን ጀምሮ ለዘላለም
ምንም ካንቺ ፍሬ አይበላ” ማር ፲፩፥፲፬ በማለት ስለረገማት መርገመ በለስ የተፈጸመበት ሰኞ
ይባላል።
ለ.አንጽሖተ ቤተ መቅደስ = ጌታ ወደ ቤተመቅደስ ሄዶ በቤተመቅደሱ የሚሸጡትን እና
የሚለውጡትን “ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች” ማቴ ፳፩፥፲፫ በማለት ከቤተ መቅደስ ገርፎ
አስወጥቷቸዋልና።
3. ማክሰኞ
ሀ. የጥያቄ ቀን = ሰኞ ዕለት በቤተመቅደስ ሲሸጡ እና ሲለውጡ የነበሩትን ሁሉ እየገረፈ በማባረሩ
ምክንያት ለሰው ልጅ ሹመትንና ስልጣንን የሰጠ ጌታ “በምን ስልጣን ይህንን ታደርጋለህ?” ማቴ ፳፩፥
፳፫ ተብሎ በፈሪሳውያን ተጠይቋልና የጥያቄ ቀን ይባላል።
ለ. የትምህርት ቀን= በዚህ ዕለት በቤተመቅደስ ረጅም ትምህርት ስላስተማረም የትምህርት ቀን
ይባላል። ሉቃ ፳፩ ፥፳፰ ፣ ማር ፲፪፥፪።
4. ረቡዕ
ሀ. ምክረ አይሁድ = ረቡዕ እለት የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጸሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንዳለባቸው
የመከሩበትና ውሳኔ ያሳለፉበት ቀን በመሆኑ ምክረ አይሁድ ይባላል። ወቅቱ የፋሲካን በዓል
የሚያከብሩበት ቀን በመሆኑ እና ብዙ ህዝብም ጌታን ይከተለው ስለነበር ሁከት እንዳይነሳ ስጋት
ነበራቸው ። ነገር ግን ከአስራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ አሳልፎ እንደሚሰጣቸው
ስለነገራቸው ሉቃ ፳፪፥፩-፮ ጭንቀታቸው ተወግዶ በጌታ መያዝ ተስማምተዋል።
ለ. የመልካም መዓዛ ቀን = ጌታችን በዚህ ዕለት በለምጻሙ በሰምዖን ቤት ተቀምጦ ሳለ መላ
ሕይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት/ባለሽቶዋ ማርያም/ ዋጋው
እጅግ ውድ የሆነ የአልባጥሮስ ሽቱ አምጥታ በራሱ ላይ በማርከፍከፍ ስለቀባቸው ማቴ ፳፮፥፮-፯
የመዓዛ ቀን ይባላል።
ሐ. የእንባ ቀን= ባለሽቱዋ ሴት (ማርያም እንተ እፍረት) ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት እየለመነች
በእግሩ ስር ተደፍታ በእንባዋ እግሩን አርሳለችና ማር ፲፬፥፱ የእንባ ቀን ይባላል።
5. ሐሙስ
ሀ. ጸሎተ ሐሙስ = ጌታችን ለአይሁድ ተላልፎ ከመሰጠቱ በፊት በጌቴሴማኒ የአትክልት ስፍራ
ሲጸልይ በማደሩ ማቴ ፳፮፥፴፮ ጸሎተ ሐሙስ ይባላል።ጌታችን የደቀመዛሙርቱን እግር በፍጹም
ትህትና ዝቅ ብሎ ያጠበበት ዕለት በመሆኑም ዮሐ ፲፫፥፫-፲፩ ሕጽበተ ሐሙስ ይባላል።
ለ. የምስጢር ቀን = ከሰባቱ ምስጢራት አንዱ የቅዱስ ቁርባን ምስጢር ማቴ፳፮፥፳፮-፳፱ በዚህ
ዕለት ተፈጽሟልና የምስጢር ቀን ይባላል።
ሐ. የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ= መሥዋዕተ ኦሪት /በእንስሳት ደም የሚቀርብ መሥዋዕት/ቀርቶ ለአለም
ድኅነት ራሱን ያቀረበበት ቀን በመሆኑ ሉቃ ፳፪፥፳ የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል።
መ. የነጻነት ሐሙስ = ለኃጢአትና ለዲያቢሎስ ባሪያ ሆኖ መኖር ማብቃቱን እንዲሁም የሰው ልጅ
ያጣውን ክብር መልሶ ማግኘቱ የተረጋገጠበት ቀን ስለሆነም ዮሐ ፲፭፥ ፲፭ የነጻነት ሐሙስ ይባላል።

6. ዓርብ
ሀ. የስቅለት ዓርብ= ጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ቤዛ ሆኖ
በመልዕልተ መስቀል ላይ ተሰቅሎ የዋለበት ዕለት ነውና ማቴ ፳፯፥፴፭ የስቅለት ዓርብ ይባላል።
ለ. መልካሙ ዓርብ= ከጌታ ስቅለት በፊት በተለይም በሮማውያን ህግ የወንጀለኛ መቅጫ ምልክት
የነበረውን መስቀል ጌታችን በደሙ ቀድሶ የምህረት፣ የሕይወት አርማ፣ የዲያቢሎስ ድል መንሻ
ስላደረገው፤ በሞቱ መልካሙን ሕይወት ስላገኘን መልካሙ ዓርብ ይባላል።

7. ቅዳሜ
ሀ. ቀዳም ስዑር፦ ይህች እለት ከድሮ በተለየ መልኩ የጌታችንን መከራ በማሰብ በጾም ታስባ
ስለምትውል የተሻረች ቅዳሜ ይባላል።
ለ. ለምለም ቅዳሜ፦ ካህናቱ ለምእመናን ለምለም ቀጤማ የሚያድሉበት ዕለት በመሆኑም ለምለም
ቅዳሜ ይባላል። ምዕመናንም ይህንን ለምለም ቀጤማ እስከ ትንሣኤ ለሊት በራሳቸው ላይ
ያስሩታል።
ሐ. ቅዱስ ቅዳሜ፦ ቅዱስ የሆነው እግዚአብሔር በጥንተ ተፈጥሮ ፍጥረታትን አከናውኖ ያረፈበት
ቀን ሲሆን በዘመነ ሐዲስ ደግሞ የማዳን ስራውን ሁሉ ፈጽሞ በሥጋው በመቃብር ሲያርፍ በነፍሱ
ወደ ሲኦል ወርዶ ሲኦልን በርብሮ ባዶዋን ሲያስቀራት በዚያ የነበሩትን ነፍሳት የዘላለም ዕረፍትን
ያወረሰበት ዕለት ስለሆነ ቅዱስ ቅዳሜ ይባላል።
 እንበለ ፦ ደዌ ወህማም እንበለ ጻዕር(ጻማ) ወድካም አመ ከመ ዮም ያብጽሃነ ያብጽሐክሙ
እግዚአብሔር በፍስሐ ወበሰላም አሜን።

በግብረ ሕማማት ውስጥ የሚገኙ እንግዳ ቃላት እና ትርጉማቸው፡- በግብረ ሕማማት ውስጥ ወደ
ግእዝም ሆነ በኋላ ወደ አማርኛ ሳይተረጎሙ የተቀመጡ የዕብራይስጥ፣ የቅብጥ እና የግሪክ ቃላት ይገኛሉ፡፡
የእነዚህ ቃላት ትርጉም የሚከተለው ነው፡፡
 ኪርያላይሶን፦ ቃሉ የግሪክ ሲሆን አጠራሩ «ኪርዬ ኤሌይሶን» ነው፡፡ «ኪርያ» ማለት «እግዝእትነ»
ማለት ሲሆን «ኪርዬ» ማለት ደግሞ «እግዚኦ» ማለት ነው፡፡ ሲጠራም «ኪርዬ ኤሌይሶን» መባል
አለበት፡፡ ትርጉሙ «አቤቱ ማረን»ማለት ነው፡፡ «ኪርያላይሶን» የምንለው በተለምዶ ነው፡፡ ይኼውም
ኪርዬ ከሚለው «ዬ» ኤላይሶን ከሚለው ደግሞ «ኤ» በመሳሳባቸው በአማርኛ «ያ»ን ፈጥረው ነው፡፡
 ናይናን፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «መሐረነ፣ ማረን» ማለት ነው፡፡
 እብኖዲ፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «አምላክ» ማለት ነው፡፡ «እብኖዲ ናይናን» ሲልም «አምላክ
ሆይ ማረን» ማለቱ ነው።
 ታኦስ፦ የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙ «ጌታ፣ አምላክ» ማለት ነው፡፡ «ታኦስ ናይናን» ማለትም «ጌታ
ሆይ ማረን» ማለት ነው፡፡
 ማስያስ፦ የዕብራይስጥ ቃል ሲሆነ ትርጉሙ «መሲሕ» ማለት ነው፡፡ «ማስያስ ናይናን» ሲልም
«መሲሕ ሆይ ማረን» ማለት ነው።
 ትስቡጣ፦ «ዴስፓታ» ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም ደግ ገዥ ማለት ነው።
 አምነስቲቲ_ሙኪርያቱ_አንቲ_ፋሲልያሱ፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም «ተዘከረነ እግዚኦ በውስተ
መንግሥትከ- አቤቱ በመንግሥትህ አስበኝ» ማለት ነው፡፡
 አምንስቲቲ_ሙዓግያ_አንቲ_ፋሲልያሱ፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን «ተዘከረነ ኦ ቅዱስ በውስተ መንግሥትከ
-ቅዱስ ሆይ በመንግሥትህ አስበን» ማለት ነው፡፡
 አምንስቲቲ_ሙዳሱጣ_አንቲ_ፋሲልያሱ፦ የቅብጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙም «ተዘከረነ እግዚአ ኩሉ
በውስተ መንግሥትከ- የሁሉ የበላይ የሆንክ ወይ በመንግሥትህ አስበን» ማለት ነው፡፡

 ቤተ ክርስቲያን በሕማማት እንዲህ እያለች ትጸልያለች ስለአገራችን ኢትዮጵያ፣ ስለአስተዳዳሪዎቿና


በጠረፎቿ ጠላትን በመከላከል ያሉትን ጌታ በሰላም ይጠብቃቸው ዘንድ፣ በዓለሙ ሁሉ ስለአሉ
አብያተ ክርስቲያናትም መልካም ነገርን ያስቡ ዘንድ፣ ኃጢአታችንንም ያስተሰርይልን ዘንድ ጸልዩ።
ንዑዳን ክቡራን ስለሚሆኑ ስለ አባቶቻችን አባ መርቆሬዎስና አባ ማትያስ የኢትዮጵያ ፓትርያርኮች
የጳጳሳቱ አለቆች ፣ስለ አባቶቻችን የጳጳሳቱ አለቆች ፣ ኤጲስ ቆጰሳት ሕይወትና አኗኗር ሰፊ
ዘመናትንና ረጅም ዓመታትን ሰጥቶ በመንበረ ስብከታቸው እያንዳንዳቸውን በሰላም ያጸናቸው ዘንድ
የእኛንም ኃጢአት ያስተሰርይልን ዘንድ ጸልዩ። ስለአንድነታችን የቀናች ሃይማኖት ስላለቻቸው ሕዝበ
ክርስቲያን አንድነት ጌታ ይጠብቃቸውና በሰላም ያስፈጽማቸው ዘንድ የእኛንም ኃጢአት
ያስተሰርይልን ዘንድ ጸልዩ።
 ለከበረች ቤተ ክርስቲያን መባን ከሰውና ከእንስሳት ስለሚያቀርቡ ሰዎች ጌታ ይባርካቸው ዘንድ፣
በሥራቸውም እንዲጸኑ ይረዳቸው ዘንድ፣ የእኛንም ኃጢአት ያስተሰርይልን ዘንድ ጸልዩ።
ምእመናንን በየስፍራቸው ሁሉ በቸርነት ስለሚያስቡና ለበጎ ነገር ስለሚደክሙ የቀና ሃይማኖት
ስላላቸው ሰዎች ሁሉ ጌታ ይባርካቸው ዘንድ፣ ዋጋቸውንም ይሰጣቸው ዘንድ፣ ይቅርታን
ያደርግላቸው ዘንድ፣ የእኛንም ኃጢአታችንን ያስተሰርይልን ዘንድ ጸልዩ።
 ለቁርባን የሚሆን ስንዴውን፣ ዕጣኑን፣ መብራቱን፣ የሚነበብባቸው መጻሕፍትን፣ ሌላውንም የቤተ
መቅደስ ንዋያተ ቅድሳት ሁሉ በመስጠት ስለሚያስቡ ሰዎች በመንግሥተ ሰማያት የበለጠ ዋጋ
ይሰጣቸው ዘንድ፣ የእኛንም ኃጢአታችንን ያስተሰርይልን ዘንድ ጸልዩ።
 ስማቸውን በየአንዳንዳቸው እንድንጠራ ስለአዘዙን ለየቤተ ክርስቲያን ሊቃውንትና ታላላቆች
አባቶችን ጌታ ይባርካቸው፣ በባለሥልጣናትና በሹማምንት ፊት በፈራጆችም አደባባይ ፍቅርን፣
መወደድን ይድላቸው ዘንድ፣ የእኛንም ኃጢአታችንን ያስተሰርይልን ዘንድ ጸልዩ።
በደዌ ሥጋ፣ በደዌ ነፍስ ለደከሙና ለተቸገሩ ለባልቴቷም አባት እናት ለሞቱባቸው ለድሆች ልጆችና
ለተጨነቁት ሰዎችም እርሻ ላረሱ፣ ዘር ለዘሩ፣ ለሚሸጡ፣ ለሚገዙ፣ ለተጨነቀችም ሰውነት
በማናቸውም ቦታ ሁሉ ጌታ ራርቶ ይቅር ይላቸው ዘንድ፣ የእኛንም ኃጢአታችንን ያስተሰርይልን
ዘንድ ጸልዩ።
 በግዞት፣ በምርኮ ተይዘው ለተጨነቁ፣ አገር ለቀው ለተሰደዱ፣ በአጋንንት አሽክላም ለተያዙ ሰዎች
ጌታ ከግዞት፣ ከምርኮኝነት ያወጣቸው ዘንድ፣ ይቅርታውንም ሰጥቶ እነሱንም እኛንም ያድነን ዘንድ፣
ኃጢአታችንንም ያስተሰይልን ዘንድ ጸልዩ።

ይቆየን….

 ጉልባን ከባቄላ ክክ፣ ከስንዴ ወይንም ከተፈተገ ገብስ ጋር አንድ ላይ ተቀቅሎ የሚዘጋጅና የጸሎተ
ሐሙስ ዕለት የሚበላ ንፍሮ ነው፡፡ በጸሎተ ሐሙስ በቤት ውስጥ ከሚፈጸሙ ተግባራት አንዱ ጉልባን
ማዘጋጀት ነው፡፡ ጉልባን እስራኤላውያን ከግብጽ ባርነት ሲወጡ በችኮላ መጓዛቸውን
የምናስታውስበት ከእስራኤላውያን የመጣ ትውፊታዊ ሥርዓት ነው፡፡ በአገራችን ኢትዮጵያ አብዛኞቹ
የትውፊት ክንዋኔዎች የብሉይ ኪዳን መነሻ ስላላቸው ይህ ሥርዓት ዛሬም በኢትዮጵያውያን
ምእመናን ዘንድ ይከበራል፡፡
 ጉልባን እስራኤላውያን ከባርነት በወጡ ጊዜ አቡክተው፣ ጋግረው መብላት አለመቻላቸውን
ያስታውሰናል፡፡ በወቅቱ ያልቦካውን ሊጥ እየጋገሩ ቂጣ መመገብ፤ ንፍሮ ቀቅለው ስንቅ መያዝ
የመንገድ ተግባራቸው ነበርና፡፡ ይህን ታሪክ ለማሰብም በሰሙነ ሕማማት በተለይም በጸሎተ ሐሙስ
ቂጣና ጉልባን ይዘጋጃል፡፡ በጸሎተ ሐሙስ የሚዘጋጀው ጉልባንና ቂጣ ጨው በዛ ተደርጎ
ይጨመርበታል፡፡ ይኸውም ጨው ውኃ እንደሚያስጠማ ዅሉ፣ ጌታችንም በመከራው ወቅት ውኃ
መጠማቱን ለማስታወስ ነው፡፡

ምንጭ፡-
ስምዐ ተዋሕዶ (ልዩ ዕትም ዘሰሙነ ሕማማት)

 ቤተክርስቲያን ከጣራዋ እስከ መሬቷ ሁሉም ሥርዓቷ ያስተምራል፤ ባህረ ጥበብ ቤተክርስቲያን
እየተናገረች ታስተምራለች ሳትናገር ዝም ብላም ታስተምራለች!!
 ቤተክርስቲያን ባህረ ጥበባት አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት የሲኦል ደጆች አያናውጧትም
ቤተክርስቲያን አ..ት..ታ..ደ..ስ..ም! ፀልዩ በእንተ ሰላም ቤተክርስቲያን አሐቲ ቅድስት ጉባኤ እንተ
ሐዋርያት ርትዕት በኅበ እግዚአብሔር! የሐዋርያት ጉባኤ ስለሆነች ስለአንዲት ቅድስት ቤተ
ክርስቲያን ሰላም እንማልዳለን! (መጽሐፈ ሚስጢር) ቤተክርስቲያን.... መሰረቷ ጉልላቷ እርሱ ነው
ሙሽራዋ መስቀል ላይ የሞተው ዛሬም ነገም ያው ነው ለዘላለም አትንገሩን አዲስ ጌታ የለም! •••
እንበለ ደዌ ወሕማም፥ እንበለ ጻማ ወድካም፥ ያብፀሓነ አመ ከመ ዮም። በፀሎታችሁ አስቡኝ
አትርሱኝ።

ቅዳሜ_ቀዳም_ሥዑር_ይባላል፡-
በዚች ዕለች ከድሮው በተለየ መልኩ የጌታችንን መከራ በማሰብ በጾም ታስባ ስለምትውል የተሻረችው
ቅዳሜ ትባላለች፡፡ የማትጾመዋ ቅዳሜ ስለምትጾም ስዑር /የተሻረች/ ተብላለች በዓል መሻርን
አይመለከትም በቀዳም ሥዑር ሌሊት ሥርዓቱ የሚጀመረው በመኀልየ ሰሎሞን ምንባብ ነው፡፡
ማኀሌቱም እዝሉ እየተቃኘ እየተመጠነ፣ እየተዘመመ እየተመረገደ እየተጸፋ ያድራል፡፡ ጥዋት አቡን
መዋሥዕት ውዳሴ ማርያም ዜማ ተደርሶ ወለመልአከ ሕይወትሰ ሰቀልዎ በሚለው ሰላም ይጠናቀቃል፡፡
በዚህ ዕለት ልብሰ ተክህኖ የለበሱ ካህናትና ዲያቆናት ቄጤማ ተሸክመው ቃጭል ሲያቃጨሉ
መታየታቸው ዕለተ ትንሣኤውን ለሚናፍቅ ምእመን ትልቅ ብስራት ነው፡፡
ለምለም_ቅዳሜ፡-
ካህናቱ ለምእመናን ለምለም ቀጤማ የሚያድሉበት ዕለት ስለሆነ በዚህ ተሰይሟል፡፡ ቀጤማውንም
ምእመናን እስከ ትንሣኤ ሌሊት በራሳቸው ላይ ያስሩታል፡፡ በቀዳም ስዑር ቀሳውስቱና ዲያቆናቱ ቃጭል
/ቃለዓዋዲ/ እየመቱ ገብረ ሰላመ በመስቀሉ ትንሣኤሁ አግሃደ የሚለውን ያሬዳዊ ዜማ በመዘመር፤ ጌታ
በመስቀሉ ሰላምን እንደሰጠን እና ትንሣኤውንም እንደገለጠልን በማብሰር፤ ቄጤማውን ለምእመናን
ይሰጣሉ፡፡ ምእመናኑም በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚውል ገጸ በረከት ያቀርባሉ፡፡ ቄጤማውንም
በራሳቸው ያስራሉ፡፡ ይህም አይሁድ ጌታችንን እያሰቃዩ ሊሰቅሉት ባሉ ጊዜ የእሾህ አክሊል ጭንቅላቱ ላይ
ያሠሩበትን ድርጊት የሚያስታውስ ነው፡፡ የቀጤማው አመጣጥና ምስጢርም ከአባታችን ከኖኅ ታሪክ ጋር
የተያያዘ ነው፡፡ ምድር በማየ አይኅ /በጥፋት ውኃ/ በጠፋችበት ወቅት የኖኅ ታማኝ መልእክተኛ ርግብ
የውኃውን መጉደል ያበሰረችው ቀጤማ ይዛ በመግባት ነው፡፡ ዛሬም ለሐዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች የኃጢአት
ውኃ ጐደለ፣ የኃጢአት ውኃ ጠፋ በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ነጻነት ተሰበከ ታወጀ በማለት ካህናት ቄጠማ
ይዘው ምእመናንን ያበሥሩበታል፡፡
ቅዱስ_ቅዳሜ_ይባላል፡-
ቅዱስ ቅዳሜ መባሉ ቅዱስ የሆነ እግዚአብሔር በጥንተ ተፈጥሮ ፍጥረታትን አከናውኖ ከፈጠረ በኋላ
በዚህ ቀን ከሥራው ሁሉ ያረፈበት ነው፡፡ በዘመነ ሐዲስ ደግሞ የማዳን ሥራውን ሁሉ ፈጽሞ በሥጋው
በመቃብር ሲያርፍ፣ በነፍሱ ሲዖልን በርብሮ ባዶዋን አስቀርቷታል፡፡ በዚያ ለነበሩት ነፍሳትም የዘለዓለም
ዕረፍትን ያወረሰበት ዕለት ስለሆነ ከሌሎቹ ዕለታት የተለየ ዕለት ለማለት ቅዱስ ቅዳሜ ተብሏል፡፡
ሥርዓተ ማኅሌት ዘትንሣኤ ተፈሥሂ ማርያም ለአዳም ፋሲካሁ ይባላል። ይ.ዲ ምስባክ መዝ: ፸፯ : ፷፭
ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃሕ እምንዋም ወከመ ኃያል ወኅዳገ ወይን ወቀተለ ፀሮ በድኅሬሁ።
አርያም ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ወለመንፈስ ቅዱስ ቀዳሚ ዜማ ግበሩ በዓለ ትፍሥሕት
እስከ አቅርንቲሁ ለምሥዋዕ ዛቲ ፋሲካ ቀዳሚት ሕግ። ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ
ወለመንፈስ ቅዱስ ይገብሩ በዓለ ሰማያት ይገብሩ በዓለ ደመናት ወምድርኒ ትገብር ፋሲካ ተሐጺባ በደመ
ክርስቶስ።አንገርጋሪ ዮም ፍሥሃ ኮነ በሰንበተ ክርስቲያን እስመ ተንሥአ ክርስቶስ እሙታንቀደሳ ወአክበራ
እምኲሎን መዋዕል አልዓላ አማን ተንሥአ እምነ ሙታን። አመላለስ አማን በአማን ተንሥአ አማን
በአማን ተንሥአ እምነ ሙታን ወረብ ዮም ፍሥሐ ኮነ በሰንበተ ክርስቲያን ቀደሳ ወአክበራ እምኲሎን
መዋዕል እስመ ለዓለም ትንሣኤከ ለእለ አመነ ብርሃንከ ፈኑ ዲቤነ። አመላለስ
ትንሣኤከ ለእለ አመነ ፈኑ ዲቤነ ብርሃነከ ፈኑ ዲቤነ ከእስመ ለዓለሙ ጋር ተያይዞ የኪዳን ሰላም
ይዘመማል ይመረገዳል። የኪዳን ሰላም ተሣሐልከ እግዚኦ ምድረከ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ
ሉያ ይእቲ ማርያም እምነ ወእሙ ለእግዚእነ ሰአሊ በእንቲአነ ከመ ይምሐረነ ወይሣሐለነ ያስተርኢ
ኂሮቶ ላዕሌነ ሠርዓ ለነ ሰንበተ ለዕረፍተ ዚአነ ፍሥሐ ወሰላም ለእለ አመነ። አመላለስ ሠርዓ ለነ ሰንበት
ለዕረፍተ ዚአነ ፍሥሐ ወሰላም ለእለ አመነ መዝሙር ትትፌሣሕ ሰማይ ወትትኃሠይ ምድር ወይንፍሑ
ቀርነ መሠረታተ ሕምዝ ወይበውኡ አድባር ወአውግር ወኲሉ ዕፀወ ገዳም ወዮምሰ ዓባይ ፍሥሐ
በሰማያት ወምድርኒ ትገብር ፋሲካ ተሐጺባ በደመ ክርስቶስ። ሰላም ፍጹመ ንጉሠ ኮነንዎ አይሁድ
ተካፈሉ አልባሲሁ ሐራ ሠገራት ወኮርዕዎ ርእሶ በኅለት ረገዝዎ ገቦሁ በኲናት ትንሣኤሁ ገብረ በሰንበት
ሰላመ ይጸጉ ለነገሥት፤ ለአሕዛብ ወለበሐውርት። እንኳን በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፡፡
ፋሲካ_ፋሲካ_ፋሲካ፤ ተዝካረ_ትንሣኤሁ_ለክርስቶስ፡፡ ትንሣኤ_ትርጉም_በዓሉና_አከባበሩ_
 «ትንሣኤ» የሚለው ቃል የግእዝ ቋንቋ ነው፡፡ መገኛ ቃሉም «ተንሥአ» = ተነሣ የሚለው ግሥ
ይሆናል፡፡ «ትንሣኤ» ማለት ታዲያ = መነሣት፣ አነሣሥ ሐዲስ ሕይወት ማግኘት ማለትን
ያመለክታል፡፡ «ትንሣኤ» በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በየመልኩ፣ በየዐይነቱ ሲተረጐም ዐምስት ክፍል
አለው፡፡

1. «ትንሣኤ» ኅሊና ነው፡፡ ይህም ማለት ተዘክሮተ እግዚአብሔር ነው፡፡


2. «ትንሣኤ» ልቡና ነው፡፡ የዚህም ምስጢሩ ቃለ እግዘብሔርን መስማትና በንስሐ
እየታደሱ በሕይወት መኖር ነው፡፡
3. «ትንሣኤ» ለጊዜው የሙታን በሥጋ መነሣት ይሆናል፡፡ ነገር ግን ድጋሚ ሞት
ይከተለዋል፡፡
4. «ትንሣኤ» የክርስቶስ በገዛ የባሕርይ ሥልጣኑ ሞትን ድል አድርጎ መነሣት ነው፡፡ የእርሰ
ትምህርታችንም መሠረት ይኸው እንደሆነ ይታወሳል፡፡
5. «የትንሣኤ» ደረጃም የባሕርይ አምላክ የጌታችን የመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን
«ትንሣኤ» መሠረት ያደረገ «ትንሣኤ ዘጉባኤ» ነው፡፡ ይህም ከዓለም ኅልፈት በኋላ
ሰው ሁሉ እንደየሥራው ለክብርና ለውርደት፣ ለጽድቅና ለኩነኔ በአንድነት የሚነሣው
የዘለዓለም ትንሣኤ ይሆናል፡፡ ወደተነሣንበት ዐላማ ስንመለስ የትንሣኤ በዓል በቃሉም
ምስጢር በይዘቱም ስለሚመሳሰሉ ጥላው ምሳሌውም፣ ስለሆነ «ፋሲካ» ተብሎ
ይጠራል፡፡
 «ፋሲካ» ማለት በዕብራይስጥ ቋንቋ «ፌሳሕ» በጽርእ በግሪክኛው «ስኻ» ይባላል፡፡ ይህም ወደ እኛው
ግእዝና ዐማርኛ ቋንቋችን ሲመለስ ፍሥሕ ዕድወት = ማዕዶት፣ በዓለ ናእት = የቂጣ በዓል፣ እየተቸኮለ
የሚበላ መሥዋዕት፣ መሻገር መሸጋገር ማለት ነው፡፡
 ነጮቹ በእንግሊዝኛው «ስኦቨር» ይሉታል የዚህም ታሪካዊ መልእክቱ በዘመነ ኦሪት ይከበር የነበረው
በዓለ ፋሲካ እስራኤል ዘሥጋ ከግብጽ የባርነት ቀንበር ወደነፃነት የተላለፉበት፣ ከከባድ ሐዘን ወደ
ፍጹም ደሰታ፣ የተሸጋገሩበት በዓል ነበር፡፡
 በዚህ ኦሪታዊ ምሳሌ በዓል አሁን አማናዊው በዓል «ትንሣኤ» ተተክቶበታል፡፡ ፋሲካ፣ በዓለ ትንሣኤ
በዘመነ ሐዲስ እስራኤል ዘነፍስ የሆኑት ምእመናነ ክርስቶስ ትንሣኤውን የሚያከብሩበት ዕለት ሆኖ
በእርሱ ትንሣኤ ከኀጢአት ወደ ጽድቅ፣ ከኀሳር = ከውርደት ወደክብር፣ ከጠላት ሰይጣን አገዛዝ ወደ
ዘለዓለማዊ ነፃነት፣ ከአደፈ፣ ከጐሰቆለ አሮጌ ሕይወት ወደ ሐዲስ ሕይወት የተሻገሩበት ታላቅ
መንፈሳዊ የነፃነት በዓል ነው፡፡ ክርስቲያኖች የትንሣኤን በዓል በታላቅ ደስታና መንፈሳዊ ስሜት
ያከብሩታል፡፡ ስለዚህም ከበዓላት ሁሉ የበለጠ ሆኖ ይታያል፡፡
 የበዓሉ_አከባበር = መድኀኒታችን ሞትን በሞቱ ድል መትቶ፣ ስሙና መቃብርን አጥፍቶ በሥልጣኑ
የተነሣው መጋቢት 29 ቀን በ 34 ዓ.ም እንደሆነ ታሪከ ቤተ ከርስቲያን ያስረዳል፡፡ የትንሣኤ በዓል
መከበር የጀመረው በቅዱሳን ሐዋርያትና በሰብዐ አርድእት፣ ኋላም በየጊዜው በተነሡት ተከታዮቹ
ምእመናን ነው፡፡ ድምቀቱና የአከባበር ሥርዐቱ ይበዛ ይቀነስ እንደሆን እንጂ መከበሩ ተቋርጦ
አያውቅም፡፡ «እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሰን» ሲወርድ ሲወራረድ ከዚህ በደረሰው ትውፊት
መሠረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ግብረ ሕማማቱን ስታነብ ሰንብታ
ለትንሣኤ እሑድ አጥቢያ ማታ በ 2 ሰዓት «ለጸሎት ተሰብሰቡ» የደወል ድምፅ-ታሰማለች፡፡ ካህናቱ
ተሰብስበው ሥርዐቱን በጸሎት ይጀምራሉ፡፡ ሕዝቡም ይሰበሰባል፡፡ ቤተ ክርስቲያኑንም ይሞላዋል፡፡
ካህናቱ ሁሉ ለጸሎተ ፍትሐትም፣ ለሥርዐቱም መዝሙረ ዳዊት፣ ነቢያት፣ ሰሎሞንና ውዳሴ ማርያም
ከደገሙ በኋላ «ተፈሥሒ ማርያም ለአዳም ፋሲካሁ» የሚለውን ግጥማዊ የደስታ መዝሙር
ይዘምራሉ፡፡
 ቀጥሎም ምንባባቱና ሌላውም ሥርዐት ከተፈጸመ በኋላ ጸሎተ አኰቴት ተደርሶ ዲያቆኑ «ወተንሥአ
እግዚአብሔር ከመ ዘንቃህ እምንዋም፣ ወከመ ኀያል ወኅዳገ ወይን፣ ወቀተለ ፀሮ በድኅሬሁ =
እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሣ፤ የወይን ስካር እንደተወው ኀያል ሰውም፣ ጠላቱን
በኋላው ገደለ፡፡» የሚለውን የዳዊት መዝሙር ለመስበክ = ለመዘመር ነጭ ልብሰ ተክህኖ ለብሶ አክሊል
ደፍቶ፣ የመጾር መስቀል ይዞ፣ እንደእርሱው ነጭ ልብሰ ተክህኖ በለበሱ ደማቅ የጧፍ መብራት
በሚያበሩና ድባብ = ጃንጥላ በያዙ ሁለት ዲያቆናት በግራ በቀኝ ታጅቦ ከመቅደስ ብቅ ብሎ በቅድስት
ይቆማል፡፡ መዝ. 77-65 ይህም በጌታችን መቃብር በራስጌና በግርጌ በታዩት መላእክት ምሳሌ ነው፡፡
ዮሐ.20-12 ዲያቆኑ ከላይ የተጠቀሰውን ምስባክ በረጅም ያሬዳዊ ዜማ በሰበከ ጊዜ ካህናቱ ከበሮ
እየመቱና በእርጋታ እያጨበጨቡ ተቀብለው ይዘምራሉ፡፡
 ሕዝቡም የቻለው በዝማሬው ያለበለዚያም በጭብጨባና በልልታ የደስታ ዝማሬው ተሳታፊ ይሆናል፡፡
ይህ ምስባኩ በዲያቆኑ 2 ጊዜ በመላው ካህናትም 2 ጊዜ ለመጨረሻ ጊዜ ዲያቆኑም መላው ካህናትም
አንድ ጊዜ ብለው 5 ጊዜ ይሆናል፡፡ 5500 ዘመን ሲፈጸም በጌታችን ሞትና ትንሣኤ ዓለም ለመዳኑ
ምሳሌያዊ ማስረጃ ነው፡፡
 ቀጥሎም ካህኑ ትንሣኤውን የሚያበሥር ወንጌል ከማቴዎስ፣ ከማርቆስና ከሉቃስ አውጥቶ ያነባል፡፡
ከዮሐንስ ወንጌል ያለው የትንሣኤው ወንጌል ኋላ ለቅዳሴው ጊዜ ይቆያል፡፡ ዮሐ. 20-1-09
በማስከተል የዲያቆኑን መስቀል ጨብጦ ከሊቃውንቱ መዘምራን ሥራው የሚመለከተው ወይም
የተመደበው ባለሙያ መዘምር «ትንሣኤከ ለእለ አመነ» የሚለውን እስመ ለዓለም ከቃኘ በኋላ ለበዓሉ
ተስማሚ የሆነው 2 አርያም ተመርቶ በመቋሚያ ይዘመማል፤ በማስከተልም «ዮም ፍሥሐ ኮነ
በሰንበተ ክርስቲያን፣ እስመ ተንሥአ ክርስቶስ እሙታን = ክርስቶስ ከሙታን ቀድሞ ተለይቶ
ተነሥቷልና በሰንበተ ክርስቲያን ዛሬ ደስታ ሆነ፡፡...» የሚለውን አንገርጋሪ ያመለጥናል = ይመራል፡፡
 በግራ በቀኝ እየተነሣ መዘምራኑም ይዘምሙታል ይጸፉታል፤ ያለዝቡታል፤ ወዲያውም «ብርሃነከ
ፈኑ፤ ለእለአመነ = ለአመነው ብርሃንህን ላክልን፡፡» የሚለውን እስመ ለዓለም እየወረቡ መብራት
እያበሩ ዑደት ያደርጋሉ = ቤተ ክርስቲያኑን በውስጥ ይዞራሉ፡፡
 በዚህ ጊዜ «በጨለማ የነበራችሁ ሕዝቦች ኑ የትንሣኤውን ብርሃን እዩ፣ ብርሃኑንም ወስዳችሁ
የብርሃኑ ተካፋይ ሁኑ፡፡» እያለች ቅ/ቤተ ክርስቲያን ስታዘጋጅ የሰነበተችውን ጧፍ እያበራች
ታድላቸዋለች፡፡ ሕዝቦቹም ካህናቱን ተከትለው በታላቅ ደስታና ድምቀት ዑደት ያደርጋሉ፡፡
 መዘምራኑና ካህናቱ ከዑደት ሲመለሱ «ይእቲ ማርያም» የተባለው የኪዳን ሰላም ይጸፋና ኪዳን
ተደርሶ ሲያበቃ እንደ ቦታው ደረጃ ፓትርያርኩ ወይም ሊቀ ጳጳሱ ወይም ደግሞ አለቃው፣ ቆሞሱ፣
ካህኑ ዘለግ ባለ ድምፅ በንባብ «ክርስቶስ ተንሥአሙታን = ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ፡፡» ሲል
ካህናቱና መዘምራኑ በዐቢይ ኀይል ወሥልጣን = በታላቅ ኀይልና ሥልጣን፡፡» ብለው ይቀበላሉ፡፡
አሁንም ካህኑ «አሰሮ ለሰይጣን = ሰይጣንን አሰረው» ባለ ጊዜ መላው ካህናት «አግዐዞ ለአዳም =
አዳምን ሐርነት ነጻነት አወጣው» ይላሉ፡፡
 ቀጠል አድርጎ ቄሱ «ሰላም፣ ፍቅር፣ አንድነት» ሲላቸው ሁሉም ካህናት «እምይእዜሰ = ከዛሬ
ጀምሮ» ብለው ይቀበላሉ፡፡ ቄሱም «ኮነ ፍሥሐ ወሰላም = ሰላምና ደስታ ሆነ» ብሎ ሦስት ጊዜ
ዐውጆ ሲያበቃ «ነዋ መስቀለ ሰላም» እያለ መስቀል ሲያሳልም ካህናትና ሕዝቡም «ዘተሰቅለ ቦቱ
መድኀኔዓለም» እያሉ ይሳለማሉ፡፡ ካህኑም «እግዚአብሔር ይፍታ» ይላል፡፡ ግብረ ሕማማት
ሲነበብበት ከሰነበተው ጠበልም ይረጫል፡፡ የተረፈውንም ጠበል ሕዝቡ ለበረከት ወደየቤቱ
ይወስደዋል፡፡
ከዚያም ልኡካኑ ለቅዳሴ እየተዘጋጁ ሊቃውንት መዘምራኑ ምስማክ መወድሱን ካዜሙ በኋላ
በመቋሚያ ይዘምሙታል፡፡ አያይዞም በዓመት ሦስት ጊዜ የሚዘመረውን «ይትፌሣሕ» የተባለውን
መዝሙር ቃኝተው ከዘመሙ በኋላ «ወምድርኒ ትገብር ፋሲካ፤ ተኀፂባ በደመ ክርስቶስ = ምድርም
በክርስቶስ ደም ታጥባ ፋሲካውን ታደርጋለች፡፡» እያሉ ይጸነጽላሉ፡፡ አያይዘውም የመዝሙሩን ሰላም
ይጸፋሉ፡፡
 ወዲያው መንፈቀ ሌሊት ሲሆን ቅዳሴ ተቀድሶ ይቆረባል፡፡ ከዚያም ዕጣነ ሞገር = በዕጣን ፈንታ
ቅኔው ተቁሞ ሠርሖተ ሕዝብ = የሕዝብ ስንብት ከሆነ በኋላ ለመፈሰክ ሕዝቡ ወደየ ቤቱ ይሔዳል፡፡
ሕዝቡ በየቤቱ፣ ካህናቱም ከቤተ ክርስቲያን በየአካባቢው ባህል በተለይ አክፋዮች መጀመሪያ ቅባት
አጥቶ የሰነበተ ሆድ እንዲለሰልስ የተሞቀ የተልባ ጭልቃ ይጠጣና የሹሮ ወጥ በቅቤ፣ በአይብ፣
የበረታም በዶሮ ወጥ፣ ወይም በበግና በከብት ሥጋ ወጥ ይገድፋል፡፡
 በእርጎ፣ በአይብ የተደራረበ እንጀራ በግፍልፍል የሚገድፉም አሉ፡፡ በአንዳንድ የሰሜኑ ሀገራችን ደግሞ
የተልባ፣ የኑግና የሱፍ ጭልቃ ከማር ጋር ታሽቶ ከተጠጣ በኋላ በእርጎ፣ በአይብ፣ በወተት፣ በቅቤና
ድልህ በተቀባ እንጀራ ይገድፋሉ፡፡ ሲነጋም ከጾሙ አጋማሽ ጀምሮ ወንዱ ለእርድ የሚሆነውን
ሰንጋውን፣ ሲቀልብ፣ በጉን ፍየሉን ሲሞክት ዶሮውን ሲመርጥ፣ ሲገዛ ሲለውጥ፣ ሰንብቶ ነበርና
በግልም በኅብረትም ያ ይታረዳል፡፡ ሴቶችም ቅቤውን ሲያነጥሩ፣ በርበሬውን ሲደልሁ፣ ለእንጀራና ዳቦ
የሚሆነውን ዱቄት ሲያዘጋጁ ለጠላ የሚሆነውንም እኸል ሲያሰናዱ አይቡን በልዩ ልዩ ቅመም መጣጣ
ሲያደርጉና ባዶ ማለትም ወገሚት የተባለውን በሽንኩርት፣ በጤና አዳም፣ ጣዕሙ እንዳይለወጥ
ሲቀምሙ ሰንብተው ዝግጅቱ ተከናውኖ ነበር፡፡ ጧትም ይህ የመግደፊያ ዝግጅት በየቤታቸው
ለሌላቸው ድኾች በየመንደሩ እየተዞረ «እንኳን ጾመ ልጓሙን ፈታላችሁ» እየተባለ ከሥጋውም፣
ከአይቡም፣ ከቅቤውም ከመጣጣሙም፣ ከእርጐውም ይታደላል፡፡ ከትንሣኤ እሑድ ጀምሮ እስከ
ዳግም ትንሣኤ ድረስ ሕዝበ ክርስቲያኑ «እንኳን ጾመ ልጓሙን ፈታላችሁ» እየተባባለ በመጠራራት
ዐብሮ ሲበላ ሲጠጣ ልዩ ልዩ ጨዋታ ሲጨዋወት ለንስሐ አባትና ለሽማግሌዎች ለወዳጅ ዘመድም
የአክፋይ ዳቦ፣ ወይም የሥጋ ወጥ ግፍልፍል ሲወስድ ይሰነብታል፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፡፡

በሕማሙ በከይነ፤ ወበትንሣኤሁ ተፈሣሕነ።


በሕማሙ_አዘንን፤ #በትንሣኤው_ደግሞ_ተደሰትን) ቅዱስ ያሬድ።
እንኳን አደረሳችሁ፡፡
በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ አሜን።

 ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሳ፥ ሰይጣንን አሰረው፥ አዳምን ነፃ አወጣ፥ ከእንግዲህ ወዲህ
ሠላም ደስታ ሆነ አሜን።
 ከትንሳዔ እሁድ በኋላ ያሉት እለታት ስያሜ ፦
1. ሰኞ ማዕዶት ይባላል፦ ማዕዶት ማለት መሻገር ፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ እለት በፋሲካችን
በክሮስቶስ ትንሳዔ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሀን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል
ወደ ገነት፣ ከአሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡
2. ማክሰኞ ቶማስ ይባላል፦ በዚህ እለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ ጌታዬና አምላኬ ብሎ
መመስከሩ ይዘከራል፡፡ (ዮሐ ፳፥፳፯-፳፱)
3.  ረቡዕ አልአዛር ይባላል፦ በዚህ እለት ትንሳዔ እና ህይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን
ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን። ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ የመቃብርን
ስርዐት ያጠፋ ትንሳዔ በድልም ያደረገ ንጉስ መሆኑን እንመሰክራለን።
4. ሀሙስ አዳመ ሀሙስ ይባላል፦ በዚህ እለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን
እንደተፈፀመ አዳምና ልጆቹ ነፃ እንደወጣን እናሶባለን፡፡
5.  አርብ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይባላል፦ በዚህ እለት ቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትሳዔ
ስለመመስረቷ ይሰበካል። ክርስቶስ ስለ እርሷ እራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንፅቶ
በትንሳዔው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል። ቤተ ክርስቲያን ስንል ህንፃውን ሳይሆን
አማኞችን ነው ክርስቶስ ለህንፃው አልሞተምና፡፡
6.  ቅዳሜ ቅዱሳት አንስት ይባላል፦ በዚህ እለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ
ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውን እና ትንሳኤውንም ቀድመው
ማየታቸው ይሰበካል፡፡
7. እሁድ ዳግም ትንሳዔ ይባላል፦ በዚህ እለት ክርስቶስ ለሶስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ
ሠላምን መስበኩ እና ስልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡

✞በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን ✞

"በቀናች ሃይማኖታችን እንጸናና እንጠነክር ዘንድ የአባቶቻችንን ትምህትና ተግሳፅ እናስተውል፤ የእለት
እለት መርሃችን ይሆኑን ዘንድም እንተግብራቸው፡፡"
ብሂለ አበው
☞ ‹‹እግዚአብሔር ሆይ አፈርና ትቢያ ሆኜ ሳለ ጻድቅ አድርገው ከሚቆጥሩኝ ሰዎች አድነኝ› /አባ
እንጦንስ/

☞‹‹ፍጡራንን መርምሮ ማወቅ ካልተቻልን ሁሉን የፈጠረ እርሱን መርምሮ ማወቅ እንደምን ይቻልናል››
/ቅዱስ አትናቴዎስ/
☞ ‹‹ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን ሁሉ የክርስቶስንም ፀጋና ክብር ሳይፈተኑ ማግኘት አይቻልም የዚህ
ዓለም ፈተናና እሳት ቶሎ ያልፋል ይጠፋል ኃጢያተኞች የሚገቡበት የገሀነም እሳት ግን ለዘላለም እንደ
ነደደ ይኖራል›› /ቅዱስ ሚናስ/
☞‹‹በማንም ላይ ክፋትን አትስሩ አትፍረዱ ይህንን ከጠበቃችሁ ርስቱን ትወርሳላችሁና›› /ታላቁ አባ
መቃርስ/
☞ ‹‹ብዙ ጊዜ ብዙ እናገራለሁ በመናገሬም አዝናልሁ በዝምታዬ ግን ያዘንኩበት ጊዜ የለም››
/ቅዱስ አርሳንዮስ/
☞ ‹‹ቤተክርስትያን መጠጊያችን ነች ቤተክርስትያን የኖኅ መርክብ ነች በውስጧ እንጠለላልን ከውጭዋ
ግን ማዕበልና ቀላያት ተከፍተዋል›› /ቅዱስ እንድርያስ/
☞ ‹‹ልባችንን ጠፊና በስባሽ ከኾነው ከምድራዊው ምኞት አርቀን ከበደል በንስሐ ነጹሕ ካደረግነው በጸጋ
መንፈስቅዱስ የተሞላን እንሆናለን›› /አባ አብርሃም መፍቀሬ ነዳያን/
☞‹‹ስጋዊ ፍላጎቶችን ማሸነፍ ለአክሊለ ህይወት የሚያበቃ ሰማዕትነት ነው››
/ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ/
☞ ‹‹የቤተክርስቲያን ህይወት በመስቀል ላይ ስለሆነ ፈተና ይበዛበታል ስለዚህ ከግል ህይወታችሁ ይልቅ
የቤተክርስቲያናችሁን አቋም አጠንክሩ›› /ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ/
☞‹‹ከመኝታህ በፊት የምታደርገውን ፀሎት ትተህ እንድትተኛ መንፈስህ ሲገፋፋህ እሺ ብለህ
አትቀበለው፡፡ እንዲያውም መዝሙረ ዳዊትን ጨምርና ሌሊቱን በሙሉ ስትፀልይ እደር›› /ቅዱስ ይስሀቅ
ሶርያዊ/
☞‹‹ኃጥያታችንን እኛ እያሰብን የምንፀፀት ከሆነ እግዚአብሔር ይረሳልናል ኃጥያታችንን እኛ እረስትን
የምንፅናና ከሆነ እግዚአብሔር ያስብብናል›› /ቅዱስ እንጦስ/ የአባቶቻችን ጸጋና በረከት ከሁላችን ጋር
ይሁን::

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር፡፡


ጥንታውያን አባቶች ስለ እመቤታችን !------------------------------- ቅዱስ አትናቴዎስ ስለ እመቤታችን
እንዲህ ብሎ ተናገረ ፡- የጥንታውያን አበው ልጆች ነን ፤የጥንቷ ኦርተዶክስ አማኞች ነን የሚሉ ተሐድሶ
መናፍቃን ይህን የጥንቱን ትምህርት ያምኑ ይሆን?
"አንቺ የተከበርሽ የተደነቅሽ ድንግል ሆይ ከየትኛውም ታላቅነት በላይ ታላቅ ነሽ፤ እንዳንቺ ያለ ታላቅነት
ያለው ርሱ ማን ነው? አንቺ የእግዚአብሔር ወልድ ማደሪያ ድንግል ሆይ ከፍጥረታት መኻከል ከማን ጋር
ላወዳድርሽ? ከኹሉም በላይ ታላቅ ነሽ፤ የዐዲስ ኪዳን ታቦት ወርቅን ሳይኾን ንጽሕናን የተጐናጸፍሽ!
እውነተኛው መና በውስጧ ያኖረችው መሶበ ወርቅ የተቀመጠባት ታቦት ነሽ ይኸውም ሥጋን
የተዋሐደው መለኮት ነው፤ ከለመለመችው ምድርና ከፍሬዋ ጋር ላነጻጽርሽን? ግን አንቺ ኹሉንም
ትልቂያቸዋለች ምክንያቱም “ምድር የእግሬ መረገጫ ናት” ተብሎ ተጽፏልና (ኢሳ 66፡1)
O noble Virgin, truly you are greater than any other greatness. For who is your equal in
greatness, O dwelling place of God the Word? To whom among all creatures shall I
compare you, O Virgin? You are greater than them all. O Covenant, clothed with purity
instead of gold! You are the Ark in which is found the golden vessel containing the true
manna, that is, the flesh in which divinity resides. Should I compare you to the fertile
earth and its fruits? You surpass them, for it is written: “The earth is my footstool” (Is
66:1).

ነገር ግን አንቺ ፍጹም የኾነውን የባሕርይ አምላክ እግር፣ ራስ እና መላ አካል ይዘሻልና፤ ሰማይ ታላቅ የኾነ
ቢኾንም ግን ያንቺ አቻ አይኾንም “ሰማይ ዙፋኔ ነው” ተብሎ ተጽፏልና (ኢሳ 66፡1)፤ አንቺ ደግሞ
የአምላክ ማደሪያ ነሽ፤ መላእክት እና የመላእክት አለቆች ታላቅ ናቸው ብልም አንቺ ከኹሉም ታላቅነት
በላይ ነሽ፤ ይኸውም መላእክት እና ሊቃነ መላእክት ባንቺ ማሕፀን ላደረው ለርሱ በረአድ የሚያገለግሉ
በመኾናቸው በፊቱ መናገር የማይችሉትን አንቺ በነጻነት ታናግሪዋለሽ፡፡ ኪሩቤልን ታላቅ ናቸው ብንልም
አንቺ ከነርሱ ታላቅነት በላይ ነሽ፤ ኪሩቤል የእግዚአብሔርን ዙፋን ይሸከማሉ (መዝ 80፡1፤ 99፡1)፤ አንቺ
ግን እግዚአብሔርን በእጅሽ ያዝሽው፤ ሱራፌልንም ታላቅ ናቸው ብልም አንቺ ከነርሱ ታላቅነት በላይ
ታላቅ ነሽ፤ ሱራፌል በክንፎቻቸው ፊታቸውን ይሸፍናሉ (ኢሳ 6፡2)፤ ፍጹም የኾነውን ጌትነቱን ማየት
አይችሉም አንቺ ግን ፊቱን እያየሽ እና እየዳሰስሽ ጡትን በከበረ አፉ ውስጥ አጥብተሻልና ከነርሱ
ትልቂያለሽ፡፡

But you carry within you the feet, the head, and the entire body of the perfect God. If I
say that heaven is exalted, yet it does not equal you, for it is written: “Heaven is my
throne” (ibid.), while you are God’s place of repose. If I say that the angels and
archangels are great—but you are greater than them all, for the angels and archangels
serve with trembling the One who dwells in your womb, and they dare not speak in his
presence, while you speak to him freely. If we say that the cherubim are great, you are
greater than they, for the cherubim carry the throne of God (cf. Ps 80:1; 99:1), while you
hold God in your hands. If we say that the seraphim are great, you are greater than them
all, for the seraphim cover their faces with their wings (cf. Is 6:2), unable to look upon
the perfect glory, while you not only gaze upon his face but caress it and offer your
breasts to his holy mouth….

ሔዋን የሙታን እናት ናት “ኹሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲኹ ኹሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን
ይኾናሉና” (1 ቆሮ 15፡22) እንደተባለ፤ ሔዋን ከዛፍ ፍሬ ወስዳ ባሏ ከርሷ ጋር እንዲበላ አድርጋለች፤
በዚኽ ምክንያት እግዚአብሔር “ከዚኽ በበላችኊ ጊዜ ትሞታላችኊ” ካላቸው ዛፍ በሉ (ዘፍ 2፡17)፤
ሔዋን ፍሬውን ወስዳ የተወሰነውን በልታ የተወሰነውን ለባሏ ሰጠችው፤ ርሱም በላው ሞተም፡፡ አንቺ
ብልኅ ድንግል ሆይ በአንቺ ግን የእግዚአብሔር ልጅ የኾነው የሕይወት ዛፍ ዐደረ፤ በእውነትም አካሉን
ሰጥቶናል እኛም ከርሱ በልተናል፤ ሕይወት ለኹሉም እንዲኽ ተሰጠ፤ ባንቺ በተወደደው ልጅሽ
በእግዚአብሔርነቱ ምሕረት ኹሉም ወደ ምሕረት መጣ፤ በዚኽም ምክንያት ነው መንፈስሽ በአምላክሽ
በመድኀኒትሽ ሐሤት ያደረገው"

As for Eve, she is the mother of the dead, “for as in Adam all die, even so in Christ shall
all be made alive” (1 Cor 15:22). Eve took from the tree and made her husband eat of it
along with her. And so they ate of that tree of which God had told them: “The day you
eat of it, you shall die” (Gen 2:17). Eve took from it, ate some of it, and gave some to her
husband with her. He ate of it, and he died. In you, instead, O wise Virgin, dwells the Son
of God: he, that is, who is the tree of life. Truly he has given us his body, and we have
eaten of it. That is how life came to all, and all have come to life by the mercy of God,
your beloved Son. That is why your spirit is full of joy in God your Savior!
St. Athanasius, Fourth Century Homily of the Papyrus of Turin, ed. T. Lefort, in Le
Muséon 71 (1958): 216-217 .

 ምንጭ: ክብረ ክህነት [ዲ/ን ሄኖክ ሀይሌ] ፠((የንስሐ አባት መያዝ ለምን ያስፈልጋል???))፠
============================
ጌታችን " በወንጌል በቀን የሚሄድ ሰው አይሰናከልም የዚህን አለም ብርሃን ያያልና በጨለማ
የሚሄድ ግን ይሰናከላል!!” ብሎ ተናግል:: የዚህ ቃል ትርጉም አንድም በምክረ ካህን በ ፈቃደ ካህን
የሚኖር ሰው ነፍሱ ከሃጢአት እንደምትጠበቅ ያስረዳል፡፡ የዚህ አለም ብርሃን የተባሉት ጌታችን
“እናንተ የአለም ብርሃን ናችሁ” ያላቸው ካህናት ሲሆኑ "በቀን የሚሄድ" የተባለው ደግሞ በምክረ
ካህን የሚኖር ሰው ነው፡፡
 በወንጌል “ ለወይን ስፍራዉ ሰራተኞችን ይቀጥር ዘንድ በማለዳ ወጣ በአስራ አንድ ሰአትም
ቀጠረ” የሚለዉ ምሳሌ፡ ማለዳ በተባለ የልጅነት እድሜ ላይ የሚጠብቅ የሚኮተኩት መምህረ
ንስሃ መያዝ እንደሚያስፈልግ ያሳያል፡፡ ዕድሜያችን ለሀጢአት በደረሰችበት ቅፅበት ለንስሃም(ለ
ኑዛዜም) ትደርሳለችና፡፡
 በሲራክ 6-6 ላይ “ብዙ ሰዎች ወዳጆች ይሁኑህ ከብዙዎች አንዱ ምክርህን
የምትነግረው ከልቡናህ ጋር አንድ ይሁን፡፡” የሚለው ቃል ምእምናን ስለ ሐይማኖትና ምግባር
የሚያስተምሯቸው ብዙ ካህናት ሊኖሩዋቸው ቢችሉም ከብዙዎች አንዱ ግን ንስሃቸውን
የሚናዘዙለት መምህረ ንስሃ ሊሆናቸው እንደሚገባ ያጠይቃል፡፡
 አዳም በገነት ለሰባት አመታት ከቆየ በሁዋላ በዲያቢሎስ ተፈትኖ እንደወደቀ፡
በሃጢያት መፈተንና መዉደቅ ለሰው የሚፀናበት ዕድሜ ከሰባት አመት ጀምሮ
ስለሆነ ወደ ንስሃ አባት መቅረብ ይኖርበታል፡፡
 በምክረ ካህን መኖር ራሱ ትልቅ መንፈሳዊ ማእረግ ነው የአዲስ ኪዳን
ክርስቲያኖች ከብሉይ ኪዳን ሰዎች የሚከብሩትን ያህል በምክረ ካህን የሚኖሩ ምእምናን
ከአማኒያን በላይ የከበሩ ናቸዉ፡፡
 ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በ 12 አመቱ ከመምህራን ጋር መገናኘቱ እኛም
ከልጅነታችን ጀምሮ ከ መምህራን አባቶች ጋር እነድንገናኝ አብነት ይሆን ዘንድ
ነዉ (ማቴ 20-2) ይቀጥላል፡፡

#ሀጢያትን_መናዘዝ_ለምን_አስፈለገ??
-----------------------------------
ሀጢያትን ለእግዚአብሄር በካህን በኩል መናዘዝ መፅሃፍ ቅዱሳዊ መሰረት ያለዉ
ጠቃሚ ጉዳይ ነዉ፡፡ እግዚአብሄር አዳም በበደለ ጊዜ “አዳም ሆይ ወዴት ነህ?”
ብሎ የጠየቀዉ አዳም እንዲናዘዝ ስለፈለገ እንጂ አዳም ያደረገዉን ሳያዉቅ ቀርቶ አልነበረም፡፡
“እምቅድመ ይፍጥሮ ለአዳም የአምር ግብሮ” ”አዳምን ከመፍጠሩ በፊት ስራዉን ያዉቃል” እንዲል፡፡
አዳምም እግዚአብሄር በጠየቀዉ ጊዜ ”ከእኔ ጋር እንድትሆን የሰጠኸኝ ሴት እርስዋ ከዛፉ ሰጠችኝና በላሁ”
በማለት ተናዝዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በተለያዩ ቦታዎች ሰዎች ሀጢያታቸዉን ይናዘዙ እንደነበር
በመፅሀፍ ቅዱስ ተገልጿል፡፡ ሐዋ 19-18 ፡ማቴ 3 5-6፡ዘሌ 5-16፡ ኢያ 2- 19፡፡ ይሁን እንጂ “ሀጢያቴን
ለመተዉ ከፈቀድኩ አይበቃም ወይ? መናዘዙ ለምን አስፈለገ?” የሚሉ ሰዎች አሉ ሀጢያትን በካህን ፊት
መናዘዝ ግን የሚከተሉት ጠቀሜታዎች አሉት፡-

☞ሀጢያትን በዝርዝር በካህን ፊት መናዘዝ ዳግመኛ በዚያ ሀጢያት ላለመያዝ ሀይልን ይሰጣል፡፡ ቅዱስ
ዮሃንስ አፈወርቅ “በበደሉ ላይ ድፍረትና ሽንገላን የሚጨምር (ሀጢያት ሰርቶ እንዳልሰራ ዝም የሚል)
ከዚያች ሀጢያት መጠበቅ አይችልም፡፡ እርስዋን በምትመስል ሀጢያት ከመዉደቅም አይድንም” እንዳለ፡፡
በ ንጉስ የሚሽረዉና የሚሾመዉን ግራና ቀኝ አቁሞ የሚሽረዉን ወቅሶ የሚሾመዉን አሞግሶ
እንደሚያከብር ያለፈ ሀጢያታችንን በካሀኑ ፊት ስንዘረዝርም ያለፈዉን ሀጢያታችንን ሽረን
በሚመጣዉም ህይወት ያንን ሀጢያት ላለመድገም እየወሰንን ነው፡፡

☞ ኑዛዜ ያሳቅቃል፡፡ መሳቀቁ ደግሞ ለሰራነዉ ሀጢያት ዋጋ ነዉ፡፡ በፍርድ ቀን ጌታ በሰማይ መላእክት ፊት
ሀጢያታችንን ገልጦ ከሚያሰቅቀን ይልቅ እኛዉ እራሳችን እዚሁ እንደኛዉ ደካማ ሰዉ በሆነው በካህኑ
ፊት በመናዘዝ ለሰራነው እጅግ ግዙፍ ሃጢያት የምንቀበለው ኢምንት ቅጣት ነው፡፡

☞በሽታውን የደበቀ መድሃኒት የለውም እንደሚባለው የነፍሱን ደዌ ሀጢያቱን


የሚደብቅም እንዲሁ መፍትሄ አያገኝም፡፡ የካህኑን ፀሎትና ምክርም ያጣል፡፡
“ሀጢያቱን የሚደብቅ /የሚሰውር አይለማም፡ የሚናዘዛትና የሚተዋት ግን ምህረትን ያገኛል”
እንደተባለ፡፡ (ምሳ 8-13)

 #ሀጢያታችንን_ለምን_በቀጥታ_ለእግዚአብሄር_ብቻ_አንናዘዝም??
❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖
 ሀጢያትን ለካህን መናዘዝ ለእግዚአብሄር አለመናዘዝ አይደለም፡፡ ሀጢያትን ለካህን መንገር
ለእግዚአብሄር መናዘዝና ክብር መስጠት ነው፡፡ እያሱ እንዳለ “ልጄ ሆይ ለአምላክ ክብርን ስጥ፡
ለእርሱም ተናዘዝ፡ ያደረግከውንም ንገረኝ አትሸሽገኝ” ኢያሱ 7-19፡፡ ኢያሱ “ክብርን ስጥ” ያለው
ለእግዚአብሄር: “ተናገር” ያለው ግን ለራሱ መሆኑ ሀጢያትን ለካህን መናዘዝ ለእግዚአብሄር ክብር
መስጠት እንደሆነ ያሳየናል፡፡ አበዉ ካሀናትም ኑዛዜን ከተቀበሉ በኋላ “እግዚአብሔር ይፍታህ”
እንጂ ”ፈትቼሃለሁ ” አይሉም፡፡ ይህም ምንም በእሱ ፊት ብንናገርም ሰሚዉም ሆነ በእነርሱ እጅ
ስርየት የሚሰጠዉ እርሱ ባለቤቱ ስለሆነ ነው፡፡ ”ሁለት ወይም ሶስት በሚሆኑበት በዚያ
በመካከላችሁ እገኛለሁ” ብሎ ቃል የገባ አምላክ በአናዛዡ ካህንና በተናዛዡ ምእምን መካከል ሆኖ
ይሰማል፡ ስርየትንም ይሰጣል፡፡
 ሰው ሲታመም ሀኪም ቤት ሄዶ በሀኪሙ ፊት ”ቆረጠኝ ወጋኝ. . . ” እያለ
ህመሙን እንደሚያብራራው ሁሉ፡ በእግዚአብሔር ቤት ውስጥ ያሉት ካህናትም የነፍስ ሀኪሞች
ናቸውና እያንዳንዱን የነፍስ በሽታ (ሀጢያት) በዝርዝር በእነርሱ ፊት ልንናዘዝ ይገባል፡፡ በሀኪሙ
ፊት ምንናዘዘው የእግዚአብሔርን ፈዋሽነት ክደን እንዳልሆነው ሁሉ በካህናት ፊት
የምንናዘዘውም የእግዚአብሔርን ሰሚነት ክደን አይደለም፡፡
 ለምን በቀጥታ ለእግዚአብሔር አልናዘዝም ማለት በራሱ ትዕቢት ነው፡፡ ንስሃ የሚገባ ሰው ሊል
የሚገባው ”ከበደሌ ብዛት የተነሳ ቀና ብዬ የሰማይን ርዝመት አይ ዘንድ እንኩዋ አግባቤ አይደለም”
ነው(ፀሎተ ምናሴ)፡፡
 በወንጌል እግዚአብሔር ”እርስ በርሳችሁ ሀጢያታችሁን ተናዝዙ” ያለው የሰው ልጅ ከፈጣሪ
ይልቅ ሰውን ስለሚፈራና ስለሚያፍር በሃጢያቱ እንዲሳቀቅ ስለፈለገ ነው፡፡
እግዚአብሔር ያየኛል ይሰማኛል ሳይል የሰራውን ሀጢያት እንዴት
እግዚአብሔር ያየኛል ይሰማኛል ብሎ ይናዘዛል? እነዚህ ከእግዚአብሔር ይልቅ
ሰውን የሚፈሩትን መጽሐፍ እንዲህ ይላቸዋል ”እስመ ዐይነ ሰብእ ያፈርሆሙ
ወኢየአምሩ ከመ አይነ እግዚአብሔር ያበርህ እምእዕላፍ ፀሀይ” ”የሰው ዐይን
ያስፈራቸዋል፡ የእግዚአብሔር አይን ግን ከብዙ አእላፍ ፀሀያት ይልቅ
እንደሚያበራ አያውቁም!!!”
 አንድ ምእመን ንስሃ በሚገባበት ጊዜ ሃጢያቱን ሳያድበሰብስ በዝርዝር ለካህኑ
በሚገባ መልኩ መናዘዝ አለበት ፡፡ እንዳው በደፈናው “እኔ ያልሰራሁት ሃጢያት የለም ” ”አድርጉ
ከተባለው ውስጥ ያደረግኩት አንድም መልካም ነገር የለም!” እያሉ የብልጠት ኑዛዜ መናዘዝ
አይገባም፡፡ አንድ በሽተኛ በሃኪም ፊት ”ታምሜአለሁ! ” ”በሽታ የተባለ ሁሉ አለብኝ!” በማለት
መድሃኒት እንደማያገኝ ሁሉ ሃጢያቱን በዝርዝር እና በግልፅ ያልተናገረም በትክክል ስርየት
አያገኝም፡፡
 ☞አንድ ምእመን ስለ ሃጢያቱ በግልፅ ሊናገር እና ሊዘረዝር ይገባል ሲባል ግን
በሆነው ባልሆነው ”እኔ ሃጢያተኛ ነኝ” ሊል ይገባል ማለት አይደለም፡፡ ”ድሃ ድህነቱን በአፉ
ይጠላታል” ሲራ 13-24 እንዳለ ”እንደኔ ሃጢያተኛ ማን አለ?” እያሉ ሃጢያትን በአፍ መጥላት ገና
ከሀጢያት ፍቅር ያለመላቀቅ ምልክት ነው፡፡ ሃጢያትን የሚጠላት በንስሃ ይርቃታልና፡፡ ሃጢያተኛ
ነኝ እያሉ በማወጅ ንጹሃን ትሁታን የሚመስላቸው አሉ፡፡ ትሁታን ግን ቅዱስ ዮሃንስ አፈወርቅ
እንዳለው:
  #ሃጢያተኛ_ነኝ_የሚሉት_ሳይሆኑ_ሃጢያተኛ_ሲባሉ_የሚታገሱት_ናቸው፡፡

☞በኑዛዜ ወቅት ትንኝን እያጠሩ ግመልን እንደመዋጥ ታላላቅ ሃጢያቶቻችንን


ከጎን ትተን ጥቃቅኑን ብቻ መናገር ስህተት ነው፡፡ ሲሰሩት ያልፈሩትን ሃጢያት
ሲናገሩት መፍራት አይገባምና፡፡ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በአርጋኖን ዘረቡዕ 7-5 እንዲህ እንዳለ”
ሃጢያቴን ለመናገር ለምን አፍራለሁ? አለመናዘዜስ ለምንድን
ነው? እኔ ሀጢያቴን ብሰውረው ሃጢያቴ ራሱ ሊከሰኝ ይጮሃል፡፡ እንኪያስ እንዳልበደለ ለምን
ዝም እላለሁ? የሰራሁትን ክፉ ስራዬ ያሳጣኛል እኔ እንዳልሰራ ለምን እሆናለሁ? የሚዘልፈኝ
አልሻም፡ እኔ ራሴ ለራሴ የራሴን ዘለፋ አነባለሁ እንጂ::”
 ☞በኑዛዜ ወቅት ለሀጢያት ምክንያት መደርደርና የሌሎችን ሀጢያት አክሎ
መናገር አይገባም ”እገሌ እንዲህ አድርጎ ስለገፋፋኝ እንዲህ አድርጌ ነበር”
አያሉ ሌላውን መክሰስና ምክንያት መስጠት ይቅር ሳይሉ ይቅርታ መሻት ነውና፡፡ ጌታችንም
በወንጌል ”ከሳሾችሽ ወዴት አሉ?” ያላትን ሴት ”አኔም
አልፈርድብሽም” ብሎ በይቅርታ ያሰናበታት ስለ ከሳሾችዋ አንዳች ባለመናገሩዋ ነበር (ዮሀ 8-
11)፡፡
 ☞ሰው ሆኖ የማይበድል እንጨት ሆኖ የማይጨስ የለምና እንዲሉ ሰው ሁልጊዜ
ከበደል ንጹህ ይሆን ዘንድ አይችልም በንስሃ ሃጢያቱን የሚናዘዝ ሰው ዳግመኛ
አይበድልም ማለት አይደለም፡፡ ከንስሃ በሁዋላ በሃጢያት ተፈትነን ብንወድቅ
ተስፋ ሳንቆርጥ ወዲያው ንስሃ ልንገባ ይገባል፡፡ ”መልሼ ልበድል ለምን ንስሃ
እገባለሁ” ማለት ግን ”መልሶ ለሚርበኝ ለምን እበላለሁ” ”መልሼ ለምቆሽሽ
ለምን እታጠባለሁ” እንደ ማለት ነው:: ቅዱስ ዮሃንስ አፈወርቅ ”መውደቅ
አዳማዊ ነው ወድቆ አለመነሳት ግን ዲያቢሎሳዊ ነው” እንዳለው ተሰፋ ቆርጦ በንስሃ መነሳት
ይኖርብናል እግዚአብሄር ይቅር ማለት ሳይሰለቸዉ ሰው ይቅር በለኝ ማለት ሊሰለቸው አይገባም::
ይቆየን፡፡
 ምንጭ፡ ክብረ ክህነት【ዲ/ን ሄኖክ ሀይሌ】

 እንኩዋን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የኪዳን በዓል በሰላም አደረሳችሁ

 7 ቱ ኪዳናት

 =>'ተካየደ' ማለት 'ተስማማ: ተማማለ' እንደ ማለት ሲሆን 'ኪዳን' በቁሙ 'ውል: ስምምነት'
እንደ ማለት ነው:: ይኸውም እግዚአብሔር ከሰዎች ጋር: ሰዎችም ከሰዎች ጋር የሚያደርጉት
ሊሆን ይችላል:: ልዩነቱ የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ቅዱስና የማይለወጥ መሆኑ ነው::

 እግዚአብሔር አምላክ ከሥነ ፍጥረት ጀምሮ በየጊዜው ከብዙ ወዳጆቹ ጋር ኪዳንን አድርጉዋል::
ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም እነዚህን ኪዳናት ጥቅልል አድርጋ 7 እንደ ሆኑ ታስተምራለች::
ስለዚህም ዛሬ ፈጣሪ ቢረዳን እነዚሁን 7 ኪዳናት በጥቂቱ እንመለከታለን::

 "ኪዳነ ተካየድኩ ምስለ ኅሩያንየ" "ከመረጥኩዋቸው ጋር ቃል ኪዳንን አደረግሁ" (መዝ. 88:3) 1.


+" ኪዳነ አዳም "+

 =>አዳም ማለት የእግዚአብሔር ድንቅ ፍጥረት: የፍጡራን አስተዳዳሪ: ነቢይ: ካህንና ንጉሥ ነው::
እግዚአብሔር ከአዳም ጋር አስቀድሞ በእጸ በለስ አማካኝነት ቃል ኪዳን ነበራቸው:: ነገር ግን
አባታችን በዲያብሎስ ሴራ በመረታቱ ኪዳኑ ፈረሰ:: (ዘፍ. 3:1)

 +አዳምና ሔዋን ተጸጽተው ቢያለቅሱ ግን አዲስ የኪዳን ተስፋ: "ከልጅ ልጅህ ተወልጄ
አድንሃለሁ" የሚል ኪዳንን ተቀበሉ:: (ቀሌምንጦስ: ገላ. 4:4)

+" ኪዳነ ኖኅ "+


=>ከአዳም እስከ ኖኅ ድረስ ባሉት 10 ትውልድ ዓለም በዓመፃ ተሞላች:: ቅዱስ ኖኅ በደግነቱ
መርከብ ሠርቶ ቤተሰቡን ሲያተርፍ ዓለም በማየ ሥራዌ ጠፋች:: ከመርከቡ ከወጣ በሁዋላ ኖኅና
እግዚአብሔር በቀስተ ደመና ምልክትነት ቃል ኪዳን ተጋቡ:: "ኢያማስና ለምድር ዳግመ በማየ
አይኅ" እንዲል:: (ዘፍ. 9:12)
+" ኪዳነ መልከ ጼዴቅ "+
=>መልከ ጼዴቅ የእግዚአብሔር ካህኑ: የክርስቶስም ምሳሌው የሆነ የሳሌም ንጉሥ ነው:: በ 15
ዓመቱ መንኖ: አጽመ አዳምን ይዞ: በቀራንዮ በሕብስትና በወይን ያስታኩት ነበር::

+እግዚአብሔር ለመልከ ጼዴቅ: በሐዲስ ኪዳን ለምትሠራው ክህነትና ምሥጢረ ቁርባን ምሳሌ
አድርጐ በቃል ኪዳን አትሞታል:: በዚህም ተሰውሮ ይኖራል እንጂ ሞትን እስካሁን አልቀመሰም::
ይህም ካህኑ መልከ ጼዴቅ ከአብርሃም ጋር በተገናኙበት ጊዜ ተገልጧል:: (ዘፍ. 14:17, ዕብ. 7:1)

+" ኪዳነ አብርሃም "+


=>ቅዱስ አብርሃም የሕዝብና የአሕዛብ አባት: ሥርወ ሃይማኖት: የጽድቅም አበጋዝ ነው:: ስለ
ፍቅረ እግዚአብሔር ሲል ከርስቱና ከወገኖቹ ተለይቶ በቅድስና ኑሯልና እግዚአብሔር "በዘርሕ
አሕዛብ ይባረካሉ" አለው:: (ዘፍ. 12:1) የቃል ኪዳን ምልክትም ይሆነው ዘንድ ግዝረትን ሰጠው::
(ዘፍ. 17:1-14)

5. +" ኪዳነ ሙሴ "+


=>ቅዱስ ሙሴ የነቢያት አለቃ: የእሥራኤል እረኛ: የእግዚአብሔር ሰው እና ፍጹም ትሑት
(የዋህ) ሰው ነው:: በፈጣሪው ትዕዛዝ እሥራኤልን ከግብጽ ባርነት አውጥቶ ለ 40 ዘመናት በበርሃ
ሲመራቸው ከእግዚአብሔር የኪዳንን ጽላትና አሠርቱን ትዕዛዛት ተቀብሏል:: (ዘጸ. 20:1,
31:18)

6. +" ኪዳነ ዳዊት "+


=>ቅዱስ ዳዊት ሥርወ ነገሥት: ጻድቅ: የዋህና ቡሩክ የሆነ አባት ነው:: እግዚአብሔር ከእረኝነት
ጠርቶ ንጉሥ አድርጐ ሹሞት "ከሆድህ ፍሬ በዙፋንህ ላይ አኖራለሁ" (መዝ. 131:11) ሲል
ምሎለታል:: አክሎም ሰፊ ቃል ኪዳን ሰጥቶ "አልዋሰሽህም" ብሎ ሲምልለት እንመለከታለን::
(መዝ. 88:35)

7. +" ኪዳነ ምሕረት "+


=>በብሉይ ኪዳን የነበሩ 6 ቱ ኪዳናት በዘመናቸው ክቡርና ሕዝቡን ከመቅሰፍት ይታደጉ የነበሩ
ቢሆንም ከሲዖል ማዳን ግን አልቻሉም:: ስለዚህም አንድ ፍጹም ኪዳን ያስፈልግ ነበር:: ይህን
ፍጹም ኪዳን ይፈጽም ዘንድም ከቅድስት ሥላሴ አንዱ ወልድ ከሰማያት ወርዶ በድንግል
ማርያም ማሕጸን አደረ::
+በፍጹም ተዋሕዶም በሕቱም ድንግልና ተወልዶ: አድጎ: ተጠምቆ: አስተምሮ: ሙቶ: ተነስቶና
ዐርጐ ሥጋ ማርያምን በዘባነ ኪሩብ አስቀመጠው:: ኪዳነ ምሕረት (የምሕረት ኪዳን) የምንለው
አንዱ ታዲያ ይሔው ነው::
+የጌታችን መጸነሱ: መወለዱ: መሰደዱ: መጠመቁ: ማስተማሩ: ሥጋውንና ደሙን መስጠቱ:
መሰቀሉ: መሞቱና መነሳቱ: ማረጉና መንፈስ ቅዱስን መላኩ በአንድ ላይ ኪዳነ ምሕረት ይባላል::
ታዲያ ይህ ሁሉ የተደረገው በሥጋ ማርያም ነውና የኪዳኑ ባለቤት እመቤታችን ቅድስት ድንግል
ማርያም ናት::
+የእርሷ ኪዳን 6 ቱን አበው ኪዳናት ፍጹም በማድረጉ የኪዳናት ማሕተም ይባላል:: የድንግል
ማርያም ኪዳኗ ከሲዖልና ከገሃነም ሊታደገን አቅሙ አለውና:: መድኃኒታችን ክርስቶስ ለድንግል
እናቱ ቃል ኪዳኑን ያጸናላት ደግሞ ካረገ ከዓመታት በሁዋላ ጐልጐታ ላይ ነው::

+እመ ብርሃን በዚያ ቁማ ስለ ኃጥአን ስታለቅስ "እናቴ ሆይ! በስምሽ ያመነውን: በቃል ኪዳንሽ
የተማጸነውን እምርልሻለሁ" ብሎ ደስ አሰኝቷታልና:: ይሔው በእመ ብርሃን ምልጃና ቃል ኪዳን
ምዕመናን ከመቅሰፍትና ከገሃነመ እሳት ማምለጥ ከጀመሩ 2 ሺ ዓመታት ሆኑ:: ዛሬም እኛ
ኃጥአን ልጆቿ ከእሳት እንደምታድነን አምነን በጥላዋ ሥር እንኖራለን::
*" ኢትዝክሪ ብነ አበሳነ: ኃጢአተነ: ወጌጋየነ: ማርያም እሙ ለእግዚእነ: በኪዳንኪ: ወበስደትኪ
ድንግል ተማሕጸነ::"
"ድንግል ሆይ! ኃጢአታችን: አበሳችንና በደላችንን አታስቢብን ዘንድ በስደትሽና በኪዳንሽ
ተማጽነናል::"

=>የአርያም ንግሥት: የሰማያውያንና ምድራውያን ኁሉ እመቤት: የአምላክ እናት: ቅድስት:


ስብሕት: ክብርት: ልዕልት: ቡርክት: ፍስሕትና ጥዕምት የሆነች ድንግል ማርያም የድኅነታችን
መሠረት: ላመኑባት አንገት የማታስደፋ እውነተኛ አማላጅ ናት::
+በዚህች ዕለት የካቲት 16 ስለ ወገኖቿ የሰው ልጆች ፍቅር በእንባ ያቀረበችውን ልመና የባሕርይ
አምላክ የሆነ ልጁዋ ተቀብሎ በማይዋሽ ንጹሕ አንደበቱ ቃል ኪዳን ገብቶላታል:: በስምሽ ያመነ
በቃል ኪዳንሽ የተማመነ እሳት አያይም ብሏታል::

=>+"+"+ . . . ኤልሳቤጥም የማርያምን ሰላምታ በሰማች ጊዜ ፅንሱ በማኅፀንዋ ውስጥ ዘለለ::


በኤልሳቤጥም መንፈስ ቅዱስ ሞላባት:: በታላቅ ድምፅም ጮኻ እንዲህ አለች:- አንቺ ከሴቶች
መካከል የተባረክሽ ነሽ: የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው:: የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ
እንዴት ይሆንልኛል? እነሆ የሰላምታሽ ድምፅ በጀሮየ በመጣ ጊዜ ፅንሱ በማኅፀኔ በደስታ
ዘሎአልና:: ከጌታ የተነገረላት ቃል ይፈፀማልና ያመነች ብፅዕት ናት:: +"+"+ (ሉቃ. 1:39)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር

ለምን 55 ቀን ጾምን?
ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ይህንን የአብይን ፆም የቀናት ቁጥር 55 አድርገው ሲወስኑ ያለ
አንዳች ምክንያት ሳይሆን በምስጢር ነው። ይሄውም እንዴት ነው ቢሉ ፆሙ 55 ቀን የሆነበት
የመጀመረያው ምክንያት በነዚህ በሚፆሙት በ 55 ቱ ቀናት መሀከል (8 ቅዳሜና፣ 7 እሁዶች
በአጠቃላይ 15 ሰንበታት) አሉና እነዚህ ሰንበታት ደግሞ ስለማይፆሙ እነርሱን ጌታችን
ከፆማቸው ከ 40 ው ቀናት ጋር በመደመር 55 ቀናትን እንድንፆም አድርገውናል ።

ሌላውና የአብይ ፆምን 55 ቀን የምንፆምበት ሁለተኛው ምክንያት በፆሙ የመጀመሪያና


የመጨረሻውን ሳምንታት በመቁጠር ነው። እነዚህ ሁለት ሳምንታት የመጀሪያው ሳምንት "ጾመ
ሕርቃን" ሲሆን የመጨረሻው ሳምንት ሰሞነ ሕማማት ይባለል።
ሕርቃን የአንድ ንጉስ ስም ነው ይህ ታላቅ ንጉስ በመስቀል ጦርነት ጊዜ ለክርስቲያኖች ተዋግቶ
የጌታችንን መስቀልን ከአህዛብ እጅ ስላስመለሰ ለዚህ ውለታው መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ከዘወረደ
እስከ ቅድስት ያለው የፆም ክፍል በእርሱ ስም ተሰይሞ እንዲፆም ሊቃውንት ደንግገዋል።

በተመሳሳይ በአብይ ፆም ከሆሳዕና በኋላ ያለው የመጨረሻውን ሳምንት የጌታችንና የአምላካችን


የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መከራ መስቀል የምናስብበት ጊዜ ነውና ሰሞነ ህማማት
ተብሎ እንዲታወስና እንዲፆም አድርገዋል። በነዚህ ከፊትና ከኋላ በገቡት ሁለት ሳምንታት
አማካኝነት የፆሙ ቀናት ቁጥር ከፍ ብሏል ማለት ነው። ልክ እንደ ላይኛው ሁሉ እነዚህንም
ሁለት ሳምንታት ብናነሳቸው የምንፆመው 40 ቀናት ይሆናል ማለት ነው።
በአጠቃላይ የአብይ ፆምን 55 ቀን አድርገን የምንፆመው ከላይ ባየናቸው ምክንያቶች ነው።

በዐቢይ ጦም መግቢያ የተሰጠ ትምህርትየእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን እንደዚህ በልጆቿ


ስትደምቅ እናንተም ጉባኤውን ለመታደም ደስ ብሏችሁ ተሰባስባችሁ ስትመጡ ዐይቼ ሐሴት
አደረግሁኝ፤ ደስም አለኝ፡፡ ፊታችሁ እንዴት በደስታ እንደ ተመላ ስመለከት ጠቢቡ “ልብ ደስ
ሲለው ፊት ይበራል” እንዳለው ልባችሁ ምን ያህል እንደ ተደሰተ ተገነዘብሁኝ (ምሳ.15፥13)፡፡
በመኾኑም፥ ዛሬ ማለዳ የተነሣሁት ከወትሮው በተለየ ትጋት ነው፡፡ ይኸውም ይህን መንፈሳዊ
ደስታ ከእናንተ ጋር እንድካፈልና ቀጣዩ ወራት ቁስለ ነፍሳችሁ ድኅነት የሚያገኝበት ወርሐ ጾም
መኾኑን አበሥራችሁ ዘንድ ነው፡፡ የኹላችንም ጌታ ልዑል እግዚአብሔር፥ ልክ እንደ ደግ አባት
ባለፉት ወራት ለሠራነው ኃጢአት ሥርየት እናገኝበት ዘንድ ሽቶ መድኃኒት የሚኾን ቅዱስ
ጾምን አዘጋጅቶልናልና፡፡

ስለዚህ የነፍሳችን ጠባቂ (እግዚአብሔር) የሕመማችንን ፈውስ የምናገኝበትን መድኃኒት


ስላዘጋጀልን እያመሰገንን ወርሐ ጾሙን ደስ ብሎን ልንቀበለው ይገባናል፡፡ ከእኛ መካከል ጾም
በመግባቱ አንድስ እንኳን የሚከፋው ወይም የሚበሳጭ ሊኖር አይገባም፡፡ ወርሐ ጾሙን እንዲህ
ደስ ተሰኝተን መቀበላችንን ዐይተውም አሕዛብ ይፈሩ፤ አይሁድም ይራዱ፡፡ በእኛና በእነርሱ
መካከል ሰፊ ልዩነት እንዳለ ዐይተውም ይማሩ፡፡ የእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን በዓል
የምትሠራው ምእመናን ራሳቸውን መግዛት እንዲችሉ፣ በበጎ ምግባር ያጌጡ ያሸበረቁ እንዲኾኑ
እንደ ኾነ፥ እነርሱ ግን በዓላትን የሚያደርጉት በዘፈንና በስካር ይህንም በመሰለ በሌላ ጸያፍ ግብር
ለመንከባለል እንደ ኾነ ለይተው ይወቁ፡፡ በእርግጥም በዓል ተከበረ የሚባለው፡- ሰዎች ነፍሳቸውን
ካዳኑበት፣ ውስጣዊ ሰላምንና ፍቅረ ቢጽን ገንዘብ ካደረጉበት፣ ዕለት ዕለት ከሚያጋጥማቸው
የነፍስ መታወክ ካረፉበት፣ ያለ ሁካታና ጋጋታ እንዲሁም እንስሳትን በማረድ ከልክ በላይ ከኾነ
መብልና መጠጥ ርቀው ያከበሩት እንደ ኾነ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በዓል ተከበረ የሚባለው፡-
አርምሞንና ጸጥታን፣ ፍቅርንና ደስታን፣ ሰላምንና ራስን መግዛትን፣ እንዲሁም ሌሎች እዚህ
መዘርዘር የማንችላቸው ብዙ ምግባር ትሩፋቶችን ገንዘብ ያደረግንበት እንደ ኾነ ነው፡፡

ጾም የሥጋ ረሀብ አይደለም የነፍስ ምግብ እንጅ አንዳንድ ሰዎች እንደሚያስቡት ጾም የሥጋ ሥቃይ
ሰማዕትነት ወይም መስቀል አይደለም ሥጋ ከነፍስ ጋር የሚተባበርበት ደረጃ ላይ ለመድረስ ከፍ ከፍ
የሚልበት እንጂ። ስንጾም የመጾማችን ዕቅድ ሥጋችንን ለማንገላታት አይደለም ጠባዩን ለመግራት
እንጂ። ይህ በመሆኑም አንድ የሚጾም ሰው መንፈሳዊ እንጂ ሥጋዊ ሰው አይሆንም ማለት ነው ።

ጾም መናኝ ነፍስ ስለሆነ በምናኔ ውስጥ ያለ ባልንጀራ ሥጋውን ይዞ ይጓዛል እንጂ ብቻውን አይጓዝም።
ጾም ማለት የተራበ ሥጋ ማለት አይደለም የመነነ ሥጋ እንጂ። ጾም የሥጋ ረሀብ አይደለም የሥጋ ልዕልና
እና ንጽህና እንጂ ለመብላት የሚናፍቅ የሚራብ ሰውነት ያለበት ሁኔታ ማለትም አይደለም፤ መብላት
ዋጋውን የሚያጣበትና ሰውነት ለመብላት ካለው ፍላጎት ራሱን የሚያላቅቅበት ሁኔታ እንጂ።

ጾም ነፍስ ከፍ ብላ ሥጋን ከእርስዋ ጋር ከፍ የምታደርግበት ጊዜ ነው። ይህ ጊዜ ሥጋ ጓዙንና ሸክሙን


የሚያራግፍበት ጊዜ ስለሆነ እግዚአብሔር ያለ ምንም እገዳ ለመንፈሳዊ ዘላለማዊነት ደስታ የሚሠራበት
ጊዜ ይሆናል። ጾም ማለት ነፍስና ሥጋ በኀብረት መንፈሳዊ ተግባር ለማከናውን የሚጠቀሙበት ጊዜ
ነው። በጾም ወቅት ነፍስና ሥጋ የነፍስን ሥራ ለመሥራት ይተባበራሉ። ይህም ማለት ለጸሎት ለተመስጦ
ለክብርና ከእግዚአብሔር ጋር የሚሆን ሕይወትን ለመጋራት ይተባበራሉ ማለት ነው።

አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ

You might also like