Download as docx, pdf, or txt
Download as docx, pdf, or txt
You are on page 1of 37

ዓባይ ሕትመትና የወረቀት ፓኬጂንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር

የንብረት አስተዳደር መመሪያ

ግንቦት 2010 ዓ/ም

ባህር ዳር

መግቢያ
አባይ የህትመትና የወረቀት ፓኬጂንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ኃላፊነቱን በሚገባ ለመወጣት እንዲሁም ራዕይና
ተልኮዉን ለማሳካት ቀልጣፋና ወጪ ቆጣቢ የሀብት አስተዳደር ስርዓት መዘርጋት አስፈላጊ በመሆኑ፤የፋብሪካዉ
ንብረት አስተዳደርና አወጋገድ መመሪያ ሌሎች መሰል ተቋማት ከሚጠቀሙበት የንብረት አስተዳደርና አወጋገድ
መመሪያ እንዲሁም የካይዘን አሰራሮችን ጋር በማገናዘብ በፋብሪካዉ ባለቤትነት ስር ለሚገኙ ንብረቶች አንድ ወጥ
እና ዘመናዊ በሆነ አሰራር ስርዓት ለማስተዳደር እንዲቻል ይህን ንብረት አስተዳደርና አወጋገድ መመሪያ እንዲወጣ
አድርጓል፡፡

ክፍል አንድ

ጠቅላላ

1. የንብረት አስተዳደር ዓላማዎች


1) ግልፅ፤ዘመናዊ፤ቀልጣፋና ዉጤታማ የፋብሪካዉ የንብረት አስተዳደር ማስፈን፤
2) ሰራተኞች/ሃላፊዎች በእጃቸዉ ያለዉን ንብረት በጥንቃቄ ለመያዝ፤በአግባቡ ለመጠቀምና
ለመቆጣጠር እንዲችሉ
3) በተገቢዉ ሁኔታ ወይም ምንም አገልግሎት መስጠት የማይችሉ ንብረቶችን በማስወገድ
ንብረቶችን ለመያዝ የሚወጣዉን ወጭ ከመቀነሱም በላይ አላስፈላጊ የንብረት ክምችት
እንዳይኖር በማድረግ አላግባብ የሚባክነዉን ጊዜ፤ጉልበትና ወጭ መቀነስ ነዉ፡፡

2. አዉጪዉ ባለስልጣን
አባይ የህትመትና የወረቀት ፓኬጂንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ስራ አመራር ቦርድ በፋብሪካዉ
መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ---- የተሰጠዉ ስልጣን መሠረት ይህን የንብረት አስተዳደር መመሪያ
አዉጥቷል፡፡
3. አጭር ርዕስ
ይህ መመሪያ አባይ የህትመትና የወረቀት ፓኬጂንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ንብረት አስተዳደር
መመሪያ ቁጥር----/2010 ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል

4. ትርጓሜ
ያቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚሰጠዉ ካልሆነ በስተቀር በዚህ መመሪያ ዉስጥ
1. “ፋብሪካዉ” ማለት አባይ የህትመትና የወረቀት ፓኬጂንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ነዉ፡፡
2. “የፋብሪካዉ ንብረት” ማለት ከጥሬ ገንዘብና መሬት በስተቀር በግዥ፤በስጦታ ወይም በሌላ
መንገድ የተገኘዉን ማንኛዉም የፋብሪካ ሀብት የሆነዉን ቋሚና አላቂ ማለት ነዉ፡፡
3. “ቋሚ ንብረት” ማለት ግዙፋዊ ህልዎት ያለዉ የተናጠል ዋጋዉ ብር 1,000.00 (አንድ ሺህ)
እና ከዚያ በላይ የሆነ፤አንድ ዓመት እና ከዚያ በላይ ለሆነ ጊዜ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ
የሚኖረዉ እንደ ህንፃ፤የቢሮ ዕቃዎች፤መሣሪያዎች፤ተሸከርካሪ፤ ማሽነሪዎች እና
የመሳሰሉትን ይጨምራል፡፡
4. “አላቂ ዕቃ” ማለት ከቋሚ ዕቃ ዉጪ የሆነ ማናቸዉም ንብረት ሲሆን ለኮንስትራክሽን
ግብዓትነት የሚዉሉ፤ለህትመት አገልግሎት የሚዉሉ ጥሬ ዕቃዎች፤ለተሸከርካሪና ለማሽነሪ
ላይ የሚገጠሙ መለዋወጫዎች እና ሌሎች ከተገዛበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ዓመት በሆነ ጊዜ
አገልግሎት ሰጥቶ የሚያልቅ እና ዋጋዉ ከብር 1,000.00 (ከአንድ ሺህ ብር) በታች የሆነ
ንብረትን ያካትታል፡፡
5. “የንብረት ምድብ” ማለት አጠቃላይ ዓይነት የሚመደብበት ክፍል (Class) ነዉ፡፡
6. “የጥበቃ ኃላፊነት” ማለት የፋብሪካዉ ንብረት እስከሚወገድ ወይም ከመዝገብ
እስከሚሰረዝ ወይም በሌላ ሠራተኛ ወይም መ/ቤት ጥበቃ ሥር እንዲዉል እስከሚተላለፍ
ድረስ የፋብሪካዉን ንብረት ለመያዝና ለመጠበቅ ለአንድ ዕቃ ግ/ቤት ሠራተኛ ወይም
የንብረት ተጠቃሚ የሚሰጥ ኃላፊነት ነዉ፡፡ ይህም ኃላፊነት መዝገብ የመያዝ ኃላፊነትን
ሊጨምር ይችላል፡፡
7. “ስቶክ” ማለት በፋብሪካዉ የተገዙ ወይም የተመረቱ ወይም በእርዳታና በሌሎች
መንገዶች የተገኙ ንብረቶች ሆነዉ በመደበኛ የስራ እንቅስቃሴ ዉስጥ አገልግሎት ላይ
እስኪዉሉ ድረስ በመጋዘን የተቀመጡ ቋሚ ዕቃዎች፤አላቂ ዕቃዎች፤የፋብሪካዉ ምርት
ግብዓቶች እና እስኪሸጡ ድረስ የተቀመጡ ምርቶች የቢሮ ዉስጥ መገልገያ መሳሪያዎች
ተሸከርካሪዎች ናቸዉ፡፡
8. “መጋዘን” ማለት የፋብሪካዉን ንብረት አገልግሎት ላይ እስከሚዉል ወይም ምርቶች
እስኪሸጡ ድረስ የሚቀመጥበት ቦታ ነዉ፡፡
9. “ንብረት አስተዳደር” ማለት ማንኛዉም በተገልጋዩ እጅ እና በስቶክ ወይም ምርት ሂደት
ላይ ያለ ዕቃና ተያያዥ አገልግሎቶችን ለማስተዳደር የሚዘረጋ የአሰራር ስልት ማለት ነዉ፡፡
10. “የእርጅና ቅናሽ” ማለት ቋሚ ንብረት ከሌሎች ተፈጥሮ ሀብት ተለይቶ በአገልግሎት
፤በጊዜ ማለፍ፤በብቃት ማጣት ወይም በሌላ ምክንያት ይኽንኑ ተከትሎ ከንብረቱ ዋጋ ላይ ወደ
ወጭ ማስተላለፍ ነዉ፡፡
11. “የንብረት ዋጋ” ማለት ቋሚና አላቂ ንብረትን ለመግዛት ወይም ለመገንባት ከተከፈለዉ
ገንዘብ በተጨማሪ ማለትም የትራንስፖርት፤የመጫንና የማራገፍ ወጪ፤የትራንዚት፤ የጥበቃ
ወጪ ኢንሹራንስና የመሳሰሉት ንብረቱን ለማግኘትና በሥራ ላይ ለማዋል የወጣ ወጪ ማለት
ነዉ፡፡
12. “የወቅቱ የገበያ ዋጋ” ማለት በንብረት ዋጋ ላይ ዕቃዉን ለማግኘትና ርክክብ
እስከሚደረግበት ባለዉ ጊዜ የሚያስፈልጉ ተጨማሪ ወጪዎች ተካተዉ የሚገኝ ዋጋ ነዉ፡፡
“ቀሪ ዋጋ” ማለት አንድ ዕቃ በአገልግሎት ምክንያት እየቀነሰ በመሄዱ የአገልግሎት ዘመኑን
ጨርሶ እስኪሸጥ ድረስ የመዝገብ ዋጋዉ ዜሮ እንዳይሆን ታስቦ የሚሰጥ አነስተኛ ዋጋ ነዉ፡፡
13. “የሐራጅ ሽያጭ” ማለት ለአንድ ዕቃ የሽያጭ መነሻ ዋጋ ከተወሰነ በኃላ
በማስታወቂያዉ መሰረት በተወሰነ ቦታና ጊዜ የተጋበዙ ተጫራቾች በተገኙበት በግልጽ
ዉድድር የተሻለ ዋጋ ያቀረበ ተጫራች የሚመረጥበት ሽያጭ ዘዴ ነዉ፡፡
5. የተፈጸሚነት ወሰን
ይህ መመሪያ አባይ የህትመትና የወረቀት ፓኬጂንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ዉስጥ ባሉት በሁሉም ስራ
ክፍሎች ተግባራዊ ይሆናል፡፡

ክፍል ሁለት

የንብረት አስተዳዳር መርሆች

6. መሠረታዊ የንብረት አስተዳደር መርሆች


1) የፋብሪካዉን ሀብትና ንብረት ሥርዓት ባለዉ መንገድ መጠቀም፤ ማለትም በህጋዊ ደረሰኝ ገቢና
ወጭ በማድረግ ጥቅም ላይ እንዲዉል ማድረግ፤
2) እያንዳንዱ የፋብሪካዉ ሠራተኛ ለፋብሪካዉ አገልግሎት የተረከበዉን ንብረት በአግባቡ በመያዝና
በመንከባከብ ለታለመለት ዓላማ ለፋብሪካዉ ስራ ብቻ የማዋልና የመቆጣጠር ሃላፊነት አለበት፡፡
3) ተገልጋዩ ስለ ዕቃዉ አጠቃቀም በቂ ችሎታ ከሌለዉ ከሚያዉቁት ጠይቆ መረዳት ወይም በቂ
ስልጠና መዉሰድ ይኖርበታል፡፡
4) እያንዳንዱ የፋብሪካዉ ሠራተኛ ወይም ክፍል ሃላፊ ለስራዉ የማይፈለጉ ንብረቶችን በመለየትና
መመለስ ወይም ቀይ ካርድ በማድረግ እንዲወገዱ ለሚመለከተዉ አካል በወቅቱ የማሳወቅ ግዴታ
አለበት፡፡
5) እቃዉን ያለ አግባብ መጠቀም፤ ላልተፈለገ አለማ ማወል፤በግዴለሽነት ማበላሸት ወይም ያለ
አግባብ መጣል ተጠያቂነትን የሚያስከትል ይሆናል፡፡
6) በአጠቃላይ የፋብሪካዉ ኃላፊዎች እና የንብረቱ ተጠቃሚ አካላት የፋብሪካዉን እቅድ
ለማስፈጸም አገልግሎት ላይ ሊዉል የሚችለዉን የንብረት መጠንና፤አይነት ብቻ ጥቅም ላይ
የማዋል ሃለፊነት አለባቸዉ፡፡
7. ቋሚ ንብረት
ከሚከተሉት መመዘኛዎች ቢያንስ ሦስቱንና ከዚያ በላይ የሚያሟሉ ንብረቶች በቋሚ
ንብረትነት ይመዘገባሉ፡፡
1) በአጠቃቀምና በአያያዝ ጉድለት ካልተበላሹ በስተቀር አንድ ዓመት እና ከዚያ በላይ አገልግሎት
የሚሰጡ፤
2) ግዙፋዊ ህልወት ያለቸዉና የተናጠል ዋጋቸዉ ብር 1,000.00 (አንድ ሺህ) እና ከዚያ በላይ ዋጋ
ያላቸዉ፤
3) አገልግሎት ዘመናቸዉና አገልግሎት የመስጠት ጥራታቸዉ እየቀነሰ የሚሄድ ፤
4) ተጠግነዉ ወይም ታድሰዉ አገልግሎት የሚሰጡ
5) አንድ ጊዜ ወጪ ቢደረጉም ተመልሰዉ በተደጋጋሚ ጥቅም ላይ የሚዉሉ፤
6) በትምህርት ሰጭነቱ፤በታሪካዊነቱና በህጋዊ ማስረጃነቱ ዘለቄታዊ ጥቅም የሚሰጡ ንብረቶችን
ያካትታል፡፡
8. አላቂ ንብረት
1) በጥቅም ላይ ከዋሉ በአንድ ዓመት ወይም ባነሰ ጊዜ ዉስጥ አገልግሎት ሰጥተዉ የሚያልቁ፤
2) የተናጠል ዋጋቸዉ ከ 1,000.00 /አንድ ሺህ/ በታች የሆኑ
3) የተናጠል ዋጋቸዉ ከ 1,000.00 /አንድ ሺህ/ በላይ ሆነዉ ለተለያዩ መሳሪያዎች በተጓዳኝነት
የሚያገለግሎ መለዋወጫዎችን ይይዛል፡፡
4) በአንቀጽ 7 ከ“1” እስከ ከ“6” በተጠቀሱ አምስት መመዘኛዎች አማካኝነት በቋሚ ዕቃ የንብረት
ምድብ ሊካተቱ የማይችሉትን ያጠቃልላል፡፡
9. ለሽያጭ የተዘጋጁ ምርቶች (Merchandize items)
1. የተለያዩ ምርቶችን፤
2. ለምርት መገጣጠሚያነት የሚዉሉ ራበር ሲሎችን እና
3. ለምርት ግብዓትነት የሚዉል ጥሬ ዕቃ ወይም ኬሚካሎችን ያካትታል፡፡
10. የንብረት አመዘጋገብ ሂደት
1) የፋብሪካዉ አቅርቦትና ሎጅስትክስ መምሪያ በንብረት ገቢ ደረሰኝ ወይም በ Good Receiving
Note (GRN) እንዲሁም በንብረት ወጭ ደረሰኝ ወይም Store Issue Voucher (SIV) ገቢ እና
ወጭ በሚያደርግበት ወቅት የተሟላ መረጃ ተይዞ እንቅስቃሴዉ በንብረት መቆጣጠሪያ ቢን
ካርድ፤ስቶክ ካርድ፤በመጋዘኖች በኮምፒዉተር ጭምር መመዝገብ ይኖርበታል፡፡
2) በዚሁ ክፍል በአንቀጽ 9 ላይ ለተጠቀሱ ለሽያጭ ምርቶች በምርት መረካከበያ ቅጽ/Finished
Goods Receiving Form/ መሰረት ገቢ ይደረጋል፡፡
3) ለሽያጭ ወጭ ለማድረግ ሲፈለግ በ Finished Goods Delivery Receiving Form/ መሰረት
ወጭ በማድረግ ያስረክባል፡፡
4) እያንዳንዱ ንብረት ገቢ ሲደረግ ሙሉ መግለጫ ሊኖረዉ ይገባል፤ለምሳሌ እቃዉ ምድብ ወይም
ኮድ፤ንብረቱ የተገኘበት መንገድ፤ዋጋዉ፤ገቢ የሆነበት ቀን በትክክል መገለጽ አለበት፡፡
5) ማንኛዉንም ንብረት በገቢና ወጭ ሰነድ ሳይመዘገብ በማስታወሻና በመሳሰሉት ገቢና ወጪ
ማድረግ የተከለከለ ነዉ፡፡
6) ማንኛዉም ንብረት የሚለይበት መለያ ማለትም ሲሪያል ቁጥር፤ሞዴል፤የቻንሲ ቁጥር፤የሞተር
ቁጥር ሳይመዘገብ ገቢና ወጪ ማድረግ በጥብቅ የተከለከለ ነዉ፡፡
7) የንብረት አስተዳደር ኦፊሰሮች ለቋሚ እቃ መለያ ቁጥርና ኮድ በመስጠት በአንድ ቋሚ መዝገብ
መመዝገብና ወጪ ባደረገዉ ሰዉ ስም ሌጀር ከፍተዉ መመዝገብ ይኖርባቸዋል፡፡
8) መለያ ሴሪያል ወይም ባች ቁጥር የሚኖራቸዉ አላቂ እቃዎች እንደ ጎማና ባትሪ የመሳሰሉ
እንዲሁም የቋሚ ተፈጥሮ ያለቸዉ እቃዎች መለያ ቁጥር እስካላቸዉ ድረስ ቁጥራቸዉ ተለይቶ
መመዝገብ ይኖርበታል፡፡
9) ወደ ተለያዩ አነስተኛ ወይም ጊዚያዊ የንብረት መጋዘኖች የሚላኩ ንብረቶች በዉስጣዊ
በማዘዋወሪያ ቅፅ /Inter Store Transfere Form/ተመዝግቦ መላክ ይኖርበታል፡፡
10) ማንኛዉም ዕቃ የገቢና ወጭ ሲደረግ በዚያዉ እለት የንብረት ማመዛዘኛ/Balance/ መሠራት
ይኖርበታል፡፡
11) ቋሚ ዕቃዎች አገልግሎት መስጠት ከጀመሩበት ጊዜ ጀምሮ አገልግሎት ጨርሰዉ ከፋብሪካዉ
ንብረት መዝገብ እስኪወገዱ ድረስ በተጠቃሚዎች ስም የተሟላ መዝገብ ተከፍቶላቸዉ
መመዝገብ አለባቸዉ፡፡
12) የንብረት ቆጣራ ዉጤት ከስቶክ መዝገብ እና ከሂሳብ ምዝገባ ጋር መመሳከር አለበት፡፡
13) ከአንድ ንብረት ጋር በአንድ ዋጋ የሚቀርቡ ተጓዳኝ እቃዎች /accessories/ ከዋናዉ ዕቃ ምዝገባ
ስር ተጓዳኝ ዕቃዎች/accessories/ ተብለዉ መመዝገብና የእያንዳንዱ መጠን መጠቀስ
ይኖርበታል፡፡ገቢና ወጭ በሚሰራበት ጊዜም በተመሳሳይ ምዝገባ ይከናወናል እንጂ ተጓዳኝ እቃዎች
/accessories/ የተለየ ምዝገባ አይካሄድለትም፡፡
14) በሴት፤በፓኬት የሚቀርቡ እቃዎች በጥቅል ምዝገባ ሲደረግ አንዱ ሴት/ፓኬቱ የያዘዉ መጠን
መገለፅ ይኖርበታል፡፡
15) ንብረት ሰራተኞች የሰሩትን ሰነድ ከፋይናንስ ጋር በየወሩ ማናበብ ይኖርባቸዋል፡፡
16) በስቶክ ያለ ንብረት ለአገልግሎት ሲጠየቅ በንብረት ወጭ መጠየቂያ መሰረት የክፍሉ ኃላፊ
ሲያጸድቅ ወጭ ሆኖ የሚሰጥ ይሆናል፡፡

11. ከተሸከርካሪና ከማሽነሪዎች ዉጭ የሆኑ ቋሚ ንብረቶችን መነሻ ዋጋ መወሰን

1) የቋሚ ንብረቶች ዋጋ በመደበኛ ሁኔታ የሚተመነዉ በተገዙበት ወይንም በተመረቱበት ጊዜ


አስፈላጊ የሆኑትን አግባብነት ያላቸዉን ወጭዎች ጨምሮ የተከፈለዉ ዋጋ ማለት ነዉ፡፡
2) ከላይ በዚህ አንቀጽ በተራ ቁጥር 1 ላይ የተጠቀሰዉ ቢኖርም ከዓመታት በፊት የተገዙና
የመዝገብ ዋጋ የሌላቸዉን ቋሚ ንብረቶች ዋጋ የማግኘት ሁኔታ ቀላል ስለማይሆን ከዚህ
በታች የተጠቀሱትን አማራጮች በመጠቀም ለቋሚ ንብረቶች የዋጋ የግምት መሰጠት
ይቻላል፡፡

ሀ/ ቀደም ሲል የተገዙ ንብረቶች ዋጋ የሚረጋገጠዉ በንብረት ካርዱ ላይ


የተመዘገበዉን የኢንቮይስ ወይም ደረሰኝ ዋጋ መሰረት በማድረግ ነዉ፡፡

ለ/ያለፉት ግዥዎች ደረሰኝ በማይገኝበት ጊዜ የመጀመሪያዉን ዋጋ የሚገምቱት


ተመሳሳይ ወይም አንድ አይነት የሆኑ ንብረቶች በተመሳሳይ ጊዜ ማለትም ከአንድ
የበጀት ዓመት ባልበለጠ ጊዜ ዉስጥ የተገዙበትን ደረሰኝ መሠረት በማድረግ
ተመሳሳይ የዋጋ ግምት መስጠት ይቻላል፡፡

ሐ/በቋሚ ንብረት መዝገብ ለማስፈር የሚያገለግል የመዝገብ ዋጋ የሌላቸዉ የቢሮ


መሳሪያዎች ወይም እቃዎች የዋጋ ግምት ለመስጠት የዕቃዎችን ያገልግሎት ዘመን
በመስፈርትነት በመዉሰድ ሲሆን ስሌቱም ከወቅቱ የገበያ ዋጋ ላይ በየዓመቱ አስር
መቶኛ/10%/ የዋጋ ቅናሽ በማድረግ የሚሰላ ይሆናል፡፡ይህ ስሌት የጠፋዉን
ንብረትን ለመተካት ጥቅም ላይ አይዉልም፡፡

3) ከላይ አንቀጽ 11 በተራ ቁጥር 2 የተጠቀሱት ሁኔታዎች ተሟልተዉ ካልተገኙ ወይንም


በተለያዩ ምክንያቶች የንብረቱ አገልግሎት ዘመን ሊታወቅ የማይችል ከሆነ፤ወይም ረዥም
አገልግሎት ያለዉ ንብረት በሚገባ የሚሰራና በጥሩ አቋም ላይ የሚገኝ በመሆኑ
በአገልግሎት ዘመን ስሌት መሰረት የሚሰጠዉ ግምት ትክክለኛ ሆኖ ካልተገኘ ንብረቱ
ያለበትን አቋም መሰረት በማድረግ በሚቀጥለዉ ሰንጠረዥ በተቀመጠዉ ከወቅቱ የገበያ
ዋጋ በሚደረግ የመቀነሻ ስሌት መሰረት ሊፈፀም ይችላል፡፡

ንብረቱ ያለበት ሁኔታ ከወቅቱ የገበያ ዋጋ ላይ


የሚደረግ ቅናሽ

ከተገዛ የቆየ ነገር ግን አዲስ (ጥቅም ላይ ያልዋለ 0%


ንብረት ሲኖር)

በጣም ጥሩ በሚባል ደረጃ ላይ ያለ ንብረት 25%

በጥሩ ሁኔታ ላይ ያለ ንብረት 50%

ጥሩ ባልሆነ አቋም ላይ ያለ ንብረት 75%

12. . የመዝገብ ዋጋ ለሌላቸዉ ተሸከርካሪዎችና ማሽነሪዎች ዋጋ ስለመተመን፤


የመዝገብ ዋጋ የሌላቸዉ ተሸከርካሪዎችና ማሽነሪዎች ያሉበትን አቋም /ይዘት/
ባገናዘበ ሁኔታ በፋብሪካዉ ባለሙያዎች የዋጋ ጥናት ሰነድ መሰረት ወይም
የክልሉ የግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ንብረት ለማስወገድ
የሚጠቀምበትን መመሪያ መሰረት በማድረግ ዋጋ መገመት ይቻላል፡፡

13. . በእርደታ፤በስጦታ የተገኙ ንብረቶች፤


1) በእርዳታ፤ በስጦታ የሚገኙ ንብረቶች ዋጋ እና የአገልግሎት ዘመናቸዉን የሚገልፅ ማስረጃ
ከለጋሾች ወይም በትዉስት ከሰጡ አካላት በወቅቱ በመጠየቅ በቋሚ ንብረት መመዝገብ/ካርድ
ላይ መመዝገብ አለባቸዉ፡፡
2) ስጦታዉን ከሰጡ አካላት የንብረቶች ዋጋ የማይገኝ ከሆነ በአንቀጽ 11 ንዑስ አንቀጽ 2
በተቀመጠዉ አማራጭ መሰረት የግምት ዋጋ ሊሰጣቸዉ ይገባል፡፡
14. የቋሚ ንብረት መለያ ቁጥር /PIN/ አሰጣጥ፤
የቋሚ የንብረት መለያ ቁጥር /Property Identification Number/ አንድን ንብረት
ከሌሎቹ ለይቶ ለማወቅ የሚያገለግል ቁጥር ሲሆን በቁጥሩ ወይም በአልፋቤትና በቁጥር
ቅልቅል ሊዘጋጅ ይችላል፡፡
1) የንብረት መለያ ቁጥር አደረጃጀት ማለትም፤ ለቋሚ ንብረቶች /Fixed Assets/ በተሰጠዉ
የሂሳብ ኮድ /Chart of account/ መሰረት የተዘጋጀ የንብረት የመለያ ቁጥር አሰጣጥ መዝገብ
ማዘጋጀት ያስፈልጋል፤ይህም በቀላሉ ለማግኘትና በቋሚ ንብረቶች ላይ ያሉትን መረጃዎች
ለመተንተንና ለማጠቃለል ያግዛል፡፡
2) ለቋሚ ንብረቶች መለያ ቁጥር ለመስጠት የተለያዩ የአሰራር ዘዴዎች፤የፋብሪካዉ ስያሜ
በምህፃረ ቃል፤የዕቃዉ አርዕስት/ምድብ የዕቃዉ ዓይነት /ንዑስ ምድብ እና የተፈላጊዉ ዕቃ
ቁጥር/ብዛት፤መጠቀም ይቻላል፡፡
3) የንብረት ኮድ አሰጣጥ
ሀ) የፋብሪካዉ ኮድ፡-ፋብሪካዉ ማን እንደሆነ ይለያል፡፡ ለምሳሌም አባይ ሕትመትና
የወረቀት ፓኬጂንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ሥር ያሉ ንብረቶች “ አሕየወፓ” በማለት
በምህፃረ ቃል በአጭሩ ይፃፋል፡፡ ፋብሪካዉ አንዴ ኮድ አሰጣጥ ስርዓቱን አስጠንቶ ኮዱ
ከተመረጠ በኃላ በዘላቂነት ጥቅም ላይ መዋል ይኖርበታል፡፡
ለ) የንብረት ምድብ ኮድ፡-ይህ ኮድ ለንብረቱ የሚሰጠዉ የሂሳብ ምድብ ነዉ፡፡
ሐ) የንብረት ንዑስ ምድብ ኮድ፡-ይኽ ኮድ በየንዑስ ምድብ የተመደቡትን ንብረቶች
ለመለየት የሚያገለግል ነዉ፡፡ ለምሳሌ “ ተሸከርካሪዎችና ሌሎች ለመጓጓዣ የሚዉሉ
ተሸከርካሪዎች” በሚለዉ አጠቃላይ ምድብ ዉስጥ ፎረክ ሊፍት፤አዉቶቡሶች፤
መጫኛና ማዉረጃ መኪኖች፤ ወዘተ..በንዑስ ምድብነት ተካተዉ ይገኛሉ፡፡ስለዚህ
ለእያንዳንዱ ንዑስ ምድብ ሁለት ቁጥሮች (Digits) መሰየሙ ተገቢ ይሆናል፡፡
መ) የስራ መምሪያዉ ወይም የስራ ክፍሉ ኮድ-ይህ የሚወክለዉ በፋብሪካዉ ባለበት
ቦታ ንብረቱ የሚገኝበትን ልዩ ቦታ ነዉ፡፡ይህ ኮድ ተግባራዊ ሚሆነዉ የፋብሪካዉን
መዋቅር በመጠቀም ነዉ፡፡ለምሳሌ ኮዱ የአቅርቦትና ሎጅስቲክስ መምሪያ
ሚያመላክት መሆን አለበት፡፡
ሠ) የንብረቱ ልዩ ኮድ- ለእያንዳንዱ ንብረት የሚሰጥ ተከታታይ ቁጥር ነዉ፡፡

15. የቋሚ ንብረት እርጅና ቅናሽ፤


የፋብሪካዉ ቋሚ ንብረት የእርጅና ቅናሽ የሚሰላዉ በፋብሪካዉ ፋይናንስ መምሪያ
መሰረት ይሆናል፡፡
16. የቋሚነት ተፈጥሮ ባህሪይ ያላቸዉን ንብረቶች ስለመቆጣጠር
1) በአንቀጽ 7 ንዑስ አንቀጽ 7.1 እና በአንቀጽ 11 ከተጠቀሱት የቋሚና አላቂ ንብረቶች መስፈርት
በተለየ ሁኔታ የአገልግሎት አድማሳቸዉ ከዓመት በላይ ሆኖ ዋጋቸዉ ግን ከብር 1,000.00/አንድ
ሺህ/ በታች የሆኑ፤-እንደ ወረቀት መብሻዎች፤ስቴፕላሮች፤በኪስ የሚያዙ የሂሳብ
መኪኖች፤መጽሐፍት እና እነዚህን የመሳሰሉ ሌሎች ንብረቶች ተገቢዉ የቁጥጥር መዝገብ
ተከፍቶላቸዉ መቆጣጠር ካልተቻለና እንደሌሎች አላቂ ዕቃዎች ለአንድ ጊዜ ጠቃሜታ ወጭ
እየተደረጉ የሚሰጡ ከሆነ ንብረቶች ሊባክኑ ይችላሉ፡፡
2) ከላይ አንቀጽ 16 ላይ ከተጠቀሱት ንብረቶች የእርጅና ቅናሽ የማይታሰብላቸዉ ቢሆንም እንደ
ማንኛዉም ቋሚ ንብረት በተጠቃሚዉ ስም የቋሚ ንብረት መቆጣጠሪያ መዝገብ ወይም ካርድ
ተከፍቶላቸዉ የገቢና ወጭ እንቅስቃሴያቸዉን በመመዝገብ ቁጥጥር መደረግ አለበት፡፡
3) ማንኛዉም ግለሰብ ወጪ የደረገዉን የቋሚ እቃ ተፈጥሮ ያላቸዉን ተመሳሳይ እቃዎች መጥፋቱ
ከተረጋገጠና አሳማኝ ሆኖ ከተገኘ የሚመለከተዉ ኃላፊ ሲፈቅድ ድጋሜ ሊሰጥ ይችላል፡፡

ክፍል ሦስት

የስቶክ አስተዳዳር ስርዓት

17. የስቶክ ቁጥጥር ስርዓት መርሆች


1) የስቶክ ቁጥጥር አስተማማኝ፤ተገቢና መሰረታዊ የስቶክ መዛግብቶችን መሰረት ያደረገ መሆን
አለበት፡፡
2) አዲስ የግዥ ጥያቄ በሚቀርብበት ወቅት የንብረት ተጠቃሚዎችና የግዥ ባለሙያዎች ግዥ
ከመፈፀሙ በፊት የተጠየቀዉ እቃ በመጋዘን ዉስጥ የሌላ መሆኑን በቅድሚያ ማረጋገጥ አለባቸዉ፤
3) ንብረት ገቢ እና ወጭ የሚሆንባቸዉ ሰነዶች ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግባቸዉ ሆነዉ አስቀድመዉ
የታተሙና ተከታታይ ቁጥሮች ያሏቸዉ መሆን፤አጠቃቀማቸዉም ከትንሽ ወደ ትልቅ በተሰጣቸዉ
ተከታታይ ቁጥር መሰረት መሆን አለበት፡፡
4) የንብረት መጉደል ወይም ማጭበርበር ተከስቷል የሚል ጥርጣሬ ሲኖር ንብረቱን ከመቀበል ጀምሮ
ማዉጣትን፤ጥቅም ላይ ማዋልንና አግባብ ያለዉ ሆኖ ሲገኝ እስከ ማስወገድ ድረስ ያለዉን፤

18.የስቶክ ቁጥጥር ዋና ዋና አለማዎች


ሀ/ ተፈላጊ ዕቃዎች በወቅቱ በበቂ ሁኔታ በመጋዘን ዉስጥ ተገኝተዉ ለተፈላጊዉ ሥራ
እንዲዉሉና የማያቋርጥ አቅርቦት እንዲኖር ለማድረግ፤
ለ/ ከሚፈለገዉ በላይ ወይም በታች የዕቃ ክምችት እንዳይኖር የክምችት መጠንን ለመወሰንና
በክምችት እጥረት የሥራ ሂደት እንዳይቋረጥ በክምችት ብዛት የስራ ማስኬጃ ገንዘብ
እንዳይታሰር ለማድረግ፤
ሐ/ ተደጋጋሚ ግዥ በመፈጸም የግዥ ማስፈጸሚያ ወጭ እንዳይኖር ጊዜም እንዳይባክን
መከታተል፤
S/ uw³} Ñ´„ ¡U‹ƒ uSÁ´ ¾›ÁÁ´ ¨ß /carrying cost/እንዳይጨምርና የመጋዘን ጥበት
እንዳያስከትል ለማድረግ፤
W/¾}ѳ¨< እቃ በወቅቱ አገልግሎት ሳይሰጥ በቴክኖሎጅ ለውጥ ምክንያት ከጥቅም ውጭ
/Obsolete/ እንዳይሆን ጥንቃቄ ለማድረግ ፤
[/ ›S ታዊ የእቃ ግዥ ፍላጎትን አውቆ እቅድ ለማውጣት ስለሚጠቅም በመጋዘን ላይ ያለውን
ስቶክ መጠን ለይቶ ማውቅ አስፈላጊ ነው፡፡

19. መሰረታዊ ንብረትና የስቶክ መዛግብቶች

1) በንብረት ወጭና ገቢ መቆጣጠሪያ ቅፆች ወይም ካርዶች የስቶክ መረጃዎችን መያዝ

አለባቸው፡፡ ወጥና ዘምናዊ አሰራርን ተግባራዊ ለማድረግ በፋብሪካው በተዘጋጁት

የንብረት መመዝገቢያና መቆጣጠሪያ ቅፆች የሚከተሉት ናቸው

ሀ. በእቃ ግምጃቤት ውስጥ የሚገኙ ቋሚም ሆነ አላቂ እቃዎች የት

እንደሚገኙ የሚያሳይ ሎኬሽን ካርድ /stock location card/

ለ. በተጠቃሚዎች እጅ ያሉ ቋሚ ንብረቶች መመዝገቢያና መቆጣጠሪያ

ካርድ /UC/ Users card/

ሐ. የቋሚ ንብረት መመዝገቢያ ካርድ (FAR) Fixd Assets Rigister

Card/Book/ ይህ ካርድ የእጅና ቅናሽ ለሚቀነስባቸው ቋሚ ንብረቶች

መመዝገቢያ ካርድ ነው፡፡

መ. የንብረት ገቢና ወጭ እንቅስቃሴ ቫላንስ የሚያሳይ ቢን ካርድ /Bin card/;

ስቶክ ኮንትሮል ካርድ፤ ነፍስ ወከፍ ካርድ፤ የምርት ማስረከቢያ ካርድ፤ የሽያጭ

ካርድ ናቸው፡፡
2) ይህንን አሰራር በማይፃረር መንገድ በኤሌክትሮኒክ ዘዴ በመጠቀም የስቶክ መረጃ
መያዝና ማስተዳደር ይቻላል፡፡
20. ስቶክ ወይም ንብረት መረከብ
1. ማንኛውም በግዥ፤ በእርዳታ ወይም በስጦታ የተገኘ ንብረት ርክክብ ሲፈፀም በመጀመሪያ ደረጃ
እቃው ገቢ እንዲሆን ከሚመለከተው አካል ትእዛዝ የተሰጠ ወይም ገቢ ለማድረግ አስፈላጊ ህጋዊ
ሁኔታዎች የተሟሉ መሆናቸው ከተረጋገጠ በኋላ በገቢ ደረሰኙ ላይ የሚከተሉት ተሟልተዎ
መመዝገብ አለባቸው፡፡
ሀ. አቅራቢውን ወይም የላኪውን ድርጅት ስም
ለ. የእቃውን አይነትና ብዛት
ሐ. የእቃው የነጠላና ጠቅላላ ዋጋ
መ. እቃው የተገኘበት ሁኔታ /በግዥ፤በእርዳታ ፤ በተመላሽ፤ በትውስት ወዘተ…
ሠ. የተላከበት ኢንቮይስ/ደረሰኝ ወይም ደብዳቤ ቁጥር ቀንና የሚያስረክበው ግለሰብ ስም
ተለይቶ ሊፃፍ ይገባል፡፡
2. በግዥ ከአቅራቢ ድርጅት የተላኩትን ሰነዶች ከግዥ ሰነዶች ጋር ለማመሳከሪያነት ከሚሆኑት
መካከል የሚከተሉትን መጠቀም ይገባል፡፡
ሀ. የእቃ ግዥ ማዘዣ /Purchase order/
ለ. የግዥ ውል /Agreement/
ሐ. የእቃ ዝርዝር መግለጫ /Specification/
3. በባለሙያ ተፈትሸው የሚረጋገጡ እንደ ማሽን፤ የመለዋወጫ እቃዎች፤ ለምርትና ለላቦራቶሪ
ግብዓትነት የሚውሉ ኬሚካሎች፤ኮምፒዉተርና ሌሎች የቴክኒክ ባህሪ ያላቸዉ ዕቃዎች ከጠያቂዉ
ክፍል ወይም ለዚሁ ተግባር ከሚመደብ ባለሙያ በሚሰጥ ማረጋገጫ ርክክቡ ይፈጸማል፡፡
4. ዉስብስብነት የሌላቸዉ በተደጋጋሚ በመደበኛነት የሚገዙ ዕቃዎች/ንብረቶች/በግዥ ኦፊሰሩና
በንብረት አስተዳደር ኦፊሰሩ በጋራ በሚሰጡት ማረጋገጫ መሰረት ገቢ እንዲሆን ይደረጋል፡፡
5. የጥራት ፍተሻ የሚደረገዉ አቅራቢዉ ድርጅት ያቀረበዉ ዕቃ እንዲገዛ ከታዘዘዉ ወይም በዉድድር
ወቅት ከቀረበዉ ወይም በዉሉ በተገለፀዉ ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ጋር ማገናዘብ ይሆናል፡፡
6. በንብረት ርክክብ ወቅት ኦፕሬሽናል ወይም የልኬት ፍተሻ የሚያስፈልጋቸዉ እቃዎች በሙሉ
ተፈትሸዉና ተረጋግጠዉ ገቢ መደረግ አለባቸዉ፡፡
ሀ/ ከላይ በዚሁ አንቀጽ ተራ ቁጥር 7 የጠቀሰዉ ቢኖርም ከእቃዉ ብዛት ወይም መፈተሸ
አቅም ጋር በተያያዘ ለሚፈጠር ችግር የናሙና ፍተሻ ማድረግ ይቻላል፡፡
ለ/ የሚወሰደዉ ናሙና መጠንና አፈፃፀም እንደአስፈላጊነቱ በቴክኒክ ክፍል ማኔጀር
ወይም በምክትል ማኔጀር ወይም በእቅርቦትና ሎጅስቲክስ ኃላፊ መወሰን ይኖርበታል፡፡
7. በጥቅል (Packages) የመጡ ንብረቶች በክብደት ጭነት ማረጋገጫ በሌላ መሰል ሰነዶች መሠረት
ትክክል ስለመሆናቸዉ መረጋገጥ አለባቸዉ፡፡የዕቃዎች ሁኔታ /Condition/ አስረካቢዉ ወይም
አጓጓዡ ባለበት ጥቅሎችን በጥንቃቄ በመመርመር
የመጉደል፤የመሰበር፤የመጨራመት፤የመላጥ፤የመሰንጠቅ፤በመቀደድ፤እና ወይም ሌላ ጉዳት
እንዳልደረሰ መረጋገጥ አለበት፡
8. የንብረት ገቢ ደረሰኞች ኮፒ ንብረት ገቢ በተደረገ ጊዜ ሁሉ በወቅቱ ለሚመለከታቸዉ መሰራጨት
አለባቸዉ፡፡ ከሶስት ቀን በላይ ሳይሰራጭ ለቆየ ሰነድ ኃላፊነቱ የንብረት መጋዘን ሠራተኛ ይሆናል፡፡
9. ከጥገና በኃላ ተመላሽ የሚሆኑ ተሸከርካሪ ወይም ሌላ ቋሚ ዕቃ መለዋወጫዎችና አሩጌ ጎማዎች
የተለያዩ ያገለገሉ ዕቃዎች ባገለገሉ ንብረቶች መመለሻ ሰነድ በመሙላት ገቢ መደረግ አለበት፡፡
10. በተለያዩ ሁኔታዎች የንብረት ርክክብ በሚፈፀመበት ጊዜ ከዋናዉ ዕቃ ወይም መሳሪያ ነቅሎ
ለማስረከብ የማይመቹ የሚገጠሙ የቋሚነት ባህሪ ያላቸዉ ዕቃዎች (Fixtures) ለምሳሌ የበር
ቁልፍ፤ጣራ ላይ የሚገጠም ቬንትሌትር፤የቢሮና የአደራሽ ሳዉንድ፤ሲስተምና የተገጣጠሙ የአደራሽ
ወንበሮች፤ጎማዎች፤መለዋወጫዎች እና ሌሎች ተመሳሳይ ባህሪ ያላቸዉ ዕቃዎች ወጭ በደረገዉ
ስም ንብረቱ ተጠቃሚዎች የቋሚ ንብረት መዝገብ /Users Card/ ላይ ተመዝግበዉ አይያዙም፡፡
11. ከላይ በተራ ቁጥር 12 የተጠቀሰዉ እንደተጠበቀ ሆኖ ንብረቶች ወጭና ገቢ ሲደረጉ የእቃዉ መለያ
የሆነዉ ሴሪያል ቁጥር እና ሞዴል መመዝገብ ይኖርበታል፡፡
12. የአቅርቦትና የተከላ/Installation/ አገልግሎት የስራ ዉል ለተቋራጭ በሚሰጥበት ጊዜ ሥራዉ
ተጠናቆ ርክክብ ሲፈጸም በስራ ዝርዝሩ መሰረት አስፈላጊ ግብዓቶች ተሟልተዉ በትክክል የተተከለ
ወይም የተገጠመ/Install/ ስለመሆኑ ማረጋገጥ አስፈላጊ ከሆነም በባለሙያ ድጋፍ ተፈትሾ
ከተረጋገጠ በኃላ በገቢ ሰነድ በዉል ተቀባይ ስም ገቢ ይደረጋል፡፡
13. ከላይ በተራ ቁጥር 14 ላይ የተገለጸዉን ባህሪ ያለዉ ቋሚ ዕቃ የንብረቱ ተጠቀሚዎች ወጭ
አድርገዉ ሲወስዱት የንብረት ምዝገባና ርክክብ ሥራ የሚያከናወን ቢሆንም ወጭ ባደረገዉ ስም
ወይም በንብረቱ ተጠቃሚዎች የቋሚ ንብረት መዝገብ /Users Card/ ላይ ተመዝግበዉ አይያዙም፡፡
14. በፋብሪካዉ ምርት ክፍል፤ጋራዥ፤በስክራፐክሬሸር ቦታዎች የሚመረቱ ዕቃዎች ንብረት ክፍል ገቢ
እና ወጪ ሳይደረጉና ዋጋዉ ሳይሰጣቸዉ ጥቅም ላይ እንዲዉሉ መደረግ የለበትም፡፡ለዚሁ ምርት
ግብዓትነት የሚያገለገሉ ጥሬ ዕቃዎችም ንብረት ክፍል በወጪና በገቢ ተመዝግበዉ መያዝ
ይኖርባቸዋል፡፡

21. የንብረት ዝዉዉር


ሀ/ የንብረት ዝዉዉር በአብዛኛዉ በሚከተሉት ሦስት ምክንያቶች ተፈፃሚ ይሆናል፡፡

1. ንብረቱን በሃላፊነት የተረከበዉ የንብረት ሰራተኛ በሌላ በሚተካበት ጊዜ፤

2. ንብረት ከአንድ ንብረት ክፍል ሰራተኛ ወደ ሌላ ንብረት ክፍል ሰራተኛ በሚዛወርበት ጊዜ፤
3. ወደ ሌላ መ/ቤት የንብረት ዝዉዉር ሲፈጸም የሚከናወን ይሆናል፡፡

ለ/ የንብረት ዝዉዉር አፈፃፀሙ እንደሚከተለዉ መሆን አለበት፡፡

1. የንብረቶችን ዝርዝር እና ብዛት፤የተረካቢና የአስረካቢ ስምና ፊርማ እንዲሁም የአረካካቢዉን ስምና

ፊርማ ሊያካትት በሚችል የርክክብ ሰነድ ወይም ቬርቫል የንብረት ዝዉዉር ሊፈጸም ይገባል፡፡

2. ንብረት አረካከቢ በፋብሪካዉ የአቅርቦትና ሎጅስቲክስ መምሪያ ኃላፊ በደብዳቤ ይወከላል፡፡

3. የአቅርቦትና ሎጅስቲክስ መምሪያ ኃላፊ የንብረት ርክክብና የኦዲት ዉጤቱ ለምክትል ስራ አስኪያጅ

ለዉሳኔ አቅርቦ ሰራተኛዉ ከእዳ ነፃ ሲሆን የተሟላ ክሊራንስ መሰጠት አለበት፡፡

4. የሚዛወሩት እቃዎች ቋሚ እቃዎች ከሆኑ የንብረቶች የቁጥጥር ስርዓት እንዳይዛባና የተጠቃሚዎችን

መዝገብ ማስተካከል እንዲቻል የመጀመሪያዉ ተጠቃሚ ገቢ ካደረገ በኃላ ዝዉዉር ለተፈቀደለት

ወጭ አድርጎ በመስጠት የሚፈጸም ሲሆን የንብረት መቆጣጠሪያ መዝገቡ በሁለተኛዉ ተጠቃሚ

ስም ማስተካካል አለበት፡፡

5. የተሰጠበት አግባብ በስጦታ/ ለአጭር ጊዜ በትዉስት የሚል ማብራሪያ መቀመጥ አለበት፡፡

6. ንብረትን በማስወገድ ሂደት ወደ ሌላ መ/ቤት በቋሚነት እንዲተላለፍ ሲደረግ ወጭ ሆኖ ሊሰጥ

ይገባል፡፡

22. የንብረት ዝዉዉር

ስቶክ ከመጋዘን የሚወጣዉ መጀመሪያ የገባዉ መጀመሪያ ይወጣል /First in first out/
FIFO/የሚለዉን የንብረት አጠቃቀምና አሰራር መርህ መሰረት በማድረግ መሆን አለበት፡፡

1. ንብረት በተሟላ መልክና በተገቢዉ አካል ወጭ ማድረግ ይቻል ዘንድ የግዥ ኦፊሰሩ ወይም አስረካቢዉ
ለተገዛዉ ዕቃዉ ለየትኛዉ ስራ ክፍል እንደሆነ የሚያሳይ መረጃ ለንብረት ኦፊሰሩ እና ለንብረት
ሠራተኛ መስጠት አለበት፡፡
2. የንብረት ወጪን የመፍቀድና የማጽደቅ ስልጣን በዋና ስራአስኪያጅ ወይም በምክትል ስራ አስኪያጆች
ወይም እንደአስፈላጊነቱ በመምሪያ ኃላፊዎች ሊሆን ይችላል፡፡
3. በሽያጭ ወጪ የሚሆን እቃ ክፍያ የተፈጸመለት ለመሆኑ የገንዘብ መቀበያ ደረሰኙን በማየት
ማረጋገጥ፤ ከዚህ በተጨማሪ የሚሸጠዉን ዕቃ ዓይነት፤ ብዛትና ዋጋ የሚያሳይ ማመሳከሪያ ሰነድ መያዝ
አስፈላጊ ነዉ፡፡
4. ዕቃዉን በሽያጭ የሚረከበዉ ሰዉ የጹሁፍ ማስረጃ ወይም የዉክልና ማስረጃ ማቅረቡን ማረጋገጥ፡፡
5. ማንኛዉም እቃ በንብረት ወጭ ደረሰኝ ወጭ ከሆነ በኃላ ከመዝገብ ላይ ተቀናንሶ ከወጭ ቀሪዉ በግልፅ
ተለይቶ መያዝ ያለበት ሆኖ የዕቃ ወጪ ደረሰኞችም ለየሚመለከታቸዉ በወቅቱ መሠራጨት
አለባቸዉ፡፡
23. ንብረት በትዉስት ስለሚሰጥበት ሁኔታ
1) አስገዳጅና አስቸኳይ ሁኔታ ካልገጠመ በስተቀር ፋብሪካዉ ዕቃ/ንብረት በሽያጭ ወይም በኪራይ
ካልሆነ በትዉስት አይሰጥም፡፡
2) አስገዳጅ ሁኔታ ኖሮ ዕቃ ወይም ንብረት በትዉስት ለሌላ አካል የሚሰጠዉ በፋብሪካዉ ዋና ስራ
አስኪያጆች ሲፈቀድ ብቻ ነዉ፡፡
3) በትዉስት የሚሰጥ እቃ በፋብሪካዉ የወጭ ሰነድ በትዉስት የተሰጠ ለመሆኑ ተገልፆና ሲመልስም
በተመላሽ (Return) ሰነድ ንብረቱ ቀደም ሲል ወጪ የተደረገበት ሰነድ ቁጥር ተጠቅሶ ገቢ መደረግ
ይኖርበታል፡፡
4) በትዉስት የተሰጠ ንብረት ዋጋ በተሰብሳቢ ሂሳብ መያዝ አለበት፡፡
5) በትዉስት የሚሰጠዉ ንብረት የሚመለስበት ጊዜ ገደብ መቀመጥ ያለበት ሆኖ በተወሰነ ጊዜ ገደብ
ዉስጥ መመለሱም ክትትል ተደርጎ በንብረት አስተዳዳር ኦፊሰር በኩል ለዋና ስራ አስኪያጅ ሪፖርት
መቅርብ አለበት፡፡
6) በትዉስት የተሰጠዉ ዕቃ/ ንብረት ብልሽት ቢደርስበት የተዋሰዉ አካል አስጠግኖ እንዲመልስ
እቃ/ንብረት ቢጠፋ ወይም በአደጋ ምክንያት ቢቃጠል፤ቢሰረቅ የተዋሰዉ አካል እቃዉን በአይነት
የሚተካ መሆኑ በቅድሚያ ለተዋሹ እንዲያዉቀዉ ተደርጎ ዉል መፈራረም ያስፈልጋል፡፡
7) ወደ ፋብሪካዉ በትዉስት የሚመጣ ዕቃ/ንብረት መቼ እንደመጣና ለምን ስራ እንደመጣ ታዉቆ
በጥንቃቄ በተለየ መዝገብ ተመዝግቦ መያዝ አለበት፡፡በትዉስት የመጣዉ ዕቃ የመጣበትን ተግባር
ከፈጸመ በኃላ በወቅቱ በሰጠዉ አካል መመለስ አለበት ይህንን ተግባር የንብረት አስተዳደር ኦፊሰሮች
ተከታትለዉ መፈጸም ይኖርባቸዋል፡፡
8) በትዉስት የወሰዱትን ማሽነሪ በጊዜ ገደቡ የማይመልሱ ከሆነ ኪራይ ሊታሰብ ይችላል፡፡ የኪራይ
ስሌቱ የትዉስት ጊዜ ገደቡ በተጠናቀቀ በመጀመሪያዉ ቀን ብር 10,000.00 (አስር ሺህ)
የሚያስከፍል ሆኖ በቀጣይ ቀናትም መሳሪያዉ ካልተመለሰ በየቀኑ 15% እየጨመረ የሚሄድ
ይሆናል፡፡
9) ማንኛዉም በትዉስት የሚሰጥ እቃ በዚህ አንቀጽ የተገለጹትን አስገዳጅ ሁኔታዎችና ሌሎች
ወቅታዊ ሁኔታዎችን ያካተተ የትዉስት ዉል መፈረም ይኖርበታል፡፡
24. የስቶክ ክምችት አወሳሰን
1. ማንኛዉም ለፋብሪካ አገልግሎት የሚዉል በመጋዘን ወይም በስቶክ መልክ የሚያዝ ንብረት
በዓይነት ተለይቶ መቼና ምን ያህል መታዘዝ እንዳለበት የሚወሰን አሠራር ያስፈልገዋል፡፡ይህ
አሰራር የሚከተሉትን ባገናዘበ መልክ መዘጋጀት አለበት፡፡
ሀ/ በእጅ የሚገኝ የክምችት መጠን
ለ/ በትዕዛዝ ያለ መጠን
ሐ/ ዕቃዉ ታዝዞ መጋዘን እስኪገባ ያለዉ ጊዜ
መ/የፍጆታ አዝማሚያ
ሠ/ የገበያ ወይም የአጠቃቀም ሁኔታን እና ጊዜዉን ታሳቢ ያደረገ መሆን አለበት፡፡
25. የንብረት መጋዘን አጠቃቀም
1. ንብረትን ለረዥም ጊዜ በብዛት በመጋዝን በማከማቸት የንብረት ብልሽትና ብክነት እንዲሁም
የካፒታል እጥረት እንዳይደረስ ጥንቃቄ መደረግ አለበት፡፡
2. መደበኛ ወይም ዓመታዊ እቅድን ለማሳካት በግብዓትነት በስቶክ የሚያዙ ንብረቶች፤
ሀ/ እቃዎችን በአይነት ፈጣን እንቅስቃሴ፤ መካከለኛ እንቅስቃሴ እና ዝቅተኛ እንቅስቃሴ
ያላቸዉን ንብረቶች በቦታ መለያየት ያስፈልጋል፡፡
ለ/ አገልግሎት ሳይሰጡ የተቀመጡ ንብረቶች የመጋዘን ጥበት እንዳያስከትሉ በሽጭ
ወይም በሌሎች የማስወገጃ መንገዶች መወገድ ይኖርባቸዋል፡፡
ሐ/ መጋዝኖችን እቃ ለመረከብ፤ለማስቀመጥ፤በቀላሉ ለማግኘትና ለማስረከብ
በሚያመች መንገድ መደራጀት ይኖርባቸዋል፡፡
መ/ ሙቀት ወይም በቅዝቃዜ ምክንያት በቀላሉ የሚጎዱ፤እንዲሁም ለጤንነት አደገኛ
የሆኑ ዕቃዎች እንደየ እቃዎች ባህሪ ተለይተዉ በተዘጋጁ መጋዝኖች መቀመጥ አለባቸዉ፡፡
ሠ/ የንብረት መጋዘን ሠራተኞችም የመጠቀሚያ ጊዜ ገደብ ያላቸዉን ዕቃዎች በተለየ
መከታተየ በመመዝገብ ክትትል ሊያደርጉ ይገባል፡፡
ረ/ በቆይታ ጊዜ የሚበላሹ ንብረቶች ሳይበላሹ የሚቆዩበት ጊዜ ከመጠናቀቁ ከ 6 ወር
በፊት ለሚመለከታቸዉ ማሳወቅ ያስፈልጋል፡፡
ሸ/ መጋዝኖች ለንብረት ድህንት ሲባል በወቅቱ በርና መስኮቶች በሚገባ መዘጋታቸዉን
እና ኤሌክትሪክ መብራት መጥፋቱን ማረጋገጥ፤ከሚመለከታቸዉ ሠራተኞች በስተቀር
በመጋዝን ዉስጥ እንዳይገቡ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

26. የንብረት ከመጋዘን ዉጭ የሚቀመጥበት ሁኔታ


1) የፋብሪካዉ ንብረት ለብልሽት እንዳይደረግ በንብረት መጋዘን እንዲቀመጥ ማድረግ ቅድሚያ
የሚሰጠዉ አሰራር ነዉ፡፡
2) ከላይ አንቀጽ 26 በተራ ቁጥር 1 ላይ የተገለጸዉ ቢኖርም በንብረቶች የተፈጥሮ ባህሪ
ምክንያት በመጋዘን ሊቀመጡ የማይችሉ እና ከመጋዝን ዉጭ ለተወሰነ ጊዜ ቢቀመጡ
ለብልሽት የማይደረጉ ወይም ከአግልግሎት ዉጭ ሊሆኑ ማይችሉ ንብረቶችን ማለትም
በጣም ረዥም እና ክብደት ያላቸዉ እቃዎችንና ሌሎች የዚህ ዓይነት ባህሪ ያላቸዉን
ንብረቶች ከንብረት መጋዘን ዉጭ በፋብሪካዉ ግቢ ዉስጥ ማስቀመጥ ይቻላል፡፡ ይህም
ሲሆን፡-
ሀ/ እንደ ንብረቱ ሁኔታ ታይቶ በተቻለ መጠን የሚቀመጡበት ቦታ የተሻለና
ጊዜያዊ ጥላ ወይም ከለላ ሊደረግላቸዉ ይገባል፡፡
ለ/ በእቃዎች ባህሪ ምክንያት በግቢ ዉስጥ እንዲቀመጡ በአቅርቦትና ሎጅስቲክ
መምሪያ ወይም በሽያጭና ገበያ ጥናት ኃላፊ እዉቅና ያላቸዉና ሰለጥበቃቸዉም
ለጥበቃ ክፍሉ/ለጥበቃ ሠራተኞች/በህጋዊ ደብዳቤ የታዘዘ መሆን ይኖርበታል፡፡
ሐ/ የጥበቃ ሠራተኞች በሚቀያየሩበት ጊዜ አስፈላጊዉን ቅኝት በማድረግ ወይም
እንደአስፈላጊነቱ ቆጣራ በማድረግ ንብረቶች በአካል መኖራቸዉን አረጋግጠዉ
መረካከብ ሥራቸዉን መጀመር ያለባቸዉ ሆኖ፤ችግር ሲኖር በእለቱ ለሚመለከተዉ
አካል በጽሁፍ ማመልከት/ማስታወቅ አለባቸዉ፡፡
መ/ እናዚህ ከመጋዘን ዉጭ የተቀመጡ ንብረቶችን በተቻለ ፍጥነት ለተፈለገዉ
አገልግሎት እንዲዉሉ የአቅርቦትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት ክትትል ማድረግ
አለበት፡፡
27. የንብረት በር መዉጫ አጠቃቀም
1) በግለሰብ ስም ወጭ ከተደረጉት ንብረቶች፤እንደ ላፕቶፕ፤ ሞባል፤ኤልሲዲ፤የፔዳል
ብስክሌት፤የደንብ ልብስ፤ካልኩሌተር በስተቀር ማናቸዉም ንብረት ከግቢ በሚወጣበት ጊዜ
በንብረት ወይም በሽያጭ ክፍል ኃላፊ ወይም በጠቅላላ አገልግሎት ኃላፊ በኩል ተፈርሞ በሚሰጥ
የበር መዉጫ ፈቃድ መሠረት ከግቢ እንዲወጡ መደረግ አለበት፡፡
2) ከላይ አንቀጽ 27 በተራ ቁጥር 1 ላይ የተቀመጠዉ ሲፈጸም፤-
ሀ/ የበር መዉጫ ፍቃዱን የያዘ ሠራተኛ፤አሽከርካሪ ወይም ደንበኛ እቃዉን ለማዉጣት
እንዲችል መዉጫ ፈቃዱን ለጥበቃ ሠራተኛዉ መሰጠት ይኖርበታል፡፡
ለ/ የጥበቃ ሠረተኛዉም የሚወጣዉን የእቀ መጠንና አይነት በማረጋገጥ እቃዉ
እንዲወጣ ካደረገ በኃላ የበር መዉጫ ፈቃዱን ፋይል አድርጎ በማስቀመጥ በተፈለገ ጊዜ
ያቀርባል፡፡
ሐ/ የተለያዩ እቃዎችን ጭነዉ በፋብሪካዉ ግቢ የሚያድሩ/የሚያራግፉ ተሸከርካሪዎች
ወይንም ደንበኞች የያዙትን ዕቃ ለጥበቃ ሠራተኞች አስመዝግበዉ ወይም የጭነት ሰነድ
አሳይተዉ መግባት ይኖርባቸዋል፡፡ ከግቢ ሲወጡም ባዶ መሆናቸዉ መረጋገጥ አለበት፡፡
28. የስቶክ ቆጠራ አፈፃፀም
1) ስቶክ ቆጣራ ቢንስ በአመት አንድ ጊዜ መካሄድ አለበት፡፡ ሆኖም ድርጅቱ በንብረት ወይም በመጋዘን
ደህንነት ላይ የተለያዩ ሁኔታዎች ሲከሰቱ ወይም አዲስ ሠራተኞች ሲመድቡ በዓመት ከአንድ ጊዜ
በላይ የስቶክ ቆጠራ ሊካሄድ ይችላል፡፡
2) የንብረት ቆጠራና ቁጥጥር በመጋዘን ያለ ንብረትንና ግለሰቦች ወጭ አድርገዉ የሚጠቀሙበትን
ንብረት ማካተት ይኖርበታል፡፡
3) የንብረት ቆጣራ የሚደረገዉ ዋና ስራ አስኪያጁ በሚያቋቁመዉ ከ 3 እስከ 5 አባላት ባሉት ጊዜያዊ
ቡድን ይሆናል፡፡
4) የንብረት ቆጠራ ቡድኑን በሰብሰቢነት የሚመራዉ ለዚህ ስራ የተመደበዉ የዉስጥ ኦዲት ክትትል
ኦፊሰር ይሆናል፡፡የዉስጥ ኦዲት ቁጥጥር ኦፊሰር እጥረት በሚያጋጥምበት ወቅት ከአባላቱ አንዱ
ሊወከል ይችላል፤

29. የንብረት ቆጠራ ከመደረጉ በፊት መደረግ ያለባቸዉ ዝግጅቶች


1) የንብረት የቆጠራ ፕሮግራም በአቅርቦትና ሎጅስቲክስ መምሪያ ወይም በሽያጭና ገበያ ጥናት
መምሪያ በኩል ለሚመለከታቸዉ የንብረት ቆጠራ ለሚደረግባቸዉ የስራ ሂደቶች/አካላት
እንዲደርስ ማድረግ ይገባል፡፡
2) በመጋዘንና በየመምሪያዉ ያሉትን ንብረቶች አቀማመጥ ማስተካከል፤
3) አዲስ የቀረቡ የእቃ ወጪ ጥያቄዎች ቆጠራዉ ከመጀመሩ በፊት ወጪ መደረግ ይኖርባቸዋል፡፡
4) ንብረት ቆጠሪዎች የተሠራባቸዉን የንብረት ገቢና ወጭ ደረሰኞች እንዲሁም የንብረት
መመዝገቢያ ካርዶች ላይ ለቆጠራ ሥራ የተደረሰበት በሚል አጭር ፊርማ /Cut off/ ማድረግ
አለባቸዉ፡፡

30. የስቶክ/የንብረት ቆጠራ ሂደት


1) በቆጠራ ወቅት ቋሚ፤አላቂ ዕቃና የምርት ግብዓቶችና ለሽያጭ የተዘጋጁ ምርቶች በዓይነትና
በየምድባቸዉ ተለይቶ መመዝገብ ይኖርበታል፤
2) ወጭ ሆነዉ በአገልግሎት ላይ ያሉ ቋሚ ንብረቶች መለያ ቁጥር (PIN) ያልተሰጣቸዉ ከሆነ
መለያ ቁጥር መሰጠት ይገባል፡፡
3) በእየለቱ በተቆጠረዉ ላይ እና ዕቃዉ ተቆጥሮ እንዳበቃ በተዘጋጀዉ ቅጽ ላይ ቆጠሪዎች እና
አስቆጣሪዉ ይፈራረሙበታል፤
4) የቆጠራዉ ዉጤት የተሞላበት ቅጽ የንብረት መዝገብ ከሚያመለክተዉ ከወጪ ቀሪ ጋር
ተመሣክሮ የብልጫ ወይም የጉድለት ሪፖርት ለዋና ስራ አስኪያጅ ይቀርባል፡፡

31. የቆጠራ ዉጤት ሪፖርት ዝግጅት


1) የቆጠራ ዉጤት ሪፖርት በቆጠራ ቡድን ሰብሳቢዉ ተዘጋጅቶ በጋራ ስምምነት ላይ ከተደረሰ
በኃላ በፊርማ ተረጋግጦ ለሚመለከተዉ ኃላፊ ይቀርባል፡፡
2) የቆጠራዉ ሪፖርት ንብረቶች የሚገኙበትን ሁኔታ ማመላከት አለበት ማለትም አገልግሎት
የሚሠጡ፤ተጠግነዉ አገልግሎት የሚሰጡ ወይም አገልግሎት የማይሰጡ በሚል ሊለዩ ይገባል፤
3) የቆጠራዉ ሪፖርት የማሻሻያ ሃሣቦችን፤በቆጠራዉ በተገኘዉ ዉጤት መሠረት
የዲሲፕሊን እርምጃ ሊወሰድባቸዉ የሚገቡ ጉዳዮች ካሉ ማመላከት አለበት፡፡
4) ኬሚካል፤መደሃኒትና የመሳሰሉ ንብረቶችን በተመለከተ የመጠቀሚያ ጊዜያቸዉን
የሚለይ ወይም የሚያመላክት መሆን ይኖርበታል፡፡
5) እንደ አስፈላጊነቱም በቆጠራዉ ወቅት የተስተዋሉ ለንብረት አስተዳደሩ
ዉጤታማነት የሚረዱ ሌሎች የማጠቃለያ አስተያየቶችን ያካተተ መሆን
ይኖርበታል፡፡
6) በንብረት ቆጣራ ወቅት የቆጠራ ኮሚቴ /ቡድን/ መወገድ ስላለበት ንብረት በሪፖርቱ
ዉስጥ በማካተት የዉሳኔ ሀሳብ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
7) ሪፖርት የቀረበለት አካል በሪፖርቱ ጭብጦች መሰረት አስፈላጊዉን ማስተካከያና
እርምጃ መዉሰድ አለበት፡፡

32.. በተለዩ ንብረቶች ላይ ኦዲትና ቁጥጥር ስለማድረግ


1) የፋብሪካዉ የዉስጥ ኦዲተር የተለየ ባህሪ ያላቸዉን ዕቃዎች ማለትም ለሕዝብ ጤና አደገኛ
የሆኑ ወይም ጉዳት የሚያስከትሉ የጦር መሳሪያዎች፤ኬሚካሎችን እንዲሁም ከፍተኛ ዋጋ
ያላቸዉ ዕቃዎችን እና ፈጣን እንቅስቃሴ በሚታይባቸዉ ንብረቶች ከሌሎች ንብረቶች በተለየ
ሁኔታ በ 3 ወር አንድ ጊዜ ቆጠራ፤ ቁጥጥርና ክትትል ማድረግ አለበት፡፡
2) የፋብሪካዉ ንብረት አስተዳደር በትክክል በመመሪያዉ መሰረት እየተፈፀመ ስለመሆኑ በዉስጥ
በኦዲተር በአመት አንድ ጊዜ እያንዳንዱ እቃ ግ/ቤት ኦዲት ተደርጎ ሊረጋገጥ ይገባል፡፡
3) ፋብሪካዉ አቅርቦትና ሎጂስቲክስ መምሪያ ኃላፊ አፈፃፀሙን የመከታተል ኃላፊነት አለበት፡፡
4) አሳማኝ ባልሆነ ምክንያት የጎደለ ንብረት ሲኖር የጉድለት መጠኑ እና ምክንያትም ካለ በዝርዝር
ለሚመለከታቸዉ ኃላፊዎች ቀርቦ ዉሳኔ እንዲያገኝ ሪፖርት መደረግ አለበት፡፡
33. የንብረት ጥገና እና አመዘጋገብ
1) ጥገናዉ የፋብሪካዉ ዋና ስራ አስኪያጅ ወይም በሚመለከታቸዉ አካላት ንብረቱ ኢኮኖሚያዊና
ዉጤታማ በሆነ መንገድ አገልግሎት እንዲሰጥ ለማድረግ በተዘረጋዉ የእንክብካቤና ጥገና ስርዓት
መሰረት ይከናወናል፡፡
2) ጥገናዉ ወጭ ከመቀነስ አንፃር በቅድሚያ የዉስጥ ባለሙያዎችን በመጠቀም የሚከናወን
ይሆናል፡፡
3) ጥገናዉ ከአቅም በላይ ሲሆን ብቻ የዉጭ ድርጅቶችን በጫረታ በማወዳደር፤አሸናፊ በመለየትና
ዉል በመያዝ የሚፈጸም ይሆናል፡፡
4) ከፍተኛ የጥገና ወጪ በቋሚ ንብረት ሂሳብ ስለመመዝገብ፤

ሀ/ ተሸከርካሪዎችን ወይም ማሽነሪዎችን አንድ ጊዜ ለማስጠገን ወይም እድሳት


ለማድረግ የወጣዉ ሙሉ ወጪ የንብረቱን አገልግሎት ዘመን ሊያራዝም ይችላል ተብሎ
ሲታመንበትና ለማስጠገን ወይም እድሳት ለማድረግ የወጣዉ ወጪም
ከማሽነሪዉ/ከተሸከረካሪዉ የግዥ ዋጋዉ ከ 25% በላይ ከሆነ በቋሚ ንብረት
ከተመዘገበዉ የንብረቱ ሂሳብ ላይ ታክሎ መመዝገብ አለበት፡፡

ለ/ የሌሎች ቋሚ ንብረቶችን አንድ ጊዜ ለማስጠገን ወይም እድሳት ለማድረግ የወጣዉ


ሙሉ ወጪ የንብረቱን የአገልግሎት ዘመን ሊያራዝም ይችላል ተብሎ ሲታመንበትና
ለማስጠገን ወይም እድሳት ለማድረግ የወጣዉ ወጪ ከእቃዉ ግዥ ዋጋዉ ከ 40% በላይ
ከሆነ በቋሚ ንብረት ከተመዘገበዉ የንብረቱ ሂሳብ ላይ ታክሎ መመዝገብ አለበት፡፡

34. ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት የጠፋ ወይም የወደመ ንብረትን ስለመሠረዝ

1) ለፋብሪካዉ ስራ አገልግሎት ወጭ ተደርጎ የተወሰደ ንብረት ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት


መጥፋቱ መበላሸቱ ወይም መዉደሙ እንደታወቀ የንብረቱ ተጠቃሚ በመጀመሪያ
ለፋብሪካዉ በፅሁፍ ማሳወቅ አለበት፡፡
2) የጠፋዉ ወይም የወደመዉ ንብረት ከተጋልጋዩ አቅም በላይ በሆነ ምክንያት የጠፋ፤የወደመ
ስለመሆኑ የሚገልጽ ማስረጃ ከፖሊስ ሲቀርብና በዋና ስራ አስኪያጁ ሲወሰን ከመዝገብ
ይሰረዛል፡፡
3) ንብረቱ በትክክል የጠፋበት ሠራተኛ በስራ ላይ መጉላላትን እንዳይፈጥር ከማሰብ አከኳያ
በተቋሙ በኃላፊዎች ተረጋግጦ ሲፈቀድለት የጠፋዉ ንብረት በድጋሚ ሊሰጠዉ ይችላል፡፡

35. የጠፋ ንብረትን ስለመተካት


1. ኃላፊዎች ከመደበኛ የስራ ሰዓት ዉጭ ከቢሮዉ ዉጭ ሆነዉ የፋብሪካዉን ስራ የሚሰሩባቸዉ
ሞባይል፤ፍላሽ እና CDMA ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ቢጠፋባቸዉ እንዲተኩ አይደረግም፡፡
2. ሠራተኞች የሚጠቀሙባቸዉን ንብረቶች ጥንቃቄ ወይም እንከብካቤ ባለማድረጋቸዉ ምክንያት
የተረከቡት ንብረት መጥፋቱ ወይም መዉደሙ ከተረጋገጠና እንዲተካ ዉሳኔ ላይ ከተደረሰ
የእቃዉን የአግልግሎት ዘመንና እቃዉ በጠፋበት ወቅት የነበረዉን የገበያ ዋጋ ግምት ዉስጥ
በማስገባት ከዚህ በታች በተመለከተዉ ሰንጠረዥ የቅናሽ መቶኛ ስሌት መሰረት ገንዘቡን
እንዲከፍሉ ይደረጋል፡፡

ተ. የንብረቱ አገልግሎት ዘመን ከወቅቱ የገበያ ዋጋ


ቁ የሚደረግ ቅናሽ %

1 እስከ 1 ዓመት ያገለገለ ንብረት ከገበያ ዋጋዉ 0.0%

2 ከ 1 ዓመት በላይ እስከ 2 ያገለገለ ከገበያ ዋጋዉ 10%

3 ከ 2 ዓመት በላይ እስከ 4 ያገለገለ ከገበያ ዋጋዉ 20%

4 ከ 4 ዓመት በላይ እስከ 6 ያገለገለ ከገበያ ዋጋዉ 30%

5 ከ 6 ዓመት በላይ እስከ 8 ያገለገለ ከገበያ ዋጋዉ 40%

6 ከ 8 ዓመት በላይ እስከ 10 ያገለገለ ከገበያ ዋጋዉ 60%

7 ከ 10 ዓመት በላይ እስከ 12 ያገለገለ ከገበያ ዋጋዉ 70%

8 ከ 12 ዓመት በላይ እስከ 14 ያገለገለ ከገበያ ዋጋዉ 80%


9 ከ 14 ዓመት በላይ እስከ 16 ያገለገለ ከገበያ ዋጋዉ 90%

10 ከ 16 ዓመት በላይ ያገለገለ ንብረት ከገበያ ዋጋዉ 95%

3. ይህ የማስከፈያ ስሌት ከባለሞተር ተሸከርካሪ እና ከጦር መሳሪያ በስተቀር በሌሎች ንብረቶች


ላይ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
4. የጠፋዉ/የወደመዉ ንብረት የመተኪያ ዋጋ ግምት በተቀመጠዉ ስሌት መሰረት የተሰላ ስለመሆኑ
ከመተካቱ በፊት በአቅርቦትና ሎጅስቲክስ ኃላፊ ከፀደቀ በኃላ ተግባራዊ ይሆናል፡፡
5. የጠፋዉ/የወደመ ንብረት ተሸከርካሪ ወይም የጦር መሳሪያ ከሆነ ከመጥፋቱ በፊት በዕለቱ
ለፖሊስ፤ለትራንስፖርት ቢሮ፤ለሚሊሻና ደኅንነት ጽ/ቤቶች ሪፖርት መደረግ ይኖርበታል፡፡
6. በተደጋጋሚ የመጥፋት ሪፖርት ለሚቀርብባቸዉ የቢሮ መጠቀሚያ ቁሳቁሶችና መሳሪያዎች
ከላይ የተቀመጠዉ የማስከፊያ ስሌት ቢኖርም፤ በጣም ዉድ የሆኑ ቋሚ ዕቃዎችን፤በቀላሉ
የማይገኙ ወይም ሊተኩ የማይችሉ ዕቃዎችን ጠፋብኝ በማለት ለመተካት የሚደረግ አዝማሚያ
ሊኖር ስለሚችል የዚህ ዓይነት ክስተት መፈፀሙን ድርጅቱ ካመነበት ከላይ አንቀጽ 35 ተራ
ቁጥር 1 ከተጠቀሰዉ የማስከፊያ ሠንጠረዥ በተለየ እንደ ልዩ ዕቃዉ ባህሪ የጠፋዉን ንብረት
ከእጥፍ በላይ በሆነ ዋጋ ወስኖ እንዲከፈል ማድረግ ይችላል፡፡

ክፍል አራት

የንብረት መድን ዋስትና

36. ኢንሹራንስ የሚገባለቸዉ የፋብሪካዉ ንብረቶች


1. የፋብሪካዉ ማሽነሪዎች፤ተሸከርካሪዎች፤ምርትና የምርት ግብዓት/ኬሚካል/ እና አንዳስፈላጊነቱ
ሌላ ንብረትም እየታየ ኢንሹራንስ ይገባላቸዋል፡፡
2. የንብረት ዋስትና በተገባበት ንብረት ላይ ጉዳት ከደረሰ በእለቱ ወይም በ 24 ሰዓት ዉስጥ ለመድን
ድርጅት ሪፖርት ይደረጋል፡፡
3. ተሸከርካሪዉ በግጭት ምክንያት ከተጎዳ፤የትራፊክ ህግን በማክበር በአቅራቢያ ለሚገኘዉ
ትራፊክ ፖሊስ ጽ/ቤት ሪፖርት መደረግ ይኖርበታል፡፡
4. ዋስትና የሰጠን የመድን ድርጅቱም ለወደመዉ/ለተጎዳዉ ንብረት በተገባዉ ዉል መሰረት ካሳ
እንዲከፈል ይደረጋል፡፡

ክፍል አምስት

የንብረት ገቢና ወጭ ደረሰኞችን መጠቀም የማያስፈልግባቸዉ ሁኔታዎች

37.በንብረት ገቢ ደረሰኝ ገቢ ማድረግ ሳያስፈልግ ሂሳብ ስለማወራረድ ስለሚቻልበት ሁኔታ፤


1. ግዥዉ በመስክ ተፈፅሞ ወዲያዉኑ ጥቅም ላይ በመዋሉ ምክንያት ዕቃዉን ወይንም
አገልግሎቱን በአካል አይቶ ገቢ ማድረግ የማይቻልባቸዉ ነዳጅና ቅባት፤የጎማ ጥገና አገልግሎት
ግዥ ገንዘቡን ወጭ አድርጎ ግዥዉን በፈጸመዉ ሠራተኛ ወይም ኃላፊ አማካኝነት በፋብሪካዉ
ስም በሚሰጡ እና በመስክ ግዥዉን በፈጸመዉ አካል ተረጋግጦ በሚቀርብ ደረሰኝ ሂሳቡ
መወራረድ ይችላል፡፡
2. የነዳጅ ግዥዉ የተፈጸመዉ በፋብሪካዉ አደራሽ ሆኖ ወዲያኑ ጥቅም ላይ በመዋሉ ምክንያት
ገቢና ወጭ ማድረግ ሳያስፈልግ በጠቅላላ አገልግሎት በኩል እየተረጋገጠ ግዥዉን በፈጸመዉ
አካል በኩል ደረሰኝ ሲቀርብ የሚወራረድ ይሆናል፡፡

ክፍል ስድስት

የተሸከርካሪዎች እና ሌሎች እቃዎች ስምሪትና ጥገና

38. ፋብሪከዉ የማሽነሪዎች እና ተሸከርካሪ ጥገናና ስምሪት


1. ¾Ti’]‹ ¾e^ eU]ƒ *ý_i” /¡ƒƒM e^ ¾T>Ÿ“¨’¨< uU`ƒ¡õM GLò ÃJ“M::
2. ¾i’]‹”“ SKª¨Ý‹ ØÑ“ lØØ`“ ¾¡ƒƒM Y^ ¾T>Ÿ“¨’¨< ¾Ti’]‹ እንክብካቤና ጥገና ክፍል
ሀላፊ ይሆናል፡፡3.
3. የተሸከርካሪዎችና የቢሮ መገልገያ ፈርፈኒቸሮች የስራ ስምሪት፤ ጥገና ቁጥጥርና የክትትል ሥራ
የሚከናወነው የሰው ሀይልና ጠቅላላ አገልግሎት የስራ ሂደት ይሆናል፡፡
39. የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች አጠቃቀምና ጥገና፤
1. የቴክኖሎጅ ውጤት የሆኑ የስራ መገልገያ መሳሪያዎች የብልሽት ጥገናቸው ከፍተኛ
ዕውቀትና ክህሎት ባላቸው ባለሙያዎች በመታገዝ የሚፈፀሙ በመሆናቸው በስራ ላይ
እንዳሉ ብልሽት ሲከሰት ጥገናው የሚከተሉትን ሂደቶች መሰረት በማድረግ መፈፀም
አለበት፡፡
ሀ/ የጥገና ጥያቄ ከተጠቃሚዎች በፎርማት ተሞልቶ እንዲቀርብ ማድረግ፤
ለ/ የጥገና በጀት መኖሩን በማረጋገጥ፤
ሐ/ የኢንፎርሽን ቴክኖሎጅ (IT) ባለሙያዊች በመ/ቤቱ ካሉ በቅድሚያ በእነሱ አቅም
የሚጠገኑ ብልሽቶችን እንዲጠገኑ ማድረግ፤
መ/ በውስጥ ባለሙያዎች ሊጠገን የማይችል ብልሽት የብልሽቱ ትክክለኛነት
በባለሙያዎች ከተረጋገጠ በኋላ ብቃትና ልምድ ካላቸው የውጭ የጥገና ተቋማት ወይም
ባለሙያዎች ጥገናውን ማካሄድ፤ ይህም በአገልግሎት ግዥ አግባብ የሚፈፀም ይሆናል፡፡
ረ/ ጠገናው በውሉ መሰረት በጥራት መጠገኑ በባለሙያው ተረጋገግጦ ክፍያ በመፈፀም
ንብረቱን መረከብ፤
40. የተሸከርካሪዎች አጠቃቀምና እቃ የመጫንና የማራገፍ ሥራ
የንብረቱን ደህንነት ከመጠበቅ አኳያ፤ ማንኛውም ሰራተኛ በእጅ፤ በእጅ በሚገፉ
ጋሪዎችን ወይም ባለሞተር ተሸከርካሪዎችን በመጠቀም ከቦታ ቦታ ንብረት ሲያንቀሳቅስ
ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ጥንቃቄዎች ማድረግ ይኖርበታል፡፡
1. አንድ ሰራተኛ በእገሩ ሲንቀሳቀስ ወይም ተሽከርካሪ ሲያንቀሳቅስ ያልተፈቀደውን መስመር
መጠቀም የለበትም፡፡
2. ተሸከርካሪውን ከተወሰነው ወይም ከሚገባው ፍጥነት በላይ በማሽከርከር ንብረት ላይ ጉዳት
ማድረስ የለበትም፡
3. በፋብሪካው ውስጥ ፎርክ ሊፍቶችን፤ እጅ ጋሪዎች ወይም ንብረት ሊያራግፉ የሚገቡ ባለሞተር
ተሸከርካሪዎች የሚጠቀሚ አሽከርካሪዎች በተሸከርካሪው ላይ በተጫነው ወይም በተቀመጠው
ንብረት ላይ ጉዳት እንዳያደርስ በጥንቃቄ ማሽከርከር አለባቸው የሚመለከታቸው ክፍሎችም
ክትትል ማድረግ አለባቸው፡፡
4. የሚቀመጠው እቃ ከተፈቀለት ቦታ ውጭ መሆን የስራ እንቅስቃሴን በሚያውክ መልኩ መሆን
የለበትም
5. እቃ ሲነሳ ወይም ሲጫንም ሆነ ሲቀመጥ /ሲራገፍ/ እንዳይጎዳ መጣል ወይም መወርወር
የለበትም
6. እቃው በቦታው ሲቀመጥ ሳይመሰቃቀል፤ ሳይዘነፍና ሳይጣመም በአግባቡ መደርደር አለበት
7. የተቀመጠው እቃ እንዳይንከባለል እንዳይንሸራተት መደገፍ ወይም መታሰር አለበት
8. በግቢ ውስጥ ተሸከርካሪ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ በመጠገንና ማጠብ፤ ዘይት እና ጋዝ በማፍሰስ
መንገዱን /አስፓልቱ/ እንዲጎዳ መደረግ የለበትም፡፡
ክፍል ሰባት
የንብረት አወጋገድ ሂደት
41. ንብረት የማጣራት ተግባር፤
1. የማስወገድ ተግባር፤ የማጣራት ተግባር ሳይካሄድ የማይሰራ ተግባር በመሆኑ ሁሉም የፋብሪካው
ሰራተኛ በተመደበበት የስራ ክፍል የማያስፈልገውን እየለየ በተዘጋጀው ቅፅ ላይ በማስፈር ለስራ
ክፍሉ ሃላፊ ማሳወቅ ይኖርበታል፡፡
2. ሂደቶች በይዞቴቸው ስር ያለውን ንብረት እንዲወገድ ለምን እንዳስፈለገ ለይተው የማወቅ
ሃላፊነት አለባቸው፡፡
3. የንብረቱ ህጋዊ ባለቤት ማን እንደሆነ መለየት፤
4. ለጤና አደገኛ የሁኑ ኬሚካሎች /የጨረር ጉዳት/ የሚያስከትሉ ሆነው ሲገኙ በማጣራት ተግባር
ላይ አስፈላጊውን እገዛ ከሚመለከተው አካል ትብብር መጠየቅ፤
5. የማያስፈልጉ ንብረቶች ከዚህ በታች የተመለከቱትን ሊያካትቱ ይችላሉ

በምድብ ሀ ምርት፤ የምርት ግብዓትና ስክራፕ

1. በዝርዝር ያልተያዙና ለረዥም ጊዜ አገልግሎት ያልሰጡ


2. ከሚፈለገው በላይ የተመረተው ምርት
3. በምርት ሂከት መካከል ከሚፈለገው በላይ ያለ ክምችት
4. እንከን /ጉድለት/ ያለበት ምርት

በምድብ ለ ማሽነሪዎች፤ ተሸከርካሪዎች እና መለዋወጫዎች፤ የላቦላቶሪ መሳሪያዎች

1. በእርጅና ምክንያት አገልግሎት የማይሰጥ


2. በአገጣጠም /በአጠቃቀም/ ጉድለት ምክንያት አገልግሎት የማይሰጥ
3. በተጠየቀው መስፈርት መሰረት ባለመገዘቱ
4. ከሚፈልገው በላይ ወጭ በመደረጉ ምክንሰያት የፈጠረ ክምችት

በምድብ ሐ የጽህፈት መሳሪያዎች፤ የፅዳት ቁሳቁሶች መድሃኒቶች ፈርኒቸሮች


1. በቆይታ ምክንያት ጊዜ አልፎበት አገልግሎት የማይሰጥ
2. በተጠየቀው መስፈርት ባለመገዛቱ

ምድብ መ/ጥቅም የማይሰጡ ልዩ ልዩ ሰነዶች/ዶክመንቶች/፤

42. . የንብረት ማስወገድ ሂደት


ሀ/ ቋሚና አላቂ ንብረቶች አወጋገድ

እያንዳንዱ የስራ ክፍል ሃላፊ ለክፍሉ ስራ የማያስፈልጉ የንብረቶችን ከክፍሉ ሰራተኞች

ጋር በማየት፤-

1. ከሚፈልገዉ መጠን በላይ/ትርፍ የሆነ ቋሚ ንብረት ወደ ንብረት ክፍል እንዲመለስ ማድረግ፤

2. ከሚፈልገዉ መጠን በላይ የሆነ አላቂ ንብረት ከሆነ የእቃ ማስተላለፊያ ፎርም በመጠቀም ወደ

ሌሎች የስራ ክፍሎች እንዲተላለፍ ማድረግ፤

3. ተጠግነዉ ለክፍሉ ስራ የሚዉሉ ከሆነ ተጠግነዉ በስራ ላይ እንዲዉሉ ማድረግ፤

4. በዚህ አንቀጽ ከ ሀ እስከ ሐ ከተጠቀሱት ዉጭ ከሆነ ቀይ ካርድ እንዲለጠፍበት በማድረግ በክፍሉ

ባለዉ ጊዚያዊ ቦታ እንዲቆይ ማድረግና ለአቅረቦትና ሎጆስቲክስ መምሪያ ክፍል በውቅቱ

በፅሁፍ ማሳወቅ አለበት

5. ሎጆስቲክስና አቅርቦት መምሪያ ቀይ ካርድ የተደረገበት ልዩ ልዩ ንብረት ከየስራ ክፍሉ ሲደርሰው

ወደ ቀይ ካርድ ማእከላዊ ቦታ ከመጓጓዘቸው በፊት ወስደው መጠቀም የሚፈልጉ ሌሎች የስራ

ክፍሎች የእቃውንን ዝርዝር በውጭ ማስታወቂያ ያስታውቃል

6. ንብረቱን ወስዶ መጠቀም የሚፈልግ አካል ጥያቄ ሲያቀርብ የተፈለገው እቃ የመደበኛን ንብረት

ገቢና ወጭ ስርአት በተከተለ መንገድ ማስተናገድ ይኖርበታል

7. የአቅርቦትና ሎጀስቲክስ ቀይ ካርድ የተደረገበት ልዩ ልዩ ንብረት ከየስራ ሂደቱ ሲደርሰውና ወስዶ

መጠቀም የሚፈልግ የውስጥ ሠራተኛ አለመኖሩ ሲረጋገጥ ወደ ማእከላዊ ቀይ ካርድ ቦታ

በመጓጓዝ እንደከማችና እንዲወገድ ያደርጋል

43. የምርት ግብአት ምርትና ተረፈምርት አወጋገድ ሂደት


1. በተለያዩ ምክንያቶች ከሚፈለገው በላይ የተመረተ የምርት ክምችት ሲኖር ምርቱን ለሚፈልጉ
ለሌሎች ደንበኞች ቅድሚያ የተመረተውን ቅድሚያ /ferst in ferst out/ /FIFO/ በሚለው
ንብረት   ›ÖnkU S`I Sc[ƒ ¾ ሽያጭና የገበያ ጥናት የስራ ሂደት መሽጥ ይኖርበታል
2. በአንቀጽ 43 በተራ ቁጥር 1 ላይ የተጠቀሰው እንደጠበቀ ሆኖ ለ 6 ተከታታይ ወራት ያህል የቆየ
የምርት ክምችት ሲፈጥር ሽያጭና የገበያ ጥናት የስራ ሂደት በአይነት በመለየት በመዘርዘር
ለአቅርቦትና ሎጆስትክስ መምሪያ ማሳወቅ ይኖረርበታል
3. የአቅርቦትና ሎጀስቲክ መምሪያ በአንቀጽ 42 ተራ ቁጥር 7 መሰረት የተከማቸውን ንብረት በዋባ
ስራ አስኪያጅ በማስወሰንና አዋጭ የሆነውን የሽያጭ ዘዴ በመጠቀም እንዲወገድ ያደርጋል፤
4. በተለየ ምክንያት ጉድለት ምርት ሲኖር የጥራት ቁጥጥርና ደህንነት የስራ ሂደት በአይነት
በመለየት በዝርዝር ለምርት ሂደት ያሳውቃል፤
5. የምርት የስራ ሂደትም ጉድለቱ እንዲስተካከል /ተመልሶ/ ጥቅም ላይ እንዲውል ያደርጋል፡፡ ከዚህ
ውጭ የሆን ስክራፕ ሲኖር በዝርዝር ለአቅርቦትና ሎጀስቲክስ መምሪያ ያሳውቃል
6. በተለያየ ምክንያት ጉድለት ያለበት የምርት ግብአት ሲኖር የጥራት ቁጥጥርና ደህንነት የስራ
ሂደት በዝርዝር ለአቅርቦትና ሎጀስቲክስ መምሪያ ያሳውቃል
7. በተለያየ ምክንያት እንደ ኬሚካል፤ ራበር፤ ሲል እና ያለ የምርት ግብአት ክምችት ሲኖር በቀጥታ
ለዋና ስራ አስኪያጅ ቀርቦ ውሳኔ እንዲያደርግ ይደረጋል፡፡
44. እንዲወገዱ ቀይ ካርድ የተደረገባቸውን ንብረቶች ማሰባሰብ
1. ከየትኛውም የስራ ክፍል የማይፈለግ ንብረት በዝርዝር ለአቅርቦትና ሎጀስቲክስ መምሪያ
ሲደርሰው ወደ ተመረጠው ቀይ ካርድ ማዕከላዊ ቦታ አጓጉዞ እንዲከማችና እንዲጠበቅ ያደርጋል
2. በማዕከላዊ ቀይ ካርድ ቦታ ላይ የተከማቸው ወይም ንብረት በወቅቱ እንዲወገድ አቅርቦትና
ሎጀስቲክስ መምሪያ ቅጹ በሚጠይቀው ዝርዝር መሰረት ሞልቶ የውሳኔ አስተያየት ወይም
ፕሮፖዛል ለዋና ስራ አስኪያጅ ያቀርባል
3. አቅርቦትና ሎጀስቲክስ መምሪያ ውሳኔ ሲደርሰው በውሳኔው መሰረት የተለያዩ የማስወገጃ
ዘዴዎችን በመጠቀም የሚያስወግድ ይሆናል፤
45. ቀይ ካርድ የተደረገባቸው ንብረቶች ማስወገጃ ዘዴዎች
የሚወገዱ ንብረቶች የሚከተሉትን አራት አማራጭ ዘዴዎች በቅደም ተከተል ተግባራዊ
በማድረግ ማስወገድ ይገባቸዋል
1. የንብረቱን ጠቃሚ አካላት ፈትቶ በመለዋወጫነት ጥቅም ላይ በማዋል ወይም በመሸጥ
ማስወገድ.፣
2. ንብረቱ ባለበት ሁኔታ በህዝብ ጨረታ ወይም በሀራጅ በመሸጥ ማስወገድ
3. ለሌሎች ተቋማት በማዛወር ወይም በማስተላለፍ ማስወገድ
4. በመጨረሻም ከላይ በተገለጹት በሶስቱ በማስወገጃ ዘዴዎች ተሞክሮ ሊወገድ ያልቻለና ምንም
ጠቀሜታ የሌለውን ንብረት በውዳቂነት /በመቅበር/ /በማቃጠል/ መወገድ አለበት፣
5. በልዩ ሁኔታ ከተለየ በስተቀር በመጋዘን ወይም በግቢ ውስጥ ወይም በማእከላዊ ቀይ ካርድ ቦታ
ያለ ጥቅም የማይሰጥ ንብረት ከአንድ የበጀት አመት በላይ ሳይወገድ መቆየት የለበትም፣
46. ንብረትን ፈታቶ በመለዋወጫነት ጥቅም ላይ ማዋል ወይም መሸጥ
1. የአንድን ንብረት አካላት በባለሙያ ድጋፍ ፈትቶ በመለዋወጫ እቃነት መጠቀም ወይም መሸጥ
የሚቻለው ንብረቱን ባለበት ሁኔታ መሸጥ የማይቻል ሲሆን ወይም ባለበት ሁኔታ ከመሸጥ ይልቅ
ፈትቶ መጠቀም ወይም መሸጥ የበለጠ ጥቅም የሚያስገኝ መሆኑ ሲታመንበት ብቻ ነው፣
2. በመለዋወጫነት ጥቅም ላይ እንዲውሉ ወይም እንዲሸጡ ከተወሰነባቸው መሳሪያዎች ላይ
ጠቃሚ አካሎችን እንዲፈታ በማድረግ አግባብ ባለው የንብረት አስተዳደር አሰራር መሰረት ገቢ
እንዲሆኑና ጥቅም ላይ እንዲውሉ ወይም በጨረታ እንዲሸጡ ማድረግ ይገባል፡፡
3. ተፈትተው እንዲሸጡ የተወሰመባቸው መለዋወጫዎች የጨረታ መነሻ ዋጋ፣ የመለዋወጫውን
አይነት የገበያውን ሁኔታባ ሌሎች መረጃዎችን መሰረት በማድረግ ሊሸጥ ይችላል፡፡
47. ንብረትብ በሽያጭ የማስወገድ ኃላፊነትና ሂደት
1. ቀይ ካርድ የተለጠፈባቸውን ንብረቶች ውሳኔ ሲያገኙ የማስወገድ ተግባርና ሃላፊነት የግዥና
ንብረት አስተዳደር ስራ ሂደት ይሆናል፡፡
2. ከላይ በተራ ቁጥር 1 ላይ የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ ተግባሩ ከግዥና ንብረት አስተዳደር
ስራ ሂደት አቅም በላይ የሚሆን ከሆነ ወይም አስተያየት ለማቅረብ የቴክኒክ እገዛን የሚጠይቅ
ከሆነ፣ እንዳስፈላጊነቱ ድጋፍ የሚያደርግ ኮሚቴ በምክትል ስራ አስኪያጅ (ድጋፍ ሰጭ)
አማካይነት ሊቋቋም ይችላል፡፡
3. ግዥና ን/አስተዳደር የስራ ሂደት የሚወገዱ ንብረቶች ዝርዝር፣ የማስወገጃ ዘዴና መነሻ ዋጋ
ለይቶ የውሳኔ ሀሳብ ለዋና ስራአስኪያጅ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
4. ለሽያጩ ስራ ቢያንስ ሶስት አባላት ያሉት የሽያጭ ኮሚቴ ይዋቀራል፡፡
5. በተናጠል ወይም በቡድን በዋጋ ግምት ስራ የተሳተፈ ግለሰብ የሽያጭ ስራ የተሳተፈ ግለሰብ
በሽያጭ ስራ ውስጥ መሳተፍ የለበትም፡፡
6. የንብረት ሽያጭ ቡድኑ በፀደቀው ውሳኔ መሰረት የጨረታ ሰነድ ያዘጋጃል፣ ማስታወቂያ
ያወጣል፣ ጨረታ ይከፍታል፣ ያጫርታል፣ አሸናፊውን በመለየት ለሥራ ሂደቱ ኃላፊ አቅርቦ
ያስፀድቃል፡፡
7. ጣውላ፣ ከረጢት፣ ቁርጥራጭ ብረት፣ ያገለገለ ዘይትና ቅባት፣ ባዶ በርሚል፣ ያገለገለ ጎማ፣
በፋብሪካው ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ በፍጥነት ጥቅም ላይ እየዋሉ የሚቀየሩ በመሆናቸውና
የማከማቻ ቦታ ጥበት የሚያስከትሉ ስለሆኑ ሌላ ውሳኔ ሳይጠብቅ በጨረታ መሸጥ አለባቸው፡፡
48. ለሚወገድ ንብረት የሽያጭ መነሻ ዋጋ መገመት
የሚወገድ ንብረት የሽያጭ መነሻ ዋጋ ግምት ከሚከተሉት አማራጮች ውስጥ
የተሸለውን አማራጭ በመምረጥ የዋጋ ግምተረ መተመን ይቻላል፡፡
ሀ. የንብረቱ አገልግሎት ዘምን የሚታወቅ ከሆነ በዚህ መመሪያ አንቀጽ 30 ንኡስ አንጽ 1
የጠፋ ንብረትን ለማስተካት በተቀመጠው ስንጠረዥ ላይ በተቀመጠው ስሌት /%/
መሰረት የመነሻ ዋጋ ግምት መስጠት ይቻላል፡፡
ለ/ በተለያዩ ምክንያቶች የንብረቱ አገልግሎት ዘመን ሊታወቅ የማይችል ከሆነ ንብረቱ
ያለበትን አቋም መሰረት በማድረግ በሚቀጥለው ሰንጠረዥ በተቀመጠው ገበያ ዋጋ
በሚደረግ የመቀነሻ /%/ ስሌት መሰረት ሊፈፀም ይችላል፡፡

ንብረቱ ያለበት ሁኔታ ከወቅቱ የገበያ ዋጋ የሚደረግ ቅናሽ (%)

በጣም ጥሩ በሚባል ደረጃ 25 %

በጥሩ ሁኔታ ላይ ያለ 50 %

ጥሩ ባልሆነ አቋም ላይ 75 %

ሐ. የምርት መገጣጠሚያ /ፊቲንግ፣ መለዋወጫዎች፣ ወይም በትንሽ መጠን ጥሬ እቃ የሚፈልጉ


ድርጅቶችና የመሳሰሉት እቃዎች ሲኖሩ የእቃ ሽያጭ ዋጋ ተመንን በተመለከተ ተጨማሪ
እሴት ታክስን ጨምሮ ባለው በተገዛበት ዋጋ ላይ ሰላሳ አምስት በመቶ /35%/ ተጨምሮ
ሽያጭ ይከናወናል፡፡ ይህም 20% አስተዳደራዊ ወጪ ሲሆን 15% የንብረት ትርፍ ነው፡፡
ይህም ሆኖ በዚህ ዘንቀጽ ሐ ከተጠቀሱት ውጪም ሌሎች ለድርደጅቱ የሚጠቅሙ
መገመቻ ዘዴዎችን መጠቀም ይቻላል፡፡

49. የሚወገዱ ንብረቶችን በጨረታ ወይም በሀረጅ መሸጥ


1. ለፋብሪካው የተሸለ ዋጋ ለማግኘት ሲባል የሚወገዱ ንብረቶች በግል ጨረታ ይሸጣሉ፡፡
2. በጨረታ ሽያጭ በቂ ተወዳዳሪ ካልቀረበ ወይም የቀረበው ዋጋ ተቀባይነት ካላገኘ ፋብሪካው
ጨረታውን የመሰረዝ ወይም በድጋሚ የማውጣት መብት አለው፡፡
3. በግልጥ ጨረታ መሸጥ ካልተቻለ የመነሻ ዋጋ በማስቀመጥ በሐራጅ መሸጥ ይቻላል፡፡
4. ለተወዳዳሪዎች የሐራጅ መሪ ሀራጁ ከመጀመሩ በፊት የመነሻውን ዋጋ መግለጽ አለበት፡፡
5. በሐራጅ እቃውን መሸጥ ካልተቻለ ፋብሪካው የተሸለ ነው የሚለውን ማስወገጃ ዘዴ መርጦ
ማስወገድ ይችላል፡፡
50. ንብረትብ በውዳቂነት ስለማስወገድ
1. ንብረት በተለያዩ የማስወገጃ ዘዴዎች ለማስወገድ ተሞክሮ ሊወገድ ካልቻለ እንዲሁም በንብረት
ማስወገድ ሂደት የሚገኘው ገቢ ለማስወገድ የሚደረገውን ወጪ የማይሸፍን ነው ተብሎ
ሲታመንበት ለምንም አይነት ጥቅም /አገልግሎት ሊውል የማይችል ሲሆን ንብረቱ በውዳቂነት
ስለሚታይ በመቅበር ወይም በማቃጠል እንዲወገድ ይደረጋል፡፡
በማቃጠል ወይም በመቅበር የሚወገድ ንብረት ከፍተኛ የሥነ-ምህዳር ወይም የጤና
ችግር የሚያስከትል ሆኖ ሲገኝ ፋብሪካው ስለአወጋገዱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር
በመመካከር ንብረቱን በተገቢው መንገድ ማስወገድ ይኖርበታል፡፡
2. ሚስጢርነታቸው እንደተጠበቀ መወገድ የሚገባቸው ወይም የማጭበርበር ስራ ሊሰራባቸው
ይችላል ተብለው ከሚገመቱ ሰነዶች በስተቀር፣ በመቅበር ወይም በማቃጠል እንዲወገዱ
የተወሰነባቸው እንደ ቆሻሻ ወረቀት፣ ፌስታል፣ ፕላስቲክና የመሳሰሉ ንብረቶች በአካባቢ ብክለት
ላይ የሚያመጡትን አሉታዊ ተፅዕኖ ከግምት ውስጥ በማስገባት መልሰው ጥቅም ላይ
ለሚያውሉ /ሪሳይክል ለሚያደርጉ/ ህጋዊ የግል ድርጅቶች ወይም ማህበራት በነፃ ሊሰጣቸው
ይችላል፡፡
6. በውዳቁበት እንዲወገዱ ውሳኔ በተላለፈባቸው ንብረቶች ላይ የፋብሪካው የበላይ ሀላፊ ማፀደቅ
አለበት፡፡
51. አገልግሎት የሰጡ የንብረት ገቢና ወጭ ሰነዶችን የማስወገድ ስርዓት
1. መዝገብ ቤት ካለው እና ከሰራተኛ ፋይል ጋር ከተያያዙት ማስረጃዎች በስተቀር ከአንድ አመት
በላይ የቆየ በግልባጭ ለማሳወቅ የተጻፉ ደብዳቤዎች፣
2. ከመዝገብ ቤትና ፕላን ክፍል ካለው በስተቀር፣ ከአንድ አመት በላይ የቆዩ እቅድና የእቅድ
አፈጻጸም ሪፖርቶች፣
3. ከአስር ዐመታት በላይ የቆዩ ኦዲት የተደረጉ የሂሳብ ሰነዶች፣ ጉርድ የንብረት ገቢና ወጭ
ደረሰኞች የምርት መረካከቢያ ደረሰኞች የሽያጭ ማስረከቢያ ደረሰኞች ልዩ ልዩ ቃለጉባኤዎችና
የውል ሰነዶች፣
4. በተለያየ ምክንያት ከፋብሪካው የተሰናበቱ ሰራተኞች ፋይል፣ የተወገዱ ማሽነሪዎችና
ተሸከርካሪዎች ፋይል፣ የማይንቀሳቀስ ፋይል ተብሎ በአንድ በተወሰነ ቦታ ሊቀመጥ ይችላል፡፡
52. የተወገዱ ንብረቶችን ሪፖርት ማድረግ
1. ለፋብሪካው አገልግሎት ባለመስጠታቸው ምክንያት የተወገዱ ንብረቶቸ ዝርዝርና
በመወገዳቸው ምክንያት የተገኘው ውጤት በአግባቡ ተለክቶ በግዥና ንብረት አስተዳደር በኩል
ሪፖርት ለዋና ስራአስኪያጅ ያቀርባል፤
2. ፋብሪካው ንብረት በሚሸጥበት ጊዜ ዋጋውን በጥሬ ገንዘብ ወይም ከባንክ በተረጋገጠ ቸክ
መቀበል ይችላል፤ ለተቀበለው ገንዘብ ህጋዊ ደረሰኝ መስጠት እንዲቻልና ለንብረቶች ምዝገባ
ለመስራት የተወገዱት ንብረቶች ዝርዝርና መጠን ለፋብሪካው ፋይናንስ ስራ ሂደት መቅረብ
ይኖርበታል፡፡
3. በንብረቱ ልዩ የተፈጥሮ ባህሪ ምክንያት በትነት ወይም በፍሳሽ ወይም በማሽን የካሊብሬሽን
,ችግር ምክንያት የጎደለው ንብረት ሪፖርት ሲቀርብ ከሚመለከታቸው አካላት በሚቀርብ
ማረጋገጫ መሰረት ገዥና ንብረት አስተዳደር የስራ ሂደት ታይቶ ውሳኔ ሲሰጠው የጉድለት
መጠኑ ከንብረት መዝገብ እንዲቀነስ ሲደረግ ገቢና ወጭ ሳይሰሩለት ሊቀናነስ ይችላል፡፡

ክፍል ስምንት
ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
53. መመሪያውን ስለማሻሻል
ይህ የንብረት አስተዳደር መመሪያ የአማራ ፓይፕ ፋብሪካ ስራ አመራር ቦርድ ሲታመንበት
ሊሻሻል ይችላል፡፡
1. የዉስጥ የስራ ማንዋል ስለማዉጣት

በዚህ መመሪያ የተደነገገዉ እንደተጠበቀ ሆኖ ይህን መመሪያ በማይቃረን አኳኋን


ፋብሪካዉ መመሪያዉን በተሻለ ሁኔታ ማስፈጸም ይቻለዉ ዘንድ አስፈላጊ የሆኑ የአሰራር
ማንዋሎች አዘጋጅቶ ሊጠቀም ይችላል፡፡

54. የተሻሩ መመሪያዎች


ሀ/ የፋብሪካዉ የንብረት አስተዳደር መመሪያ----ተሸሮ በዚህ መመሪያ ተተክቷል፡፡
ለ/ይህን መመሪያ የሚቃረኑ ሌሎች ህጎች፤መመሪያዎችና ልማዳዊ አሰራሮች በዚህ መመሪያ
ተሸረዋል፡፡
55. መመሪያዉ የሚፀናበት ጊዜ
ይህ መመሪያ ከፀደቀበት ቀን---2010 ዓ.ም ጀምሮ የፀና ይሆናል
የአባይ ሕትመትና የወረቀት ፓኬጂንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር
ሥራ አመራር ቦርድ
ባህር ዳር 2010 ዓ/ም

56. የልዩ ልዩ ቅፆች አጠቃቀምና ስርጭት


1) የንብረት ገቢ ደረሰኝ (Goods Receiving Note)
ይህ ደረሰኝ ንብረት ገቢ የሚደረግበት ሲሆን፤ገቢዉ ሲመዘገብም የንብረቱ ትክክለኛ
መጠሪያ፤መለያ ቁጥር፤ሞዴል /ማርክ/፤
መለኪያ/ቁጥር፤በሴት፤በፓኬት፤በኪሎ/ብዛት፤መጠንና የአንዱንና ጠቅላላ ዋጋዉን
በመሙላት ምዝገባዉን ማከናወን ሲሆን፤

ደረሰኙ በአንድ ዋናና በ 4 ኮፒ የሚዘጋጅ ሆኖ ስርጭቱም፡-

 ዋናዉና የመጀመሪያዉ ለፋይናንስ


 1 ኛዉ ኮፒ ለአቅራቢዉ /አስረካቢዉ/
 2 ኛዉ ኮፒ ለንብረት ክፍል ሠራተኛ
 3 ኛዉ ኮፒ ለንብረት ሪከርድ ኦፊሰር
 4 ኛዉ ኮፒ ከጥራዙ ጋር ቀሪ ይሆናል፡፡

ሀ/ የንብረት ገቢ ደረሰኝ ምዝገባ የሚከናወነዉ በስቶክ ክለርክነዉ፡፡

ዕቃዎቹ ገቢ በሚሆኑበት ወቅት በንብረት አስተዳደር ኦፊሰሮች የኢንስፔክሽን ስራ


መከናወን አለበት፡፡

ለ/ የንብረት ወጪ መጠየቂያ ንብረቱን በሚፈልገዉ ክፍል የሚፈልገዉን ዕቃ ትክክለኛ


መጠሪያ፤ መለያ ቁጥር፤ሞዴል/ማርክ/፤ብዛት፤መጠንና የመሣሰሉትን በመጥቀስ እቃ
/ንብረት/ ከንብረት ክፍል ወጭ አንዲሆን ጥያቄ ማቅረቢያ ቅጽ ነዉ፡፡

1. ወጭ እንዲሆን የተጠየቀዉ ዕቃ ወይም ንብረት በደረሰኝ ላይ በተሟላ ሁኔታ መመዝገብ፤


2. ወጪ መጠየቂያዉ በጠያቂዉ ባለሙያና በጠያቂዉ ክፍል ሱፐርቫይዘር ወይም በንዑስ ስራ
ሂደት ኃላፊዉ (በመምሪያ ኃላፊዉ) መረጋገጥ እና መፅደቅ አለበት፡፡
3. መጠየቂያዉ ቁጥር ያለዉ መሆን አለበት፡፡
4. በንብረት መጠየቂያ ቅፅ ላይ ቋሚና አላቂ እቃዎች በአንድ ላይ አይጠየቁም
5. የንብረት ወጪ መጠየቂያ የሚሞላዉ የተፈለገዉ እቃ ወይም ንብረት በንብረት ክፍል /መጋዘን/
መኖሩ ከተረጋገጠ በኃላ ነዉ፡፡
6. መጠየቂያዉ የሚሞላዉ በተጠቃሚዉ ክፍል ሲሆን
 ዋናዉ የመጀመሪያዉ ለፋይናንስ ኦፊሰር
 1 ኛዉ ኮፒ ለንብረት ሠራተኛ
 2 ኛዉ ኮፒ ለጠያቂዉ
 3 ኛዉ ኮፒ ከጥራዙ ጋር ቀሪ ይሆናል
7. የንብረት ወጪ መጠየቂያ ጥራዞች ለስራ ሂደቶች ወጭ ሆኖ የሚሰጥ ሲሆን፤ተሠርቶበት
ሲያልቅ ለዋናዉ እቃ ግ/ቤት ገቢ መደረግ አለበት፡፡ወጭ የተደረገዉንና ገቢ የተደረገዉን መዝግቦ
መያዝ የመረጃ ምንጭ ስለሚሆን ተገቢ ነዉ፡፡

2. የንብረት ወጪ ደረሰኝ (Store Issue Voucher)


የንብረት ወጪ ደረሰኝ የሚዘጋጀዉ ወጭ እንዲሆን የተፈቀደ እቃ/ንብረት/ ለድርጅቱ
ስራ የሚዉል መሆኑ ሲረጋገጥ ነዉ፡፡
1. ወጪ እንዲሆን የተጠየቀዉን እቃ ወይም ንብረት በደረሰኙ ላይ በተሟላ ሁኔታ መመዝገብ፤
2. ወጪ እንዲሆን ትዕዛዝ የተሰጠበት ዕቃ /ንብረት/ መጠየቂያ በተገቢዉ ሠራተኛ
መጠየቁን፤በጠያቂዉ ኃላፊ መረጋገጡን እና መፅደቁን እቃዉን ወጭ የሚያደርገዉ
የንብረት ክል ሠራተኛ ማረጋገጥ አለበት፡፡
3. የንብረት ወጪ ደረሰኝ የሚዘጋጀዉ በስቶር ክለርክ ሠራተኛ ነዉ፡፡
4. የንብረት ክፍል ሠራተኛዉ ዕቃ/ ንብረት/ ወጭ ከማድረጉ በፊት በመጠየቂያዉ ላይ
የተሞላዉንና በንብረት/ዕቃ/ወጭ ደረሰኝ ላይ የተሞላዉን ዝርዝር ሁኔታ ትክክለኛ
መሆኑን የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት፡፡
5. ንብረት ወጪ የሚያደርግ ሠራተኛ ቆጥሮና ለክቶ የመረከብ፤ንብረቱን
የሚያስረክብ የንብረት ክፍል ሠራተኛ ቆጥሮና ለክቶ የማስረከብ ግዴታና ኃላፊነት
አለባቸዉ፡፡
6. የንብረት/ዕቃ/ ተረካቢም ሆነ አስረካቢ በንብረት ወጪ ደረሰኝ ላይ ሙሉ
ፊርማቸዉንና ስማቸዉን መፃፍ አስፈላጊና ተገቢ ነዉ፡፡
7. የንብረት ወጪ ደረሰኝ ስርጭት በአንድ ዋናና በ 5 ኮፒ ሚዘጋጅ ሆኖ
 ዋናዉ የመጀመሪያዉ ፋይናንስ
 1 ኛዉ ኮፒ ለንብረት ክፍል ሠራተኛ
 2 ኛዉ ኮፒ ለንብረት ሪከርደር ኦፊሰር
 3 ኛዉ ኮፒ ለጠየቂዉ
 4 ኛዉ ኮፒ ለጥበቃ ንብረቱ ከግቢ የሚወጣ ከሆነ
 5 ኛዉ ኮፒ ከጥራዙ ጋር ቀሪ
3. የንብረት ተመላሽ ማድረጊያ ቅፅ፤
ይህ ቅፅ ንብረት /ዕቃ/ ከንብረት ክፍል በንብረት ወጭ ደረሰኝ ለአገልግሎት ወጭ
ከሆነ በኃላ ትርፍ ሲሆን፤ብልሽት የደረሰበት ሲሆንና ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት
የሚችል ሲሆን ወይም እቃ ተመላሽ ሲሆን፤ገቢ የሚደረግበት ነዉ፡፡

አፈፃፀሙም፡-
1. ቅጹ የሚሞላዉ እቃዉን በሚመልሰዉ ሠራተኛ ነዉ፡፡
2. እንዲመለስ የተጠየቀዉ እቃ ንብረት ክፍል ገቢ እንዲሆን በሚመልሰዉ ሠራተኛ የቅርብ
ኃላፊ መረጋገጥ አለበት፡፡
3. የሚመለሱት ዕቃዎች ሁኔታ ተጠግኖ ‘’አዲስ‘’ ‘’የሚያገለግል‘’ ‘’ተጠግኖ የሚያገላግል‘’
በሚል መለየት አለባቸዉ፡፡አስፈላጊ ሲሆን የተክኒክ ባለሙያዎችን አስተያየት መዉሰድ ተገቢ
ይሆናል፡፡
4. የንብረት ክፍል ሠራተኛዉ ተመላሽ የሆኑ ዕቃዎችን ሥርዓቱን ጠብቆ በንብረት ተመላሽ
ማድረጊያ ቅፅ በገቢ ይመዘግባል ለንብረት ምዝገባ የሚያገለግሉ ካርዶችንም ያስተካክላል፡፡
5. የንብረት ተመላሽ ማድረጊያ ቅፅ በማዕከላዊነት የንብረት አስተዳደር ኦፊሰር በሚመደበዉ
ሠራተኛ ኃላፊነት ተይዞ ንብረት በሚመልስ ሠራተኛ ጥያቄ ሲቀርብ የሚሰጥ ይሆናል፡፡
6. ቅፁ በ 4 ኮፒ የሚሞላ ሲሆን
 ዋናዉና የመጀመሪያዉ ለፋይናንስ
 1 ኛዉ ኮፒ ለዕቃ ግምጃ ቤት ሠራተኛ
 2 ኛዉ ኮፒ ለአስረካቢዉ ለፋይናንስ የሚሰጠዉ
 3 ኛዉ ኮፒ ለአስረካቢዉ
 4 ኛዉ ኮፒ ከጥራዙ ጋር ቀሪ ይሆናል፡፡
4) አገልግሎት ሰጥተዉ የተመለሱ እቃዎች ወጭ ማድረጊያ ቅፅ (Serviceable goods issue
voucher)
ይህ ቅጽ የሚያገለግለዉ አግልግሎት ሰጥተዉ ተመላሽ ከሆኑ ዕቃዎች ዉስጥ ለሥራ
የሚያስፈልጉ ቢኖሩ ወጭ አድርጎ ለመጠቀም ሲያስፈልግ፤ለሁለተኛ ጊዜ እቃዎች
ወጭ የሚሆኑበት ቅፅ ነዉ፡፡

አፈፃፀሙም፡-
1. እቃዎች ወጭ እንዲሆኑ ሲጠየቅ ከዚህ በፊት አገልግሎት የሰጡ መሆናቸዉ መጠቀስ
አለበት፡፡
2. የዕቃ መጠየቂያና መፍቀጃ ሂደቱ በአንቀጽ 27.2.1 በተጠቀሰዉ ሂደት መሰረት ይፈጸማል፡፡
3. የዉጭ ሰነድ በ 3 ኮፒ የሚሰራ ሆኖ፤
 ዋናዉና የመጀመሪያዉ ለፋይናንስ መምሪያ
 1 ኛዉ ኮፒ ለንብረት ሠራተኛ
 2 ኛዉ ኮፒ ለተረካቢዉ
 3 ኛ ኮፒ ከጥራዝ ቀሪ ይሆናል፡፡

5) የንብረት መላኪያና ማዛወሪያ ቅፅ (Stores Transfer Shipping Document)


(Material Dispatch Note)
ይህ ቅጽ የሚያገለግለዉ ንብረት/እቃ/ ከድርጅቱ ዕቃ ግ/ቤት ወደ ቀጠና ጽ/ቤቶች

እና ወደ ተለያዩ ድርጅቶች ወይም ፕሮጀክቶች እንዲሁም ከቀጠና ጽ/ቤቶች፤

ከፕሮጀክቶች ወደ ዋናዉ ድርጅት ዕቃ ግ/ቤት ንብረት የሚላክበት ቅፅ ነዉ፡፡

ይህም የሚሆነዉ ንብረቱን ሚረከበዉ በግንባር ሳይኖር ሲቀር ነዉ፡፡

1. ቅፁ የሚሞላዉ በጠያቂዉ ክፍል እና በስቶር ክለርክ ሠራተኛ ሆኖ ጥያቄዉ

ከሚመለከተዉ አካል መቅረቡ ሲረጋገጥ ይሆናል፡፡በቅጹ ላይ ንብረቱ የሚላክበት

ፕሮጀክት የሚወስደዉ ሰዉ ስም እንደአስፈላጊነቱ ተሸከርካሪ በዝርዝር መሞላት

አለበት፡፡

2. የንብረት ማዘዋወሪያ ቅጽ ላይ የጠያቂዉ ኃላፊ አረጋግጦ ያፀድቃል፡፡

3. ቅፁ የሚሞላዉ በ 7 ኮፒ ሆኖ ሥርጭቱም፡-
 ዋናዉና የመጀመሪያዉ ለፋይናንስ ኦፊሰር
 1 ኛዉ ኮፒ ለንብረት ሠራተኛ
 2 ኛዉ ኮፒ ለንብረት ሪከርድ ኦፊሰር
 3 ኛዉ ኮፒ ለአድራሹ/ንበረቱን/ ለሚወስደዉ
 4 ኛዉ ኮፒ ንብረቱ የተላከለት አካል የሚፈርምበት በአድራሹ ለፋይናስ
የሚሰጥ
 5 ኛዉ ኮፒ ለንብረት ተቀባዩ ምዝገባ
 6 ኛዉ ኮፒ ለጥበቃ ሠራተኛ
 7 ኛዉ ኮፒ ከጥራዙ ጋር ቀሪ ይሆናል፡፡
1. የተላከዉ ዕቃ ለመድረሱ 4 ኛዉ ኮፒ ላይ የቀጠና ወይም የፕሮጀክት ንብረት ሠራተኛ
ተፈርሞበት እቃዉ ወጭ ከተደረገበት ንብረት ክፍል ላሉ ኦፊሰሮች ዋናዉ ጽ/ቤት ይመለሳል፡፡
የንብረት ኦፊሰሮች ለፋይናስ ያስተላልፋሉ፡፡
2. የተላከዉ ንብረት በትክክል የተፈለገበት ቦታ ለመድረሱ የንብረት አስተዳደር ኦፊሰሮች ክትትል
ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡
3. የተላከዉ ንብረት ሙሉ በሙሉ ሳይደርስ ቢቀር ብልሽት ቢኖር ተቀባዩ አካል ወይም ንብረት
ክፍሉ፡-
 ንብረቱ የተላከበትን ሰነድ ቁጥር ቀንና ዓ.ም
 የአጓጓዡን ስም፤የአሽከርካሪዉን ሰሌዳ ቁጥር፤
 የጎደለዉን ወይም ጉዳት /ብልሽት/ የደረሰበትን ዕቃ ዓይነትና ብዛት በመግለፅ
ወዲያዉኑ ለሚመለከታቸዉና ለዋናዉ ፋብሪካዉ ጽ/ቤት በደብዳቤ ማሳወቅ ግዴታ
ነዉ፡፡
 በቀረበዉ ሪፖርት መሠረት ፋብሪካዉ ጽ/ቤት ተገቢዉን የዲሲፒሊን እርምጃ
ይወስዳል፡፡
6) የነዳጅ ዘይትና ቅባት መጠየቂያና ወጭ ማድረጊያ (Petroleum,Oil & Lubricants
Store Requisition & Issue voucher)

ይህ ቅጽ ለፋብሪካዉ ሥራ ለሚያገለግሉ ተሸከርካሪዎችና የተለያዩ መሣሪያዎች

ነዳጅ፤ዘይትና ቅባት የሚጠየቅበትና ወጭ የሚደረግበት ቅፅ ሲሆን የሚሞላዉ

በጠያቂዉ ስም የሚመለከተዉ አካል ሲያፀደቅ ይሆናል፡፡


.

You might also like