Professional Documents
Culture Documents
Diseases On Biodiversity (Amharic)
Diseases On Biodiversity (Amharic)
የእንስሳትን ብዝሀ ሕይወት ዘላቂነት እና ዋስትና የሚፈታተኑ በርካታ ተግዳሮቶች አሉ፡፡ በእንስሳት ብዝሀ
ይጠቀሳሉ፡፡ የእንስሳት በሽታ በለማዳም ሆነ በዱር እንስሳት ውስጥ ዋነኛው የጤና እና ደህንነት ስጋት ነው፡፡
በተለይም በሽታው በጣም አጣዳፊ፣ በለማዳና በዱር እንስሳት መካከል ተላላፊና ከፍተኛ የሞት ደረጃ
የሚያስከትል እንዲሁም በሰዎች ላይ የመተላለፍ እድል ያለው ከሆነ ደግሞ የበሽታውን አሳሳቢነት ደረጃ ከፍ
ያደርገዋል፡፡ በርካታ ወረርሽኞች በብዙ የዓለማችን ክፍሎች ላይ አስከፊ ጉዳት ያስከተሉ ሲሆን እነዚህም
የተለያዩ ገፅታዎች አሏቸው፤ ወደ ሰው ተላላፊ (ለምሳሌ በርድ ፍሉ፣ ኢቦላ …)፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ቀውስ
የሚፈጥሩ (ለምሳሌ አባሰንጋ፣ ኤፍ-ኤም-ዲ …) እና እንዲሁም ከባድ ኢኮኖሚያዊ ኪሳራን የሚያደርሱ
ናቸው፡፡
ተላላፊ የእንስሳት በሽታዎች በተለይም አጣዳፊ ወረርሽኞች በሺታዎች የሚቆጠሩ በተወሰነ አካባቢ ወይም
በተለያዩ ሥፍራዎች የሚገኙ እንስሳትን በአጭር ጊዜ ውስጥ ሊገድሉ ይችላሉ፡፡ ተላላፊ፣ አጣዳፊ የሆኑና
በወረርሽኝ ደረጃ ሊከሰቱ የሚችሉ በርካታ በሽታዎች የሚገኙ ሲሆን በለማዳም ይሁን በዱር እንስሳት ላይ
ከፍተኛ ጉዳትና ሞት ሊያስከትሉ ይችላሉ፡፡ እነዚህ በሽታዎች ከዚህ ቀደም ተጠቅተው ወደማያውቁ እና በተለያዩ
መንስኤዎች ስጋት ላይ በሚገኙ ዝርያዎች ጭምር እየተስፋፉ ይገኛሉ፡፡ በሽታው በእንስሳት ዝርያው ላይ
የሚያደርሰውን ተፅዕኖ በጣም ከባድ የሚያደርገውና አገራዊ/አለም አቀፋዊ ትኩረትን የሚጠይቀው በተለይም
የእንስሳቱ ዝርያ አናሳ ቁጥር ብቻ ያለው ከሆነና እንዲሁም በአንድ ሥፍራ ላይ ብቻ የሚገኝ ከሆነ ነው፡፡
የእንስሳት ዝርያዎችን ከሚያጠፉ ወይም ስጋት ላይ ከሚጥሉ አምስት ዋና ዋና ተፅዕኖዎች መካከል የእንስሳት
በሽታ ይጠቀሳል፡፡
በተፈጥሮ ጥበቃ ላይ የሚሰራው አለም አቀፉ ሕብረት (IUCN) ለአንዳንድ የተመናመኑ የእንስሳት ዝርያዎች
በሽታ ዋነኛው መንስኤ እንደሆነ ጠቅሶ ስጋቱ ግን በአብዛኛው ዝርያዎች ላይ እንደሚገኝ ያትታል፡፡ በአጠቃላይ
በሽታ በእንስሳት ብዝሀ ሕይወት ላይ ያለውን ስጋት ሲገልፅ ዝርያቸው ከተጎዱ እንስሳት መካከል፤ የወፍ
በእንስሳት ብዝሀ ሕይወት ላይ ትልቅ ስጋትና ተፅዕኖ ማድረስ የሚችሉ ብዙ የበሽታ አይነቶች አሉ፡፡ የስጋት
ደረጃውም አንድን ንዑስ-ዝርያ ከማጥቃት እስከ አጠቃላይ የእንስሳውን ዝርያ ማመናመን ሊደርስ ይችላል፡፡
የበሽታው ወረርሽኝ በአንድ አካባቢ ከሚገኙ ተጋላጭ እንስሳት አብዛኛውን ወይም ሙሉ በሙሉ ጠራርጎ
ሊገድል ይችላል፡፡ ለምሳሌ ሪንደርፔስት በከብቶችና የጎሽ ዝርያዎች ላይ፣ አባሰንጋ በአባዛኛው ሳርበል
ዝርያዎች ላይ፣ አፍሪካን ሆርስ ሲክነስ በጋማ ከብቶች ላይ፣ ኤቪያኒ ኢንፍሉኤዛ እና ኒውካስትል ዲዝስ
በአብዛኛው የወፍ ዝያዎች ላይ፣ ችትሪዲኦማይኮሲስ በእንቁራሪት-አስተኔ ዝርያዎች ላይ እንዲሁም ራቢስ እና
ካናይን ዲስቴምፐር በለማዳና የዱር ስጋበል እንስሳቶች ላይ ከባድ ወረርሽኝ ሊፈጥሩ ይችላሉ፡፡
በኢትዮጵያ ውስጥ ለብዝሀ ሕይወት መጥፋትና መመናመን ዋነኛውን መንስኤ የእርሻና ግጦሽ መሬት
መስፋፋት እና ፍላጎት መጨመር የመጀመሪያውን ደረጃ ይወስዳል፡፡ ሆኖም የእንስሳት በሽታዎች ከሌሎች
አስጊ ሁኔታዎች ጋር በመዳመር የእንስሳት ብዝሀ ሕይወት ዘለቄታና ጥበቃ ላይ እንቅፋቶች ናቸው፡፡ ብዙ
የእንስሳት በሽታዎች በኢትዮጵያ ውስጥ በከፍተኛ ደረጃ ተስፋፍተው የሚገኙ ሲሆን አስከፊ
ወረርሽኝዎችንም ያስከትላሉ፡፡ ምንም እንኳን የእንስሳት እርባታው ዘርፍ ለአገሪቷ ኢኮኖሚ ብዙ አስተዋፅ
እያደረገ ቢሆንም እድገቱ ግን በብዙ የእንስሳት በሽታዎች (ቫይራል፣ ባክቴሪያል እና የጥገኛ ትላትል
በሽታዎች) ካለው ዝቅተኛ የእንስሳት ህክምና አገልግሎት እና ዝቅተኛ የበሽታዎች ክትትል እና ቁጥጥር ጋር
በአገሪቱ ውስጥ የተለያዩ የበሽታ ወረርሽኞች በለማዳ እና የዱር እንስሳት ዘለቄታዊነት ላይ ስጋት ሆነው
ይከሰታሉ፡፡ እ.ኤ.አ. በ 19 ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ ላይ የሪንደርፔስት ወረርሽኝ በወቅቱ ከነበረው ድርቅ ጋር
ተደማምሮ አብዛኛው የኢትዮጵያ ከብቶችን አጥፍቷል፡፡ እ.ኤ.አ. በ 1887 በኢትዮጵያ የባህር ወደብ
አማካኝነት ወደሀገራችን እንደገባ የሚታሰበው ይህ በሽታ በሰሜኑ ኢትዮጵያ ከብቶችን እያጠቃና ወደ ቀሪው
የሀገሪቷ ክፍሎች ባልተለመደና አስገራሚ በሆነ ፍጥነት እየተስፋፋ መጣ፡፡ በሽታው በትግራይ እና ሸዋ ብሎም
ወደደቡብ በመስፋፋት ወደ 90% ያህል የሀገሪቱ ከብቶች እና የዱር እንስሳት ሞትን አስከትሏል፡፡ ገንዲ
(ትርይፓኖሶሞሲስ) የተባለዉ በሽታ ደግሞ በተለይም በኢትዮጵያ ምዕራባዊ እና ደቡብ ምዕራብ ዝቅተኛ
ቦታዎች እና ሸለቆዎች ውስጥ በሰፊው ተሰራጭቶ ይገኛል፡፡ በነዚህ ሥፍራዎች የሚገኙ ሰፋፊ የመሬት
በ 1990 ዎቹ በባሌ ተራራ ብሔራዊ ፓርክ የታየው አስደንጋጭ የቀይ ቀበሮ ቁጥር መቀነስ ውስጥ በሽታ
ዋነኛው ችግር ሆኖ ተግኝቷል፡፡ ራቢስ ለዱር ስጋበል እንስሳቶች ልዩ ስጋት ሆኖ የተገኘበትና በኢትዮጵያ ብቻ
በሚገኘው ቀይ ቀበሮ/ተኩላ ላይ መከሰቱ ነው፡፡ ከአጠቃላዩ 500 ገደማ ተኩላዎች ከግማሽ በላይ የሚሆኑት
በሚኖሩበት በኢትዮጵያ የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ውስጥ የራቢስ እና ካናይን ዲስቴምፐር ተደራራቢ
ወረርሽኞች ተከስቷል፡፡ እ.ኤ.አ. በ 2003/2004 የተደረገ ጥናት እንደሚያመለክተው በዚህ ለሀገራችን ብርቅዬ
በሆነውና በጣም እየተመናመነ በመጣው ቀይ ቀበሮ ወደ 74 ገደማ የሚሆኑ ቀበሮዎች ሞተው የተገኙ ሲሆን
ለዚህም “ራቢስ” ወይም የእብድ ውሻ በሽታ የሚባለው ወረርሽኝ ትልቁን ግምት ወስዷል፡፡ በላብራቶሪ
አንትራክስ (አባሰንጋ) የተባለው ወረርሽኝ በደቡብ ኢትዮጵያ በሚገኘው በማጎ ብሔራዊ ፓርክ ከፍተኛ የዱር