20

You might also like

Download as pdf or txt
Download as pdf or txt
You are on page 1of 14

ሁለቱን ባሎቼን ላስማማ እያሸማገልኳቸው ነው!!

(ሜሪ ፈለቀ)
ግርምታችሁን እና እርግማናችሁን ከማዥጎድጎዳችሁ በፊት ትንፋሽ እየሰበሰባችሁ ከመጀመሪያው
ልጀምርላችሁና ሁለቱንም ላስተዋውቃችሁ።
የመጀመሪያው ባሌ “ባለቤቴ ነው ተዋወቂው!” ብዬ ያስተዋወቅኳት ጓደኛዬ “ወየው በፈጣሪ ባልሽ ሲያምር
አጣብሺኝ!” ያለችለት ውብ ነው።
የገዛ እናቴ ልክ እንደጠበስኩት ስታውቅ “ውይ ልጄ የልጁን ህይወት አታበልሺ አጉል ታደርጊዋለሽ !ይቅርብሽ
በሞቴ!!” ብላ የለመነችለት ስነስርዓታም ነው።
የቤተክርስቲያናችን ፓስተር ጠርቶኝ “ሜሪ ሰይጣን አንቺን ተጠቅሞ ልጁን ከጌታ ቤት ሊያስኮበልል እየተጋ
ነው።” ያለለት የቸርቻችን ዓይን የሆነ አገልጋይ ነው።
እሱስ ብትሉ? መጀመሪያ እጄን የጨበጠ ቀን “ሜሪ እባላለሁ!” ስለው
"ሜሪ ....ሜሪ ? " ብሎ ሰይጣንን ራሱን የጨበጠ ይመስል እንዴት እጄን አሽቀንጥሮ እንደጣለው። የጨበጠኝን
እጁን ልብሱ ላይ ሁላ ቢጠርገው ደስ የሚለው ይመስለኛል።
እሱ ለከተማውም ለቸርቹም አዲስ ነበር። እኔ ደግሞ ከቸርቹም ከወሬውም ገለል ለማለት ክረምት ስለነበር
ሁለት ወር አዲስአበባ ከርሜ መመለሴ ነው። ጫፉን እንኳን ያልነካሁትን ቀድሞ የነበረውን ፓስተር በዝሙት
ጣለችው ተብዬ ተወንጅዬ መሆኑ ነው። ቢችሉ እንደጌታ ቢሰቅሉኝ ደስ ይላቸው ነበር። ያው ጫፉን አልነካሁትም
አልኳችሁ እንጂ ከንፈሩን ነክቼዋለሁ። ከንፈርና ጫፍ ይለያያል አይደል? እኮ!! ነገሩ ውስብስብ ሆኖ
አይደለም ሲያወሳስቡት እንጂ። ስለፓስተሩ በኃላ እመለስላችኋለሁ።
ስለዋናዬ ላውጋችሁ። ክረምቱን ጨርሼ እንደተመለስኩ እቤት ከምላሳቸው ላይ የሱን ስም እንዴት ላውርደው?
ቸርች ውስጥ የማይገባበት የለውም። ይሰብካል ..... ይዘምራል(ውብ ድምፅ ድክመቴ ነውኮ ደግሞ) ........ ፒያኖ
ይጫወታል....... ወላ ኤሌክትሮኒክስ ነገር ሲበላሽ ይጠጋግናል ........ ቸርቹን ያፀዳል የማያደርገው የለውም። በቃ
ምንም ይሁን
እነማሚ ....ቸርች አዲስ የመጣው .... ልጅ እንዲህ ብሎ .... እንዲያ ብሎ .... ሳላየው ብዙ ሰማሁ:: የተዋወቅን
ቀን ደግሞ እሱም ሳያየኝ ብዙ እንደሰማ ገባኝ። ያው ክፉ ክፉውንም ቢሆን......
ወንድሜ አጠገቡ ነበረ “እህቴ ናትኮ!” ይለዋል
“ሜሪ ያንተ እህት ናት?” አባባሉ ይህቺ አጋንንት እንዴት ብላ ከእናንተ ቤተሰብ ተፈጠረች? እንዴት ነው
መልዓክና ሰይጣን ተስማምታችሁ አንድ ቤት የምትኖሩት? አይነት ለዛ ነው። የለመድኩት ነገር ስለሆነ ስቄ
ለወንድሜ ምግቡን አቀብዬ ተመለስኩ።
ከዛ በኋላ እኔ አልደረስኩበትም። ስለእውነቱ ጭራሽ በሀሳቤም በልቤም የለም። ለራሴ በአንድ ፓስተር ከንፈር
ጦስ ሳቢያ መፅሃፍ ቅዱስ ላይ ያሉ ክፉ ሴቶች መንፈስ ሁላ ስም (የኤልዛቤል መንፈስ የደሊላ መንፈስ ሲወጋ
የሚውለው የሴቶች መንፈስ ብዛት ) እየተጠቀሰልኝ እጅ በመጫን ፀሎት ብዛት ሌላ አገልጋይጋ መድረሻ እጅም
እግርም ፍላጎትም የለኝም።
ከወንድሜጋ ሁሌ እሁድ ከቸርች በኋላ እቤት ይመጣሉ። እሱ ማውራት ሲጀምር እቤት አፉን የሚከፍት የለም።
ፀጥ ብለው ይሰሙታል። ስለምንም ርእስ ይነሳ ይቀዳል የቸርቹ ወሬ ብዙም ስለማይጥመኝ አልሳተፍም።
ድንገት በሆነ ሰበብ ወደሳሎን ብቅ ካልኩ በገዛ ቤቴ ይገላምጠኛል። ወይ በነገር ይተናኮሳል። ቤቴ ነው ብዬ
አልፈዋለሁ።
“ቸርች ለምንድነው የማትመጪው?” አለኝ የሆነ ቀን ኮስተር ብሎ ውጪ ተቀምጬ የማነብበት መጥቶ
“ለምንድነው የምመጣው?”
“ለመፀለይ ..... ጌታን ለማምለክ ..... ጌታን ለመፈለግ .... ወንድሞች በህብረት ቢቀመጡ መልካም ነው እነሆም
ያማረ ነው!!”
“ዌል ወንድም አይደለሁም እንደምታየው!”
“የምሬን ነው!” አለ ፈገግ ብሎ:: „ጥርስህኮ ሲያምር በየሱስ ስም! ምን ሆነህ ነው ሁሌ የምትኮሳተረው?‟ ልለው
ነበር። ያው በደህና አያይብኝም ብዬ ዋጥኩት
“ሲገባኝ ቸርች የምትሄደው ሸክምህን ለማራገፍ ነው። ፈራጅ በየመንገዱ ሞልቷል። ለምን ብዬ ቸርች ሄጄ
የፈራጆቼን አይን እያየሁ ራሴን እኮንናለሁ? አምላክ ፍቅር ነው እኔ እስከገባኝ። ፍቅርን ፍለጋ የምሄድበት ቸርች
ገና እግሬ ሲረግጥ ዘማዊት ናት ትወገር የሚሉ አይኖች እና እኛ ካንቺ የተሻልን ፃድቃን ነን ብለው የሚመፃደቁ
ሰዎች ጋር ተቀላቅዬ ራሴን ለምን አሳንሳለሁ? Am ok where I am now. “
ዝም አለኝ። ሁለታችንም ዝም ከምንል ብዬ ቀጠልኩለት
"ታውቃለህ ያቺ ዘማዊት ሴት መፅሃፍ ቅዱስ ላይ ስትዘሙት አጊንተናት ነው ብለው ወደእየሱስ ያመጧት? ህም
ሁሌ የሚገርመኝ ነገር ከሆነኛው ሰውዬጋ ነውኣ ስታመነዝር ያዩዋት? እሱን 'በል ሱሪህን ታጠቅና አምልጥ
ብለውት ነው እሷን ብቻ ይዘዋት የመጡት? ለምን እሷን ብቻ ኮነኗት? ምናልባት ሰውየው ወዳጃቸው ነው?
አልያም ክብሩ የማይነካ ስም ያለው ሰው ነው? ለሁለት ባጠፉት ጥፉት እሷ ብቻ እንድትወገር ለምን ተፈለገ?"
ብዙ ዝም አለኝኛ "የሚወራው ግን እውነት ነው?" አለኝ
"አይገርምህም ግን ማንም ሰው እውነት ነው ወይ ብሎ ጠይቆኝኮ አያውቅም! ቤተሰቤን ጨምሮ የተፈጠረውን
እንኳን ሳያውቁ ነው ሲወጉ የሚውሉት" ድክም ብሎ ሳቀ
"እውነት ነው ግን?"
"ግማሹ እውነት ነው። እውነት የሆነው ክፍል 'የሆነ ነገር ነበራቸው' የሚለው ነው። 'በሷ ምክንያት ነው
ከአገልግሎት የታገደው!' የሚለውም እውነት ነው። እርግጥ 'አሳሳተችው' የተባለውም እውነት ነው ያው
የተሳሳተው ምን ድረስ ነው የሚለውን ነው ልክ ያልሆኑት።"
እንደሆነ ተዓምር ያየኛል። ...... ፈገግ ይላል። እሱ እንደሚለው ይሄን ቀን ነው ነፍሴን የወደዳት ....
"ፓስተር የመጣ ጊዜ እኔ ዼንጤነቱን እርግፍ አድርጌ ትቼው ነበር:: ... ማሚ በስንት ጉቦ የሆነ ቀን ይዛኝ
ስትመጣ ... ሸበላ .. ወጣት ... ሲናገር የሚጣፍጥ አዲስ ፖስተር እየሰበከ ነው:: ከጏደኞቼጋ ነበር የመጣነው::
ተያየን ... 'በየሱስ ስም ይሄ ዼንጤ ብሆን ራሱ ሲኦል ደርሶ መልስ ትኬት ያስቆርጠኛል' አልኳቸው:: 'በፍፁም
አይደረስበትም ... ፓስተርኮ ነው!' ተባባልን:: ከዛ በብር አስያዝን ... እጠብሰዋለሁ ብዬ!! ... ያው አባቢ ፓስተር
ስለሆነ መግባባት ጊዜ አልፈጀብኝም:: ... እንዳልኩትም ጠበስኩት:: ችግሩ እሱ የምሩን የጌታ ሰው ነው.... ልክ
የደፈርኩት አስመስለው የሚያወሩት (ልክ ልፉ ነገር አስመስለው) ... እሱ እወድሻለሁ ካለኝ በኃላ ራሱ ንሰሃ
የሚገባ ነው የሚመስለኝ::"
ድክም ብሎ እየሳቀ ይሰማኛል:: .... ይኼኛው ዼንጤው እሱ አይደለም:: ሰው የሆነው እሱ ነው:: ከቤት እየወጡ
ቼክ እያደረጉ ስላስቸገሩን ወክ እያደረግን ወሬውን ቀጠልኩለት::
"ከዛማ በቃ ... የሆነ ቀን ስሞኝ .... በፀፀት አለንጋ ሲዠለጥ ከረመ:: ... እኔ ብሬን በላሁ:: እሱ አመረረ ... ጭራሽ
በቅድስና ፍቅራችንን እንድንኖር እንጋባ አለ:: ... ከዛ እውነቱን ነገርኩት:: ... መልቀቂያ አስገብቶ ወደአዲስ አበባ
መሄዱን ሰማሁ.... ከዛ እዛም እንዳያገለግል መታገዱን ሰማሁ !! ከዛ የማውቀው ታሪክ የለም:: ... ምን
እንዳላቸውም አላውቅም:: ብቻ በኔ ምክንያት መሆኑን ነግሯቸዋል!! .... "
ሳናውቀው ብዙ መንገድ ተጏዝን!! .... ስንመለስ እጁን ትከሻዬ ላይ ጣል አድርጎ .... እብድ እንደሆንኩ እየነገረኝ
ነበር::
"ይቅርታ በጣም! በሰማሁት ልዳኝሽ አይገባም ነበር::" አለኝ እቤት ልንደርስ አካባቢ
"እሺ ይኸው እኔ እውነቱን ነግሬህ የለ? ምንድነው የሰማኸው?"
"ካንቺ በጣም መጠንቀቅ እንዳለብኝ:: ካለበለዚያ እንደምታባልጊኝ " እየሳቀ ነው...
ማሚ በሩጋ ቆማ እየጠበቀችኝ ነው:: ..... አስተያየቷ 'ደሞ በምን አገኘሽው?" አይነት ነው::
........ አልጨረስንም......
ሁለቱን ባሎቼን ላስማማ እያሸማገልኳቸው ነው !!
(ክፍል ሁለት)
የሳመኝ ቀን "በናትህ ይሄን ነገር በምስክር ፊት አድርግልኝ" ብለው ደስ ባለኝ። ስሜ መራራ ነዋ። ሳመችው እንጂ
ሳማት አይባልልኝማ! እርግጥ የሳመኝ እለት ያልኳችሁ ቀን ማለት በዋዛ የተገኘ እንዳይመስላችሁ
"ጌታ ሆይ ይሄ ሰው በወንድምነት ይሁን በባልነት ፍቅር የሚወደኝ መለየት የምችልበት ፀጋ ስጠኝ! .... ወይ
ምልክት ነገር አሳየኝ! ..... ቢያንስ በህልሜ አንድ ጋቢ ለሁለት ስንለብስ ምናምን ....... አለ አይደል የሆነ ምልክት
በቃ ...... እኔ ልጅህ በውዝግብ ስንገላታ በቤትህም እንደሚገባህ እያገለገልኩህ አይደለም! (ይሄኛው በእርግጥ
ለራስህ ስትል ባሪያህን አስባት አይነት ልምምጥ ነው። ውለታዬ አለብህ በዚህ እንኳን ክፈለኝ አይነት ሰፋጣም
ነው።) ብዬ ፆም ፀሎት ልይዝ ትንሽ ሲቀረኝ ነው ያው ምልክት መሆኑ ነው መሳሙ!!
ከምልክቱ አስቀድሞ ከወራት በፊት
ሲሊፐር ያጠለቁ እግሮቼ የቸርቹን በር አልፈው ሲገቡ ራሴን አገኘሁት። ከቤት የወጣሁት ቁምጣዬን ሆዴን
በሚያሳይ አላባሽ ለብሼ ከእግዜሩ የተጣላሁበት የወንድሜ መቃብር ጋር ለመሄድ ነበር። እንደለመድኩት
"የማይሰማ ፀሎት ለምን እፀልያለሁ? ወይም ቁልጭ አድርገህ በዚህ ጉዳይ አትፀልዩ ምናምን ብለህ ህግ
ብታወጣ ጥሩ ...... በደፈናው ብቻ አንኳኩ ...... ብቻ ፀልዩ አልክ ...... ከዛ ግን የማትሰማው ፀሎት ብዛቱ ....."
እያልኩ ከራሱ ከፈጣሪ ጋር እየተነታረኩኝ በእግሬ እስኪደክመኝ ከተጓዝኩ በኋላ ነው ድንገት አቅጣጫዬን
ወደቸርቹ ያዞርኩት ......... ገባሁ።
ለወራት ያላዩኝ አስተናጋጆች በፈገግታ ሰላም እያሉኝና አለባበሴን እየገላመጡ ክፍት ቦታ አሳዩኝ። እሱ መድረኩ
ላይ አይኑን ጨፍኖ ፒያኖውን እየመታ ይዘምራል።
ከተደረገልኝ በጎነትህ
አንዳችም ለእኔ የማይገባ ነበር
በቸርነትህ አድርገሃልና እደነቃለሁ
አብዝቼ ተመስገን እላለሁ ......
እያለ በሚጣፍጥ ድምፁ ይዘምራል:: ህዝቡ ቆሞ ግማሹ እጁን ወዳፈጣሪ አንስቶ .... ግማሹ ወሬ እያየ ግማሹ
ጨፍኖ አብሮት ይዘምራል። መግባቴን ያወቀ ይመስል አይኖቹን ገልጦ አየኝ። ተያየን!! ፈገግ ብሎ አይኖቹን
ጨፍኖ ማስመለኩን ቀጠለ። ያስተዋለ ሰው ምላስ ማሟሻ ሆኜ መክረሜን እያወቅኩት ሳቅ ብዬ ተቀመጥኩ።
የዛን ቀን ስንወጣ ሲንደረደር መጥቶ አቀፈኝ (በጌታ ፍቅር ነው ይህኛው)
"ስለመጣሽ ደስ ብሎኛል። ሳይሽ በጣም ነው ደስ ያለኝ" አለኝ ወደጆሮዬ ጠጋ ብሎ "ምንም እንኳን ቸርች
ለመምጣት አስበሽ ባትመጪም!" አለኝ። አለባበሴን መሆኑ ገብቶኛል።
ከዛን ቀን በኋላ የጌታ ፍቅር ይሁን የሱ ፍቅር መጀመሪያ ሰሞን ባልለየሁት ምክንያት ቸርች እመላለሰው ጀመር።
በሳምንት እሮብና እሁድ መደበኛ የቸርቹ ፕሮግራም አልበቃ ብሎኝ ...... አርብ የአገልጋዩች ፕሮግራም ......
ቅዳሜ የወንድሞች ፕሮግራም ...... ማክሰኞ የማለዳ ፀሎት ..... ብቻ ምንም ይሁን እሱ ካለ እኔ አለሁ!!
ፕሮግራሞቹ ሲያልቁ እስከቤት መንገድ እያራዘምን ወክ እያደረግን የባጥ የቆጡን እናወራለን። ጠዋት ተነስቶ
ትምህርት ቤት ድረስ ሸኝቶኝ ይመለሳል። የማነባቸውን መፅሃፍቶች ተከራይቶልኝ ይመጣል:: ... አንብቦ ነው
የሚሰጠኝ... እኔ አንብቤ ስጨርስ መፈጠራችንን ለማያውቀው ደራሲ ሂስ እንሰጣለን.... እንከራከራለን....
ማታ በየቀኑ ደብዳቤ ይፅፍልኛል... እኔም እፅፍለታለሁ ... ጠዋት ስንገናኝ ደብዳቤዎቹን እንቀባበላለን:: ከሰዓት
ከስራ የሚወጣበት ሰዓት ከኔ ጋር ስለማይዛመድ ከሱጋር ሳይክሌን እየገፋሁ በእግሬ 40 ደቂቃ የሚወስድብኝን
መንገድ በሳይክል በ10 ደቂቃ እልሰዋለሁ።
ደጋግመን የሄድንባቸው መንገዶች ኮቴያችንን ሰምተው እስኪያውቁት .... በየመንገዱ ያሉ የንግድ ቤት ዘበኞችና
ቋሚ የኔቢጤዎች እንደወዳጅ ሰላምታ መስጠት እስኪጀምሩ ...... ቤተኞቼም የኔና የእሱን አብሮ መውጣትና
መግባት ከመልመዳቸው የተነሳ እሱ የአጥሩን በር ሲያንኳኳ 'ሜሪ መጥቷል!' ብለው መጥራት እስኪለምዱ .....
ከዚህን ያህል የጊዜ ለውጥ በኋላ ነበር የሳመኝ። (መፀለይ ይነሰኝ?) እንደጠጣ ሰው ጀብረር አድርጎኝ ነበር
አሳሳሙ ሳልዋሻችሁ (ቤተኞቼ አንድም እሱን ስለሚያምኑት 'የጌታ ሰው' ስለሆነ ... ሁለትም ለወትሮው በየቀኑ
የሆነ ጥፋት የማጠፋ የነበርኩትን ልጅ ስላለዘበላቸው ... በተጨማሪም ወደ ቸርች ስለተመለስኩላቸው ....
ከእርሱ ጋር መውጣት መግባቴ ብዙም አልጎረበጣቸውም)
ይሄ በሆነ በጥቂት ቀን "የስራ እድገት አጊንቼ ሌላ ሀገር ልሄድ ነው አለኝ!" እንዴት እንደሚነግረኝ አፉ ላይ
ቃላቶቹን ሲያንገዋልላቸው ቆይቶ
"እኔስ? ስምንት ወር ሙሉ እጅህን ተመርኩዤ ሀዘኔን የረሳሁት እኔስ? ትተኸኝ ስትሄድ ምን ልስራ? በቀን ሁለቴ
የማይህ እኔስ አንተ የሌለህበትን ቀን እንዴት ልለፍ? ምን ልስራ? አንተ ሳትኖር ማነኝ? ንገረኝ ምን ልሁን?"
እንደሚሄድ እርግጠኝነት ነበረው ድምፁ ስለዚህ 'ቅርልኝ' ልለው አቅሙ አልነበረኝም። ምን ያህል በፍቅር ሙክክ
ብዬ እንደበሰልኩ የገባኝ የዛን ቀን ነው። ለወትሮ በሰው ፊት ማልቀስ ያውም ለማልቀስ ምክንያት በሆነኝ ሰው
ፊት ማልቀስ ሽንፈት የሚመስለኝ እኔ ....... በሱ ፊት ተዝረከረኩ።
"በቃ አልሄድም እቀራለሁ::" አለኝ "በቃ አንቺ ትምህርትሽን እስክትጨርሺ የትም አልሄድም ይቅር !" አለኝ
አቅፎ እያባበለኝ። አዲሱ ስራው አዲስ በተከፈተው የአቢሲንያ ባንክ ማናጀር ሆኖ ነው የሚሄድ የነበረው። ገና
እንደተመረቀ ነው አሁን የሚሰራውን ስራ አጊንቶ የጀመረው። በአንድ አመቱ አሁን ያገኘው እድገት ለእሱ ምን
ያህል ትልቅ ነገር መሆኑን አውቃለሁ። 'ትቼልሻለሁ' ሲለኝ የባሰ ሙክክ ከማለት ውጪ ምርጫ ነበረኝ? እኔ
ደግሞ አስራ ሁለተኛ ክፍልን ገና መጀመሬ ነበር። ተስማማን!! በሆነ መልኩ ራስ ወዳድ እንደሆንኩ ገባኝ።
"ይዘኸኝ ሂድ!" አልኩት በነገታው ጠዋት ትምህርት ቤት ሊሸኘኝ እንደመጣ እስክነግረው ጓጉቼ እላዩ ላይ
እየተንጠለጠልኩ ምን እንዳልኩ ገብቶታል። ግን ማመን አልፈለገም።
"የት ነው ይዤሽ የምሄደው? የምትዪው የማስበውን ከሆነ.... አይሆንም!!" አለኝ ኮስተር ብሎ
"ለምንድነው የማይሆነው?"
"ስለምወድሽ ነው የማይሆነው!! ...የኔ ሚስት በስነስርዓት ለቤተሰቦቿ ሽማግሌ ልኬ .... ቸርች ቆሜ በጌታ ፊት
ቃል ገብቼላት .... በቤተዘመድ ተመርቀን ..... ነው የማገባሽ! በፍፁም እንደወመኔ ብድግ አድርጌ ይዤሽ
አልሄድም። ትምህርትሽን በጥሩ ውጤት ትጨርሻለሽ .... እንደህልምሽ ህግ ትማሪያለሽ ..... ስትመረቂ ከፈለግሽ
የምርቃትሽ ቀን ሰርጋችንን ማድረግ እንችላለን።" አለኝ ኮስተር ብሎ ቀጠል አድርጎ "አንቺ ግን የምርሽን ነው?"
"እሱማ የምሬን ነው። ቆይ ምንድነው ያልከውን ሁሉ ከማድረግ የሚያግደኝ? ሰሞኑን ሽማግሌ ትልካለህ .... ከዛ
ቸርች ሄደን ቃል እንገባባለን.... ይዘኸኝ ትሄዳለህ .... አንተም ስራህን እኔም ትምህርቴን ..."
"እ እ አይሆንም አልኩ አይሆንም!" አለኝ ከአፌ ቀምቶ "እብድ እኮ ነሽ ..."
ማታ ምን አቅብጦኝ እንደሆነ ሳላውቅ ለማሚ ነገርኳት። በቤቴኮ 'እንዴት ያለ የተባረከ ልጅ ነው::' ብላ
እንድታሞግስልኝ ነበር:: ቦንብ ማፈንዳቴ አልታወቀኝም። ከዛን ቀን በኋላ እሱ እኛ ቤት በምንም ሰበብ ቢሆን
እንዳይመጣ ለእርሱም ለወንድሜም ማስጠንቀቂያ ተሰጠ። ትምህርት ቤትም ሆነ ቸርች ወይ ማሚ ወይ አባቴ
ሆኑ የሚያደርሱኝ። ቸርች የምሄድባቸው ቀናት ተወሰኑልኝ። እሱም ቸርች ማስጠንቀቂያ ደረሰው። አንድ
ሳምንት ሳናገናኝ አለፈ። ... እንደዛ እንደመልዓክ የሚያዩት ቤተኞቼ .... ሲያዩት ሁላ የሞት መንፈስ እንዳዩ
ይሸሹት ጀመር ... ማሚ ጭራሽ ተከርብታ 'ባንተ ተመስሎ ልጄን ከአላማዋ ሊያሰናክል ያለ መንፈስ ወጋሁ!!"
ብላዋለች ለትምህርት ቤት ሁላ ማንም ቢጠራኝ እንዳያስጠሩኝ መልእክት ተላለፈ። በርቀት መድረክ ላይ
ብቻ አየዋለሁ።
(ምንም አልገቡኝም:: ቀላሉ መንገድ ከኔጋር ማውራት ነበርኮ ... እውነቱንኮ ነግሬያቸዋለሁኝ... )
ከዛ ግን ያቺ እንቢ ባዩዋ እኔ ሁሉንም "የራሳችሁ ጉዳይ!" አለች ከትምህርት ቤት አሞኛል ብዬ አስፈቅጄ ስራ
ቦታው ስበር ደረስኩ ሲያየኝ ሊጮህ ሁላ ዳዳው በደስታ ከመሬት አንስቶ አየር ላይ አሽከረከረኝ።
"የማብድ መስሎኝ ነበር::" አለኝ ፀጉሬን.. አንገቴን .. ጉንጬን ... ከንፈሬን ... እየሳመ... እንደሌላው ቀን
ለሚያየው ሰው ሁላ ሳይጨነቅ
"አሁንስ ይዘኸኝ አትጠፋም?" አልኩት
ፈገግ ብሎ "መቼ?" አለኝ
........ አልጨረስንም ......
(ደሞ ከዚህ ስርም የሚቀጥለው ክፍል አሁን ይሁን እንዳትሉ)

ሁለቱን ባሎቼን ላስማማ እያሸማገልኳቸው ነው!!


(ክፍል አራት)
በሚንቀጠቀጡ እጆቼ ደመነፍሴን ቢላ አንገቴ ላይ ያደረገ እጁን ለቀም አድርጌ ያዝኩት። ያዝኩት እንጂ
እንዲያሸሽልኝ ልገፋው ወይ ራሴን ላሸሽ አቅሙ አልነበረኝም። የአቅሜ ጥግ ሳጌ ድምፁ እንዳይሰማ አፍኜ
እንባዬን ማዝነብ ብቻ ነበር። እጁ አንገቴ ላይ ቢላዋ መደገኑን እጆቼ ሲይዙት ገና ያወቀ ይመስል ደነገጠ። በጣም
ቀስ ብሎ እጁን አወረደው ........ ቢላውን ወረወረው ........ በጣም ቀስ ብሎ መሬቱ ላይ ተቀመጠ። አንገቱን
ወደመሬቱ ደፍቶ እንባው መሬቱ ላይ ተንጠባጠበ። ይሄኔ 'ዋጥ አድርጋት' ተብሎ ታፍኖ እንደተገረፈ ህፃን "ህእእ
ህእእእ ......" ብዬ ድምፄን አውጥቼ ማልቀስ ጀመርኩ።
ይሄኛው ሌላ ሰውዬ ነው። የእኔ ባል እንኳን ቢላዋ አንስቶ አንገቴ ላይ ሊያደርግ እጅሽን ይቆርጥሻል ብሎ
ሽንኩርት የሚከትፍልኝ ...... ትልልቅ አይኖቹ እያለቀሱ ሲያስቸግሩት
"እማ ቆይ ወጥ ያለሽንኩርት ቢሰራ ምን ይሆናል?" የሚለኝ
"እሺ አንተ ነጭ ሽንኩርቱን ላጥልኝ ሽንኩርቱን እኔ ልጠዋለሁ" ስለው ሊልጥ ይታገልና
"እማ ቆይ ወጥ ውስጥ ነጭሽንኩርት ባይገባ ምን ይሆናል?" የሚለኝ።
"እህ? እና ያለሽንኩርት ያለነጭሽንኩርት ዘይት ላይ በርበሬ አድርገን እናቁላላ? "
"አንቺ ከምትቃጠዪብኝ አይሻልም?" እያለ የሚያባብለኝ። ሁሉ ነገር ከእሱ ሲወዳደር የሚያንስብኝ የኔ ባል ይሄ
ነው።
የኔ ባል በቀደም በእግር እየሄድን ከእርግዝናው ጋር ተያይዞ በመጣ ደም ማነስ አዙሮኝ ስወድቅ እንደህጻን
በእጆቹ አቅፎ ሀኪም ቤት ያደረሰኝ።
"አባ መራመድ እችላለሁ እኮ!" ስለው
"እኔ ምን እሰራለሁ?" የሚለኝ ዶክተሩን
"ደም ማነስ እንዴት አዙሮ ይጥላታል? ደግመህ መርምርልኝ ካለበለዚያ የሆነ ነገር ብትሆንብኝ እጣላሃለሁ!"
ብሎ የሚቀውጠው
"ፈሳሽ ነገር በብዛት መውሰድ አለባት!" ብሎ ሲለው። ያለ የሌለ የጁስ መዓት እያስጠጣኝ በሽንት ብዙት የረጋ
እንቅልፍ የማያስተኛኝ
ለእኔ ከሆነ ምንም የሚያደርግ የትም የሚሄድልኝ።
የኔ ባል ገና ለከተማው አዲስ ሆነን እንደመጣን አንዱ ቸርች ይዞኝ ሄዶ "ባለቤቴ ናት የሚያምር ድምፅ አላት
እኔም እሷም ጌታን ማገልገል እንፈልጋለን ብሎ ኮስተር ብሎ ሲያወራ (ማስፈራቱ ግርማሞገሱ ደግሞ )
ከሳምንታት በኋላ አብሬው ማስመለክ የጀመርኩት ......
ከእግዜር ጋር ያለኝን ፀብ በሚገባኝ ጣፋጭ ቃል አይኔን ከሰዎች ላይ እና ካልተደረገልኝ ነገር ላይ አንስቼ ትልቁ
አምላክ ላይ እንዳደርግ ያስተማረኝ መምህሬ .......
እንኳን እኔ ወንድሜ እጁን ይዞ ፒያኖ ያስተማረው። ወንድሜ ምን መሆን ትፈልጋለህ ቢባል "እሱን" የሚልለት
የሚያስቀና ስብእና ያለው (ያሸነፈኝ ምን ሆነና?)
የኔ ባል
ጎረቤት ዶሮ ወጥ ተሰርቶ አይቼ ከስራ ሲመጣ እያለቀስኩ "ወጥ ሰርተው እንብላ እንኳን ሳይሉኝ ወደቤት
አስገቡት!" ብዬ ስነግረው በአንድ እርምጃ የሰው ቤት ገብቶ
"እንዴት ሚስቴ እርጉዝ መሆኗን እያወቃችሁ ወጣችሁን ከለከላችኋት?" ብሎ የሚጣላልኝ። በሰው ዶሮ ወጥ
'እሷ የምትወደው እግር ነው' ብሎ መርጦ ይዞልኝ የሚመጣ ...
የኔ ባል "መንገድ ላይ ጮክ ብሎ መዘመር አማረኝ" ስለው እንዘምራለና ታዲያ ብሎ በሰው ሀገር መንገድ ላይ
ቀውጢ አምልኮ ፈጥረን ሰው ከመንገዱ የምናሰናክል .....
"አባ ደከመኝ ትንሽ እንረፍ!" ስለው እሽኮኮ ካላደረግኩሽ ብሎ የሚያስቸግር ...
መንገድ እየሄድን በሃሳብ ተውጬ የሆነኛው መንገድ ላይ የተንጠለጠለ ሙዝ ላይ ሳፈጥ የሰው ማሳ ገብቶ
ያልበሰለ ሙዝ ሰብሮ ከጠባቂው ጋር ግብ ግብ የሚገጥምልኝ ....
የኔ ባል ሁለት ልጆች አንድ ሴትና አንድ ወንድ ወልደን ስማቸውን አውጥተን ስናረጅ ምን እንደምንሰራ አቅደን።
ፀጉራችን ነጭ ሆኖ ጥርሳችን አልቆ ምን እየተባባልን እንደምንፎጋገር አውርተን የጨረስን ....
የኔ ባል "ባንተ ድምፅ ሲሆንኮ ሲጣፍጠኝ" ስለው ቁጭ ብሎ መፅሃፍቶች የሚያነብልኝ።
ሰው ውጪ ምሳ ልጋብዝህ ሲለው ሚስቴ ብቻዋን ናት ብሎ የሚመጣልኝ ...
የእኔ ባል ብዙ ነው ...... በእያንዳንዱ በሚያደርጋቸው ጥቃቅን ነገር ሁላ ሳይቀር ከምንም እንዳላወዳድረው ሆኖ
ልቤን የሞላ ነው
.....
ይሄኛው የኔ ባል አይደለም:: እንዴት ሁለት ማንነት አንድ ስጋ ውስጥ ይቀመጣል???
.....
.....
ለሰዓት ያህል ከተቀመጥንበት እሱ ቀድሞ ተነሳ
"ሄጄ አምሳሉን (ስራ በመስራት የምታግዘን ልጅ ናት) ልጥራትና እሷ ወጡን ትስራው በቃ ወይም ይቅር በቃ
ስጋ ገዝተን ጠብሰን እንብላ .....አይሻልም ? ..... አንቺ ተነሺ በቃ አረፍ በይ እ?" ሊወጣ መንገድ ከጀመረ በኋላ
"የትም አትሄጂብኝምኣ?" አለኝ እግሬ ስር መጥቶ ጉልበቴን እያሻሸ
"ልሂድ ብል የት እሄዳለሁ?" አልኩት ሳላስበው። በዛ ቁመቱ ዝርፍጥ ብሎ ስሬ ቁጭ አለ። በእርግዝናው ሳቢያ
ማበጥ የጀመሩ እግሮቼን ከጫማው ላይ አንስቶ ሁሌን እንደሚያደርገው እያሸልኝ
"እማ እባክሽ ማሪኝ!" አለኝ እንባው ጠብ ሲል እግሬ ላይ ያርፋል:: እሺም ..እንቢም ... ሙግትም ... ትግልም ...
የለኝም ብቻ ፀጥ !!
"እማ እባክሽ አትተይኝ! ???ይቅር በይኝ!??" ከማልቀስ ውጪ መልስ አልሰጠውም:: ሁሉም ነገር ግልብጥብጥ
ብሎብኛል የተፈጠረው ቅፅበት ህልም ቢሆን ..... እሱን ክፍል ብቻ መደምሰስ ብችል ከጭንቅላቴ ውስጥ .....
ለምን? እንዴት? ጭንቅላቴ ውስጥኮ ብዙ ጥያቄ ይንከላወሳል።
እንዴት አንድ የዚህኛውን እሱን ምልክት ይሄን ያህል ጊዜ አላየሁበትም? ግን አፌን ለቆ የሚወጣ ምንም ቃል
የለም። ልጅ ልኮ የምትሰራልንን ሴት አስጠርቷት አመት በአል አስመስላው ሄደች እንደነገሩ እራታችንን
ቀማመሰን በጊዜ ተኛን። እኔና እሱ ኩባያ የምንለውን አስተኛነት (ለምን እንደዛ እንዳልነው አላስታውስም)
ጀርባዬን ሰጥቼው በጎኔ በእጆቹ በሃል ታቅፌ ጀርባዬና ደረቱ ተጣብቀው .... እጥፍ ያለ ጉልበቱ መሃል እግሮቼን
አጥፌ ተኛኝ። ማልቀሴን ማቆም አቃተኝ:: ሳጌ እንዳያመልጠኝ እታገላለሁ።
እያለቀሰ ነው። ሳጉን እንዳልሰማው ውጦታል። እንባዬ ክንዱን ሲያርሰው ይሞቀዋል:: እንባው አንገቴ ስር
ሲያርሰኝ ይሞቀኛል። አልቅሼ እንባዬ ሲያልቅ ነው መሰለኝ ...
"ምን ያህል እንደማፈቅርህ ህቅ ህቅ (ሳጌ ያቋርጠኛል) አልገባህም ማለት ነው?" አልኩት ዞሬ
"እማ እባክሽ ማሪኝ?" አንገቴን ፀጉሬን እጄን በእንባ የራሱ ጉንጮቼን አይኖቼን ይስማቸዋል። ለደቂቃዎች
ምላሳችን ላይ እንባችን ጨው ጨው እያለን ስንሳሳም ቆይተን ደረቱ ላይ እንቅልፍ ይዞኝ ሄደ።
በነገታው ለሱ ሳልነግረው ከቤት ወጥቼ እናቴጋ እቤት ስልክ ደወልኩ። የተፈጠረው ነገር ለሱ ያለኝን ፍቅር
አልነበረም የቀነሰው። እኔኑ ራሴኑ ነበር በሆነ መጠን የሸረፈኝ። ምክንያቱም ከትናንት በፊት የነበረችው ሜሪ
ለማንም ብላ ማንንም የምትፈራ ሴት አልነበረችም።
በስልኩ ውስጥ የእናቴን ድምፅ ስሰማ:: ማውራት አቃተኝ!!! እንባ እና ህቅታ ብቻ ....
......... አልጨረስንም እንግዲህ.......
ሁለቱን ባሎቼን ላስማማ እያሸማገልኳቸው ነው!!
(ክፍል አምስት)
"ማሚ" ከማለቴ እናቴ በስልኩ እልልታዋን አቀለጠችው። ፀሎት አይሉት ወሬ
"ጌታ ሆይ ምን ይሳንሃል? ጸሎቴን ሰማኸኝ እልልልልል ...... ልጄ? ደህና ነሽ?"
"ደህና ነኝ!" እያልኳት እሪታዬን እለቀዋለሁ
"ምን ሆነሽ ነው? የት ነው ያለሽው ?አሁኑኑ ልምጣ ?"
"ምንም አልሆንኩም! ናፍቃችሁኝ ነው።"
ስለእሱ ላወራት አልችልም። እሱን ከማሳማው ያን ቢላ አንገቴ ላይ ድጋሚ ባገኘው ይቀለኛል። እሱን
እንድትጠላብኝ አልፈልግማ!! ልጇን ያደረጋትን እንጂ ልጇ ለሱ ያላት ገደብ የለሽ ፍቅር አይገባትማ! ግን የእናት
ሆዷ ነግሯታል።
"እሺ ይሁን እንዴት ሆንሽ? ትምህርትሽን እየተማርሽ ነው? "
"አይደለም ማም እርጉዝ ነኝ። በዚህ ዓመት አልማርም። ልጄን ከወለድኩ በኋላ እማራለሁ!"
ዝም አለች። ወደፊቴን አስባው ልቧ ዝሎባት መሰለኝ ዝም አለች። ከወለዱ ኋላ ያለውን አቀበት አይታው ነው
መሰለኝ ዝም አለችልኝ። የምትለው የማታጣው እናቴ ዝም
"ማም ?"
"ወዬ? እስኪ ይሁን ብቻ አንቺ ደህና ሁኚ!..... እሱ አሁን አጠገብሽ አለ? (አባባሏ ይሄ እንትን .... ብላ የሆነ ስድብ
የመቀጠል ነገር ነው። )ምንም ባልላትም ጠምዳዋለች።
"የለም ስራ ነው!"
"ይሁን እንደምትዪው ..... በወጉ ሽማግሌ ላክ በዪው ..... ሳትወልጂ በስነስርዓቱ ተደግሶ ቃልኪዳን
ትፈፅማላችሁ። በምንም ሁኔታ ቢሆን ልጄን እንደማልተውሽ ማወቅ አለበት።"
"ማሚ እሱኮ ከእናንተ እንድጣላ አይፈልግም ለምን እንደጠላት ታዪዋለሽ? ምርጫዬን የመረጥኩት እኔ ነኝ እሱ
እንደውም ሁሌ ደውዪላቸው ነው የሚለው።" (ደግሞ የምሬን ነው። በከፋኝ ቁጥር ለምን አትደውይላትም ነበር
የሚለው)
"እሱን እንኳን ተይው .... የውልሽ ልጄ ወንድ ልጅ ብቻሽን ሲያገኝሽ እና መሄጃ እንደሌለሽ ሲያውቅ ጥሩ
አይደለም። ያኔ ከርሱ ውጪ ምርጫ የሌለሽ ንብረቱ ነሽ። ያን ክፍተት አትስጪው ...... አይደላደል .....
ተንከባክቦ በፍቅር ካላኖረሽ አማራጭ ያለሽ መሆንሽን ሲያውቅ እንደሚገባሽ ያከብርሻል!!"
የኔ ባል ይለያል ብዬ እንዴትም ላስረዳት አልችልም። እናቴ አንድም በህይወቷ ሴትነትን ከፍ አድርጋ የምትኖር
ሁለትም ሴቶች ጉዳይ የምትሰራ ያውም በከፍተኛ ሃላፊነት ደረጃ ላይ ያለች ሴት ናት።
"What happen to ስታስተምሩ ያሳደጋችሁኝ 'ሚስት ለባሏ ትገዛ?'"
"ሚስት ለባሏ ትገዛ ሲል ለባልም ሚስቱን ነፍስን እስከመስጠት ባለ የክርስቶስ ፍቅር የመውደድን ሀላፊነት
እንደሰጠው አትርሺ!" አለችኝ ኮምጠጥ ብላ።
"ማሚዬ እንደዛ ይወደኛል።" አልኳት ለእሷ ... ለራሴ መልሼ ግን 'እንደዛ ይወደኛል?' ብዬ አሰብኩ። ያልጠየቀችኝ
ነገር የለም።
"ለመሆኑ ቤቱን በትክክል ያስተዳድራል?" ምን ማለቷ እንደሆነ አውቃለሁ። ገንዘብ ይሰጥሻል ወይ ነው?
"ማሚ ደሞዙን አምጥቶ ለእኔ ነው የሚሰጠኝ (የምሬን ነው። ሙሉውን ደሞዝ አምጥቶ ለእኔ ነበር የሚሰጠኝ።
ልክ አባቴ ለእናቴ እንደሚያደርገው። በወር የሚያስፈልገንን ፅፌ አዘጋጃለሁ። ለሱ የኪስ ብር እሰጠዋለሁ።
የሚደረገውን ሁሉ እኔ ነኝ የማደርገው። )
"እሺ ጉዳዩ ላይ እንዴት ነው?"
"ማሚ ኸረ በጌታ ?" ለቅሶዬን አስትታ አስፈገገችኝ
"እህህ የምሬን ነው። ከዚህ ሰው ጋርኮ ነው የምታረጂው። ትዳር እኮ ቆይ ለጉዳዩ ለጉዳዩ ጊዜ ወጣ ብዬ ልምጣ
አይባልበትም!"
መጨረሻ ላይ አባቴን ላወራው እንደምፈልግ ስነግራት። እሷ ሰበብ ብትነግረኝም አባቴ ሊያናግረኝ እንዳልፈለገ
ገባኝ። ዝምተኛው አባቴ በዝምታው ሊቀጣኝ ፈልጓል። ሁሌም እንደዛ ነው። ጥፋት ሳጠፋ ተቆጥቶኝ አያውቅም።
በዝምታ ነው የሚቀጣኝ። ጥፋቴን እስካርም ወይም ይቅርታ እስክጠይቅ ድረስ አያዋራኝም። ይሄኛውን ግን
ለማረም ዓመታት ሊፈጅብኝ ይችላል። እሱ የሚስላትን ልጁን ሆኜ ላሳየው ብዙ ይፈጃል እና በዝምታው
የሚቀጣኝ እስከዛ ከሆነ?......
የዛን ቀን ማታ ከስራ መጥቶ ወክ እያደረግን ለእናቴ እንደደወልኩ ልነግረው ፈራሁት። ምኑ እንዳስፈራኝ
አላውቅም። ካፈቀርኩት ጀምሮ ከሱ ጋር ሳልማከር አድርጌ የማውቀው ነገር ባለመኖሩ ስለደበቅኩት? 'ግን
እናቴጋ ለመደወል የግድ ከእርሱ ጋር መማከር አለብኝ?' እላለሁ ለራሴ ነገሩን ለማቅለል።
"አባ ዛሬ ማሚጋ ደወልኩኮ!" መገረምም መደንገጥም ፊቱ ላይ እያየሁ ምንም እንዳልመሰለው ለመሆን ጣረ
ሁለታችንም እየተቀየርን እንደሆነ አሰብኩና ፈራሁ። መደባበቅ እየጀመርን ነው። ፈራሁ!!
"ቆንጆ አደረግሽ! ምን ተሰማሽ? ደስ አለሽ? ማሚ ምን አለች? ደህና ናቸው?" ስሜቱን ለመደበቅ በጥያቄ
ያጣድፈኛል። ያለችኝን ነገርኩት
"ደስ ይላል እማ!" አለኝ ማንን ሽማግሌ እንደሚልክ ምናምን ሰርጋችን ላይ ማን እንደሚጠራ ምናምን
ማውራት ጀመርን!!
ስለሰርጋችን ማውራቴ ትቼው ልሄድ አለማሰቤን ስለነገረው ይመስለኛል ቀለል አለው። እኔ ግን ከፋኝ !! እኔ እና
እሱ መሰለኝ እየተባባልን ስሜታችንን አንገማመትም:: ይነግረኛል አውቃለሁ። እነግረዋለሁ ያውቃል።
"ቤተሰቦችህጋ ትደውላለህ?" አልኩት።
"አላውቅም!" አለኝ ከቤተሰቡ ጋር ለረዥም ዓመታት ተገናኝቶም ደውሎም አያውቅም።
ማውራት የማይፈልገው አጀንዳ ነው። እሱ ጴንጤ ከሆነ በኋላ ምንም አይነት መጠያየቅ ተጠያይቀው
አያውቁም። ትዳራችን ላይ የሚያመጣው መዘዝ አለ ብዬ አስቤውም ስለማላውቅ ትኩረት ሰጥቼው
የማውቀው ነገር አልነበረም።
ከዚህ ክስተት በኋላ ከዋነኛው ባሌጋ የምናነባቸው መፅሃፍት ውስጥ እንዳሉት ፍቅረኛሞች የሚያስቀና
ትዳራችንን ቀጠልን። መፅሃፍቶቹ ውስጥ ያሉ ባለትዳሮችም ሆነ በገሃዱ አለም ያሉ ባለትዳሮች ሳይነግሩሽ
የሚዘሏቸው ጥቃቅን የሚመስሉ ከባባድ ነገሮች አሉ። ለምሳሌ ምስር ወጥ ለመስራት ከወጡ ሙሉ ሂደት
ምስሩን መልቀም እንደሚያደክም አይነግሩሽም ....... እርጉዝ ሆነሽ እንጣዬ ስታደርጊ ልጄን እየነካው ይሆን?
የሚለው ሀሳብ ከስሜት እንደሚያወጣ አይነግሩሽም። (ምነው እማ? ሲለኝ በመሃል ልጁን ትነካው እንደሆነ
ሃሳብ መጥቶልኝ ስለው አቋርጠን ለሰዓታት በሳቅ መዛላችንስ?)
የሰርጋችን ቀን ተወሰነ። ሽማግሌ ተላከ። ሆዴ እየገፋ ሲመጣ ደም ማነሴ እየጨመረ መጣ። ስለሚያዞረኝ ድንገት
እንዳልወድቅ እርሱ እንደህፃን እጄን ይዞኝ ካልሆነ በቀር ከቤት አልወጣም። የሆነ ቀን እንጀራ የሚጋግሩልኝ
ሴትዮ 'ምጣዱ ተሰበረ' ሲሉኝ። አብሪያቸው ምጣድ ላጋዛ ገበያ ሄድኩ።(ይሄንንም አይነግሩሽም በነገርሽ ላይ)
ገበያው መሃል ጎንበስ ብዬ ቀና ስል አዙሮኝ ወደቅኩ። እኔ እቤት ሳልደርስ ወሬው ባሌጋ ደርሷል። ሲመጣ እጅ
እግሩ እየተንቀጠቀጠ ደባብሶ ደህና መሆኔን ካረጋገጠ በኋላ ..... ልቡ በአፉ ልትወጣ እስኪደርስ ደንግጧል። ከዛ
ያልገባኝ የድንጋጤው ብዛት ወደ ቁጣ ተቀየረ።
"አትውጪ አላልኩሽም? አይቀርም? ለምን ሰው የሚልሽን አትሰሚም? የሆነ ነገር ሆነሽ ቢሆንስ? " (ያ ደባሉ
ባሌ መጣ) ረስቼው ነበር እና አላስተዋልኩትም።
"በቃ ምንም አልሆንኩምኮ ! በጣም አካበድክ" ከተኛሁበት ብድግ አልኩ እሱ በሚናገርበት ድምፅ ጮክ ብዬ
(ምላሴ ቢያርፍስ ?)
አንዴ በጥፊ ሲያልሰኝ እኔ ከሲኖትራክ ልውደቅ ሲኖትራኩ በኔ ላይ ይሂድ አላውቀውም! ብቻ ስሜቱ እንደዛ
ነው። የሰው ጥፊማ እንዲህ ጭው አይልም።
አመንኩ። ይሄ የአንድ ቀን ስህተት አይደለም። ባሌ ሁለት ነው። እሺ ምን የሚሉት ነው? ፍቅር ነው ጥላቻ?
በምነኛው ዘርፍ ልቀበለው? ነፍሱ እስክትወጣ ስለሚያፈቅረኝ የሆነ ነገር ሆነሽብኝ ቢሆን ኖሮስ ብሎ ተናዶ
እርጉዝ ሚስቱን እሱ በነፃ በአንድ ሲኖትራካዊ ጥፊ የሆነ ቦታ ደርሶ መልስ ትኬት የሚያስቆርጠኝን ባሌን በምን
ዘርፍ ልመዝግበው? ለሁለት ባል እያወቅኩት ልሞሸር?
(እዚህ ክፍል ድረስ ከዘለቃችሁ ይሄን ልንገራችሁ። የሆነችዋ ሴት በዚህ መንገድ አልፋለች ወይም እያለፈች ነው።
ምናልባት ለሆነችዋ ሴት ብርታት ሊሆን ይችላልና ይህ የእኔ የሜሪ እውነተኛ ህይወት ነው። ብታምኑም
ባታምኑም ስፅፈው ከ17 ዓመት በኋላ ከእንባዬ ጋር ነው። የስራችሁን ይስጣችሁ በቀን ሁለቴ
ታስቸክሉኛላችሁኣ?)
........... አልጨረስንም ባይዘዌያችሁ ላይ......

ሁለቱን ባሎቼን ላስማማ እያሸማገልኩ ነው


(ክፍል ስድስት)
ሳፈቅር ገገማ ነኝ!! ግግም ያልኩ ሰገጥ!! የተመታሁት እኔ ...... ቢላ አንገቴ ላይ የተደረገው እኔው ...... እሱ
ለሰራው ጥፋት ማስተባበያ የምሰጠውም እኔው ....... ሁለቱንም ጊዜ እኔ ስቆጣ ነው ሌላ ሰው የሆነው ስለዚህ
እኔ እሱ ሲቆጣ ባልፈው ያኛው እሱ አይመጣም ብዬ አሰብኩ!(ሰገጥ ነኝ አላልኳችሁም?)
እንዴት እንደማስተካክለው .... እንዴት ሁለቱን ማንነቱን እንደማስማማ እንጂ የማስበው ከሱ መለየት
በፍፁም ለምርጫ የሚቀርብ አይደለም። ከሚሆነው ሁሉ እሱን የማፈቅርበት ጥግ ያልፋል። እናም ሁለቱን
ባሎቼን በአንድ ሱፍ አገባኋቸው!! አባቴ እግሩን ስሜ እንኳን ስወጣ በሙሉ ዓይኑ አላየኝም። እሱኛው ቅፅበት
ባሌ ካላሰኝ ጥፊ በላይ ያም ነበር።
በሆነ ጊዜ አንዴ የሚመጣውን ያኛውን እሱን በየቀኑ እንደሚሰበር ነገር ለሚጠነቀቅልኝ እሱ ስል ልችለው
ወሰንኩ!! ምን እንደሚያስከፍለኝ የማውቅበት የእድሜም የብስለት ደረጃም ላይ አልነበርኩም። የማውቀው
ያለእድሜዬ ያነበብኳቸው የፍቅር መፅሃፍት ውስጥ እና ያየኋቸው ፊልም ላይ ያለውን አድቬንቸር የሆነ ፍቅር
ነው። ያ ደግሞ እንኳን ጥፊ ሞት ይጨለጥበታል።
ማሚ "የመጀመሪያ ልጅ እናት ቤት ነው የሚወለደው" ብላ አላፈናፍን ስትለን እሱ ደስ ሳይለው ሄድኩ።
ወለድኩ!! ፀግዬን ወለድኩ!! ልክ ተገላግዬ ክፍሉ ውስጥ ሲገባ አልጋዬ አጠገብ በጉልበቱ ተነበርክኮ የሆነው
መሆን ....... አምጥተው ህፃኗን ሲያስታቅፉት የተሰፈሰፈው መንሰፍሰፍ በጥይት መቶኝ ቢሆን ሁላ እረሳለት
ነበር። (ሰግጣለሁ አልኳችሁኮ)
ልጄን አቅፎ በሚያምር ድምፁ እየዘመረ ሲያስተኛት እያየሁት ለሁለቱ ስል ምንም መሰናክል እንደማልፍ
ወሰንኩ። ማሚ ህፃን ማጠብ ለእኔ ሳይሆን ለሱ ነበር ያስተማረችው። ለሊት ተነስታ ስታለቅስ ልናስተኛት
አሳራችንን ስናይ የምታሰቃየን ልጅ ልክ እሱ አቅፏት መዘመር ሲጀምር ትተኛለች። እና በዚህ ፍቅር ቂም መያዝ
ይቻለኝ ነበር?
የእናቴ ቤት ድሎት ኮሰኮሰኝ ምክንያቱም እሱ ስራ መግባት ስለነበረበት ተመልሶ ሄደኣ። በየቀኑ ስልክ
እየደወለልኝ ለሰዓትት እናወራለን። አባቴ አሁንም ከ'ደህና አደርሽ?' እና 'ህፃኗ እንዴት አደረች?' ያለፈ
አያወራኝም። ጭራሽ ሆድ ባሰኝ እሪሪሪሪ ብዬ በ45 ቀኔ ወደ ባሌ እቅፍ ተመለስኩ። (መሰስ ብዬ ቦክስ ሪንግ
ውስጥ መግባቴ የታወቀኝ ሰንብቶ ነው።)
የሚናደድበት ምክንያትና ሰዓት እስኪዋቀጥብኝ የሚናደድባቸው ነገሮች እየበዙ መጡ። ሲናደድ ምን እንዳደረገ
የሚያውቀው ካደረገ በኋላ ነው። ጭራሽ አያውቀውም። ካደረገው በኋላ ለቀናት በሙሉ ዓይኑ አያየኝም።
የተለመደ ይቅርታ.... የተለመደ ማሪኝ.... የተለመደ ለቅሶ.... ለሰርጋችን ያልመጡት ቤተሰቦቹ መውለዴን
ሲሰሙ ደወሉ። እናቱ ልክ የሆነ አንዳንዴ መክሰስ መብላት ይዘላል አይነት ነገር ቀለል አድርገው
"አንዳንዴ ሲናደድ አብሾ አለችበት ቦግ ይላል !! አይዞሽ ታገሺው ..... እንጂ ልቡ ወርቅ ነው!!" ብለውኝ አረፉት።
"ለምን ነርሲንግ አትማሪም?" አለኝ የሆነ ቀን አለ አይደል? 'ገና አስራሁለተኛ ክፍል ተምረሽ ዩንቨርስቲ መግባት
ከልጅ ጋር ይከብድሻል' የሚል አንድምታ የያዘ። ማሚ ናት ለኳሿ እሷን አልሰማ ስላልኩ ነው በሱ በኩል
የመጣችው!!
"አባ 12 እማራለሁ አሪፍ ውጤት አመጣለሁ። ህግ እማራለሁ። ምንም የሚቀየር እቅድ የለም።"
"እሺ ካልሽ ከጎንሽ ነኝ አለሁልሽ" አለኝ። ማሚም ንቅንቅ እንደማልል ስታውቅ ይጠቅማታል ያለችውን ሀሳብ
ሰነዘረች። እሷጋ ከነልጄ ሄጄ እንድማር እና ስጨርስ ወደባሌ እንድመለስ ወይም ልጄን እሷጋ ትቼ ከባሌጋ ሆኜ
እንድማር። ሁለቱንም እንቢ አልኩ። ልጄን እያሳደግኩ ከባሌጋ ሆኜ እማራለሁ። ያለችኝን ነገርኩት። በሆነ መልኩ
እናቴ እኔን እየነጠቀችው እንደሆነ ተሰማው ተጠማመዱ።
ማሚ በደወለች ቁጥር ቤታችን በአንድ እግሩ ይቆማል። ሁሌ እምላለሁ "እሱ ሲናገር አልመልስለትም ዝም
እላለሁ" ብዬ ሁሌ ያን ማድረግ ያቅተኝና የተዋበች ቡጢ ስቀምስ ፀጥ እላለሁ። እየተደጋገመ ሲሄድ
የሚቀጥለው ህይወቴ ቀላል እንዳልሆነ ገባኝ። ይሄ ሁሉ ሆኖ ለእሱ ያለኝ ፍቅር ንቅንቅ አለማለቱ ይገርመኛል።
ሁሌም እሱን ብቻ ጥፋተኛ ማድረግ አይሆንልኝም። እንዲህ አድርጌ ቢሆን እንዲያ አድርጌ ቢሆን እላለሁ ግን
አይሆንምኮ ሲቆጣ እንደማዕበል ከየት መጣ ሳልለው ነው ዱብ የሚልብኝ። በተጣላን ቁጥር ወይም
ሊያስቆጣው ይችላል ብዬ የማስበው ነገር ሲፈጠር ስለት ያላቸውን ነገሮች ሰብስቤ እቆልፋለሁ። ....
የሆነ ቀን እሱ እየተቆጣ ሲያወራ ፀጊ አልቅሳ አላባራ አለች። "ዝም አስብያት" ብሎ ጮኸ። ምንም ባደርጋት
ጭራሽ ዝም አልል አለች። ይሄኔ ልብ አይሞትምኮ የሱ ብስጭት ቅውስ አድርጎኝ እኔ ብሼ ተገኘሁ።
"ለጸብ ሰበብ ነው እንዴ የምትፈልገው? ምን ልሁን ነው የምትለው? ጭራሽ ልጅህ አለቀሰች ብለህ ፀብ
ታጋግላለህ?" ብዬ ፊጥ ፊጥ ማለት።
ፀጊን ከእጄ ተቀብሎ ሊያባብላት ሲሞክር እኔን ማን ያቁመኝ ብሶቴ ሁሉ ተሰብስቦ መጣብኝ። እያለቀስኩ እደነፋ
ጀመር። ፀጊም እሪታዋን አላቆም አለች።
ሰይጣኑ ቆንጆ ተቀባብሎ ሰፈረበታ!! ልጅቷን እንደሆነ ነገር አልጋው ላይ ጥሏት። ብቻ በጠረባ ከታች ወደላይ
ሲያነሳኝ አየር ላይ ትንሽ ተንሳፍፌ .... ጣራውጋ ያለችውን እስከዛሬ እርቃኝ ያልደረስኩባትን የሸረሪት ድር
እግረመንገዴን አፅድቼ ተመልሼ ፈረጥኩ። የዛን ቀን በዛው ወጥቶ አምሽቶ ገባ። ቁጭ ብዬ አሰብኩ። የትኛው
ህመም እንደሚብስ ልጄን ለእናቴ ሰጥቼ ቡጢዬን ለምሳ እየሸከፍኩ ትምህርቴን ከእርሱ ጋር ሆኜ መቀጠል።
"አልፈልጋችሁም እሱ ይበልጥብኛል" ያልኳቸው ቤተሰቦቼጋ "እንደወደዳችሁ አድርጉኝ" ብዬ ሽንፈቴን
መዋጥ(ይሄ እሱን ማጣት አለው) ወይም ልጄንም ይዤ ቡጢዬንም ችዬ ትምህርቴን መቀጠል። የመጨረሻው
የማይታሰብ እንደሆነ የገባኝ ልጄን አልጋው ላይ ወርውሮ እንደጨርቅ ሲያነጥፈኝ ነው። እሱን ማጣትም
አልችልም!! ከዛ በሚያነክስ ልብ ትምህርቴን ተምሬ ውጤት ማምጣት እንደማይሆንልኝ ገባኝ። ልጄን ለማሚ
ልሰጣት እንደሆነ ስነግረው "በፍፁም!" ብሎ በጣም ተጣላን።
"ልጄ ናት በልጄ ላይ የመወሰን መብት አለኝ!" አለኝ
"ያ ማለት ሰይጣንህ ሲመጣ እየወረወርካት ማለት ነው? ይቅር አልማር? ከዛ ቁጭ ብዬ ልጄን ላሳድግ? ያውም
ባሻህ ጊዜ እየጠፈጠፍከኝ?" ይሄ ድክመቱ ነው!! ብቻ ከብዙ ጭቅጭቅ በኋላ ተስማማ ግን ለሚቀጥሉት ብዙ
ቀናት የፀብ እርሾ ሆነ። 'ልጄን ቀማሽኝ' የሁል ጊዜ ፀብ ሁለት ነጥብ ሆነ::
መስከረም መጥቶ ትምህርት ሊጀመር ሲል ፀግዬ 6 ወሯ ነበር። ለማንም ስለእሱ አንዲት ነገር ተናግሬ
አላውቅም። ልጄን እያጠባሁ ወስጄ ለእናቴ ሰጥቻት ተመለስኩ። ከመሳሳቴ የተነሳ ብዙ ጊዜ ሀሳቤን ልቀይር
ዳዳኝ።
'ለምን ትምህርቱ ራሱ ጥንቅር ብሎ አይቀርም ልጄን ለምን አርፌ አላሳድግም እኔ ከሌሎች ሴቶች በምን
ተለይቼ ነው ዓላማ ቅብርጥሶ እያልኩ የምጋጋጠው? ወይም ለምን ልጄ ከፍ ብላ ትምህርት ቤት ስትገባ ከዛ
አልማርም?' ብዙውን አሰብኩ
የጡቴ ወተት ሞልቶ ማጅራቴን ህመሙ እያሰቃየኝ ከሀዋሳ አርባምንጭ እንባዬን እየዘራሁ ልጄን ትቼ
ተመለስኩ። እንደዛ እንደምሆን ገብቶት ስለነበር ፈቃድ ወስዶ ምግብ ሰርቶ ቤቱን አስተካክሎ ጠበቀኝ። እሱን
ሳገኘው ጭራሽ ማን ይቻለኝ ? በነገታው ተመልሼ አልፈልግም በቃ ልጄን ስጡኝ የምል ነበር የመሰለኝ። ለቀናት
አለቀስኩ:: እየደወልኩ መንሰቅሰቅ ስራዬ ሆነ ....
............ አልጨረስንም............
ሁለቱን ባሎቼን ላስማማ እያሸማገልኳቸው ነው
(ክፍል ሰባት)
ይሄ ሁሉ ሲሆን በጌታ ነን በጌታ ፍቅር ጥላ ስር ሆነን ነው የምንፋቀረውም የምንቧቀሰውም። ቸርች
እናስመልካለን። የምሬን የምፀልይለትስ “ጌታ ሆይ ቁጣውን እንዲገታ እርዳው” ብዬ እሱ በተቃራኒው “ጌታ ሆይ
ዱላዬን የምትችልበት ፀጋ ስጣት!” እያለ እየፀለየ ይሁን እንጃ አይደለም ተመትቼ ጮክ አድርገው ተናግረውኝ
ቤት የማምስ ልጅ ዝም አልኩ ......... ውርድ አልኩ.....
"ትቼለትለሁ የእኔን ጉዳይ ትቼለታለሁ የእኔን ታሪክ
መላ አለው እንዴት እንደሚያደርግ ያውቃል
ዘዴ አለው እንዴት እንደሚያደርግ ያውቃል"
የሚለው የሊሊ መዝሙር እየዘመርኩ ስነፋረቅ አመሻለሁ። ዛሬም ድረስ ስሰማት እንባዬ ይመጣልኮ
ጎበዝ ተማሪ ከመሆን ውጪ ለሌላ ምንም ምርጫ ጭንቅላቴ ዝግ ነው። ገና ትምህርት ቤት እንደገባ ህፃን
ቦረቅኩ ሰው በማትስ ይወሰወሳል? በቃ በትምህርት ጠፋሁ ...... ከሱ ውጪ ጓደኞች ኖሩኝ። Bilen ቢዬ መጣች
...... ሳልነግራት ገባኋት። እሱን እንዴት እንደምወደው ማውራት ከጀመርኩ የሚሰማኝ ሁሉ ጤንነት
አይመስለውም። ጓደኞቼን አስተዋወቅኩት ወደዱት። እያደር እየዋለ ግን በአጠገቤ ዝንብ ራሱ ብታልፍ ጾታዋን
ማጣራት ጀመረ። እንዴት እንደምወደው እንዴት እንደማይገባው ይነደኛል። ወንድ አይደለም እኔ አይቼው እሱ
አይቶኝ ነገር አከተመ። ችግሩ ትምህርት ቤት ውስጥ አንድ ነጠላ ማገር በህይወቷ ዝንፍ ያለባት የማልመስል
ተጫዋች ነኝና ወንዱም ሴቱም ይቀርበኛል። እቤት ስመጣም ቆንጆ ነገር ይቀርብልኛል። "ቅድም አብሮሽ
ሲገለፍጥ የነበረው ልጅ አስተያየቱን አልወደድኩትም ሁለተኛ አብረሽው እንዳላይሽ"
ቆዩኝማ መሆን የነበረበትኮ ተቃራኒው ነው። እኔ ነኝ መቅናት የነበረብኝ። ቁመቱ ሜትር ከ83 ሰውነቱ ገራሚ
አይኖቹ ጥርሱ ከንፈሩ (ልጆቼን አይታችሁ መስክሩኣ?) የትም ቦታ ሄደን ሲያወራኮ ሴቶቹ አፉ ውስጥ ሊገቡ
ትንሽ ነው የሚቀራቸው ሲቀልድ ሲያምርበት ሲኮሳተር ግርማ ሞገሱ ሲደመጥ (እየቀለድኩ አይደለም! አሁን
ይሄንኑ ታሪክ እየነገራችሁ ያለው እሱ ቢሆን ተከርብታችሁ እንዲህ እየወደደሽ ቢቀጠቅጥሽ ምናለበት ቻዪው
ነበር የምትሉኝ!! ፍቅርንማ እሱ ያውራት) የትም ብወስደውኮ ኩራቴ ነው:: ሁሉም ሰው ይወደዋል። እሺ በዚህ
ላይ ፍቅር ችሎበት ..... በዚህ ላይ ስለምንም ርእስ ቢነሳ በሃሳብ መከራከር ችሎበት.... በዛ ላይ ጉዳዩ ላይ ጉድ
አርጎኝ (ከዛኛው እሱ ውጪ ሌላው ነገሩ እኮ በምድር የሌለ ሰው ነው።)
የተለወጠው ነገር ልጄን ለማሚ ሰጥቻት ከመጣሁ በኋላ በጣም ተሰብሬ ስለነበር ድጋሚ እንዳይሰብረኝ ራሱን
ይፈራው ነበር። ሲናደድ መማታቱን ትቶ ጥሎኝ ይወጣ ጀመር። እንደመፍትሄ የወሰድነው ያንን ነው። ከዛ ግን
ትምህርት ቤት መዋሌ ለኔ ሳቅ ሲጨምርልኝ ለሱ ስጋት ሆነበት። አስተማሪዎቼን የክፍል ተማሪዎችን በሙሉ
ማለት በሚቻል ደረጃ ያውቃቸዋል።
አንድ ቀን የሆነ ርእስ ተሰጥቶን በግሩፕ በተማሪ ፊት ከግሩፑ ሁለት ሰው ወጥቶ present ሊያደርግ አሳይመንት
ተሰጠን። ከኛ ግሩፕ እኔና ሙሄ የሚባል ጓደኛዬ ተመረጥን። በደስታ ተቀብለን ተዘጋጀን!! የሚቀርብ ቀን 60
የማይሞላ ተማሪ ፊት ወጥቶ ለማቅረብ ፈራሁ። እኔ ሜሪ ሰው ፊት መቆም ፈራሁ ....... በ10 ዓመቴ በሺዎች
ፊት ቆሜ ግጥም ያነበብኩ ልጅ ........ ማንንም ፈርቼ የማላውቅ ልጅ እጄን ሲያልበኝ አገኘሁት ........
የምወደው ነገርኮ በሰዎች ፊት ቆሞ ያን ሁሉ ጆሮ መያዝ ነበር .... የዛን ቀን ፍቅሬን ላለማጉደል ራሴ እየጎደልኩ
እንደሆነ ገባኝ። "ደህና ነሽኣ?" ይለኛል ሙሄ መቶ ጊዜ ..... ይግባው አይግባው አላውቅም " ፈሪ ሆኛለሁ ማለት
ነው!" አልኩት
"አንቺ? እኮ አንቺ ... በይ አትቀልጂ ..." ብሎኝ የሱን ፓርት ቀጠለ
የሆነው ሆነና ጨርሰን ስንወጣ አስተማሪያችን ለባሌ "ሚስትህ በራስ መተማመኗ ምናምን ...." ብሎ አዳንቆ
ነግሮታል። ያለፉትን ዓመታት ምርጥ ከሚባሉት ትምህርት ቤቶች ውስጥ በአንደኛው ስለተማርኩ ጥሩ መሰረት
ነበረኝ። ...... እና ባልዬ ሊኮራብኝ ሲገባ (የትኛው ሰይጣን ሹክ እንዳለው መድሃንያለም ብቻ ነው የሚያውቀው)
አቴንሽን ፍለጋ ሆነ ብዬ ሰበብ እየፈለግኩ ተማሪ ፊት እንደምቆም ነገረኝ። ከተፈጠረው ነገር ጋር ተደማምሮልኝ
የዛን ቀን ፀቡን እኔው ጀመርኩት። ልክ ከሆነ ነገር እንደነቃ ሰው ሁሉም ነገር ዛሬ እንደተገለጠልኝ ነገር። .....
የተዋበች ቡጢዬን ቀምሼ ባበጠ ፊቴ ትምህርት ቤት ገባሁ። ወድቄ ነው አልኩ። ... ለመጀመሪያ ጊዜ ባሌ መታኝ
ብዬ ለሰው ተናገርኩ። ለቢዬ !! ምሳ እየበላን ብቻችንን ቁጭ ብለን ነገርኳት። እቤት ስመጣ ግን ከፋኝ!! እሱን
ማንም በዛ መንገድ እንዲያውቅብኝ አልፈልግማ!! ማንም እሱን ከዛ ማንም ከሚያውቀው ተወዳጅ ስብዕናው
እንዲያወርደው አልፈልግም!!
አንዳንዴ ምልክት ኖሮኝ ትምህርት ቤት እገባለሁ:: ሙሄ "እሺ ዛሬስ ምንላይ ወድቀሽ ነው?" ይለኛል:: ቢዬ
ታውቃለች:: .... የልጄ ናፍቆት ሊያስነቅለኝ ይደርሳል:: እንዲያም ሆኖ ዓመቱ አለቀ::
ማትሪክ ሰኞ ልፈተን ቅዳሜ እሱ ታመመ። ቅዳሜ ለሊት ሀኪም ቤት ሄድን። እጄ ላይ ያለው ገንዘብ 1000 ብር
አይሞላም። ለሊት 6 ሰዓት ገደማ ነው። አሁኑኑ መተኛት አለበት ሰርጀሪ መደረግ አለበት ተባልኩ። የሆስፒታሉ
በረንዳ ላይ በቂጤ ዘጭ ብዬ ተቀመጥኩ።
"ለምን? ምን አድርጊ ነው የምትለኝ? ለምንድነው አንዱን በአንዱ የምትጭንብኝ? እላይ ሆነህ ሙድ ነው
የምትይዝብኝኣ? ለመሆኑ ትሰማኛለህ ግን?" ከሰው ጋር እንደሚያወራ ሰው ከእግዜሩ ጋር ጭቅጭቅ ጀመርኩ።
ገንዘብ ልጠይቀው የምችለው ብቸኛ ሰው በዛ ሰዓት ቢዬ ብቻ ነበረች። ደወልኩላት!! ከእናቷ ጋር ሲመጡ
ሳያቸው ላለማልቀስ ታገልኩ። ተኛ። ሆስፒታል እያደርኩ ፈተናዬን ተፈተንኩ።
ከሆስፒታል ሲወጣ ብር ስላልነበረኝ እናቴ ለሰርጌ የሰጠችኝን ወርቆች ሸጬ የሚደረገውን ሁሉ አደረግኩ። ሳድግ
እንዳየሁት ሰው ከታመመ በግ ይታረዳል:: ወግ ነው ብዬ በግ ገዝቼ አሳረድኩ:: (እራሴው እንባባባባ ብል ይሻለኝ
ነበር) ሲሻለው በቀረኝ ብር ለልጄ የሆነ የሆነ ነገር ገዝቼ ልጄጋ ሄድኩ። አንዳንዴ ምኑም አይገባኝም። ወርቆቼን
እንደሸጥኳቸው ሲያውቅ እኔ ለሱ ብዬ የምሄደው ርቀት ሳይሆን የታየው "ለምን አልነገርሽኝም" ብሎ መቀወጥ
ነበር። ደከመኝ። ልቤ ዛለ ...... የምር ደከመኝ። ..... ምን ባደርግ ደስተኛ እንደሚሆን አላውቅም:: ያስቆጣዋል
ብዬ የማስበው ነገር ምንም ሳይመስለው ያልፋል:: ጭራሽ ያልጠበቅኩት ነገር እብድ ያደርገዋል:: ክረምቱን
ልጄጋ ከሱ ተለይቼ አሳለፍኩ። እዛ እያለሁ ውጤት መጣ።
ውጤቴ መጣ። ከትምህርት ቤቱ ከፍተኛውን ውጤት አምጥቼ አለፍኩ። ቅብርር ያለ ውጤት አምጥቼ።
ውጤቴን ያየልኝ እሱ ነበር። በስልክ እየነገረኝ አላስጨረስኩትም ሳቅና ለቅሶዬ ተደባለቀብኝ። ነፍስ ዘራሁ
ነገር..... አለሁኝ አልኩ.... ለእናቴ ስነግራት እልልልልልልል አለች። አባቴ ውጤቴን ሲሰማ አቀፈኝ። በቃ ዝም ብሎ
ለደቂቃዎች አቀፈኝ። ምንም ሳይናገር ሁሉንም አለኝ። .... ልጄ ይህቺ ናት ያለ መሰለኝ...... ኮራሁብሽ ያለ
መሰለኝ..... ከዛ በኃላ ምንም ዳገት የሚወጣ አቅም እንዳለኝ አመንኩ:: .... ትችያለሽ አልኳት ራሴን!!!
የዛኔ ልክ ውጤት ሲመጣ ነበር የትምህርት ምርጫችንን የምንሞላው።
"አባ በቃ ሙላልኝ እና አስገባ!" አልኩት ምክንያቱም የትና ምን እንደምፈልግ ያውቀዋል። እኔን የሚያውቀኝ
በሙሉ ያውቃል ህግ መማር እንደምፈልግ። ከተማ የመጀመሪያ ምርጫ ሀዋሳ ሁለተኛ አዲስ አበባ
ወደ እሱጋ ተመልሼ መጣሁ:: አቃቤ ህግ ነሽ ወንጀለኛ መቅጫ ብቻ ሊጠቅመኝ ይችላል ብዬ የማስበውን
በሙሉ መፅሃፍ ከላይብረሪ እያወጣሁ ማንበብ ሆነ ስራዬ እዚህ ወቅት ላይ ምንም ተጨማሪ ፈጣሪዬን
የምጠይቀው ነገር አልነበረኝም።
አዳራሽ ውስጥ ተቀምጠን በፕላዝማ ምድባችን ሲነገር ስሜ ብቅ አለ አርባምንጭ ዩንቨርስቲ FBE Faculty
...... ተማሪው አብሮኝ “WHAT?” አለ.... ዓይኔን ማመን አቃተኝ...
እግሬ እንዴት እየረገጠልኝ እቤት እንደደረስኩ አላውቅም። ለመጀመሪያ ጊዜ እሱ ከልቤ ግምስ ሲል ታወቀኝ።
ለመጀመሪያ ጊዜ ልለየው እንደምችል አሰብኩ። በቃ ለመጀመሪያ ጊዜ ሞልቶ ከጠበበው ልቤ ሲቀነስ ታወቀኝ።
"እንኳን ደስ ያለህ እዚሁ ነው የደረሰኝ" አልኩት ማታ ሲመጣ
"እማ እርቀሽኝ እንድትሄጂ ስላልፈለግኩ ነው። ....ስለማፈቅርሽ አንቺን ላለማጣት ......." እንባው ለመጀመሪያ
ጊዜ የማንም ሰው እንባ ዓይነት ሆነብኝ።
"አላሳዝንህም? ቢያንስ ህግ እንደምማር አምኜ ያን ሁላ መፅሃፍ በፍቅር ሳነብ 'እማ ተይ የሞላሁልሽ ሌላ ነገር
ነው እንዲህ አትልፊ አትለኝም?' ልቤ እንደሚሰበር መገመት ከባድ ነበር? አላሳዝንህም? የ5ተኛ ክፍል
አስተማሪዬ እንኳንኮ ህግ መማር እንደምፈልግ ያውቃል። እንዴት አንተ ከአይንህ እንዳታጣኝ ህልሜን
ትቀማኛለህ? እስቲ ራስህን ጠይቅ የእውነት ትወደኛለህ? እኔስ ራሴን ነጥቀኸኝ... ህልሜን ነጥቀኸኝ ... ከዛም
ዝም ብዬ ማፍቀሬን ልቀጥል?"
......
.....
.....
................ አልጨረስንም.................
ሁለቱን ባሎቼን ላስማማ እያሸማገልኳቸው ነው
(ክፍል ስምንት)
'ጊቢ ግቡ' እስኪባል ድረስ ምን መወሰን እንዳለብኝ ግራ ገባኝ። ማንም FBE በLAW እንደማይቀይረኝ
እያወቅኩ ሞከርኩ። ላለመማርም አስቤያለሁ። ከዛ ልጄን ይዤ የሆነ ቦታ እልም ብዬ መጥፋት ....... ማንም
የማያውቀኝ ቦታ ሄጄ ከዜሮ መጀመር። በእኔ እልህ ልጄን ማስከፈል የማይታሰብ ነው። እጅ መስጠትም
ምርጫዬ አልሆነም። ልክ ጊቢ ግቡ ሲባል አሁንም አቧራዬን አራግፌ ተነሳሁ ....... እማራለሁ ........ ጥሩ ውጤት
አመጣለሁ ..... ለሚጠብቀኝ ሁሉ ኩራት እሆናለሁ ...... ከማንም በላይ ራሴን እና ልጄን አኮራለሁ ........ ቀና
ብላ የምትሄድ ሴት እሆናለሁ ....... ህይወቴን ሳሸንፍ የሆነ ቀን ህግ እማራለሁ። ራሴን ሳፅናና "ያውም ህግ
መማር የምፈልገው ወንጀል ነክ መፅሃፎች ለመፃፍኣ? እደርስበታለሁ"
እሱን? ግራ ቂጡን ትወጋዋለች ብላችሁ ነው የምትጠብቁትኣ? አልገባችሁም ግራ ቂጤ እስኪጨስ
እንደማፈቅረው።
"አምላክ ሆይ እባክህ ለሱ ያለኝን ፍቅር ውሰድልኝ አልችልም ብዙ ነው" ብዬ የምፀልይ ሰገጥ እንደሆንኩ
አልገባችሁም። በዚህ ሁሉ ውስጥ እንዴት እንደምወደው ቢያውቅልኝና ድሮ እንደማውቀው 'እሱ' ፍቅራችንን
ብንኖረው ስለቴ እንደሆነ አልገባችሁም። በዚህ ሁሉ ውስጥ ለነገ አብሮ ኑሮኣችን መሰረት ይሆነናል ብዬ ከወር
ደሞዙ ላይ የሚከፈል መሬት በሊዝ እንደዳስገዛሁት አታውቁማ (ለዛዛ በሉኝ ስትፈልጉ።)
እናም ተውኩለት "ይቅር ብዬሃለሁ" አልኩት "ካንተ አይበልጥብኝም!" አልኩት በአዋቂ ደንብ ቁጭ ብለን
አወራን (እኔ 20 ዓመቴ እሱ 25 ነበርን ይሄ ሲሆን ለሚያጠፋቸው ጥፋቶች ለራሴ ከምሰጠው ምክንያት አንዱ
'ስላልበሰለ ነው ወደፊት እንዲህ አይሆንም' የምለው ነገርስ? የሆነች አሮጊት ሴትዬማ ውስጤ ነበረች )
"ይሄን ማሪኝና ሁን ያልሽኝን ልሁን" አለኝ። ከዛም እሱም የማታ ኢኮኖሚክስ MA ሊማር ተመዘገበ።
ጊቢ የገባሁ ቀን አብሮኝ ሄደ። ከዘበኛው የጀመረ በጋሞኛ ሰላምታ እየሰጠ ሚስቱ መሆኔን አበክሮ እየነገረ።
ፕሮክተር ነሽ ወጥ ቤት ያልዞረበት የለውም እጄን ይዞ ....... እንዴት እንደሚያወራ ያውቅበታል። ስቆ አያውቅም
የሚባል ሰፊ ፊት ማስፈታት ያውቅበታል።
"ባልሽ ግን 'የሜሪ ባል ነኝ' እያለ ራሱን የሚያስተዋውቀው ማነሽ ብሎ ነው የሚያምነው ሴሌብሪቲ ነው እንዴ
የምትመስዪው?" ብሎኛል አንዱ የአርክ ተማሪ 'ሚስቴ ናት' ሲል ኩራቱን አይቶት .....
አብረን ዶርም ድረስ ሄድን:: አልጋዬን አንጥፎልኝ። ዶርሚተሪዎቼን ተዋውቆ ሲያስቀን ቆይቶ ወደቤት ተመለሰ።
"ወንድምሽ ነው?" ሲሉኝ የምበሳጨው መበሳጨት
"ባሌ ነው። የልጄ አባት እሺ" እላለሁ:: በነገታው አዳዲስ ልብሶች ገዝቶልኝ መጣ። ግራ ገባኝ ምክንያቱም ብር
እንደሌለው አውቃለሁ። ከሁለት ቀን በኋላ እቤት ስሄድ ቴሌብዥኑን እንደሸጠው አየሁ። እኔ እንደሱ 'አልበላ
አልጠጣ ብዬ የገዛሁትን ...... እንዴት አትነግረኝም' አላልኩም:: ዶርም የገባሁ ቀን ቱታ እንደለበስኩ ነው
የሄድኩት ሴቶቹ ዘንጠው ሲያያቸው ሚስቴ ከነሱ አትነስብኝ ብሎ እንዳደረገው ገብቶኛል አቅፌው አለቀስኩ
ብዙ እንደምወደው ነገርኩት.....
እኔ የሀብታም ልጅ አይደለሁም። ግን ቤተሰቦቼ ባላቸው አቅብጠውኝ ነው ያደግኩት። እሱን እስካገባሁበት
ሰዓት ድረስ እግሬን ሰራተኛ ያጥበኝ ነበር። ሀብታሞች የሚማሩበት የግል ትምህርት ቤት ነው የተማርኩት። ይሄ
ሁሉ ሆኖ ካነበብኳቸውም መፅሃፍት ሆነ መፅሃፍ ቅዱስ ከሚታየው የላይ ለውጥ ራሴን ውስጤን ስለመቀየር
እንድጨነቅ ነው አብዝቼ የተማርኩት። ልብስና እህል በፍፁም ብርቄ አይደሉም። ስለእውነቱ ከእኩዮቼ በተሻለ
የምፈልገውን በእድሜዬ አጊጫለሁ። እዛ እድሜዬ ላይ ቁሳቁስ የሚያሳስበኝ ሴት አልነበርኩም። ሀብት ካፈራሁ
የምመኘው ከእርሱ ጋር ስለምናፈራው ሀብትና እኔና እሱ ከልጆቻችን ጋር ስለምንኖረው ድሎት እንጂ ጊቢ
እገሊት የለበሰችው ቀሚስ ግድ የሚሰጠኝ ሴት አልነበርኩም። ለእሱ ግን ለእኔ የሚያስፈልገኝን አለማሟላት
ሞቱ ነበር። የቤተሰቤ ቤት የሚናፍቀኝ ...... የማያቸው ሰዎች የሚያስቀኑኝ ይመስለው ነበር ....... ላስረዳው
ይቸግረኛል።
ተማሪዎቹ ስልክ ስለነበራቸው የሱን ስልክ ለእኔ ሰጠኝ። 'ስትናፍቂኝ እኔ መጥቼ አይሻለሁ ስልክ እኔ ምንም
አያደርግልኝም' አለኝ ስለእውነቱ ለእኔ ከሚያደርግልኝ በላይ ለእርሱ ያደርግለት ነበር።
አንደኛ ሴሚስተር አርባምንጭ ተማሪ በማባረር አንደኛ ነው ብለው አስፈራርተውኝ ስለነበር ድምፄን አጥፍቼ
ትምህርት ላይ አደፈጥኩ። ያው በሳምንት ብዙውን ቀን ነው እሱጋ የማድረው ዶርም ያደርኩ ቀን ደግሞ
ስለእርሱ እያወራሁ ሳደነቁራቸው አድራለሁ። እሱም በሳምንት ብዙውን ቀን ትምህርት ቤት ጊቢ ይመጣል።
ማታ ከክላስ መልስ ጊቢ ውስጥ አቅፎኝ ሲንጎራደድ ትምህርት ቤቱን የገዛ ባለሃብት ነው የሚመስለው።
የሚያየን ሁላ ታድለሽ ባልሽ ደስ ሲል እንዲህ ዓይነት ባል ቢኖረኝ' የማይቀናብኝ የለም።
ነፃነቴን በሆነ መልኩ እንደያዘው ባውቅም አልጎረበጠኝም። ለምሳሌ ከጠዋት እስከማታ የለበስኩትን ያገሳሁትን
የበላሁትን የሄድኩበትን የፈሳሁትን ፈስ ቁጥር ልክ የሚነግሩት ሰዎች አሉት። አውቃለሁ። ከእሱ ተደብቄ
የማደርገው ነገር ስላልነበረ ግድ የለኝም። ቢበዛ 'ዛሬ ለብሰሽ የነበረው ቦዲ ግን አልሳሳም? ደረብ አታደርጊም?'
ቢለኝ ነው። ወይም ከጓደኞቼጋ ሻይ ልንጠጣ ወደከተማ ስንወጣ ከየት መጣ ሳንለው ዱብ ብሎ ሰላም ብሎን
ይሄዳል። ወይም ስንጨርስ 'ባልሽ ሂሳብ ከፍሎላችሁ ነው የሄደው' እንባላለን ሳናየው
"ይሄ መንፈስ የሆነ ባልሽ ትከሻዬ ላይ ዱብ እንዳይል" ይሉኛል ጓደኞቼ ሙድ ሲይዙ የሆነ ቦታ ስንሄድ
ደስተኛ ሆንኩ። ደሞኮ ብዙ የማልፈጀው ነገሬ ..... በቃ ደስተኛ አደረገኝ ...... የመጀመሪያ ሴሚስተር ውጤት
መጣ። ሁሉንም ትምህርት A ሳመጣ ካልኩለስ B አመጣሁ። ካልኩለስ አስተማሪያችን ሴት ናት (ይሄን ፅሁፍ
አታየውም ብዬ ተስፋ ላድርግ) ቂጧ ትልቅ የሚያምር ...... ስታስተምረን ፊቷን አዙራ አዳሜ ይቸክልና ልክ
ስትዞር ሁሉም በልቡ ኤጭ የሚል አይነት ይመስለኛል። ያልሰራሁት ጥያቄ በጣም ቀላሉን ስለነበር በዛ ላይ ሴት
መሆኔ በዛ ላይ ሌሎቹን በሙሉ A ማምጣቴ ይመስለኛል ቢሮ አስጠራችኝ።
"ከባዱን ሰርተሽ ቀላሉን ነው

You might also like