Download as pdf or txt
Download as pdf or txt
You are on page 1of 99

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ

የማኀበራዊ ሳይንስና ስነሰብዕ ኮሌጅ

የኢትዮጵያ ቋንቋ(ዎች)እና ስነጽሑፍ- አማርኛ ትምህርት ክፍል

የድኅረምረቃ መርሐግብር

የአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ከመርሃ ትምህርቱ ጋር


ያላቸውን ዝምድና ፍተሻ

በልስቲ ጫኔ

መስከረም 2013 ዓ.ም


ጎንደር
የአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ከመርሃ ትምህርቱ ጋር
ያላቸውን ዝምድና ፍተሻ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ
ማኀበራዊ ሳይንስና ስነሰብዕ ኮሌጅ

የኢትዮጵያ ቋንቋ (ዎች)ና ስነጽሑፍ- አማርኛ ትምህርት ክፍል

የድኀረምረቃ መርሐግብር

በተግባራዊ ስነ ልሳን አማርኛን ለማስተማር የማስተርስ ዲግሪ የቀረበ ማሟያ ጥናት

በልስቲ ጫኔ

የጥናቱ አማካሪ

አስቴር አስራት (ዶ/ር)

መስከረም 2013 ዓ.ም

ጎንደር
2
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ

ማኀበራዊ ሳይንስ ና ስነሰብዕ ኮሌጅ

የኢትዮጵያ ቋንቋ (ዎች)ና ስነጽሑፍ- አማርኛ ትምህርት ክፍል

የድኀረምረቃ መርሐግብር

የአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ከመርሃ ትምህርቱ ጋር ያላቸውን ዝምድና
ፍተሻ በሚል ርዕስ በተግባራዊ ሥነልሳን አማርኛን ለማስተማር የማስተርስ ዲግሪ ማሟያ
በበልስቲ ጫኔ የቀረበው ይህ ጥናት የዩኒቨርሲቲውን የጥራትና የወጥነት መስፈርት ስለማሟላቱ
በፈታኞች ተረጋግጦ ተፈርሟል፡፡

የፈተና ቦርድ አባላት

አማካሪ ----------------------------------------- ፊርማ ---------------------- ቀን --------------------

ፈታኝ ------------------------------------------- ፊርማ ----------------------- ቀን --------------------

ፈታኝ ------------------------------------------- ፊርማ ----------------------- ቀን…………………


ማረጋገጫ

የአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ከመርሃ ትምህርቱ ጋር ያላቸውን ዝምድና
ፍተሻ በሚል ርዕስ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ ማህበራዊ ሳይንስና ስነሰብዕ ኮሌጅ የኢትዮጵያ ቋንቋ
(ዎች)እና ሥነጽሑፍ-አማርኛ ትምህርት ክፍል በተግባራዊ ስነልሳን አማርኛን ለማስተማር
ለኤም.ኤ ዲግሪ ማሟያ ያቀረብኩት ይህ ጥናት ከዚህ በፊት በማንኛውም አካል ያልተሠራ የራሴ
ወጥ ሥራ መሆኑንና የተጠቀምኩባቸው ድርሳናትም በትክክል ዋቢዎች የተደረጉና ጎንደር
ዩኒቨርሲቲም የጥናቱ ህጋዊ የባለቤትነት መብት ያለው መሆኑን በፊርማዬ አረጋግጣለሁ፡፡

ስም --------------------------------------------------------------

ፊርማ -----------------------------------------------------------

ቀን ---------------------------------------------------------------
ምስጋና
በመጀመሪያ ይህ ጥናት ከዚህ እንዲደርስ ጤናውንና ብርታቱን ሰጥቶ አነሳስቶ ላስጀመረኝ
አስጀምሮ በሰላም ላስፈፀመኝ ልዑል እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይገባዋል፡፡

በመቀጠል የተጀመረው ጥናት እዚህ እንዲደርስ በአካልም ሆነ በስልክ እንዲሁም በኢሜል


ከትልመ ጥናቱ ጀምረው ዋናው ጥናት እሰኪጠናቀቅ የጥናቱን እያንዳንዱን ምዕራፍ በማንበብ
እርማት የሚያስፈልጋቸውን የቃላት፣ የሓረጋት፣ የሓሳብ፣ የሰዋሰው እና የፊደል ግድፈት
ለጠቆሙኝ እና አስተያየት ለሰጡኝ ዶ/ር አስቴር አስራት ከልብ አመሰግናለሁ፡፡ እንዲሁም የጎንደር
ዩኒቨርስቲ የጥናቱን ባጀት በመመደብ ምርምሩ ከዳር እንዲደርስ አስፈላጊውን ትብብር ያደረገልኝ
በመሆኑ ምስጋናየ ከልብ ነው፡፡ ጥናቱን መስራት ከጀመርኩበት ጊዜ አንስቶ ከዚህ ደረጃ
እስከበቃበት ድረስ ከፍተኛ ሞራል ለሰጡኝ እና የበኩላቸውን ድጋፍ ላደረጉልኝ ለባለቤቴ ብርሃን
ግዛ ከልብ አመሰግናለሁ፡፡ ጊዜያችሁን መሰዋዕት አድርጋችሁ ረቂቁን በማንበብ መልካም
አስተያየት ለለገሳችሁኝ የስራ ባልደረቦቼ ከልብ የመነጨ ምስጋናየ ይድረሳችሁ፡፡ ለዚህ ጥናት
መሳካት አስፈላጊውን መረጃ በመስጠት ለተባበሩኝ አባይ ምንጭ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
የሚያስተምሩ የአማርኛ ቋንቋ መምህራን እና የቋንቋ ትምህርት ይዘቶችን በመመደብ እገዛ
ያደረጋችሁልኝ መ/ርት የሽ ብርሐን፣መ/ርት አንችናሉ መዝገቡእና መ/ር ወርቅነህ ደሳለው የአባይ
ምንጭ ከፍተኛ ሁለተኛ እና መሰናዶ ትምህርት ቤት የአማርኛ ቋንቋ መምህራንን ከልብ
አመሰግናለሁ፡፡ እንዲሁም ከጎኔ በመሆን ጽሁፉን እና እርማቱን ለአስተካከሉልኝ ውድ ወንድሞቼ
አባትሁን ጫኔ እና ጌታቸው አያሌው አንዲሁም ለጓደኞቼና ለቤተሰቦቼ በሙሉ የከበረ ምስጋናዬን
ከልብ አቀርባለሁ፡፡

i
ማውጫ
ይዘት ገጽ

ምስጋና i
የሰንጠረዥ ማውጫ ....................................................................................................... vi
አህጽሮተ ጥናት ........................................................................................................... vii
ምዕራፍ አንድ፤መግቢያ ...................................................................................................1
1.1 የጥናቱ ዳራ .................................................................................................................................... 1
1.2 የጥናቱ አነሳሽ ምክንያት ................................................................................................................ 5
1.3 የጥናቱ ዓላማ ................................................................................................................................. 7
1.4 የጥናቱ አስፈላጊነት ............................................................................................................................... 8
1.5 የጥናቱ ወሰን ......................................................................................................................................... 9
1.6 የጥናቱ ውስንነት ................................................................................................................................... 9
1.7 የጥንቱ ቁልፍ ቃላት እና ሃረጋት....................................................................................................... 10

ምዕራፍ ሁለት፤ክለሳ ድርሳናት ...................................................................................... 10


2.1 የመርሃ ትምህርት ምንነት.................................................................................................................. 10
2.1.1 የመርሀ ትምህርት ባህሪያት ............................................................................................................ 12
2.1. 2 የመርሃ ትምህርት ዓላማ ............................................................................................................... 13
2.1.3 የመርሀ ትምህርት ይዘት አመራረጥ ............................................................................................... 14
2.2 የቋንቋ መማሪያ መፅሃፍ ምንነት ................................................................................................ 15
2.2.1 የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍትት ውስጣዊ ይዘት ................................................................................ 16
2.2.2 የቋንቋ መማሪያ መጻህፍት አዘገጃጀት............................................................................................. 17
2.3 የቋንቋ ትምህርት ይዘቶች አደረጃጀት ................................................................................................. 19
2.3.1 ተከታታይነት (Continuity) .............................................................................................................. 21
2.3.2 ተለጣጣቂነት (Sequence) ................................................................................................................. 23
2.3.3 ውህድነት (Integration) .................................................................................................................... 24
2.4 የክሂሎችና የችሎታዎች አደረጃጀት እና አቀራረብ............................................................................. 25
2.4.1 የክሂሎች አደረጃጀት እና አቀራረብ.................................................................................................. 25
2.4.1.1 የማዳመጥ የክሂል አደረጃጀት እና አቀራረብ ............................................................................... 26

ii
2.4.1.2 የመናገር የክሂል አደረጃጀት እና አቀራረብ .................................................................................... 28
2.4.1.3 የንባብ ክሂል አደረጃጀት እና አቀራረብ .......................................................................................... 29
2.4.1.4 የፅህፈት ክሂል አደረጃጀት እና አቀራረብ ...................................................................................... 30
2.4.2 የችሎታዎች አደረጃጀት እና አቀራረብ ............................................................................................ 32
2.4.2.1 የሰዋስው ትምህርት አደረጃጀት እና አቀራረብ............................................................................. 32
2.4.2.2 የስነፅሁፍ ትምህርት አደረጃጀት እና አቀራረብ ........................................................................... 35
2.5 በመማሪያ መፅሓፍ ውስጥ የምዘና ተግባራት .................................................................................... 35
2.6 የቋንቋ መርሃ ትምህርትና የመማሪያ መፅሃፍ ዝምድና.................................................................... 36
2.7 የቀደምት ጥናቶች ቅኝት ..................................................................................................................... 37

ምዕራፍ ሦስት፤የጥናቱ ንድፍና ዘዴ ............................................................................... 40


3.1 የጥናቱ ንድፍ ............................................................................................................................... 40
3.2. የመረጃ ምንጭ ................................................................................................................................... 40
3.3. የናሙና አመራረጥ ስልት .................................................................................................................. 40
3.4 የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎች ......................................................................................................... 41
3.4.1 ሰነድ ፍተሻ ....................................................................................................................................... 41
3.5 የመረጃ አተናተን ዘዴ.......................................................................................................................... 42

ምዕራፍ አራት፤የመረጃ ትንተናና የውጤት ማብራሪያ ...................................................... 43


4.1 የመረጃ ትንተና .................................................................................................................................... 43
4.2 የውጤት ማብራሪያ ............................................................................................................................. 52

ምዕራፍ አምስት፤ማጠቃለያ፣መደምደሚያና አስተያየት ..................................................... 55


5.1 ማጠቃለያ ............................................................................................................................................. 55
5.2 መደምደሚያ ........................................................................................................................................ 57
5.3 አስተያየት............................................................................................................................................. 58

ዋቢ ፅሁፎች ................................................................................................................ 59
አባሪዎች ..................................................................................................................... 64
አባሪ አንድ፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን
የአንብቦ መረዳት ይዘቶች ............................................................................................................. 64
አባሪ ሁለት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ
ንዑሳን የመፃፍ ይዘቶች ................................................................................................................ 65
አባሪ ሦስት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ
ንዑሳን የማዳመጥ ይዘቶች ........................................................................................................... 66

iii
አባሪ አራት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ
ንዑሳን የመናገር ይዘቶች.............................................................................................................. 67
አባሪ አምስት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ
የቀረቡ ንዑሳን የሰዋስው ይዘቶች ................................................................................................ 68
አባሪ ስድስት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ
ንዑሳን የስነፅሁፍ ይዘቶች............................................................................................................ 69
አባሪ ሰባት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን
የምንባብ ይዘቶ የቀረቡበት ዘዴ.................................................................................................... 70
አባሪ ስምንት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ
ንዑሳን የመፃፍ ይዘቶችየቀረቡበት ዘዴ ........................................................................................ 71
አባሪ ዘጠኝ፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ
ንዑሳን የመናገር ይዘቶችየቀረቡበት ዘዴ .................................................................................... 72
አባሪ አስር፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ
ንዑሳን የማዳመጥ ይዘቶችንየቀረቡበት ዘዴ ................................................................................ 73
አባሪ አስራ አንድ፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ
የቀረቡ ንዑሳን የሰወሰውአውቀት ይዘቶች የቀረቡበት ዘዴ ......................................................... 74
አባሪ አስራ ሁለት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ
የቀረቡ ንዑሳን የስነፅሑፍእውቀት ይዘቶች የቀረቡበት ዘዴ ....................................................... 75
አባሪ አስራ ሦስት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍ በየምዕራፉ
የቀረቡ ንዑሳን የአንብቦመረዳት ይዘቶች ...................................................................................... 76
አባሪ አስራ አራት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍ በየምዕራፉ
የቀረቡ ንዑሳን የመፃፍ ይዘቶች ................................................................................................... 77
አባሪ አስራ አምስት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ እና በእንግዝኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍ በየምዕራፉ
የቀረቡ ንዑሳን የማዳመጥይዘቶች ................................................................................................ 78
አስራ ስድስት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍ በየምዕራፉ የቀረቡ
ንዑሳን የመናገር ይዘቶች.............................................................................................................. 79
አባሪ አስራ ሰባት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍ በየምዕራፉ የቀረቡ
ንዑሳን የሰዋስው ይዘቶች.................................................................................................................... 80
አባሪ አስራ ስምንት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ እና በእንግሊዝ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍ በየምዕራፉ የቀረቡ
ንዑሳን የስነፅሁፍይዘቶች .................................................................................................................... 81
አባሪ አስራ ዘጠኝ ፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃ ትምህርቱ በየምዕራፉ
የቀረቡ ንዑሳን የምንባብለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች .................................................................... 84
አባሪ ሃያ ፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃ ትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ
ንዑሳን የመፃፍለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች................................................................................... 85

iv
አባሪ ሃያ አንድ፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃ ትምህርቱ በየምዕራፉ
የቀረቡ ንዑሳን የመናገርለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች .................................................................... 86
አባሪ ሃያ ሁለት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍ እና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ
የቀረቡ ንዑሳን የማዳመጥለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች ................................................................. 87
አባሪ ሃያ ሦስት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ
የቀረቡ ንዑሳን የሰወሰውእውቀት ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች .................................................... 88
አባሪ ሃያ አራት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መራሃትምህርቱ በየምዕራፉ
የቀረቡ ንዑሳን የስነፅሑፍእውቀት ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች .................................................. 89

v
የሰንጠረዥ ማውጫ

ሰንጠረዥ 4.1. በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሃፍ እና በመርሃ ትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ
የክሂል እና የእውቀት ዘርፎች ………………………………………………. 44
ሰንጠረዥ 4.2. የአማርኛ መማሪያ መፃሕፍቱ እና የመርሃ ትምህርቱ ይዘቶች የተማሪዎችን
የመማር ሁኔታ ወይም ዳራዊ እውቀት ያገናዘቡ ስለመሆናቸው ------------..46
ሰንጠረዥ 4.3. በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሃፍ እና በመርሃ ትምህርቱ
በየምዕራፉ የቀረቡ የክሂልና የእውቀት ዘርፎች ተከታታይንት ዝምድና...... 47
ሰንጠረዥ 4.4. በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሃፍ እና በመርሃ ትምህርቱ
የክሂልና የእውቀት ዘርፎች ተለጣጣቂነት ዝምድና ………………………. 48
ሰንጠረዥ 4.5. በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሃፍ ያለው የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት
ውህዳዊነት የዝምድና ……………………………………………………... 50
ሰንጠረዥ 4.6. በአስረኛእና አስራአንደኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሃፍ የክሂልና
የእውቀት ዘርፎች ዝምድና ………………………………………………… 51
ሰንጠረዥ 4.7 በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት በመርሃ ትምህርቱ ውስጥ
ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች ያላቸውን የዝምድና ……………………... 52

vi
አህጽሮተ ጥናት
የዚህ ጥናት ዋና አላማ በ2004 ዓ.ም በአንደኛ እትም ታትመው በአሁኑ ወቅት ሥራ ላይ ያሉትን የአስረኛ
ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና መርሀ ትምህርቱ ያላቸውን ዝምድና በመፈተሽ ላይ ያተኮረ
ነው፡፡ የጥናቱን ዋና አላማ ከግብ ለማድረስ አጥኚው በሰነድ ፍተሻ በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ
መማሪያ መፃሕፍት እና በመርሃ ትምህርቱ መካከል ያለውን የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት አደረጃጀት
እና ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎችን በአይነታዊ እና መጠናዊ ዘዴዎች ተንትኖ አቀርቧል፡፡ ይህን ዓላማ
ከግብ ለማድረስ ተዛምዷዊ የምርምር ንድፍ ተግባራዊ ሁኗል፡፡ እንዲሁም አላማ ተኮር የናሙና ዘዴን
በመከተል በአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍትእና በመርሀ ትምህርቱ ላይ አተኩሯል፡፡
በሰነድ ፍተሻ አማካኝነት ከናሙናው የተሰበሰበው መረጃ ተደራጅቶ በፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት
የተዝምዶ መለኪያ በመጠቀም ተተንትኗል፡፡በጥናቱ ውጤት መሰረት የአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ
መማሪያ መፃህፍት ከመርሃ ትምህርቱ ጋር የይዘት ተከታታይነት ዝምድና እንዳለው ታይቷል፡፡
በመማሪያ መፅሃፉም ይሁን በመርሐ ትምህርቱ የተለያዩ ምዕራፎች ላይ የቀረቡ ይዘቶች የተማሪዎችን
የመማር ሁኔታ ወይም ዳራዊ እውቀት ጠብቀው የቀረቡ ናቸው፡፡ መማሪያ መፃህፍቱ ከመርሐ ትምህርቱ
ጋር ያለው የይዘት ተከታታይነት የዝምድና መጠን በስታትስቲክስ ትንተናው 0.98 በመሆኑ በአዎንታዊ
አቅጣጫ በጣም ከፍተኛ የተዛምዶ መጠን እንዳለው ጥናቱ አረጋግጧል፡፡ ይሁን እንጅ በመርሐ ትምህርቱ
በሁሉም ምዕራፎች የቀረበው፣ ዝርዝር ሃሳብ መለየት በመማሪያ መፃሕፍቱ ምዕራፍ ሁለት እና ሦስት
አልተካተተም፡፡ በመቀጠልም በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃህፍትና በመርሃ ትምህርቱ
የይዘት ተለጣጣቂነት ተዛምዶ መመርመር ነበር፡፡ መማሪያ መፃህፍት ከመርሃ ትምህርቱ ጋር ያለው
የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት ተለጣጣቂነት የዝምድና መጠን በስታትስቲክስ ትንተናው 0.91
በመሆኑ በአዎንታዊ አቅጣጫ በጣም ከፍተኛ የተዛምዶ መጠን እንዳለው ውጤቱ አሳይቷል፡፡ እንዲሁም
በአስረኛ ክፍል በአማርኛእና እንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ መፃህፍት መካከል ያለው የክሂሎችና የእውቀት
ዘርፎች የይዘት ውህዳዊነት ተዛምዶ የተመረመረ ሲሆን የዝምድና መጠኑ በስታትስቲክስ ትንተናው
0.84 በመሆኑ በአዎንታዊ አቅጣጫ በጣም ከፍተኛ የዝምድና መጠን እንዳለው ጥናቱ አረጋግጧል፡፡ የዚህ
ጥናት የመጨረሻው ጉዳይ በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍትና በመርሃ ትምህርቱ
ውስጥ ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች ያላቸውን ዝምድና መፈተሸ ሲሆን በዚሁ መማሪያ መፃሕፍት እና
በመርሃ ትምህርቱ ውስጥ ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች የዝምድና መጠን በስታትስቲክስ ትንተናው
0.99 በመሆኑ በአዎንታዊ አቅጣጫ በጣም ከፍተኛ የተዛምዶ መጠን እንዳለው ውጤቱ አሳይቷል፡፡
በጥናቱ ግኝት ላይ በመመስረት የመፍትሄ ሓሳቦች የተጠቆሙ ሲሆን መፃሕፍት አዘጋጆች በቀጣይ የቋንቋ
መማሪያ መፃሕፍት ሲያዘጋጁ ሙሉ በሙሉ ከመርሐ ትምህርቱ ጋር ዝምድና እንዲኖረው ይጠበቃል፡፡

vii
ምዕራፍ አንድ፤መግቢያ
1.1 የጥናቱ ዳራ
የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት አጠቃላይ ዓላማዎች የተማሪዎችን የማዳመጥ፣የመናገር፣ የማንበብ
እና የመፃፍ ክሂሎች ማጎልበት እና የሥነፅሑፍና የሥነልሳን እውቀት ማዳበር ናቸው፡፡ እነዚህ
ዓላማዎች እንዲሳኩ የይዘት መረጣ፣አደረጃጀትእና አቀራረብ በመርሐ ትምህርቱ እና በመማሪያ
መፃሕፍቱ ተዛምደው በግልፅ መስፈር አለባቸው፡፡

Yalden (1987)፣ Dubin and Olishtain(1986)እና Ur (1996) አገላለፅ መርሃ ትምህርት በውሥጡ
የትምህርቱን አይነት አስመልክቶ የሚቀርቡትን አላማዎች፣ ይዘቶች፣ መረጃ መሣሪያዎችና
የምዘና ሥልቶችን በማካተት ሥርዓት ባለው መንገድ ተቀነባብሮ የሚቀርብእና ለመማር
ማሥተማሩ የተዘጋጀ የትምህርት ፕሮግራም ነው፡፡ በተጨማሪም ታላሚው አካል ወይም
ተማሪው ከአካባቢው የሚያገኘውን የሕይወት ልምድና እውቀት በመጠቀም የባሕርይ ለውጥ
እንዲያመጣ በተወሠነ ቦታና ጊዜ የሚሠራበት የትምህርት እቅድ ነው፡፡ Nunan(1988) Widdowson
(1984)ን ጠቅሰው እንደገለፁት መርሀ ትምህርት መማርን የሚያፋጥን የማሥተማረያ መሣሪያ
እንዲሁም ክንውኖች የሚካሄዱበት ማዕቀፍ ነው፡፡ ከአጠቃላይ ሥርዓተ ትምህርት የሚመነጭ
በየትምህርት አይነቶች የሚቀርቡ ይዘቶችን አካቶ የሚያዝ ሠነድ ነው፡፡ መርሀ ትምህርት የተለያዩ
የትምህርት አይነቶችን ለማቀድ እንደመሠረት ሆኖ የሚያገለግል የይዘቶች ሀተታ ነው፡፡ ቋንቋን
በመማር ማሥተማር ረገድ መምህራንና ተማሪዎች ግባቸውን ለማሣካት የሚመሩበት መማሪያ
መንገድ ነው፡፡ Prabhu (1987) እንደሚገልፁት መርሃ ትምህርት ለማስተማር የታሰበውን ነገር
መግለጫ ነው፡፡ ፍላጎት መለየት፣ የማስተማሪያ ዘዴዎችን መምረጥ፣ የመማሪያ መፃህፍት
ማዘጋጀት፣ የይዘት መረጣ፣ ቅደም ተከተሉንና ወሰኑን መለየት፣ የትግበራ እቅዱን በቅደም
ተከተል ማዘጋጀት፣ የማስተማሪያ መርጃ መሳሪያዎችእና አላማን ማስቀመጥ የመርሃ
ትምህርት አካላት ናቸው(Richarde 1990እና Taba1962)፡፡

ከላይ ከተነሱ ነጥቦች አኳያ የመርሃ ትምህርት አይነቶች በርካታ ናቸው፡፡በርካታ የመሆናቸው
ተጨማሪ ጉዳይም ቋንቋን ለማስተማሪያነት ተብለው የሚነደፉት መርሃ ትምህርቶች
ከሚኖራቸው የትኩረት አቅጣጫ፣ከሚዘጋጅለት ተማሪ የእውቀት ደረጃና ዕድሜ፣
ከሚያከትቱት ይዘትና አዘጋጆቹ ከሚከተሉት የትምህርት ስልት አኳያ ነው፡፡ዋና ዋናዎቹም

1
መዋቅራዊ፣ ክሂልዊ፣ ሁኔታዊ፣ርእሳዊ፣ አገልግሎታዊ፣ ቅደም ተከተላዊ፣ ተግባራዊና እሳቤያዊ
መርሐ ትምህርት ናቸው(ur 1996፣ Nunan 1986፣ R:chards 2001፣ Dubin and olshtain 1986)::
Olishtain(2000) አገላለፅ መርሐ ትምህርት በቀጥታ ለመምህራን እና ተማሪዎች በአንድ
የትምህርት አይንት ወይም የአንድ ትምህርት ዓይነት ተከታታይ የመማሪያ መፃሕፍት
የሚዘረዝር ነው፡፡

Cunning worth (1989)የቋንቋ መማሪያ መፃሐፍት ለቋንቋ ትምህርት ዓላማ መሳካትና ለመማር
ማስተማር ሂደት አጋዥ የሆኑ መሳሪያዎችን የያዘ እንደሆነ ያስረዳሉ፡፡Richards and Rogers
(1996)' Sheldon (1987)ን ዋቢ በማድረግ•እንደሚያብራሩት የህብረተሰቡን የዕደገት ደረጃ፣የኑሮ
ሁኔታ፣ወግ፣ባህል፣ፍላጎት፣ምንነት ወዘተ.ግምት ውስጥ በማስገባት የሚዘጋጁ የቋንቋ መማሪያ
መፃሐፍት ከፍተኛ ጠቀሜታ ስለሚሰጡ አስፈላጊነታቸውን በአፅናኦት በመስጠት ገልፀዋል፡፡
Richards (1985)ደግሞ ሲያስረዱ የመማሪያ መፅሐፉ በመርሃ ትምህርቱ የገለፁትን ይዘቶች
አደራጅቶ የያዘ የማስተማሪያ ዘዴ ነው፡፡ በመማሪያ መፃሕፍት ውስጥ መስፈር ስላለባቸው ይዘቶች
አደረጃጀትና አቀራረብ የሚወስን በመሆኑም ለመማሪያ መፃሕፍት ዝግጅት መነሻ በመሆን
ሲያገለግል የመማሪያ መፅሐፉን በመርሃ ትምህርቱ የተካተቱት ዓላማዎች ግብ መምታት ወሳኝ
ሚና የሚጫወቱ ናቸው፡፡

የመማሪያ መፃሐፍትን ታሪካዊ ዳራ በመቃኘት የመፃሐፍት ዝግጅት አሁን ከደረሰበት ደረጃ


ለመድረስ የተለያዩ ጊዜያትንና ታሪኮችን አሳልፏል፡፡የጥንታዊ፣የሄለንሰተቲክ፣የጨለማው፣
የመካከለኛው፣የተሃድሶእና ዘመናዊ ዘመን ናቸውSheldon (1988):: የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት
ታሪካዊ ዳራ አመጣጥ በጥንታዊ ዘመን በግሪክና በሮም የሥልጣኔ ዘመን አብቦ ይታይ የነበረው
የፍልሥፍና፣ የሥነ-ፅሁፍ፣ የተፈጥሮ ሳይንስ እውቀት ዘርፍ መከሠት እንደተጀመረ ይነገራል፡፡
ከተጠቀሡት የእውቀት ዘርፎች ጋር በጥንታዊ መንገድ የግሪክና የላቲንን ቋንቋ በመደበኛ
ትምህርት ለወጣቶች ለማሥተማር እንዲቻል የሥነ-ፅሁፍና የሰዋሰው መፃሕፍት ተዘጋጅተዋል
(Hutchinson and Torres 1994)፡፡

የመማሪያ መፅሀፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በጥንታዊት ግሪክ፣ ቻይና፣ህንድ፣ግብፅና


ሌሎች ጥንታዊ ማህበረሰቦች ነው፡፡ ጀማሪው አርስቶትል ሲሆን የጀመረውም ቁጥር ነክ ወይም
ቁጥርን የሚወክሉ መፅሀፎችን በማዘጋጀት ነበር፡፡ በመሆኑም ከዚህ በፊት ታይተው የማይታወቁ
መማሪያ መፅሀፎች መታተም ጀመሩ፡፡ ነገር ግን በጣም አናሳ ከመሆናቸው የተነሳ ሀብታሞች
ብቻ የሚጠቀሙበት ቅርፁ በእጅ እንዲያዝ ሆኖ የተዘጋጀ ነበር፡፡የመፅሀፉ ይዘትም በላቲን ቋንቋ
2
መሰረታዊ ንባብንና ፅህፈትን ማስቻል ሲሆን ምንባቡ የሚዘጋጀውም ከመፅሀፍ ቅዱስ እና
እንደአማራጭም ከተወሰኑ ግጥሞች ነበር (Ells worth እና ሌሎች 1994)፡፡ Encyclopedia of
Education (2008 ) በካናዳ ቅኝ ግዛት ዘመን ከሀይማኖታዊ ታሪክ ጋር ባይዛመድም ልክ
እንደእውነት ያስተምሩበት እንደነበርና ዋና ጠቀሜታውም የትውልድ ቦታን ታሪክ ማሳመኛ እንደ
ነበር ይናገራሉ፡፡

Richards (2001) አገላለጽ የመማሪያ መጻህፍት በጣም አስፈላጊ የትምህርት ቁሳቁሶች እንደሆኑ
ይገልፃሉ፡፡ Dubbin & olishtain (1986) የተሰኙ ምሁራን ደግሞ ስለቋንቋ መማሪያ መፃህፍት
ጠቀሜታ የሚገልፁት እንደሚከተለው ነው፡፡ የቋንቋ መማሪያ መፃህፍት ተማሪውን ከታቀደው
የቋንቋ ትምህርት ጋር ያስተዋውቃሉ፡፡ የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት የተለያየ ርዕስ ለማስተማር
የሚረዱ መሳሪያዎችን፣ ቃለ ምልልሶችን፣ የማንበብና የማዳመጥ ክሂሎችን ለማዳበር የሚረዱ
ምንባቦችን፣ ትምህርቱን ለማጠናከር የሚያስችሉ መልመጃዎችንና ወደ ትግበራ ለመሸጋገር
የሚያስችሉ መንደርደሪያዎችን በማቅረብ ለመምህሩ ከፍተኛ እገዛ ያደርጋሉ፡፡ አንድ ክሂል
በሌላው ክሂል ላይ የተመሰረተ እንደመሆኑ መጠን የቋንቋ ክሂሎች ቅንጅት ሲጠብቅ የቋንቋ
ትምህርት አሰጣጡን ወደሚፈልገው ግብ ለማድረስ መንገድ ይከፍታል፡፡Cunnings worth (1995)
ሲገልፁ የቋንቋ መማሪያ መፅሀፍ ሰፊና በርካታ አገልግሎት አለው፡፡ ይኸውም የተለያዩ የቋንቋ
ግብዓቶችን ያቀርባል፡፡ተማሪዎች ተግባራዊ ልምምዶች እንዲያደርጉ እንደምንጭ ሆኖ ያገለግላል፡፡
በሰዋሰው፣ በመድበለ ቃላት፣ ንበት ወዘተ. ጥናት ላይ ለተማሪዎች እንደማገናዘቢያ
ያገለግላል፡፡በመረርሃ ትምህርት የተንፀባረቁትን መሰረተ ሀሳቦች በዝርዝር ያቀርባል፡፡የማስተማር
ብቃት ወይም የመምህሩ መምሪያ ለሌላቸው መምህራን ድጋፍ ይሰጣል፡፡

እንደ Grant (1987) ደግሞ የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት የተደራጁ፣ የተመጠኑና የተውጣጡ የቋንቋ
ትምህርት ይዘቶችን ከተማሪው አካባቢያዊና ዳራዊ እውቅት አንጻር አካቶ በመያዝ የተነደፉ የቋንቋ
ትምህርት አላማዎችን ከግብ ለማድረስ የተዘጋጁ ሠነዶች እንደሆኑ ይገልፃሉ፡፡ Hutchinson &
Torres (1994) እንዳስቀመጡት የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ከአንድ ትምህርት ተቋም
እስከተጠቃሚው ሕብረተሠብ ድረስ ያለውን የቋንቋ ትምህርት ሂደት እና የትምህርት ፍላጎት
ምላሽ ለመሥጠት ከትምህርት ፖሊሲ፣ ከሥርዓተ ትምህርት እና መርሀ ትምህርቱ የተቀረፁ
ይዘቶችን በማጣጣም በሙያው በተሠለፉ ባለሞያዎች የሚዘጋጁ ለቋንቋ ትምህርት አላማ ግብ
መምታት ዋና መሣሪያ በመሆን የሚያገለግሉ ሠነዶች መሆናቸውን ያብራራሉ፡፡ በተጨማሪም

3
ቋንቋን በማስተማር ሂደት በተሟላ መንገድ የሚያገለግሉ ዋነኛ የቋንቋ ትምህርት አካል
መሆናቸውን አፅንኦት በመስጠት ገልፀዋል፡፡

Harmer (1991)' McDonough and Shaw (1993)' Cunnings worth (1995) እንደሚያብራሩት የቋንቋ
መማሪያ መፅሀፍ ሲዘጋጅ የይዘት መረጣ፣አደረጃጀትእና አቀራረብ ትኩረት የሚሹ ነገሮች ናቸው፡፡
በመሆኑም ይዘቶች ሲመረጡ፣ ሲደራጁ እና ሲቀርቡ ተገቢነት፣ ብቃት፣ ግልፅነት፣ ትክክለኝነት፣
እውነተኝነት፣ ባህላዊነት፣ አስተማማኝነት፣ ፅንዑነት፣ ተመጣጣኝንት፣ አጠቃላይነት፣
ተለዋዋጭነት፣ ጠቃሚነት፣ አመችነት፣ መመሪያ ሰጭነት፣ አነሳሽነት፣ ተከታታይነት፣
ተለጣጣቂነትእና ውህዳዊነት ትኩረት የሚሰጣቸው ናቸው፡፡ Nunan (1988)' Cunnings worth
(1984) እንደሚያብራሩት ደግሞ የቋንቋ ትምህርት ይዘቶች ተገቢ በሆነ መልኩ ከተመረቱ በኋላ
በቀጣይነት የሚመጣው ነገር አደረጃጀት ነው፡፡Tyler (1949) በበኩላቸው ደግሞ የትምህርት ይዘቶች
ውጤታማ ይሆኑ ዘንድ አንዱ ይዘት በሌላው ይዘት ላይ ተመስርቶ መደራጀት ይገባዋል፤
የትምህርት ይዘቶችም ለማደራጀት ተከታታይነት፣ተለጣጣቂነትና ውህደት ያላቸው ዋናዎቹ
መለኪያ መስፈርቶች መሆናቸውን ይገልፃሉ፡፡ Harmer (1991) እንደሚገልጹት ተገቢ በሆነ መልኩ
የተዘጋጁ የቋንቋ መማሪያ መጽሐፍት ለተማሪዎቹ የቋንቋ ችሎታ መዳበር አስተዋጽኦ
ያደርጋሉ፤የትምህርቱን ይዘት በግልጽ ያመላክታሉ፤ ትምህርቱን ስኬታማ ለማድረግ የሚረዱ
ተግባራትን ያሳያሉ፤ እንዲሁም ተማሪዎቹ የተለየ ትኩረት መስጠት የሚኖርባቸውን ዋና
ዋና ነጥቦች ያመላክታሉ፡፡

በሌላ በኩል በቋንቋ ትምህርት ሂደት ውስጥ ስኬታማ የሆነ የመማር ማስተማር ሂደት
ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ከሚያደርሱ መሰረታዊ ጉዳዮች ውስጥ እንደዋነኛ ምክንያት
የሚጠቀሰው የመማሪያ መፃሐፍት ብቃት ማነስ እንደሆነ Sheldon (1988) ያስረዳሉ፡፡ ይህ
ሲባል ግን ሌሎች ተያያዥ ችግሮች ሊኖሩ እንደሚችል አብሮ መገንዘብ አስፈላጊ ነው፡፡ እነዚህም
መማሪያ መፃሐፍት የሚታዩባቸውን ችግሮች ለመቀነስ የመማሪያ መፃሐፍቱን በየጊዜው
ማሻሻል አስፈላጊ ነው፡፡ የመማሪያ መፃሐፍት አንድ ጊዜ ተዘጋጅተው የሚቆሙ እና ለረዥም
ጊዜ አግልግሎት እንዲሰጡ የሚደረጉ ሳይሆን፤ በየጊዜው ጥንካሬያቸው እና ድክመታቸው
እየታየና እየተለየ እንደተማሪዎቹ ሁኔታ ማሻሻል እንደሚጠበቅ ያስረዳሉ፡፡ ስለሆነም በዚህ ጥናት
በ2004 ዓ.ም በተሻሻለው የአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሃፍ ከመርሀ ትምህርቱ
ጋር ያለውን ዝምድና መፈተሸ ነው፡፡

4
1.2 የጥናቱ አነሳሽ ምክንያት
የዚህ ጥናት አነሳሽ ምክንያቶች በዋናነት ሶስት ነገሮች ናቸው፡፡ የመጀመሪያው በመማሪያ
መፃሕፍት አደረጃጀት እና አቀራረብ ዙሪያ በውጭም ሆነ በሃገር ውስጥ የተካሄዱ ጥናቶች ችግሩ
እንዳለ መጠቆማቸው ሲሆን ሁለተኛው የዚህ ጥናት አነሳሽ ምክንያት የአጥኝው የመምህርነት
ተሞክሮ ይህንን ሁኔታ የሚያጠናክር ሁኖ መገኘቱ ነው፡፡ ሦሰተኛው ደግሞ አጥኝው ይዞት
በተነሳው ርዕሰ ጉዳይ ላይ ትኩረት አድርጎ የተካሄደ ጥናት አጥኝው ማግኘት አለመቻሉ ናቸው፡፡

የመጀመሪያው በመማሪያ መፃሕፍት አደረጃጀት እና አቀራረብ ዙሪያ በውጭም ሆነ በሃገር ውስጥ


የተካሄዱ ጥናቶች ችግሩ እንዳለ መጠቆማቸው ሲሆን እንደ Cunnings worth (1995)አገላለፅ በቋንቋ
መማሪያ መፃህፍት ይዘቶች አቀራረብእና አደረጃጀት ላይ ሰለሚደደርጉ የግምገማ አይነቶች
ሲዘረዝሩ ግምገማው በሚካሄድበት ወቅት መታየት ያለባቸው ጉዳዮች በሶስት ደረጃ እንደሚከናወኑ
አብራርተው አስቀምጧቸዋል፡፡ ቅድመ አገልግሎት ግምገማ፣የአገልግሎት ጊዜ ግምገማእና ድህረ
አገልግሎት ግምገማ ናቸው፡፡ ከነዚህ መካከል የአገልግሎት ጊዜ ግምገማ ትኩረት በአገልግሎት
ላይ ያለ መማሪያ መጽሐፍ ታትሞ ተማሪዎች በክፍል ውስጥ እየተማሩበት ወይም
እየተገለገሉበት ባለበት ሂደት የሚከናወን የግምገማ ስርዓት ነው፡፡Dubbin & olishtain (1986)
እንደሚያስረዱት መርሃ ትምህርት እና መማሪያ መፃሕፍት መጣጣማቸውን በየጊዜው መፈተሽ
እንዳለበት በሁለቱ መካከል አለመጣጣም ሲከሰትም ጥናትና ምርምር በማድረግ የችግሮችን ምንጭ
ነቅሶ በማውጣት የሚሻሻሉበትንና የሚስተካከሉበትን ዘዴ ማመቻቸት ያስፈልጋል፡፡እንዲሁም
በዚህ ዙሪያ ላይ የተጠኑ ቀደምት ጥናቶች የሚያሳዩት ይህንን ጉዳይ በመሆኑ ነው፡፡ ይህም
ሲባል እያሱ (2003)በ1997 ዓ.ም.በተሻሻሉት የ9ኛና የ10ኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ
መፃህፍት የሥነ ትምህርታዊ ሰዋስው ይዘት አመራረጥ፣ አቀራረብና አደረጃጀት ግምገማ በሚል
ርዕስ ጥናት አቅርቧል፡፡ በውጤቱም የሰዋስው ትምህርት ይዘቶች ከቋንቋው ሰዋስዋዊ ክፍሎች
የተውጣጡ አለመሆናቸው፣ የግልጽነት ችግር የሚስተዋልባቸው ከመሆናቸውም በተጨማሪ
ከመርሀ ትምህርቱ ጋር ያልተዛመዱ እንደሆኑ፣ ከተከታታይነትና ከተለጣጣቂነት አንፃርም
ክፍተት ያለባቸው መሆናቸውን እና የአቀራረብ ችግር እንደተስተዋለባቸው አረጋግጧል፡፡
ሐዋዝ(2000) ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማና በአማራ ክልል አንደኛ ደረጃ ሁለተኛ እርከን የአማርኛ
ቋንቋ መማሪያ መፃህፍት ውስጥ የሰዋስው ትምህርት አቀራረብና አደረጃጀት ንጽጽራዊ ግምገማ
በሚል ርዕስ ለሁለተኛ ዲግሪ ያቀረበው ጥናት ተጠቃሽ ነው፡፡ በውጤቱም ክልሎቹ መሠረት
ያደረጉት አንድ አይነት መርሀ ትምህርት ቢሆንም በአቀራረብና በአደረጃጀታቸው

5
መለያየታቸውን፣ በሁለቱም ክልሎች የሰዋስው ትምህርት የአቀራረብ መርሆዎችን አልሞ
አለመተግበር፣ የጽንሰ ሃሳብ፣ የዓርትኦትና ከመርሀ ትምህርቱ የመውጣት ችግሮች በጥናቱ ሂደት
የተደረሰባቸው ግኝቶች መሆናቸውን ገልጿል፡፡ እንዲሁም ሰሚራ(2010) በ2009ዓ.ም. ስራ ላይ
በዋለው የደቡብ ክልል የ8ኛ ክፍል አማርኛ ቋንቋ መማሪያ መጻህፍ ውስጥ የተካተቱ የሰዋስው
ትምህርት ይዘቶች አቀራረብና አደረጃጃት ምን እንደሚመስል ጥናት አካሂዳለች፡፡በጥናቱ የተገኘው
ውጤት እንደሚያመለክተው የይዘቶቹን አቀራረብ በተመለከተ ከአጠቃላይ ወደ ዝርዝር ይልቅ
ከዝርዝር ወደ አጠቃላይ የቀረቡ የሰዋስው ትምህርት ይዘቶች አብላጫውን ሽፋን ይይዛሉ፡፡ ይሁን
እንጂ ከዝርዝር ወደ አጠቃላይና ከአጠቃላይ ወደ ዝርዝር የቀረቡት ይዘቶች በጥሩ ሁኔታ የቀረቡ
ሲሆን እንደደካማ ጎን የታየው በአንድ ትእዛዝ ስር የተለያዩ ሶስትና ከዚያ በላይ የሆኑ ርዕሰ
ጉዳዮችን ማካተቱና ገለጻ ሲቀርብ መልእክት በትክክል አለመቅረቡ ነው፡፡

ሁለተኛው የዚህ ጥናት አነሳሽ ምክንያት የአጥኝው የመምህርነት ተሞክሮ ሲሆን ልምዱ ይህንን
ሁኔታ የሚያጠናክር ሁኖ መገኘቱ ነው፡፡ አጥኝው በመምህርነት ስራ ከተሰማራበት ጊዜ ጀምሮ
ከትምህርት ክፍል ባልደረቦቹ ጋር በነበረው መስተጋብር ከመማር ማስተማሩ ሂደት ጉን ለጎን
ኢ-ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ የአስረኛ ክፍል የአማረኛ ቋንቋ በመማሪያ መፅሐፉ እና በመርሃ
ትምህርቱ ላይ ይታዩ በነበሩ ክፍተቶች ዙሪያ ውይይት እና ግምገማ ያደርግ ነበር፡፡ በመሆኑም
በተለያዩ የትምህርት ክፍል ስብሰባዎች በመማር ማስተማር ተግባር ጊዜ በመማሪያ መፃሕፍትቱ
እና መርሐ ትምህርቱ መካከል ያለመጣጣም ችግር ያጋጥም ነበር፡፡ እንዲሁም በወሰነ ትምህርቱ
መገባደጃ እና በአመቱ መጨረሻ በትምህርት ክፍል ደረጃ የመፃሕፍት ግምገማ በማካሄድ በታዩ
ክፍቶች ዙሪያ ሃሳብ ልውውጥ ይደረግ ነበር፡፡ ስለዚህም በትምህርት ክፍሉ ይነሱ የነበሩ ሃሳቦችን
መነሻ በመዳረግ ለመፈተሽ ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ በ2004 ዓ.ም በአንደኛ እትም ታትመው
በአሁኑ ወቅት ሥራ ላይ ያሉትን የአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና መርሀ
ትምህርቱ ያላቸውን ዝምድና በተመለከተ ለመፈተሽ ፍላጎት በማሳደሩ ነው፡፡ሦሰተኛው ደግሞ
አጥኝው ይዞት በተነሳው ርዕሰ ጉዳይ ላይ ትኩረት አድርጎ የተካሄደ ጥናት አጥኝው ማግኘት
አለመቻሉ ናቸው፡፡

አጥኝው በአስረኛ ክፍል መማሪያ መፃሕፍት እና መርሃ ትምህርቱ መካከል ያለውን ዝምድና
በሰነድ ፍተሻ አመካኝነት የተሰበሰበውን መረጃ ፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት የተዛምዶ መለኪያ
(pearson product-moment correlation) በመጠቀም የተነተነ ሲሆን ከእያሱ (2003) ጥናት
የሚለይበት በዚህ ጥናት መረጃ የተሰበሰበው እና የተተነተነው ከጽሁፍና ከቃል መጠይቅ

6
በተጨማሪ የሰነድ ምርመራ በተሰበሰበ መረጃ ሲሆን ትኩረቱ የነበረውም የ9ኛና የ10ኛ ክፍል
የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃህፍት የሥነ ትምህርታዊ ሰዋስው ይዘት አመራረጥ፣ አቀራረብና
አደረጃጀት ግምገማ ነበር፡፡በመማሪያ መፅሐፉ እና በመርሃ ትምህርቱ መካከል ያለውን ዝምድና
አልፈተሸም፡፡

ከሐዋዝ(2000) እና ሰሚራ(2010) የሚለይበት የነዚህም ጥናቶች ትኩረት የሰዋስው ትምህርት


ይዘቶች አቀራረብና አደረጃጃት ምን እንደሚመስል ምርምር ያካሄዱ ሲሆን የአጥኘው የትኩረት
አቅጣጫ ግን በመማሪያ መፅሐፉ እና በመርሃ ትምህርቱ መካከል ያለውን አደረጃጀት እና ለምዘና
ተግባር የዋሉ ስራዎችን እና መልመጃዎችን ዝምድና መፈተሽ ነው፡፡ በመሆኑም በዚህ ጥናት
አጥኝው ካጋጠሙት ቀደምት ጥናቶች ትኩረት ያልተደረገበትን ጉዳይ የሚፈትሽ መሆኑ
ጥናቱን የተለየ ያደርገዋል፡፡ስለዚህም ጥናቱ ለሚከተሉት ጥያቄዎች መልስ ለመስጠት
ሞክሯል፡፡

1. በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና በመርሃ ትምህርቱ መካከል ያለው
የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት ተከታታይነት ዝምድና ምን ይመስላል?
2. በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍትና በመርሃ ትምህርቱ መካከል ያለው
የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት ተለጣጣቂነት ዝምድና ምን ይመስላል?
3. በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ያለው የክሂልና የእውቀት ዘርፎች
የይዘት ውህዳዊነት ምን ይመስላል?
4. በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍትና በመርሃ ትምህርቱ ውስጥ ለምዘና
ተግባር የዋሉ ስራዎች ያላቸው ዝምድና ምን ይመስላል?

1.3 የጥናቱ ዓላማ


የዚህ ጥናት ዋና አላማ በ2004 ዓ.ም በአንደኛ አትም ታትመው በአሁኑ ወቅት ሥራ ላይ ያሉትን
የአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና መርሀ ትምህርቱ ያላቸውን ዝምድና
መፈተሸ ሲሆን፣ዝርዝር ዓላማዎችም የሚከተሉት ናቸው፡፡

1. በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍትእና በመርሃ ትምህርቱ መካከል


ያለውን የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት ተከታታይነት ዝምድና መፈተሽ
2. በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍትና በመርሃ ትምህርቱ መካከል
ያለውን የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት ተለጣጣቂነት ግንኙነት መመርመር

7
3. በአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ያለውን የክሂልና የእውቀት ዘርፎች
የይዘት ውህዳዊነት መመርመር
4. በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍትና በመርሃ ትምህርቱ ውስጥ ለምዘና
ተግባር የዋሉ ስራዎች ያላቸውን ዝምድና መፈተሸ

1.4 የጥናቱ አስፈላጊነት


የዚህ ጥናት ውጤት የሚከተሉት ዝርዝር ጠቀሜታዎች ይኖሩታል ተብሎ ይታመናል፡፡

ሀ. ለትምህርት ቤት፡- መርሀ ትምህርት እና መማሪያ መፃሕፍት በቋንቋ መማር ማስተማር


ሂደት ውስጥ የሚገኙ በመማሪያ መፅሐፉና በመርሀ ትምህርቱ የተካተቱ ክሂሎችን፣ የእውቀት
እና የሥነ ልሳን ዘርፎችን የትምህርት መተግበሪያ መሣሪያዎች በመሆናቸው ትምህርት ቤቱ
ይህንን አውቆ ሥልጠና በመስጠት ለማሥተግበርና ውጤታማ ለመሆን መነሻ ሆኖ ሊያገለግል
ይችላል፡፡

ለ. ለመምህራን፡- የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍቱን በመማር ማሥተማር የዕለት ከዕለት ተግባር


በሚጠቀሙበት ጊዜ መርሀ ትምህርቱን ከቋንቋ መማሪያ መፃሕፍቱ ጋር እያጣመሩ በመጠቀም
በሁለቱ መካከል በአጠቃላይ አቀራረቡም ሆነ ይዘቱ ላይ ዝምድና መኖሩን ለማወቅና ችግር
ካለበትም ነቅሶና አበጥሮ በማውጣት ምቹ ሁኔታዎችን በማመቻቸት ከተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር
እያዋሀዱና. እያደረጁ ለመጠቀም ያግዛል፡፡

ሐ. ለተማሪዎች፡- መምህራን መርሀ ትምህርቱንና የቋንቋ መማሪያ መፃሐፍትን ዝምድና


በመመርመር ሥርዓተ ትምህርቱና ሥነ ዘዴው በሚፈቅደወ መንገድ አዋቅረውና አቀናጅተው
በማሥተማር ለተማሪዎች የሚጠበቀውን የክሂሎት፣ የእውቀት እና ሥነ-ልሳን ዘርፎችን
ስለሚያስተምሯቸውና ስለሚገነቧቸው በቋንቋ ትምህርት እንዲካኑ ያደርጋል ተብሎ ይታሠባል፡፡

መ. ለሥርዓተ ትምህርት አዘጋጆች፡- በመርሀ ትምህርቱ እና በቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ውስጥ


ያለውን ዝምድና እና ችግርም ካለ ችግሩን ስለሚጠቁም ሥርዓተ ትምህርቱን ለሚያዘጋጁትና
በመማሪያ መፅሐፉና መርሀ ትምህርት ዝግጅት ለተሠማሩት ባለሙያዎች ጥቆማ ስለሚሠጥ
የመነሻ ሀሳብ ሆኖ ያገለግላል ተብሎ ይታሠባል፡፡

ሠ. ለጥናት አድራጊዎች ፡- ይህን ርዕስ ተመርከዘው ወደፊት ከዚህ የጥናት ርዕስ ጋር ተያያዥነት
ያለው ምርምር ለማድረግ ለሚፈልጉ አጥኚዎች እንደመነሻ ሀሳብ ሆኖ ሊያገለግል ይችላል፡፡

8
1.5 የጥናቱ ወሰን

ይህ ጥናት በዋነኛነት ትኩረት አድርጎ የተነሳው በ2004 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር ታትሞ
በስራ ላይ በዋሉት የአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍ ከዚሁ የክፍል ደረጃ መርሀ
ትምህርት ጋር ዝምድና እንዳለው በመፈተሸ ላይ ነው፡፡ በመሆኑም የመረጃ ምንጮቹ የ10ኛ
ክፍል የአማረኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና ለዚህ የክፍል ደረጃ ይመጥናል ተብሎ በተዘጋጀው
መርሀ ትምህርት በተጨማሪም የአስራ አንደኛ ክፍል አማርኛ መማሪያ መፅሀፍ ብቻ ነው፡፡በመረጃ
መሰብሰቢያነት አገልግሎት ላይ የሚውለው ሰነድፍተሻ ሲሆን የተሰበሰበው መረጃም የሚተነተነው
በአይነታዊና በመጠናዊ የምርምር ዓይንት ላይ የተወሰነ ይሆናል፡፡

ጥናቱ ከይዘት አኳያ ሢታይም በመፅሐፉ የይዘት አደረጃጀት ላይ የሚያተኩር ይሆናል፡፡ ይህም
በክሂሎችና የእውቀት ዘርፎች የይዘት ሽፋንና አደረጃጀት እና ለምዘና ተግባር በሚውሉ ሥራዎች
ተዛምዶ ብቻ መርምሯል፡፡

እንዲሁም በዚህ ጥናት መርሃ ትምህርት ከሚያካትታቸው ጉዳዬች ወይም ንጥረ ነገሮች መካከል
ትኩረት ያደረገው በይዘቶች አደረጃጀት እና የምዘና ተግባራት ላይ ብቻ ነው፡፡ በመሆኑም አጥኝው
የትምህርቱ ገለፃ፣የትምህርቱ ዓላማዎች፣የይዘት አመራረጥ፣የማስተማሪያ ዘዴው አመራረጥና
የማስተማሪያ መርጃ መሳሪያዎች አጠቃቀም ወዘተ. ትኩረት አያደርግም፡፡

1.6 የጥናቱ ውስንነት


የዚህን ጥንት አስተማማኝነት እና ተገቢነት ለማሳደግ ጥረት ተደርጓል፡፡በጥናቱ ርዕሰ ጉዳይ ላይ
መሰረት ያደረጉ መስፈርቶች ማዘጋጀት፣ በመስፈርቶቹ መረጃ ለመሰብሰብ የሚያስችሉ ተገቢ
መረጃ የመሰብሰቢያ ዘዴዎችን መምረጥ እና ማዘገጀት፣ የተዘጋጁ የመረጃ መሰብሰቢ
መሳሪያዎችን በአማካሪ እና በባለሙያ ማስገምገም፣ ተገቢ የመረጃ መተንተኛ ዘዴዎችን
መምረጥ፣ የተጠየቁትን መሰረታዊ ጥያቄ መሰረት ያደረገ ተገቢ ትንተና እና ማብራሪያ ማድረግ፣
ማጠቃለያ፣ መደምደሚያ እና የመፍትሄ ሀሳብ ለማቅረብ ጥረት ተደርጓል፡፡ ከላይ የተጠቀሱ
ጥረቶች የተደረጉ ቢሆንም ይህ ጥናት ከተለያዩ ችግሮች የፀዳ አይደለም፡፡ ቀደሚው በጥንቱ
መረጃ ሲሰበሰብ እና ሲደራጅ ከዚህ በፊት በመረጃ መሰብሰቢያት የተዘጋጀ መሳሪያ አጥኝው
ባለማግኘቱ የተዋጣለት የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያ ለማዘጋጀት እና በሚገባ አስፈላጊውን መረጃ
ለመሰብሰብ ተቸግሮ ነበር፡፡ እንዲሁም አጥኝው በክለሳ ድርሳናት ውስጥ የተጠቀመችባቸውን
የውጭ መፃሕፍት ፅንሰ ሃሳቦች በሚገባ ለመረዳት ፈታኝ ነበር፡፡

9
1.7 የጥንቱ ቁልፍ ቃላት እና ሃረጋት
በዚህ ጥንት ውስጥ ከፍተኛ ሚና የነበራቸው ቁልፍ ቃላት እና ሐረጋት ስድስት ሲሆኑ እነሱም
ተከታታይነት፣ ተለጣጣቂነት፣ ውህዳዊነት፣ የምዘና ተግባራት፣ መማሪያ መፃሕፍትና መርሐ
ትምህርት ናቸው፡፡

ተከታታይነት፡-በአንድ መማሪያ መፃሕፍት ውስጥ የቀረቡ ይዘቶች በሚቀጥሉት ምዕራፎች


እየተከታተሉ መምጣቱን የሚመለከት ነው፡፡
ተለጣጣቂነት፡-ተመሳሳይ የሆኑ የትምህርት ይዘቶች በአንድ የክፍል ደረጃ ላይ በተለያየ
አቀራረብ ተደጋግመው መቅረብን የሚመለከት ነው፡፡
ውህዳዊነት፡-በተለያዩ የትምህርት ዓይነቶች መካከል ያለውን ጎናዊ ግንኙነት በማጤን
የማደራጀት ተግባር የሚከናወንበት ሂደት ነው፡፡
የምዘና ተግባራት፡-በመማሪያ መፃሕፍት ወይም በመርሐ ትምሕርቱ ውስጥ ለምዘና ተግባር
የዋሉ ስራዎችን ይመለከታል፡፡
መማሪያ መፃሕፍት፡- የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት በመርሐ ትምህርቱ የተገለፁ ይዘቶችን
አደራጅቶ የያዘ የማስተማሪያ ዘዴ ነው፡፡
መርሐ ትምህርት፡- መርሐ ትምህርት የትምህርት ይዘቶችን አደራጅቶ የያዘ መመሪያ
ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ መማርን የሚያፋጥን፣ ከስርዓተ ትምህርት
የሚቀዳ የማስተማሪያ መሳሪያና ክንውኖች የሚካሄዱበት ማዕቀፍ ነው፡፡

ምዕራፍ ሁለት፤ክለሳ ድርሳናት

2.1 የመርሃ ትምህርት ምንነት


መርሐ ትምህርት የሀገሪቱን አጠቃላይ የትምህርት ፍልስፍና እና ፖሊሲ መሰረት በማድረግ
ተማሪው ምን መማር ወይም ማወቅ እንደሚጠበቅበትና መምህሩም ምን ማስተማር እንዳለበት
የሚጠቁም መሰረታዊ የሆነ የቋንቋ ትምህርት ዋነኛ ሰነድ ነው፡፡

10
Carl wenning (2009) አገላለፅ መርሀ ትምህርት ቃሉ የላቲን ሲሆን ትርጉሙም የአንድ ኮርስ
አጠቃላይ ዝርዝር ማለት ነው፡፡ መርሀ ትምህርት ለውጥ ማሥገኛ የትምህርት መርሀ ግብር
ነው፡፡ መምህሩ ምን እንደሚያሥተምር፣ ተማሪዎች ምን እንደሚማሩ የሚመራ ሠነድ ነው፡፡
መርሀ ትምህርት በአንድ የመማሪያ ተቋም በተወሠነ የጊዜ ገደብ የሚጠና የትምህርት ዝርዝር
ይዘት ማቅረቢያ ነው (Dubbin & olishtain 1986):: የአንድ የተወሠነ የትምህርት መሥክና
አላማዎች ለማሣካት የሚቀረብ የርዕስ ጉዳዮች ሥብሥብ ነው፡፡ መርሀ ትምህርት በትምህርት
የሚቀርቡ ተከታታይ ይዘቶች ዝርዝር ነው (Farrant 1980)::

መርሀ ትምህርት የቋንቋና የመማር ባሕሪያት የሚመለከቱ አሥተያየቶች የሚገለፁበት መምህራን


እና ተማሪዎች የሚያሳኳቸውን ግቦች በማቅረብ እንደመመሪያ የሚያገለግል፣ ለትምህርት
የሚቀርቡ ይዘቶችን የሚዘረዝር፣ ተማሪዎች የሚማሩትን ይዘት ማጠቃለያ አድርጐ ሊወሰድ
የሚችል ነው (Yalden 1987)::

መርሃ ትምህርት በተወሰነ የጌዜ ገደብ ውስጥ የሚሸፈኑ የአንድ ትምህርት አይነት ርዕሰ ጉዳዮችን
እና ተማሪዎች የሚማሯቸውን የትምህርት ልምዶች የያዘ የኮርስ ቢጋር ነው፡፡ መምህሩ
የሚያስተምረውን ትምህርት ለማዘጋጀት የሚጠቀምበት መሳሪያ ነው፡፡ መርሃ ትምህርት
የመማርና የማስተማር አለባዊያን ዝርዝርና ተግባራዊ ዶክመንት የሆነ፣ የስርዓተ ትምህርት
አጠቃላይ ፍልስፍና የሚተረጎምበት መሳሪያ እና የአንድ ትምህርት ተዛማጅ ርዕሰ ጉዳዮች
ስብስብም ነው፡፡

መርሃ ትምህርት የአንድ የተወሰነ ትምህርት ንድፍ ወይም ቢጋር ሲሆን የትምህርቱ ዝርዝር
ዓላማ፣ ይዘቱ፣ የማስተማር ዘዴው፣ የማስተማሪያ መረጃ መሳሪያ፣ የምዘና ስልትና የተወሰኑ
የክፍል ደረጃ የተመደበለትን የጊዜ ክፍፍል የሚያሳይ ነው(Brumfit 1984)፡፡ Yalden (1987)
ደግሞ በአንድ የትመህርት ተቋም በየክፍል ደረጃው የሚቀርብ ዝግጅት ሆኖ በየትምህርት አይነቱ
የተቀነባበሩ ይዘቶችን፣ የማስተማሪያ ዘዴዎችን፣ የመገምገሚያ መሳሪያዎችንም የሚያመለክት
መግለጫና ለመማር ማስተማሩ የተዘጋጀ የትምህርት ፕሮግራም ነው፡፡ በተጨማሪም
cunningsworth (1995) በበኩላቸው መርሀ ትምህርት በአንድ የትምህርት አይነት ወይም የክፍል
ደረጃ የሚሸፍን የትምህርት ርዕስ የሚገለጽበት ነው፡፡

Yalden (1987)፡ widdowson (1990) እና wilkins (1976) እንደገለጹት መርሃ ትምህርት ውጤታማ
የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖር በአንድ የትምህርት አይነትና የክፍል ደረጃ የትምህርቱን

11
ዝርዝር ርዕሰ ጉዳይና የአተገባበር ቅደም ተከተልና ወይም የማስተማር ዘዴንና የምዘና ስርዓትን
አጠቃሎ የያዘ ዝርዝር መግለጫ ሲሆን መምህሩና ተማሪዎች የትምህርቱን ግብ ማሳካት
እንዲችሉ የሚመሩበት እቅድ ነው በማለት ገልጸዋል፡፡

የመርሃ ትምህርት አይነቶችን Nunan (1988) ሂደት ተኮር እና ውጤት ተኮር በማለት በሁለት
ይከፍሏቸዋል፡፡ አክለውም ሂደት ተኮር መርሀ ትምህርት እንደአውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር
የ1980ዎቹ ውጤት ሲሆን ተንታኝ ባህርይ የሚንፀባረቅበት፣ ከውጤት ይልቅ ሂደት ላይ
የሚያተኩር እና ለማስተማር ስነዘዴ ከፍተኛ ቦታ የሚሰጥ ነው ይላሉ፡፡ በተጨማሪም Nunan
(1988) ሂደት ተኮር መርሀ ትምህርት ሂደት ተኮር ነው ሲባል ትኩረቱ በቋንቋ እውቀትና ችሎታ
ላይ ሳይሆን በመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ ተማሪዎች የሚያገኟቸውን ልምዶች ማደራጀት
ላይ እንደሆነ ይገልጻሉ፡፡

ውጤት ተኮር መርሃ ትምህርት አንድን ትምህርት ተማሪዎች ከተማሩ በኋላ ከተማሩት
ትምህርት ምን ማወቅ ይችላሉ በሚለው ላይ ያተኩራል፡፡ ትኩረቱ ተማሪዎች ከተማሩት
ትምህርት በሚያገኙት እውቀት እና ክሂሎት ላይ ነው (Nunan 1988)፡፡ እንደ Thakur (2013)
አገላለጽ ውጤት ተኮር መርሀ ትምህርት ከቀረበው የቋንቋ ትምህርት ተማሪዎች ምን ይማራሉ
በሚለው ላይ ያተኩራል፡፡ አያይዘውም ሂደት ተኮር መርሀ ትምህርት እንዴት የቋንቋውን
ትምህርት እናስተምራለን በሚለው ላይ ሲያተኩር፣ ውጤት ተኮር መርሀ ትምህርት ደግሞ
ተኩረቱ ይዘት ላይ ሲሆን፣ ሂደት ተኮር መርሃ ትምህርት ግን ትኩረቱ ከማስተማሪያ ዘዴ ላይ
ነው ይላሉ፡፡

በአጠቃላይ የምንጠቀምበት የመርሀ ትምህርት አይነት የቋንቋ ትምህርት አላማው የቋንቋ


ተማሪዎች ዳራ፣ የቋንቋ ተማሪዎች እድሜና ፍላጎት እንዲሁም ለቋንቋ ትምህርት የተያዘው
ጊዜና በጀት ወዘተ. የሚመሳሰሉት ጉዳዮች የሚወስኑት ቢሆንም መርሀ ትምህርት በተቻለ መጠን
ከዘመኑ የቋንቋ ንድፈ ሀሳብ ጋር ተጣጥሞ የሚሄድ እንጂ ከዚህ ውጭ ሆኖ የሚዋቀር ሊሆን
አይገባም (widdoson 1990)::

2.1.1 የመርሀ ትምህርት ባህሪያት


ጥሩ መርሀ ትምህርት በውስጡ ብዙ ነገሮችን ያካተተ ነው፡፡ የአንድ ትምህርት አጠቃላይ ሂደት
አቅጣጫ ጠቋሚ መሳሪያ ወይም ኮምፓስ ነው፡፡ ጥሩ መርሃ ትምህርት የሚቀረፀው ከተማሪዎች
የኋላ ታሪክ፣ የተማሪዎችን ፍላጎት፣ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ ወዘተ መነሻ በማድረግ ነው፡፡

12
Breen (1984) የመርሀ ትምህርት መገለጫ ገጽታዎች ወይም ባህሪያት ናቸው ተብለው የሚገልጹት
ወደ ሰባት ይደርሳሉ፡፡ እነሱም አብዛኛውን ጊዜ በመግቢያው ላይ ግልጽ አላማዎችን የሚያሰፍር፣
የተለያዩ ይዘቶችን ማለትም ቃላትን፣ ሀረጋትና አረፍተ ነገሮችን አጠቃላይ በሆነ መልኩ
የሚገልጽ በጣም ተፈላጊና ቀላል የሆነውን የቋንቋ ትምህርት መጀመሪያ የሚያስቀምጥ፣ ሁሉንም
የህብረተሰብ ክፍል በጋራ የሚያስተናግድ፣ የቋንቋ ትምህርት በቅደም ተከተል የሚቀርብበትን
ስልት የሚጠቁም፣ ከቋንቋው ይዘት ጋር ሊሄዱ የሚችሉ የትምህርት መርጃዎችን አካቶ የያዘ
እና በትምህርት ሂደት የቋንቋ ትምህርት የሚተላለፍበትን ስልት የሚጠቁም ነው፡፡

በአጠቃላይ አንድ መርሀ ትምህርት ለተማሪዎች የሚቀርብን ይዘት አጭርና ግልጽ በሆነ መንገድ
ማቅረብ፣ ተማሪዎች ለምን ወደ ትምህርት ቤት እንደሚሄዱና ምን እንደሚማሩ ግልጽ ማድረግ፣
የትምህርት መርጃ መሳሪያዎችን በማሳካት ትምህርቱን በሚገባ እንዴት መስጠት እንዳለበት
አቅጣጫ ማስቀመጥ እና የጊዜ ሁኔታዎችን ወይም አጠቃቀምን በተመለከተ መቼ ለምን እና
በምን እንደምንጠቀም በመጠቆም ከአጋዥ መሳሪያዎች ጋር ማስተሳሰር ወዘተ ባህሪያቶቹ ናቸው፡፡

በሌላ በኩል የአንድ ጥሩ መርሀ ትምህርት ገጽታዎችን በተመለከተ Features of good syllabus
(2008) የተሰኘው ድህረ ገጽ እንዳስገነዘበው አንድ መልካም የሆነ መርሀ ትምህርት ታላሚዎችን
በግልጽ የሚያሳይ፣ ግብና አላማዎችን የያዘ፣ የማስተማሪያ ይዘቶቸን የሚጠቁም፣ ማስፈጸሚያ
ስልቶችን የሚወስን እና የመገምገሚያ መርሆዎችን የሚያሟላ መሆን አለበት በማለት ይገልጻል፡፡

2.1. 2 የመርሃ ትምህርት ዓላማ


አላማዎች አጠቃላይ ዓላማ እና ዝርዝር ዓላማ ተብለው በሁለት ይከፈላሉ፡፡ በጣም ሰፊ የሆኑ
በአንድ ክፍለ ጊዜ የማይፈፀሙና የማይለኩ፣ የአንድ ጊዜ ተግባራዊ ክንዋኔን የሚያሳዩ አጠቃላይ
አላማዎች ናቸው፡፡ በመርሀ ስርዓተ ትምህርቱ ላይ የተዘጋጁ ቢሆንም መምህራን ከአካባቢያቸው
ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማዛመድ አስተካክለው ሊነድፏቸው ይችላሉ፡፡ ዝርዝር አላማዎች
በአንድ ክፍለ ጊዜ የሚፈፀሙና የሚለኩ የአላማ አይነቶች ናቸው፡፡ የሚዘጋጁትም በከፍል
መምህራን ነው፡፡ ዝርዝር አላማ ከአጠቃላይ አላማ በኋላ በጥንቃቄ መስፈር አለበት እንጂ ዝርዝር
ዓላማ ከአጠቃላይ ዓላማ መቅደም የለበትም፡፡ የቋንቋ ትምህርት አላማዎች የትምህርት ርዕሶችን
ፅንሰ ሀሳቦችን አጠቃላይ መመሪያዎችን ወይም ደግሞ የትምህርት ይዘትን የሚገልጹ አይነት
ተደርገው መስፈር የለባቸውም፡፡ ትምህርቱን የሚማረው የግዴታ ተማሪው ነውና ከተማሪው
አንጻር መጻፍ አለበት፡፡ የተነደፈው መርሀ ትምህርት ሲጠቃለል ተማሪዎች እንዲያውቁ
የሚጠበቀውን ጉዳይ ይመለከታል፡፡ አላማውም መሰረቱን የጠበቀና ግብ መቺ ሆኖ በግልጽ ቋንቋ

13
መስፈር አለበት፡፡ ተማሪዎች ከተቀመጠላቸው ትምህርታዊ ይዘትና ተግባር መጠናቀቅ በኋላ
የሚቀስሙት እውቀት ክሂሎትና አመለካከት መለካት እንዲችል ተደርጎ ሊዘጋጅ ይገባዋል፡፡
ሲዘጋጁም ተማሪዎች ሊፈጽሟቸው በሚችሏቸው ተግባራት ላይ በመንተራስ ነው፡፡

Ur (1991) መርሃ ትምህርት በሚዘጋጅበት ጊዜ ግልጽና የሚያሻማ ዓላማ ሊኖረው እንደሚገባ


ገልጸው አላማውም በሰነዱ መጀመሪያ ላይ የተቀመጠ፣ በአላማው መሰረትነትም ይዘቶች ደረጃ
በደረጃ ተለይተው መቀመጥ እንዳለባቸው ያስረዳሉ፡፡ የመርሀ ትምህርት ዓላማዎች ደግሞ
የትምህርቱን ይዘት ለመምረጥ፣ የማስተማሪያ መሳሪያዎችን ለማዘጋጀት፣ በተገቢው የትምህርት
ዘርፍ ተገቢውን አጽንኦት ለመስጠት፣ የትምህርት ይዘቶችን በተፈለገው ጊዜና ቦታ በተገቢው
መንገድ በቅደም ተከተል ለማቀናበርና ለማደራጀት፣ የትምህርት ስርዓቱን በወጉና በአግባቡ
ለመከታተልና ለመተግበር እንዲሁም ለመገምገም የሚያስችሉ በርካታ ጠቀሜታ የሚያበረክቱ
ናቸው፡፡

2.1.3 የመርሀ ትምህርት ይዘት አመራረጥ


Bilabo Lucido and Iringan (2008) አገላለፅ ይዘት ለመምረጥ የሚያስፈልጉ ሰባት መስፈርቶች
በሚል የሚከተሉትን ዘርዝረው እናገኛለን፡፡ የመጀመሪያው ማብቃት የሚችል(self-sufficiency)
ሲሆን የሚመረጠው ይዘት ተማሪዎች በራሳቸው አቅማቸውን በከፍተኛ ደረጃ እንዲጠቀሙ
የሙከራ እድል ሊሰጣቸው፣ እንዲያዩ እንዲሁም የመስክ ጥናት እንዲያደርጉ እድል የሚሰጥ
መሆን አለበት፡፡ ጠቀሜታ(significance) ደግሞ ሁለተኛው መስፈርት ሲሆን ይዘቱ የሚጠቅምና
የእውቀት የአመለካከት እና የክሂል ዘርፎችን (cognitive,affective and psychomotor domans)
ሊያሳድግ የሚችልና የተማሪዎችን ባህል ከግምት ውስጥ ያስገባ መሆኑን ማረጋገጥ፡፡
ተገቢነት(validity) ሶስተኛው መስፈረት ነው፡፡ ተገቢነት የተመረጠው ይዘት እውነተኛነትን
የሚገልፅ እና ያላለፈበት ርዕሰ ጉዳይ መሆኑን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡ ለምሳሌ የታይፕ ፅሁፍ
ክሂልን ለኮሌጅ ተማሪዎች ከማስተማር ስለኮምፒውተር ወይም ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ
ማስተማሩ ተገቢ ነው፡፡በመርሃ ትምህርቱ ያለው ይዘት እንደአስፈላጊነቱ መለወጥም
አለበት፡፡ፍላጎት(Interest) ደግሞ የተመረጠው ይዘት ለተማሪዎቹ ትርጉም የሚሰጥ ከሆነ የተሻለ
መማር ይችላሉ፡፡ ትርጉም የሚሰጣቸው ደግሞ በጉዳዩ ላይ ፍላጎቱ ካላቸው ነው፡፡
አገልግሎት(Utility)፡- የትምህርቱ ይዘት ሲመረጥ አገልግሎቱ መታየት አለበት፡፡ ተማሪዎች
አንዳንድ ትምህርቶች እንደማይጠቅሟቸው ያስባሉ፡፡ ማለትም አገልግሎቱን ስራ ለመስራት
ከማስፈለግ፣ ለሕይወት ትርጉም የሚሰጥ ከመሆን፣አቅምን ማሳደግ ከመቻል፣ ችግርን መፍታት

14
ከመቻል፣ፈተና ላይ የሚካተት እንዲሁም ይዘቱን መማሩ የማለፊያ ማርክ ለማግኘት የሚረዳ
ከመሆን ጋር ያያይዙታል፡፡ ስለዚህ ተማሪዎች የሚጠቅማቸውን ይዘት እንደመፈለጋቸው መጠን
ዋጋ ያለው ይዘት ቢመረጥ፡፡ ሊማሩት የሚችል(Learnability)፡- በቀላሉ ሊማሩት የሚችሉት ይዘት
መሆን ማለትም ካላቸው ልምድ ጋር የተያያዘ ቢሆን፡፡ሊተገበር የሚችል(Feasibility)፡- ይዘቱ
ተማሪዎች ባለው ጊዜ እና ቁሳቁስ ሊማሩት የሚችል መሆን አለበት፡፡ ሊጨርሱት የማይችሉት
ጉዳይ ሊቀርብላቸው አይገባም፡፡ ለምሳሌ ትምህርቱን ለመጨረስ ያለው ጊዜ አንድ ሳምንት ሆኖ
የተሰጠው ተግባር አንድ ወር የሚፈጅ ቢሆን ወይም ኮምፒውተር ወይም መብራት በሌለበት
ሁኔታ የኮምፒውተር ተግባር የሚጠይቅ ይዘት ቢመረጥ ተተግባሪ አይደለም፡፡

መርሀ ትምህርቱ ሲዘጋጅ በቅድሚያ ሁኔታዎች የሚጠኑና አላማዎች የሚነደፉ ሲሆን ይዘት
መረጣው እነዚህነ ተከትሎ የሚመጣና በትምህርት እውነታዎች፣ ሀሳቦች፣ክሂሎች ወዘተ
የሚቀርቡበት ክፍል ነው፡፡ ሲመረጥም መጀመሪያ ከቀረበው ስርዓተ ትምህርት እና መርሀ
ትምህርት ኣላማ የማይጣረስ እንዲሁም የተማሪዎችን ፍላጎት ከግምት ውስጥ ያስገባ መሆን
አለበት (www.creating a syllabus/teaching at (UNL) University of Nebraska, lin coln)::
ለትምህርት የሚመረጡ የቋንቋ መርሀ ትምህርት ይዘቶች የተለያዩ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡
www.interjournals.org ድህረ ገጽ ላይ mohammed and et al waqar (1999) haymen የተባሉ
ምሁራን ጠቅሶ ያስቀመጠውን ብያኔ ሲገልጹ ይዘት እውቀትን (እውነታ፣ ገለጻ፣ መርህ፣ ብያኔ፣
ሰዋሰውና ስነጽሁፍ)፣ ክሂሎችና ተግባሮችን (ማንበብ፣ መጻፍ፣ ማዳመጥ፣ መናገር፣ማስላት፣
ማሰብ፣ መግባባት፣ ውሳኔ መስጠት) እና እሴቶችን (እምነት ማድረግ ያለበትና የሌለበት፣
መልካምና መጥፎ የሆኑ ነገሮች) የያዘ ነገር እንደሆነ ይገልጻል፡፡

2.2 የቋንቋ መማሪያ መፅሃፍ ምንነት


የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍትት የቋንቋ ትምህርት ዓላማን መሰረት በማድረግ በስርዓት የተደራጁና
ስርዓት የተከተሉ የቋንቋ ትምህርት ይዘቶችን በውስጣቸው ያካተቱ ሠነዶች ናቸው
ተስፋዬ(1981'43):: የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት የተደራጁ፣የተመጠኑና የተውጣጡ የቋንቋ
ትምህርት ይዘቶችን ከተማሪው አካባቢያዊና ዳራዊ ዕውቀት አንፃር አካቶ በመያዝ የተቀረፁ የቋንቋ
ትምህርት ዓላማዎችን ከግብ ለማድረስ የተዘጋጁ ሰነዶች እንደሆኑ ያብራራሉ፡፡ በተመሣሣይ
መልኩ Cunning worth (1989) የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ለቋንቋ ትምህርት ዓላማ መሳካትና
ለመማር ማስተማር ሂደት አጋዥ የሆኑ መሳሪያዎች እንደሁኑ ይገልፃሉ፡፡ በሌላ በኩል Richards
(2001) እንደሚያብራሩት የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍትት በቋንቋ ትምህርት ፕሮግራም ያላቸው

15
ሚናና ድርሻ ከፍተኛ ነው፡፡ የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍትቱ በመምህሩ ወይም በተወሰነ ተቋም
የተዘጋጁ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ Richards and Rogers (1996) Sheldon (1987) ን ዋቢ በማድረግ
እንደሚያብራሩት የህብረተሰቡን የዕድገት ደረጃ፣ የኑሮ ሁኔታ፣ ወግ፣ ባህል፣ አስተሳሰብና ፍላጎት
ወዘተ. ግምት ውስጥ በማስገባት ወይም ትኩረት በመስጠት የሚዘጋጁ የቋንቋ መማሪያ
መፃሕፍትት ከፍተኛ ጠቀሜታ ስለሚሰጡ አስፈላጊነታቸውን አፅንዖት በመስጠት ገልፀዋል፡፡
ይህም በመሆኑ ነው Cunning worth (1995) የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ጥሩ አገልጋይ ነው
በማለት የገለፁት፡፡

2.2.1 የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍትት ውስጣዊ ይዘት


የቋንቋ መማሪያ መፅሀፍ ውስጣዊ ይዘት ሲመረጥ ምን ምን ጉዳዮችን ማካተት እንዳለበትና
ምንን መስፈርት መሰረት አድርጎ መምረጥ እንደሚገባው ምሁራን ይገልጻሉ፡፡ ስለዚህም በመርሃ
ትምህርቱም ሆነ በመማሪያ መፅሃፍ ውስጥ የአንድ የቋንቋ ትምህርት ይዘት ከመመረጡ በፊት
ሊተኮርባቸው የሚገቡ ነጥቦች መኖራቸው መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ እንደ yalden (1987) አገላለፅ
ለቋንቋ ትምህርት ይዘት መረጣ መሰረታዊ ጉዳዮች ናቸው ያሏቸውን እንደሚከተለው
ያስቀምጣሉ፡፡የቋንቋ ትምህርት ሲመረጥ የቋንቋው ተማሪ ዕድሜ የእውቀት ደረጃ ሁኔታ ፍላጎት
ወ.ዘ.ተ ለትምህርት የተጠና ሊሆን ይገባል፡፡ የቋንቋ ትምህርቱ በሚመረጥበት ጊዜ በመርሃ
ትምህርቱ ውስጥ የተነደፈውን ዝርዝር አጠቃላይ አላማ ከግምት ውስጥ ያስገባ ሊሆን ይገባል፡፡
የሚመረጠው የቋንቋ ትምህርት ውስጣዊ ይዘት ከተነደፈው የመርሃ ትምህርት አይነት ጋር
የሚጣጣም የሚስማማ መሆን አለበት፡፡ ምክንያቱም የሚነደፈው መርሃ የትምህርት አይነት
የሚጣጣመውን ይዘት ስለሚወሰ ነው፡፡ ይህንንም ሃሳብ ለማጠናከር ያህል የቋንቋ መርሃ
ትምህርት አነዳደፍ በይዘት አመራረጡ እንደሚወሰነው እና በዋናዋና ጉዳዮዎች ላይ ማተኮሩ
የትምህርቱን ዓላማ ከግብ እንደሚያደርሰው ሳሙኤል (2002፣20) በሞጅዩላቸው ያስቀምጣሉ፡፡
በቋንቋው ይዘትና በቋንቋው አጠቃለይ ባህሪ ወይም ተፈጥሮ ላይ የሚያተኩር የመርሃ ትምህርት
ንድፍ፣ በቋንቋው ተማሪና በቋንቋው ትምህርት አሰጣጥ ላይ የሚያተኩር የመርሃ ትምህርት
ንድፍ፣ የቋንቋው ተማሪ በበለጠ እንዲያዳብር የሚፈለገው የቋንቋ ክፍል ላይ የሚያተኩር የመርሃ
ትምህርት ንድፍ መሆን አለበበት፡፡ስለዚህ መርሃ ትምህርቱ ሲነደፍ አንዱን መሰረት ማድረግ
እንዳለበት ያስገነዝባሉ፡፡ በመሆኑም የመርሃ ትምህርቱ አነዳደፍ የቋንቋ ትምህርት ይዘቱን መረጣ
የተሳካ ያደርገዋል ማለት ነው፡፡

16
2.2.2 የቋንቋ መማሪያ መጻህፍት አዘገጃጀት
በአንድ አውድ ውስጥ በሚኖር የመማር ማስተማር ሂደት ውስጥ እንደትምህርቱ አይነት ታስቦና
ሆን ተብሎ የሚዘጋጅ የመማሪያ መጻህፍት መኖራቸው ግልጽ ነው፡፡ ከትምህርት አይነቶች አንዱ
ደግሞ የቋንቋ ትምህርት ነው፡፡

የቋንቋ መማሪያ መጻህፍትን በተመለከተ ከተለያዩ ምሁራንና መዝገበ ቃላት የተለያየ ብያኔ
ሰጥተዋል፡፡ እንደተስፋየ (1981) ትንተና የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት የቋንቋ ትምህርት ዓላማን
መሰረት በማድረግ በስርዓት የተደራጁና ስርዓት የጠበቁ ሆነው የቋንቋ ትምሀርት ይዘቶችን
በውስጣቸው ያካተቱ ሰነዶች ናቸው፡፡ Grant(1987) ደግሞ የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት የተደራጁ፣
የተመጠኑና የተውጣጡ የቋንቋ ትምህርት ይዘቶችን ከተማሪው አካባቢያዊና ዳራዊ እውቀት
አንጻር አካቶ በመያዝ የተነደፉ የቋንቋ ትምህርት አላማዎችን ከግብ ለማድረስ የተዘጋጁ ሰነዶች
እንደሆኑ ይገልጻሉ፡፡

Grant(1987) የቋንቋ መማሪያ መጻህፍትን ምንነት መሰረታዊ እሳቤ እንዲህ ሲሉ


ገልፀውታል፡፡አንድሰው ወደማያውቀው አካባቢ ለመድረስ የግድ መረጃ የሚሆነው የጉዞ ካርታ
እንደሚያስፈልገው ሁሉ የቋንቋ መማሪያ መጻሕፍትም የተማሪውን ወደ አላማው ግብ ለመድረስ
አስተማማኝ መሆኑና መሳሪያ በመሆን ለተማሪዎች የሚያስፈልጉ የትምህርት ካርታዎች
መሆናቸውን ይገልጻሉ፡፡ የቋንቋ መማሪያ መጻህፍትም መሰረት አድርገው የሚነሱት የቋንቋውን
ትምህርት አላማ ማዕከል ባደረገ መንገድ በስርዓተ ትምህርቱና በመርሀ ትምህርቱ ዝግጅትና
አደረጃጀት የሚካተቱ ይዘቶችን የያዙ ሰነዶች እንደሆኑ ይታመናል፡፡ Dubbin and olishtain (1986)
የጥንታዊና ዘመናዊ የቋንቋ መጻህፍትን በተመለከተ ሲገልጹ በጥንታዊ የቋንቋ መጻህፍት ውስጥ
ቋንቋን ማስተማር ሰዋሰውን እንደማስተማር ይቆጠር ነበር፡፡ ይህም ዋነኛትኩረቱ በሰዋሰው ላይ
ብቻ የሚያደርግ ነው፡፡ የመፅሐፉም የመጀመሪያ ተግባር ሰዋሰዋዊ መጻህፍትን በትኩረት መዳሰስ
ላይ ነው፡፡ በዘመናዊ የቋንቋ መማሪያ መጽሐፍ ደግሞ ለተማሪዎች ምቹና ተስማሚ በሆነ መልኩ
ማዘጋጀት ሲሆን ገፀባህሪያትን በመወከል ቋንቋው ማስተማር ላይ ተዝናኖታዊ ትምህርትን
ይፈጥራል፡፡ ምዕራፎቹም የተዋቀሩት ከምንባቦች፣ ከሰዋሰው አጫጭር ጽሁፎች፣ የንበት ልምምድ
ተግባራትን በማስፈጸም ላይ ነው፡፡ ተማሪዎች የሚያከናውኗቸውን ተግባራት በጥንድና በቡድን
በመሆን ችግሮች መፍትሄ እንዲያገኙ ትዕዛዝ መስጠትን ሁሉ መማሪያ መፅሐፉ ያጠቃልላል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ አራቱን ክሂሎች ከማዳበር አንጻር የተለያዩ ተግባራትን ይይዛል፡፡

17
የቋንቋ መማሪያ መጻህፍት ለተማሪው ብቻ ሳይሆን ለመምህሩም ጠቃሚ ነው፡፡ ምክንያቱም
የቋንቋውን ይዘት ደረጃ በደረጃ ለማስተማር የሚቻለው በዚህ መጽሐፍ ነው፡፡ ስለዚህ የቋንቋ
መማሪያ መፃሕፍት የትምህርቱን ሂደት የሚመራ፣ ለጥናቱ እንደዋነኛ ምንጭ የሚያገለግል፣
ለተማሪውም ሆነ ለመምህሩ ጠቃሚ የተግባር መመሪያ በመሆኑ ከተለያዩ የቋንቋ ማስተማሪያ
መሳሪያዎች ጥቅም አንጻር ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል፡፡

እንደተስፋየ (1981) ለትምህርት የቀረበው ቋንቋ ማስተማሪያ የሚሆኑ ደረጃቸውን የጠበቁ


መጻህፍት መገኘት የመምህሩን ስራ የሚያጠናክር ይሆናል፡፡ ተማሪው የተለያዩ መጻህፍትን
ሲያነብ ከተለያዩ ይዘቶች ጋር ለመተዋወቅ ብቻ ሳይሆን ከተለያዩ የአጻጻፍ ስልቶችም ጋር
ለመተዋወቅ ይረዳል፡፡ በዚያውም ልክ አስተሳሰቡ ሲሰፋ የቋንቋ ችሎታው ሊዳብር ይችላል
ይላሉ፡፡ በቋንቋ ትምህርት ውስጥ የቋንቋን መማሪያ መጻህፍት የማይተካ ሚና ቢኖራቸውም
እነዚህ መጻህፍትን የሚያግዙና የሚያዳብሩ ተጨማሪ ጽሁፎች፣ መልመጃዎችና ሌሎች አጋዥ
የማስተማሪያ መሳሪያዎቸ በመማር ማስተማሩ ማካተት ውጤታማ ያደርጋል፡፡

እንደ Cunningsworth(1995) አገላለጽ የተመረጡና የተቀነባበሩ የቋንቋ ትምህርት ይዘቶች


የሚከተሉትን ነጥቦች ያገናዘበ ሊሆን ይገባል፡፡ እነሱም፡- የቋንቋን አላማና ጭብጥ ለማግኘት
ምንጭ የሆኑ ይዘቶች፣የተማሪውን ፍላጎትና እውቀት መሰረት በማድረግ ለተማሪው የመማር
ፍላጎት የሚፈጥሩ፣አራቱን የቋንቋ ክሂሎች አመጣጥኖ የሚያቀርብ፣የመፅሐፉ ይዘት እድገት
ከቀላል ወደ ከባድና ከቅርብ ወደ ሩቅ የተደራጀ፣የተማሪውን የመማር ዘዴ (ስትራቴጅ) የሚያሳይ
እና መምህራንና ተማሪውን በጋራ የሚያስተሳስር የሚያሳትፍ ወዘተ.. ናቸው፡፡ በቋንቋ መማሪያ
መጻህፍት ዝግጅት መረጣ ወቅት እንደመሰረታዊ ጉዳይ ታሳቢ ሆነው የሚታዩ መርሆዎች
የሚከተሉት ናቸው፡- የቋንቋ መማሪያ መጻህፍት ዝግጅት መረጣ (አደረጃጀት) የቋንቋ ትምህርቱ
በሚከተለው የትምህርት ፍልስፍና ወይም ትወራ ላይ እንደሚመሰረት መረዳት፣የቋንቋ መማሪያ
መጻህፍት ዝግጅት ታሪክ ከቋንቋ ፖሊሲ ጋር ሊኖር የሚገባውን ቀረቤታና ከዚህም አንጻር
ያለውን ፖለቲካዊና ማህበራዊ አገልግሎት ከአፍ መፍቻና ከሁለተኛ ቋንቋ አንጻር እንደሚታይ
መገንዘብ፣የቋንቋ መማሪያ መጻህፍት የተዘጋጁላቸው ተማሪዎች ዳራ፣ ባህል፣ ዕድሜ የእውቀት
ደረጃ፣ ተማሪው ቋንቋውን የሚማርበት ምክንያት ለተግባቦት ወይም ለስራ እንደሆነ ተለይቶ
መታየቱ አስፈላጊ መሆኑን ማወቅ፣ለአንድ የትምህርት አይነትና የክፍል ደረጃ አስፈላጊ ናቸው
ተብለው የሚዘጋጁና የሚመረጡ የቋንቋ መማሪያ መጻህፍት ሊያሟሉ የሚገባቸውን መመዘኛ
ባህሪያት ማለትም እውነተኛነት፣ ግልጽነት፣ ማራኪነት፣ አበረታችነት፣ ተጣጣሚነት፣ ጥልቀት

18
ተተግባሪነት (ተግባራዊነት) የሚሉትን ያካተተ መሆኑን በጥንቃቄ መለየት እንደሚገባ
መረዳት፣የቋንቋ መማሪያ መጻህፍት ዝግጅት ታሪክ ከባህላዊ (ጥንታዊ) እና ከዘመናዊ የቋንቋ
መማሪያ መጻህፍት አዘጋጆች ሞዴል አንጻር መታየት አንደሚኖርባቸው መርሆዎች ያዝዛሉ፡፡

2.3 የቋንቋ ትምህርት ይዘቶች አደረጃጀት


Taba (1962) እንደሚያስረዱት የትምህርት ይዘቶች የተቀናጀ ውጤት እንዲያስገኙ እርስ
በእርሳቸው ተደጋግፈው መደራጀት አለባቸው፡፡ አደረጃጀታቸውም ተዋረዳዊና ጎናዊ ግንኙነትን
የጠበቀ መሆን ይኖርበታል፡፡ የተለያዩ የክፍል ደረጃዎች የሚቀርቡ የትምህርት ይዘቶች ያላቸው
ግንኙነት በተዋረዳዊ ግንኙነት የሚነሳ ሲሆን ለምሳሌ ለስምንተኛ ክፍል የሚቀርቡ የትምህርት
ይዘቶች ከሰባተኛ ክፍል የቀረቡትን መሰረት አድርገው እንደሚደራጁ ያስገነዝባል፡፡ በተጨማሪም
የስምንተኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ ይዘቶች ከስምንተኛ ክፍል ሌሎች የትምህርት አይነቶች ጋር
የሚኖራቸውን ዝምድና ያመላክታል፡፡

Cunnings worth (1995) ይህንኑ በሚመለከት ሲገልጹ አንድ ትምህርት ከሌሎች የትምህርት
አይነቶች ጋር የሚኖረው ግንኙነት የትምህርት ይዘቶችን እርስበርስ በማደጋገፍ የተማሪውን
ብቃት ለማጎልበትና ለማሳደግ ያግዛል፡፡ ይህ ደግሞ ተማሪውን በትምህርቱ የሚተጋ ሊያደርገው
ይችላል፡፡ ለምሳሌ በአራተኛ ክፍል የሚሰጠው የአማርኛ ትምህርትና በአራተኛ ክፍል የሚሰጠው
የህብረተሰብ ትምህርት እንዲዛመዱ የተደረገ እንደሆነ አንዱ ሌላውን የሚያጎለብት ይሆናል፡፡
በዚህም ተማሪው በተለያዩ የትምህርት አይነቶች መካከል መሰረታዊ ቅንጅት እንዳለ ሊገነዘብ
ይችላል፡፡

Nunan (1988)' Cunnings worth (1984) እንደሚያብራሩት ደግሞ የቋንቋ ትምህርት ይዘቶች ተገቢ
በሆነ መልኩ ከተመረቱ በኋላ በቀጣይነት የሚመጣው ነገር አደረጃጀት ነው፡፡ የይዘት አደረጃጃት
በቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ውስጥ የተካተቱ ይዘቶች በምን ዓይነት ቅደም ተከተል መቅረብ
እንዳለባቸው፣ማን ቀድሞ ማን ተከትሎ መምጣት እንደሚኖርብት የሚያሳይ ነው፡፡ በተጨማሪም
የትምህርት ይዘቶች በምን አይነት ተደጋግሞ፣በስፋትና ጥልቀት እየጨመሩ መቅረብ እንዳለባቸው
ያሳያል፡፡ ይህም ማለት የትምህርት ይዘቶች፣ አደረጃጃት ከቀላላ ወደ ከባድ ፣ተጨባጭ ከሆነ ወደ
ረቂቅ፣ ከዝርዝር ወደ ጠቃላይ፣ ወዘተ. ሊሆን ይገባል፡፡

በተጨማሪም ተስፋዬ (1981፣35) እንደሚገልፁት አንድ የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት


ተገቢነት፣ግልፅነት፣ተከታታይንትና ተለጣጣቂነት ያለው ሆኖ መደራጀት እንደለበት ያስገነዝባሉ፡፡

19
Tyler (1949) በበኩላቸው ደግሞ የትምህርት ይዘቶች ውጤታማ ይሆኑ ዘንድ አንዱ ይዘት በሌላው
ይዘት ላይ ተመስርቶ መደራጀት ይገባዋል፤ የትምህርት ይዘቶችንም ለማደራጀት
ተከታታይነት፣ተለጣጣቂንትና ውህደት ያላቸው ዋናዎቹ መለኪያ መስፈርቶች መሆናቸውን
ይገልፃሉ፡፡የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ውስጥ የይዘት ማዋቀሪያ መስፈርቶችን ደግሞ
ዓለም(1995፣27-28) እንደሚከተው ይዘረዝሩታል፡፡ የትኛው የቋንቋ ትምህርት ለመማር ቀላል
ነው ይህን መሰረታዊ ጥያቄ የቋንቋውን ትምህርት ይዘት ከቀላል ወደ ከባድ፣ ከግልፅ ወደ
ውስብስብ፣ ከተጨባጭ ወደ ረቂቅ፣ ደረጃ በደረጃ እየዳበረ በሚሄድ መልኩ የተዋቀረ መሄድ
እንዳለብት ይጠቁማል፡፡ ተማሪው በቋንቋ ትምህርቱ መጀመሪያ ሊማር የሚገባው የትምህርት
ይዘት የትኛው ነው የዚህ ትኩረት ተማሪው መጀመሪያ ሊማር የሚገባውን በሚገባ አገናዝበው
ከለዩና ተከትሎ ሊመጣ የሚችለውንም በሚገባ ከመረመሩ በኋላ በቅደም ተከተላቸው በማስቀመጥ
ተጠየቃዊ አካሄድ እንዲይዝ መደረግ አለበት፡፡ ይህም የይዘት አወቃቀሩን አዎንታዊ መልክ
እንዲይዝ ያደርጉታል፡፡ አንዱን የቋንቋ ትምህርት ይዘት ለማስተማር የሚያግዙ ሌሎች የቋንቋ
ትምህርት ይዘቶች አሉ በቋንቋ ትምህርት ወቅት አንዳዴ የአንዱ ይዘት መጠቀስ የሌላውን ይዘት
መጠቀስ የግድ ሊጠይቅ የሚችልበት ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ ስለዚህ ተደጋግፈው መምጣት
የሚኖርባቸው የቋንቋ ትምህርት ይዘቶች ስለሚኖሩ እነዚህን ለይቶ በማውጣት በተገቢ ቦታቸው
ማዋቀርና ማቀናበር ይገባል፡፡ በመማሪያ ክፍል ለሚከናወነው የቋንቋ መማር ማስተማር ሂደት
አስፈላጊና ጠቃሚ የሆነ ድርሻ የሚኖረው ይዘት የትኛው ነው ይህ ማለት በመማሪያ ክፍል
ውስጥ ለሚከናወነው የመማር ማስተማር ሂደት ጠቃሚና አስፈላጊውን ይዘት ቀዳሚ ስፍራ
በመስጠት ተማሪዎቹ በቅድሚያ እንዲማሩዋቸው ማድረግ ነው፡፡ የቋንቋ ተማሪ በጣም
የለመደውና በጣም የሚያውቀው የትምህርት ይዘት የትኛው ነው? በዚህ መስፈርት ስር ሊታይ
የሚገባው በጣም ከለመደውና ከሚያውቀው የቋንቋ ትምህርት ይዘት ወደ አልለመደውና
ወደማያውቀው የቋንቋ ትምህርት ይዘት የተዋቀረ መሄድ እንዳለበት ያሳያል፡፡ ይህም በቀጥታ
ያለመደውንና የማያውቀውን አዲስ የቋንቋ ትምህርት ይዘት በድንገት ከማምጣት ይልቅ
በለመደውና በማያውቀው የቋንቋ ትምህርት ይዘት በመንደርደር ወደ አልለመደውና የማያውቀው
መሻገር አግባቢነት ያለው የይዘት አወቃቀር ሂደት በመሆኑ ነው፡፡ ለቋንቋ መአስተማሪያነት
የሚመረጡ የሚመረጡ ይዘቶች ተገቢውን የትምህርት ዓላማ ለማሳካት ብቃት እንዲኖራቸው
በዕውቀትና ልማድ ላይ ተደራጅተው መቅረብ አለባቸው፡፡ ምክንያቱም ዓላማን መሰረት አድርገው
የቀረቡ የትምህርት ይዘቶች ለተማሪዎች የተፈለገውን ዕውቀት ማስጨበጥ ይችላሉ፡፡
በተጨማሪም በመማሪያ መፃሕፍት ዝግጅት ወቅት የተለያዩ ይዘቶች ይመረጡና አግባብ በሆነ

20
መንገድ ይደራጃሉ፡፡ ማለትም የስነ ልሳንና የቋንቋ አገልግሎት፣ የቋንቋ ክሂሎች የተመለከቱ
ይዘቶች አግባብ ባለው ሁኔታ በሚተገበሩት መንገድ በመፃሕፍት ውስጥ ተደራጅተው ሊቀርቡ
ይገባል፡፡ ከዚህ አንፃር የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ሲዘጋጃ የተማሪውን የቋንቋ ክሂሎች የስነ
ልሳንና የስነፅሑፍ ዕውቀቶችን ለማጎልብት የሚያስችሉ ልዩ ልዩ ይዘቶች በምንባብና
በመልመጃዎች ላይ ለመስርተው ለተጨማሪ ልምምድ የሚያነሳሱ መረጃዎችን በመጠቀም
ተደራጅተው መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡

አንድ መማሪያ መፃሐፍ ሲዘጋጅ በውስጡ የሚያካትታቸውን ይዘቶች በስርዓት አደራጅቶ ማቅረብ
ይኖርበታል፡፡ ይዘቶችን በወጉ ለማደራጀት ጎናዊና ተዋረዳዊ ዝምድናቸውን የጠበቀ ማድረግ
ያስፈልጋል፡፡ የይዘቶች ተዋረዳዊ ዝምድና ማስጠበቅ የሚቻለው እንደይዘቱ ስፋትና ጥልቀቱን
እያሳደገ በመሄድ በአንድ መማሪያ መፃሐፍም ይሁን ለተከታታይ የክፍል ደረጃዎች በተዘጋጁት
ውስጥ ተደጋግፎና ተደጋግሞ ሲቀርብ ነው፡፡ የይዘቶች ጎናዊ ዝምድና ከተለያዩ የትምህርት
አይነቶች ጋር ያላቸውን ግንኙነት የሚመለከት መሆኑን Tyler(1949)፣ Larsen(1991)እና Cunnings
worth(1984)ገልጸዋል፡፡ አያይዘው የይዘቶች ማደራጃ መርሆዎች ተከታታይነት፣ ተለጣጣቂነትና
ውህዳዊ እንደሆኑ አስረድተዋል፡፡ ይህ ጥናት ይዞት ከተነሳው አላማ አንፃር በተለያዩ ትምህርቶች
መካከል ያለውን ዝምድና በመተው በአንድ የትምህርት አይነት በመማሪያ መፃሐፍ ውስጥ ሲቀርብ
ይዘቶች የሚደራጁበት ስርዓት በተመለከተ ብቻ አስፈላጊ የሆኑትን ይመለከታል፡፡Yalden (1987)
የትምህርት ዓላማዎች ከተነደፉና ይዘቶች ከተመረጡ፣ ቀጣይ ክንውን ይዘቶች በቅደም
ተከተል በጥንቃቄ እንዲደራጁ መደረግ አለበት በማለት ይገልፃሉ፡፡

2.3.1 ተከታታይነት (Continuity)


Tyler (1949) ገለፃ ተከታታይነት በአንድ መማሪያ መፃሐፍ ውስጥ የቀረቡ ይዘቶች በሚቀጥሉት
ምዕራፎች እየተከታተሉ መምጣቱን የሚመለከት ነው፡፡በይዘቶች መካከል ያለው ድግግሞሽም
ተማሪዎቹ የተማሩትን ትምህርት የበለጠ እያጠናከሩት እንዲሄዱ ይረዳቸዋል፡፡ትምህርት ረዥም
ጊዜና የማያቋርጥ ክትትል የሚያሻው ጉዳይ እንደመሆኑ ውስን የትምህርት ይዘት የተፈለገውን
የትምህርት ዓላማ ግቡን ይመታል ተብሎ ስለማይታሰብ ተማሪዎች የተፈለገውን ለውጥ ያመጡ
ዘንድ ተደጋጋፊነት ያላቸው የትምህርት ልምዶች እየተደገሙ ደረጃ በደረጃ መቅረብ
ይኖርባቸዋል፡፡ ይህም መሆኑ ተማሪዎቹ ካላቸው የቀደመ ዕውቀት በመነሳት በትምህርቱ ሂደት
ጥልቅ ዕውቀትን እንዲጨብጡ ያስችላቸዋል፡፡ ይህንንም ሀሳብ Nunan (1988) እንደሚያጠናክሩት
ተመሳሳይ የሆኑ የቋንቋ ትምህርት ይዘቶች ሳይዘበራረቁ ወይም ሳይቆራረጡ በየክፍል ደረጃዎቹ

21
እንደተማሪዎቹ ማንነት ተሳስረው መሄድ የሚችሉ ከሆነ የተማሪዎቹ ግንዛቤ በሂደት
እንዲጨምር አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡ Reid (1999) ደግሞ ይዘቶች በቅደም ተከተል መደራጀታቸውን
መገምገም ይገባቸዋል፡፡ ይዘቶች የተማዎችን ዕድሜ፣የክፍል ደረጃ፣ ፍላጎት፣የዕውቀት
ዳራ፣ወዘተ.መደራጀት ይገባቸዋል፡፡ በተጨማሪም ከትምህርቱ ውስብስብነት አንፃር ከቀላሉ በመጀመሪያ
ወደ መካከለኛውና ክብደት ወደ አላቸው ይዘቶች አደራጅቶ መግለፅ አስፈላጊ ነው፡፡ ይህን ገምግሞ
የይዘቶችን ቅደም ተከተል ከስነ ትምህርታዊ፣ ስነልቦናዊ ተጠየቃዊነት አንፃር ከቅርብ ወደ ሩቅ፣ ከቀላል
ወደ ከባድ፣ወዘተ. መደራጅት አለባቸው፡፡ ተስፋዬ (1981) ተከታታይነት ሲባል በአንድ የትምህርት

ዓይነት ውስጥ በየክፍል ደረጃው እየተደጋገመ የሚመጣ ነገር ነገር ግን የተማሪዎችን ክፍል
ደረጃ ጠብቆ የሚሄድ አደረጃጀት ነው፡፡ ይህን በምሳሌ ለማየት ብንሞክር በማንኛውም ደረጃ
ከ1ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል በአማርኛ ትምህርት ለአንብቦ መረዳት ክሂል ማስተማሪያነት
የሚውሉ ምንባቦች ይዘጋጃሉ፡፡ በየትኛውም የክፍል ደረጃ ምንባቦች አሉ ማለት ነው፡፡ በዚህ
ምክንያት ነው ተደጋግሞ የሚመጣ የተባለው፡፡ነገር ግን ምንባቦቹ በምንባብነታቸው ተደጋግመው
ይምጡ እንጅ ይዘታቸው የክፍል ደረጃውን የጠበቀና ተማሪዎችም በክፍል ደረጃው የሚጠበቀውን
ዕውቀት እንዲያገኙ በማድረግ ይዘጋጃሉ፡፡ የተከታታይነትን ምንነት በዚህ መልክ ካየን
መልመጃዎችም የሚዘጋጁት የተሰጠውን ትምህርት የበለጠ ለማዳበርና ለማጎልበት የሚረዱ
መልመጃዎች በመሆናቸው የይዘት አደረጃጅታቸው የትምህርቱን ይዘት *ተከትለው ይደራጃሉ ፡፡
ይህውም በአንድ የትምህርት አይነት በየክፍል ደረጃው እየተደጋገመ የሚመጣ የመልመጃ ይዘት
የሚመለከት ሆኖ ነገር ግን የክፍል ደረጃውን የጠበቀና ተማሪ ዎቹም በክፍል ደረጃው
የሚጠበቀውን እውቀት ለማስጨበጥ እንዲረዱ ሆነው የሚዘጋጁ መልመጃዎች ናቸው ፡፡
በተጨማሪም በቋንቋ ትምህርት ውስጥ ተማሪዎች ሊያዳብሯቸው የሚገቡ ክሂሎች እና የዕውቀት
ዘርፎች አሉ፡፡ ተማሪዎቹም፣ እነዚህን ክሂሎች እና የዕውቀት ዘርፎች ዓላማዊ በሆነ መንገድ
እንዲማሩ በየክፍል ደረጃቸው ሊያሳኩ የሚችሉ የትምህርት ይዘቶችን አደራጅቶ ማቅረብ አስፈላጊ
ነው፡፡ ይህም ማለት በአንዱ የክፍል ደረጃ የተካተተው ይዘት ቀጣይ የክፍል ደረጃ ላይ ተጠይቃዊ
በሆነ መልኩ በማስገባት ማደራጀት ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም ቀጣይነት የሚለው የማደራጃ
መስፈርት የሚያመለክተው በተለያየ የትምህርት የክፍል ደረጃዎች ለሚገኙ ተማሪዎች ተመሳሳይ
የትምህርት ዓይነት ወይም ይዘት እንደየክፍል ደረጃቸው መጥኖ መቅረብ አስፈላጊ እንደሆነ ነው፡፡
ለምሳሌ ያህል የአስረኛ ክፍል ተማሪዎች ከሰዋስው የትምህርት ይዘቶች ውስጥ በዓረፍተ ነገር
መዋቅር ውስጥ ስለሚኖሩ ባለቤት፣ ተሳቢ እና ማሰሪያ አንቀጽ የተመለከተ ተካቶ ቢቀርብ፤
በአስራ አንደኛ ክፍልም ይህኑ ይዘት ጠለቅ ባለ መልኩ እንዲካተት ማድረግ አስፈላጊ እንደሆነ

22
የሚያሳይ ነው፡፡ ይህም መሆኑ ተማሪዎቹ ካላቸው የቀደመ ዕውቀት በመነሳት በትምህርቱ ሂደት
ጥልቅ ዕውቀትን እንዲጨብጡ ያስችላቸዋል (Tyler 1949)፡፡

2.3.2 ተለጣጣቂነት (Sequence)


Larsen(1991)እና Tyler(1949) ገለፃ ተለጣጣቂነት ተዋረዳዊ የትምህርት ይዘቶች አደረጃጀትን
የሚመለከት ነው፡፡ ለተከታታይ ክፍል ደረጃዎች በሚዘጋጁ ክፍል ደረጃዎች በሚዘጋጁ መማሪያ
መፃሕፍት ውስጥ የሚገኙ ይዘቶች ያላቸውን ተዋረዳዊ ዝምድናና ተደጋጋፊነት የሚመለከት
ነው፡፡ይህም ብቻ ሳይሆን ይዘቶች እርስ በእርስ ተያይዘው በመሄድ የተማሪው የቋንቋ ደረጃ እያደገ
በሄደ ቁጥር በመማሪያ መፃሕፍት ውስጥ ያሉ ይዘቶችም ስፋትና ጥልቀት እያገኙ እንዲሄዱ
የሚደረግበት አደረጃጀት ነው፡፡

Tyler(1949) ተመሳሳይ የሆኑ የትምህርት ይዘቶች በአንድ የክፍል ደረጃ ላይ በተለያየ አቀራብ
ተደጋግመው መቅረብ እንደሚኖርባቸው ይገልፃሉ፡፡ የትምህርት ይዘቶቹ በአንድ የክፍል ደረጃ
ላይ ተደጋግመው በሚቀርቡበት ጊዜ ግን ስፋታቸው እና ጥልቀታቸው በተለያየ መንገድ ሊደራጁ
ይገባል፡፡ በዚህ መልኩ የመማሪያ መጽሐፍት መደራጀት ከቻሉ በመማር ማስተማሩ ሂደት
ተማሪዎቹ ተመሳሳይ የትምህርት ይዘቶችን በተለያዩ ምዕራፎች ላይ ማግኘት የሚችሉ በመሆኑ
ይዘቱን በጥልቀት እንዲረዱት አስተዋጽኦ ያደርግላቸዋል፡፡ ተስፋዬ (1981) ተለጣጣቂነት የሚለው
ከተከታታይነት ጋር የሚዛመድ ቢሆንም ልዩነት ግን አላቸው፡፡ ልዩነታቸው ተለጣጣቂነት
በስርዓተ ትምህርት የሚቀርብ የትምህርት ጉዳይ በየደረጃው ስፋትና ጥልቀት እያገኘ እንዲሄድ
የሚመራ ነው፡፡ የተለጣጣቂነት ትኩረት የትምህርት ይዘቱ ድግግሞሽ ላይ ሳይሆን በየክፍል
ደረጃው የሚቀርበው ትምህርት እንደደረጃው እየሠፋና እየጠለቀ መሄዱን የሚመራ ነው፡፡
ተለጣጣቂነት በአንድ የክፍል ደረጃ በአንድ የትምህርትዓይነት ያሉት ምዕራፎች መካከል ያለውን
ስፋትና ጥልቀት፣ ክብደትና ቅለት ተጨባጭ ከሆነው ወደ ረቂቁ የሚሄደውን አካሄድ የሚመራ
ሲሆን ከመጀመሪያው ምዕራፍ የሁለተኛ ከሁለተኛው ምዕራፍ የሶስተኛ እያለ ከቀላል ወደ ከባድ፣
ከጠባብ ወደ ሰፊ፣ ከተጨባጭ ወደ ረቂቅ መሄድ እንዳለበት የሚዋቀር ነው፡፡ እንዲሁም ከአንዱ
የክፍል ደረጃ ወደሚቀጥለው የክፍል ደረጃ በሚጓዝበት ጊዜም ይዘቱ ከጠባብ ወደ ሰፊ፣ ከቀላል
ወደ ከባድ፣ ከተጨባጭ ወደ ረቂቅ መሄድ እንዳለበት እንደ መሪ ሆኖ የሚያገለግል አወቃቀር
ነው፡፡ በምሳሌ ሲብራራ የ4ኛ ክፍል የአማርኛ ትምህርት ምዕራፍ ሁለት ያለው የትምህርት ይዘት
ምዕራፍ አንድ ካለው፣ ምዕራፍ ሶስት ያለው ምዕራፍ ሁለት ካለው፣ ምዕራፍ አራት ያለው
ከምዕራፍ ሶስት ካለው የትምህርት ይዘት ከቀላል ወደ ከባድ፣ ከጠባብ ወደ ሰፊ፣ ከተጨባጭ

23
ወደ ረቂቅ ይሄዳል ማለት ነው፡፡ ተለጣጣቂነት ይህን ከመሰለ የመልመጃዎች ይዘት አደረጃጅት
ከተለጣጣቂነት አንፃር ስናየው ከተከታታይነት ጋር የሚመሳሰል ቢሆንም ልዩነቱ ግነ የቋንቋ
መልመጃችን ይዘቶች ሲደራጁ ትኩረቱ ከምዕራፍ ምዕራፍ ያለውንና ከክፍል ክፍል ያለውን
የመልመጃዎች ስፋትና ጥልቀት የሚመለከት ነው፡፡

2.3.3 ውህድነት (Integration)


Tyler(1949) እንደሚገልጹት ውህድነት በተለያዩ የትምህርት ዓይነቶች መካከል ያለውን ጎናዊ
ግንኙነት በማጤን የማደራጀት ተግባር የሚከናወንበት ሂደት ነው፡፡ ለምሳሌ በአማርኛ ቋንቋ
ውስጥ ያለ አንድ የትምህርት ይዘት፣ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ውስጥ ካለ ተቀራራቢ የትምህርት ይዘት
ጋር ተደራጅቶ በተመሳሳይ የትምህርት ወቅት የመማር ማስተማሩ ሂደት ቢከናወን ተማሪዎቹ
ስለአንድ የትምህርት ይዘት በሁለቱም የትምህርት ዓይነቶች ላይ ማግኘት የሚችሉት ዕውቀት
ወይም ክሂል በመኖሩ ግንዛቤያቸው እንዲሰፋ የበኩሉን አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡ በመሆኑም
ውህድነት በአንድ የክፍል ደረጃ በተለያዩ የትምህርት ዓይነቶች መካከል ያለውን ጎናዊ ግንኙነት
በማጤን የማደራጀት ተግባር የሚከናወንበት ሂደት ነው፡፡ Reid (1999) ደግሞ ይዘቶች የመርሃ
ትምህርቱ ጎናዊ ዝምድናቸው መገምገም ይጋባቸዋል፡፡ በአንድ የክፍል ደረጃ ባሉት የትምህርት ዓይነቶች
መካከል ዝምድና ሊኖር አስፈላጊ ነው፡፡ ምክንያቱም ለተማሪውም ሙሉና ጥምረት ያለው ዕውቀት ሊያስገኝ
ስለሚችል ነው፡፡ በአንድ የትምህርት ዓይነት ውስጥ ያለው ትክክለኛ መረጃ በዚህ የትምህርት ዓይነት
ብቻ ሊጎለብት አይችልም፡፡ በሌላ አባባል በአንድ የትምህርት ዓይነት የተገለፀ መርሆዎች ንድፈ ሀሳቦች
በሌላው የትምህርት ዓይነት ከሚገለፁት ጋር የሚስማሙ ሊሆኑ ስለሚገባ መጣጣም ያለባቸውና
የማይቃረኑ ሃሳብ መሆናቸውን መርምሮ ማስተካከል አስፈላጊ ነው፡፡ ተስፋዮ(1981) የውህደት
ምንነት ሲገልፅ “ውህደት የሚባለው በስርዓተ ትምህርት ውስጥ ያሉትን የትምህርት ልምዶች
መስመራዊ ግንኙነት የሚመለከት ነው፡፡ውህደት የትምህርት ልምዶች ቅንብር ፣ የትምህርት
ልምዶችን የርእስ በእርስ መደጋገፍ፣ የትምህርት ልምዶች አንዱ ሌላውን የማዳበርና
የማበልፀግ ጉዳይ የሚያተኩር ነው፡፡” በማለት ይገለፃል፡፡ ውህደት በስርዓተ ትምህርቱ ውስጥ
ያሉተን የትምህርት ይዘቶች መስመራዊ ግንኙነት የሚመለከት ነው፡፡ ተዋህዶ አወቃቅር
የትምህርት ይዘቶች ቅንብር የይዘቶችን የእርስ በርስ መደጋገፍ አንዱ የትምህርት ይዘት ሌላውን
የትምህርት ይዘት የሚያዳብርና የሚያጐለብት እንጅ አንዱ ሌላውን የሚያፈርስ፣ የሚቃወም
መሆን የሌለበት መሆኑን የሚመለከት አወቃቀር ነው፡፡

24
2.4 የክሂሎችና የችሎታዎች አደረጃጀት እና አቀራረብ
በቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ውስጥ የሚቀርቡ ይዘቶች ከሚኖራቸው ዋና ዋና ዓላማዎች መካከል
አንዱ የተማሪዎችን የቋንቋ ክሂሎች ማጎልብት ነው፡፡ ለዚህ ሁኔታ ደግሞ አበይት ንዑሳን
ክሂሎች በተመጣጣኝ ደረጃ ተዋቅረው በመማሪያ መፃሕፍት መገለፅ ይኖርባቸዋል፡፡ ምክንያቱም
ክሂሎችን በተመጣጠነ መንገድ አዋቅሮና አደራጅቶ ማቅረብ ለማህበራዊ ተግባቦት የቋንቋ
አጠቃቀም ትግበራ ጉልህ ሚና ይኖረዋል፡፡ ለዚህም Gower (1995) ክሂሎችን አመጣጥኖ በማዋቀር
አደራጅቶ ማስፈር ተግባራዊ ለሚደረገው የቋንቋ ትምህርት መሠረታዊ ጉዳይ እንደሆነ
የሚገልፁት፡፡ምንም እንኳን ክሂሎች ተቀናጅተው መዋቅርና መደራጀት እንደሚገባቸው ከዚህም
በላይ በቀረበው ሃሳብ የተገለፀ ቢሆንም የአደረጃጀት ስርዓታቸው ምን እንደሚመስል ለመግለፅ
እንዲመች አበይትና ንዑሳን ክሂሎች በሚል ከፋፍለን እንመልከት፡፡

2.4.1 የክሂሎች አደረጃጀት እና አቀራረብ


አበይት የቋንቋ ክሂሎች ሲባል አራቱን የቋንቋ ክሂሎች ማዳመጥ፣መናገር፣ማናበብና መፃፍን
የሚሉትን ያጠቃልላል፡፡ እነዚህ ክሂሎች በተናጥል ሲገለፁ ይደመጡ እንጂ በተግባቦት ግልጋሎት
ጊዜ አንዱን የቋንቋ ክሂል ያለ ሌላው አገልግሎት ላይ ሊውል አይችልም፡፡ ይህም ማለት በቃል
ምልልስ ወቅት አንድ ተናጋሪ ሲናገር ሌላው ያዳመጠውን ማስታወሻ ሊይዝ ይችላል፡፡ ከዚህ
ሃሳብ የምንገነዘበው ፍሬ ነገር ቢኖር አብይ የቋንቋ ክሂሎች በአንድ ጊዜ ተግባቦታዊ አውድ ውስጥ
ሳይነጣጠሉ አገልግሎት ላይ መዋላቸውን እንገነዘባለን፡፡ በቋንቋ መማር ማስተማር ትግበራ ላይ
አንደኛውን የቋንቋ ክሂል ለማስተማር በሚታቀድበት ጊዜ ትኩረቱ በዚያ ክሂል ላይ እንደሆነ
ለማመልከት እንጅ ብቻውን ነጥሎ ማስተማር ይቻላል ማለት አይደለም፡፡ ለምስሌ የማዳመጥ
ክሂል ለማስተማር በታቀደና በክፍል ውስጥ ትግበራ ቢካሄድ ተማሪዎች ባዳመጡት ርዕሰ ጉዳይ
ላይ ተመስርተው በተለያየ መንገድ ሃሳባቸውን በንግግር ይገልፃሉ፡፡ በራሳቸው አገላለፅ
አስፋፍተው ወይም አሳጥረው በመፃፍ ለክፍል ጓደኞቻቸው በንባብ ሊያቀርቡ ይችላሉ፡፡ ይህም
ተግባራዊ እንዲደረግ ከቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት የቋንቋ ክሂሎችን በተዋሃደ መንገድ
የሚያለማምዱ ተግባራት ማዘጋጀት ይኖርባቸዋል፡፡ ይህን ሀሳብ አስመልክቶ Byrne (1981)
በሚዘጋጀው የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት በአንድ የቋንቋ ትግበራና በሌላው መካከል ቁርኝት
እንዲኖር ማቀድና ተፈጥሯዊ በሆነ መንገድ የቋንቋ ክሂሎችን ማለማመድ የሚቻልበትን ሂደት
መቅረፅ የመማሪያ መፃሕፍት አዘጋጆች ተግባር እንደሆነ በመግለፅ ያጠናክሩታል፡፡ ከዚህም የተነሳ
የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ሲዘጋጅ ተማሪ ተኮር የመማር ማስተማር ሂደትን መነሻ በማድረግ
የተለያዩ የቋንቋ ይዘቶችን ከስነፅሁዊ ስራዎች ጋር አዋህዶ ማቅረብ ክሂሎችን በቅንጅት

25
ለማስተማር ዕድል ይሰጣል፡፡ ይህንንም ሃሳብ አስመልክቶ Celce Murcia (1991) ክሂሎች ሲደራጁ
ይዘት ተኮር ቁምነገሮችን፣የተማሪውን ልምድና ስነፅሁፍን መሠረት በማድረግ ክሂሎችን አቀናጅቶ
ማቅረብ ለመማር ማስተማር ክንውን ጠቀሜታ እንደሚፈጥር ይጠቁማሉ፡፡ ከላይ ከቀረቡት
ገለፃዎች የምንገነዘበው ነገር ቢኖር ጥሩ የተግባቦት ችሎታዎች ሊኖር የሚችለው ተማሪዎች
በሚፈጠርላቸው አውድ አማካኝነት የክሂሎችን አቀናጅቶ ለመጠቀም የሚያስችሏቸው ተግባራት
በጥንቃቄ ተሰናድተው ሲቀርብላቸው ብቻ ነው፡፡ ስለዚህ የመማሪያ መፃሕፍት አዘጋጆች
አመንጪና ተቀባይ ክሂሎችን ትኩረት በመስጠት የቋንቋ ክሂሎችን ማደራጀት ይገባቸዋል፡፡

2.4.1.1 የማዳመጥ የክሂል አደረጃጀት እና አቀራረብ


አዳምጦ መረዳትን ለማስተማር የሚዘጋጁ የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍትት የሚደመጠውን የቋንቋ
ይዘትና የሚተገበረውን ተግባር ማካተት አለበት፡፡ ይዘቶቹ ሲዳራጁ የማዳመጥ ክሂሎችን ርዕሰ
ጉዳይ እና የአድማጩን ሚና የሚደመጠውን አሃድ ዓይነት ከግምት ውስጥ ማስገባት አግባብ
እንደሆነ McDonough and Shaw (1991) ያብራራሉ፡፡ እንዲሁም በቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ውስጥ
የሚካተቱ ይዘቶች የማዳመጥ ትምህርት መልመጃዎች ሲሆኑ የአቀራረብ ደረጃዎችን መሠረት
አድርገው መደራጀትና መገለፅ ይኖርባቸዋል፡፡ የማዳመጥ ክሂልን ለማዳመጥ የሚያስችሉ
መልመጃዎችን ለማዘጋጀት ሲታሰብ መሠረት ሊደረጉ የሚገባቸው ነጥቦች ዓለም (1995፣20-
21) እንደሚከተለው አሰፍሯቸዋል፡- ያዳመጡትን ፅሁፍ ተግባር(መዝርዝራዊ፣ ቀስቃሽ፣ወዘተ.)
የሚጠይቁ መልመጃዎች እንዲታከሉ በማድረግ፣ የሚደመጠውን ቁም ነገር መሰረት በማድረግ
እንዲተነበዩና እንዲገምቱ የሚረዱ ጥያቄዎችን ማዘጋጀት፡፡ ከሚደመጡ የሰዎች ንግግር በመነሳት
ቀጥሎ ምን ሊሆን እንደሚችል የሚገምቱበትን መንገድ የሚያመቻቹ የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎች
መታከላቸውን ማረጋገጥ፣ከተደመጠው ጉዳይ ላይ ዕውነታነታቸውን መዘው እንዲያወጡ
ማድረግ፣ለማዳመጥ በቀረበው ጉዳይ ላይ ማን ምን ተናገረ በሚል የሚጠይቁ መልመጃዎችን
ማከል፣አዝናኝ ፅሁፎችን አንብበው ያስደሰታቸውን፣የተለየ ስሜት የፈጠረባቸውን ጉዳይ ምን
እንደሆነ በፅሁፍ ወይም በቃል እንዲያቀርቡ የሚጠይቁ መልመጃዎችን ማካተት፣ የተለያዩ
የአዳምጦ መረዳት መልመጃ መንገዶችም አሉ፡፡ ስለዚህ ጥያቆዎችን በተለያዩ የአቀራረብ መንገድ
ለማቅረብ መሞከር አስፈላጊ ይሆናል፡፡ ጥያቄዎቹ የተገለፁበት ቋንቋ ከተደመጠው የፅሁፍ ቋንቋ
የከበደ ወይም የጠነከረ መሆን የለበትምና ወዘተ.ናቸው፡፡ ከዚህ በላይ በተገለፀው ሁኔታ
የሚቀርቡት የአዳምጦ መረዳት ጥያቄዎች በቃል ወይም በፅሁፍ ሊቀርቡ ይችላሉ፡፡
አቀራረባቸውም በክፍት አጠያየቅ፣ እውነት ሐሰት በል፣ ምርጫ ሊሆን ይችላል፡፡ የማዳመጥ
መልመጃ ይበልጥ ውጤታማ የሚሆነው በቀጥታ ምላሽ ከሚጠይቁ ጉዳዮች ጋር ሲያያዝ ነው፡፡

26
ለዚህም ሲባል ተማሪዎች ካዳመጡ በኋላ ምላሽ የሚሰጡበትን መንገድ አብሮ መቀየስ
ይኖርበታል፡፡ ለዚህም ካዳመጡ በኋላ ምላሽ የሚሰጡበትን መንገድ አብሮ መቀየስ ይኖርበታል፡፡
ካዳመጡ በኋላ መስማማት አለመስማማታቸውን እንዲገልጹ ማድረግ፣ማስታዎሻ እንዲወስዱ
ማድረግ፣ወዘተ. በማለት የማዳመጥ ክሂልን የሚያዳብሩ መልመጃዎች በምን ዓይነት ሁኔታ
መቅረብ እና መደራጀት እንዳለባቸው በሰፊው አትተዋል፡፡

Under Wood (1989)አገላለፅ ተማሪዎች ተገቢውን የማዳመጥ ክሂላቸውን በተገቢው መንገድ


ለማስጨበጥ ይችሉ ዘንድ የርዕሰ ጉዳዮቹ ይዘቶች የሚቀርቡት በተለያዩ ዐውዶች ነው፡፡ ከነዚህ
መካከል አንደኛው አሃዳዊ ዐውድ ነው፡፡ ይህም የመልዕክት ወይም የመረጃ መተላለፊያ
በማዳመጥ ስርዓት ሂደት ውስጥ እንደ አንድ ዐውድ ሊጠቀስ ይችላል፡፡ ምክንያቱም በተፈጠረው
ሁኔታ አማካይነት መልዕክት ወይም መረጃ ከአንድ በኩል ወይም ከአንድ ወገን ብቻ ወደ ተቀባዩ
ወገን መተላለፉ ነው፡፡ አድማጩ ከተናጋሪው ጋር ቀጥተኛ የሆነ ተዛምዶ ስለሌለው ይጠቅመኛል
ያለውን ብቻ ከሚሰማቸው መካከል መርጦ ያዳምጣል፡፡ በዚህ ስር በርካታ የማዳመጥ አውዶች
ሊካተቱ ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ፡- ዜናዎች፣ልዩ ልዩ ማስታወቂያዎች፣ትምህርት ነክ መግለጫዎች፣
ድራማዎችና ትያትሮች፣ ፊልሞች፣ የተቀረፁ ድምፆችና የመሳሰሉት የማድመጥ ዐውዶች በዚህ
ስር ሊካተቱ የሚችሉ መሆናቸው ሊታወቅ ይገባል፡፡ ሁለተኛው ደግሞ አውደክልዔ የሃሳብ
መለዋወጫ መንገድ፡-በዚህ አውድ ውስጥ የመልዕክቱ ወይም የመረጃ ማስተላለፊያ ሂደቱ
በምልልስ የታጀበ የግራና ቀኝ (ወዲያ ማዶና ወዲህ ማዶ) በሆነ ሂደት የሚከወን ነው፡፡ በመልዕክት
ወይም መረጃ የሚተላለፈው ከአንድ ወገን ብቻ ሳይሆን በሌላኛው ጎራ ከሚገኘውም ወገን ነው፡፡
በምልልሱ ወቅት የድምፅ ብቻ ወይም እንደ አስፈላጊነቱ የአካልም ቢሆን ግንኙነት ሊኖር ይችላል፡፡
እንደ መጀመሪያው በዚህም ስር የሚካተቱ ዐውዶች አሉ፡፡ለምሳሌ፡- የስልክ ምልልስ፣ቃለ መጠይቅ
ወይም ቃለ ምልልስ፣ የመምህርና የተማሪ መስተጋብር፣የዘመድና የጓደኛ የናፍቆት ምልልስ
ወዘተ. የመሳሰሉትን የማዳመጥ ዐውዶች መጥቀስ እንደሚቻል ምሁራን ይገልፃሉ፡፡የመጨረሻው
ደግሞ ራስን ማዳመጥ ሲሆን ከሌሎች አቀራረብ አንፃር ራስን ማዳመጥ የሚለው ከዐውዶች
እንደ አንዱ ይቆጠራል፡፡ ራስን ማዳመጥ የሚለው ፅንሰ ሐሳብ እውን የሚሆንባቸው አጋጣሚዎች
እንዳሉ የሚታወቅ ሲሆን በተለይ በንባብ፣ በንግግር፣ በህመምና በድንጋጤ በመሳሰሉት ጊዜያት
ከሌላው በበለጠ ይከወናል፡፡ በተለይ ደግሞ አንድ ሰው ንግግር በሚያደርግበት ወቅት ራሱን
በየመሀሉ ያዳምጣል፡፡ ንባብ በሚያነብበት ጊዜም ቢሆን እንዲሁ ንባቡን በህሊናው ውስጥ

27
ይቀርፃል፡፡ እንደ ባለሞያዎች አስተያየት ይህ ራስን የማዳመጥ ክንውን አንድን መልዕክት፣
መረጃ፣ ወዘተ. የራስ አድርጎ ለማስቀረት ወይም ለመያዝ እጅግ ጠቃሚ ስልት ነው፡፡

2.4.1.2 የመናገር የክሂል አደረጃጀት እና አቀራረብ


Ur (1967) እንደገለፁት ለንግግር ማስተማሪያነት በመማሪያ መፃሕፍት ውስጥ የሚደራጁ ይዘቶች
ተማሪውን ብዙ እንዲናገር የሚገፋፉ፣ ሁሉንም ተማሪዎች ለማሳተፍ ዕድል የሚሰጡ፣
የሚያነቃቁ ደረጃዎች የጠበቁ ለማድረግ የሚያግዙ መሆን አለባቸው፡፡ ይህም ማለት በመማሪያ
መፃሕፍት ውስጥ የሚዘጋጁ ይዘቶችን ሁሉንም ተማሪዎች የሚያሳትፍ ደረጃውን የጠበቀ ንግግር
ለማድረግ የሚረዳና አሳታፊ መሆን ይኖርበታል፡፡

በተጨማሪም ጥሩ የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ሲዘጋጅ ተደጋጋሚ ልምምዶችን ተግባቦታዊ


ተግባራትን የሚከናወንባቸው መልመጃዎችና ተፈጥሯዊ የቋንቋ አጠቃቀምን መሠረት ያደረጉ
ይዘቶችን ማካተት እንዳለባቸው Grant (1987) ይገልፃሉ፡፡ ዓለም (1995፣23) የመናገር ክሂልን
የሚያዳብሩ መልመጃዎች አቀራረብና አደረጃጀትን ሲገልፁ፡- በክፍል ውስጥ ውይይትና ክርክር
የሚያደርጉበትን መንገዶች የሚያመቻቹ መልመጃዎችን ማቀናበር፣ ተዘጋጅተው እንዲወጡ
በማድረግ በክፍል ውስጥ ጭውውቶችን እንዲያቀርቡ የሚያነሳሱ መልመጃዎችን
ማዘጋጀት፣የአዳምጦ መረዳት ጥያቄዎች ከሌሎች ጋር ተዋቅረውና ተዋህደው የሚቀርቡበት ሂደት
አፅንኦት እንዲሰጠው ማድረግ፣በቃል ማብራሪያ ለማቅረብ የሚያስችሉ የንግግር ተጨማሪ
መልመጃዎች ማዘጋጀት፣አስቀድሞ እንዲዘጋጁበት በማድረግ በክፍል ውስጥ አጫጭር ትረካዎችን
እንዲያቀርቡ የሚያነሳሱ መልመጃዎችን ማዘጋጀት፣ሌሎችን መስለው ንግግር እንዲያቀርቡ
የሚያደርጉ መልመጃዎችን ማዘጋጀት፣ በጓደኞቻቸው ፊት ቀልድ እንዲናገሩ የሚያደርጉ
መልመጃዎች ማሰናዳትና ጅምር ዓረፍተ ነገሮችን ጨርሰው እንዲናገሩ የሚያደርጉ መልመጃዎች
ማዘጋጀት ናቸው፡፡

በሌላ በኩል McDonough and Shaw (1993)' Cunnings worth (1995) ሲገልፁ በዘመናዊ የቋንቋ
መማሪያ መፅሐፎች ውስጥ በተነደፉ መልመጃዎች ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጠው ተማሪዎች
በድርድሮች እንዲሳተፉና ሃሳብን እንዲያካፍሉ የሚያደርግ፣በጨዋታ ላይ የተመሰረቱ ንግግራዊ
ተግባራት ላይ እንዲሳተፉ የሚያደርግ፣በተለያዩ ቡድኖች በመከፋፈልና በየቡድናቸው የተለያየ
ስራ መርጠው ስለስራው ሁኔታ አንዱ ቡድን ሌላውን ቡድን ቃለ መጠይቅ በማድረግ በየተራ
ለክፍሉ እንዲገልፁ በማድረግ፣ተማሪዎች በተለያየ ማህበራዊ አውድ ውስጥ እንዲናገሩ

28
የሚያደርግ፣የሚና ጨዋታ በማድረግ፣መልመጃ ማካተት፣ፕሮጀክት ስራ እንዲሰሩ የሚያደርግ
ስራ ማካተት፣ወዘተ.ለመናገር ክሂል መዳበር ከፍተኛ ድረሻ ይኖራቸዋል፡፡

2.4.1.3 የንባብ ክሂል አደረጃጀት እና አቀራረብ


የንባብ ክሂል ትምህርት ይዘቶች ሲደራጁ የንባብ ንዑሳን ክሂሎችና አንብቦ መረዳት ደረጃዎችን
መሠረት በማድረግ የተለያዩ የንባብ ስልቶችን ለመጠቀም ተማሪው አንብቦ እንዲረዳ
እንዲያለማምዱ መልመጃዎች፣ እንደየውህዱ አሃድ የተነደፉ መማሪያ መፃሕፍት መዘጋጀት
ይኖርባቸዋል፡፡ በተለይም ይዘቶቹ ከዝርዝር ወደ አጠቃላይ፣ከአጠቃላይ ወደ ዝርዝር የአንባቢያንን
ተሞክሮ የሚያስተምር ዘዴ በማካተት ማቅረብ ተማሪዎቹ የሚጠበቀውን የትምህርት ግብ በቀላሉ
እንዲያሳኩ በር ይከፍትላቸዋል፡፡ የአንብቦ መረዳት ችሎታዎችን ለማዳበር ጥያቄዎችን በመልመጃ
መልክ ማዘጋጀት እንደሚቻል ዓለም (1995'11-12) ሲገልፁ መልመጃዎችን በሁለት አበይት
ክፍል መድቦ በሚከተለው መንገድ ማቅረብ ይቻላል፡፡ በማለት እንደሚከተሉት ይገልፃሉ፡፡
የምንባቡ ጠቅላላ አቀራረብ ወይም የአደረጃጀት መንገድ እንደሚገልፁት ማድረግ፣በዚህ ስር
የሚከተሉትን ተዛማጅ ጥያቄዎች መጠየቅ ይቻላል፡፡ የምንባቡን ተግባር መጠየቅ
(መዘርዝራዊ፣ቅስቃሽ፣ኪነታዊ፣ወዘተ. የምንባቡን ዓይነት
መጠይቅ(ልቦለድ፣ኢልቦለድ፣ዘገባ፣ማስታወቂያ፣ወዘተ.). ስለአያያዥ ቃላቶች ተግባር መጠይቅ፣
በዓረፍተ ነገሮች መካከል ስላለው ዝምድና መጠይቅ ይቻላል፡፡ ግልፅ በሆነ መንገድ የሰፈሩ ግልፅና
ያልተሸፈኑ ጉዳዮች መጠይቅ፣ በውስጥ አዋቂነት የተገለፁ ጉዳዮችን በምንባቡ መሰረትነት
መጠየቅ፣ በግምት ወይም በይምሰል ሊደርስባቸው የሚችሉትን ትርጉሞች መጠይቅ፣በምንባቡ
የቀረበውን ሃሳብ መገምገምና መመዘን ናቸው፡፡

የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎች አቀራረብ በፅሁፍ ወይም በቃል ሊቀርቡ ይችላሉ፡፡ አቀራረባቸውም
በክፍት አጠያየቅ፣በምርጫ፣እንዲሁም በእውነት ወይም ሀሰት በል በሚል መልኩ ሊቀርብ
ይችላል፡፡ ጥያቄዎች የሚቀርቡበት መንገድ የተለያየ ሲሆን ቢቻልም የአንብቦ መረዳት ጥያቄዎች
አንድ አንባቢ ሊኖረው ከሚገባው የንባብ ስትራቴጂ ጋር ማስታወቅ ይኖርባቸዋል፡፡ ጥያቄዎች
ምንባቡን ባላነበበ ሰው ሊመለሱ የሚችሉ ሊሆኑ አይገባም፡፡ ጥያቄዎች ተማሪዎቹ ምንባቡን
በበለጠ እንዲረዱ የሚያግዙ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡ የጥያቄዎቹ መልሶች ተማሪው በደረጃው
ሊኖረው የሚገባው የቋንቋ ብቃት የሚልቅ የቋንቋ አጠቃቀም መጠየቅ አለባቸው፡፡ የአንብቦ
መረዳት ጥያቄዎች ከሌሎች ክሂሎች ጋር ተጣምረውና ተቀናጅተው የሚቀርቡበት መንገድ
አስፈላጊ ነው፡፡ ጥያቄዎቹ የተገለፁበት ቋንቋ ከምንባቡ ቋንቋ የጠነከረ መሆን ይኖርበታል፡፡

29
2.4.1.4 የፅህፈት ክሂል አደረጃጀት እና አቀራረብ
የፅህፈት ክሂል ትምህርት በመማሪያ መፃሕፍት ውስጥ ተካተው የሚቀርቡበት ሁለት መንገዶች
እንዳሉትGrant (1987) ይገልፃሉ፡፡ አንደኛው ተማሪዎች እንደሁኔታው በፅሁፍ ምላሽ እንዲሰጡ
ማስቻል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ተማሪዎች የቋንቋ ችሎታቸውን በማዳበር ከፍ ወዳለ ሁኔታ
እንዲደርሱ ለማስቻል ነው፡፡ የፅህፈት ክሂል እንደማዳመጥ እና እንደመናገር በልምድ ሳይሆን
በትምህርት ብቻ የሚገኙ መሆኑ ነው፡፡ ማለትም በተፈጥሯዊ አውድ የምናገኘው ክሂል
አይደለም፡፡ ዓለም (1995'14) ይህንን ሃሳብ እንዲህ በማለት ያብራሩታል፡፡ የፅሁፍ ክሂል በቀላሉ
የሚጨበጥ ክሂል አይደለም፡፡ የፅህፈት ክሂል ውስብስብና ረቂቅ የሆነ ክሂል ነው፡፡ በተለይ ደግሞ
አስቸጋሪነቱን የሚያጎላው እንደማዳመጥ እና መናገር በልምድ ሳይሆን በትምህርት ብቻ የሚገኝ
መሆኑ ነው፡፡በትምህርት ሂደትም ውስብስብና አስቸጋሪ የሚያደርገውም በውስጡ ከሰዋሰዋዊ
ጉዳዮች በተጨማሪ የግንዛቤ፣የአስተውሎትንና የማመዛዘንን ችሎታ የመጠየቅ ጉዳዩ ነው፡፡

የፅህፈት ክሂል ተማሪዎች በደረጃቸው በተሻለ ሁኔታ መፃሕፍት የተፃፈውን መገንዘብ እንዲችሉና
ስህተቶችንም እንዲያስተካክሉ የሚገፋፉበት መንገድ ነው፡፡ ስለሆነም በቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት
ውስጥ የሚካተቱ የፅህፈት ክሂል ይዘቶች ሲደራጁ የተማሪዎችን ችሎታ፣ዕድሜ፣ደረጃ፣ፍላጎት
እና የአካባቢ ሁኔታ ከግምት ውስጥ ሊገባና የተቀረፅውን መርሃ ትምህርት መነሻ በመዳረግ
የፅህፈት ንዑሳን ክሂሎችን ለማዳበር የሚያስችሉ በሚቀርብላቸው ሞዴሎች መሰረት ከራሳቸው
አፍልቀው እንዲፅፉ ወዘተ. አካተው የያዙ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡የፅህፈት ክሂልን አዘገጃጀት
አስመልክቶ ዓለም (1995'15)ፒንካስ (1989'2)ን ጠቅሰው የፅህፈት ክሂል መልመጃዎች
ተማሪዎችን የሚያግባባ ወይም መልዕክት ያለው ፅሁፍ እንዲያዘጋጁ የሚያበረታቱ ቢሆኑ
ይመረጣል፡፡ ስለሆነም የፅሁፍ ክሂል መልምጃዎች ሲዘጋጁ የሚከተሉት ነጥቦች ትኩረት
ቢደረግባቸው የተሻለ እንደሚሆኑ ያብራራሉ፡፡ የፅህፈት ክሂል መልመጃዎች ተግባራዊና ጠቃሚ
በሆኑ የፅሕፈት ዓይነቶች ላይ ማተኮር ይኖርበታል፡፡ የፅህፈት ክሂል መልመጃዎች
የሚያተኩሩበት ልምምድ ተግባቦታዊ ወይም አገልግሎታዊ መሆን አለበት፡፡ ይህ ክሂል ሰዋሰውና
ቃላትን ለማስተማር ከመርዳቱ ጎን ለጎን ሌሎች ክሂሎችንም ለማሳደግ የሚረዳ መሆን አለበት፡፡
ከላይ የተዘረዘሩ ነጥቦችን መሠረት በማድረግ የፅህፍት ክሂል መልመጃዎችን ማዘጋጀት
የመልመጃዎችን ውጤታማነት ያሳድገዋል፡፡ በተጨማሪም ከዚህ በታች የቀረቡትን ዝርዝር
ነጥቦች በተጓዳኝ ማጤን ተገቢ ነው፡፡ የሚዘጋጁት የፅህፈት ክሂል መልመጃዎች በቡድን ሁነው
በውይይት የሚሰሩት ቢሆን የተሻለ ነው፡፡እንዲህ ያለው መንገድ አንዱ ከሌላው መማር እንዲቻል
እድል ከመፍጠሩም ባሻገር ከፅህፈት ጎን ለጎን የማዳመጥ፣የመናገር እና የማንበብ ችሎታዎች

30
አቀናጅቶ ለማዳበር የሚረዳ ነው፡፡የሚዘጋጁት የፅህፈት ክሂል መልመጃዎች ለተማሪዎች ስሜት
እና ፍላጎት የቀረቡ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡ ሲዘጋጁም ተመጥነው የተማሪውን ዕድሜ፣ብስለት
እና የትምህርት ደረጃ ያገናዘቡ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡ የሚዘጋጁት የፅህፈት ክሂል መልመጃዎች
ከተለያዩ የፅህፈት ዓይነቶች ጋር የሚያስተዋውቁ መሆን አለባቸው፡፡በመሆኑም መልመጃዎች
ሲዘጋጁ የግል ፅሁፎችን ከዋና ፅሁፎች፣ጥናታዊ ፅሁፎች፣ተቋማዊ ፅሁፎች ወዘተ. ያካተቱ
ሊሆኑ ይገባል፡፡

በተጨማሪም ዓለም (1995፣16)ፒናካስ(1989)ን ጠቅስው እንደገለጡት የፅህፍት ክሂል


መልመጃዎች የአቀራረብ ቅደም ተከተልን ሲገልፁ የሚከተሉትን ሦስት ደረጀዎች መሠረት
ቢያደርጉ የተሻለ ነው ካሉ በኋላ በሚከተለው መንገድ ገልፀውታል፡፡የትውውቅ ደረጃ፡- ይህ ደረጃ
ተማሪዎች ከሚጽፉት የፅሁፍ ዓይነት ቅርፅእና የይዘት አደረጃጃት ጋር የሚተዋወቁበት ደረጃ
ነው፡፡ በጥንቃቄ የሚመረጡ ምንባባት በዚህ ደረጃ ውስጥ ጥሩ ሚና ሊጫወቱ
ይችላሉ፡፡የልምምድ ደረጃ፡-ይህ ደረጃ የቀረበውን የፅሁፍ ዓይነት ቅርፅና አደረጃጀት ጋር በበቂ
ሁኔታ መተዋወቅ መቻላቸውን የምናረጋግጥበት ደረጃ ነው፡፡ በዚህ ደረጃ ስር የሚቀርቡት
መልመጃዎች ውስን ናቸው፡፡ መልመጃዎቹ ከአንድ ፅሁፍ ላይ የጎደለውን ነገር
የመሙላት፣አደረጃጀትን የማስተካከልና የመሳሰሉት ጉዳዮችን የሚጠይቁ ሊሆን ይችላል፡፡
የውጤት ደረጃ፡-በዚህ ደረጃ ተማሪዎች የጎደለውን ነገር ከመሙላት እና አደረጃጀትን ከማስተካከል
አልፈው ከራሳቸው በማፍለቅ ወጥ ፅሁፍ ያዘጋጃሉ፡፡ ከዚህ አንፃር ጠቃሚ ናቸው የተባሉ
መልመጃዎችን አዘገጃጀትና የአቀራረብ ቅደም ተከተል በተገቢው ሁኔታ ተሟልቶ የተዘጋጀ
መፃሕፍት የታቀደውን ዓላማ ግብ ከመምታት አንፃር ከፍተኛ ፋይዳ አላቸው፡፡ በአጠቃላይ
Raimes(1983)እና Meriwether(1997) እንደሚያስረዱት የመፃፍ ክሂል ማቅረቢያ መንገዶች
ተብለው የሚታወቁት ውጤታዊ የመፃፍ ክሂል ትምህርት አቀራረብ፣ሂደታዊ የመፃፍ ክሂል
ትምህርት አቀራረብእና ዘውግ ተኮር አቀራረብ ናቸው፡፡ እንደ Meriwether(1997) አገላለፅ
ውጤታዊ የመፃፍ ትምህርት አቀራረብ ተማሪዎች በቅድሚያ የመፃፍ ሂደቶችን ተከትለው
እንዴት መፃፍ እንዳለባቸው እንዲማሩ ሳይደረግ በቀጥታ የተሟላ ፅሁፍ ፅፈው
እንዲያቀርቡ የሚጠበቅበትና መምህሩም በቀረበው ፅሁፍ ውስጥ ያለውን የይዘትና የቅርፅ
ትክክለኛነት የሚገመግምበት አቀራረብ ነው፡፡ Raimes(1983) ደግሞ ሂደታዊ የመፃፍ ክሂል
ትምህርት አቀራረብ መፃፍ በተፈጥሮው ሂደት ነው የሚል እሳቤን የያዘ በመሆኑ መፃፍ
ዙር መጥ ተግባር ነው፡፡ስለሆነም በዚህ አቀራረብ ፅሀፉው ወደ ፊትና ወደኋላ

31
የተከሰቱና ሊከሰቱ የሚችሉ ስህተቶችን በመለየት የመፃፍን ተገባራት የሚያቀርብበት
ነው፡፡ በመሆኑም በመጀመሪያ የተመረጠውን ርዕስ በተመለከተ ሀሳብን በዝርዝር ማስፈር፣
አስተዋፅኦ መንደፍ፣ ረቂቅ ማዘጋጀት፣ ረቂቁን መንደፍ፣ ረቂቁን ማስተካከልና
የመጨረሻውን ፅሁፍ መፃፍን ያጠቃልላል፡፡ ዘውግ ተኮር አቀራረብ ደግሞ ከውጤት ተኮር
አቀራረብ ጋር ተቀራራቢ ሲሆን፣ ለሰዋስዋዊ ህግጋት ትኩረት በመስጠት ህግጋቱ
ከማህበረሰቡ አውድ ጋር ተዋህደው መቅረብ እንደሚኖርባቸው የሚያምን አቀራረብ ነው፡፡
Hamadouche(2010) Nimoch (2008)ን ዋቢ በማድረግ እንደሚገልፁት ዘውግ ተኮር የመጻፍ
ትምህርት አቀራረብ የሚያተኩረው አንድን ሁነት መሰረት በማድረግ የተለየ አላማን
ለማሳካት በማሰብ የሚቀርብ ሲሆን በቋንቋው ውስጥ ያለን የዲስኩር ገጽታ እንዲሁም
አውድን መሰረት በማድረግ ጽሁፍ መጻፍን ይመለከታል፡፡

2.4.2 የችሎታዎች አደረጃጀት እና አቀራረብ


Cunnings worth (1984) ሲያብራሩ አዘጋጆች የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ሲያዘጋጁ አፅንዖት
ሊሰጡት የሚገባ ፍሬ ነገር ቢኖር በቅድሚያ መፃሕፍት የትኛውን ዓይነት የቋንቋ ይዘት
ሊያስተምር እንደሚችል ለይተው ማወቅ ይኖርባቸዋል፡፡ ከአንድ በላይ የቋንቋ ትምህርቶችን
በመጠቀም ተግባቦታዊ የመማር ማስተማር ክንውኖችን ተግባራዊ ማድረግ እንደሚቻል በመገንዘብ
መተግበር የሚቻል መሆኑ የሚታወቅ ቢሆንም ለመማር ማስተማር ዓላማ ሲባል ግን የቋንቋ
ትምህርት ይዘቶችን የማዳበር ትምህርት ተማሪዎች ሊገባቸው በሚችል መንገድ መደራጀትና
መዘጋጀት አለባቸው፡፡ በመሆኑም የቃላትና የሰዋሰው ንዑሳን ችሎታዎች በመማሪያ መፅሃፉ
ውስጥ እንዴት መደራጀትና መቅረብ እንዳለባቸው ቀጥለን እንመለከታለን፡፡

2.4.2.1 የሰዋስው ትምህርት አደረጃጀት እና አቀራረብ


ዋናውና ትልቁ የሰዋሰው ትምህርት ዓላማ ተማሪዎች የሰዋሰውን ህግ በተግባቦታዊ አገልግሎት
እንዲጠቀሙበት ማድረግ ነው ፡፡ እንደ ባየ (2000'xxi) ገለፃ ከማንኛውም የክህሎት ትምህርት
በስተጀርባ የቋንቋ ተማሪ ሊገነዘበው የሚገባ ጥልቅ ረቂቅ እውቀት አለ፡፡ ይህውም የቋንቋው
ስርዓት ሰዋስው በሚባል የሚታወቀው ክፍል ነው፡፡ ይህ ትምህርት የአንድ ቋንቋ ስርዓት ከድምፅ
አሰካኩ እስከ ሀረግ አመሰራረቱ የሚያሳይ ሳይንስ ነው፡፡ሆኖም አንዳንድ የሰዋሰው ትምህርት
አሰጣጦች የትምህርቱን አቀራረብ በተዛባ ሁኔታ በመተርጎም ለተማሪዎች የሰዋሰው ህግና ቅርፅ
ብቻ በማሳወቅ የቋንቋ አዋቂዎችን ለማፍራት ሲጥሩ ይታያል፡፡ Harmer (1987)የሰዋስወ ትምህርት
አቀራረብ ላይ ችግር እንዳይፈጥር ጥሩ፣ጠቃሚ፣ ተወዳጅና ስሜትን የሚቀሰቅስ ይዘት መሆን

32
አለበት በማለት ያብራራሉ፡፡ በመሆኑም የሰዋሰው ትምህርት በቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ውስጥ
ለማዘጋጀት ሲታሰብ በሚከተሉት መስፈርቶች ላይ ተመስርቶ ሊቀርብ እንደሚገባ Ur
(1996)ያስረዳሉ፡፡ የተማሪውን የመገንዘብ ችሎታ ለማጎልበት ከሰፊ አውዳዊ ሁኔታዎች ጋር
የሚታይ የማስተማሪያ መሳሪያዎችን ማቅረብ፣የቃላትን ፍች የሚያስተምር ማቅረብ፣ ጥሩ
የተሸሻለ የሰዋሰው አቀራረብ፣የንግግርና የፅሁፍ፣የቅርፅና የፍች ይዘቶችን የያዘ ሊሆን
ይገባል፡፡ከራስ የአስተሳሰብ ሁኔታና ውሳኔ ላይ በመነሳት ሊቀርቡ የሚችሉ መሆን አለበት፡፡ስለዚህ
በቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ዝግጅት ጊዜ ሰዋስወን ለማስተማር ሲታቀድ በጣም ጥንቃቄ ማድረግ
እንደሚገባ መገንዘብ ያሻል፡፡ምክንያቱም ሰዋሰው ከይዘት ጋራ ተቀናጅቶ በማያሰለች ስልት መቅረብ
አለበት፡፡ አደረጃጀቱና አቀራረቡ ከክፍሉና ከትምህርቱ ጋር የተመጣጠነ መሆን
ይኖርበታል፡፡በተጨማሪም በቅርፅ ላይ ብቻ ያላተኮረ ሆኖ መደራጀት ይኖርበታል፡፡

በቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ውስጥ የሰዋሰው ትምህርት አደረጃጀት ጥልቀትና ስፋት ቀጣይንትና
ድግግሞሽ፣የሃሳብ ስደራ ቅደም ተከተል፣ወዘተ. ትኩረት ሊሰጡ የሚገባቸው ነጥቦች
ናቸው፡፡ምክንያቱም የትምህርት ይዘቶች ከአንዱ ክፍል ወደ ሌላው ክፍል በሚደረገው ሽግግር
የስነ ትምህርትን ስልት የተከተሉ ከሆነ በተማሪዎች ዘንድ ተወዳጅና ተነሳሽነትን የሚፈጥር
ይሆናል፡፡ ስለዚህም Celce-Murica (1994)በአንድ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ውስጥ አንድ ይዘት
ሲደራጅ በተማሪዎች ዘንድ ተነሳሽነትን የሚፈጥርና የተለያዩ ስሜቶችን የሚቀሰቅስ፣ የሚጠቅም፣
ከአንዱ ወደ ሌላ ሽግግር የሚፈጥር፣ ስነልሳናዊ ፋይዳዎችን ያካተተ መሆን እንዳለበት ገልፀዋል፡፡

የሰዋሰው ትምህርት ሲደራጅ በመማሪያ መፃሕፍት ውስጥ በቅድሚያ ሊታሰብ የሚገባውን ጉዳይ
ከልምምድ በፊት በመምህሩ ሊነሱ የሚገባቸው ወይም ተማሪው ተገንዝቦ ወደ ዋናው ስራው
ሊያንደረድረው የሚገባ መግለጫ መዘጋጀት አለበት፡፡ ከዚሁ ጋር ተያይዘው የሚቀርቡት
መልመጃዎች ደረጃ በደረጃ፣ጥልቀትንና ድግግሞሽን አካተው መደራጀትእና ግብ ተኮር መሆን
ይገባቸዋል Ur (1987)::ምክንያቱም ተማሪዎች እንደ ቋንቋ ተማሪነታቸው የመተማመን
ችሎታዎች መፍጠር ተነሳስተው የሚሰሩበትን ስሜት መፍጠር ስላለበት ነው፡፡ በቋንቋ መማሪያ
መፃሕፍት አደረጃጀት ውስጥ መካተት ያለበት ቁልፍ ጉዳይ የሰዋስው መልመጃ ዓይነቶች ናቸው፡፡
መልመጃዎች ሊደራጁ የተለያዩ ሰዋሰዋዊ ይዘቶችን በዓይነትና መጠን ተመጣጥነውና ተጣጥመው
እንዲቀርቡ ማድረግ ነው፡፡ ሰዋሰዋዊ ይዘቶች ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ወጥ መሆን
የለባቸውም፡፡ ምክንያቱም የተማሪውን የመማር ፍልጎትም ሆነ ችሎታ ይገድባሉ፡፡

33
የሰዋሰው መልመጃ አቀራረብ የእያንዳንዱ የሰዋሰው ግብአት ባህሪውን በማስገንዘብ ላይ ያተኮረ
ምሳሌ ወይም ማስታወሻና አተገባበሩን በማለማመድ ላይ ያተከረ ጥያቄ ሊቀርብ
ይችላል፡፡አቀራረባቸውም ከግንዛቤ ተኮር ወደ አጠቃላይ ተኮር መሆን አለበት፡፡ ግንዛቤ ተኮር
መልመጃ የተባለው ሰዋስዋዊ ገፅዎችን በማስገንዘብ ላይ ትኩረት የሰጡ እንደምሳሌና ማስታወሻ
ያሉትን ይመለከታል፡፡ ተማሪዎች በቀረበው የሰዋሰው ግብአት ምንም ነገር ከመተግበራቸው በፊት
ባህሪውን መተግበር አለባቸው፡፡ ከዚህም አንፃር የግብአቱን ሰዋሰዋዊ ባህሪ ሊያስገኝ የሚችል ላይ
ብቻ አፅንኦት የሰጠ ግንዛቤ ተኮር መልመጃ መጀመሪያ ተማሪው ማቅረብ እንደሚገባUr (1996) “
Harmer (1991)ያስረዳሉ፡፡

ግንዛቤ ተኮር መልመጃ ለቀላል የመማር ክንውን በሚመች መንገድ ከቀላል ወደ ከባድ ማለትም
ከተራ ወደ ውስብስበ መደራጀት እንደሚገባ Battstone (1994) እ“ Ur (1996)ያስረዳሉ፡፡
በተጨማሪያም የተማሪውን ዳራዊ ዕውቀት መሠረት ያደረገ ሰዋሰዋዊ ግብእና አውድ መጀመሪያ
ላይ መመረጥ አለበት፡፡ ከዚያም የፍች ወይም የቅርፃዊ ሰዋሰው ከፍተኛ ደረጃና መካከለኛ ደረጃ
ባህሪያቱ ተቀምረው ሊቀርቡ ይገባል፡፡ ከላይ እንደተገለፀው ግንዛቤ ተኮር መልመጃን በማዘጋጀት
እና በማደራጀት ሂደት ውስጥ አንዱ ተግባር የግብአቱን ሰዋሰዋዊ ባህሪያት በከፍተኛና በመካከለኛ
ባህሪያት አንፃር ከፋፍሎ ማቅረብ ነው፡፡ ቀጥሎም የሚመጣው ተግባር ባህሪያቱን በገለፃ፣በውል
በተደገፈ ምሳሌ አዘጋጅቶ ማቅረብ ያስፈልጋል ሲሉ Battstone (1994)ያስረዳሉ፡፡ በሌላ በኩል

የተተኳሪውን ግብአት ሰዋስዋዊ ባህሪ በማሳወቅ ላይ ካተኮረው ግንዛቤ ተኮር መልመጃ ወይም
ምሳሌ ውስጥ መምጣት ያለበት መዋቅር ተኮር መልመጃ የተባለው በግብአቱ አንዳች ነገር
መስራትን ወይም መጠቀምን የሚያመለክት ፅንሰ ሀሳብ ነው፡፡ ይህም በግብአቱ ተጠቅሞ መናገርን
ወይም መፃፍን በጠቅሉ አንዳች ነገርን መተግበርን ወይም መግለፅን ይመለከታል፡፡ ስለዚህም
የሚቀርበው መልመጃ በግባአቱ አንዳች ነገር መተግበርን የሚጠይቁ ጥያቄዎችን ማቅረብ አለበት
በማለት ያብራራሉ፡፡

የግንዛቤ ተኮር ዋና ዓላማ የታለመው ግብአት አውዳዊ አጠቃቀም ባህሪ በጠነከረ ሁኔታ
ለማስረዳት ነው፡፡Battstone (1994)ከቋንቋ መማር ክንዋኔ አንፃር ደግሞ መሠረቱ ጠንካራ የሆነ
ግንዛቤ ሊመሠረት የሚችለው በግንዛቤ ተኮር መልመጃ ሳይሆን ይበልጥ በዚህ በመዋቅር ተኮር
መልመጃ እንደሆነ Ur (1996)ይገልፃሉ፡፡ ምክንያታቸውም የመዋቅር ተኮር መልምጃ ተማሪውን
በመማር ሂደቱ ውስጥ ቀጥተኛና ንቁ ተሳታፊ ስለሚያደርግ ነው፡፡በሌላ አገላለፅ የግብአቱን ባህሪ
እንዲመለከቱ የሚያደርግ ሳይሆን በግብኣቱ አንዳች ነገር እንዲተገብሩ የሚያደርግ ነው፡፡ ስለሆነም

34
በቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ውስጥ የሰዋሰው ትምህርት ሲደራጅ የስነልሳን ክፍሎችን በቅደም
ተከተል አካቶ መያዝ ይኖርበታል፡፡ በአጠቃላይ Larsen Freeman (1991)፣ Harmer (1991) እና
Batstone (1994) እንደሚያስረዱት የሰዋስው ማቅረቢያ መንገዶች ተብለው የሚታወቁት ከጥቅል
ወደ ዝርዝር፣ ከዝርዝር ወደጥቅል፣ ውጤት ተኮር እና ሂደት ተኮር ናቸው፡፡

2.4.2.2 የስነፅሁፍ ትምህርት አደረጃጀት እና አቀራረብ


የስነፅሁፍ ማቅረቢያ መንገዶች መካከል ዋናዎች አራት ናቸው፡፡ ቋንቋ ተኮር አቀራረብ፣ይዘት
ተኮር አቀራረብ፣ግለሰባዊ ተሳትፎ የሚጨምር አቀራረብእና ስልታዊ አቀራረብ ናቸው፡፡ ቋንቋ
ተኮር አቀራረብ የስነፅሁፍ ስራው ይዘቱ የቀረበበትን የያዘው ቋንቋ ላይ ያተኩራል፡፡ ምሳሌ፡-
በቃላት፣በዓረፍተ ነገር ቅንብርና አወቃቀር በዘይቤና በፈሊጣዊ አነጋገር ላይ ያተኩራል፡፡
እንዲሁም ድምፅ፣ምዕላድ፣ቃል፣ሐረግ፣ዓረፍተ ነገር፣አንቀፅ፣ድርሰትና ዲስኩር ወዘተ. ሁሉ
ይመለከታል፡፡ አላማውም የተማሪዎችን የቋንቋ ችሎታ ለማጎልብት ነው፡፡ ይዘት ተኮር አቀራረብ
ደግሞ በቋንቋ ውስጥ ያሉ ይዘቶችን መሰረት ያደረገ ነው፡፡ ይህም በሦስት ነገር ላይ ያተኩራል፡፡
የደራሲው ዳራ የደራሲውን የህይወት ታሪክ የሚመለከት ነው፡፡ ስነፅሑፋዊ ዳራ ደግሞ
የስነፅሑፍን ምንነት የሚመለከት ሲሆን ለአብንትም ስለልቦለድ አላባዊያን፣ዘውጎች ይመለከታል፡፡
ባህላዊ ዳራ ስነፅሁፍ ውስጥ የቀረቡ ባህላዊ ነገሮችን ይመለከታል፡፡ ሌላኛው የስነፅሁፍ ትምህርት
አቀራረብ ግለሰባዊ ተሳትፎን የሚጨምር አቀራረብ ነው፡፡ ይህ የተለመደ ባይሆንም እያንዳንዱ
ተማሪ በስነፅሁፍ ስራ ውስጥ ግላዊ ተሳትፎ እንዲያደርግ አመቻችቶ ማቅረብ ነው፡፡ ምሳሌ
ጭውውት፣ክርክር፣ተውኔት ወዘተ. ተጠቃሽ ናቸው፡፡ የመጨረሻው አቀራረብ ስልታዊ ሲሆን
ተማሪዎች የስነፅሁፍ ስራን ከራሳቸው ልምድና የቋንቋ ችሎታዎች እንዲዳብር የሚያስችል ነው፡፡
ስልታዊነት ከማፈንገጥ አንፃር (ከይዘት፣ጭብጥ፣ቅርፅ)ስልታዊነት ከዘመን አንፃር፣ ስልታዊነት
ከምርጫ አንፃር፣ ስልታዊነት ከግለሰብ ጋር ይያያዛል ይህ ዘዴ ግለሰቡ የሚያተኩሩበት ስራ ነው፡፡

2.5 በመማሪያ መፅሓፍ ውስጥ የምዘና ተግባራት


ምዘና መምህራን ውሳኔ ለመስጠት የሚያስችሏቸውን መረጃ የሚሰበስቡበት፣ የሰበሰቡትን መረጃ
የሚተነትኑበትና ትንተናውን የሚተረጉሙበት ሂደት ነው፡፡ በመማሪያ መፃሕፍትት ውስጥ
የሚገኙ የክፍል ውስጥ ምዘናዎች የተማሪዎችን የመማር እድገት ለመወሰን የሚያስችሉ
መረጃዎችን የመሰብሰብ መሳሪያዎች ናቸው፡፡ እነዚህ የምዘና መሳሪያዎች ወይም የመመዘኛ
ስልቶች (የሙከራ ፈተና፣ ምልከታ፣ የክፍልና የቤት ስራ፣ ወዘተ ናቸው፡፡ ምዘናው ማነኛውንም
አይነት ስለተማሪው መሻሻልና የመማር እድገት፣ ስለ መማር ማስተማር ክንውንና ስለተማሪዎች

35
የችሎታ ደረጃ ለመለየት የሚያስችሉ መረጃዎችን የመሰብሰብ፣ የማደራጀትና የመተንተን ሂደት
ነው(Hughes 1989):: መመዘን አጠቃላይ ሁሉንም የተለያዩ መንገዶች በመጠቀም መምህራን
በሚያስተምሩት ክፍል ያለውን መረጃ የሚሰበስቡበት ሂደት ነው፡፡ ይህም ምልከታን፣ የቃል
ጥያቄዎችን፣ የጽሁፍ ሙከራዎችን፣ የቤት ስራዎችን፣ የላብራቶሪ ሙከራዎችን፣ የጥናት
ወረቀቶችን የመሳሰሉትን ያካትታል (Nitko 1996 and Airasian 1996)፡፡ መመዘን የልኬታ አንዱ
ክፍል ሲሆን በአጠቃላይ ትኩረት የሚያደርገው የትምህርት ስርዓት እና በአብዛኛው የአካቶ
ትምህርቱን ነው፡፡ መመዘን በመማር ተፈጥሮአዊ ሁኔታ ላይ ብቻ የሚያተኩር ሳይሆን ምን?
እና እንዴት? እንዴት እንደምንማርም ትኩረት ያደርጋል(Payne 1997)::
የመምህራን ማሰልጠኛ ሞጁል (2008) ምዘና መረጃ የማሰባሰብ ሂደት ሲሆን ይህንንም መረጃ
በመጠቀም በትምህርት ፖሊሲዎች በስርዓተ ትምህርቱና በትምህርት ፕሮግራሞች ይዘት ወይም
አተገባበር ዙሪያ ውሳኔ መስጠት መቻል ነው ይላል፡፡ በሌላ አገላለፅ ምዘና ስለተማሪዎች በተሻለ
ለመረዳት እንዲቻል መረጃ ማሰባሰብ፣ ማደራጀት መተንተንና ትርጉም መስጠትን የሚመለከት
ተግባር ነው፡፡ ምዘና በውስጡ ግለምዘና፣ ድንገተኛ ምዘና ሙከራ፣ አሳይመንት፣ ፕሮጀክት፣
ምልከታ፣ መረጃ ትንተና፣ የቢጤ ምዘና፣ ቃለመጠይቅ፣ የቡድን ስራ ሪፖርት፣ ሙከራ (ፈተና)
ወዘተ የሚሉትን የተለያዩ የምዘና ስልቶችን ያጠቃልላል፡፡

በምዘና ሂደት የተማሪዎች የጽሁፍ ስራ ለምዘና የሚያገለግሉ ሲሆኑ እነዚህም በአቻ ወይም በሌላ
ጓደኛ እንዲሁም በመምህራን ይገመገማሉ፡፡ መምህራንን በተመለከተ ውጤታማ የሆኑና ብቃት
ያላቸው ሊሆኑ ይገባል፡፡ ጥሩ አስተማሪ ተማሪዎችን ለመመዘን ሁሌም ዝግጁ ነው፡፡ ምዘናውንም
ሲያካሂድ ድንገተኛ፣አጋጣሚ ወይም በዕቅድ ሊሆን ይችላል(Brown 2004)::

2.6 የቋንቋ መርሃ ትምህርትና የመማሪያ መፅሃፍ ዝምድና


Nunan (1984)የመማሪያ መፅሃፍእና የመርሃ ትምህርት ግንኙነት አስመልክቶ የቋንቋ መማሪያ
መፅሃፍ ያለምንም ማወላወል መርሃ ትምህርቱ በተግባር የሚገለፅበት ነው፡፡በመሆኑም የቋንቋ
መማሪያ መፃሕፍት ሲገመገም፣ሲሻሻል፣ሲዘጋጅ፣ሲፃፍ ወዘተ. የተዘጋጀውን መርሃ ትምህርት
መሠረት ማድረግ እንዳለበት የሚያስገነዝብ በመሆኑ በሁለቱ መሳሪያዎች መካከል የጠበቀ
ዝምድና ሊኖር ይገባል፡፡Dubin and Olshtain (1986)በበኩላቸው በመርሃ ትምህርቱ ውስጥ የሰፈሩት
ትምህርታዊ ዓላማዎች በግልፅ የሚታዩት በመማሪያ መፃሕፍት ላይ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
በተጨማሪም የመማሪያ መፃሕፍት ከመርሃ ትምህርቱ ጋር መስማማትና መርሃ ትምህርቱ
ውስጥ የሚነሱት ፍሬ ነገሮች ሁሉ አንድነታቸው በግልፅ ማየትና የይዘቶች ቅደም ተከተል

36
ከመርሃ ትምህርቱ ጋር መስማማት ግድ ነው፡፡ ማለትም በመርሃ ትምህርቱ የተገለጹ ሃሳቦች
በሙሉ በመማሪያ መፃሕፍት ውስጥ መስፈር ይኖርባቸዋል፡፡ በተጨማሪም Yalden (1987)
ሲያብረሩ ትምህርት አጠቃላዩንና ዝርዝሩን የትምህርት ዓላማ በዝርዝር በመግለፅ አስተማሪ
የትኞቹን ይዘቶች በምን ያህል ጊዜና የአተገባበር ስርዓት ማስተማር እንዳለበት፣ተማሪዎቹን
የትኞቹ ከተቀረፀው መርሐ ትምህርት አንፃር ምን ማወቅ እንዳለባቸው የሚያስገነዝብ ሠነድ ነው
ይላሉ፡፡መርሐ ትምህርት የትምህርት ሂደት ተግባራዊ የሚደረግበት፣ የትምህርት ይዘቶች
የሚመረጥበት፣የትምህርት ማስተማሪያ መርጃ መሳሪያዎች የሚገለፅበት፣ወዘተ.መመሪያ ነው፡፡
ከዚህ አንፃር መርሃ ትምህርት በዋነኛነት የትምህርት ክንውን በተግባር የሚተረጎምብት መመሪያ
የያዘና በስርዓተ ትምህርት የሚጠቃለሉ ነገሮች በይዘት አመራረጥ፣አደረጃጀትና አቀራረብ ላይ
አፅንኦት የሚሰጥ ነው፡፡ የመማሪያ መፃሕፍት የዕውቀት ክፍሎችን የያዘ ተማሪው ሊረዳው
በሚችል መልክ ለማስተማሪያ የተዘጋጀ መሣሪያ ነው በማለት ያስረዳሉ፡፡ Richards (1985)
ሲያስረዱ የመማሪያ መፅሐፉ በመርሃ ትምህርቱ የተገለፁትን ይዘቶች አደራጅቶ በየጊዜው
የማስተማሪያ ዘዴ ነው፡፡ በመማሪያ መፃሕፍት ውስጥ መስፈር ስላለባቸው ይዘቶች አደረጃጀትና
አቀራረብ የሚወስን በመሆኑ፣ለመማሪያ መፃሕፍት ዝግጅት መነሻ በመሆን ሲያገለግል የመማሪያ
መፅሐፉን በመርሃ ትምህርቱ የተካተቱት ዓላማዎች ግብ መምታት ወሳኝ ሚና የሚጫወቱ
ናቸው፡፡

2.7 የቀደምት ጥናቶች ቅኝት

በዚህ ንዑስ ክፍል ውስጥ የሚጠናው ጥናት ተዛማጅ ከሆኑ ቀደምት ጥናቶች ጋር ሲነፃፀር በምን
እንደሚመሳሰልና እንደሚለያይ በዝርዝር የሚዳሰስበት ክፍል ሲሆን ይህ ጥናት ከቀደምት ጥናቶች
ጋር ያለውን አንድነትና ልዩነት እንደሚከተለው ለማቅረብ ተሞክሯል፡፡

ሰሚራ(2010) በ2009ዓ.ም ስራ ላይ በዋለው የደቡብ ክልል የ8ኛ ክፍል አማርኛ ቋንቋ መማሪያ
መጻህፍ ውስጥ የተካተቱ የሰዋስው ትምህርት ይዘቶች አቀራረብና አደረጃጃት ምን እንደሚመስል
ጥናት አካሂዳለች፡፡የጥናቱ አላማ የነበረው በመማሪያ መፅሐፉ ውስጥ የሰዋሰው ይዘቶች
አቀራረብና አደረጃጀት መፈተሽ ነበር፡፡ጥናቱን ከዳር ለማድረስ ጥቅም ላይ የዋለው የመረጃ
መሰብሰቢያ ሰነድ ፍተሻ ሲሆን ይህም በአይነታዊ የምርምር ዘዴ በመጠቀም በገላጭ ስልት
ቀርቧል፡፡ በጥናቱ የተገኘው ውጤት እንደሚያመለክተው የይዘቶቹን አቀራረብ በተመለከተ
ከአጠቃላይ ወደ ዝርዝር ይልቅ ከዝርዝር ወደ አጠቃላይ የቀረቡ የሰዋስው ትምህርት ይዘቶች

37
አብላጫውን ሽፋን ይይዛሉ፡፡ ይሁን እንጂ ከዝርዝር ወደ አጠቃላይና ከአጠቃላይ ወደ ዝርዝር
የቀረቡት ይዘቶች በጥሩ ሀኔታ የቀረቡ ሲሆን እንደ ደካማ ጎን የታየው በአንድ ትእዛዝ ስር
የተለያዩ ሶስትና ከዚያ በላይ የሆኑ ርዕሰ ጉዳዮችን ማካተቱና ገለጻ ሲቀርብ መልእክት በትክክል
አለመቅረቡ ነው፡፡ ውጤት ተኮር በሆነ መንገድ የቀረቡት ይዘቶች ሂድት ተኮር ሆነው ከቀረቡት
በተሻለ ጥቅም ላይ እንደዋሉ ታይቷል፡፡ ከአደረጃጀት አንጻርም በመማሪያ መጽሃፉ ውስጥ
የተካተቱት የሰዋስው ትምህርት ይዘቶች በአብዛኛው ተከታታይነት ኖሯቸው የተደራጁና ስፋትና
ጥልቀታቸው እየጨመሩ የሚሄዱ ናቸው፡፡በመጻህፉ አጠቃላይ በሆነው የይዘት አደረጃጀትና
ከመርሃ ትምህርቱ ጋር ባለው ተዛምዶ እንዳላቸው አጥኝዋ ድምዳሜ ላይ መድረስ ችላለች፡፡

ሐዋዝ(2000) ደግሞ“በአዲስ አበባ ከተማና በአማራ ክልል አንደኛ ደረጃ ሁለተኛ እርከንየአማርኛ
ቋንቋ መማሪያ መፃህፍት ውስጥ የሰዋስው ትምህርት አቀራረብና አደረጃጀት ንጽጽራዊ ግምገማ”
በሚል ርዕስ ለሁለተኛ ዲግሪ ያቀረበው ጥናት ተጠቃሽ ነው፡፡ የጥናቱ አላማ የተጠቀሱት ሁለት
ክልሎች በሚጠቀሙባቸው የ7ኛና የ8ኛ ክፍል የአማርኛ መማሪያ መጻህፍት ውስጥ የሰዋስው
ትምህርት አቀራረብና አደረጃጀት በማነፃፀር ተመሳስሎና ልዩነታቸውን ነቅሶ ማውጣት ነው፡፡
ጥናቱን ከድምዳሜ ለማድረስም የጽሁፍ መጠይቅ፣ ቃለ መጠይቅና የሰነድ ምርመራ የተጠቀመ
ሲሆን በውጤቱም ክልሎቹ መሠረት ያደረጉት አንድ አይነት መርሀ ትምህርት ቢሆንም
በአቀራረብና በአደረጃጀታቸው መለያየታቸውን፣ በሁለቱም ክልሎች የሰዋስው ትምህርት
የአቀራረብ መርሆዎችን አልሞ አለመተግበር፣ የጽንሰ ሃሳብ፣ የአርትኦትና ከመርሀ ትምህርቱ
የመውጣት ችግሮች በጥናቱ ሂደት የተደረሰባቸው ግኝቶች መሆናቸውን ገልጿል፡፡

እያሱ (2003)በ1997ዓ.ም በተሻሻሉት የ9ኛና የ10ኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃህፍት
የሥነ ትምህርታዊ ሰዋስው ይዘት አመራረጥ፣ አቀራረብና አደረጃጀት ግምገማ በሚል ርዕስ ጥናት
አቅርቧል፡፡ የእያሱ ጥናት ዓላማ በተተኳሪዎቹ የመማሪያ መፃህፍት ውስጥ የተካተቱት የሰዋስው
ትምህርት ይዘቶች አመራረጥ፣ አቀራረብና አደረጃጀት በመፈተሽ ያለውን ደካማና ጠንካራ ጎን
መጠቆም ነው፡፡ ጥናቱንም ከዳር ለማድረስ ከጽሁፍና ከቃል መጠይቅ በተጨማሪ የሰነድ ምርመራ
በማድረግ ወደ ጥናቱ ማጠቃለያ ደርሷል፡፡ በውጤቱም የሰዋስው ትምህርት ይዘቶች ከቋንቋው
ሰዋስዋዊ ክፍሎች የተውጣጡ አለመሆናቸው፣ የግልጽነት ችግር የሚስተዋልባቸው
ከመሆናቸውም በተጨማሪ ከመርሀ ትምህርቱ ጋር ያልተዛመዱ እንደሆኑ፣ ከተከታታይነትና
ከተለጣጣቂነት አንፃርም ክፍተት ያለባቸው መሆናቸውን እና የአቀራረብ ችግር እንደ
ተስተዋለባቸው በመጠቆም መፍትሄ ያላቸውን ሃሳቦች ሰንዝሯል፡፡ ከላይ የቀረቡት የጥናት

38
ስራዎች ሰዋስው ላይ ትኩረት ያደረጉና የመማሪያ መፅሀፍ ይዘቶችን አደረጃጀት የፈተሹ
መሆናቸው ከዚህ ጥናት ጋር የሚያመሳስላቸው ዝምድና ቢኖርም ይዘውት ከተነሱት የጥናት
አላማ፣ ከመማሪያ መጻሕፍቱ የክፍል ደረጃ፣ ከታተሙበት ዘመንና ከጥናቱ አካሄድ ወዘተ. አንፃር
ፍፁም ተዛማጅ ወይም ተመሳሳይ አይደሉም፡፡

39
ምዕራፍ ሦስት፤የጥናቱ ንድፍና ዘዴ

3.1 የጥናቱ ንድፍ


የዚህ ጥናት ዋና አላማ በ2004 ዓ.ም በአንደኛ አትም ታትመው በአሁኑ ወቅት ሥራ ላይ ያሉትን
የአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና መርሀ ትምህርቱ ያላቸውን ዝምድና
መፈተሸ ነው፡፡ ይህን ዓላማ ከግብ ለማድረስ ተዛምዷዊ የምርምር ንድፍ ተግባራዊ
ሁኗል፡፡አጥኝው ተዛምዷዊ የምርምር ንድፍን የመረጠበት ምክንያት ይዞት የተነሳው በአስረኛ
ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና በመርሃ ትምህርቱ መካከል ያለው የክሂልና
የእውቀት ዘርፎች የይዘት ተከታታይነት ዝምድና፣የይዘት ተለጣጣቂነት ዝምድና፣ የይዘት
ውህዳዊነት ግንኙነት እና ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች ያላቸው ዝምድና የፈተሸ በመሆኑ ነው፡፡
ይህ ንድፍ ደግሞ በሁለት ወይም ከዚያ በላይ በሆኑ ተለዋዋጮች መካከል ሊኖር የሚችልን
የግንኙነት አቅጣጫ መጠን ለመወሰን የሚያስችል በመሆኑ ነው፡፡

3.2. የመረጃ ምንጭ


የዚህ ጥናት ዋና አላማ ከግብ ለማድረስ ይቻል ዘንድ አጥኚው ለጥናቱ ተገቢ መረጃዎችን
በመሰብሰብ የተለያዩ የመረጃ ምንጮችን ጥቅም ላይ አውሏል፡፡ለዚህ ጥናት አብይ የመረጃ
ምንጭ በ2004ዓ.ም ታትሞ በትምህርት መርጃ መሳሪያነት በማገልገል ላይ ያለው የአስረኛ
ክፍል የአማርኛ ቋንቋ የተማሪው መማሪያ መፃሕፍት እና መርሐ ትምህርቱ የመረጃ ምንጭ
ወይም ተጠኝ በመሆን አገልግለዋል፡፡

3.3. የናሙና አመራረጥ ስልት


ይህ ጥናት አላማ ተኮር የናሙና ዘዴን የሚከተል ሲሆን በዋናነትም በአስረኛ ክፍል የአማርኛ
ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና በመርሀ ትምህርቱ ላይ ያተኩራል፡፡ በአላማ ተኮር የንሞና ዘዴ
ተመራማሪው የጥናት ተሳታፊውን የሚመርጠው ከጥናቱ ዓላማ አንፃር ነው፡፡እነማንን ብመርጥ
የምፈልገው መረጃ ኖሯቸው ሊሰጡኝ ይችላሉ? የትኞቹ አካላይ አባላት በጥናቱ ቢሳተፉ
አስፈላጊውን መረጃ ላገኝባቸው እችላለሁ? የሚሉትን ጥያቄዎች በማንሳት የጥያቄዎችን አላማ
ለማሳካት ሰዎችን ወይም ሌሎች ነገሮችን ይመርጣል ይላሉ ያለው (2009፣136)፡፡ ጥናቱ በአስረኛ
የክፍል ደረጃ ላይ እንዲያተኩር የሆነበት ምክንያት አጥኝው በአሁኑ ወቅት በዚህ የክፍል ደረጃ
የአማርኛ ቋንቋ መምህር ሆኖ እየሰራ የሚገኝ በመሆኑና የቋንቋ መማሪያ መፅሀፉና መርሀ
ትምህርቱ ተጣጥመው ከመገኘት አንፃር ዝምድናቸውን ለማጥናት ነው፡፡

40
3.4 የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎች
በዚህ ጥናት የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያ ተደርጎ የተመረጠው ሰነድ ፍተሻ ነው፡፡ ይህን የመረጃ
መሰብሰቢያ መሳሪያ በመጠቀም በአሁኑ ወቅት አገልግሎት እየሰጡ ያሉት የአስረኛ ክፍል
የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና ለዚህ የክፍል ደረጃ የተዘጋጀውን መርሀ ትምህርት
ዝምድና ይፈትሻል፡፡ ጥናቱንም ከግብ ለማድረስ የሚመለከታቸውን የመረጃ ምንጮች፣ እውነተኛና
ትክክለኛ የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያዎችን እንዲሁም ተገቢውን የመረጃ መተንተኛ ዘዴ ስልት
በመከተል የተለያዩ ግኝቶችን መርምሯል፡፡

3.4.1 ሰነድ ፍተሻ


በዚህ ጥናት የተማሪው መማሪያ መፃሕፍት እና መርሃ ትምህርቱ በመረጃ ምንጭነት
አገልግለዋል፤ በመሆኑም በሰነድ ፍተሻ የታዩት እነዚህ ናቸው፡፡ የዚህ ጥናት ዋና አላማ በ2004
ዓ.ም በአንደኛ አትም ታትመው በአሁኑ ወቅት ሥራ ላይ ያሉትን የአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ
መማሪያ መፃሕፍት እና መርሀ ትምህርቱ ያላቸውን ዝምድና መፈተሸ ነው፡፡ በመሆኑም
የእያንዳንዱ ንዑስ የቋንቋ ክሂል እና ችሎታ አንዲሁም ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎችን ለመለየት
የሚያስችል ቅፅ ከተዘጋጀ በኋላ በባለሙያ እና በጥናቱ አማካሪ በማስገምገም መረጃ የመሰብሰብ
ስራ ተካሂዷል፡፡ በተዘጋጀው ቅፅ አማካኝነት የቋንቋ ክሂል እና ችሎታ አንዲሁም ለምዘና ተግባር
የዋሉ ስራዎችን ለማወቅ በመማሪያ መፃሕፍቱና በመርሃ ትምህርቱ ያለው የድግግሞሽ መጠን
ቆጠራ ተካሂዷል፡፡ አቆጣጠሩ ስልጠና በተሰጣቸው ሦስት የሁለተኛ ደረጃ የቋንቋ መምህራን
የተከናወነ ሲሆን አስቀድሞ ይህን ተግባር ለሚያከናውኑት ለእነዚህ መምህራንም በአጠቃላይ
ስለጥናቱ አካሄድ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በአጥኝው ተሰጥቷል፡፡ በመቀጠልም በመፃሕፍቱ
የቀረቡትን ይዘቶችና የምዘና ስልቶች ለምን ያህል ጊዜ ቀርበዋል? የሚለውን ለመለየት የመረጃ
መሰብሰቢያ መሳሪያ የሆነውን የሰነድ መፈተሻ ቅፅ እና የተሰበሰበውን መረጃ አስተማማኝነት
ሁኔታ በክሮንባኸ አልፋ( Inter rater Agreement ተሰርቶ Reliability coefficient) ተረጋግጧል፡፡
የተገኘው ውጤት 0.865 ሲሆን ይህ ውጤት የዳኞቹ የስምምነት ደረጃ በጣም ጥሩ በሚባል
አስተማማኝነት ደረጃ ላይ መሆኑን ያመለክታል፡፡ ከዚህ በኋላ መዳቢዎች በግል የሰጡት ውጤት
አማካዩ ተሰልቶና ወደ መቶኛ ተቀይሮ ለጥናት ስራው ውሏል፡፡ ይህም የተደረገበት ዋናው
ምክንያት የጥናቱን የአስተማማኝነት ደረጃ ለማጎልበት ነው፡፡

41
3.5 የመረጃ አተናተን ዘዴ

ከላይ በተጠቀሰው የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያ የሚሰበሰቡት መረጃዎች በወጉ ከተቀናጁ በኋላ
ለአንባቢው ግልፅና ተነባቢነት እንዲኖራቸው በመጠናዊ እና አይነታዊ የመረጃ መተንተኛ ዘዴ
ተተንትነው ቀርበዋል፡፡ የጥናቱ ቀዳሚ ዓላማ የሆነውን በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ
መፅሃፍ እና በመርሃ ትምህርቱ መካከል ያለውን የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት
ተከታታይነት ዝምድና ለመፈተሽ አጥኝው አይነታዊ እና መጠናዊ የመተንተኛ መሳሪያ የተጠቀመ
ሲሆን፣በዚህ መሰረት በቀጣይ ተላውጦዎች (Continuous Vairables) መካከል ያለውን ተዛምዶ
በፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት የዝምድና መለኪያ (pearson product-moment correlation) (Muijs
2004) ዘዴ ተተንትኗል፡፡ ይህ መተንተኛ መሳሪያ የሚያገለግለው በሁለት ተለዋዋጮች መካከል
ያለን የግንኙነት አቅጣጫ እና መጠን ለማመልከት ሲሆን፣ሁለቱ ተለዋዋጮች በመጠናዊ የመረጃ
መሰብሰቢያ ዘዴው አማካኝነት የሚገኘው የልኬታ አይነት ደግሞ እኩል ወይም ተካፋይ ልኬታ
መሆን ይገባል፡፡ በተላውጦዎች መካከል ያለው ግንኙነት የታየው ‹‹SPSS 20›› የሚባለውን መረጃ
መተንተኛ ፕሮግራም በመጠቀም ነው፡፡ የዚህን ጥናት ሁለተኛ ዓላማ የሆነውን በአስረኛ ክፍል
በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍትና በመርሃ ትምህርቱ መካከል ያለውን የክሂልና የእውቀት
ዘርፎች የይዘት ተለጣጣቂነት ግንኙነት ለመመርመር ደግሞ አጥኝው አይነታዊ እና መጠናዊ
(ፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት የተዝምዶ መለኪያ) መሰረት በማድረግ አገልግሎት ላይ ውሏል፡፡
በአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሃፍ ያለውን የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት
ውህዳዊነት መመርመር የጥናቱ ሦስተኛ ዓላማ ሲሆን ይህን ዓላማ ከግብ ለማድረስ ተሰብስቦ
የተደራጀውን መረጃ ለመተንተን አጥኝው አይነታዊ እና መጠናዊ (ፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት
የተዝምዶ መለኪያ)ተጠቅሟል፡፡ የዚህ ጥናት የመጨረሻው ዓላማ በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ
መማሪያ መፃሕፍት በመርሐ ትምህርቱ ውስጥ ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች ያላቸውን
ዝምድና መፈተሸ ነበር፡፡ ይህንን ዓላማ ከግብ ለማድረስም ፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት የተዝምዶ
መለኪያ አገልግሎት ላይ ውሏል፡፡

42
ምዕራፍ አራት፤የመረጃ ትንተናና የውጤት ማብራሪያ

4.1 የመረጃ ትንተና


የአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መጽሐፍ በ2004ዓ.ም ተሻሽሎ የቀረበ ሲሆን፣ በውስጡም
አስር ምዕራፎችን አካቶ ይዟል፡፡ በእነዚህ ምዕራፎች ውስጥም የማንበብ፣ የመጻፍ፣ የመናገር፣
የማዳመጥ ፣ የሥነ ጽሑፍ እና የሰዋስው ይዘቶች ቀርበዋል፡፡ በዚህ ጥናት ውስጥ በዋነኝነት
እንደመረጃ ምንጭነት የተወሰዱት በ2004ዓ.ም ተሻሽለው የወጡት የአሰረኛ ክፍል የአማርኛ
ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና መርሐ ትምህርቱ ሲሆኑ፣ ከዚህም በተጨማሪ የአሰረኛ ክፍል
እንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ለጥናቱ በውስን ደረጃ በመረጃ ምንጭነት ተግባር ላይ
ውሏል፡፡ የአስረኛ ክፍል የእንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ መጽሐፍ በመረጃ ምንጭነት እንዲካተት
የተደረገበት ምክንያት የታላሚውን ቋንቋ መማሪያ መጽሐፍ የይዘት ውህዳዊነት ምሁራን
ከሚያስቀምጧቸው ንድፈ ሀሳብ አንጻር ለማጤን ሲባል ነው፡፡ የዚህን ጥናት ዋና ዓላማ ከግብ
ለማድረስ ተግባር ላይ የዋለው የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴ የሰነድ ምርመራ ነው፡፡ በመሆኑም
በአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ውስጥ የክሂል እና የእውቀት ትምህርት
ይዘቶች ከመርሃ ትምህርቱ ጋር ያላቸውን ዝምድና በመፈተሽ የይዘቶች አደረጃጀት ምሁራን
ከሚያስቀምጧቸው ንድፈ ሀሳቦች በመነሳት እና መረጃ መሰብሰቢያ ቅፅ በማዘጋጀት የትንተናው
ሂደት በአይነታዊና መጠናዊ መተንተኛ ዘዴ እንዲቀርብ ተደርጓል፡፡

ጥናቱ ከመለሳቸው መሰረታዊ ጥያቄዎች መካከል ቀዳሚው በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ
መማሪያ መፃሕፍት እና በመርሃ ትምህርቱ መካከል ያለው የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት
ተከታታይነት ዝምድና ምን ይመስላል?ነው፡፡ በመሆኑም በመማሪያ መፃሕፍት የተቀረፁት
የክሂልና የእውቀት ዘርፎች ተከታታይነት በመርሐ ትምህርቱ ከቀረቡ ይዘቶች ተከታታይነት ጋር
ያላቸውን ዝምድና ለማወቅ ፍተሻ ተካሂዷል፡፡ በተላውጦዎች መካከል ያለው ግንኙነት የታየው
በአይነታዊ የመተንተኛ ዘዴ በቃላት አስረጅዎችን በማጣቀስ እና በፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት
የተዛምዶ መለኪያ (pearson product-moment correlation)ነው፡፡ በመሆኑም በአስረኛ ክፍል
መማሪያ መፃሕፍት እና በመርሐ ትምህርቱ የይዘቶች ተከታታይንት መካከል ያለው የግንኙነት
መጠን ከዚህ በታች በቀረበው ሰንጠረዥ ቀርቧል፡፡

ሰንጠረዥ 4.1. በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍቱ እና በመርሃ ትምህርቱ መካከል

ያለው የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት ተከታታይነት ዝምድና

43
ተ.ቁ የትምህርት ይዘቶች በመርሐ ትምህርቱ በመማሪያ መፅሐፉ

የሚገኙበት ምዕራፍ የሚገኙበት ምዕራፍ

1 የምንባቡን ሃሳብ መገመት ምዕራፍ1፣2፣3፣4፣5፣6፣7፣8፣9፣10 በተመሣሣይ

2 የቀደመ እውቀትን ማነሳሳት ምዕራፍ 2፣4፣6፣8፣10 በተመሣሣይ

3 ዝርዝር ሃሳቦችን መለየት ምዕራፍ1፣2፣3፣4፣5፣6፣7፣8፣9፣10 በምዕራፍ 2፣3


አልተካተተም

4 የቃላትንናሓረጋትን አውዳዊ ፍች ምዕራፍ 1፣2፣3፣4፣5፣6፣8፣9፣10 በተመሣሣይ


መረዳት
5 ከተለያዩ የመረጃ ምንጮች ማሳተዋሻ ምዕራፍ 1፣3፣5፣7 ምዕራፍ 1፣3፣5፣7
መያዝ
6 አሳጥሮ መፃፍ ምዕራፍ 2፣4፣6፣9 ምዕራፍ 2፣4፣6፣9

7 አንቀፅ ምዕራፍ 1፣4፣7፣10 ምዕራፍ 1፣4፣7፣10

8 በፈሊጣዊ ቃላት ዓረፍተ ነገር ምዕራፍ 2፣4፣6፣8፣10 ምዕራፍ


መመስረት 2፣4፣6፣8፣10

9 ነፃና ጥገኛ ምዕላዶች ምዕራፍ 1፣2፣6፣10 ምዕራፍ 1፣6፣10

10 የሓረግ አይነቶችን ምዕራፍ 2፣4፣9 ምዕራፍ 2፣4፣9

ከላይ በቀረበው ሰንጠረዥ መረዳት እንደሚቻለው በአስረጅነት በየምዕራፉ የቀረቡት የቋንቋ


ትምህርት ይዘቶች በመርሐ ትምህርቱ እና በመማሪያ መፃሕፍቱ ውስጥ በተመሣሣይ መልኩ
በተከታታይነት እንደተደራጁ የሚያሳይ ነው፡፡ እነዚህም የትምህርት ይዘቶች በእያንዳንዱ ምዕራፍ
ውስጥ ተከታታይነት ባለው መልኩ ተደራጅተው ቀርበዋል፡፡ ለዚህም እንደማሳያ በተራ ቁጥር
አንድ የቀረበውን ይዘት ብንመለከት በሁሉም ምዕራፎች በመርሐ ትምህርቱም ይሁን በመማሪያ
መፅሐፉ በተመሣሣይ መልኩ ተከታትለው እንደቀረቡ ነው፡፡ አንዲሁም ከተራ ቁጥር ሁለት እስከ
አስር የቀረቡ ይዘቶችም ቢሆኑ በተለያዩ ምዕራፎች ይዘቶች ተከታትለው እንደመጡ ያሳያል፡፡
ይህም በመማሪያ መፅሐፉ እና በመርሐ ትምህርቱ መካከል ዝምድና እንዳለ ያመላክታል፡፡ ይሁን
እንጂ በተራ ቁጥር ሦስት በመርሐ ትምህርቱ በምዕራፍ ሦስት እና አራት የተካተተው ዝርዝር
ሃስብ የመለየት ንዑስ የአንብቦ መረዳት ይዘት በመማሪያ መፅሐፉ እንዳልቀረበ መመልከት
ተችሏል፡፡ በአጠቃላይ ሲታይ ግን ከላይ ከቀረበው አስረጅ መረዳት እንደሚቻለው በመርሐ
ትምህርቱ እና በመማሪያ መፃሕፍቱ የይዘቶች የተከታታይነት ዝምደና እንዳላቸው ነው፡፡ በዚሁ
ሃሳብ ስር የመርሐ ትምህርቱ እና የመማሪያ መፃሕፍቱ ይዘቶች የተማሪውን የመማር ሁኔታ
እና ዳራ ከግምት ውስጥ ያስገቡ መሆን አለመሆናቸው ፍተሻ ተካሂዷል፡፡ በመሆኑም የአስረኛ

44
ክፍል የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ይዘቶች ሲደራጁ የተማሪውን ዳራዊ ሁኔታ ከምግት ውስጥ
ያስገቡ ስለመሆናቸው ወይም አለመሆናቸው በአስረጃ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

ሰንጠረዥ 4.2. የአማርኛ መማሪያ መፃሕፍቱ እና የመርሃ ትምህርቱ ይዘቶች የተማሪዎችን


የመማር ሁኔታ ወይም ዳራዊ እውቀት ያገናዘቡ ስለመሆናቸው
ተ.ቁ የትምህርቱ ይዘት የሚገኝበት የሚገኝበት ገፅ
ምዕራፍ
በመርሐ በመፅሐፉ

1 ከተለያዩ ምንጮች ማስተዎሻ መያዝ ምዕራፍ 1 1 13

2 አንድን ሃሳብ በራስ አባባል መግለፅ ምዕራፍ 2 8 23

3 ከልቦለድ አላባዊያን ውስጥ መቼት እና ችብጥ የለያሉ ምዕራፍ 3 16 46

4 ቃላትን ነፃና ጥገኛ ምዕላድ በማለት ይለያሉ ምዕራፍ 1 1 14

5 የአንቀፅ ቅርፆችን ይለያሉ ምዕራፍ 3 16 39

6 አመዛዛኝ ድርሰት ይፅፋሉ ምዕራፍ 5 31 70

7 በቃል ውስጥ የሚጠብቁ እና የሚላሉ ድምፆችን ይለያሉ ምዕራፍ 4 8 60

8 በግጥም ውስጥ የሚጠብቁና የሚላሉ ቃላትን ይለያሉ ምዕራፍ 6 37 83

9 ነፃ እና ጥገኛ ምዕላዶችን አቀናጅተው ቃል ይመሰርታሉ ምዕራፍ 9 59 125

ከላይ ከቀረበው አስረጅ ሰንጠረዥ መረዳት እንደሚቻለው በመማሪያ መፅሃፉም ይሁን በመርሐ
ትምህርቱ የተለያዩ ምዕራፎች ላይ የቀረቡ ይዘቶች የተማሪዎችን የመማር ሁኔታ ወይም ዳራዊ
እውቀት ጠብቀው የቀረቡ መሆናቸውን መገንዘብ ይቻላል፡፡ ለአብነትም ቃላትን ነፃ እና ጥገኛ
ምዕላድ በማለት ይለያሉ በሚል ርዕስ ምዕራፍ አንድ ከተማሩ በኋላ ምዕራፍ ዘጠኝ ላይ ሲደርሱ
ደግሞ ነፃ እና ጥገኛ ምዕላድ አቀናጅተው ቃል እንዲመሰርቱ ይደረጋል፡፡በተመሳሳይ ስለአንቀፅ
ቅርፆች ምዕራፍ ሦስት ላይ እንዲማሩ ከተደረገ በኋላ በምዕራፍ አምስት ድርሰት እንዲፅፉ
ይበረታታሉ፡፡ ይህም አቀራረብ የተማሪዎችን አቅም እያዳበረ በሚሄድ ሁኔታ እንደተዘጋጀ
ከመጠቆሙም በላይ ቀጣዮቹ ይዘቶቹም የተማሪዎችን ዳራዊ እውቀት መሰረት እያደረጉ
እንደተዘጋጁ መገንዘብ ይቻላል፡፡ በተጨማሪም በመማሪያ መፅሐፉ እና በመርሐ ትምህርቱ

45
መካከል የቀረቡትን የይዘቶች ተከታታይነት የድግግሞሽ መጠን መሰረት በማድረግ በመካከለቻው
ያለውን ዝምድና አንደሚከተላው በፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት የተዛምዶ መለኪያ (pearson
product-moment correlation) ተሰልቷል፡፡ በዚህ ክፍል ጥናቱ ትኩረት ባደረገባቸው ከአስረኛ ክፍል
የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና ከመርሐ ትምህርት የተሰበሰቡት በየምዕራፉ የቀረቡ
ንዑሳን ይዘቶች ድምር ውጤቱ ብቻ የቀረበ ሲሆን በየምዕራፉ የቀረቡ ይዘቶች ብዛት
በአባሪ(አንድ፣ሁለት፣ሦስት፣አራት፣አምስትና ስድስት) ተያይዞ ቀርቧል፡፡

ሰንጠረዥ 4.3. በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሃፍ እና በመርሃ ትምህርቱ
በየምዕራፉ የቀረቡ የክሂልና የእውቀት ዘርፎች ተከታታይንት ዝምድና
ተ.ቁ የቋንቋ በመርሃ ትምህርትቱ የቀረቡ ይዘቶች በመማሪያ መፅሃፉ የቀረቡ
ትምህርት የድግግሞሽ ብዘት ይዘቶች የድግግሞሽ ብዛት
ይዘቶች በቁጥር በመቶኛ በቁጥር በመቶኛ
1 አንብቦ መረዳት 59 29.5 56 29.78
2 መናገር 25 12.5 25 13.3
3 ማዳመጥ 25 12.5 24 12.76
4 መፃፍ 37 18.5 35 18.6
5 ሰዋስው 28 14 23 12.2
6 ስነፅሁፍ 26 13 25 13.3
ድምር 200 100 188 100

የፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት የትንተና ውጤት


የይዘት ተከታታይነት ተዛምዶ መፃሕፍት መርሐ
መፃሕፍት ፒርሰን ተዛምዶ 1 0.98**

የጉልህነት ደረጃ .004

ብዛት 6 6

መርሐ ፒርሰን ተዛምዶ 0.98** 1

የጉልህነት ደረጃ .004

ብዛት 6 6

ከዚህ በላይ በቀረበው ሰንጠረዥ መረዳት እንደሚቻለው በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ
መፃሕፍቱ እና በመርሃ ትምህርቱ መካከል ያለውን የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት
ተከታታይነት ዝምድና በፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት የተዛምዶ መለኪያ (pearson product-moment
correlation) ተሰልቷል፡፡ በዚህም መሰረት መማሪያ መፃሕፍቱ ከመርሃ ትምህርቱ ጋር ያለው

46
የዝምድና መጠን በአዎንታዊ አቅጣጫ በጣም ከፍተኛ የተዛምዶ መጠን እንዳለው በስታትስቲክስ
ትንተና የስህተት ይሁንታ መጠን (p value) 0.05 ደረጃ በንሞና መጠን (sample size) 6 (r(6)=0.98,
p=0.004) ያሳያል፡፡

ጥናቱ ከመለሳቸው መሰረታዊ ጥያቄዎች መካከል ሁለተኛው በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ
መማሪያ መፃሕፍቱ እና በመርሃ ትምህርቱ መካከል ያለውን የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት
ተለጣጣቂነት ዝምድና ምን ይመስላል? የሚል ነበር በመሆኑም በመማሪያ መፃሕፍቱ የተቀረፁት
የክሂልና የእውቀት ዘርፎች ተለጣጣቂነት ከመርሐ ትምህርትቱ ከቀረቡ ይዘቶች ተለጣጣቂነት
ጋር ያላቸውን የዝምድና መጠን ለማወቅ ፍተሻ ተካሂዷል፡፡ በዚህ መሰረት በቀጣይ ተላውጦዎች
(Continuous Vairables) መካከል ያለውን ተዛምዶ በፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት የዝምድና መለኪያ
(pearson product-moment correlation) ተተንትኗል፡፡ በመሆኑም በአስረኛ ክፍል መማሪያ
መፃሕፍቱ እና በመርሐ ትምህርቱ የይዘቶች ተለጣጣቂነት መካከል ያለው የግንኙነት ከዚህ በታች
በቀረቡት ሰንጠረዦች ቀርበዋል፡፡ በዚህ ክፍል ጥናቱ ትኩረት ባደረገባቸው ከአስረኛ ክፍል
የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና ከመርሐ ትምህርት የተሰበሰቡት የክሂልና የእውቀት
ዘርፎች የቀረቡበት ዘዴ ድምር ውጤቱ ብቻ የቀረበ ሲሆን ንዑሳን የክሂልና የእውቀት ዘርፎች
የቀረቡበት ዘዴ ብዛት በአባሪ (ሰባት፣ ስምንት፣ ዘጠኝ፣ አስር፣ አስራ አንድ እና አስራ ሁለት)
ተያይዞ ቀርቧል፡፡

ሰንጠረዥ 4.4 በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሃፍ እና በመርሃ ትምህርቱ
የክሂልና የእውቀት ዘርፎች ተለጣጣቂነት ዝምድና
ተ.ቁ የቋንቋ ትምህርት በመርሃ ትምህርትቱ ይዘቶች የቀረቡበት በመማሪያ መፅሃፉ ይዘቶች የቀረቡበት
ይዘቶች ዘዴ የድግግሞሽ ብዘት ዘዴ የድግግሞሽ ብዛት

በቁጥር በመቶኛ በቁጥር በመቶኛ


1 አንብቦ መረዳት 21 12.96 19 12.5
2 መናገር 37 22.8 37 24.3
3 ማዳመጥ 20 12.3 16 10.5
4 መፃፍ 30 18.5 29 19.1
5 ሰዋስው 29 17.9 27 17.7
6 ስነፅሁፍ 25 15.4 24 15.7
ድምር 162 100 152 100

47
የፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት የትንተና ውጤት
የይዘት ተለጣጣቂነት ተዛምዶ መፃሕፍት መርሐ
መፃሕፍት ፒርሰን ተዛምዶ 1 0.91**

የጉልህነት ደረጃ .010

ብዛት 6 6

መርሐ ፒርሰን ተዛምዶ 0.91** 1

የጉልህነት ደረጃ .010

ብዛት 6 6

ከዚህ በላይ በቀረበው ሰንጠረዥ መረዳት እንደሚቻለው በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ
መፃሕፍት እና በመርሃ ትምህርቱ መካከል ያለውን የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት
ተለጣጣቂነት ዝምድና በፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት የተዛምዶ መለኪያ (pearson product-moment
correlation) ተሰልቷል፡፡ በዚህም መሰረት መማሪያ መፃሕፍቱ ከመርሃ ትምህርቱ ጋር ያለው
የዝምድና መጠን በአዎንታዊ አቅጣጫ በጣም ከፍተኛ የግንኙነት መጠን እንዳለው በስታትስቲክስ
ትንተና የስህተት ይሁናታ መጠን (p value) 0.05 ደረጃ በንሞና መጠን (sample size) 6 (r(6)=0.91,
p=0.01) ያሳያል፡፡

ጥናቱ ከመለሳቸው መሰረታዊ ጥያቄዎች መካከል ሦስተኛው በአስረኛ ክፍል በአማርኛ እና


እንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት መካከል ያለው የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት
ውህዳዊነት ዝምድና ምን ይመስላል? ነው፡፡ በመሆኑም በአስረኛ ክፍል አማርኛ መማሪያ
መፃሕፍት የተቀረፁት የክሂልና የእውቀት ዘርፎች ከአስረኛ ክፍል የእንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ
መፃሕፍት ከቀረቡ ይዘቶች ውህዳዊነት ጋር ያላቸውን ዝምድና ለማወቅ ፍተሻ ተካሂዷል፡፡
በመሆኑም በአስረኛ ክፍል አማርኛ እና እንግሊዝኛ መማሪያ መፃሕፍት የይዘቶች ውህዳዊነት
መካከል ያለው ግንኙነት ከዚህ በታች በቀረበው ሰንጠረዥ ቀርቧል፡፡

ሰንጠረዥ 4.5. በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሃፍ ያለው የክሂልና የእውቀት ዘርፎች

48
የይዘት ውህዳዊነት የዝምድና መጠን

ተ.ቁ በመርሀ ትምህርቱ ውስጥ የቀረቡ የቋንቋ ትምህርት ይዘቶች

10ኛ ክፍል አማርኛ መማሪያ መፃሕፍት 10ኛ ክፍል እንግሊዝኛ መማሪያ መፃሕፍት

1 የምንባቡን ሃሳብ መገመት Prognosis introspection of reading

2 የቀደመ እውቀትን ማነሳሳት motivation background knowledge

3 ዝርዝር ሃሳቦችን መለየት Identifying the main point

4 የቃላትንናሓረጋትን አውዳዊ ፍች መረዳት Drawing inferences about the meaning of a word in


context

5 ከተለያዩ የመረጃ ምንጮች ማስታዎሻ መያዝ Recognise and understand expressions of


preferences

6 አሳጥሮ መፃፍ Summarising a new report

7 አንቀፅ Argumentative or persuasive paragraphs

8 በፈሊጣዊ ቃላት ዓረፍተ ነገር መመስረት building correct and appropriate sentences

9 ነፃና ጥገኛ ምዕላዶች Prefixes and affixes

10 የሐረግ አይነቶች word building

ከላይ የቀረበው ሰንጠረዥ እንደሚያሳየው በአስረኛ ክፍል የአማርኛ እና እንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ
መጽሐፍ ውስጥ የተካተቱ የተወሰኑ የቋንቋ ትምህርት ይዘቶች በአስረጅነት ቀርበዋል፡፡ እነዚህም
ይዘቶች ውህዳዊነት ባለው መልኩ ማለትም የአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ ከእንግሊዝኛ መማሪያ
መጽሐፍ ተዋህዶ የመቅረቡ ሁኔታ ሲታይ፣ በሁለቱም የትምህርት ዓይነቶች በተመሳሳይ
የትምህርት ይዘት ገብተው የተማሪዎችን ደረጃ ባገናዘበ አኳያ የተደራጁ የትምህርት ይዘቶች
እንዳሉ ለመለየት ተችሏል፡፡ ለዚህም እንደማሳያ በሁለቱም የትምህርት ዓይነቶች የቀረቡ
ተመሳሳይ የትምህርት ይዘቶችን ከዚህ በታች በቀረበው መልኩ እንመልከት፡፡ እነዚህም የምንባብን
ሃሳብ መገመት፣ የቀደመ እውቀት ማነሳሳት፣ ዝርዝር እና ዋና ሃሳቦችን መለየት፣ አሳጥሮ
መፃፍ፣ አንቀፅ፣ ፈሊጣዊ ቃላት፣ ምዕላድ ወዘተ. እነዚህ ከላይ የተዘረዘሩት የትምህርት ይዘቶች
በአስረኛ ክፍል የአማርኛ እና እንግሊዝኛ የቋንቋ ትምህርት ይዘቶች ውስጥ ተመሳሳይነት ባለው
መልኩ የቀረቡ ናቸው፡፡ እነዚህም ይዘቶች፣ በሁለቱም የትምህርት ዓይነቶች የሚገኙ ቢሆንም፣
አቀራረባቸው ግን የተለያየ ሆኖ ይገኛል፡፡ ለምሳሌ፡ በአስረኛ ክፍል እንግሊዝኛ ቋንቋ ተማሪዎች
የአንቀፅ ማስፋፊያ ዘዴዎች እንዲማሩ የተደረገ ሲሆን በአስረኛ ክፍል አማርኛ ትምህርት ደግሞ

49
የአንቀፅ ቅርፆች ላይ ትኩረት አድርጓል፡፡ እንዲሁም ምዕላድን በተመለከተ አስረኛ ክፍል አማርኛ
ቋንቋ መማሪያ ላይ የዕርባታ እና መስራች ቅጥያ ምዕላዶችን እንዲለዩ የተደረገ ሲሆን በአስረኛ
ክፍል እንግሊዝኛ መማሪያ መፃሕፍት ውስጥ ደግሞ ለቃላት አገነባብ ትኩረት ተሰጧል፡፡ ከዚህም
መረዳት የሚቻለው በሁለቱም የቋንቋ ትምህርቶች ውስጥ የቀረበው የቋንቋ ትምህርት ይዘት
ከውህዳዊነት አንጻር በተገቢው ሁኔታ ተደራጅቶ መቅረብ እንደቻለ ነው፡፡

በተጨማሪም በአስረኛ ክፍል የአማርኛ እና እንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት መካከል


የቀረቡትን የይዘቶችን ውህዳዊነት የድግግሞሽ መጠን መሰረት በማድረግ በመካከላቸው ያለውን
ዝምድና እንደሚከተለው በፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት የተዛምዶ መለኪያ (pearson product-
moment correlation) ተሰልቷል፡፡ በዚህ ክፍል ጥናቱ ትኩረት ባደረገባቸው በአስረኛ ክፍል
የአማርኛ እና እንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት የተሰበሰቡ ንዑሳን ይዘቶች ድምር ውጤቱ
ብቻ የቀረበ ሲሆን በየምዕራፉ የቀረቡ ይዘቶች ብዛት በአባሪ(አስራ ሦስት፣ አስራ አራት፣ አሰራ
አምስት፣ አስራአ ስድስት፣ አስራ ሰባትእና አስራስ ምንት) ተያይዞ ቀርቧል፡፡

ሰንጠረዥ 4.6. በአስረኛ ክፍል በአማርኛ እና እንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሃፍ የክሂልና
የእውቀት ዘርፎች ውህዳዊነት ዝምድና

ተ.ቁ የቋንቋ በ10ኛ ክፍል አማርኛ መማሪያ መፅሃፍ በ10ኛ ክፍል የእንግሊዘኛ መማሪያ መፅሃፍ
ትምህርት የተካተቱ ይዘቶች የድግግሞሽ ብዘት የተካተቱ ይዘቶች የድግግሞሽ ብዛት
ይዘቶች በቁጥር በመቶኛ በቁጥር በመቶኛ
1 አንብቦ መረዳት 59 29.5 57 30.2
2 መናገር 25 12.5 33 17.5
3 ማዳመጥ 25 12.5 27 14.3
4 መፃፍ 37 18.5 23 12.2
5 ሰዋስው 28 14 24 12.7
6 ስነፅሁፍ 26 13 25 13.22
ድምር 200 100 189 100

የፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት የትንተና ውጤት

50
የይዘት ውህዳዊነት ተዛምዶ አ.መፃሕፍት 10ኛ እ.መፃሕፍት 10ኛ
ክፍል ክፍል
አ.መፃሕፍት 10ኛ ፒርሰን ተዛምዶ 1 .84**
ክፍል የጉልህነት ደረጃ .004

ብዛት 6 6
እ.መፃሕፍት 10ኛ ፒርሰን ተዛምዶ .84** 1
ክፍል የጉልህነት ደረጃ .004

ብዛት 6 6

ከዚህ በላይ በቀረበው ሰንጠረዥ መረዳት እንደሚቻለው በአስረኛ ክፍል የአማርኛና የእንግሊዝኛ
ቋንቋ መማሪያ መፅሃፍ መካከል ያለውን የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት ውህዳዊነት ዝምድና
በፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት የተዛምዶ መለኪያ (pearson product-moment correlation)
ተሰልቷል፡፡ በዚህም መሰረት የአስረኛ ክፍል የአማርኛ መማሪያ መፃሕፍት ከእንግሊዝኛ መማሪያ
መፃሕፍት ጋር ያለው የግንኙነት መጠን በአዎንታዊ አቅጣጫ በጣም ከፍተኛ የዝምድና መጠን
እንዳለው በስታትስቲክስ ትንተና የስህተት ይሁንታ መጠን (p value) 0.05 ደረጃ በንሞና መጠን
(sample size) 6 (r(6)=0.84, p=0.004) ያሳያል፡፡

ጥናቱ ከመለሳቸው መሰረታዊ ጥያቄዎች መካከል አራተኛው በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ
መማሪያ መፃሕፍት እና በመርሃ ትምህርቱ ውስጥ ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች ያላቸው
ዝምድና ምን ይመስላል? ነው፡፡ በመሆኑም በመማሪያ መፃሕፍቱ ውስጥ ለምዘና ተግባር የዋሉ
ስራዎችና መልመጃዎች ከመርሐ ትምህርቱ ውስጥ ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎችና
መልመጃዎች ጋር ያላቸውን የዝምድና መጠን ለማወቅ ፍተሻ ተካሂዷል፡፡ በመሆኑም በአስረኛ
ክፍል መማሪያ መፃሕፍት እና በመርሐ ትምህርቱ ውስጥ ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎችና
መልመጃዎች መካከል ያለው የግንኙነት መጠን ከዚህ በታች በቀረበው ሰንጠረዥ ቀርቧል፡፡ በዚህ
ክፍል ጥናቱ ትኩረት ባደረገባቸው ከአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና
ከመርሐ ትምህርት ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች የተሰበሰቡት ንዑሳን ይዘቶች ድምር ውጤቱ
ብቻ የቀረበ ሲሆን በክሂል እና የእውቀት ዘርፎች የቀረቡ ይዘቶች ብዛት በአባሪ(አስራ
ዘጠኝ፣ሃያ፣ሃያአንድ፣ሃያ ሁለት፣ሃያ ሦስት እና ሃያ አራት) ተያይዞ ቀርቧል፡፡

ሰንጠረዥ 4.7 በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍትና በመርሃ ትምህርቱ

51
ውስጥ ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች ያላቸውን የዝምድና መጠን
ተ. የቋንቋ ትምህርት በመርሃ ትምህርትቱ ለምዘና ተግባር በመማሪያ መፅሃፉ ለምዘና ተግባር
ቁ ይዘቶች የዋሉ ስራዎች የድግግሞሽ ብዘት የዋሉ ስራዎች የድግግሞሽ ብዛት

በቁጥር በመቶኛ በቁጥር በመቶኛ


1 አንብቦ መረዳት 30 14.7 27 14.4
2 መናገር 44 21.6 41 21.9
3 ማዳመጥ 35 17.2 34 18.2
4 መፃፍ 42 20.6 39 20.8
5 ሰዋስው 24 11.8 21 11.22
6 ስነፅሁፍ 28 13.8 25 13.4
ድምር 203 100 187 100

የፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት የትንተና ውጤት


ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች ተዛምዶ
መፃሕፍት መርሐ
መፃሕፍት ፒርሰን ተዛምዶ 1 0.99**

የጉልህነት ደረጃ .010

ብዛት 6 6

መርሐ ፒርሰን ተዛምዶ 0.99** 1

የጉልህነት ደረጃ .010

ብዛት 6 6

ከዚህ በላይ በቀረበው ሰንጠረዥ መረዳት እንደሚቻለው በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ
መፅሃፍ እና በመርሃ ትምህርቱ ውስጥ ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎችና መልመጃዎች ዝምድና
በፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት የተዛምዶ መለኪያ (pearson product-moment correlation)
ተሰልቷል፡፡ በዚህም መሰረት መማሪያ መፅሃፍ ከመርሃ ትምህርቱ ጋር ያለው የዝምድና መጠን
በአዎንታዊ አቅጣጫ በጣም ከፍተኛ የተዛምዶ መጠን እንዳለው በስታትስቲክስ ትንተና የስህተት
ይሁንታ መጠን (p value) 0.05 ደረጃ በንሞና መጠን (sample size) 6 (r(6)=0.99, p=0.01) ያሳያል፡፡

4.2 የውጤት ማብራሪያ


የዚህ ጥናት ዋና አላማ በ2004 ዓ.ም በአንደኛ አትም ታትመው በአሁኑ ወቅት ሥራ ላይ ያሉትን
የአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና መርሀ ትምህርቱ ያላቸውን ዝምድና
መፈተሸ ነበር፡፡ ይህንን ዓላማ ከግብ ለማድረስ መረጃዎች በሰነድ ፍተሻ ተሰብስበው በአይነታዊ

52
እና መጠናዊ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴ ተተንትኗል፡፡ የዚህ ጥናት የመጀመሪያው ዓላማ በአስረኛ
ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሃፍ እና በመርሃ ትምህርቱ መካከል ያለውን የክሂልና
የእውቀት ዘርፎች የይዘት ተከታታይንት ዝምድና መፈተሽ ሲሆን የተገኘው መረጃ ከተደራጀ
በኋላ በአይነታዊ እና በመጠናዊ (ፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት የተዛምዶ መለኪያ) የዝምድና ሁኔታ
ተተንትኗል፡፡ ውጤቱ እንደሚያሳየው መማሪያ መፃሕፍቱ ከመርሃ ትምህርቱ ጋር ዝምድና
እንዳለው ነው፡፡ የዝምድና መጠኑ በአዎንታዊ አቅጣጫ በጣም ከፍተኛ መሆኑን ነው፡፡ ይህም
Nunan (1984)የመማሪያ መፃሕፍትእና የመርሃ ትምህርት ግንኙነት አስመልክቶ የቋንቋ መማሪያ
መፅሃፍ ያለምንም ማወላወል መርሃ ትምህርቱ በተግባር የሚገለፅበት ነው፡፡በመሆኑም የቋንቋ
መማሪያ መፃሕፍት ሲገመገም፣ ሲሻሻል፣ ሲዘጋጅ፣ ሲፃፍ ወዘተ. የተዘጋጀውን መርሃ ትምህርት
መሠረት ማድረግ እንዳለበት የሚያስገነዝብ በመሆኑ በሁለቱ መሳሪያዎች መካከል የጠበቀ
ዝምድና ሊኖር ይገባል፡፡ Dubin and Olshtain (1986) በበኩላቸው የመማሪያ መፃሕፍት ከመርሃ
ትምህርቱ ጋር መስማማትና መርሃ ትምህርቱ ውስጥ የሚነሱት ፍሬ ነገሮች ሁሉ አንድነታቸውን
በግልፅ ማየትና የይዘቶች አደረጃጀት ከመርሃ ትምህርቱ ጋር መስማማት የግድ ነው በማለትም
በመርሃ ትምህርቱ የተገለጹ ሃሳቦች በሙሉ በመማሪያ መፃሕፍት ውስጥ መስፈር ይኖርባቸዋል
በማለት ያስረዳሉ፡፡ የጥናቱ ግኝትም ከዚህ ንደፈ ሃሳብ ተገናኝቶ ታይቷል፡፡ እንዲሁም መማሪያ
መፃህፍት ከመርሐ ትምህርቱ ጋራ ዝምድና ይጎሏቸዋል ከሚሉት እያሱ (2003)፣ ሐዋዝ(2000)
የጥናት ውጤት ተቃርኗል፡፡ከሰሚራ(2010) የጥናት ውጤት ጋር ተመሳስሏል፡፡

የዚህ ጥናት ሁለተኛ ዓላማ በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃህፍትና በመርሃ
ትምህርቱ መካከል ያለውን የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት ተለጣጣቂነት ዝምድና መመርመር
ሲሆን የተገኘው መረጃ ከተደራጀ በኋላ በፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት የተዛምዶ መለኪያ (pearson
product-moment correlation) የዝምድና ሁኔታ ተተንትኖ ውጤቱ እንደሚያሳየው መማሪያ
መፃህፍት ከመርሃ ትምህርቱ ጋር ያለው የዝምድና መጠን በአዎንታዊ አቅጣጫ በጣም ከፍተኛ
መሆኑን ነው፡፡ (ዝርዝር ጉዳዩን አባሪ ሁለት፣ሦስት እና አራት ይመልከቱ)፡፡ይህም በምዕራፍ
ሁለት Grant(1987) የቋንቋ መማሪያ መጻህፍትን መሰረት አድርገው የሚነሱት የቋንቋውን
ትምህርት አላማ ማዕከል ባደረገ መንገድ በስርዓተ ትምህርቱና በመርሀ ትምህርቱ ዝግጅትና
አደረጃጀት የሚካተቱ ይዘቶችን የያዙ ሰነዶች እንዲሆኑ ይታመናል በማለት ያስረዳሉ፡፡
Cunningsworth(1995) አገላለጽ የቋንቋ መማሪያ መጻህፍት ዝግጅት መረጣ (አደረጃጀት) የቋንቋ
ትምህርቱ በሚከተለው የትምህርት ፍልስፍና ወይም ትወራ ላይ እንደሚመሰረት መረዳትእና

53
ተከታታይነት፣ ተለጣጣዊነት፣ ውህዳዊነት፣ አበረታችነት፣ ተጣጣሚነት፣ ጥልቀት ተተግባሪነት
(ተግባራዊነት) የሚሉትን ያካተተ መሆኑን በጥንቃቄ መለየት እንደሚገባ መረዳት፣የቋንቋ
መማሪያ መጻህፍት ዝግጅት ታሪክ ከባህላዊ (ጥንታዊ) እና ከዘመናዊ የቋንቋ መማሪያ መጻህፍት
አዘጋጆች ሞዴል አንጻር መታየት አንደሚኖርባቸው መርሆዎች ያስገነዝባሉ፡፡የጥናቱ ግኝትም
ከዚህ ንደፈ ሃሳብ ተገናኝቶ ታይቷል፡፡ ይህም መማሪያ መፅሐፍት ከመርሐ ትምህርቱ ጋራ
ዝምድና ይጎሏቸዋል ከሚሉት እያሱ (2003)፣ ሐዋዝ(2000) የጥናት ውጤት ተቃርኗል፡፡

የዚህ ጥናት ሦስተኛው ዓላማ በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሃፍ ያለውን የክሂልና
የእውቀት ዘርፎች የይዘት ውህዳዊነት መመርመር ሲሆን የተገኘው መረጃ ከተደራጀ በኋላ
በአይነታዊ እና መጠናዊ (ፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት የተዛምዶ መለኪያ) የዝምድና ሁኔታ
ተተንትኗል፡፡ ውጤቱ እንደሚያሳየው የአስረኛ ክፍል የአማርኛ መማሪያ መፃሕፍት ከእንግሊዝኛ
መማሪያ መፃሕፍት ጋር ዝምድና እንዳለው ነው፡፡ የዝምድና መጠኑም በአዎንታዊ አቅጣጫ
በጣም ከፍተኛ መሆኑን ነው፡፡ ይህም Dubin and Olshtain (1986) በበኩላቸው የመማሪያ መፃሕፍት
ከመርሃ ትምህርቱ ጋር መስማማትና መርሃ ትምህርቱ ውስጥ የሚነሱት ፍሬ ነገሮች ሁሉ
አንድነታቸውን በግልፅ ማየትና የይዘቶች አደረጃጀት ከመርሃ ትምህርቱ ጋር መስማማት የግድ
ነው በማለትም በመርሃ ትምህርቱ የተገለጹ ሃሳቦች በሙሉ በመማሪያ መፃሕፍት ውስጥ መስፈር
ይኖርባቸዋል በማለት ያስረዳሉ፡፡ የጥናቱ ግኝትም ከዚህ ንደፈ ሃሳብ ተገናኝቶ ታይቷል፡፡
እንዲሁም መማሪያ መፃህፍት ከመርሐ ትምህርቱ ጋራ ዝምድና ይጎሏቸዋል ከሚሉት እያሱ
(2003)፣ ሐዋዝ(2000) የጥናት ውጤት ተቃርኗል፡፡

የዚህ ጥናት አራተኛ ዓላማ በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና በመርሃ
ትምህርቱ ውስጥ ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች ያላቸውን ዝምድና መፈተሸ ሲሆን የተገኘው
መረጃ ከተደራጀ በኋላ በፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት የተዛምዶ መለኪያ (pearson product-moment
correlation) የዝምድና ሁኔታ ተተንትኖ፣ ውጤቱ እንደሚያሳየው በመማሪያ መፃህፍት ውስጥ
ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች በመርሃ ትምህርቱ ውስጥ ለምዘና ተግባር ከዋሉ ስራዎች ጋር
ያለው የዝምድና መጠን በአዎንታዊ አቅጣጫ በጣም ከፍተኛ መሆኑን ነው፡፡ ይህም Nunan
(1984)የመማሪያ መፃህፍትእና የመርሃ ትምህርት ግንኙነት አስመልክቶ የቋንቋ መማሪያ
መፃህፍት ያለምንም ማወላወል መርሃ ትምህርቱ በተግባር የሚገለፅበት መሆኑን ያስረዳሉ፡፡
የጥናቱ ግኝትም ከዚህ ንደፈ ሃሳብ ተገናኝቶ ታይቷል፡፡ ይህም መማሪያ መፃህፍት ከመርሐ

54
ትምህርቱ ጋራ ዝምድና ይጎሏቸዋል ከሚሉት እያሱ (2003)፣ ሐዋዝ(2000) የጥናት ውጤት
ተቃርኗል፡፡

ምዕራፍ አምስት፤ማጠቃለያ፣መደምደሚያና አስተያየት

5.1 ማጠቃለያ
የዚህ ጥናት ዋና አላማ በ2004 ዓ.ም በአንደኛ እትም ታትመው በአሁኑ ወቅት ሥራ ላይ ያሉትን
የአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና መርሀ ትምህርቱ ያላቸውን ዝምድና
መፈተሽ ነበር፡፡በዚህ መሰረት ጥናቱ የመለሳቸው ዝርዝር ጥያቄዎች፡-

1. በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና በመርሃ ትምህርቱ መካከል ያለው
የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት ተከታታይነት ዝምድና ምን ይመስላል?

55
2. በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት በመርሃ ትምህርቱ መካከል ያለው
የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት ተለጣጣቂነት ዝምድና ምን ይመስላል?
3. በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ያለው የክሂልና የእውቀት ዘርፎች
የይዘት ውህዳዊነት ግንኙነት ምን ይመስላል?
4. በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና በመርሃ ትምህርቱ ውስጥ ለምዘና
ተግባር የዋሉ ስራዎች ያላቸው ዝምድና ምን ይመስላል? የሚሉት ናቸው፡፡

ለነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ ለማግኘት አጥኝው አይነታዊ እና መጠናዊ የምርምር አይነቶችን


በመጠቀም ተዛምዷዊ ስልት ተከትሏል፡፡ በክለሳ ድርሳን ላይ ምሁራን ያቀረቧቸውን ንድፈ
ሃሳባዊ መሰረቶች በመንተራስም ሰነዶቹን ለመገምገም የሚያስችል ቅፅ በማዘጋጀት መረጃዎችን
ለመሰብሰብ ተችሏል፡፡መረጃዎች በግብዓትነት የተወሰዱት በአላማ ተኮር የንሞና ዘዴ በተመረጡ
በ2004ዓ.ም ታትሞ ስራ ላይ በዋለው የአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና
ከመርሀ ትምህርቱ ሲሆን በተጨማሪም የአስረኛ ክፍል የእንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍ
ነው፡፡በፍተሻው የተለያዩ ሊቃውንት ስለመማሪያ መፃሕፍት የቋንቋ ትምህርት ይዘቶች አደረጃጀት
እና ግምገማ በተመለከተ ያስቀመጧቸውን ንድፈ ሀሳቦች መሰረት በማድረግ መማሪያ መፃሕፍቱ
ከመርሐ ትምህርቱ ጋር ያለውን የዝምድና ፍተሻ ለማድረግ ተችሏል፡፡ መማሪያ መፃሕፍቱ
ከመርሐ ትምህርቱ ጋር ያለውን የዝምድና መጠን ምን ያክል እንደሆነ በሰነድ ፍተሻ ተሰብስቦ
በበፒርሰን ፕሮዳክት ሞመንት የተዛምዶ መለኪያ (pearson product-moment correlation) የዝምድና
ሁኔታው ተተንትኗል፡፡ የተገኙ መረጃዎችን በመተንተንም የሚከተሉት ግኝቶች ላይ ተደርሷል፡፡

የዚህ ጥናት የመጀመሪያ ዓላማ በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና በመርሃ
ትምህርቱ መካከል ያለውን የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት ተከታታይነት ዝምድና መፈተሽ
ነበር፡፡ በመሆኑም መማሪያ መፃሕፍቱ ከመርሃ ትምህርቱ ጋር ያለው የክሂልና የእውቀት ዘርፎች
የይዘት ተከታታይነት የዝምድና መጠን በስታትስቲክስ ትንተናው 0.98 በመሆኑ በአዎንታዊ
አቅጣጫ በጣም ከፍተኛ የተዛምዶ መጠን እንዳለው ጥናቱ አረጋግጧል፡፡

የዚህ ጥናት ሁለተኛ ዓለማ በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍቱና በመርሃ
ትምህርቱ የይዘት ተለጣጣቂነት ዝምድና መመርመር ነበር፡፡ መማሪያ መፃሕፍቱ ከመርሃ
ትምህርቱ ጋር ያለው የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት ተለጣጣቂነት የዝምድና መጠን
በስታትስቲክስ ትንተናው 0.91 በመሆኑ በአዎንታዊ አቅጣጫ በጣም በከፍተኛ የተዛምዶ መጠን
እንዳለው ውጤቱ አሳይቷል፡፡

56
የጥናቱ ሥስተኛ ዓላማ ደግሞ በአስረኛ ክፍል የአማርኛ እና እንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት
መካከል ያለው የክሂሎችና የእውቀት ዘርፎች የይዘት ውህዳዊነት ተዛምዶ መመርመር ነው፡፡
በመማሪያ መፃሕፍቱ ያለው የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት ውህዳዊነት የዝምድና መጠን
በስታትስቲክስ ትንተናው 0.84 በመሆኑ በአዎንታዊ አቅጣጫ በጣም ከፍተኛ የዝምድና መጠን
እንዳለው ጥናቱ አረጋግጧል፡፡

የዚህ ጥናት የመጨረሻው ጉዳይ በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና በመርሃ
ትምህርቱ ውስጥ ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች ያላቸውን ዝምድና መፈተሸ ሲሆን በአስረኛ
ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ውስጥ ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች በመርሃ
ትምህርቱ ውስጥ ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች የዝምድና መጠን በስታትስቲክስ ትንተናው
0.99 በመሆኑ በአዎንታዊ አቅጣጫ በጣም ከፍተኛ የተዛምዶ መጠን እንዳለው ውጤቱ
አሳይቷል፡፡

5.2 መደምደሚያ
የዚህ ጥናት ዋና ዓለማ በ2004 ዓ.ም በአንደኛ እትም ታትመው በአሁኑ ወቅት ሥራ ላይ
ያሉትን የአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና መርሀ ትምህርቱ ያላቸውን
ዝምድና መፈተሽ ነበር፡፡በመሆኑም የጥናቱን ትንተናና ውጤት መነሻ በማድረግ ከሚከተሉት
መደምደሚያዎች ላይ ተደርሷል፡፡

የአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍቱ ከመርሃ ትምህርቱ ጋር ያለው የክሂልና
የእውቀት ዘርፎች የይዘት ተከታታይነት የዝምድና መጠን በአዎንታዊ አቅጣጫ በጣም ከፍተኛ
የተዛምዶ መጠን እንዳለው መደምደሚያ ላይ መድረስ ተችሏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ እነዚህ
መማሪያ መፃሕፍት ከመርሃ ትምህርቱ ጋር ያለው የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት
ተለጣጣቂነት የዝምድና መጠን በአዎንታዊ አቅጣጫ በጣም ከፍተኛ የተዛምዶ መጠን እንዳለው
ተረጋግጧል፡፡እንዲሁም በአስረኛ ክፍል አማርኛና እንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት መካከል
ያለው የክሂልና የእውቀት ዘርፎች የይዘት ውህዳዊነት የዝምድና መጠን በአዎንታዊ አቅጣጫ
በጣም ከፍተኛ የዝምድና መጠን እንዳለው ጥናቱ አረጋግጧል፡፡ በመጨረሻም በአስረኛ ክፍል
በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ውስጥ ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች በመርሃ ትምህርቱ
ውስጥ ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች ዝምድና በተመለከተ ደግሞ በአዎንታዊ አቅጣጫ በጣም
ከፍተኛ የተዛምዶ መጠን እንዳለው ድምዳሜ ላይ ተደርሷል፡፡

57
5.3 አስተያየት
የዚህ ጥናት ዋና ዓላማ በ2004 ዓ.ም በአንደኛ እትም ታትመው በአሁኑ ወቅት ሥራ ላይ ያሉትን
የአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት እና መርሀ ትምህርቱ ያላቸውን ዝምድና
መፈተሽ ነበር፡፡ይህን በተመለከተም በሰነድ መፈተሻ የመረጃ መሰብሰቢያ መሳሪያ ተሰብስቦ እና
ተደራጅቶ ተተንትኗል፤ ውጤቱም ማብራሪያ ተደርጎበታል፡፡ ከዚህ በመነሳትም ማጠቃለያና
መደምደሚያ ላይ ተደርሷል፡፡ ከመደምደሚያው በመነሳትም አጥኝው የሚከተሉትን የመፍትሄ
አስተያየቶች ሰንዝሯል፡፡

 መማሪያ መፃሕፍቱ ከመርሐ ትምህርቱ ጋር ያለውን የተከታታይንት ዝምድና በተመለከተ


በአዎንታዊ አቅጣጫ በጣም ከፍተኛ የተዛምዶ መጠን እንዳለው የተረጋገጠ ሲሆን በቀጣይ
የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ሲዘጋጁ ሙሉ በሙሉ ከመርሃትምህርቱ ጋር ዝምድና
እንዲኖራቸው ቢደረግ እንዲሁም ከዚህ መማሪያ መፃሕፍት ተሞክሮ ቢወሰድ፣
 መማሪያ መፃሕፍቱ ከመርሐ ትምህርቱ ጋር ያለውን የተለጣጣቂነት ዝምድና በተመለከተ
በአዎንታዊ አቅጣጫ በጣም ከፍተኛ የተዛምዶ መጠን እንዳለው የተረጋገጠ ሲሆን በቀጣይ
የቋንቋ መማሪያ መፃሕፍት ሲዘጋጁ ሙሉ በሙሉ ከመርሃትምህርቱ ጋር ዝምድና
እንዲኖራቸው ቢደረግ እንዲሁም ከዚህ መማሪያ መፃሕፍት ተሞክሮ ቢወሰድ፣
 የአስረኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መመሪያ መፃሕፍት ከዚሁ የክፍል ደረጃ እንግሊዘኛ
መማሪያ መፃሕፍት ጋር ያለው የዝምድና መጠና በጣም ከፍተኛ ቢሆንም በቀጣይ የቋንቋ
መማሪያ መፃሕፍት ሲዝጋጅ ከዚህ በተሻለ የይዘት ውህዳዊነቱ የጠበቀ መማሪያ መፃሕፍት
እንዲዘጋጅ ጥረት ቢደረግ፣
 በአማርኛ መማሪያ መፃሕፍቱ ውስጥ ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎችና መልመጃዎች
በመርሃ ትምህርቱ ውስጥ ለምዘና ተግባር ከዋሉ ስራዎች ጋር ያላቸው የዝምድና መጠን
በጣም ከፍተኛ ቢሆንም በቀጣይ የመማሪያ መፃሕፍት አዘጋጆች መማሪያ መፃህፍት
ሲያዘጋጁ ሙሉ በሙሉ ከመርሃትምህርቱ ጋር ዝምድና እንዲኖራቸው ቢያደርጉ፣

 በመጨረሻም የቋንቋ ትምህርት ይዘቶች አደረጃጀት በተመለከተ በጥልቀት ምርምር


ቢደረግብት የሚል ምክረ ሃሳብ አጥኝው አቅርቧል፡፡

58
ዋቢ ፅሁፎች
ሐዋዝ ወልደየስ (2000)፡፡ “በአዲስ አበባ ከተማና በአማራ ክልል አንደኛና ሁለተኛ እርከን
የአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መጽሀፍት ውስጥ የሰዋስው ትምህርት አደረጃጀትና አቀራረብ
ንጽጽራዊ ጥናት፡፡” በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ድህረ ምረቃ ትምህርት ቤት ለአማርኛ
ማስተማር ኤም.ኤ.ዲግሪ በከፊል ማሟያነት የቀረበ ጥናት (ያልታተመ)፡፡
ሰሚራ አሊ፡፡ (2010)፡፡ በደቡብ ክልል በ2009 ዓ.ም. ስራ ላይ በዋለው የ8ኛ ክፍል የአማርኛ
ቋንቋ መማሪያ መጽሐፍ ውስጥ የተካተቱ የሰዋስው ትምህርት ይዘቶች አቀራረብና
አደረጃጀት፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ድህረ ምረቃ ትምህርት ቤት ለአማርኛ ማስተማር
ኤም.ኤ.ዲግሪ በከፊል ማሟያነት የቀረበ ጥናት (ያልታተመ)፡፡
ተስፋዬ ሽዋየ፡፡ (1981 ዓ.ም)፡፡ “ስነ ልሳንና ቋንቋን ማስተማር”፡፡ አዲስ አበባ /ያልታተመ/፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር፡፡ (2004 ዓ.ም)፡፡ አማርኛ የመምህሩ መማሪያ 10ኛ ፍፍል፡፡ የአል-
ጉራር አታሚና አሳታሚ ድርጅት፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር፡፡ (2004 ዓ.ም)፡፡ አማርኛ የተማረው መፅሀፍ 10ኛ ክፍል፡፡ የአል-ጉራር
አታሚና አሳታሚ ድርጅት፡፡

59
¯KU እg~:: (1995):: «
uG<K}— s”s ¾Te}T]Á Sd]Á ´Óσ H>Ń ¨<eØ ¾¡H>KA‹
›Å[Í˃“ }Ÿ<[ƒ ¾T>g< ò„‹ ›ÖnkU::» ŸØpUƒ 25-29/1995 ¯.U. K›T`— እ”Å
G<K}— s”s ƒUI`ƒ ¾}²ÒÌ ¾7—“ ¾8— ¡õKA‹ S`H ƒUI`„‹” KThhM K}²Ò˨<
›¨<Å Ø“ƒ ¾k[u (ŸY/ƒ/´/Ø/U/›=”c+ƒ¿ƒ)' ›Ç=e ›uv:: (ÁMታ}S)

እያሱ መሰለ (2003)፡፡ “በ(1999) ዓ.ም. በተሻሻሉት የ9ኛ እና የ10ኛ ክፍል መማሪያ መፃህፍት
የስነ ትምህርታዊ ሰዋስውይዘት አመራረጥ፣ አቀራረብና አደረጃጀት ግምገማ፡፡” አዲስ
አበባ ዩኒቨርስቲ ድህረ ምረቃ ትምህርት ቤት ለአማርኛ ኤም.ኤ.ዲግሪ
ከፊል ማሟያነት የቀረበ (ያልታተመ)፡፡
የመምህራን ትምህርት ኮሌጅ ማሰልጠኛ ሞጁል፡፡ (2008)፡፡ የትምህርት ምዘና ግምገማ
በመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣አማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ፣
ባህር ዳር፡፡

ያለው እንዳወቀ፡፡ (2009)፡፡የምርምር መሰረታዊ መርሆች እና አተገባበር፡፡ ሦስተኛ


እትም፣ንግድማተሚያ ድርጅት፣አዲስ አበባ

Batstone, R. (1994) Grammar. Oxford: Oxford University Press.


Bachman,L.F.(1990).Fundamental Considerations in Language Testing. Oxford University Press.
Bilabo, P.P, Lucido, P.I, Iringan, T.C,Javier, R.B,(2008). Curriculum development. Quezon
City, Qc;Lorimar publishing, Inc. Retieued From http://www.linkedin. Com/puse/7-
Criteria-selection-Subject-matter-content-dr-mary-aluior.
Breen, M & Candlin, C. (1987) "Which materials? A consumers'
Brown, H. Douglas. (2004). Language assessment principles and classroom practices/ H.
Douglas Brown. P. com. Includes bibliogt 4:1 phical references and index.
Carl wenning. (2009). Elemets of Syllabus. Lllinois State Univerasity
Celce-Murcia, M. (1991). Towards more Context and Discourse in Grammar Instruction. Los
Angeles፡ University of California.
Cunnings worth, A (1984). Evaluating and selecting EFL Teaching Materials. London
Heinemann Education books.
Cunnings worth, A (1985). Evaluating and selecting EFL Teaching materials and Oxford
university press.
Cunningsworth, A. (1995) Choosing Your Course Book. Oxford. Oxford: Heineman

60
Dubbin, F and E, olishtain (1986). Course design: Developing programs and materials for
language learning. Cambridge cug. Features of good syllabus (2008) ድረገፅ
Encyclopedia of education. Retrieved (2008) from answers. Com.websit:

http://www.answers. Com/topic text book.

Ells worth,et.al.(1994).The History of the text book in Education. Brian lamb.


Grant, N. (1987). Making The most of your Text book. Langman. London.
Graves, K. (1996). Teachers as course developers. Cambridge: cup.
Graves (2001).Teachers as course developers. Cambridge: cup.
Green Land. (1980). Measurment & Evaluation In Teaching 4th ed. New York,Mac,Mac.Millan
Publishing

Hamadouche, M.(2010). eloping the writing skill through increasing learners awarness of

the writing process the case of second year students. university of Constantine
Dissertation submitted in partial filfillment for the Requirement Master of Arts
Degree in Language Sciences
Harmer, J. (1991). The Practice of English Language Teaching (2rd Ed). London: Longman.
Hughes, A. (1989). Testing for Language Teachers. Cambridge university Press.
Hutchinson, T and Torres, E. (1994). The textbook as agent of change. Hongkong: longman
group LTD.
Kifle Adera. (2009). A short cut to curriculum designing, planning, development and
implementation. Addis Ababa, Artistic printing Enterprise.
MC Donough, Jo and Christopher show. (1991). Materials and methods in Elt. Oxford: Black
Well
Meriwether, N. W. (1997). Strategies For Writing Successful essays, Newyork: NTC Publishing

Muijs,D. (2004).Doing Quantitative Research in Education.London: sage Pulications.

Muhmmed, K & etal. (2013). Educational research. Pakistan. Retrived From: http://www. interes
journals. Org/full/ articls/aligning-objectives-content-learning-experiences- and
evaluation-in-teaching-learning- of-english-atprin..
Nunan, D. (1988 ). The learner centered curriculum. Cambridge cup.
Nunan, D. (1988). Syllabus Design. Oxford, oxford university press.

61
Prabhu, N.S. (1987). Second Language Pedagogy. Hong Kong: Oxford University Process.

Raimes.A. (1983). Techniques in Teaching Writing. Hong Kong; Oxforduniversity.

Richard. J.C.(1990).The language teaching matrix. Cambridge university press.


Richards, J. C. (2001). Curriculum Development in language Teaching. Singapore. Cambridge
University.
Sheldon, leslie E. (ed.) (1987). Textbooks and materials: problems in evaluation and
Development. ELT Documents: 126. London; modern English publications.
Shelden, L. E. (1988). Evaluating ELT Text books and materials. ELT journal
Thakur amkrishana- (2013). Of English language Teaching syllabi and its implication. The
criterion an international journal in English. R .N college Halipur December 2013. Vol. 4.
Under Wood, M (1989). Teaching Listening. London Longman; UK group Ltd.

Ur. P. (1991). A course in Language Teaching practice and theory. Cambridge: university
press.
Ur. P. (1996). A course in language Teaching practice and theory. Cambridge university
press.
Widdowson, H. G. (1990). Aspects of language Teaching. Oup.
Wilkins, D. A. (1976). Notional syllabus. Oxford: oxford university press.
White Ronald V. (1991). The ELT curriculum Design innovation and management.
Cambridge: Basil Blackoville Ltd.
White, R (1993) The ELT curriculum Design innovation and management. Cambridge: Basil
Blackoville Ltd.www. Creating a sysllabus/teaching at university of Nebraska. Lin coin.
Yalden, J. (1987). Principles of caurse Design for Language Teaching.Cambridge;
Cambridge university press.
Yalden, J. (1987). The communicative syllabus; Evolution design and implementation. Prentice
Hall.

62
63
አባሪዎች
አባሪ አንድ፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የአንብቦ መረዳት ይዘቶች
በመርሃ ትምህርትቱ የይዘቶች የሚገኙበት ምዕራፍ በመማሪያ መፅሃፉ የይዘቶች የሚገኙበት
ተ.ቁ ምዕራፍ
ንዑሳን የአንብቦ መረዳት ይዘቶች

ምዕራፍ 1

ምዕራፍ 1
ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ
ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ
ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ
ድምር

ድምር
10

10
2

4
5

7
8

9
1 የምንባቡን ሃሳብ መገመት √ √ √ √ √ √ √ √ √ √ 10 √ √ √ √ √ √ √ √ √ √ 10
2 የቀደመ እውቀትን ማነሳሳት √ √ √ √ √ 5 √ √ √ √ √ 5
4 አከራካሪ ሃሳቦችን ማዳበር √ √ √ 3 √ √ √ 3
5 ዋና ዋና ሃሳቦችን መለየት √ √ √ √ √ √ √ 7 √ √ √ √ √ √ √ 7
6 ዝርዝር ሃሳቦችን መለየት √ √ √ √ √ √ √ √ √ √ 10 √ √ √ √ √ √ √ √ 8
7 የግል አስተያየትን ከእውነታ መለየት √ √ √ 3 √ √ √ 3
8 የአገላለጾችን መልእክት መረዳት √ √ √ √ 4 √ √ √ √ 4
9 የፅሁፍን ጭብጥ መረዳት √ √ √ √ √ √ 6 √ √ √ √ √ 5
10 የፅሁፉን አላማ መረዳት √ √ √ 3 √ √ √ 3
11 የቃላትንናሓረጋትን አውዳዊ ፍች መረዳት √ √ √ √ √ √ √ √ 8 √ √ √ √ √ √ √ √ 8
ድምር 59 56

64
አባሪ ሁለት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የመፃፍ ይዘቶች
በመርሃ ትምህርትቱ የይዘቶች የሚገኙበት በመማሪያ መፅሃፉ የይዘቶች የሚገኙበት
ምዕራፍ ምዕራፍ
ተ. ንዑሳን የመፃፍ ይዘቶች

ምዕራፍ 1

ምዕራፍ 1

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ
ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ
ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ድምር

ድምር
10

10
2

4
5

7
8

2
3
4
5
6
7
8
9
1 እውነታን ከየግል አስተያየትን መለየት √ √ √ 3 √ √ √ 3
2 አማርኛ ከሌላ ቋንቋ የተዋሳወቸውን ቃላት መለየት √ √ √ 3 √ √ √ 3
3 ከተለያዩ የመረጃ ምንጮች ማሳተዋሻ መያዝ √ √ √ √ 4 √ √ √ √ 4
4 አሳጥሮ መፃፍ √ √ √ √ 4 √ √ √ √ 4
5 የአንቀፅ ክፍሎች √ √ √ √ 4 √ √ √ √ 4
6 ቃለ ጉባኤ መያዝ √ √ 2 √ √
7 በፈሊጣዊ ቃላት ዓረፍተ ነገር መመስረት √ √ √ √ √ 5 √ √ √ √ √ 5
8 አመዛዛኝ ድርሰት መፃፍ √ √ 2 √ √ 2
9 አያያዥ ቃላት በመጠቀም አንቀፅ መገንባት √ √ √ √ 4 √ √ √ √ 4
10 የንግድ ስራ ደብዳቤ መፃፍ √ √ 2 √ √ 2
11 ስዕላዊ ድርሰት መፃፍ √ √ 2 √ √
12 የቅስቀሳ ንግግር መፃፍ √ √ 2 √ √ 2
ድምር 37 35

65
አባሪ ሦስት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የማዳመጥ ይዘቶች
በመርሃ ትምህርትቱ የይዘቶች የሚገኙበት በመማሪያ መፅሃፉ የይዘቶች
ምዕራፍ የሚገኙበት ምዕራፍ
ተ.ቁ
ንዑሳን የማዳመጥ ይዘቶች

ምዕራፍ 1

ምዕራፍ 1
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ድምር

ድምር
10

10
2
3
4

2
3
4
5
6
7
8
9
1 ስለገለፃው ያለውን ሃሳብ መተንበይ √ √ √ 3 √ √ √ 3
2 አመላከች ነገሮችን መገንዘብ √ √ √ 3 √ √ √ 3
3 የሚቀርቡ እሰተያየቶችን መገንዘብና ማስታዎስ √ √ 2 √ √ √ 3
4 አማራጭ ሃሳቦችን መረዳት እና ማስታዎስ √ √ √ √
5 የግል አስተያየቶችን መረዳት እና ማስታዎስ √ √ 2 √ √ 2
6 ለጥያቄ የተሰጠን ማብራሪያ መረዳትእና ማስታዎስ √ √ √ √
7 በውይይት የዳበሩ ሃሳቦችን መረዳት እና ማስተዎስ √ √ √ √ 4 √ √ √ 3
8 ሌሎችን ለማሳመን የቀረበን ሃሳብ መረዳትና ማስተዎስ √ √ √ 3 √ √ √ 3
9 የቀረበን ሃሳብ መገንዘብና ማስታዎስ √ √ √ 3 √ √ √ 3
10 ዋና ዋና ሃሳቦችን የመለየና ማስታዎስ √ √ √ 3 √ √ 2
ድምር 25 24

66
አባሪ አራት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የመናገር ይዘቶች
በመርሃ ትምህርትቱ ይዘቶች የሚገኙበት በመማሪያ መፅሃፉ የይዘቶች የሚገኙበት
ተ.ቁ ምዕራፍ ምዕራፍ
ንዑሳን የመናገር ይዘቶች

ምዕራፍ 1

ምዕራፍ 1
ምዕራፍ
ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ
ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ድምር

ድምር
10

10
2

8
9

2
3
4
5
6
7
8
9
1 አሳማኝ ሃሳብ ማቅረብ √ √ √ 3 √ √ √ 3
2 ለቀረበ ሃሳብ አስተያየት መስጠት √ √ 2 √ √ 2
3 የሌላኛውን ተናጋሪ ሃሳብ ማስታዎስ √ √ √ 3 √ √ √ 3
4 አከራካሪ ሃሳቦች ማቅረብ √ √ 2 √ √ 2
5 ሃሳብን መተንተን √ √ √ 3 √ √ √ 3
6 ሃሳብን ለሌሎች የማጋራት √ √ √ √
7 መረጃ መስጠት √ √ 2 √ √ 2
8 መላምት መስጠት √ √ 2 √ √ 2
9 ሀሳቡን በሌላ መንገድ መግለፅ √ √ √ 3 √ √ √ 3
10 ፍሬ ሃሳብ ማቅረብ √ √ 2 √ √ 2
11 ለነገሮች ያለንን አተያይ መግለፅ √ √ 2 √ √ 2
ድምር 25 25

67
አባሪ አምስት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የሰዋስው ይዘቶች
በመርሃ ትምህርትቱ ይዘቶች የሚገኙበት ምዕራፍ በመማሪያ መፅሃፉ ይዘቶች የሚገኙበት ምዕራፍ
ተ.ቁ
ንዑሳን የስዋሰው ይዘቶች

ምዕራፍ 1

ምዕራፍ 1
ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ድምር

ድምር
10

10
2

8
9

7
8
9
1 ነፃና ጥገኛ ምዕላዶች √ √ √ √ 4 √ √ √ 3

2 የሓረግ አይነቶችን √ √ √ 3 √ √ √ 3

3 ሓረግ መመስረት √ √ 2 √ √ 2

4 የአያያዥ ሓረጋትና ቃላትን √ √ √ 3 √ √ √ 2

5 ተራና ውስብስብ ዓረፍተ ነገር √ √ √ 3 √ √ √

6 የቃላት እማሪያዊና ፍካሪያዊ ፍች √ √ 2 √ √ 2

7 ቃል መመስረት √ √ √ 3 √ √ √ 3

8 የአረፍተ ነገር ስልቶች √ √ 2 √ √ 2

9 የስርዓተነ ጥባችን አገልግሎት መገንዘብ √ √ 2 √ √ 2

10 የሚጠብቁና የሚላሉ ድምፆች √ √ √ √ 4 √ √ √ 3

ድምር 28 23

68
አባሪ ስድስት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የስነፅሁፍ ይዘቶች
በመርሃ ትምህርትቱ ይዘቶች የሚገኙበት ምዕራፍ በመማሪያ መፅሃፉ ይዘቶች የሚገኙበት ምዕራፍ
ተ.ቁ
ንዑሳን የስነፅሁፍ ይዘቶች

ምዕራፍ 1

ምዕራፍ 1
ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ
ድምር

ድምር
10

10
2

9
1 የምሳሌያዊ ንግግሮች ፍች √ √ √ √ 4 √ √ √ √ 4
2 መጥበቅ እና መላላት √ √ 2 √ √ 2
3 የልቦለድ አላባዊያን √ √ √ 3 √ √ √ 3
4 የፈሊጣዊ ንግግሮች ፍች √ √ √ 3 √ √ √ 3
5 ዘይቤ √ √ √ √ 4 √ √ √ 3
6 የግጥም አይነቶች √ √ √ 3 √ √ √ 3
7 ቃላዊ ግጥሞች √ √ √ √ 4 √ √ √ √ 4
8 ቅኔ √ √ √ 3 √ √ √ 3
ድምር 26 25

69
አባሪ ሰባት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የምንባብ ይዘቶ የቀረቡበት
ዘዴ
በመርሃ ትምህርትቱ ይዘቶች የቀረቡበት ዘዴ በመማሪያ መፅሃፉ ይዘቶች የቀረቡበት ዘዴ
ተ.

ምዕራፎች

ምዕራፎች
ንዑሳን የምንባብ ይዘቶች

ውጤት

ውጤት
ውህድ

ውህድ
ድምር

ድምር
ሂደት

ሂደት
ተኮር

ተኮር

ተኮር

ተኮር
1 የምንባቡን ሃሳብ መገመት √ 1 √ 1

2 የቀደመ እውቀትን ማነሳሳት √ √ 2 √ 1

4 አከራካሪ ሃሳቦችን ማዳበር √ √ 2 √ √ 2

5 ዋና ዋና ሃሳቦችን መለየት √ √ 2 √ √ 2
6 ዝርዝር ሃሳቦችን መለየት √ √ 2 √ √ 2

7 የግል አስተያየትን ከእውነታ መለየት √ √ 2 √ √ 2

8 የአገላለጾችን መልእክት መረዳት √ √ 2 √ √ 2


9 የፅሁፍን ጭብጥ መረዳት √ √ 2 √ √ 2

10 የፅሁፉን አላማ መረዳት √ √ √ 3 √ √ √ 3


11 የቃላትንና ሓረጋትን አውዳዊ ፍች መረዳት √ √ √ 3 √ √ 2

ድምር 21 19

70
አባሪ ስምንት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የመፃፍ ይዘቶች
የቀረቡበት ዘዴ
በመርሃ ትምህርትቱ ይዘቶች በመማሪያ መፅሃፉ ይዘቶች የቀረቡበት
ተ. የቀረቡበት ዘዴ ዘዴ
ቁ ንዑሳን የመፃፍ ይዘቶች

ምዕራፎች

ምዕራፎች

ውጤታዊ
ውጤታዊ

ሂደታዊ

ሂደታዊ
ድምር

ድምር
ዘውግ

ዘውግ
ተኮር

ተኮር
1 ከፅሑፍ ውስጥ እውነታን ከየግል አስተያየትን መለየት √ √ √ 3 √ √ √ 3
2 አማርኛ ከሌላ ቋንቋ የተዋሳወቸውን ቃላት መለየት √ √ 2 √ √ √ 3

3 ከተለያዩ የመረጃ ምንጮች ማሳተዋሻ መያዝ √ √ √ 3 √ √ 2

4 አሳጥሮ መፃፍ √ √ 2 √ √ 2
5 የአንቀፅ ክፍሎች √ √ √ 3 √ √ √ 3
6 ቃለ ጉባኤ መያዝ √ √ 2 √ √ 2

7 በፈሊጣዊ ቃላት ዓረፍተ ነገር መመስረት √ √ 2 √ √ 2


8 አመዛዛኝ ድርሰት መፃፍ √ √ 2 √ √ 2

9 አያያዥ ቃላት በመጠቀም አንቀፅ መገንባት √ √ √ 3 √ √ √ 3


10 የንግድ ስራ ደብዳቤ መፃፍ √ √ √ 3 √ √ 2
11 ስዕላዊ ድርሰት መፃፍ √ √ 2 √ √ √ 3
12 የቅስቀሳ ንግግር መፃፍ √ √ √ 3 √ √ 2

ድምር 30 29

71
አባሪ ዘጠኝ፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የመናገር ይዘቶች
የቀረቡበት ዘዴ
በመርሃ ትምህርትቱ ይዘቶች የቀረቡበት ዘዴ በመማሪያ መፅሃፉ ይዘቶች የቀረቡበት ዘዴ
ተ.
ቁ ንዑሳን የመናገርይዘቶች

ጭውውት

ጭውውት
ምዕራፎች

ምዕራፎች
ውይይት

ውይይት

ጭዋታ
ጭዋታ

ንግግር

ንግግር
ክርክር

ክርክር
ድምር

ድምር
የሚና

የሚና
ቃላዊ

ቃላዊ
1 አሳማኝ ሃሳብ ማቅረብ √ √ √ √ √ 5 √ √ √ √ √ 5
2 ለቀረበ ሃሳብ አስተያየት መስጠት √ √ √ 3 √ √ √ 3

3 የሌላኛውን ተናጋሪ ሃሳብ ማስታዎስ √ √ √ 3 √ √ √ 3

4 አከራካሪ ሃሳቦች ማቅረብ √ √ √ 3 √ √ √ 3


5 ሃሳብን መተንተን √ √ √ 3 √ √ √ 3

6 ሃሳብን ለሌሎች የማጋራት √ √ √ 3 √ √ √ 3

7 መረጃ መስጠት √ √ √ 3 √ √ √ 3
8 መላምት መስጠት √ √ √ 3 √ √ √ 3

9 ሀሳቡን በሌላ መንገድ መግለፅ √ √ √ √ √ 5 √ √ √ √ √ 5


10 ፍሬ ሃሳብ ማቅረብ √ √ √ 3 √ √ √ 3
11 ለነገሮች ያለንን አተያይ መግለፅ √ √ √ 3 √ √ √ 3

ድምር 37 37

72
አባሪ አስር፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የማዳመጥ ይዘቶችን
የቀረቡበት ዘዴ
በመርሃ ትምህርትቱ ይዘቶች የቀረቡበት በመማሪያ መፅሃፉ ይዘቶች የቀረቡበት
ተ. ዘዴ ዘዴ
ቁ ንዑሳን የማዳመጥ ይዘቶች

አውደክልዔ

አውደክልዔ
ምዕራፎች

ምዕራፎች
ማዳመጥ

ማዳመጥ
አሃዳዊ

አሃዳዊ
ድምር

ድምር
ዐውድ

ዐውድ
ራስን

ራስን
1 ስለገለፃው ያለውን ሃሳብ መተንበይ √ √ √ 3 √ √ √ 3
2 አመላከች ነገሮችን መገንዘብ √ √ 2 √ 1

3 የሚቀርቡ እሰተያየቶችን መገንዘብና ማስታዎስ √ √ 3 √ 1

4 አማራጭ ሃሳቦችን መረዳት እና ማስታዎስ √ √ 2 √ √ 2


5 የግል አስተያየቶችን መረዳት እና ማስታዎስ √ 1 √ 1

6 ለጥያቄ የተሰጠን ማብራሪያ መረዳትእና ማስታዎስ √ 1 √ 1

7 በውይይት የዳበሩ ሃሳቦችን መረዳት እና ማስተዎስ √ √ 2 √ √ 2


8 ሌሎችን ለማሳመን የቀረበን ሃሳብ መረዳትና ማስተዎስ √ √ 2 √ 1

9 የቀረበን ሃሳብ መገንዘብና ማስታዎስ √ √ √ 3 √ √ √ 3


10 ዋና ዋና ሃሳቦችን የመለየና ማስታዎስ √ 1 √ 1

ድምር 20 16

73
አባሪ አስራ አንድ፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የሰወሰው
አውቀት ይዘቶች የቀረቡበት ዘዴ
በመርሃ ትምህርትቱ ይዘቶች የቀረቡበት ዘዴ በመማሪያ መፅሃፉ ይዘቶች የቀረቡበት ዘዴ
ተ.ቁ

ምዕራፎች

ምዕራፎች
አጠቃላይ

አጠቃላይ
ከአጠቃላ

ከዝርዝር

ከአጠቃላ

ከዝርዝር
ንዑሳን የስዋሰው ይዘቶች

ውህዳዊ

ውህዳዊ
ውጤት

ውጤት
ዝርዝር

ዝርዝር
ይ ወደ

ይ ወደ
ድምር

ድምር
ሂደት

ሂደት
ተኮር

ተኮር

ተኮር

ተኮር
ወደ

ወደ
1 ነፃና ጥገኛ ምዕላዶች √ √ √ 3 √ √ √ 3

2 የሓረግ አይነቶችን √ √ √ √ 4 √ √ √ 3

3 ሓረግ መመስረት √ √ 2 √ √ 2

4 የአያያዥና መሸጋገሪያ ሓረጋትና ቃላትን √ √ √ 3 √ √ √ 3

5 ተራና ውስብስብ ዓረፍተ ነገር √ √ √ 3 √ √ √ 3

6 የቃላት እማሪያዊና ፍካሪያዊ ፍች √ √ 2 √ √ 2

7 ቃል መመስረት √ √ √ 3 √ √ √ 3

8 የአረፍተ ነገር ስልቶች √ √ 2 √ √ 2

9 የስርዓተነ ጥባችን አገልግሎት መገንዘብ √ √ √ √ 4 √ √ √ √ 4

10 የሚጠብቁና የሚላሉ ድምፆች √ √ √ 3 √ √ 2

ድምር 29 27

74
አባሪ አስራ ሁለት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የስነፅሑፍ
እውቀት ይዘቶች የቀረቡበት ዘዴ
በመርሃ ትምህርትቱ ይዘቶች የቀረቡበት ዘዴ በመማሪያ መፅሃፉ ይዘቶች የቀረቡበት ዘዴ
ተ.
ቁ ንዑሳን የስነፅሁፍ ይዘቶች

ምዕራፎች

ምዕራፎች
ግለሰባዊ

ግለሰባዊ
ስልታዊ

ስልታዊ
ተሳትፎ

ተሳትፎ
የሚጨ

የሚጨ
ድምር

ድምር
ይዘት

ይዘት
ተኮር

ተኮር

ተኮር

ተኮር
ቋንቋ

ቋንቋ
ምር

ምር
1 ምሳሌያዊ ንግግሮች √ √ √ √ 4 √ √ √ √ 4
2 መጥበቅ እና መላላት √ √ √ 3 √ √ √ 3

3 የልቦለድ አላባዊያን √ √ √ 3 √ √ √ 3

4 የፈሊጣዊ ንግግሮች √ √ √ 3 √ √ √ 3
5 ዘይቤ √ √ √ 3 √ √ 2

6 የግጥም አይነቶች √ √ √ 3 √ √ √ 3

7 ቃላዊ ግጥሞች √ √ √ 3 √ √ √ 3
8 ቅኔ √ √ √ 3 √ √ √ 3

ድምር 25 24

75
አባሪ አስራ ሦስት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የአንብቦ
መረዳት ይዘቶች
በ10ኛ ክፍል አማርኛ መማሪያ መፅሃፍ የተካተቱ በ10ኛ ክፍል እንግሊዘኛ መማሪያ መፅሃፍ
፡. ይዘቶች የሚገኙበት ምዕራፍ የተካተቱ ይዘቶች የሚገኙበት ምዕራፍ

ንዑሳን የአንብቦ መረዳት ይዘቶች

ምዕራፍ 1

ምዕራፍ 1
ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ድምር

ድምር
10

10
2

5
6
7
8
9
1 የምንባቡን ሃሳብ መገመት √ √ √ √ √ √ √ √ √ √ 10 √ √ √ √ √ √ √ √ √ √ 10
(Prognosis introspection of reading)
2 የቀደመ እውቀትን ማነሳሳት √ √ √ √ √ 5
(motivation background knowledge)
4 አከራካሪ ሃሳቦችን ማዳበር √ √ √ 3
(outline the development an argument)
5 ዋና ዋና ሃሳቦችን መለየት √ √ √ √ √ √ √ 7
(Identifying the main point )
6 ዝርዝር ሃሳቦችን መለየት √ √ √ √ √ √ √ √ √ √ 10 √ √ √ √ √ √ √ √ √ √ 10
(Reading for specific information)
7 የግል አስተያየትን ከእውነታ መለየት √ √ √ 3
(Distingush opinion from fact)
8 የአገላለጾችን መልእክት መረዳት √ √ √ √ 4 √ √ √ 3
(Understanding expressions in text)
9 የፅሁፍን ጭብጥ መረዳት √ √ √ √ √ √ 6 √ √ 2
(Understanding theme in text)
10 የፅሁፉን አላማ መረዳት √ √ √ 3
(Recognising a writer purpose,attitude,tone and
mood)
11 የቃላትንና ሓረጋትን አውዳዊ ፍች መረዳት √ √ √ √ √ √ √ √ 8 √ √ √ √ √ √ 6
(Drawing inferences about the meaning of a word
in context)
ድምር 59 31

76
አባሪ አስራ አራት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የመፃፍ ይዘቶች
በ10ኛ ክፍል አማርኛ መማሪያ መፅሃፍ በ10ኛ ክፍል እንግሊዘኛ መማሪያ መፅሃፍ
፡. የተካተቱ ይዘቶች የሚገኙበት ምዕራፍ የተካተቱ ይዘቶች የሚገኙበት ምዕራፍ

ንዑሳን የመፃፍ ይዘቶች

ምዕራፍ 1

ምዕራፍ 1
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ
ምዕራፍ

ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ድምር

ድምር
10

10
2
3
4

2
3
4
5
6
7
8
9
1 ከፅሑፍ ውስጥ እውነታን ከየግል አስተያየትን መለየት √ √ √ 3
(Distingush opinion from fact)
2 አማርኛ ከሌላ ቋንቋ የተዋሳወቸውን ቃላት መለየት √ √ √ 3
(The characteristic of language)
3 ከተለያዩ የመረጃ ምንጮች ማሳተዋሻ መያዝ √ √ √ √ 4
4 አሳጥሮ መፃፍ(Summarising a new report) √ √ √ √ 4 √ 1
5 የአንቀፅ ክፍሎች(Parts of a paragraph) √ √ √ √ 4
6 ቃለ ጉባኤ መያዝ(Minutes) √ √ 2
7 በፈሊጣዊ ቃላት ዓረፍተ ነገር መመስረት √ √ √ √ √ 5 √ √ 2
(building correct and appropriate sentences)
8 አመዛዛኝ ድርሰት መፃፍ √ √ 2 √ √ 2
(Argumentative or persuasive paragraphs)
9 አያያዥ ቃላት በመጠቀም አንቀፅ መገንባት √ √ √ √ 4
(The conjunction)
10 የንግድ ስራ ደብዳቤ መፃፍ(Letters of application) √ √ 2 √ √ √ 3
11 ስዕላዊ ድርሰት መፃፍ(Descriptive paragraphs) √ √ 2 √ √ 2
12 የቅስቀሳ ንግግር መፃፍ(Write stimulating speech) √ √ 2
ድምር 37 10

77
አባሪ አስራ አምስት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ እና በእንግዝኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የማዳመጥ
ይዘቶች
በ10ኛ ክፍል አማርኛ መማሪያ መፅሃፍ በ10ኛ ክፍል እንግሊዘኛ መማሪያ መፅሃፍ
፡. የተካተቱ ይዘቶች የሚገኙበት ምዕራፍ የተካተቱ ይዘቶች የሚገኙበት ምዕራፍ

ንዑሳን የማዳመጥ ይዘቶች

ምዕራፍ 1

ምዕራፍ 1
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ
ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ድምር

ድምር
10

10
2
3
4

3
4
5
6
7
8
9
1 ስለገለፃው ያለውን ሃሳብ መተንበይ √ √ √ 3 √ √ √ 3
(understand speculation of explanation)
2 አመላከች ነገሮችን መገንዘብ √ √ √ 3
(Recognise indications of understand)
3 የሚቀርቡ እሰተያየቶችን መገንዘብና ማስታዎስ √ √ 2 √ √ √ 3
(Recognise and understand comments)
4 አማራጭ ሃሳቦችን መረዳት እና ማስታዎስ √ √
(Recognise and understand expressions of preferences)
5 የግል አስተያየቶችን መረዳት እና ማስታዎስ √ √ 2 √ √ √ 3
(Recognise and understand opinions)
6 ለጥያቄ የተሰጠን ማብራሪያ መረዳትእና ማስታዎስ √ √
(recognizes when speaker questions assertions made by other
speakers)
7 በውይይት የዳበሩ ሃሳቦችን መረዳት እና ማስተዎስ √ √ √ √ 4
(Recognise and understand modifications of statements and
comments)
8 ሌሎችን ለማሳመን የቀረበን ሃሳብ መረዳትና ማስተዎስ √ √ √ 3
(Recognise attempts to persuade others)
9 የቀረበን ሃሳብ መገንዘብና ማስታዎስ √ √ √ 3 √ √ √ 3
(Recognise and understand suggestion)
10 ዋና ዋና ሃሳቦችን የመለየና ማስታዎስ √ √ √ 3 √ √ 2
(Recognise and identifing main point)
ድምር 25 14

78
አስራ ስድስት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የመናገር ይዘቶች
በ10ኛ ክፍል አማርኛ መማሪያ መፅሃፍ የተካተቱ ይዘቶች በ10ኛ ክፍል እንግሊዘኛ መማሪያ መፅሃፍ የተካተቱ
፡. የሚገኙበት ምዕራፍ ይዘቶች የሚገኙበት ምዕራፍ
፡ ንዑሳን የመናገር ይዘቶች

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ
ምዕራፍ

ምዕራፍ
ምዕራፍ
ድምር

ድምር
10

10
1
2

1
2

7
8

9
1 አሳማኝ ሃሳብ ማቅረብ √ √ √ 3
(attempt to persuade others)
2 ለቀረበ ሃሳብ አስተያየት መስጠት √ √ 2
(make comments)
3 የሌላኛውን ተናጋሪ ሃሳብ ማስታዎስ √ √ √ 3
(Recognise other speakers purpose )
4 አከራካሪ ሃሳቦች ማቅረብ √ √ 2
(present an argument)
5 ሃሳብን መተንተን (thought analyse) √ √ √ 3
6 ሃሳብን ለሌሎች ማጋራት √ √ √ 1
(respond to requests for clarification)
7 መረጃ መስጠት √ √ 2 √ √ 2
(provision required information)
8 መላምት መስጠት √ √ 2
(provision required hypothesis)
9 ሀሳቡን በሌላ መንገድ መግለፅ √ √ √ 3 √ √ √ 3
(paraphrase)
10 ፍሬ ሃሳብ ማቅረብ(present an main √ √ 2 √ √ 2
point )
11 ለነገሮች ያለንን አተያይ መግለፅ √ √ 2
(express opinions)
ድምር 25 8

79
አባሪ አስራ ሰባት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የሰዋስው ይዘቶች
በ10ኛ ክፍል አማርኛ መማሪያ መፅሃፍ የተካተቱ በ10ኛ ክፍል እንግሊዘኛ መማሪያ መፅሃፍ
፡. ይዘቶች የሚገኙበት ምዕራፍ የተካተቱ ይዘቶች የሚገኙበት ምዕራፍ

ንዑሳን የስዋሰው ይዘቶች

ምዕራፍ 1

ምዕራፍ 1
ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ
ድምር

ድምር
10

10
2

2
3
4
5
6
7
8
9
1 ነፃና ጥገኛ ምዕላዶች(Prefixes and affixes) √ √ √ √ 4 √ 1

2 የሓረግ አይነቶችን(Kinds of phrases) √ √ √ 3

3 ሓረግ መመስረት(phrases building) √ √ 2

4 የአያያዥና መሸጋገሪያ ሓረጋትና ቃላት √ √ √ 3


(The conjunction)
5 ተራና ውስብስብ ዓረፍተ ነገር √ √ √ 3
(Simple, compouned and complex sentences)
6 የቃላት እማሪያዊና ፍካሪያዊ ፍች √ √ 2
(denotative and connotative meaning)
7 ቃል መመስረት(word building) √ √ √ 3 √ √ 2

8 የአረፍተ ነገር ስልቶች(Kinds of sentences) √ √ 2

9 የስርዓተነ ጥባችን አገልግሎት መገንዘብ √ √ 2 √ 1


(Punctuation)
10 የሚጠብቁና የሚላሉ ድምፆች √ √ √ √ 4

ድምር 28 4

80
አባሪ አስራ ስምንት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ እና በእንግሊዝ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የስነፅሁፍ
ይዘቶች
፡. በ10ኛ ክፍል አማርኛ መማሪያ መፅሃፍ የተካተቱ በ10ኛ ክፍል እንግሊዘኛ መማሪያ መፅሃፍ የተካተቱ
፡ ይዘቶች የሚገኙበት ምዕራፍ ይዘቶች የሚገኙበት ምዕራፍ
ንዑሳን የስነፅሁፍ ይዘቶች

ምዕራፍ 1

ምዕራፍ 1

ምዕራፍ
ምዕራፍ
ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ

ምዕራፍ
ድምር

ድምር
10

10
2
3

9
1 ምሳሌያዊ ንግግሮች (proverbs) √ √ √ √ 4
2 መጥበቅ እና መላላት √ √ 2
3 የልቦለድ አላባዊያን √ √ √ 3
(elements of fiction)
4 የፈሊጣዊ ንግግሮች √ √ √ 3 √ √ √ √ √ √ √ √ √ √ 10
(Vocabulary)
5 ዘይቤ √ √ √ √ 4 √ 1
(Figures of speech)
6 የግጥም አይነቶች √ √ √ 3 √ √ 2
(Tayps of Poem)
7 ቃላዊ ግጥሞች (Oral Poem) √ √ √ √ 4
8 ቅኔ(English puns) √ √ √ 3
ድምር 26 13

81
አባሪ አስራ ዘጠኝ ፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃ ትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የምንባብ
ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች
በመርሃ ትምህርቱ ለምዘና ተግባር የዋሉ በመማሪያ መፅሃፉ ለምዘና ተግባር
ተ. ስራዎች የዋሉ ስራዎች
ቁ ንዑሳን የምንባብ ይዘቶች

የቤት ስራ

ድምር ስራ
ምዕራፎች

ምዕራፎች
የክፍልና

የክፍልና
ምልከታ
ምልከታ

የቡድን

የቡድን
ድምር
የቢጤ

የቢጤ
ጥያቄ

ጥያቄ
የቃል

የቃል
ምዘና

ምዘና

የቤት
ስራ

ስራ
1 የምንባቡን ሃሳብ መገመት √ 1 √ 1
2 የቀደመ እውቀትን ማነሳሳት √ √ 2 √ √ 2
4 አከራካሪ ሃሳቦችን ማዳበር √ √ √ 3 √ √ √ 3
5 ዋና ዋና ሃሳቦችን መለየት √ √ √ √ √ 5 √ √ √ √ √ 5
6 ዝርዝር ሃሳቦችን መለየት √ √ √ √ 4 √ √ √ √ 4
7 የግል አስተያየትን ከእውነታ መለየት √ √ 2 √ √ √ 3
8 የአገላለጾችን መልእክት መረዳት √ √ √ 3 √ √ √ 3
9 የፅሁፍን ጭብጥ መረዳት √ √ 2 √ √ √ 3
10 የፅሁፉን አላማ መረዳት √ √ 2 √ √ 2
11 የቃላትንና ሓረጋትን አውዳዊ ፍች መረዳት √ √ √ 3 √ √ √ √ 4
ድምር 27 30

84
አባሪ ሃያ ፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃ ትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የመፃፍ
ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች
በመርሃ ትምህርቱ ለምዘና ተግባር በመማሪያ መፅሃፉ ለምዘና
ተ የዋሉ ስራዎች ተግባር የዋሉ ስራዎች
.ቁ ንዑሳን የመፃፍ ይዘቶች

የቤት ስራ

የቤት ስራ
ምዕራፎች

ምዕራፎች
የክፍልና

የክፍልና
ምልከታ

ምልከታ
የቡድን

የቡድን
ድምር

ድምር
የቢጤ

የቢጤ
ጥያቄ

ጥያቄ
የቃል

የቃል
ምዘና

ምዘና
ስራ

ስራ
1 ከፅሑፍ ውስጥ እውነታን ከየግል አስተያየትን መለየት √ √ √ √ 4 √ √ √ √ 4
2 አማርኛ ከሌላ ቋንቋ የተዋሳወቸውን ቃላት መለየት √ √ √ √ 4 √ √ √ √ 4
3 ከተለያዩ የመረጃ ምንጮች ማሳተዋሻ መያዝ √ √ √ 3 √ √ √ 3
4 አሳጥሮ መፃፍ √ √ √ 3 √ √ √ 3
5 የአንቀፅ ክፍሎች √ √ √ √ 4 √ √ √ √ 4
6 ቃለ ጉባኤ መያዝ √ √ √ 3 √ √ √ 3
7 በፈሊጣዊ ቃላት ዓረፍተ ነገር መመስረት √ √ √ 3 √ √ √ √ 4
8 አመዛዛኝ ድርሰት መፃፍ √ √ √ 3 √ √ √ 3
9 አያያዥ ቃላት በመጠቀም አንቀፅ መገንባት √ √ 2 √ √ √ 3
10የንግድ ስራ ደብዳቤ መፃፍ √ √ √ 3 √ √ √ √ 4
11ስዕላዊ ድርሰት መፃፍ √ √ √ 3 √ √ √ 3
12የቅስቀሳ ንግግር መፃፍ √ √ √ √ 4 √ √ √ √ 4
ድምር 39 42

85
አባሪ ሃያ አንድ፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃ ትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የመናገር
ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች
በመርሃ ትምህርቱ ለምዘና ተግባር የዋሉ በመማሪያ መፅሃፉ ለምዘና ተግባር
ተ. ስራዎች የዋሉ ስራዎች
ቁ ንዑሳን የመናገርይዘቶች

የቤት ስራ

የቤት ስራ
ምዕራፎች

ምዕራፎች
የክፍልና

የክፍልና
ምልከታ

ምልከታ
የቡድን

የቡድን
ድምር

ድምር
የቢጤ

የቢጤ
ጥያቄ

ጥያቄ
የቃል

የቃል
ምዘና

ምዘና
ስራ

ስራ
1 አሳማኝ ሃሳብ ማቅረብ √ √ √ 3 √ √ √ 3
2 ለቀረበ ሃሳብ አስተያየት መስጠት √ √ √ 3 √ √ √ √ 4
3 የሌላኛውን ተናጋሪ ሃሳብ ማስታዎስ √ √ √ 3 √ √ √ 3
4 አከራካሪ ሃሳቦች ማቅረብ √ √ 2 √ √ √ 3
5 ሃሳብን መተንተን √ √ √ √ √ 5 √ √ √ √ √ 5
6 ሃሳብን ለሌሎች የማጋራት √ √ √ √ √ 5 √ √ √ √ √ 5
7 መረጃ መስጠት √ √ √ 3 √ √ √ 3
8 መላምት መስጠት √ √ 2 √ √ √ 3
9 ሀሳቡን በሌላ መንገድ መግለፅ √ √ √ √ √ 5 √ √ √ √ √ 5
10 ፍሬ ሃሳብ ማቅረብ √ √ √ √ √ 5 √ √ √ √ √ 5
11 ለነገሮች ያለንን አተያይ መግለፅ √ √ √ √ √ 5 √ √ √ √ √ 5
ድምር 41 44

86
አባሪ ሃያ ሁለት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍ እና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የማዳመጥ
ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች
በመርሃ ትምህርቱ ለምዘና ተግባር የዋሉ በመማሪያ መፅሃፉ ለምዘና ተግባር
ተ. ስራዎች የዋሉ ስራዎች
ቁ ንዑሳን የማዳመጥ ይዘቶች

የቤት ስራ

ድምር ስራ
ምዕራፎች

ምዕራፎች
የክፍልና

የክፍልና
ምልከታ

ምልከታ
የቡድን

የቡድን
ድምር
የቢጤ

የቢጤ
ጥያቄ

ጥያቄ
የቃል

የቃል
ምዘና

ምዘና

የቤት
ስራ

ስራ
1 ስለገለፃው ያለውን ሃሳብ መተንበይ √ √ √ √ √ 5 √ √ √ √ √ 5
2 አመላከች ነገሮችን መገንዘብ √ √ √ √ 4 √ √ √ √ √ 5
3 የሚቀርቡ እሰተያየቶችን መገንዘብና ማስታዎስ √ √ √ 3 √ √ √ 3
4 አማራጭ ሃሳቦችን መረዳት እና ማስታዎስ √ √ 2 √ √ √ 3
5 የግል አስተያየቶችን መረዳት እና ማስታዎስ √ √ √ √ 4 √ √ √ √ 4
6 ለጥያቄ የተሰጠን ማብራሪያ መረዳትእና ማስታዎስ √ √ √ 3 √ √ √ 3
7 በውይይት የዳበሩ ሃሳቦችን መረዳት እና ማስተዎስ √ √ √ 3 √ √ 2
8 ሌሎችን ለማሳመን የቀረበን ሃሳብ መረዳትና ማስተዎስ √ √ √ 3 √ √ √ 3
9 የቀረበውን ሃሳብ መገንዘብና ማስታዎስ √ √ 3 √ √ 2
10 ዋና ዋና ሃሳቦችን የመለየና ማስታዎስ √ √ √ √ 4 √ √ √ √ √ 5
ድምር 34 35

87
አባሪ ሃያ ሦስት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መርሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የሰወሰው
እውቀት ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች
በመርሃ ትምህርቱ ለምዘና ተግባር የዋሉ በመማሪያ መፅሃፉ ለምዘና ተግባር
ተ.ቁ ስራዎች የዋሉ ስራዎች
ንዑሳን የስዋሰው ይዘቶች

የቤት ስራ

ድምር ስራ
ምዕራፎች

ምዕራፎች
የክፍልና

የክፍልና
ምልከታ

ምልከታ
የቡድን

የቡድን
ድምር
የቢጤ

የቢጤ
ጥያቄ

ጥያቄ
የቃል

የቃል
ምዘና

ምዘና

የቤት
ስራ

ስራ
1 ነፃና ጥገኛ ምዕላዶች √ √ √ 3 √ √ √ 3

2 የሓረግ አይነቶችን √ √ 2 √ √ √ 3

3 ሓረግ መመስረት √ √ 2 √ √ 2

4 የአያያዥና መሸጋገሪያ ሓረጋትና ቃላትን አገልግሎት √ √ 2 √ √ 2

5 ተራና ውስብስብ ዓረፍተ ነገር √ √ 2 √ √ 2

6 የቃላት እማሪያዊና ፍካሪያዊ ፍች √ √ 2 √ √ √ 3

7 ቃል መመስረት √ √ 2 √ √ 2

8 የአረፍተ ነገር ስልቶች √ √ 2 √ √ 2

9 የስርዓተነ ጥባችን አገልግሎት መገንዘብ √ √ 2 √ √ 2

10 የሚጠብቁና የሚላሉ ድምፆች √ √ 2 √ √ √ 3

ድምር 21 24

88
አባሪ ሃያ አራት፡-በአስረኛ ክፍል በአማርኛ ቋንቋ መማሪያ መፅሀፍእና መራሃትምህርቱ በየምዕራፉ የቀረቡ ንዑሳን የስነፅሑፍ
እውቀት ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች
በመርሃ ትምህርቱ ለምዘና ተግባር የዋሉ ስራዎች በመማሪያ መፅሃፉ ለምዘና ተግባር የዋሉ
ተ. ስራዎች
ቁ ንዑሳን የስነፅሁፍ ይዘቶች

የቤት ስራ

የቤት ስራ
ምዕራፎች

ምዕራፎች
የክፍልና

የክፍልና
ምልከታ

ምልከታ
የቡድን

የቡድን
ድምር

ድምር
የቢጤ

የቢጤ
ጥያቄ

ጥያቄ
የቃል

የቃል
ምዘና

ምዘና
ስራ

ስራ
1 ምሳሌያዊ ንግግሮች √ √ √ √ 4 √ √ √ √ 4
2 መጥበቅ እና መላላት √ √ 2 √ √ 2

3 የልቦለድ አላባዊያን √ √ 2 √ √ √ 3

4 የፈሊጣዊ ንግግሮች √ √ √ √ 4 √ √ √ √ 4
5 ዘይቤ √ √ √ √ 4 √ √ √ √ 4

6 የግጥም አይነቶች √ √ √ 3 √ √ √ √ 4
7 ቃላዊ ግጥሞች √ √ √ 3 √ √ √ 3
8 ቅኔ √ √ √ 3 √ √ √ √ 4

ድምር 25 28

89

You might also like