Professional Documents
Culture Documents
1
1
ነብዩ (ሰ.ዓ.ወ) ስለ አለፉ ሰዎች ታሪክ ለማስተማር አቡበክርን ፣ ዑመርን እንዲሁም ሌሎችን ሶሃቦች በመሰብሰብ
ድራማ በማሰራት አላስተማሩም፡፡ ይልቁንም ያለምንም ተከሉፍ (ከአቅም በላይ መጨናነቅ) ታሪኩን ግልጽ በሆነ
ቋንቋ በማስተማር ይኸው አለም ከምእራብ እስከ ምስራቅ ሀዲስን በማንበብ ላይ ይገኛል፡፡ በድራማ መልክ
ማስተማር ይበልጥ ጠቃሚና የተፈቀደ ቢሆን ኖሮ ለአለም ብርሀን ይሆኑ ዘንድ የተላኩት ነብይ በሰሩት
ነበር፡፡ሸይኽ ዓብዱሰላም ኢብኑ በርጀስ "አልሁጀጁል ቀዊያህ " በተሰኘው ኪታባቸው ገጽ 40 ላይ እንደጠቀሱት
ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያህ ረሂመሁሏህ እንዲህ ብለዋል፡-"ማጠቃለያ፡-ሸሪዓህ ጥቅም ያለውን ነገር በፍጹም
ቸላ አይልም፡፡ይልቁንም አሏህ (ሱ.ወ) ሀይማኖታችንን አሟልቶልናል ፤ ሌሊቱ እንደ ቀን በሆነበት ሁኔታ ላይም
ትቶናል ፤ ይህንን መንገድ የሳተ ሰው ጠፊ ነው፡፡"