Professional Documents
Culture Documents
Biomedical Engineer IV
Biomedical Engineer IV
በሁሉም የህክምና መሳሪያዎች ደረጃ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት በማደርግ ዉሳኔ መስጠት፡፡
በእርዳታ የሚሰጡ መሳሪያዎችን መቆጣጠርያ መመርያ በማዘጋጀት እንዲጸድቅ ያደርጋል፡፡
የሚሰጡ የእርዳታ መሳሪያዎች በህጉ መሰረት ተሟልተው መቅረባቸውን ያረጋግጣል፤
መሰረታዊ የኤሌክትሪክ ደህንነት ቁጥጥር የአሰራር መመሪያዎችን ያዘጋጃል፤ በአግባቡም መዘጋጀታቸውን ይከታተላል
ለእያንዳንዱ የህክምና መሳሪያዎች የቁጥጥር፤ የጥራት፤ የደህንነት፤ የአስተዳደር መመሪያዎች ያዘጋጃል፤ በአግባቡ
መተግበራቸውን ይከታተላል
የአገልግሎት ግዚያቸውን የጨረሱ የህክምና መሳሪያዎች ማስወገጃ መመሪያ ማዘጋጀት፣ ሲወገዱም መመሪያውን
በመከተል መወገዳቸውን ይከታተላል
ለኢንጅነሮችና ቴክንሺያኖች ስልጠና ለመስጠት የሚያስችሉ የስልጠና ማኑዋሎችን ማዘጋጀት፤
በድርጅቱ ለተገዙም ሆነ በእርዳታ ለተሰጡ መሳሪያዎች የተሰጡ የተከላ ማንዎሎችን በመከተል ተገቢውን የተከላ ቦታ
መመቻቸቱንና ተከላው መከናወኑን ይከታተላል፣ ያጸድቃል፣ ድጋፍና ክትትል ያደርጋል
1
የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ሚኒስቴር የሥራ ዝርዝር መግለጫ ቅጽ
2
የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ሚኒስቴር የሥራ ዝርዝር መግለጫ ቅጽ
ወይም ከአቅራቢው ድርጅት በቂ ስልጠና አለማግኘት እና የመለዋወጫ እቃዎች የአቅርቦት ችግር መከሰት፣
የቴክኖሎጅው በየጊዜው መለዋወጥ፣ የመረጃ እጥረት የሚያጋጥም ሲሆን ስለመሳርያው አጠቃላይ ሁኔታ
የሚያስረዱ ማንዋሎች እንዲቀርቡ በማድረግ፣ ከመሳሪያ አቅራቢው ድረጅት ሥልጠና በመውሰድ፣ በየጊዜው
ከሚሰሩ የህክምና መሳሪያዎች ጋር ራሱን በማስተዋወቅ፣ ወቅታዊና የተሟላ መረጃ የሚያገኝበትን ሥልት በመቀየስ
እና የመለዋወጫ እቃዎች የሚገኙበትን አማራጭ በማየትና ተግባራዊ እንዲሆኑ በማድረግ መፍታትን ይጠይቃል፡፡
3.2 ራስን ችሎ መስራት
3.2.1 ሥራው የሚከናወንበት አግባብ
የመሳሪያዎች የአጠቃቀም ደንብና በመመሪያ ከቅርብ ሃላፊ በሚሰጥ አጠቃላይ መመሪያ በአሰራር መመሪያዎች
እንዲሁም የአሰራር መርሆዎችን መሰረት በማድረግ የሚከናወን ነው፡፡
3.2.1 ሥራው የሚጠይቀው የክትትልና ድጋፍ ደረጃ
የህክምና መሳሪያዎች ጥገናና ተከላ ሥራው አስፈላጊውን ውጤት ከማምጣቱና ከለሌች የህክምና ሥራዎች ጋር
ካለው ውህደት አኳያ በመጨረሻ ይገመገማል፡፡
3.3 ተጠያቂነት
3.3.1 ተጠያቂነት ለሥራ ውጤት፣
የህክምና መሳሪያዎች የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ባያካሂድ፣ በእርዳታ የሚሰጡ መሳሪያዎችን መቆጣጠሪያ መመርያ
ባያዘጋጅ፣ መሰረታዊ የኤሌክትሪክ ደህንነት ቁጥጥር የአሰራር መመሪያዎችን ባያዘጋጅ፣ ለእያንዳንዱ የህክምና
መሳሪያዎች የቁጥጥር፤ የጥራት፤ የደህንነት፤ የአስተዳደር መመሪያዎች ባያዘጋጅ፣ የአገልግሎት ጊዜያቸውን የጨረሱ
የህክምና መሳሪያዎች ማስወገጃ መመሪያ ባያዘጋጅ፣ ለኢንጅነሮችና ቴክንሺያኖች ስልጠና ለመስጠት የሚያስችሉ
የስልጠና ማኑዋሎችን ባያዘጋጅ፤ የህክምና መሳሪያዎች የተከላ ማንዎሎችን በመከተል ተከላው መከናወኑን
ባይከታተል፣ ድጋፍና ክትትል ባያደርግ፣ በመሳሪያዎች ዙሪያ አስፈላጊውን የማማከር አገልግሎት ባይሰጥ፣ ዝርዝር
የመሳሪያ technical specification ባያዘጋጅ፤ በሌሎች ባለሙያዎች የተዘጋጁትንም ባይመረምር እና የህክምና
መሳሪያዎች ከመገዛታቸው በፊትና ከተገዙ በኋላ የምርመራና የግምገማ ሥራን ባይሰራ ደረጃቸውን ያልጠበቁ
መሳሪያዎች እንዲገዙ ያደርጋል፤ መሳሪያው የሚጠበቅበትን ያክል ጊዜና አገልግሎት እንዳይሰጥ ያድረጋል፣ በድርጅቱ
የሚሰጠውን የጤና አገልግሎት ያስተጓጉላል፣ በመሳርያው ተጠቃሚ የጤና ባለሙያና በህሙማኑ ላይ አደጋ ያስከትላል
እንዲሁም በተቋሙ እቅድ አፈጻጸም ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ያሳድራል፡፡
3.3.2 ተጠያቂነት ለሚስጥራዊ መረጃ፣
የለበትም
3.4 ፈጠራ
ሥራው አጠቃላይ የጤና አገልግሎት መስጫ መሳሪያዎችን ተከላና ጥገና እንዲሁም ማስወገድ ስራን መስራት፣
3
የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ሚኒስቴር የሥራ ዝርዝር መግለጫ ቅጽ
መምራት መክታተልና መደገፍ ሲሆን የመሳሪያዎች አጠቃላይ ሁኔታ የሚያስረዳ ማንዋል ባልተገኘበት እና በጥገና
ወቅት የመለዋወጫ እጥረት ቢገጥም የመሳሪያውን ባህሪ ተረድቶ ስራውን ለማከናወን እና እንዲያከናዉኑ ለማድረግ
አዳዲስ ሲስተሞችንና አሰራሮችን በመፍጠር፣ አለማቀፍ ምርጥ ተሞክሮዎችን በመቀመርና ትግባራዊ እንዲሆን
በማድረግ እና ከፍተኛ የሞዲፊኬሽን ስራዎችን በመስራት ስራውን ውጤታማ ማድረግን ይጠይቃል፡፡
3.6 ኃላፊነት
3.6.1 ኃላፊነት ለሰው ሀብት
3.6.1.1 በኃላፊነት የሚመራቸው ሠራተኞች ብዛት
የለበትም፡፡
3.6.1.2 የኃላፊነት አይነትና ደረጃ
የለበትም፡፡
3.6.2 ኃላፊነት ለንዋይ
የለበትም ፡፡
3.6.3 ኃላፊነት ለንብረት
ሥራው ለተከላ፤ለጥገና እንዲሁም ለካሊብሬሽን የሚያገለግሉ የዎርክሾፕ መሳሪያዎችን እና የቢሮ መገልገያ
ቁሳቁሶች (computer, laptop, printer….) የመያዝ ሃላፊነት ያለበት ሲሆን ግምቱም እስከ ብር 5,000,000 ብር
4
የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ሚኒስቴር የሥራ ዝርዝር መግለጫ ቅጽ
ይሆናል፡፡
3.7. ጥረት
3.7.1 የአዕምሮ ጥረት
ሥራው የህክምና መሳሪያዎች የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት የማካሄድ፣ በእርዳታ የሚሰጡ መሳሪያዎችን መቆጣጠሪያ
መመርያ የማዘጋጀት፣ መሰረታዊ የኤሌክትሪክ ደህንነት ቁጥጥር የአሰራር መመሪያዎችን የማዘጋጀት፣ ለእያንዳንዱ
የህክምና መሳሪያዎች የቁጥጥር፤ የጥራት፤ የደህንነት፤ የአስተዳደር መመሪያዎች የማዘጋጀት፣ የአገልግሎት
ጊዜያቸውን የጨረሱ የህክምና መሳሪያዎች ማስወገጃ መመሪያ የማዘጋጀት፣ ለኢንጅነሮችና ቴክንሺያኖች ስልጠና
ለመስጠት የሚያስችሉ የስልጠና ማኑዋሎችን የማዘጋጀት፤ የህክምና መሳሪያዎች የተከላ ማንዎሎችን በመከተል
ተከላው መከናወኑን የመከታተል፣ ድጋፍና ክትትል ማድረግ፣ በመሳሪያዎች ዙሪያ አስፈላጊውን የማማከር አገልግሎት
የመስጠት፣ ዝርዝር የመሳሪያ technical specification የማዘጋጀት፤ የተዘጋጁትንም የመመርመር እና የህክምና
መሳሪያዎች ከመገዛታቸው በፊትና ከተገዙ በህዋላ የምርመራና የግምገማ ሥራን የመስራት የአዕምሮ ውጥረት
የሚጠይቅ ሲሆን ይህም ከስራ ጊዜው እስከ 75 በመቶ ይሆናል፡፡
3.7.2.ስነልቦናዊ ጥረት
ሥራው በተደጋጋሚ ከቅርብ ሀላፊው፤ከባልደረቦቹ፤ከሂሳብና ፋይናንስ ክፍል፤ ከመሳሪያው ተገልጋዮቹ እንዲሁም
ከመሳሪያው አቅራቢ ጋር በሚያደርጋቸው ግኑኝነቶች የሚነሱ የተለያዩ
አለመግባባቶችን(ትችት፤ማጥላላት፤አለመታዘዝ፤ወዘተ) ተቋቁሞ ስራውን ውጤታማ ለማድረግ የስነ ልቦና
ዝግጁነትና ቁርጠኝነት እንዲኖረው ይጠይቃል፡፡
3.7.3 የዕይታ ጥረት፣
ስራው ከኢንተርኔት የመሳሪያዎችን አተካከልና አጠጋገን የሚያስረዳ ማንዋልና መረጃዎችን መፈለግን እና ጨረር
አመንጭ የሆኑ የህክምና መሳሪያዎችን መትክልና መጠገን የሚጠይቅ ሲሆን ይህም የእይታ ጥረትን ይጠይቃል ከስራ
ጊዜው እስከ 50 በመቶ ይወስዳል፡፡
3.7.4 የአካል ጥረት
ሥራው 30% በመቀመጥ፤ 30% በመቆም እና 40% በመንቀሳቀስ የሚከናወን ነው፡፡
3.8. የሥራ ሁኔታ
3.8.1. ሥጋትና አደጋ
በሥራው ወቅት በጋሉ የመሳሪያ ክፍሎች አማካኝነት ለቃጠሎ፣ የህክምና መሳሪያዎች አማካኝነት የመቆረጥና በከፊል
የሰውነት ክፍልን ማጣት እንዲሁም በአግባቡ ባልተዘረጉ የመብራት መስመሮች ለሚከሰት የኤሌክትሪክ ንዝረት
ይጋለጣል፡፡
5
የፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ሚኒስቴር የሥራ ዝርዝር መግለጫ ቅጽ