Professional Documents
Culture Documents
JK R Student Conduct Discipline Procedures Amharic
JK R Student Conduct Discipline Procedures Amharic
መግቢያ
የሚከተሉት የተማሪ ፀባይ እና ሥነ ምግባር መመሪያዎች ለት/ቤት ቦርድ ፖሊሲ JK - የተማሪ ሥነ ምግባር አፈጻጸም የተዘጋጁ
ናቸው። እነዚህ መመሪያዎች የተቀረጹት በፖሊሲ JK ውስጥ እንዲሁም በፌደራል እና የስቴት ሕጎች እና በአካባቢ መመሪያዎች ውስጥ
ከተቀመጡ ጠቅላላ ዓላማዎች እና መርሆች ጋር እንዲጣጣሙ ተደርገው ነው።
1-4 በት/ቤት ሥነ ምግባር ውስጥ የዘር ልዩነቶችን እና ሌሎች የጥብቅ መደብ ልዩነቶችን ማስተካከል/ማረም
ሀ. በት/ቤት ሥነ ምግባር ውስጥ ማንኛውንም ዓይነት የዘር ልዩነትን ለማጥፋት ጥረቶች ማድረግ ይገባል። የሠራተኞች አባላት ከታገዱት፣
ከተባረሩት፣ ወይም ለህግ ተላልፈው ከተሰጡት ተማሪዎች መካከል በታሪክ ከፍተኛ ውክልና የነበራቸው በዘር እና በብሔር ቡድኖች
ወይም ሌሎች ጥበቃ የሚደረግላቸው መደቦች ተማሪዎች ላይ የሚያደርጓቸውን ድርጊቶች ያለውን ተጽዕኖ የመቆጣጠር የተለየ ኃላፊነት
አለባቸው።
1-5 የሥነ ምግባር እርምጃ ሊወሰድበት የሚገባው ተማሪ ፀባይሀ. ተማሪው በክፍል ውስጥ፣ በት/ቤት ህንፃዎች ውስጥ፣ በት/ቤት
መጫዎቻ ቦታዎች፣ ወይም በት/ቤት መኪኖች ላይ በአጠቃላይ በዋና ትምህርቶች ወይም ተኳዳኝ ትምህርቶች ጊዜ የሚያደርጋቸው
እንቅስቃሴዎች በት/ቤቱ ውስጥ አደናቃፊ ሊሆኑ የሚችሉ ወይም ለሌሎች ተማሪዎች ወይም የት/ቤቱ ሠራተኞች ጤናማነት ወይም
ደህንነት አስጊ ከሆነ የሥነ ምግባር እርምጃ የሚወሰድባቸው ይሆናል።
1-7 ስርጭት
ሀ. ዲስትሪክቱ ይህን ፖሊሲ በዲስትሪክቱ ድር ጣቢያ እና በእያንዳንዱ ት/ቤት ውስጥ በእንግሊዝኛ እና በስፓኒሽኛ ይለጥፋል። ይህን
ፖሊሲ እና የት/ቤት ሕጎች ቅጅዎች ለሚጠይቅ ተማሪ እና ወላጅ/አሳዳጊ የሚሰጡ ይሆናል፤ እንዲሁ በጥያቄ ወላጁ/አሳዳጊው በሚረዳው
ቋንቋ የሚተረጎሙ ይሆናል።
ለ. ት/ቤቶች በተናጥል ተማሪዎቻቸውን በዚህ ፖሊሲ እና ባጸደቋቸው ሌሎች የት/ቤት ሕጎች እና መተዳደሪያ ደንቦች ላይ
ተማሪዎቻቸውን እንዲያሰለጥኑ ይበረታታሉ።
ክፍል ሁለት፦ የእርምት እርምጃዎች እና ውጤቶቻቸው
2-1 አጠቃላይ
ሀ. ውጤታማ የት/ቤት ሥነ-ምግባር ፖሊሲዎች በሚቻለው መጠን የተማሪን ትምህርት ከማቋረጥ የሚገቱ ሥነ-ምግባራዊ ምላሾችን
ያበረታታሉ። ት/ቤቶች የመንግስት ሕጎችን፣ የአካባቢ ደንቦችን እና አስገዳጅ ሪፖርት የማድረግ ሕጎችን እስካልተጻረሩ ድርስ ከት/ቤት-
ውጭ የማቆየት ቅጣትን፣ በማባረር ለመቅጣት መሞከርን እና ወደ ሕግ መውሰድን መቀነስ አለባቸው።
2-3 በሥነ ምግባር ጥፋት ላይ እርምጃ በሚውሰድ ጊዜ ሊታዩ የሚገባቸው ጠቃሚ ነገሮች
ሀ. ለተማሪዎቸ ምግባረ-ብልሹነት ቅጣቶችን በመምረጥ ጊዜ መምህራን፣ አስተዳደሮች እና ሠራተኞች የዲስትሪክቱን የት/ቤት ውስጥ
ረብሻዎችን ማጥፋትን እና የተማሪዎችን የትምህርት ጊዜ ማብዛት ዓላማዎችን ማመዛዘን/ማጣጣም ያስፈልጋቸዋል። ተማሪዎችን ሥርዓት
ከማስያዝ/ከመቅጣት አስቀድሞ፣ የሚከተሉት ጉዳዮች ግንዛቤ ውስጥ ይገባሉ፦
1. የዕድሜ፣ የጤና፣ እና የአካል ጉዳተኝነት ወይም የልዩ ፍላጎት ትምህርት ሁኔታ2.
2. የተማሪው አካዳሚያዊ ምደባ ተግቢነት
3 የተማሪው ቀደምት ፀባይ እና የፀባይ ማህደር (ሪከርድ)
4. የተማሪው አመለካከት
5. የወላጅ/አሳዳጊ የትብብር እና የተሳትፎ ደረጃ
6. ጉዳትን ለመጠገን/ለማረም የተማሪው ፈቃደኝነት
7. የጥፋቱ ከባድነት እና ያስከተለው የጉዳት መጠን
8. የክስተቱ በአጠቃላይ የት/ቤቱ ማኅበረሰብ ላይ ያደረሰው ተጽዕኖ
ሀ. ተማሪዎችን ሥርዓት ከማስያዝ/ከመቅጣት አስቀድሞ የተማሪዎችን ምግባረ-ብልሹነት ለማስተካከል የተቀረጹ መከላከያ እና
ማስተካከያ ፕሮግራሞች መኖራቸውን ማየት ያስፈልጋል።
ሠ. የDPS ደህንነት እና ፀጥታ ዲፓርትመንት ወንጀል የሚባሉ የት/ቤት ውስጥ ጥፋቶች ዝርዝር ያዘጋጃል። እነዚህ ወንጀሎች የሕግ
መስፈርቶችን ያሟሉ ዘንድ ለሕግ አስከባሪ አካል ሪፖርት መደረግ አለባቸው። እያንዳንዱ ት/ቤት በርዕሰ መምህሩ እና/ወይም በተወካይ
አማካኝነት ስለሁሉም እንዲህ ዓይነት ወንጀሎች ወይም የተጠረጠሩ ወንጀሎች የጽሑፍ ሪፖርት ያቀርባሉ። የሁሉም ሪፖርቶቹም
በዲስትሪክት አቀፍ ተጠናቅሮ በፍጥነት ለሕግ አስከባሪ ሪፖርት ይደረግ ዘንድ ለDPS ደህንነት እና ፀጥታ ክፍል ማስገባት ይኖርባቸዋል።
ረ. ከዚህ በታች የተዘረዘሩት የሥነ ምግባራዊ ጥፋቶች እና የሚያስከትሏቸው ውጤቶች ናቸው፦
2. ለደረጃ ስድስት ጥቃት፣ የችሎት ባለሙያው /hearing officer/ተማሪው በት/ቤት ግቢ ውስጥ የእጅ ጠመንጃ /firearm/ ይዞ
ተገኝቷል ብሎ ከወሰነ፣ የሚከተለው ቅጣት ለአንድ ዓመት ማባረር ይሆናል።
ሠ. ዋና ተቆጣጣሪው ወይም ተወካዩ የተጠቆመውን እርምጃ እና የችሎት ባለሙያውን ሪፖርት ከመረመሩ በኋላ በቀረበው
የማባረር ሃሳብ ላይ እርምጃ ይወስዳሉ። ስለተወሰደው እርምጃ ተማሪውን እና ወላጁን/አሳዳጊውን የሚያሳውቅ የጽሑፍ ደብዳቤ ችሎቱ
ከተያዘበት ቀን አንስቶ በአምስት (5) ቀናት ውጥ መላክ አለበት። ዋና ተቆጣጣሪው ወይም ተወካዩ ለደረጃ ስድስት ጥፋት የአንድ
ዓመት ማባረር አይገባውም ብሎው ከወሰኑ፣ የጽሑፍ ሀሳቡ ልዩ የሆነባቸው ምክንያቶችን ይዘረዘራል። ማስታወቂያው ወላጁ/አሳዳጊው
ሊረዳው በሚችል ቋንቋ ሊሰጣቸው ይገባል።
ረ. ዋና ተቆጣጣሪው ወይም ተወካዩ ለተማሪው እና ለወላጁ/ለአሳዳጊው ማስታወቂያ ደብዳቤው በደረሳቸው በአሥር (10) ቀናት
ውስጥ ውሳኔውን ለትምህርት ቦርዱ ይግባኝ የማለት መብት እንዳላቸው ያሳውቃሉ። ማስታወቂያው ወላጁ/አሳዳጊው ሊረዳው
በሚችል ቋንቋ ሊሰጣቸው ይገባል።
ሰ. ይግባኝ በሰዓቱ ከተጠየቀ፣ የትምህርት ቦርዱ ማኅደሩን ይገመግም እና የዲስትሪክቱ ተወካዮች እና ተማሪው መግለጫዎችን
ለትምህርት ቦርዱ እንዲያቀርቡ ዕድል ይሰጣቸዋል። የትምህርት ቦርዱ፦
1. የሚከተሉትን ለማረጋገጥ በቂ ማስረጃ መቅረቡን ውሳኔ ይሰጣል።
ሀ. የተባለው ወንጀል/ጥፋት መፈጸሙን፣ እና
ለ. የተጣለው ቅጣት አግባብ መሆኑን።
2. ስብሰባ በተካሄደ በአምስት ቀናት ውስጥ የጽሑፍ ውሳኔ ይሰጣል።
3. ምንም ጥፋት/ወንጀል አልተፈጸመም ተብሎ ከተወሰነ፣ እገዳውን የሚመለከቱ ሁሉም ሰነዶች/ማኅደሮች ከተማሪው ፋይል
ይሰረዛሉ/ይፋቃሉ። ከዚያም የተስተካከለው የተማሪው ፋይል ቅጅ ለተማሪው ወላጅ ወይም አሳዳጊ በፖስታ ይላክላቸዋል።
4. የተጣለው ቅጣት ከጥፋቱ/ከወንጀሉ አንፃር አግባብ ያልሆነ ሆኖ ከተገኘ፣ ሁሉም የት/ቤት ሰነዶች/ማኅደሮች በትምህርት ቦርዱ
የተሻሻለውን ቅጣት እንዲያሳዩ ለማድረግ ይከለሳሉ።
ሸ. እያንዳንዱ ተማሪ በተባረረበት ወቅት ስለሚኖሩት የትምህርት አማራጮች ለወላጁ/አሳዳጊው መረጃ
ይሰጣል። ወላጁ/አሳዳጊው የቤት ውስጥ የትምህርት ፕሮግራምን ከመረጡ፣ የሚፈለገው የክፍል ደረጃ ሥርዓተ ትምህርቶች
ይቀርቡላቸዋል።
መተግበር የተጀመረበት ቀን
ኦክቶበር 1፣ 1996
የፀደቀበት ቀን፦ 19፣1996
የተከለሰበት ቀን:- ኦገስት 21፣ 2008
የተከለሰበት ቀን:- ኦክቶበር 15፣ 2008
የተከለሰበት ቀን:- ሴፕቴምበር 15፣ 2011
ሕጋዊ ማጣቀሻዎች፦
C.R.S. 22-32-109.1 (የተማሪ ፀባይ፣ ደህንነት እና ጤናማነት)
C.R.S. 22-32-126(5) (የሥነ ምግባር ነክ መረጃዎች አያያዝና አሰጣጥ)
C.R.S. 22-33-105 (እገዳ፣ ማባረር፣ እና ቅበላ/ምዝገባ መከልከል)
C.R.S. 22-33-106 (የእገዳ፣ የማባረር፣ እና ቅበላ/ምዝገባ የመከልከል ምክንያቶች)
C.R.S. 22-33-106.3 (በማባረር ችሎት ላይ ጥቅም ላይ የሚውሉ የተማሪ መግለጫዎች)
C.R.S. 22-33-202 (በአደጋ ወይም ሥጋት ውስጥ ያለ ተማሪን መለየት)
C.R.S. ከ18-3-202 እስከ 204 (አንደኛ፣ ሁለተኛ፣ እና ሦስተኛ ደረጃ ጥቃት)
C.R.S. ከ18-8-704 እስከ 706 (ምስክርን ማስፈራራት እና መበቀል)
C.R.S. 19-3-304 (ስለ ህፃናት ብዝበዛ/መተው ወይም ትኩረት መነፈግ ሪፖርት እንዲያደርጉ የሚጠበቅባቸው ሰዎች)
C.R.S. 19-1-103 (የህፃናት ብዝበዛ)
C.R.S. 16-22-102 (ሕገ ወጥ የሆነ ፆታዊ ባሕርይ፣ ሕገ ወጥ የሆነ ፆታዊ ግንኙነት፣ ጸያፍ ራቁትነት)
የቤተሰብ የትምህርታዊ እና የግላዊነት መብቶች (FERP) 20 U.S.C. 1232g(h))