Professional Documents
Culture Documents
የክበባት-ና-ቡድኖች-አደረጃጀት-መመሪያ
የክበባት-ና-ቡድኖች-አደረጃጀት-መመሪያ
የክበባት-ና-ቡድኖች-አደረጃጀት-መመሪያ
የኪነ ጥበብ ዝንባሌና ተሰጥኦ ያላቸውን ተተኪ ከያኒያን በማፍራት በክልሉ የኪነ
ጥበብ ሙያና ሙያተኛነት እንዲስፋፋ ለማድረግ የሚያስችል ዘላቂነትና አግባብነት
ያለውን የክትትልና ድጋፍ ሥርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ፣
1
የቢሮውን በሥራ ላይ ያለውን የአማተር ኪነ ጥበባት ክበባትና ማህበራት
አደረጃጀት መመሪያ ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፣
ክፍል አንድ
ጠቅላላ
1. አጭር ርዕስ
2. ትርጓሜ
2
አስተዳደሮች የሚገኝ የባህልና ቱሪዝም መምሪያና በወረዳ የሚገኝ የባህልና
ቱሪዝም ጽ/ቤት ማለት ነው፡፡
3. “የኪነ ጥበብ ክበብ ” ማለት በአስፈፃሚው መ/ቤት የሚደራጁና ክትትል
ድጋፍ የሚደረግላቸው፣ ወጣት ተተኪ ከያኒያን የኪነ ጥበብ ተሰጥኦ፣
ፍላጎትና ዝንባሌያቸውን የሚፈትሹባቸው፣ መሠረታዊ ዕውቀት
እንዲጨብጡና በቀጣይ ሙያውን አጠናክረው እንዲቀጥሉበት የማስቻል
ተልኮ ያላቸው የክልሉ መሠረታዊ የኪነ ጥበብ አደረጃጀት ናቸው፡፡
4. “የባህል ሙዚቃ ቡድኖች” ማለት በክልሉ ውስጥ በወረዳ፣ በዞንና በከተማ
አስተዳደር ደረጃ በአስፈፃሚው መ/ቤትና በአካባቢው የመንግሥት
አስተዳደር አካላት የሚደራጁና ክትትል ድጋፍ የሚደረግላቸው፤
የአካባቢውን ሕብረተሰብ ትውፊታዊ የሙዚቃና ቴአትር እሴቶች
የሚያስተዋውቁ፣ የሚያስፋፉና እንዲጠበቅ የሚያደርጉ፤ በኪነ ጥበብ
ለአካባቢው ልማት አስተዋፆ የማበርከት ተልዕኮ የተሰጣቸው አደረጃጀት
ናቸው፡፡
5. “የኪነ ጥበብ ኢንተርፕራይዝ” ማለት በተለያዩ የኪነ ጥበብ የሙያ ዘርፎች
ኪነ ጥበባዊ የፈጠራ ውጤቶችን በማምረት፣ በማከፋፈል፣ በመሸጥ፣
በማከራየት፣ በማስተዋወቅ፣ አገልግሎቱን በመስጠት ወይም በመሳሰሉት
ሥራዎች በየደረጃው ከሚገኝ የባህልና ቱሪዝም አስፈፃሚ መ/ቤት የሙያ
መስፈርት ብቃት ማረጋገጫ አግኝቶ በክልሉ በሚመለከተው አካል ሕጋዊ
የንግድ ፍቃድ በማውጣት በሥራው የተሠማራ ወይም የሚሠማራ የንግድ
ተቋም ማለት ነው፣
6. “የኪነ ጥበብ የሙያ ማህበር” ማለት በአንድ ዓይነት የኪነ ጥበብ ዘርፍ
ሙያ በተሰማሩ ባለሙያዎች በፈቃደኝነት ትርፍ ለማግኘትና ለመከፋፈል
ሳይሆን በሙያቸው የሚገባቸውን ሕጋዊ መብት ለመጠበቅ፣ ሙያቸውን
በጋራ ለማስፋፋትና ለማሳደግ ዓላማ በክልሉ ከሚመለከተው አካል ሕጋዊ
ፍቃድ በማግኘት የተደራጀና የሚመሠረት የሙያ ማህበር ነው፡፡
3
7. “የሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት” ማለት በአስፈፃሚ
መሥሪያ ቤት አደራጅነት በዚህ መመሪያ መሠረት ለሚደራጁ የኪነ ጥበብ
ክበባት ወይም የባህል ቡድን በአሥፈፃሚ መሥሪያ ቤት የሚሰጥ የሕጋዊ
ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ማለት ነው፡፡
8. “የሙያ መስፈርት ብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት” ማለት በባህል
ኢንዱስትሪ የሙያ ዘርፎች ገቢ ማስገኛ የንግድ ስራዎች ለመሰማራት
ለሚጠይቅ ሰው ወይም ድርጅት የንግድ ፍቃዱን ለማውጣት
የሚያስችለው፣ ፍቃዱን ከማግኘቱ አስቀድሞ የግዴታ በመስኩ ለመስራት
የሚያስችለውን ባህላዊ መስፈርቶች ማሟላቱ ተረጋግጦ በየደረጃው
በአስፈፃሚው መ/ቤት የሚሰጥ የሙያ ብቃት ማረጋጫ የምስክር ወረቀት
ነው፡፡
9. “ የበጀት ዓመት” ማለት በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከሐምሌ 1 እስከ ሰኔ 3ዐ
ወይም በግሪጎሪያን አቆጣጠር ከጀንዋሪ 1 እስከ ዲሴምበር 31 ያለው ጊዜ
ነው፡፡
3. የተፈፃሚነት ወሰን
4
ክፍል ሁለት
4. ዓላማ
5
5. አባላት ትርፍ ጊዜያቸውን በአልባሌ ቦታ እንዳያሳልፉ፣ በኪነ ጥበብ
እየተዝናኑ ለወደፊት ሕይወታቸው ጠቃሚ እውቀት በመገብየት
የሚያሳልፉበትን አማራጭ መፍጠር፣
6. ለአስፈፃሚው መ/ቤት ተተኪ ከያኒያንን ለማፍራት የሚያስችል የክትትል፣
የድጋፍ አሠጣጥ፣ የመረጃ አያያዝና አጠቃቀም ምቹ ሁኔታን መፍጠር፣
1. የኪነ ጥበብ ክበብ በአንድ ዓይነት የኪነ ጥበብ ዘርፍ ወይም ከአንድ በላይ
ናቸው ፡-
ሀ. የሙዚቃ ክበብ
ለ. የቴአትር ክበብ
የሚከተሉት ናቸው፡-
6
4. ከላይ በንዑሥ አንቀፅ 2 እና 3 ላይ ከተዘረዘሩት ውጪ የሆነ የክበብ
7
መ/ በሥልጠናው ማጠናቀቂያ ሠልጣኞች አጫጭር የተሰጥኦ
መፈተሻ ሥራዎችን በተናጥል ወይም በቡድን ሠርተው
እንዲያሳዩ በማድረግ መገምገምና ከፍተኛ ተሰጥኦ
የሚታይባቸውን በክበብ ለማደራጀት መመልመል ውጤታማ
የማይሆኑትን መክሮ ማሰናበት፣
8
ተዛማጅ በሆኑ የኪነ ጥበባት ጥምረት የሚደራጁት እስከ አሁን
ለእያንዳንዱ የተጠቀሰውን በማጣመር ያልበለጠ መሆን አለበት፤
6. ከላይ በንዑስ አንቀፅ 3፣ 4 እና 5 ሥር የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ
9
ሀ/ በአካባቢው በሚገኝ ታዋቂ ተፈጥሯዊ የመልክአ ምድር መስህብ
ገፅታን ማለትም ተራራ፣ ኮረብታ፣ ጅረት ሐይቅ ፏፏቴ ወዘተ..
የመሳሰለውን ስያሜ በመጠቀም፣
10
4. ለክበብ የተሰጠ ስያሜን ብቻ ነጥሎ በመጥራት ወይም ክበብ የሚለውን
11
ይችላል፣ ነገር ግን አርማና ማሕተሙ ከክበቡ ስያሜና ዓይነት ጋር
የተጣጣመ መሆን አለበት፣ የተጠቀሱትን እንዲያወጣ አስፈፃሚው መ/ቤት
የድጋፍ ደብዳቤ ይሰጣል፣
5. የሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ለሶስተኛ ወገኖች ተላልፎ
1. በሙዚቃ ክበብ
12
መሣርያ አጨዋወት ስልቶችን ልምምድ በቋሚ ፕሮግራም
ማካሄድ፣
ሠ/ የአካባቢውን ሕብረተሰብ ትውፊታዊ የሙዚቃ ባህልንና
አጨዋወትን፣ የውዝዋዜና ዳንኪራ ስልቶችን ትክክለኛ
መረጃዎችን ከምንጫቸው በማሰባሰብ በግብአት መጠቀም፣
ረ/ በአስፈፃሚው በመ/ቤት ባለሙያ ብቃታቸው የተረጋገጠ የሙዚቃ
ዝግቶችን፣ ሕብረ ዝማሬዎችንና አጫጭር ሙዚቃዊ ድራማዎች
በተለያዩ ህዝባዊና መንግሥታዊ በዓላት ቋሚ ፕሮግራም
በመዘርጋት ለተመልካች ማቅረብ፣
13
ሀ/ በአባላት በተናጥልና በቡድን አጫጭር የመድረክ፣ የቴሌቪዥንና
የሬድዮ ተውኔቶችን፣ የማይም ድራማና የኮሜዲ ዝግጅቶችን
መፍጠር በአስፈፃሚው መ/ቤት ባለሙያ ማስገምገም በሚሰጥ
አስተያየት ማሻሻልና በማዘጋጀት ለተመልካች ማቅረብ፣
ለ/ በልማታዊና ወቅታዊ ጉዳዮች ፣ በማህበራዊ ጠንቆችና በጎጂ
ልማዳዊ ድርጊቶች ዙሪያ ሕብረተሰቡን እያዝናኑ በማስተማር
መልዕት የሚያስተላልፉ አጫጭር ጭውውት ድራማዎችን፣
ጉዳዩ ከሚመለከታቸው መንግስታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ
ተቋማት የፋይናንስ ድጋፍ በማፈላለግ አዘጋጅቶ ማሳየት፣
ሐ/ የተዘጋጁና ብቃታቸው የተረጋገጠ የቴአትር ዝግጅቶችን በተለያዩ
ህዝባዊና መንግሥታዊ በዓላት፣ በቋሚ ፕሮግራም፣ በአዳራሽ፣
በአደባባዮች፣ በገበያ ላይ ወዘተ… ለተመልካች ማቅረብ ፣
መ/ የትወና ብቃትና ክህሎትን የሚያሳድጉ የሰውነት ማፍታቻ
እስፖርታዊ እንቅሰቃሴዎችንና የድምጽ አወጣጥ ልምምዶችን፣
አጫጭር የመነባንብና የድንገቴ ፈጠራ ሥራዎችን በቋሚ
ፕሮግራም ልምምድ ማድረግ፣
ሠ/ የአካባቢውን ሕብረተሰብ ትውፊታዊ ድራማ ክዋኔዎችን
በሚቀርቡቧቸው ማሕበረሰባዊ የክዋኔ መድረኮች ላይ በመገኘት
ማጥናት፣ ትክክለኛ መረጃቸውን ከምንጩ በማሰባሰብ ለዝግጅት
በግብአት መጠቀም፣
ረ/ ብቃታቸው የተረጋገጠ የክበቡን አጫጭር ጭውውትና የቪዲዮ
ድራማ ሥራዎችን በማሳተም ለሕዝብ ማቅረብ፣
ሰ/ አባላት ክህሎታቸውን ለማሻሻል የሚረዱዋቸውን የቴአትር
አፃፃፍ፣ የትወናና የቴአትር አዘገጃጀት ስልጠናዎችን እንዲያገኙ
የተለያዩ ስልቶችን በመቀየስ ተግባራዊ ማድረግ፣
14
ሸ/ በአካባቢው ጠንካራ እንቅስቃሴ ያላቸውን የቴአትር ቡድኖችን፣
ታዋቂና ዝናን ያተረፉ ፀሐፌ ተውኔቶችን፣ ተዋናዮችንና የቴአትር
ጥበብ ምሁራንን በመጋበዝ ልምዳቸውን እንዲያካፍሉና አባላት
የተሞክሮ ልውውጥና ልምድ እንዲቀስሙ ማድረግ፣
15
ሐ/ የአባላት የፈጠራ ድርሰቶች፣ ከታዋቂ ደራሲያን የተመረጡ
ሥራዎች፣ ሥነ ቃሎችና ሌሎች አዝናኝ የሥነ ጽሁፍ ዝግጅቶች
የሚቀርቡባቸውን የሥነ ጽሁፍ ምሽቶችን በወርሐዊነት ወይም
በተለያየ ቋሚ ፕሮግራም በመዘርጋት ማካሄድ፣
መ/ የሥነ ጽሁፍ ምሽቶች ሳቢና ማራኪ፣ ቁጥሩ እየጨመረ የሚሄድ
ቋሚ ታዳሚ ያላቸው እንዲሆኑ፣ የድራማ፣ የሙዚቃ፣ የቅኔ
ዘረፋ ወዘተ… አድማቂ ሥራዎችን ማካተት፣ ለዚህም ከተለያዩ
ክበባት፣ ከቅኔ ት/ቤቶች ወዘተ.. ጋር በቅንጅት መሥራትና
ስፖንሰሮችን በማፈላለግ ማሳተፍ፣
ሠ/ በተለያዩ መንግስታዊና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት
በማስታወቂያና በሚዲያ በሚወጡ የሥነ ጽሁፍ ውድድሮች ላይ
መሳተፍ፣
ረ/ በተለያዩ መንግስታዊና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት በሚዘጋጁ
መድረኮች በመገኘት ለመድረኩ ተሳታፊዎችን እያዝናኑ ጠቃሚ
መልእክቶችን የሚያስተላልፉ ሥነ ጽሁፋዊ የፈጠራና የሥነ ቃል
ሥራዎችን ማቅረብ፣
ሰ/ ብቃታቸው በአስፈፃሚው መ/ቤት የተረጋገጠ፣ የተለያዩ የሥነ
ጽሁፍ ፈጠራ ሥራዎችን፣ የተሰበሰቡ ሥነ ቃሎችን በአባላት
በተናጥል ወይም በቡድን ወይም እንደ ክበብ በማደራጀት፣ ጉዳዩ
ከሚመለከታቸውን ስፖንሰሮችን በማፈላለግ ማሳተምና
ለአንባቢያን ማቅረብ፣
ሸ/ አባላት ክህሎታቸውን ለማሻሻል የሚረዱዋቸውን የሥነ ጽሁፍ
ኪነ ጥበባት ስልጠናዎችን እንዲያገኙ የተለያዩ ስልቶችን በመቀየስ
ተግባራዊ ማድረግ፣
ቀ/ ጠንካራ እንቅስቃሴ ያላቸውን አቻ ክበባትን፣ ታዋቂና ዝናን
ያተረፉ የሥነ ጽሁፍ ሰዎችን፣ የኪነ ጥበብ ምሁራንን በመጋበዝ
16
ልምዳቸውን እንዲያካፍሉና አባላት የተሞክሮ ልውውጥና ልምድ
እንዲቀስሙ ማድረግ፣
17
ሠ/ በተለያዩ መንግስታዊና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት
ተዘጋጅተው በሚካሄዱ መድረኮች በመገኘት ለመድረኩ
ተሳታፊዎች የአባላትን የሥዕልና ቅርፃ ቅርጽ የፈጠራ ሥራዎችን
ለተሳታፊዎች ማቅረብና አስተያየት መሰብሰብ፣
ረ/ በአባላት በተናጥልና በቡድን የተሠሩ የክበቡን ምርጥ የሥዕልና
ቅርፃ ቅርፅ የፈጠራ ውጤቶች ስፖንሰሮችን በማፈላለግ
በመጽሔት ማሳተምና ማቅረብ፣
ሰ/ አባላት ክህሎታቸውን ለማሻሻል የሚረዱዋቸውን የሥዕልና ቅርፃ
ቅርፅ ኪነ ጥበባት ስልጠናዎችን እንዲያገኙ የተለያዩ ስልቶችን
በመቀየስ ተግባራዊ ማድረግ፣
ሸ/ ጠንካራ እንቅስቃሴ ያላቸውን አቻ ክበባትን፣ ታዋቂና ዝናን
ያተረፉ ሠዓሊያንና ቀራፂያንን፣ የዘርፉ ምሁራንን በመጋበዝ
ልምዳቸውን እንዲያካፍሉና አባላት የተሞክሮ ልውውጥና ልምድ
እንዲቀስሙ ማድረግ፣
18
ሀ/ የሥነ ጽሁፍና የቴአትር ክበብ በዚህ አንቀጽ ንዑሥ አንቀፅ 2
ላይ ከተራ ቁጥር ሀ እስከ ቀ እና በንዑሥ አንቀጽ 3 ከተራ
ቁጥር ሀ እስከ በ የተጠቀሱትን በማጣመር፣
19
4. በማንኛውም ጊዜ በአስፈፃሚው መ/ቤት ማናቸውም ዓይነት መረጃ ሲጠየቅ
የመስጠትና የማቅረብ፣ በሚሰጠው ቅጽ መሠረት መረጃ የመያዝና
ሲጠየቅም የማቅረብ እንዲሁም በማንኛውም ጊዜ ጥሪ ሲያደርግለት
የመቅብና የመሳተፍ፣
5. የአስፈፃሚውን መሥሪያ ቤት በክትትልና ግምገማው የደረሰባቸውን
በእንቅስቃሴው ላይ የሚታዩ ጉድለቶችን እንዲያስተካክል በቃል ወይም
በጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ወይም ማስተካከያ ሲደርሰው በተገለፀው የጊዜ ገደብ
ውስጥ ጉድለቱን የማስተካከል፣
6. ከክበባት ዓላማ ውጪ በሆኑ በገቢ ወይም በትርፍ ማግኛ ተግባራት ወይም
በዚህ መመሪያ አንቀፅ 9 ከተዘረዘሩትና እንዲከናውን ከተፈቀዱለት
ተግባራት ውጪ ከኢንተርፕራይዞች ጋር በጨረታ የመሳተፍና የመሳሰሉ
ተግባራትን አለመፈፀም፣
7. ብቃታቸው የተረጋገጡ ሥራዎችን ለሕዝብ እንዲያቀርብ በአስፈፃሚው
መ/ቤት የድጋፍ ደብዳቤ ካልተሰጠው በስተቀር ከተቋቋመበት አካባቢ ውጪ
ያለመንቀሳቀስ፣
8. የክበቡን ስያሜ ከለወጠ ለውጡን ወይም ማሻሻያውን ለአስፈፃሚው መ/ቤት
አቅርቦ የማስመዝገብና የማሳወቅ ፣
9. የክበቡን ጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባዎች በክበቡ መተዳደሪያ ደንብ በተደነገገው
መሠረት ማካሄድና ስብሰባውን ከማካሄዱ ከሶስት የሥራ ቀናት አስቀድሞ
የስብሰባውን ጊዜና ቦታ ለአስፈፃሚው መቤት በጽሁፍ የማሳወቅ የመ/ቤቱ
ተወካይ በስብሰባው በታዛቢነት እንዲሳተፍ የማድረግ፣
10.የክልሉን ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ባህሎች፣ ቅርሶች፣ ቋንቋዎች፣
ታሪኮች እና ሕጎች የሚፃረር ድርጊት ያለመፈጸም፣ በሌሎች ሲፈፀምም
በወቅቱ ለአስፈፃሚው መ/ቤት ሪፖርት የማድረግ፣
20
11.በዕቅድ የመመምራት፣ አባላትን ባሳተፈ አግባብ ዓመታዊ ዕቅድ ማዘጋጀትና
ማፅደቅ፣ የፀደቀውን የክበብ ዓመታዊ ዕቅድ ለአስፈፃሚው መ/ቤት አንድ
ቅጂ የማቅረብ፣
12.የክበቡን ዓመታዊ የሥራ ዕቅድ ክንውን አፈፃፀም ሪፖርትን፤ ታቅደው
የተከናወኑ ተግባራትን፣ በአባላት መዋጮ፣ በስጦታ፣ ከተሰጠ አገልግሎት፣
ወዘተ… የተገኘ ፋይናንስ ገቢና የወጪ አጠቃቀምን፤ ያጋጠሙ ችግሮችና
የተወሰዱ መፍትሔዎችን ባካተተ አግባብ በየ6 ወሩ በማዘጋጀት 6ኛው
ወር በገባ በ 15 ቀናት ውስጥ ለአስፈፃሚው መ/ቤት የማቅረብ፣
13.የአባላትን መረጃዎችን፣ በክበቡ ወይም በአባላት የተሠሩ ማናቸውም
አይነት ኪነ ጥበባዊ ሥራዎችንን፣ ዓመታዊ ዕቅድና ሪፖርት ፋይሎችን፣
የቋሚ ንብረቶች፣ የገቢና ወጪ ሰነዶችን እና ሌሎች ስለ ክበቡ እንቅስቃሴ
የተመለከቱ የጽሁፍ፣ የምስል፣ የድምፅ ወዘተ… መረጃዎችንና ሠነዶችን
በአግባቡ አደራጅቶ የመሠነድና የመያዝ፣
14.የባንክ አካውንት በመክፈት የክበቡን የፋይናንስ እንቅስቃሴ በመተዳደሪያ
ደንቡ በተደነገገው መሠረት የማንቀሳቀስ፣
15.የፋይናንስና የማቴሪያል ድጋፎችን ወይም ልገሳዎችን ስሙ ካልተገለፀ ሰው
ወይም ተቋም አለመቀበል ፣ በክበቡ የተገዙ ወይም በድጋፍ፣ በልገሳ ወይም
በሌላ ማናቸውም አግባብ የተገኙ ቋሚ ቁሳቁሶችን ወይም ንብረቶችን
ለአስፈፃሚው መ/ቤት በፅሁፍ ዘርዝሮ የማሳወቅ፣
16.ክበቡ ሲፈርስ ማናቸውንም ዓይነት የክበቡን ቋሚ ንብረቶችና የሠነድ
ማስረጃዎች ለአስፈፃሚው መሥሪያ ቤት የማስረከብ ኃላፊነትና ግዴታ
አለባቸው፡፡
21
አስፈፃሚው መ/ቤት ለማንኛውም ክበብ የሚከተሉትን ድጋፍና ክትትል
ማድረግ አለበት ፡-
22
እንዲንቀሳቀሱ ወይም ከፍተኛ ትምህርት እንዲቀጥሉ መደገፍ፣
ማበረታታት፣ አስፈላጊ ሁኔታዎችን የማመቻቸት፣
9. በዚህ አንቀፅ ከላይ ከንዑሥ አንቀፅ 1 እስከ 6 የተዘረዘሩት ድጋፎች፣
ያሉትን ክበባት በሙሉ ፍትሐዊ በሆነ መንገድ በሚያስተናግድ፣ ቀጣይነት
ባለው ሁኔታ የተዘጋጀ ቋሚ ፕሮግራም ወጥቶለት፣ በቼክ ሊስት ተደገፈና
ግብረመልስ በመቀበል መሰጠት አለበት፣
10. ማንኛውም ክበብ ሕጋዊ ፍቃድ ማውጣቱን፣ ፍቃዱ በወቅቱ
መታደሱን፣ በተፈቀደለት የሙያ ዘርፍ እየተሠራ መሆን ፣ ዕድሜያቸው
26 የሞላቸው አባላቱን በክብር ማሰናበቱንና ሌሎች አግባብነት ያላቸው
ጉዳዮችን በሚመለከት በየጊዜው ክትትልና ቁጥጥር በማካሄድ ፍተሻ
ያደርጋል፣
11. በሕግ አግባብ ፍቃድ ሳያወጡና በዚህ መመሪያ
መሠረት የማይሰሩ አካላት በመቆጣጠርና ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ
ያደርጋል፣
23
ሀ/ ውህደቱን የሚፈፅሙት ሁለት ክበባት ጠቅላላ ጉባዔ አባላት
የተገኙበት የውህደት ስምምነት መፈፀሚያ ጉባኤ ወይም የጋራ
ስብሰባ ማካሄድ፣
24
2. የሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት የሚታደሰው ክበቡ በዚህ
መመሪያ መሠረት መንቀሳቀሱ፣ በዓመቱ ውስጥ አጥጋቢ እንቅስቃሴ
ማድረጉና በእንቅስቃሴው መቀጠል ያለበት መሆኑ በአስፈፃሚው መሥሪያ
ቤት ሲታመንበት ብቻ ነው፡፡
25
ክፍል ሶስት
የባህል ቡድን አስፈላጊነት፤ የአመሠራረት መርህ ፤
ተልዕኮና ዓላማ፤ ተግባርና ኃላፊነት፤ አደረጃጀት እና አስተዳደር
2. ዓላማዎች
ሀ/ የካባቢውን ሕዝብ ያልተበረዘና ያልተከለሠ ባህላዊ የሙዚቃ
ትውፊቶች ማስተዋወቅ ፣
27
መ/ ለአካባቢው ሕብረተሰብና ቱሪስቶች ደረጃውን የጠበቀ የኪነ ጥበብ
መዝናኛ መድረክ መፍጠር፤
28
ብቃት ያላቸው ሙዚቃዎችን ፤ መዝሙሮችን፣ አጫጭር ጭውውት
ድራማዎችን፣ ሙዚቃዊ ተውኔቶችንና ክሊፖችን በማዘጋጀት ማቅረብ ፤
5. መጤ የባህል ወረራን፣ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችና አሠራሮችንና ፀረ ልማት
አስተሳሰብና አመለካከቶችን እያዝናኑ በማስተማር የሚያስወግዱና
ሁለንተናዊ ልማት ለማፋጠን የሚረዱ፣ የገፅታዋን የሚገነቡ ዝግጅቶችን
ማዘጋጀትና ማቅረብ፤
6. ለከተማዋ የውጪና የሐገር ውስጥ ቱሪስቶቿ ደረጃውን የጠበቀ፣ የክልሉን
ሕዝቦች ባህል በተሟላ አግባብ የሚያስተዋውቅ የኪነ ጥበብ መዝናኛ
መድረክ ማቅረብና የቱሪዝም እንቅስቃሴዋን ማጎልበት፣
7. በከተማዋ ክፍለ ከተሞች ለሚገኙ አማተር የኪነ-ጥበባት ቡድኖች
ሥራዎቻቸው መድረክ የሚየገኙበትን ሁኔታ ማመቻቸት ፤ ሥልጠና፣
የሙያ እገዛ በማድረግ ማበረታታትና መደገፍ፤ በከተማዋ የኪነ-ጥበብ
የፈጠራ እንቅስቃሴ እንዲጎለብት የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መፍጠር፣
8. በከተማዋ የኪነ ጥበብ ፍላጎትና ተሰጥኦ ላላቸውና ስልጠና ለሚፈልጉ
በባህል ሙዚቃ ፤ በውዝዋዜና በተለያዩ የመድረክ ኪነ ጥበባት ሙያ
ሥልጠና መስጠት ፤ ለዚህም ተገቢውን የአገልግሎት ዋጋ ማስከፈል፤
9. መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር ቅንጅታዊ አሰራር
በማጠናከርና ወጪን የሚሸፍኑ ስፖንሰሮችን በማፈላለግ ትርኢቶችን
ማቅረብ፡
10. የተዘጋጁ ትርኢቶችን በአውዶቪዥዋል በማሳተምና በማሰራጨት ሰፊ
ተደራሲ እንዲያገኙ የገቢ ምንጭ ማስቻል በፌስቲቫሎች ማቅረብ
11. የአገልግሎት ገቢ ምንጭና አሰባሰብን ማሳደግ የስፖንሰር
የማስታወቂያ ፕሮሞሽንና ሌሎች የገቢ ምንጮችን ማስፋት” ፕሮጀክት
ፕሮፖዛሎችን በማዘጋጀት ሀብት ማፈላለግ ለተልዕኮ ማዋል፣
29
18. የባህል ቡድን አደረጃጀት
31
ረ/ በዞኑ የባህል ተቆርቋሪና ታዋቂ የሆኑ ሁለት የሐገር ሽማግሌዎች
አባል
32
ሰ/ የከተማ አስተዳደሩ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን መምሪያ የመምሪያ
ኃላፊ አባል
ሰብሳቢ፣
ሀ. በአስፈፃሚው መሥሪያ ቤት አቅረቢነት የቦርዱን አባላት
ይሰይማል፣
ለ. ከፀሀፊው ጋር በመሆን አጀንዳዎችን ያዘጋጃል፣ የቦርዱን
ስብሰባዎች ይጠራል፤ ስብሰባውን በሊቀመንበርነት ይመራል፣
33
ምክትል ሰብሳቢ
ሀ. ሰብሳቢው በማይኖርበት ጊዜ ተክቶ ይሠራል፣
ለ. በሰብሳቢው ወይም በቦርዱ የሚሰጡ ሌሎች ስራዎች ያከናውናል፣
ፀሐፊ
ሀ. ከሰብሳቢው ጋር በመሆን ለቦርዱ ስብሰባ አጀንዳዎችን ያዘጋጃል፣
ለ. የቦርዱን የስብሰባ ቃለ ጉብኤ ይይዛል፣
ሐ. በሰብሳቢው ወይም በቦርዱ የሚሰጡ ሌሎች ስራዎች
ያከናውናል፣
7. በየደረጃው የሚደራጀው የባህል ቡድን የበላይ ጠባቂ ቦርድ የሚከተሉት
ስልጣንና ተግባራት ይኖሩታል፡-
34
መርምሮ ያፀድቃል፣ እንዲተገበሩ ያመቻቻል፣ አፈፃፀማቸውን
ይከታተላል፣
35
ሀ. በበጀት ዓመቱ ውስጥ ቦርዱ አራት መደበኛ ስብሰባ ያካሂዳል፣
መደበኛ ስብሰባው በሰብሳቢው ጠሪነት የበጀት ዓመቱ ሩብ ዓመት
ከተዘጋ በኋላ ባሉት 10 ቀናት ውስጥ መካሄድ ይኖርበታል፣
37
8. የባህል ቡድኑን የሰው ኃይል አደረጃጀትና አስተዳደር በዚህ መመሪያ
በተደነገገው መሠረት እንዲተገበር ያደርጋል፣ ድጋፍ ይሰጣል፣ ክትትልና
ቁጥጥር በማድረግ ተፈፃሚ እንዲሆን ያደርጋል፣
9. በየጊዜው የባህል ቡድን መንግሥስታዊና መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች
ከግለሰቦች የማተሪያልና የፋይናንስ ድጋፍ እንዲያገኝ ስልቶችን ይቀይሳል፣
ይተገብራል፣ አስፈላጊ ሁኔታዎችን ያመቻቻል፣
10. በቦርዱ የሚሰጡትን እና ከባህል ሙዚቃ ቡድኑ ጋር ግንኙነት ያላቸውን
ሌሎች ሕጋዊያን ተግባራት ያከናውናል፡፡
38
ሠ. ከሶስተኛ ወገኖች ጋር በሚደረጉ ግንኙነቶች የባህል ሙዚቃ ቡድኑን
ይወክላል፤
39
ሕብረተሰብ ባህላዊ አልባሳቶች፣ ጌጣጌጦች፣ የወግ ዕቃዎችና
ቁሳቁሶች ፣
40
1. በሁሉም ደረጃ ለሚቋቋሙ የባህል ቡድኖች በየዕለቱ ኪነ ጥበባዊ ስራቸውን
የሚያከናውንበት፣ የሚያቀርብበትና የተለያዩ የገቢ ምንጭ ማስገኛ
ተግባራትን የሚፈፅሙበት አዳራሽና ተጓዳኝ ክፍሎችን ያካተተ በአማካኝ
ሥፍራ ላይ የሚገኝ የመሥሪያ ቦታ እንዲኖራቸው መደረግ አለበት፣
2. በዚህ አንቀፅ ከላይ በንዑስ አንቀፅ 1 የተገለፀው አጠቃላይ ድንጋጌ
እንደተጠበቀ ሆኖ ፡-
ሀ/ በወረዳ ደረጃ ለተቋቋሙና ለሚቋቋሙ የባህል ቡድኖች በወረዳው
ርዕሠ ከተማ የሚገኝና በሌላ መመሪያ ወደ መሥሪያ ቤቱ
እንዲዛወር የተደረገ የሕዝብ መሰብሰቢያ አዳራሽ ለቡድኑ
የመሥሪያ ቦታ እንዲሆን መደረግ አለበት፣
ለ/ በዞን ደረጃ ለተቋቋሙና ለሚቋቋሙ የባህል ቡድኖች በሚመለከት
በከተማው አማካይ ስፍራ የመሥሪያ ቦታ የሚያገኙበት ሁኔታ
በበላይ ጠባቂ ቦርድ እንዲወሰን አስፈፃሚው መ/ቤት ያመቻቻል፣
ተግባራዊ ያደርጋል፣
ሐ/ በከተማ አስተዳደር ደረጃ ለሚቋቋሙ የባህል ቡድኖች በከተማ
አስተዳደሩ በሚገኝ የሲኒማ አዳራሽን ከሲኒማው አስተዳደር ጋር
በመቀናጀት የሚጠቀሙበትን ሁኔታ አስፈፃሚው መ/ቤት አጥንቶ
ለቦርዱ በማቅረብ ተፈፃሚ እንዲሆና ያደርጋል፣
41
ሙሉ በሙሉ ማሟላቱን አረጋግጦ የሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር
ወረቀት ይሰጣል፣
3. በየደረጃው በአስፈፃሚው መ/ቤት የሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር
ወረቀት የተሰጠው የባህል ቡድን የራሱ አርማና ማሕተም፣ የባንክ
አካውንት ሊኖረውና በመመሪያው መሠረት መንቀሳቀስ ይችላል፣
42
ለ/ ፕሮፖዛል ቀርፆ የፋይናንስና የማቴሪያል ድጋፍ ከመንግስታዊና
መንግሥታዊ ካልሆኑ ተቋማት በማፈላለግ እያዝናኑ መልዕት
የሚያስተላልፉ ትርኢቶችን አዘጋጅቶ በማሳየት፣
ሐ/ በተለያዩ ተቋማት በሚዘጋጁ የስብሰባና መሰል መድረኮች፣
በሠርግ ሥነ ሥርዓትና መሠል ማህበራዊ ሁነቶች በተመጣጣኝ
ክፍያ ትርኢቶችን በማቅረብ፣
መ/ የአካባቢውን ትውፊታዊ የሙዚቃ ባህልንና አጨዋወትን፣
አጫጭር ሙዚቃዊ ድራማ ጭውውት ሥራዎችን በሲዲና
በካሴት በማሳተምና ለሽያጭ በማቅረብ፣
3. ከሚሰጠው አገልግሎት ከሚሰበሰብ ገቢ በተጨማሪ የገቢ ማስገኛ
አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን በማቋቋም ገቢ መሰብሰብ አለበት፣ ለዚህም
አስፈፃሚው መ/ቤት ከቡድኑ ጋር በመቀናጀት የአካባቢውን ተጨባጭ
ምቹ ነባራዊ ሁኔታዎችን ያተገናዘበ የቢዝነስ እቅድ አዘጋጅቶ ለቦርዱ
አቅርቦ የማፀደቅና መነሻ ካፒታል የማስፈቀድ ተግባር ያከናውናል፣
4. ከላይ በንዑሥ አንቀፅ 3 በተገለፀው አግባብ ሊከናወኑ ከሚችሉ የገቢ
ማስገኛ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ዓይነቶችን በሚመለከት፡-
ሀ/ የተለያዩ ባህላዊ ምግብና መጠጦች አቅርቦቶችን ያካተተ የባህል
ምሽት ቤት መዝናኛ አገልግሎት፣
ለ/ የዲኤስ ቲቪ የእግር ኳስ ፊልምና ሌሎች ፊልሞችን ከፊልም
ሠሪዎች ጋር በመዋዋል በቋሚ ፕሮግራም ማሳየት፣
ሐ/ የባህል ውዝዋዜ እና የባህል ሙዚቃ መሣሪያዎች /ክራርና
መሰንቆ/ ማሰልጠኛ አገልግሎት፣
መ/ የአካባቢው የባህል ወግ ዕቃዎች፣ ባህላዊ ጌጣጌጦችና አልባሳት
መሸጫ ሱቅ፣
ሠ/ ፑል፣ ካራምቦላ፣ ጆቶኒና የመሳሰሉ የቤት ውስጥ የስፖርት
መዝናኛ አገልግሎት፣
43
ረ/ ለስብሰባና መሰል ዝግጅቶች የአዳራሽ ኪራይ አገልግሎት
መስጠት፣
ሰ/ እና ሌሎች በአካባቢው አዋጪ የሆኑ ተመሳሳይ አገልግሎቶች
ሊሆኑ ይችላሉ፣
5. በዚህ አንቀፅ ከላይ በንዑሥ አንቀፅ 3 እና 4 ላይ ለተደነገጉት ተፈፃሚነት
44
ሰ/ ከቡድኑ መደበኛ ሪፖርት በተለየ የገቢ ማስገኛ ስራውን የገንዘብ
እንቅስቃሴ ሊያሳይ የሚችል አመታዊ የኦዲት ሪፖርት ማዘጋጀት
ለቦርዱ ማቅረብ፣
6. ከዚህ በፊት የንግድ ፈቃድ አውጥተው የንግድ ስራ በማከናወን ላይ ያሉ
45
ረ/ የቡድኑ የባንክ አካውንቶችና የገቢ መሰብሰቢያ ደረሰኞች በቦርዱ
ውሳኔ የሚከናወኑና በቦርዱ በግልፅ የሚታወቁ መሆን አለባቸው፣
46
7. የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 6 ቢኖርም ቦርዱ በሚያወጣው መመሪያ
መሰረት ማንኛውም ዓይነት የቡድኑ የሂሳብ ምርመራ በማንኛውም ጊዜ
በውጭ ወይም በውስጥ በቦርዱ በሚሰየም ኦዲተር ሊመረመር ይችላል፣
8. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 6 እና 7 መሠረት በቦርዱ የተሰየመ ኦዲተር
ለሚገኝ ማናቸውም ስህተቶች ጥፋተኛና ተጠያቂዎቹ ሒሳቡን
የሚያንቀሳቅሱት የሥራ መሪዎቹና ሠራተኞች ይሆናሉ፣
9. የሥራ መሪዎቹ የበጀት ዓመት የፋይናን ክንዋኔዎች ሪፖርትና አስፈላጊ
መረጃ በማዘጋጀት ለቦርዱ ማቅረብ አለባቸው፣ የተመለከተው ሪፖርት
የሂሣብ ዓመቱ ባለቀ ጊዜ ውስጥ እንዲሁም ቦርዱ በማናቸውም ልዩ
ምክንያት በሚጠይቅበት ጊዜ ውስጥ ማቅረብ አለባቸው፣
10. በዚህ አንቀፅ ከላይ በንዑስ አንቀፅ 3 እና 4 የተጠቀሱትን ድጋፍ
ሰጪ ሠራተኞችን ቡድኑ እስኪያሟላ ድረስ የሚያከናውኑት ተግባር
ለቦርዱ በማስወሰን የአስፈፃሚውን መ/ቤት በጀት በሚያንቀሳቅሱ የፋይናንስ
ድጋፍ ሰጪ ሠራተኖች ይከናወናል፣
47
መ/ ደረጃ አንድ ወንድና ሴት ተወዛዋዦች፣ ገንዘብ ያዥ፣ የሒሳብ
ሠራተኛ፣
48
1. በማንኛውም የባህል ቡድን የሥራ መደብ ላይ የሚፈፀም የሰው ኃይል
የቅጥር ዓይነት ዘላቂነት የሌለው ወይም የኮንትራት ቅጥር ሆኖ የሚፈፀም
ነው፣
2. የማንኛውም የባህል ቡድን የሰው ኃይል ምልመላ፣ መረጣና ቅጥር
የሚካሄደው ባለቤቱ በሆነው አስፈፃሚ መ/ቤት ሲሆን ቅጥሩ ተግባራዊ
የሚሆነው ለበላይ ጠባቂ ቦርድ ቀርቦ በቦርዱ ውሳኔ ሲፀድቅ ብቻ ይሆናል፣
3. አስፈፃሚው መ/ቤት ክፍት የሥራ መደቦችን በሠራተኛ ማስያዝ የሚችለው
በቅጥር ወይም በዝውውር ወይም በደረጃ ዕድገት ሲሆን ማስታወቂያ
ማውጣት አመልካቾችን መጋበዝ በፈተና ማወዳደርና የሥራ መደቡ
የሚጠይቀውን ተፈላጊ ችሎታ አሟልቶ በውድድሩ ብልጫ ያገኘውን
በመምረጥ ብቻ ነው፣
4. የክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ አወጣጥ፣ አመልካቾች አመዘጋገብ፣
የፈተና አዘገጀጀት፣ የፈተና አሰጣጥና ውጤት አገላለጽ የመንግሥት
ሠራተኞች የቅጥር አፈፃፀም መመሪያን በተከተለ አግባብ የሚፈፀም
እንዲሆን በአስፈፃሚው መ/ቤት መደረግ አለበት፣
5. በክፍት የሥራ መደብ ለመቀጠር የማያስችሉ ሁኔታዎች ዕድሜ ከ18
ዓመት በታች መሆን፣ ወንጀል ፈፅሞ ስልጣን ባለው ፍርድ ቤት
የተፈረደበት መሆንና ከሌላ የባህል ቡድን በዲሲኘሊን ጉድለት ከሥራ
ተሰናብቶ ከተሰናበተ ሁለት ዓመት ያልሞላው ሆኖ መገኘት ብቻ ሲሆኑ
በሌላ በማንውም ሁኔታ በሥራ ፈላጊ ተወዳዳሪዎች መካከል ልዩነት
ማድረግ ክልክል ነው፣
6. ለክፍት የሥራ መደቡ በውድድር ብልጫ የተመረጠው ተወዳዳሪ የሥራ
ልምድ፣ የትምህርት፣ ከወንጀሎች ነፃ መሆኑን የሚያረጋግጥ የፖሊስ
ማስረጃና ሌሎች አስፈላጊ ማስረጃዎችን የማቅረብ ግዴታ አለበት፣ በሃሰተኛ
ማስረጃ ቅጥር መፈፀም ወይም እንዲፈፀም ማድረግ ክልክል ነው፣
49
7. የክፍት የስራ መደቡ ምደባ በቦርዱ ከፀደቀ ለተመረጠው እጩ የሥራ
መደቡን መጠሪያ፣ የኮንትራት ቅጥር መሆኑን፣ የተመደበበትን ደረጃ፣
ደመወዙንና ሥራውን የሚጀምርበትን ቀን የሚገልፅ በባህል ቡድኑ ኃላፊ
የተፈረመ የቅጥር ደብዳቤ ከሚያከናውነው የሥራ ዝርዝር መግለጫ ጋር
መሰጠት አለበት፣
8. በአንድ የባህል ቡድን ውስጥ ተፈላጊ ችሎታውን እስካሟሉ ድረስ ከዝቅተኛ
የሥራ ወደ ከፍተኛ የሥራ መደብ ሰራተኞችን በደረጃ ዕድገት አወዳድሮ
መመደብ ይቻላል፣ ነገር ግን ምደባው ማስታወቂያ ወጥቶ ተወዳዳሪዎችን
በመጋበዝ፣ በማወዳደርና ብልጫ ያላቸውን በመምረጥ የሚፈፀም ነው፣
9. አስፈፃው መሥሪያ ቤት ለሥራው አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው ከሌላ የባህል
ቡድን ባለሙያን በተመሳሳይ የሥራ መደብ ላይ በዝውውር ተቀብሎ
በመመደብ ማሠራት ይችላል፣ ነገር ግን በዝውውሩ ላኪው የባህል ቡድን
እንዲሁም ሠራተኛው ስምምነታቸውን በጽሁፍ መግለፅና ማሳወቅ
አለባቸው፣
51
ያልተሰጠበትን በፈቃድ ላይ እያለ የተከፈለውን ደመወዝ እንዲመልስ
ይደረጋል፣
6. ለማንኛዋም ነፍሰጡር የሆነች የባህል ቡድን ባለሙያ እወልዳለሁ ብላ
ከገመተችበት ቀን በፊት 3ዐ ተከታታይ ቀናት የቅድመ ወሊድና
ከወለደችበት ቀን ጀምሮ 30 ተከታታይ ቀናት የድህረ ወሊድ በድምሩ 60
ቀናት ደመወዝ የሚከፈልበት ፈቃድ ይሰጣታል፣ እንዲሁም የተወሰነውን
የወሊድ ፈቃድ ከጨረሰች በኋላ ብትታመምና ተጨማሪ ፈቃድ
የሚያስፈልጋት መሆኑ በሐኪም ከተረጋገጠ የሕመም ፈቃድ መውሰድ
ትችላለች፣
7. ማንኛውም የባህል ቡድን ባለሙያ በሕመም ምክንያት ሥራ መሥራት
ያልቻለ እንደሆነና መታመሙን ለኃላፊው ካሳወቀ የሕመም ፈቃድ
ይሰጠዋል፣ ይሁን እንጂ ከስድስት ቀን በላይ በሕመሙ ምክንያት ከሥራ
የቀረ እንደሆነ ለመታመሙ የሕክምና ማስረጃ ማቅረብ አለበት፣
8. ከላይ በንዑስ አንቀጽ 7 የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ ባለሙያው ህመሙ
ጠንቶበት በሐኪም ትእዛዝ ከወር በላይ በህክምና ላይ ከቆየ ለመጀመሪያው
አንድ ወር ከሙሉ ደመወዝ ጋር፣ ለሚቀጥሉት ሁለት ወራት ከግማሽ
ደመወዝ ጋር እና ለመጨረሻው አንድ ወር ያለ ደመወዝ የሕመም ፈቃድ
ይሰጠዋል፣
9. ማንኛውም የባህል ቡድን ባለሙያ ለሐዘን፣ ለጋብቻ፣ ለፈተና እና
ለመሳሰሉት በአንድ የበጀት ዓመት ውስጥ የአምስት ቀን ፈቃድ እንዲሁም
ከፍርድ ቤት መጥሪያ ሲደርሰው የተጠራበት ጉዳይ ለሚጠይቀው ጊዜ
ደመወዝ ሚከፈልበት ፈቃድ ይሰጠዋል፣
52
1. ማንኛውም የባህል ቡድን ባለሙያ የሚከተሉትን ..የሙያ ሥነግባሮች
የመተበቅ ኃላፊነትና ተግባራዊ የማድረግ ግዴታዎች አሉበት፡-
ሀ/ ለባህል ቡድኑ ታማኝ የመሆን፣ መላ ጉልበቱንና ኪነ ጥበባዊ
የፈጠራ ችሎታውን ለቡድኑ አገልግሎት ማዋል፣
ለ/ በሥራ ዝርዝሩ መሠረት የሚሰጡትን የሥራ እቅዶች እና ሌሎች
ከሥራው ጋር አግባብ ያላቸው የሚሰጡትን ትዕዛዞች መፈፀም፣
ሐ/ ከባህል ቡድን ባልደረቦቹ ጋር ተግባብቶ የመሥራትና
በማንኛውም የቡድን ተግባር ላይ የነቃ ተሳትፎ የማድረግ፣
መ/ የአካባቢውን ሕብረተሰብ፣ የክልሉን ብሄር፣ ብሔረሰቦችና
ሕዝቦች ባህሎች፣ ቅርሶች፣ ቋንቋዎች፣ ታሪኮች እና ሕጎች
የሚፃረር ድርጊት ያለመፈጸም፣
ሠ/ የቡድኑን ሥራ የሚመለከቱ በበላይ ጠባቂ ቦርድና በአስፈፃሚው
መ/ቤት የሚወሰኑና የሚተላለፉ ውሳኔዎችን፣ ደንቦችና
መመሪያዎችን ማክበር፣ በብቃት መፈፀም አለበት፡
ረ/ ማንኛውንም የቡድኑን የጋራ ንብረት ደህንነት የመንከባከብ
የመጠበቅ፣ ለሥራው ማከናወኛ የተሰጡትን የግል መሣሪያዎችና
መገልገያዎች በአግባቡ የመጠበቅና የመጠቀም ኃላፊነት አለበት፣
ሰ/ በማንኛውም የቡድኑ ንብረትና ለሥራው ማከናወኛ በተሰጡት
መሣሪያዎችና መገልገያዎች ላይ በቸልተኝነት ወይም ሆን ተብሎ
በሚፈፀመው ጉዳት ወይም ጥፋት በዕዳ ተጠያቂ የመሆንና
የመተካት ግዴታ አለበት፣
2. ከላይ በንዑስ አንቀፅ 1 ላይ የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ አስፈፃሚው
መሥሪ ቤት ከባህል ቡድን ኃላፊ ጋር በመሆን ባለሙያዎች
የሚተዳደሩበትን፣ ከአካባቢውና ከሙያው ሁኔታጋር በተገናዘበ አግባብ
ዝርዝር የሥነ-ሥግባር ደንብ በማውጣት በበላይ ጠባቂ ቦርድ አፀድቆ
ተግባራዊ ማድረግ ይችላል፣
53
33. የዲሲኘሊን ጥፋት እርምጃዎችና የቅሬታ አቀራረብ
54
ሰ/ በሥራ ቦታ በጠብ አጫሪነት መደባደብ፣ በልማዳዊ ስካር ወይም
በአደንዛዥ ዕፅ ሱስ በመመረዝ ሥራን መበደል፣
ሸ/ ጉቦ መቀበል ወይም እንዲሰጠው መጠየቅ ፣ የማታለል ወይም
የማጭበርበር ድርጊት መፈፀም ፣በቡድኑ ውስጥ ወይም በሌላ
የሌብነት ወይም የእምነት ማጉደል ድርጊት መፈፀም ፣
ቀ/ በቡድኑ የጋራ ንብረት ላይ ወይም ለግል መገልገያ በተሰጠ
ንብረት ላይ ሆን ብሎ ወይም በቸልተኝነት ጉዳት ማድረግ ፣
በ/ ኃላፊነትን ወይም የሥራ ድርሻን አለአግባብ መጠቀም በሴቶች
ወይም በሌላ ባልደረባ ተፅኖ መፍጠር፣
ተ/ የሴሰኝነት ወይም በሥራ ቦታና ባልደረቦች ላይ ፆታዊ ጥቃት
መፈፀም ፣
ቸ/ በዚህ አንቀፅ ከተዘረዘሩት ጋር ተመሳሳይ ክብደት ያለው ሌላ
የዲሲኘሊን ጉድለት መፈፀም፡፡
3. ከላይ በንዑስ አንቀፅ 2 የተዘረዘሩንና መሰል የዲሲኘሊን ጉድለቶችን የፈፀመ
ማንኛውም የባህል ቡድን ባለሙያ እንደጥፋቱ ክብደት ተመዝኖ
ከሚከተሉት ቅጣቶች አንዱ ሊወሰንበት ይችላል ፣
55
ለ/ ከባድ የዲሲኘሊን ቅጣት ከሆነ ቅጣቱ ከተወሰነበት ቀን ጀምሮ
ለሁለት ዓመት፣ ይሆናል፡፡
56
34. የሥራ አፈፃፀም ምዘናና የሥልጠና ሁኔታ
57
35. የሥራ ውል መቋረጥ ወይም ከሥራ መሰናበት
58
ከአጥጋቢ በታች መሆኑ ሲረጋገጥ እና ስልጠና እንዲወስድ ተደርጎ በድጋሜ
ውጤታማ መሆን ከተሳነውና ቀርቦ በቦርዱ ሲወሰን ብቻ ነው፣
60
ክፍል አራት
61
በየደረጃው በመቋቋም የሚንቀሳቀሱና ተቋቁመው ሊንቀሳቀሱ የሚችሉት
የኪነ ጥበብ የሙያ ዘርፎች ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ዓይነቶች
ቀጥሎ የተዘረዘሩት ይሆናሉ ፡-
1) የሙዚቃ /የፊልም፣ የትያትር እና ሌሎች የኪነጥበብ/መሣሪያዎች
መፈብረክ /ማምረት/ 39220
2) የሙዚቃ /የፊልም የቲያትር እና ሌሎች ኪነጥበብ/መሳሪያዎች
የጅምላ ንግድ 61332
3) የተቀዱ /ኦሪጅናል/ ካሴቶችና ሲዲዎች ቪሲዲ እና ዲቪዲዎች
የጅምላ ንግድ 61335
4) የሙዚቃ /የፊልም የቲያትር እና ሌሎች ኪነጥበብ/መሳሪያዎች
የችርቻሮ ንግድ 62396
5) የተቀዱ /ኦሪጂናል/ ካሴቶች ሲደወችና ቪሲዲዎች እና ተዛማጅ
ምርቶች የችርቻሮ ንግድ 61335
6) የሙዚቃ መሣሪያዎች አስመጭ /የሙዚቃና የፊልም የትያትር
እና ሌሎች የኪነጥበብ/ 65332
7) የተቀዱ /ኦሪጂናል/ ካሴቶች ሲደዎችና ቪሲዲዎች እና ተዛማጅ
ምርቶች አስመጭ 65333
8) የሙዚቃና መሣሪያዎች ላኪ /የሙዚቃና የፊልም የትያትር እና
ሌሎች የኪነጥበብ/ 66232
9) የተቀዱ /ኦሪጂናል/ ካሴቶች ሲዲወች ቪሲዲና ዲቪዲዎች ላኪ
10) የባህል እና የኪነጥበብ ኮንሰልታንሲ/ የማማከር አገልግሎት
8815
11) የባህልና ኪነጥበብ ትምህርት ትያትር፣ ሙዚቃ፣ፊልም፣
ሞዴሌንግ፣ ዳንስ/ውዝዋዜ፣ የቪዲየና ፎቶግራፍ፣ የስዕልና ደዛይን
ወዘተ ሠርከስ ት/ቤት 9222
62
12) ተንቀሳቃሽ የቴአትርና የቪዲዮ ፊልም ሥራና ማከፋፈል
96111
13) ተዛማጅ ሥራዎች የፊልምና የካሴት ክር ለሌሎች
ኢንዱስትሪዎች ማከራየት፣ ፕሮግራም ማስያዝ መስጠትና
ማከማቸት 96112
14) የፊልም ሥራ ዝግጅት፣ የፊልም ፕሮዳክሽን ፣ ሲኒማ ቤት
፣ የፊልም ስቱዲዮ፣ የፊልም ቀረጻ 96113
15) የትያትር ሥራ ፣ ትያትር ቤት፣ የትያትር ፕሮዳክሽን 96114
16) ሌሎች ሌላ ቦታ ያልተጠቀሱ የተንቀሳቃሽ ፊልም ፊልም
የቪዲዮ ቀረፃና ማከፋፈል፣ የድምጽና የምስል ፕሮዳክሽን ስርጭት
/የሬድዮና ቴሌቪዥን ተዛማጅ የኪነጥበብ ስራዎች/96119
17) የፊልምና ቴአትር /ሲኒማ በአዳራሽ ማሳየት ስራዎች 96121
18) በግቢ ውስጥ የሲኒማ የማሳየት ስራ በመኪና በሌላ መንገድ
96122
19) የድራማ የሙዚቃና እና ሌሎች ተዛማጅ የኪነጥበብ ሥራዎች
የፕሮሞሽን አገልግሎቶች /የትያትር፣ ስነጽሁፍ፣ የሙዚቃ፣
ፊልም፣ የስዕልና ቅርፃቅርጽ ወዘተ/96140
20) የሙዚቃ ባንድ ፣ ሚኒ ባሕላዊ ባንድ ፣ መለስተኛ ባሕላዊ
ባንድ፣ ሁለገብ ባሕላዊ ባንድ 96141
21) ሙዚቃ መሣሪያ ኪራይ /የሙዚቃ፣ የፊልም የትያትር ሌሎች
የኪነጥበብ መሣሪያዎችን ማከራየት፣ ፕሮግራም ማስያዝ፣
መስጠትና ማከማቸት ስራ 96142
22) የሙዚቃ መሣሪያ አጫዋች /ዲ²/96143
23) ቀረጻ ስቱዲዮ የሙዚቃ 96144
24) የስዕልና ቅርፃ ቅርጽ ጋለሪ 96145
25) የስዕልና ቅርፃ ቅርጽ ስቱደዮ 96146
63
26) ሌሎች የማዝናናት ስራዎች ልዩ ዝግጅት ማስተባበር
(Eventorganizer)ፌስቲቫሎች ኤግዚቪሽን ኮንፍረንሶች 96190
27) የባህል ማዕከል 96323
28) የፋሽንና የቁንጅና ትርኢት ስራዎች 99028
64
5. እንቅስቃሴያቸው በዞን፣ በወረዳ እና በከተማ አስተዳደር ደረጃ በመሆን
65
ለ/ ባላቸው እውቀት የተፈጥሮ ክህሎትና ሙያዊ ተሞክሮ
ኢንተርፕራይዝ መሥርተው ቢንቀሳቀሱ ውጤታማ የሚሆኑ
አካላትንና ሊሠማሩ ሚችሉባቸውን የሙያ ዘርፎች በመለየት
የዘርፉን የገበያ አዋጭነትና የገበያ አማራጮችን አስመልክቶ በቂ
ዕውቀት እንዲያገኙ የግንዛቤ ማስጨበጫ የጋራና የተናጥል
መድረኮችን በማመቻቸት ግንዛቤ ማስጨበጥ፡
66
ዘርፎች ላይ የመሰማራት ወይም የወሰደውን የሙያ ፈቃድ የመመለስ
መብት፣
4. የክልሉን የንግድ ምዝገባና የንግድ ሥራ ፈቃድ ህጎችን፣ በአስፈፃሚው
መ/ቤት በኪነ ጥበባት ዙሪያ የወጡና የሚወጡ መመሪያዎችን በአግባቡ
አውቆ ማክበርና ለማስከበር በመንቀሳቀስ መሥራት፣
5. የሙያ ፈቃድ በተሰጠው የስራ ዘርፍና እንዲሠራ በተፈቀደለት ቦታ ወይም
ክልል ውስጥ ብቻ መስራትና በየአመቱ የአገልግሎት ሙያ ብቃት
ማረጋገጫ መስፈርት የምስክር ወረቀቱን እና የንግድ ምዝገባና የንግድ
ሥራ ፈቃዱን በተቀመጠው የጊዜ ገደብ የማሳደስ ግዴታ አለበት፣
6. የአድራሻ ለውጥ ወይም በሚሰራው ስራ ላይ ማንኛውንም ለውጥ ካደረገ
ለውጡን ካተደረገበት ቀን ጀምሮ ባሉ 15 ቀናት ውስጥ ፍቃዱን ለሰጠው
አስፈፃሚ መ/ቤት ማስታወቅ አለበት፣
7. የተሰጠውን የአገልግሎት ሙያ ብቃት ማረጋገጫ መስፈርት የምስክር
ወረቀትና የንግድ ምዝገባና የንግድ ሥራ ፈቃዱን በሥራ ቦታው
ለማንኛውም አካል በግልፅ ሊታይ በሚችል ሁኔታ መስቀል ወይም
ማስቀመጥ ይኖርበታል፣
8. የሕብረተሰቡን ባህል፣ ታሪክና ሕጎች የሚፃረር ድርጊት ያለመፈጸም፣
በሕገ-ወጥ ሥራ ከተሰማሩ ግለሰቦች ወይም ድርጅቶች ጋር ያለመስራት፣
ያለማበር፣ ያለባለቤቱ ፈቃድ የሌላውን ሰው የፈጠራ ስራ ያለመጠቀም፣
ስራውን ያለማባዛት፣ ያለማሰራጨት፣ ድርጊቱ በሌሎች ሲፈፀምም በወቅቱ
ለአስፈፃሚው መቤትና ለሚመለከተው አካል ሪፖርት የማድረግ ግዴታ
አለበት፣
9. በአስፈፃሚው መሥሪያ ቤት በማንኛውም ጊዜ ስለ ኢንተርፕራይዙ
እንቅስቃሴ መረጃ ሲጠየቅ በአግባቡ የመስጠት፣ መ/ቤቱ በሚያስተላልፈው
ቅጽ መሠረት መረጃ የመያዝና ሲጠየቅም የማቅረብ፣. የአስፈፃሚውን
67
መሥሪያ ቤት ጥሪ የመቀበልና በቀጠሮው ቀን ቀርቦ የመሳተፍ ግዴታ
አለበት፣
10. የአስፈፃሚውን መሥሪያ ቤት በሚያደርገው ክትትል የደረሰበትን
ጉድለቶችን እንዲያስተካክል የጽሁፍ ማስታወቂያ ሲደርሰው
በማስታወቂያው በተገለፀው የጊዜ ገደብ ውስጥ ጉድለቱን የማስተካከል፣
11. የፊልም ቀረፃ ለማካሄድ የቀረጻ ፈቃድ መያዝ አለበት፣ ያለ
አስፈፃሚው መሥሪያ ቤት እውቅና እና ፈቃድ ማናቸውም የኪነ-ጥበብ
ሥራዎችን በመድረክ፣ በሲኒማ፣ በDVD፣ በቪዲዮ፣ በሲዲ፣
ያለማሰራጨት፣
68
5. ከባለድርሻና አጋር አካላትን በማስተባበር የተለያዩ ፌስቲቫሎችን ኤግዚቢሽና
69
1. የአገልግሎት ሙያ ብቃት ማረጋገጫ መስፈርት የምሥክር ወረቀትና
የንግድ ሥራ ፈቃድ ከተሰጠበት ወይም የታደሰበት የበጀት ዓመት ካበቃ
በኋላ ባሉት 3 ወራት ጊዜ ውስጥ ከሀምሌ 1 እስከ መስከረም 3ዐ መታደስ
አለበት፣
2. አስፈፃሚው መ/ቤት በዚህ መመሪያ እና በአገልግሎት የሙያ ብቃት
መመሪያ የተቀመጡት መሥፈርቶች መሟላታቸውን ከገመገመ በኋላ
ጥያቄው የተሟላ ሆኖ ሲያገኘው በአንድ የሥራ ቀን ውስጥ የምሥክር
ወረቀቱን ያድሳል፣
3. ማንኛውም የኪነ ጥበብ ሙያ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ በዚህ
አንቀጽ ንዑስ አንቀፅ 1 በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ፈቃዱን ካላሳደሰ ፈቃዱ
ይሰረዛል፣
4. በንግድና ትራንስፖርት ቢሮ እና በየደረጃው ባሉት አስፈፃሚ አካላቶቹ
ማንኛውም በኪነ ጥበባት የሙያ ዘርፎች በጥቃቅንና አነስተኛ
ኢንተርፕራይዝ የንግድ ሥራ ፈቃድ እድሳት ሲጠይቅ በቅድሚያ የምስክር
ወረቀቱ በሰጠው አስፈፃሚው አካል መታደሱን ወይም ማሳደሱን
ሲያረጋግጥ ብቻ የንግድ ሥራ ፍቃድ እድሳት ይፈፅማል፣
70
ሐ/ የአገልግሎት ብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ ለመውሰድ ወይም ለማደስ
የተሳሳተ መረጃ ከሰጠ፣
መ/ በዚህ መመሪያ ውስጥ የተደነገጉትን ግዴታዎች በመጣስ ከህግ
ውጭ ሲሰራ ከተገኘ ይታገዳል፣
2. የማንኛውም ኢንተርፕራይዝ የአገልግሎት ብቃት ማረጋገጫ የምስክር
ወረቀትና የንግድ ስራ ፈቃድ በሚከተሉት ምክንያቶች ይሰዘራል፣
ክፍል አምስት
71
43. የኪነ ጥበባት ዘርፍ የሙያ ማህበራት ዓላማና ተግባራት
72
10. የሙያዉን የሥነ-ምግባር ደንቦች መመሪያዎች ማውጣት፣ በአባላትና
በሌሎች የሕብረተሰብ ክፍሎች ግንዛቤ እንዲጨበጥባቸው ማስቻል፣
እንዲጠበቁ ማድረግ፣
11. በተለያዩ ምክንያቶች ከባድ ማህበራዊ ችግር የሚገጥማቸውን የማህበሩን
73
ሐ/የደራሲያን ማኅበር
74
ሀ/ በሙ ማህበራት መደራጀት ስለሚያስገኘው ጠቀሜታ የተለያዩ
የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን ያዘጋጃል በቂ ግንዛቤ
ያስጨብጣል፣
ለ/ በየደረጃው በክልሉ የሚመሠረቱ የኪነ ጥበባት የሙ ማህበራትን
ይደግፋል፣ ያበረታታል፣
ሐ/ ስለ ኪነ ጥበባት ሙያ ማህበራት አመሠራረት ሒደቶች በቂ
ማብራሪያና መረጃ እንዲጨብጡ ያደርጋል፣
መ/ የሙያ ማህበራትን የመመሥረት፣ የመመዝገብና ፍቃድ
የመሥጠት ሥልጣን ለተሰጠው አካል ስለ መመስረታቸው
አግባብነትና የሙያው ባለቤት ስለመሆናቸው መረጃና መግለጫ
ይሠጣል፣ ድጋፍና ትብብር እንዲሰጣቸው ያደርጋል፣
77
11. በዘርፋቸዉ ባሉት ላሉት ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርኘራይዝ ዕድገት
ላይ በቀጥታ የመሳተፍ የማገዝና የመምራት ሚና የመጫወት፣
12. በማህበር የመደራጀትን ጠቀሜታና ለተደራሽነት ያለዉን ጉልህ
አስተዋጾ አዳዲስ በዘርፉ ለተሰማሩት ማስገንዘብ፣
13. በዘርፉ ከተደራጁ አቻ ማህበራትና ተቋማት ጋር ግንኙነትና የትብብር
ስምምነት በመፍጠር እንዲሁም ለሀገራዊ ትብብር በሚያግዙ በአጋርነት
በመሳተፍ ለዘርፉ ልማት የድርሻቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት፣
14. የአስፈፃሚውን መሥሪያ ቤት ጉድለቶችን እንዲያስተካክል የጽሁፍ
ማስታወቂያ ሲደርሰው በማስታወቂያው በተገለፀው የጊዜ ገደብ ውስጥ
ጉድለቱን የማስተካከል፣
15. በሕገ-ወጥ ሥራ ከተሰማሩ ግለሰቦች ወይም ድርጅቶች ጋር
ያለመስራት፣ ያለማበር
16. የክልሉን ሕዝብ ቅርስ፣ ባህል፣ ታሪክና ሕጎች የሚፃረር ድርጊት
ያለመፈጸም፣ በሌሎች ሲፈፀምም በወቅቱ ለሚመለከተው አካል ሪፖርት
የማድረግ፣
78
2. በሙያ ዘርፋቸው የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከመንግሥት ጋር የጋራ ውይይት
የሚያደርጉባቸውን መድረኮች ያመቻቻል.፣
3. ከክልሉ፣ ከሌሎች ክልሎች፣ ከፌደራልና ከውጭ ሐገራት አቻ የሙያ
ማህበራት፣ ባለድርሻና አጋር አካላት፣ ድርጅቶችና ተቋማት ጋር በጥምረት
ለመስራት የሚችሉባቸውን ሁኔታዎች የማመቻቸትና የመፈፀም፣
4. በየጊዜው በአባላቶቻቸው ያለውን የአቅም ክፍተት በማጥናት ተከታታይነት
ያላቸው የረጅምና የአጭር ጊዜ ስልጠና በየዘርፋቸው እንዲያገኙ ያደርጋል፣
5. በዘርፉ የዕውቀትና የክህሎት ክፍተት ላለባቸው አባላት የአጫጭር እና
የረጅም ጊዜ ስልጠና በመስጠት ክፍተቱ እንዲሞላ ያደረጋል፣አባላቱ
ስልጠና የሚያገኙባቸውና የልምድ ልውውጥ የሚያደርጉባቸው መድረኮች
እንዲመቻቹ ይደረጋል፣
80
ሐ/በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (1) መሠረት ለዕግድ ምክንያት
የሆኑትን ጉድለቶች ቢሮው በሚወስነው የጊዜ ገደብ ውስጥ
ካላስተካከለ፣ ወይም
ክፍል ስድስት
ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
82
የወረዳ መ/ቤቶች ቅሬታው ከቀረበበት ጊዜ ጀምሮ ባለው አንድ ወር ጊዜ
ውስጥ ውሳኔውን በጽሁፍ ማሳወቅ ይኖርበታል፡፡
አወቀ እንየው
83