Professional Documents
Culture Documents
Decons. Docx - Docx2
Decons. Docx - Docx2
ዲያቆናት
ዲያቆናት በቤተ ክ/ን ዉስጥ ችግርን በመቅረፍና ሁሉንም በባርነት (ዝቅ ብሎ በነፃ) በማገልገል
ማዕድ/ ገበታን ( የሚለዉ ቃል አስፈላጊ አቅርቦቶችን ያጠቃልላል ሮሜ 16፡1-2) በማደል
አንድነትን የሚገነቡ አገልጋዮች ናቸዉ፡፡ ሐዋ 6፡ 1-7
1. ትርጉም፡
3. ምርጫ፡ እና መስፈርቶች፡-
ሐዋ 6፡3 ዘጸ 31፡3 መልካም ምስክርነት፤ በመንፈስ ቅዱስ የተሞሉ፤ ጥበብ የሞላባቸው(
ጥበብ ማለት እግዚአብሔርን መፍራት ወይም እዉቀትና ልምድ ላይ ያለንን ጥልቅ ግንዛቤ/
ማስተዋል በመጠቀም ችግርን የመፍታት ብቃት) የሚለዉ እንደተጠበቀ ሆኖ የጸሎት ሰዎችና
በወንጌል ስርጭት የሚሳተፉ ስለሆነ ጳዉሎስ ከችሎታና አስተዳደራዊ ክህሎት ይልቅ ሰብአዊና
መንፈሳዊ ባህሪይን እንደ ቁልፍ ክራይቴርያ ይወስዳል፡፡ 1ጢሞ3፡ 8-13 ምክንያቱም እነዚህ
1
2
- ንብረቶችን ወንበሮችን፤ ወለሉንና ግድግዳዉን በንጽህና እንዲያዙ ማገዝ፡፡ ቆሻሻ በቤተ ክ/ን
ዉስጥ እንዳይጣልና ሰዉ ሁሉ ድርሻዉን እንዲወጣ መምከርና ማስተማር፡፡ - የቤተ ክ/ን ግቢ
ንጹህ የማረና አረንጓዴ ማድረግ፡፡ - በቂ ብርሃንና አየር መኖሩን ማረጋገጥ፤ የሚረብሹ
ንፋሶችና ሙቀቶች፤ ከዉስጥም ሆነ ከዉጪ የሚወጡ ድምጾችን አጣርቶ እንዲሰተካከሉ
ማድረግ፤ ለምሳሌ፡ ሞንታረቦ ፊትለፊት የሚቀመጡ ሰዎች ለጆሮአቸዉ ምቾት እንዳላቸዉና
እንደሌላቸዉ ማጣራትና እንዲመች ማስመጠን፡፡ - ቅዱስ ስርአቶች ሲደረጉ ከወንጌል ሰዎች
ጋር ሆኖ ሁኔታዎችን የማመቻቸቱን ስራ በዋናነት መስራት፡፡ ለህሙማን የሚጸልዩና ህሙማን
እንዲጸለይላቸዉ ማገዝና ማዳናቸዉን በመከታተል ሲድኑም ለምስክርነት ማዘጋጀት፡፡ -
በሀዘንና በለቅሶ በቀብር ሥነ ስርዓት የሚሰሩ የዕድርና ባልትና አገልግሎትን ማደራጀት
2
3
አገልጋዮቹንም ማገዝ፡፡ የግቢ ዉስጥ አካል ጉዳተኛን በማሰብ መንገድ ማበጀትና ማስታወቅያ
መለጠፍ/ቢልቦርድ ማቆም
በቤተ ክ/ን ያሉ በኑሮ የሚቸገሩ ምዕመናንን በመለየት ስራና ገቢ እንዲያገኙ ት/ትና ስልጠና
እንዲያገኙ ሰርተዉ ራሳቸዉን እንዲችሉ፤ ስራን ሳይንቁ እንዲሰሩ እርስ በርስም እንዲረዳዱ
በመደራጀት በመንግስትና ሲቪል ማህበራት አከባቢ የሚገኘዉንም ዕድል እንዲጠቀሙ መምከር
ማስተዋወቅ ማበረታታት፡፡ ወገኖችን በመቅረብና በማቅረብ የግል ኑሮአቸዉን ቤታቸዉን
በመረዳት ልብስና ምግብ የሌላቸዉን ካላቸዉ በማሰባሰብ ማከፋፈል፤ እቤታቸዉ የፈረሰባቸዉና
በተለይም ክረምት በጎርፍና በዝናብ የሚጎዱ አረጋዊያንን አስቀድሞ በመለየት ምዕመናንን
በማስተባበር መርዳት፡፡ ወላጅ ያጡ ህጻናትን፤ በጦርነትና በተፈጥሮ አደጋ የተፈናቀሉ ፤
እንዲሁም በተለያዩ ምክንያቶች የታሰሩ ወይም በሞት የተለዩን የቤተሰብ መሪዎች ቀሪ
ወገኖችን በመለየት በሚያስፈልጋቸዉ መደገፍ፡፡ እየተማሩ ያሉ ግን በእርዳታ ማጣት
ምክንያት ት/ታቸዉን አቋርጠዉ ላልተፈለገ ህይወት የተጋለጡ ወጣቶች ካሉ መከታተልና
ከዲያብሎስ ወጥመድ ማስመለጥ፡፡
ቤተ ክ/ን ያላት ሀብት (ገንዘብና ንብረት) የእግዚ/ር እና የህዝቡ የምዕመኑ ስለሆነ በተለይ
ዲያቆናት በሀላፊነት ንብረት ሳይባክን ሳይሰበር ሳይሰረቅ በንጽህናና በጥንቃቄ ተጠብቀዉ
ለረጂም ጊዜ እንዲቆዩ አገልግሎት እንዲሰጡ ልዩ የእንክብካቤና የጥበቃ ሀላፊነት ላይ
በመሰራት በዚህ ጉዳይ ከሚሰሩ ምዕመናን ወይም ሰራተኞች ጋርም በመቀናጀት ወይም
በትብብር መስራት ይጠበቅባቸዋል፡፡
እነዚህ ከላይ የጠቀሱት 5ቱ አገልግሎቶች ከቃልና ከጸሎት የተለዩ ቢሆኑም ሁሉም የማዕድ
ሳይሆኑ መንፈሳዊና የቤተ ክርስትያን አካላዊ አስተዳደራዊ ፤ማህበራዊና የአምልኮ ስርዓቶች
ናቸዉ፡፡ መልዕክት/ደብዳቤ ወይም
4
5