Download as docx, pdf, or txt
Download as docx, pdf, or txt
You are on page 1of 5

የወ 05 የግንዛቤ ህ / /

ሰብ ተሳትፎ የስራ ሂደት በስራ ሂደቶች መካከል የተደረገ

////
በን ስ ላ ክ ከ የወረዳ 05
/ ///
ሥራ አስኪያጅ ጽ ቤት የግ ህ ተ ቡድን

የ 2014 በጀት ዓመት

የውስጥ ትስስር ሰነድ

መስከረም 2014 ዓ.ም

መግቢያ
ድህነትና ኋላቀረነትን ታርክ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት በማዘጋጃ ቤታዊ ዘርፍ የታቀዱ የበጀት ዓመቱ የልማት ግቦች፤ የእድገትና
ትራንስፎርሜሽን እቅድና የተዛማጅ ልማት ግቦች ስኬታማ ለማድረግ መንግስት በማዘጋጃ በታዊ ዘርፎች ሰፍኖ የቆየውና የተበታተነ
፤ጥራት የጎድለውን አስተዳደርና የቁጥጥር ስርአት ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድርግ አዲስና የተቀናጀ አስተዳደርና ቁጥጥር ስርአት
መዘርጋት በማስፈለጉ በፌደራል ህገ መንግስት አንቀጽ 92 መሰረት ማንኛውም ዜጋ ንፁህና ውብ በሆነ አካባቢ የመኖር መብት
እንዳለው ይደነግጋል፡፡ በዚህ መሰረት የመኖሪያ ቤቶች፤ንግድ ተቋማትና የልየ ልዩ ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ በሚፈለገው ደረጃ ጥራቱን
የጠበቀ እንዲሆን እና በተቀመጠላቸው ስታንዳደርድ መሠረት አገልግሎት መስጠት እንዲቻል ለሁሉም ተመሳሳይ ድጋፍ እና ክትትል ማድረግ
በተለይም ግንዛቤው በደንብ እንዲሰርፅ አስፈላጊ በመሆኑ በወረዳውም ደረቅ ቆሻሻ አስተዳደር ጽ/ቤት በግንዛቤና ህብረተሰብ ተሳትፎ ቡድን
በስራ አስኪያጅ ሆኖ እንዲደራጅ ተደርጓል፡፡ ከዚህም በመነሳት በወረዳችን ይህንን አሰራር የተጠናከረ እና የተደራጀ ለማድረግ እና
የህብረተሰቡን ጤናና ውበት በሚገባ ለማረጋገጥ ከባለ ድርሻ የስራ ሂደቶች ጋር ተቀናጅቶ መስራት አስፈላጊ በመሆኑ ከባለድርሻ ስራ
ሂደቶች ጋር በጋራ መስራት የሚያስችል የትስስር ሰነድ በሚከተለው መልኩ ተዘጋጅቷል፡፡

የሴክተሩ/ስራ ሂደቱ/ ተልዕኮ፤ራዕይ፤እሴቶችና መርሆዎች

1. ራዕይ

አዲስ አበባን ብሎም ወረዳ 05 በ 2017 ዓ.ም የአፍሪካ ሞዴል ከተማ ሆና ማየት፡፡
2. ተልዕኮ

የወ 05 ስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት የህብረተሰቡንና የባለድርሻ አካላትን ተሳትፎ መሰረት በማድረግ የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና አሰባሰብ ስራን በመከታተል እና በመቆጣጠር
በመሰብሰብ በማጓጓዝ እና የወረዳውን ነዋሪ ግንዛቤ በማሳደግ ዘመናዊና ዘላቂነት ባለው መልኩ አገልግሎት በመስጠት ከተማዋን ጽዱ ማድረግ ነው፡፡
3. እሴቶችና የእምነቶች መገለጫዎች

1. ተጠያቂነት 6. የሰው ሀይል ቀዳሚ ሀብታችን ነው! !


2. ግልጽነት 7. ስራዎችን የጋራ አመለካከትና ግንዛቤ ከመፍጠር ይማራሉ
3. የላቀ አገልግሎት መስጠት 8. የቡድን ስራ ለስኬታማነታችን መሰረት ነው
4. ለለውጥ ዝግጁነት 9. ከተማን ማጽዳት ተቀዳሚ ተግባራችን ነው፡፡
5. በእውቀትና በእምነት መምራት/መሰራት

የትስስሩ ዓላማ

በጽ/ቤታችን ከሚገኙ የስራ ሂደቶች መካከል ከስራ ሂደታችን ጋር የስራ ግንኙነት ያላቸውን በመምረጥ በተደራጀ እና
በተቀናጀ መልኩ ተግባራት ውጤታማ እንዲሆኑ መንቀሳቀስ፤ የጥራት ደረጃውን እና ፍትሃዊነቱን የጠበቀ አገልግሎት
በመስጠትና ተከታታይነትና ቀጣይነት ያለው ድጋፍና ክትትል በማድረግ የህዝብ ንቅናቄ በመፍጠር የራሱን ጤና በራሱ
መጠበቅ የሚችል ጤናማ እና ምርታማ ማህበረሰብ መፍጠር ነው፡፡

የትስስሩ ግብ
ከባለድርሻ ስራ ሂደቶች ጋር በመቀናጀት፤ በተልዕኮ ዙሪያ የሚረባረብ አመራርና ባለሙያ በመፍጠር፡የማስፈፀም አቅምን ቀጣይነት
ባለው ሁኔታ በመገንባት እና ምርጥ ተሞክሮዎችን በመቀመርና በማስፋፋት ንፁህና ማራኪ አካባቢ መፍጠርና የወረዳው ነዋሪ ፅዳቱ
የተጠበቀ ምርታማ እንዲሆን ማድረግ፡፡
የትስስሩ ወሰን

በ 2014 ዓ.ም በንፋሰ ስልከ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 አስተዳደር በስራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ስር በሚገኙ እና ከስራ ሂደታችን ጋር
በስራ በሚያገናኙን የስራ ሂደቶች መካከል ይሆናል ፡፡

የባለ ድርሻ አካላት አስተዋፅኦ

ሥራ ሂደቱ የሚያከናወናቸውን ተግባራት ውጤታማ እንዲሆኑ እና ህብረተሰቡ ተጠቃሚ እንዲሆን ከተለያዩ አካላት ጋር
ተቀናጅቶ መንቀሳቀስ አስፈላጊ በመሆኑ ይህን የትስስር ሰነድ ማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኗል፡፡

ከሥራ ሂደቱ ጋር በአጋርነት የሚሠሩ አካላት በዝርዝር ተግባራቸው እንደሚከተለው

1) ከደረቅ ቆሻሻ መሰብሰብና ማጓጓዝ አገልግሎት የስራ ሂደት የሚጠበቅ

 ቆሻሻ ከምንጩ እንዲቀንስ የደረቅ ቆሻሻ ማህበራት ለመልሶ መጠቀም የሚውሉ ደረቅ ቆሻሻዎችን በዓይነት እንዲለዩ
ክትትልና ድጋፍ ማድረግ
 በሕገ ወጥ ቆሻሻ አጣጣል ላይ በንግድ ተቋማት ላይ ለሚወሰደው ሕጋዊ እርምጃ ድጋፍ ማድረግ እና ህገ ወጥ ቆሻሻ
እንዳይፈጠር መከታተል፡፡

 የሥራ ሂደቱ ሰራተኞች በፅዳት ዘመቻዎች ላይ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ማድረግ


 በማህበረሰቡና በአንድ ማዕከል የሚፀዱ ቆሻሻዎችን በወቅቱ እንዲነሱ ማድረግ
 የማህበረሰቡን የእርካታ ደረጃ ከፍ ለማድረግ ማህበራት በፕሮግራማቸው እንዲያገለግሏቸው ማድረግ
 ቆሻሻ ሳይዝረከረክ እንዲነሳ ማድረግ በተለይ በየሰፈሩ በሚሰበስቡበት ቦታ ሁሉ፡፡
 በቢሮ ውስጥ በጋራ የሚሰሩ ስራዎችን በጋራ በመስራት ውጤታማ እንዲሆኑ ማድረግ
 የወረቀት ብክነትን መቶ ፐርሰንት እንዲቀንስ ማድረግ
2) ከመልሶ መጠቀምና ዑደት ማድረግ የስራ ሂደት የሚጠበቅ
 ቆሻሻ ከምንጩ እንዲቀንስ ለመልሶ መጠቀም የሚውሉ ደረቅ ቆሻሻዎችን ከባለሀብት ጋር የገበያ ትስስር እንዲፈጠር ማድረግ
 በቢሮ ውስጥ በጋራ የሚሰሩ ስራዎችን በጋራ በመስራት ውጤታማ እንዲሆኑ ማድረግ
 የሥራ ሂደቱ ሰራተኞች በፅዳት ዘመቻዎች ላይ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ማድረግ
 የሚበሰብሱ ቆሻሻዎች ለቀልዝ/ኮምፖስት /አገልግሎት እንዲውል የሙያ እገዛ ማድረግ
 የተለያዩ መልሶ ጥቅም የሚሰጡ እንደ ወረቀት እና ካርቶን ያሉ ቆሻሻዎችን በህጋዊ መንገድ የተራጁ ማህበራት እንዲሰበስቧቸው
ማድረግ
 የወረቀት ብክነትን መቶ ፐርሰንት እንዲቀንስ ማድረግ

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 የስራ አስኪያጅ ፅ/ቤት የግ/ህ/ሰ/ተሳትፎ የስራ ሂደት ጋር ትስስር የፈጠሩ አካላት
ተ.ቁ የስራ ሂደቶች ስም ስም ፊርማ የተሳሰሩበት ቀን
1 ከደረቅ ቆሻሻ መሰብሰብና ማጓጓዝ አገልግሎት
የስራ ሂደት
2 ከመልሶ መጠቀምና ዑደት ማድረግ
የስራ ሂደት

ያዘጋጀው ባለሙያ ስም------------------- ያረጋገጠው ኃላፊ ስም----------------------


ፊርማ-------------------------- ፊርማ-------------------------
ቀን------------------------- ቀን-------------------------

You might also like