Download as docx, pdf, or txt
Download as docx, pdf, or txt
You are on page 1of 3

የአምራች ኢንዱስትሪው የሰው ሀብት ልማት አቅጣጫ

በኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ልማት ፍኖተ-ካርታ በግልጽ እንዳስቀመጠው የኢንዱስትሪው ዘርፍ በማዋቅራዊ


የኢኮኖሚ ሽግግር የመሪነቱን ሚና ከግብርናው ዘርፍ በመረከብ እና በ 2025 ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት
ድርሻው 28 በመቶውን በመሸፈን እንዳለበት አመላክቷል። የኢትዮጵያ አምራች ኢንዱስትሪዎች የሰው ሃይል
ፍላጎት እቅድ ከ 2016-2025 በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ሰነድ እንደሚያሳየው በኢንዱስትሪው በራሱ ውስጥ
በሚያደርገው የእድገት ሽግግር ላይ በመመርኮዝ በሁለት ምዕራፎች የተከፈለ የሰው ሀብት የልማትና የአቅም
ግንባታና ልማት አቅጣጫዎችን አስቀምጧል፡፡

ምስል-1 የአምራች ዘርፉ የልማት እድገት ምዕራፎች

ከላይ በምስል 1 እንደተመላከተው በአምራች ኢንዱስትሪው ዘርፍ ፈጣን እና ዘላቂ የሆነ ልማትን በማረጋገጥ
የታሰበውን የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ለማምጣት በመጀመሪያ ደረጃ በለዘርፉ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር
አስፈላጊ ይሆናል፡፡

ከታች ባሉት ምስሎች እንደተመላከተው የመጀመሪያው ምዕራፍ የሰው ሀብት የአቅም ልማት እቅድ በዋናነት
የሚያተኩረው ኢንዱስትሪውን ባሳተፈ መልኩ ለቀላል ኢንዱስትሪዎች እድገት አስተዋጽኦ የሚያስፈልጉ
ቴክኖሎጂዎችን ከወቅቱ ፍላጉት አንጻር ለይቶ መቅዳትና ማላመድ እንዲሁም በተግባር ላይ የሚተኩሩ
ስልጠናዎች እና የትምህረት መስኮች ላይ ነው፡፡

ሁለተኛው ምዕራፍ በአንጻሩ ትኩረት የሚያደርገው የመጀመሪው ምእራፍ አፈጻጸም የሚፈጥራቸውን ከባድ
ኢንዱስትሪዎች ፍላጉት ማሟላት ላይ ነው፡፡ እነዚህ ኢንዱስትሪዎች የአመራረት ስርዓታቸው በከፍተኛ እና
ውስባስብ ቴክኖሎጂዎች ላይ የሚመሰረት በመሆኑ ይህን ፍላጎት ማሳካት የሚችል የቴክኖሎጂ አቅምን
በጥናትና ምርምር በታገዘ ፈጣራ መደገፍን እንዲሁም በከፍተኛ የክህሎት ደረጃ የሰለጠነ እና በተመረጡ
የትምህርት መስኮች በእውቀት ስፔሻላይዝድ ያደረገ የሰው ሀብት ማልማት ላይ ያተኩራል ፡፡

ምዕራፍ I (2016-2020) ምዕራፍ II (2021-2025)

ነባርና ቅድሚያ ትኩረት ነባርና ቅድሚያ ትኩረት


የኢንዱስትሪ ልማት የሚሰጣቸው የሚሰጣቸው
ምዕራፎች ኢንዱስትሪዎች ኢንዱስትሪዎች
+ +
ቁልፍ የሆኑ አዲስ ከፍተኛ ቴክኖሎጂን
ኢንዱስትሪዎችን የሚጠቀሙ ከባድ
ማስፋፋት ስብጥራቸውን ኢንዱስትሪዎች
መጨመር

በዝቅተኛ እና በመካከለኛ በከፍተኛ የክህሎት ደረጃ


የሰው ሀብት ልማት ደረጃ የሰለጠነ የሰው ስፔሻላይዝድ ያደረገ የሰው
አቅጣጫ ሀብት የቴ/ሙ/ት/ስ ሀብት
ሰልጣኞች +
+ ጥናትና ምርመር
በመካከለኛና ከፍተኛ ደረጃ የማከናወን በቂ አቅም
ክህሎት የበቃ የሰው ሀብት ያለው የሰው ሀብት

የአቅም ግንባታና ልማት በከፍተኛ የክህሎት ደረጃ በእውቀትና በፈጠራ የበቃ


ስፔሻላይዝድ ያደረገ የሰው የሰው ሀብት
ሀብት

ምስል-2 የአምራች ዘርፍ የሰው ሀብት ልማት አቅጣጫ

You might also like