Professional Documents
Culture Documents
2013
2013
የኮንስትራክሽን ሥራዎች ጥራትና ደረጃቸውን ጠብቀው እንዲሰሩ ለማድረግ እንዲቻል በሴክተሩ ተዋናይ የሆኑ
ፈጻሚና አስፈጻሚ አካላት መኖራቸው የሚታወቅ ነው፡፡ በመንግስትና በግሉ ዘርፍ በሚካሄዱ የተለያዩ የግንባታ
ፕሮጀክቶች ላይ ከቅድመ ግንባታ ጀምሮ እስከ የግንባታ ውል አስተተዳደር ድረስ ባለው ሂደት ተዋናይ ከሆኑ
የሙያ አካላት ውስጥ አማካሪዎች በግንባር ቀደምትነት ከሚጠቀሱት አንዱ መሆናቸው ይታወቃል፡፡
በመሆኑም የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውን ጤናማ እድገቶች የሚጎዱ መልካም ያልሆኑ ገፅታዎችን፣ ሙስናንና
ብልሹ አሰራር ለመከላከል፣ ሙያዊ ሥነ ምግባርን እንዲከበር ማድረግ እና የስራ ዲሲፕሊን በማስፈን በዘርፉ
የሚሳተፉ አካላት የሚመሩበት የድጋፍ፣ ክትትል፣ ቁጥጥርና የተጠያቂነት ሥርዓት መዘርጋት አስፈላጊ ሆኖ
በመገኘቱ ፣
ክፍል አንድ
ጠቅላላ ድንጋጌ
1. አጭር ርዕስ
1
ይህ መመሪያ “የኮንስትራክሽን አማካሪዎች አሰራር መመሪያ ቁጥር --------/2013 ” ተብሎ ሊጠቀስ
ይችላል፡፡
2. ትርጓሜ
የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ መመሪያ ውስጥ ፡-
1) “ኮንስትራክሽን ማለት“ ከመሬት በታችና በላይ የሚከናወኑ ህንጻን እና ሌሎች የምህንድስና መሠረተ
ልማትን ጨምሮ በቋሚ ንብረቶች ላይ የዕቃዎች እና አገልግሎቶች ጥምር የሆነ የልማት፣
የማስፋፋት፣ የመገጣጠም፣ የጥገና፣ የዕድሳት፣ የማሻሻል፣ የቁፋሮ፣ የማወላለቅ እና የማፍረስ
ሥራዎችን የሚያካትት ተግባር ነው ፡፡
2) የኮንስትራክሽን ፕሮጀክት” ማለት በመንግስት፣ በግሉ ዘርፍ እና በመንግስትና በግሉ ዘርፍ ጥምረት
የሚከናወኑ ማናቸውም የምህንድስና ጥናት፣ እቅድ፣ ዲዛይንና የኮንስትክሽን ሥራዎችን
ያጠቃልላል፡፡
3) “አማካሪ” ማለት ሕጋዊ ሥልጣን በተሰጠው አካል ተመዝግቦ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ
የአማካሪነት የምዝገባ/ብቃት ምስክር ወረቀት ፈቃድ የተሰጠው እና የንግድ ፈቃድ ያለው ድርጅት
ነው፡፡
4) “የሥራ ተቋራጭ” ማለት ሕጋዊ ሥልጣን በተሰጠው አካል ተመዝግቦ የኮንስትራክሽን ሥራዎች
የሥራ ተቋራጭነት የምዝገባ/ብቃት ምስክር ወረቀት ፈቃድ የተሰጠው እና የንግድ ፈቃድ ያለው
ድርጅት ነው፡፡
5) “የዲዛይን ባለሙያ” ማለት ሕጋዊ ሥልጣን በተሰጠው አካል ተመዝግቦ የኮንስትራክሽን ዲዛይን
ለመስራት የምዝገባ ምስክር ወረቀት የተሰጠው ሰው ነው፡፡
6) “አሰሪ“ ማለት ማንኛውንም የግንባታ ፕሮጀክት አፈጻጸም የሚከታተልና የሚያስፈጽም ከአማካሪ
ድርጅት ወይም ከሥራ ተቋራጭ ጋር ውል ገብቶ የሚያሰራ አካል ነው፣
7) “ብክነት” ማለት ዲዛይን ሲዘጋጅ ተገቢውን ግብዓት ተጠቅሞ መስራት እየተቻለ ለፕሮጀክቱ
ከተቀመጠው በጀት፣ ጥራትና ጊዜ በላይም ሆነ በታች በመጠቀሙ የሚፈጠር ብክነት ወይም ኪሳራ
ማለት ነው፡፡
8) “ቅድመ ዲዛይን” ማለት ዲዛይን ከመሰራቱ በፊት የፕሮጀክት የመስክ ምልከታን፣ አዋጪነት
ጥናትንና የቅየሳ ሥራን ያካትታል፡፡
9) “ዲዛይን” ማለት የአንድን የኮንስትራክሽን ፕሮጀክት መጠን፣ ዓይነትና ስፋት እንዲሁም
የሚሠራበትን ቁሳቁስና የአገነባብ ዘዴን የሚያሳይ ንድፍ ወይም ሞዴል ሲሆን የአርክቴክቸር፣
የስትራክቸር፣ የሳኒተሪ፣ የኤሌክትሪካል፣ የሜካኒካል፣ የእሳት አደጋ መከላከልና የሌሎች ሥራዎችን
ንድፍ ሊያካትት ይችላል፤
10) “ሚኒስቴር” ማለት የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ነው፡፡
2
11) “ሰው” ማለት የተፈጥሮ ወይም በህግ የሰውነት መብት የተሰጠው ማንኛውም አካል ነው፡፡
12) በዚህ መመሪያ ውስጥ በወንድ ጾታ የተገለጸው ሁሉ በሴት ጾታ ላይም ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
3. የተፈጻሚነት ወሰን
1. ይህ መመሪያ ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ላይ ተፈጻሚ ይሆናል፡-
4. መርሆዎች
ማንኛውም በኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ላይ የሚሳተፍ አማካሪ ሊከተላቸው የሚገቡ መርሆዎች
3
1. ማንኛውም የኮንስትራክሽን ዲዛይን አማካሪ የኮንስትራክሽን ዲዛይን ሲሰራ ለሥራው በሚመጥን የዲዛይን ባለሙያ
ቀጥሮ ማሠራት አለበት፣
2. የሚቀጠሩ የዲዛይን ባለሙያዎች የዲዛይን ሥራ ለማከናወን የተመዘገቡና ለበጀት ዓመቱ የታደሰ የባለሙያ ምስክር
ወረቀት ያላቸው መሆን አለበት
ክፍል ሁለት
የዲዛይንና ተጓዳኝ ሥራዎች
6. ስለቅድመ ዲዛይን ሥራ
1. በቅድመ ዲዛይን አማካሪ የሚያዘጋጀው የፕሮጀክት አዋጭነት ጥናት የቅየሳ ሥራ በውሉ
ባይገለጽም የአካባቢውን ነባራዊ ሁኔታ በትክክልና በዝርዝር የሚገልጽ መሆን አለበት፡፡
7. የአፈር ምርመራ
1. የአፈር ምርመራ እንዲያካሂድ የተቀጠረ አማካሪ ስራውን ሲሰራ ሳይንሳዊ የሆኑ አገር አቀፍ እና
አለም አቀፍ ስታንዳርዶችንና ኮዶችን መሠረት አድርጎ ፕሮጀክቱ የሚያርፍበትና የአካባቢውን
ወካይ(ገላጭ) ናሙና መውሰድ አለበት፤
2. አማካሪው የዲዛይን ስራ የሚሰራ ከሆነ ወደዚያ ሰራ ከመግባቱ አንድ ወር በፊት የአፈር ምርመራ
ውጤቱንና ዝርዝር መረጃዎችን ለአሰሪው ማሳወቅ አለበት፤
3. አማካሪው ያገኘውን የአፈር ምርመራ ውጤት መሰረት አድርጎ በፕሮጀክት ቦታ ለሚዘጋጅ
ዲዛይን ወይም ለሚካሄድ ግንባታ ተገቢነት ያለው ሳይንሳዊና ሙያዊ አስተያየት መስጠት አለበት፡፡
8. የዲዛይን ዝግጅት
ማንኛውም ዲዛይን እንዲያዘጋጅ የተቀጠረ አማካሪ ፡-
1. የሕንጻ፣ የመንገድ፣ የከተማ፣ የአረንጓዴ ስፍራ ማስዋብ፣ የድልድይ፣ የመሰረተ-ልማት እና
ሌሎች ተያያዥ ዲዛይኖችን ማናበብና ማጣጣም ይኖርበታል፤
2. በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ግንኙነት ያላቸውን የአገር አቀፍና አለም አቀፍ ህጎች፣ ኮዶችና
ስታንዳርዶች እንዲሁም የአካባቢው ፕላን ያስቀመጣቸውን ህግጋት መከተል ይኖርበታል፤
4
5. አስፈላጊ የሆነ የግንባታ ፕሮጀክት የዲዛይኑ የቆረጣ ምልከታ (section) ተወስዶ ዝርዝር
ዲዛይኖችን (Design details)፣ መለኪያዎችን እና የግብዓት ዝርዝርን (materials) በግልጽ
ማስቀመጥ ይኖርበታል፤
ክፍል ሶስት
5
የግንባታ ቁጥጥር አማካሪ
2) የግንባታ ቁጥጥሩን /ሱፐርቪዝን/ ሲያከናውን አጠቃላይ ስራውን በአግባቡ ለመቆጣጠር በሚያስችለው አስቀድሞ የተዘጋጀ
ቸክ ሊስት መሠረት መሆን አለበት፣
ክፍል አራት
ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
15 ስለ ቅጣት
አማካሪው በዚህ መመሪያ የተገለፁት ግዴታዎቹን በመጣስ በአሰሪው ወይም ሌሎች ስራው የሚነካቸው
አካላት ለሚያደርሰው ጉዳት የሚኖረው የወንጀል፣ ፍትሀ ብሄር እና አስተዳደራዊ ሀላፊነት በተመለከተ ሌሎች
አግባብነት ያላቸው ሕጎች የሚደነጉግት ቅጣት እንደተጠበቁ ሆኖው፤
6
15.1 በዚህ መመሪያ ከአንቀፅ 6-11 የተደነገጉት ግዴታዎች በመጣስ አማካሪዎች በቅድመ ግንባታ
ስራዎች የሚፈፀሙት ጥፋት
15.2 ከቅየሳ ጋር የተያያዙ ጥፋቶች
ሀ. አማካሪው ያቀረበው የአካባቢ ነባራዊ ሁኔታ በግንዛቤ ውስጥ ያላስገባ የቅየሳ ስራ ሰርቶ ሲገኝ ጥፋቱ
የመጀመሪያው ሆኖ በፕሮጀክቱ ያደረሰው ጉዳት የሌለ እንደሆነ ፤ አማካሪው በራሱ ወጪ ጥፋቱን
እስከሚያርም ሊደርስ ለሚችል ማንኛውም ብክነት ወይም ጉዳት ከአሰሪው ጋር በገባው ውል
የሚኖረው ሀላፊነት እንደተጠበቀ ሆኖ ዳግም ተመሳሳይ ጥፋት አንዳይፈፅም የፅሑፍ ማስጠንቀቅያ
ተሰጥቶት በስራው ሊቀጥል ይችላል፡፡
ለ. አማካሪው ሰርቶ ባቀረበው የቅየሳ ስራ ውጤት የፈፀመው ጥፋት በፕሮጀክቱ ላይ ጉዳት ያደረሰ ከሆነ
፤ቀጣሪው ችግሩን ለማስተካከል ያወጣውን ሙሉ ወጪ ሸፍኖ የስራ ውሉ መቋረጡና ሌሎች
በገባው ውል መሰረት ለአሰሪው ወይም ቀጣሪው የሚኖረው ሀላፊነት እንደተጠበቀ ሆኖ የሙያ
ብቃት ማረጋገጫ ፈቃዱ ለ 2 (ሁለት) ዓመት ይታገዳል እንዲሁም በገባው የመድን ዋስትና መሰረት
የተጠቀሰውን ካሳ ይከፍላል፡፡
ሐ. አማካሪው የፈፀመው ጥፋት ሆን ብሎ፤ ለራሱ ወይም ለሌሎች ሕጋዊ ያልሆነ ጥቅም ለማስገኘት
ወይም በአሰሪው ሆነ በተቋራጩ ላይ ጉዳት ለማደረስ ከሆነ ወይም ጥፋቱ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሰ
እንደሆነ፤ አግባብነት ባለው የወንጀል ሕግ መጠየቁ፣ ውሉ መቋረጡ፣ በገባው ዋስትና መሰረት
የሚከፍለው ካሳ ወይም በገባው ውል መሰረት የሚኖሩት ሌሎች ሀላፊነቶች እንደተጠበቁ ሆኖው፤
እንደ ጥፋቱ ክብደት ከ 3 (ሶስት) አስከ 5 (አምስት) ዓመት ለሚደርስ ጊዜ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ
ፈቃዱ ይታገዳል፡፡
7
ሀ. አማካሪው በዚህ መመሪያ 7.1 ተዘረዘሩት ዲዛይኖች ሳያናብብ ካቀረበ በራሱ ወጭ ያስተካክላል
ስህተቱን ለማስተካከል ለሚፈጀው የጊዜ ብክነት ለስራው ሊከፈለው የተዋዋለውን ገንዘብ መጠን
10%ቅጣት ይጣልበታል፡፡
ለ. አማካሪው በአንቀጽ 8.2 የጠጠቀሱትን ህጎች ኮዶች እና ስታንዳርዶች ያልጠበቀ ዲዛይን ሰርተው
ካቀረቡ ፍቃዳቸው ለተከታታይ 3 አመት ታግዶ ለዲዛይ ዝግጅት ተከፈለውን ገንዘብ መጠን 50%
እንዲቀጣ ይጣልበታል፡፤
ሐ. አማካሪው ባዘ ጋጀው ዲዛይን ምክኒያት ያላግባብ ብክነት የፈጠረ እንደሆን ብክነቱን 25%ቅጣት
ይጣልበታል እንዲሁም ፈቃዱ ለ 2 ተከታታይ አመት ይታገድበታል፡፡
መ. አማካሪው በዚህ መመሪያ አንቀጽ 7.4 የተዘረዘሩትን ይዘቶች የማያሟላ ዲዛይን ሰርቶ ካቀረበ ፈቃዱ
ለ 2 ተከታታይ አመት ይታገድበታል፡፡
ሠ. አማካሪው ያዘጋጀው ዲዛይን ዚህ መመሪያ አንቀጽ 7.4 የተዘረዘሩትን ይዘቶች የማያሟላ ዲዛይን
ሰርቶ ካቀረበ እና ዲዛይኑ ሊያሰራ የማችል መሆኑ ከተረጋገጠ በራሱ ወጭ እንዲያስተካክል
እና ለማስተካከል ሲባል ለተፈጠረው የጊዜ ብክነት በቀጣሪው ላይ የደረሰውን ኪሳራ
25%ቅጣት ይጣልበታል እንዲሁም ፈቃዱ ለ 2 ተከታታይ አመት ይታገድበታል፡፡
15.5 ከስራ ዝርዝር ጋር የተያያዙ ጥፋቶች
ሀ. በአማካሪው የተዘጋጀ ማንኛውም የስራ ዝርዝር (specification) ከዲዛይኑ ጋር ልዩነት ካለው በራሱ
ወጭ እንዲያስተካክል እና በቀታሪው ላይ ደረሰውን ኪሳራ ተሰልቶ 25-50% እንዲከፍል
ይደረጋል፤
ለ. በአማካሪው የተዘጋጀው የስራ ዝርዝር የሚሰራውን ስራ በበቂ ሁኔታ ያልገለጸ፣ አስፈላጊውን ይዘት
ላሟላ ዌም ሊከተለው የሚገባውን አቀራረብ ስክት ያልተከተለ እንደሆን ሰነዱን በራሱ ወጭ
እንዲያስተካክል ይደረጋል እንዲሁም በቀጣሪው ላይ የደረሰው ኪሳራ 50% እንዲከፍል
ይደረጋል፤
ሐ. አማካሪው በብቃት ማነስ ምክኒያት ሚሰራውን ስራ በበቂ ሁኔታ ያልገለጸ እንደሆን የስራ ውሉ
እንዲቅረጥ ይደረጋል እንዲሁም የስራ ፈቃዱ ለተከታታይ 2 ዓመት ይታገዳል፡
15.6. ከስራ መጠን መክፈያ ሰነድ/BOQ ጋር የተያያዙ ጥፋቶች
ሀ. አማካሪ ያዘጋጀው የሥራ መጠን መክፈያ በተቻለ መጠን ከዲዛይኑ ጋር በመተንም ሆነ በይዘት
መለያየት የለበትም
ለ. አማካሪው ስራ መጠን ሲያዘጋጅ የስራ ዝርዝሩንና መለኪያውን እንዲሁም የክፍያ መጠን በትክክል
መግለጽ አለበት፡፡
15.7 የስራ መጠን መክፈያ BOQ ጋር የተያያዘ ጥፋት
8
ሀ. አማካሪው ሆን ብሎ ያለአግባብ ጥቅም ለማግኘት ወይም የሌሎችን ጥቅም ለማስገነት የስራ
መጠን መክፈያ ሰነድ ሲያዘጋጅ ከዲዛይኑ ጋር በመተን ወይም በይዘት ወይም በሁለቱም ላይ ልዩነት
ከፈጠረ ሰነዱን ከንደገና አስተካክሎ በራሱ ወጭ የሚያዘጋጅ ሆኖ ክፍያው 10% እንዲቀጣ ይደረጋል::
ለ. አማካሪው ያዘጋጀው የስራ መጠን መክፈያ ሰነድ በዚህ መመሪያ አንቀጽ 10 የተገለጹትን ማያሟላ
ከሆነ ሰነዱን በራሱ ወጭ እንዲያስተካክል ተደርጎ የአንድ ወር ክፍያ ሙሉውን እንዲቀጣ ይደረጋል፡፡
15.8 ከግንባታ ውል ማዘጋጀት ጋር የተያያዘ ጥፋት
ሀ. ማንኛውም የግንባታ ውል የሚያዘጋጅ አማካሪ አግባብነት ያላቸውን የኮንስትራክሽንና የግዢ ሕጎች፣
እና የፕሮጀክቱን አጠቃላይ ሁኔታ ያገናዘበ እንዲሁም የግዢ ህጉን በመተው ፈቃዱ ለ 4 ተከታታይ አመት
ይታገዳለል፤
ለ. ማንኛውም አማካሪ በውል ጊዜ መከተል ያለበትን የግዚ ህግ ተከትሎ ያልተዘጀ ሰነድ በራሱ ወጭ እና
ጊዜ እንዲያስተካክል ይደረጋል፡
ሐ. ማንኛውም አማካሪ የግዢ ህጉን በመተው የራሱን ጥቅም ለማስጠበቅም ሆነ ለሌሎች ጥቅም
ለማስገኘት ሲባል ውል ያዘጋጀ እንደሆን ከማንኛውም ስራ የሚታገድ ይሆናል፡፡
9
ሀ. የግንባታ ግብአቱ ከግንባታው ከስትራክቸራል ጋር ተያያዥነት ካለው ለአራት አመት የስራ ፈቃዱ
ይታገዳል፤በቀጣሪው ላይ ያደረሰውን ኪሳራ የመክፈል አቅሙ ታይቶ እንደ ኪሳራው መጠን ከ 5 እስከ 15
በመቶ እንደቅጣት ይጣልበታል፤
ለ. የግንባታ ግብአቱ ከግንባታው ስትራክቸራል ጋር ተያያዥነት የሌለው ከሆነ የስራ ፈቃዱ ለሁለት አመት
ይታገዳል፤በቀጣሪው ላይ ያደርሰውን ኪሳራ 25 በመቶ እንደቅጣት ይጣልበታል፤
6) አማካሪው በሚመለከተው የመንግስት አካል ናሙና ሊያስጸድቅ ሲገባው ሳያጸድቅ ወደ ስራ እንዲገባ
ካደረገ የአንድ ወር ክፍያው እንደ ቅጣት ይጣልበታል፤ናሙናውንም እንዲያጸድቅ ይደረጋል፤
7) ከላይ በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ 6 መሰረት ናሙናው ጸድቆ ሲመጣ ከስታንዳርድ በታች መሆኑ
ከተረጋገጠ በአንቀጽ 13.5.ሀ እና 13.5.ለ ላይ የተደነገጉት ተፈጻሚ ይሆናሉ፤
8) አማካሪው በሚመለከተው አካል ከጸደቀ ናሙና የተለየ የግንባታ ግብአት ወደ ስራ እንዲገባ ካደረገ
ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የስራ ውሉ የሚቋረጥ ሆኖ የስራ ፈቃዱ ከሶስት አመት ላልበለጠ ጊዜ
ይታገዳል፤ወይም ስራው በመሰራቱ በቀጣሪው ላይ የደርሰውን ኪሳራ 25 በመቶ እንደቅጣት ይጣልበታል፤
9) አማካሪው ያጸደቃቸውን የግንባታ ግብአቶች ዝርዝር የሙከራ ውጤት/ Test result በተቀመጠው የጊዜ
ገደብመሰረት ለቀጣሪው ካላሳወቀ ለመጀመሪያ ጊዜ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ከአንድ ጊዜ በላይ ከደገመና
የአንድ ወር ክፍያው እንደ ቅጣት ይጣልበታል፤
10) በአንቀጽ 13.9 የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ አማካሪው እነዚህን ግብአቶች ለቀጣሪው ሳያሳውቅ ወደ
ስራ ካስገባ የመጨረሻ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያና የሶስት ወራት፤ ክፍያው እንደ ቅጣት ይጣልበታል፤
11) አማካሪው ለቀጣሪው ሊያቀርብ የሚገባውንሳምንታዊና ወርሀዊ ሪፖርት ሳያቀርብ ከቀረ እና
የመጀመሪያው ከሆነ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ይሰጠዋል ነገር ግን ጥፋቱ የተደጋገመ እንደሆን እንደሳምንቶቹ
ብዛት ከ 1/4 ኛ እስከ ሙሉ ወርሀዊ ክፊያው ድረስ ቅጣት ይጣልበታል፤
12) በዚህ መመሪያ አንቀጽ 12.7 መሰረት የተቀመጡትን ተፈላጊ አነስተኛ ይዘት ያላሟላ ሪፖርት ካቀረበ
ለመጀመሪያ ጊዜ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ከአንድ ጊዜ በላይ ከደገመ የአንድ ወር 1/2 ኛ ክፍያው እንደ ቅጣት
ይጣልበታል፤
13) አማካሪው ውሸት ሪፖርት ካቀረበ ለመጀመሪያ ጊዜ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ከአንድ ጊዜ በላይ ካጠፋ
ያለምንም ቅድመ ማስጠንቀቂያ ምክንያቱ ተጠቅሶ የስራ ውሉ የሚቋረጥ ሆኖ ጥፋቱ እንደሚያስከትለው
ጉዳት ክብደት የስራ ፈቃዱ እና ከአንድ እስከ ሁለት አመት ይታገዳል፤
14) የቅድሚያ ክፍያ ዋስትና እና የስራ አፈጻጸም ዋስትና ጊዜው ያለፈ ተቋራጭ ዋስትናውን ሳያድስ
እንዲሰራ ያደረገ አማካሪ የሙያ ፈቃዱ ለተከታታይ 4 አመት የሚታገድ ይሆናል፤
15) የተጨማሪ ስራ መጠኑ በውሉ ከተቀመጠው በላይ ሆኖ በቅድሚያ ለባለቤቱ ሳያሳውቅ ስራው
እንዲቀጥል ያደረገ አማካሪ ለአራት ተከታታይ አመት ፈቃዱ የሚታገድ ሆኖ የልዩነቱን 30 በመቶ እንዲቀጣ
ይደረጋል ፡፡
10
15.10 .ከበጀትና ለውጥ ስራ ጋር የተያያዙ ጥፋቶች
1) አማካሪው ላልተሰራ ስራ የስራ ተቋራጩን የክፍያ ጥያቄ አጽድቆ ለቀጣሪው ክፍያ እንዲፈጸም ጥያቄ
ካቀረበ ውሉ የሚቋረጥ ሆኖ ለዛ ስራ ተጠየቀውን የክፍያ መጠን እንደ ቅጣት ይጣልበታል፤
2) አማካሪው የክፍያ ጥያቄ ቀርቦለት ከ 14 ቀናት በላይ ለቀጣሪው ሳያስተላልፍ ካዘገየ በዘገዩት ቀናት ልክ
የወቅቱ የባንክ የወለድ መጠን ተሰልቶ ሁለት እጥፍ እንደ ቅጣት ይጣልበታል፤
3) አማካሪው ለቀጣሪው ሳያሳውቅ የለውጥ ስራ ካዘዘ ለተከታታይ ሁለት አመት ፈቃዱ የሚታገድ ሆኖ
የሁለት ወር ክፍያው እንደ ቅጣት ይጣልበታል፤
4) አንቀጽ 14.3 እንደተጠበቀ ሆኖ አማካሪው ያዘዘው የለውጥ ስራ አስፈለጊ መሆኑን ቀጣሪው ካመነበት
ለለውጥ ስራው የወጣው ወጪ ከገበያ ዋጋ ጋር ተነጻጽሮብልጫ ካለው ልዩነቱ እንደ ቅጣት ይጣልበታል፤
5) አማካሪው እንደባለሙያ አይቶና መዝኖ የለውጥ ስራ አስፈለጊ መሆኑን ለቀጣሪው ማሳወቅ ሲገባ
ሳያሳውቅ የለውጥ ስራው ሳይሰራ ከታለፈ ችግሩን ለማስተካከልየሚወጣውን ወጪ 50 በመቶ እንደ ቅጣት
ይጣልበታል፤ በዚሁአንቀጽ መሰረት የሚጣልበት ቅጣት በምንም ዓይነት ከ 25000 ብር ማነስ የለበትም፡፡
11
ቅጣት የተጣለበት እና ቅሬታውን እንዲስተናገድ ይግባኝ ያቀረበ አማካሪ በሙያ ብቃት ፈቃዱ ላይ እግድ
ወይም ስረዛ የተጣለበትን ምክኒያት ባሉት 10 የስራ ቀናት ውስጥ የዘርፉ የሚመለከተው የስራ ክፍል በቀጥታ
ተጠሪ የሆነው የመንግስት አካል ለደንበኛው ማሰወቅ ግዴታ አለበት አለበት፡፡
20. የኮንስትራክሽን ዲዛይን አማካሪ ተግባርና ኃላፊነት
1. ማንኛውም የተመዘገበ የዲዛይን አማካሪ ወደ ሥራ ከመግባቱ በፊት ለሰራው ዲዛይን፣ ፕላንና የሥራ ዝርዝር
ወይንም ሶስቱንም አገልግሎት በጣምራ ሲያከናውን ሊደርሱ ለሚችሉ ጉዳቶች እና ግድፈቶች ለዲዛይን ሥራ
በወጡ ሕጎች መሰረት ከታወቀ የመድህን ድርጅት የጉዳት ማካካሻ ዋስትና ማቅረብ አለበት፣
2. የመተባበር ግዴታ
ማንኛውም ሰው ይህንን መመሪያ ከማስፈጸም አኳያ የመተባበር ግዴታ አለበት፡፡
21.መሪያውን ስለማሻሻል
ይህ መመሪያ ማሻሻል ሲያስፈልግ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሊያሻሽለው ይችላል፡፡
22 መመሪያው የሚፀናበት ጊዜ
ይህ መመሪያ በጠቅላይ ዓቃቢ ቁጥር ተሰጥቶ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጸና ይሆናል፡፡
12