Professional Documents
Culture Documents
Bible Study Mathewos
Bible Study Mathewos
አስረኛ ሳምንት
16. ስትጦሙም እንደግብዞች አትጠውልጉ ለሰዎች እንደ ጦመኛ ሊታዩ ፊታቸውን
ያጠፋሉና እውነት እላችኋለሁ ዋጋቸው ተቀብለዋል፡፡
ሀ.24. ለሰዎች እንደ ጦመኛ ሊታዩ ሲል ምን ማለት፡፡
እንደ ጾሙ ሰው እንዲያውቅላቸው እየፈለጉ ማለት ነው፡፡
17. አንተ ግን ስትጦም በስውር ላለው አባትህ እንጂ እንደ ጦመኛ ለሰዎች
18. እንዳትታይ ራስህን ተቀባ ፊትህንም ታጠብ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ
ያስረክብሃል፡፡
ሀ.25. ራስህን ተቀባ ፊትህንም ታጠብ ሲል ምን ማለት ነው?
- የተቀባና የታጠበ እንደማይታወቅበት አይታወቅብህ ሲል ነው፡፡
ሀ.26. ራስን በመቀባት ፊትንም በመታጠብ እንዳይታወቅ ማድረግ የሚገባው በየትኛው ጾምና
በየት ነው?
- በጾመ ፈቃድና በከተማ ነው፡፡
- በጌታ ጾምና በገዳም ውዳሴ ከንቱ የለበትም
ሀ.27. ራስህን ተቀባ የሚለውን ምን ተብሎ ሊተረጎም ይችላል?
- ፍቅርን ያዝ
- ንጽሕናን ገንዘብ አድርግ
- ትህትናን ያዝ
ሀ.28. ፊትህን ታጠብ የሚለው ምን ተብሎ ሊተረጎም ይችላል?
- በእንብዓ ንስሀ ታጠብ
19. ብልና ዝገት በሚያጠፉት ሌቦች ቆፍረው በሚሠርቁት ዘንድ ለእናንተ በምድር ላይ
መዝገብ አትሰብስቡ፡፡
ለ.1. ይህን አንቀጸ ምጽዋት ስለምን አመጣው?
ስለ 3 ነገሮች እነሱም፡-
1. እህሉን ነዳያን ከሚበሉት ብለው አኑረውት ነቀዝ ቢበላው ምቀኝነት ነውና፡፡
2. ልብሱን ነዳያን ከሚለብሱት ብለው አኑረውት ብል ቢበላው ምቀኝነት ነውና፡፡
3. ለክፉ ጊዜ ይሆነኛል ብሎ ማኖር እግዚአብሔርን ከዳተኛ ማድረግ ነው፡፡
- ምንም እጅ እግር ባያወጡለት ገንዘብ ማኖር ጣዖት ማኖር ነውና ህልፈት፣ ጥፋት
ያለበትን ምድራዊ ድልብ አታደልብ፡፡
20. ነገር ግን ብልም ዝገትም በማያጠፉት ሌቦችም ቆፍረው በማይሠርቁት ዘንድ ለእናንተ
በሰማይ መዝገብ ሰብሰቡ
21. መዝገብህ ባለበት ልብህ ደግሞ በዚህ ይሆናልና፡፡
ለ.2. ብልና ዝገት የሚጣጠፉት መዝገብ፣ ሌቦች፣ የተባሉት ትርጓሜ ምንድን ነው፡፡
- ውዳሴ ከንቱ ያለበት ምጽዋት አጋንንት
22. የሰውነት መብራት ዓይን ናት እንግዲህ ጤናማ ብትሆን ሰውነትህ ሁሉ ብሩህ ይሆናል፡
፡
- የስራህ መከናወኛ ዓይንህ ስለሆነ የቀና እንደሆነ ሥራህ ሁሉ የቀና ይሆናሉ፡፡
23. ዓይንህ ግን ታማሚ ብትሆን ሰውነትህ ሁሉ የጨለመ ይሆናል እንግዲህ በአንተ ያለው
ብርሃን ጨለማ ከሆነ ጨለማውስ እንዴት ይበርታ፡፡
- በተፈጥሮ የተሰጠህ ዓይንህ የታመመ ከሆነ ጨለማ እንደምን ይጸናብህ ይሆን
24. ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ማንም የለም ወይም አንዱን ይጠላል ሁለተኛውንም
ይወዳል ወይም ወደ አንዱ ይጠጋል፡፡ ሁለተኛውንም ይንቃል ለእግዚአብሔርና ለገንዘብ
መገዛት አትችሉም፡፡
- አንድ ቆላ ውረድ ሲለው ሌላው ደጋ ውጣ ቢለው እንዴት ለሁለቱም ሊታዘዝ
ይችላል
25. ስለዚህ እላችኋለሁ ስለ ነፍሳችሁ በምትበሉትና በምትጠጡት ወይም ስለሰውነታችሁ
በምትለብሱት አትጨነቁ ነፍስ ከመብል ሰውነትስ ከልብስ አይበልጥምን?
ለ.3. መብል መጠጥን ለነፍስ ልብስን ለሰውነት ሰጥቶ ለምን ተናገረ?
- የበሉት የጠጡት ደም ይሆናልና በዚህ ምክንያት ነፍስ ከስጋ ጋር ተዋሕዳ
ትኖራለችና ለዚህ ነው፡፡
- ምንም የምታፍር ነፍስ ብትሆን አጊጦ ከብሮ የሚታይ ሥጋ ነውና
ለ.4. ነፍስ ከመብል ሰውነትም ከልብስ እንዴት ሊበልጥ ይችላል?
- በተፈጥሮ
- በትንሳኤ
ለ.5. የምትበሉትና የምትጠጡት እንዲሁም የምትለብሱት ሲል ምን ዓይነት ትርጓሜ
ይኖረዋል?
- ሥጋወ ደሙና እንዲሁም ልጅነት የሚያሰጥ በመሆኑ
26. ወደ ሰማይ ወፎች ተመልከቱ አይዘሩም አያጭዱምም በጎተራም አይከቱም የሰማዩ
አባታችሁም ይመግባቸዋል እናንተ ከእነርሱ እጅግ አትበልጡምን?
ለ.6. ወደ ሰማይ ወፎች ተመልከቱ ማለት ምን ማለት ነው?
- አብነት አድርጎ ማለት ነው፡፡
ለ.7. እናንተ ከእነርሱ እጅግ አትበልጡምን ሲል በምንድን ነው?
- በተፈጥሮ
ለ.8. የሰማይ ወፎች የሚለው ትርጓሜ (ምሳሌያዊ) ምንድን ነው?
- እስራኤላውያን የሰማይ መና ተመግበዋልና
- ትንቢት ያልተነገረላቸውን፣ ሱባኤ ያልተቆጠረላቸውን፣ ሰማያዊ አባታችሁ ሥጋውን
ደሙን የሚመግባቸው አሕዛብን አብነት አድርጉ፡፡
27. ከእናንተ ተጨንቆ በቁመቱ አንድ ክንድ መጨመር የሚችል ማነው?
ለ.9. በቁመቱ አንድ ክንድ መጨመር ማለት ምን ማለት ነው?
- ካላጠርኩ ልርዘም ብሎ አንድ ክንድ ራስን ማርዘም
- በቃሁ ነቃሁ ብሎ ሥልጣነ ክህነትን ለራስ ገንዘብ ማድረግ
28. ስለ ልብስ ስለ ምን ትጨነቃላችሁ? የሜዳ አበቦች እንዴት እንደሚያድጉ ልብ
አድርጋችሁ ተመልከቱ አይደክሙም አይፈትሉምም
29. ነገር ግን እላችኋለሁ ሰሎሞንስ እንኳ በክብሩ ሁሉ ከነዚህ አንድ አንዱ አለበሰም
ለ.10. ሰሎሞን አበባ ያለበት፣ ሐረግ የተሳበበት ወርቀ ዘቦ ግምጃ ይለብስ እንደነበር ለምን
በክብሩ ከነዚህ እንደ አንዱ አለበሰም አለ?
- የሱ የባሕርዩ አይደለም የነሱ ግን የባሕርያቸው ነውና
- እሱ እነሱን አብነት ነው እነዚያ ግን እሱን አብነት አድርገው አይደለፈምና
ለ.11. ስለ ልብስና ስለ የሜዳ አበቦች ያለው ትርጓሜ ምንድን ነው?
- ልብስ ልጅነትን ያሳያል
- የሜዳ አበቦች አህዛብን ያመለክታል
30. እግዚአብሔር ግን ዛሬ ያለውን ነገም ወደ እቶን የሚጣለውን የሜዳን ሳር እንዲህ
የሚያለብሰው ከሆነ እናንተ እምነት የጎደላችሁ እናንተንም ይልቁን እንዴት?
ለ.12. ዛሬ ያለውን ነገም ወደ እቶን የሚጣለውን ሲል ምን ማለቱ ነው?
- ማገዶ የሚሆነውን እንጨት (ዛሬ በልምላሜ ያለውን)
- ዛሬ በተድላ የሚኖረው ነገ ወደ ገሃነም የሚጣለው (ከሀድያን)
31. እንግዲህ ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ
32. ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ ይህ ሁሉ እንደሚያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ
ያውቃልና
ለ.13. አሕዛብ ሲል ምን ማለቱ ነው?
- ከምግባር ከሃይማኖት ውጪ የሆኑ
33. ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግስት ጽድቁንም ፈልጉ ይህም ሁሉ
ይጨመርላችኋል፡፡
ለ.14. የእግዚአብሔር መንግስትና ጽድቅ የተባሉት ምንድን ናቸው?
- ሀይማኖትና ምግባር
- ልጅነትና መንግሥት ሰማይ
34. ነገ ለራሱ ይጨነቃልና ለገነ አትጨነቁ ለቀኑ ክፋቱ ይበቃዋል፡፡
ለ.15. ነገ ለራሱ ይጨነቃል ማለት ምን ማለት ነው?
- የነገውን ነገ ታስቡታላችሁ ማለት ነው፡፡
- ለነገ ያጸናናል ብላችሁ አብዝታችሁ አትመገቡ የነገውን ነገ ትመገቡታላችሁና፡፡
- ነገ እንናዘዛለን ብላችሁ ኃጢአታችሁን አታሳድሩ የነገረውን ነገ ትናገሩታላችሁና ሰል
ነው፡፡