Professional Documents
Culture Documents
( - WPS Office
( - WPS Office
Page - 1 -
የአበዳሪና ተበዳሪ ግዴታዎች፡- አበዳሪና ተበዳሪ የራሳቸው የሆኑ ሊያከብሯቸው የሚገቡ
ግዴታዎች አሉባቸው፡፡ በቅድሚያ የአበዳሪው ግዴታዎችን ስናይ ሕጉ የአበዳሪውን ግዴታዎች
በተመለከተ የሽያጭ ውልን በሚደነግገው ክፍል ላይ የሻጩ ግዴታዎች ተብለው የተገለፁት
ደንቦች በአበዳሪ ላይ ተግባራዊ ይሆናሉ ይላል፡፡ በፍትሐብሔር ሕጉ የሻጭ ግዴታዎች ናቸው
የተባሉት ደግሞ የሚከተሉት ናቸው፡፡
Page - 2 -
የብድር ማስረጃ በሚል ርእስ የሚከተለውን ደንግጓል፡-
(1) በብድር የተሰጠው ገንዘብ ከብር 500 በላይ ሲሆን የብድሩን ውል በፅሑፍ ወይም በፍርድ
ቤት በተደረገ የእምነት ቃል ወይም መሐላ ካልሆነ በስተቀር ለማስረዳት አይቻልም፡፡
(2) ለብድር ውል ማናቸውም ሌላ ዓይነት ማስረጃ ለማቅረብ አይቻልም ፡፡ (3) እንዲሁም ከብር
500 የበለጠ ገንዘብ የመክፈል ነገር በዚህ ዓይነት ይፈፀማል፡፡ በዚህም መሰረት የብድሩ
መጠን ብር 500 እና ከዛ በታች ከሆነ በማንኛውም ዓይነት ማስረጃ ለምሳሌ በቦታው የነበረ
የሰው ምስክር በመስማት ማረጋገጥ የሚቻል መሆኑን እና መጠኑ ከዛ በላይ ከሆነ ግን ከሦስቱ
የማስጃ ዓይነቶች መካከል በአንዱ ካልሆነ በስተቀር በሌላ በምንም መንገድ ማረጋገጥ
የመማይቻል መሆኑን ነው መረዳት የሚቻለው፡፡ እነዚህን ሦስት የማስረጃ ዓይነቶች ቀጥለን
እንመልከት፡፡
የመጀመሪያውና የበለጠ አስተማማኝ የሆነው ማስረጃ የፅሑፍ ማስረጃ ነው፡፡ ይህም ማለት ገና
ከጅምሩ የብድር ውሉ ሲደረግ በፅሑፍ የተደረገ ሲሆን ያንን ፅሑፍ ለፍርድ ቤት በማቅረብ
ማስረዳት ይቻላል፡፡ በሌላ አነጋገር ከብር 500 በላይ የሆነ የብድር ውል በፅሑፍ እንዲሆን ሕጉ
አስገዳጅ የሚመስል ድንጋጌ ያስቀመጠ በመሆኑ ከላይ ካነሳነው የውል አመሰራረት መርሆች
መካከል የተለየ ፎርም የሚፈልግ መሆኑን ማየት ይቻላል፡፡ ሁለተኛው የማረጋገጫ መንገድ
በፍርድ ቤት በተደረገ የእምነት ቃል ነው፡፡ ይህም ማለት ተበዳሪው በፍርድ ቤት ቀርቦ በከሳሹ
የቀረበበትን ክስ ማለትም ከከሳሹ ገንዘብ የተበደረ መሆኑን፣ መጠኑ ምን ያክል እንደሆነ
በማያሻማ መንገድ ካመነ በቀላሉ የብድሩ መኖር የሚረጋገጥ ይሆናል፡፡ ሦስተኛውና
የመጨረሻው የማረጋገጫ መንገድ በመሐላ የማረጋገጥ ሂደት ነው፡፡ መሐላ ማለት በክርክር
ወቅት አንድ ተከራካሪ ወገን በሚያቀርበው ማስረጃ ወይም በሚናገረው ፍሬ ነገር እውነትነትን
ለማረጋገጥ ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀ ቅፅ ላይ የሚሰጡት ማረጋገጫ ነው፡፡
የብድር መመለሻ ጊዜ፡- ብድር ውል እንደመሆኑ መጠን ለተዋዋይ ወገኖች ሰፊ ነፃነት መሰጠት
አለበት፡፡ በመሆኑም ሕጉ ስለብድር መመለሻ ጊዜ በተዋዋይ ወገኖች የተወሰነ ጊዜ በሚኖርበት
ወቅት ይህንኑ ዕውቅና በመስጠት ክፍያው በዛ ጊዜ መሆን እንደሚገባው ሕጉ አፅንኦት
Page - 3 -
ሰጥቶበታል፡፡ ከዚህም ባለፈ ብድሩ ወለድ የሌለበት ከሆነ የተበደረውን ገንዘብ ለመመለስ
ማሰቡን ለአበዳሪው ከአንድ ወር በፊት አስታውቆ የመመለሻ ጊዜው ከመድረሱ በፊት
ሊመልስለት እንደሚችልም ሕጉ ይደነግጋል፡፡ የብድሩ መመለሻ ጊዜ በተዋዋይ ወገኖች
ያልተወሰ በሚሆን ጊዜ ሕጉ ብድሩ በምን ያክል ጊዜ ውስጥ ሊከፈል እንደሚገባው ደንግጓል፡፡
ይኼውም አበዳሪው መልስልኝ ሲል ከጠየቀበት ቀን አንስቶ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ መመለስ
እንዳለበት ተደንግጓል፡፡ ተበዳሪውም በአበዳሪው ሳይጠየቅ መክፈል ቢፈልግ ለመክፈል
ያለውን ሀሳብ ከአንድ ወር በፊት ካስታወቀ በኋላ ዕዳውን መመለስ እንደሚችል እንዲሁ
ተደንግጓል፡፡
የብድር አከፋፈል (የሚከፈለው ነገር)፡- በብድር አመላለስ ወቅት ሌላው ግለፅ መሆን ያለበት
ጉዳይ ብድሩ በየትኛው ሀገር የገንዘብ ዓይነት ነው? ከብድሩ በኋላ የምንዛሬ ዋጋ መለዋወጥ
ቢያጋጥምስ ምን ይሆናል? የሚለው ነው፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ የፍትሐብሔር ሕጉ ግልፅ
ድንጋጌዎች አሉት፡፡ በዚህም መሰረት የብድር ውሉ የተደረገው በኢትዮጵያ ብር ከሆነ ብድሩ
በሚመለስበት ወቅት ባለው ሕጋዊ የኢትዮጵያ የመገበያያ ገንዘብ ወይም ለዚህ የገንዘብ መጠን
Page - 4 -
የሚተካ የውጭ ምንዛሬ በማቅረብ ከዕዳው ነፃ እንደሚሆን ተደንግጓል፡፡ የሚከፈለውን የገንዘብ
መጠን በተመለከተ የብድር ውሉ በሚከናወንበት ጊዜ በትክክል የተበደረውን ያክል እንጂ ሌላ
ነገር እንደማያካትትና በመሀል ሊያጋጥም የሚችለውን ወይም ያገጠመውን የገንዘቡ ዋጋ
መለዋወጥ ግምት ውስጥ መግባት እንደሌለበትም ሕጉ አያይዞ ይገልፃል፡፡ ብድሩ በውጭ
አገር ገንዘብ ተደርጎ ከነበረ ደግሞ ብድሩ በሚከፈልበት ጊዜ በዛ አገር ሕጋዊ መገበያያ በሆነው
የገንዘብ ኖት መከፈል ያለበት ሲሆን መጠኑም የተበደረውን ያክል ብቻ መሆን እንዳለበት ሕጉ
አመልክቷል፡፡ የብድር ውሉ የተደረገው ከገንዘብ ውጪ ባሉ የሀብት ዓይነቶች በሚሆንበት ጊዜ
ለምሳሌ፡- ለምግብ የሚሆኑ ነገሮች፣ ሸቀጦች ወይም መአድናት ሲሆኑ ተበዳሪው በተበደረው
ልክ ብዛቱንና ዓይነቱን በመክፈል ከዕዳው ነፃ ይሆናል፡፡ በተመሳሳይ መልኩ ከብድሩ በኋላ
በሚኖር የዋጋ መለዋወጥ የብድድር አመላለሱን መጠንና ዓይነት ላይ የሚያሳድረው ተፅእኖ
የለም፡፡
Page - 5 -