Download as docx, pdf, or txt
Download as docx, pdf, or txt
You are on page 1of 2

ቀን ነሐሴ 28/2015 ዓም

ከርዕሰ አድባራት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን አካባቢ
ወጣቶችና ነዋሪዎች ምዕመናን የቀረበ የቅድመ ጥንቃቄ ማመልከቻ

በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ለጉለሌ ክፍለ ከተማ ለሽሮሜዳ መህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ ጽ/ቤት

በአዲስ አበባ ከተማ መስተደድር ለጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት

በቅድሚያ የአክብሮት ሠላምታችንን እያስቀደምን እኛ ስማችን ከዚህ ማመልከቻ በታች


የተጠቀስነው በዚሁ በርዕሰ አድባራት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን ነዋሪዎች
ስንሆን እነሆ በደብራችን ከ 150 አመታት እድሜ ያስቆጠረ እጅግ ጥንታዊ እና ታሪካዊ ቅርስ የሆነውን መንበር
ያለበቂ ጥናት በተለይ እንደሚታወቀው ቤተክርስቲያኑ ባለፎቅ እንደመሆኑ መጠን እና በጣውላ የተከፋፈለ
እንደመሆኑ መጠን መንበሩም ከመቅደሱ ከስድስት እስከ ሰባት ሜትር ጥልቀት መነሻ የተሰራ ነው የሚል
የታሪክ ገለጻ እያለ ፦

በትክክለኛ ባለሙያዎች ተገቢ የሆነ ጥናት ሳይከናወን ፣

በማህበረ ካህናቱ እና በምእመናኑ ተገቢ የሆነ የማወያየት ስራ ሳይሰራ ፣

ታላቅ ቅርስ ለሆነው ነባር መንበር የሚያርፍበት ቦታ በተገቢው ሁኔታ ሳይዘጋጅ ፣

በቤተክርስቲያን የአስተዳደር ሂደት ውስጥ ዋና ውሳኔ ሰጪ የሆነው የሰበካ ጉባኤ ውሳኔና ስምምነት በሌለበት ፣

በአጠቃላይ በማንአለብኝነት ለታሪክ እና ለቅርስ ተገቢውን ትኩረት እና ጥበቃ ባልተከናወነበት ከምንም በላይ
ጥልቅ ምርምር እን ጥናት ሳይከናወን ለዋናው ቤተመቅደስ ሊፈጥር የሚችለው ጉዳት ባልተጠናበት መልኩ
መንበሩን ቆርጠን እናነሳለን በሚል እንቅስቃሴ ማህበረ ካህናቱን እና ህዝቡን በሚያውክ ሁኔታ የቅርስ
ውድመት ለመፈጸም እንቅስቃሴ እየተከናወነ ስለሆነ ከምንም በላይ ሰላም ወዳድ የሆነው ማህበረ ካህናት እና
ምእመናኑ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ስለሆንን ከወቅታዊ ጉዳይ አንጻር ተገቢ የሆነ የማወያየት እና የጥናት ጉዳይ
መቅደም ስላለበት የቀጠናችን የፖሊስ ጽ/ቤት ጉዳዩን በቅርበት እንዲከታተል እና የጉዳዩ ባለቤት የሆኑት
ጠቅላላ ከምንም በፊት ሰላም መቅደም ስላለበት ተገቢውን የማግባባት ስራ እንዲሰራ እያሳሰብን ትልቅ ጉዳይ
እና ታሪክ ከምንም በላይ የ 150 አመታት በላይ ቅርስ ለሆነ ቅዱስ ንዋየቅዱሳት ተገቢ የሆነ ጥናትና ጥበቃ
ከምንም በላይ ፍጹም መግባባት እንዲቀድም እያሳሰብን በዚህ መሀል ለመስከረም 1 የሚከበረውን የመልአኩ
የቅዱስ ራጉኤል እና የአዲስ አመት በአል በሰዎች ዘንድ ሙገሳ ለማግኘት ሲባል በድጋሚ ለነባሩ ቅርስ ተገቢ
ማሳረፍያ ባልተዘጋጀበት በሚመለከታቸው ባለሙያዎች ሊከሰት የሚችለው ጉዳት ባልታወቀበት ለሚደርሰው
የታሪክ እና የቅርስ ውድመት ተያይዞ ለሚከሰተው የሠላም መደፍረስ ሙሉ በሙሉ የቤተክርስቲያኒቱ
አስተዳደር አካላት ተጠያቂ መሆናቸውን ለማሳሰብ እየወደድን ይህን ማመልከቻ ከአንድ ገጽ የአካባቢው
ነዋሪዎች ፊርማ ጋር አያይዘን የላክን መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ግልባጭ ፦

ለመንበረ ፓትርያርክ የቅርስ ጥበቃ እና ንዋየ ቅድሳት ጥበቃ ጽ/ቤት

ለአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት ጽ/ቤት

በአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ለአራዳና ጉለሌ ክፍላተ ከተማ ቤ/ክ ጽ/ቤት

ለፌዴራል ቅርስና አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት

ለአዲስ አበባ ከተማ ቅርስና አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት

ለጉለሌ ክፍለ ከተማ ቅርስና አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት

ለጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ቅርስና አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት

You might also like