Download as pdf or txt
Download as pdf or txt
You are on page 1of 3

የአማራ ክልል የፍትሕ ባሇሙያዎች ማሰልጠኛና የሕግ

ምርምር ኢንስቲትዩት የሕግ መፅሔት

ቅፅ ፭ ሰኔ ፪ሺ፲
Vol. 5 June 2010

ዋና አዘጋጅ
ጋሻዬ ቢያዴግ (LLB, LLM) (የህግ ጥናትና ምርምር አስተባባሪ)

የኢንድቶሪያል ኮሚቴ አባላት

ጋሻው ዘውደ (LLB, LLM) ዋና ዲይሬክተር

ፀጋዬ ወርቅአየሁ (LLB, LLM) ጠቅላይ ፍርዴ ቤት ዲኛ)

ኢዮስያስ ዯምሴ (LLB, LLM) ክልል አቃቤህግ)


ምህረት አለማየሁ (LLB, LLM) ባህር ዲር ዩኒቨርስቲ ህግ ትምህርት ቤት ም/ዱን)
ማውጫ ገፅ
1. የዋና ዲይሬክተር መልዕክት ........................................................................ .......................... I

2. በኢትዮጵያ የውል ምዝገባ ለቤት ሽያጭ ውል መሰረታዊ እና አስገዲጅ መስፇርት


ነውን? (በሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔወች ዋቢነት የቀረበ) .................................. ............................. 1
ወርቅነህ አለሙ

3. በአዱሱ የአማራ ክልል የገጠር መሬት አስተዲዯር ሕግ ላይ የሚታዩ በጎ ጎኖች


እና ችግሮች............................................................................................... ............................ 25
በሪሁን አደኛ

4. በኢትዮጽያ የወንጀል ፍትህ አስተዲዯር ውስጥ በጊዜ ቀጠሮ መፇቀዴ ወይም በዋስትና
መከልከል፣ በጥበቃ ስር ማቆየት የጽንሰ ሀሳብ ይዘትና ክርክር አመራር .............................. 57
ሰለሞን ጎራው

5. በወንጀል ይግባኝ ሥርአት የእስራት ቅጣት እንዲይፇጸም ማገዴና አመልካችን በዋስትና


የመልቀቅ ጽንሰ ሀሳብ ......................................................................................................... 106
ሳባ ዯመቀ

6. ዯጋጋሚ ወንጀለኛነት እና የቀዴሞ የወንጀል ሪከርዴ የህግ ማዕቀፍ እና ተግባራዊ


አፇጻጸም በአማራ ክልል ...................................................................... .............................. 139
ይማም ሰይዴ

7. ተከሳሽ በሌለበት የወንጀል ክርክር ስለማዴረግ፡ ህጉና አፇፃፀሙ በአማራ ክልል ፍርዴ
ቤቶች ................................................................................................................................. 164
ታፇሰች ወልዳ

8. በምርመራ ወቅት በፖሊስ ጣቢያ የተሰጠ የምስክሮች ቃል በፍርዴ ቤት እንዱቀርብ


ስለሚዯረግበት የህግ አግባብ፣ በፍርዴ ቤት ያለው ተቀባይነትና ተግባራዊ አፇጻጸሙ በአማራ
ክልል ፍርዴ ቤቶች ............................................................................. ............................. 187
ሰለሞን ተገኝወርቅ

9. በሴቶች ላይ የሚፇጸሙ ፆታዊ ጥቃቶች ፍትሃብሔራዊ መፍትሔዎች በኢትዮጵያ


የህግ ማዕቀፍ .................................................................................................................... 205
ይበልጣል ይመር

10. የመሬት ይዞታ ይገባኛል እና የይርጋ መከራከሪያ በአማራ ብሔራዊ ክልል የመሬት አዋጅ
ከፌዯራል መንግስት የህግ ማዕቀፍ አንጻር ............................................................................ 236
ጋሻዬ ቢያዴግ
የዋና ዳይሬክተር መልዕክት

የአብክመ የፍትህ ባሇሙያዎች ማሠልጠኛና የህግ ምርምር ኢንስቲትዩት በደንብ ቁጥር


74/2003 ዓ.ም መሠረት ሲቋቋም የፍትህ ባሇሙያዎች በእውቀት፣ በክህሎት፣ በስነ-ምግባርና
አመሇካከት ብቁና የህዝብ አገልጋይነት ስሜት የተላበሱ እንዲሆኑ ሇማስቻል ተከታታይነት
ያሇውና አዳጊ ስልጠና መስጠት እና የክልላችን የፍትህ ስርዓት ተደራሽነት፣ ከቅልጥፍና፣
ጥራት፣ ውጤታማነትና ተገማችነት ጋር የተያያዙ ችግሮችን ሳይንሳዊ በሆነ የህግ ጥናትና
ምርምር በመሇየት የመፍትሄ ኃሳቦችን ማመንጨትና ሇፍትህ ስርዓቱ መሻሻል አስተዋፅኦ
ማድረግ ነው፡፡ በዚህ መሠረት በቅድመ ስራና ስራ ላይ ከ8,000 በላይ ባሇሙያዎችን
በማሠልጠን እና በማስመረቅ ሇፍትህ ስርዓቱ ላይ የሰው ኃብት ልማት አቅም ግንባታ ላይ
አትኩሮ በመስራት ሇፍትህ ስርዓቱ ውጤታማነት ጉልህ አስተዋፅኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡

ከአጫጭር ጊዜ ስልጠና አኳያ የባሇድርሻ አካላትን ፍላጐት እና ጥያቄ መሠረት ያደረገ


የፍላጐት ዳሰሳ ጥናት ተሰርቶ በዚህም ላይ የተመሠረተ ስርዓተ ትምህርት ተቀርጾ ሇዚህ
የሚመጥን የስልጠና ማንዋል ተቀርጾ በተቀናጀና በተደራጀ አኳኃን በተሇያዩ ጭብጦች ላይ
አትኩሮ ከ16,000 በላይ የሚሆኑ ባሇሙያዎችን በማሰልጠን ውጤታማነቱን አሳድጓል፡፡

ባሇፉት ሁሇት ዓመታት የባሇድርሻ ፍላጐት እና ጥያቄ እንዲሁም በኢንስቲትዩቱ መነሻነት በ50
ርዕሰ ጉዳዩች ላይ የጥናትና የምርምር ስራ በማከናወን የህግ መጽሄት ቁጥር 1 እና 2,3,4
ጥቅም ላይ እንዲውል ጥረት ተደርጓል፡፡ ይህም ሇክልለ የፍትህ ስርዓት መሻሻል ጉልህ
አስተዋፅኦ አበርክቷል፡፡ በዚህ በጀት ዓመትም የጥናትና የምርምር ስራዎች የተሰሩ ሲሆን
በኢዲቶሪያል ቦርድ ከሚታወቁና ከሚያግባቡ የጥናትና የምርምር ስራዎች መስፈርትና መሇኪያ
አንፃር ታይተውና ተመርምረው ተቀባይነትና ይሁንታ አግኝተው ሇህትመት ብቁ ናቸው የተባለ
የምርምር ስራዎችን በዚህ መፅሄት በማሳተም የኢንስቲትዩቱ ሇ5ኛ ጊዜ የሆነውን ቁጥር 5
የህግ መፅሄት በአክብሮት ስናቀርብ በታላቅ ደስታ ነው፡፡ በመሆኑም ይህን ስራ የሰሩትን
የውስጥና የውጭ ተጋባዥ ተመራማሪዎች በአርትኦት የተሳተፉት ሙህራንና የኢዲቶሪያል
ቦርድ አባላት በራሴና በኢንስቲትዩቱ ስም ከፍ ያሇ ምስጋናየን እያቀረብኩ ሇአንባቢያን መልካም
ንባብ እንዲሆንላችሁ ልባዊ ምኞቴን ሇመግሇፅ እዋዳሇሁ፡፡

አመሰግናለሁ!

You might also like