Professional Documents
Culture Documents
(LLB, LLM)
(LLB, LLM)
በሰለሞን ተገኘወርቅ1
አጽርኦተ ይዘት
በባለሙያዎች ዘንድ ከላይ የተመለከቱት ሁለት ዓይነት ግንዛቤዎችና አሰራሮች ቢኖሩም የህግ አውጭው
ሀሳብና የድንጋጌው አላማ በፖሊስ የተሰጠ የምስክርነት ቃልን ፍርድ ቤት ሊመለከተው የሚችለው
ሰነዱ ኮፒ ተደርጎ እንደ ጽሁፍ ማስረጃ ዓይነት ሳይሆን የዓቃቤ ህግ ምስክሮች በፍርድ ቤት ቀርበው
የሰጡት ቃል ቀደም ሲል ለመርማሪ ፖሊስ ከሰጡት ቃል ጋር የሚቃረን /አስጠቂ/ ሲሆን ይህንኑ
1
ሰለሞን ተገኘወርቅ (LLB, LLM) ቀደም ሲል በአብክመ ፍትህ ባለሙያዎች ማሰልጠኛና ህግ ምርምር ኢንስቲትት የሰሩ ሲሆን
በአሁን ወቅት በአብክመ ፍትህ ቢሮ የክልል ዐቃቤ ህግ ሆነው በመስራት ላይ ይገኛሉ፡፡
በፍርድ ቤት የተሰጠውን ምስክርነት ውሸት መሆኑን ለማስተባበል ሲባል ፍርድ ቤቱን አስፈቅዶ ዐቃቤ
ህግ ወይም ተከሳሽ በመሪ ጥያቄ ወይም በመስቀለኛ ጥያቄ አማካኝነት የተሰጠውን የምስክርነት ቃል
ማስተባበል እንዲችሉ በማሰብ የተቀረጸ ድንጋጌ እንደሆነ ግንዛቤ መያዝ ይገባል፡፡
ማስረጃ የአንድን አከራካሪ ጭብጥ መኖር ወይም አለመኖር በማረጋገጥ የዳኛን አእምሮ
በማሳመን ወደ አንድ ድምዳሜ ላይ የሚያደርስ ፍሬ ነገር ነው2፡፡ በወንጀል ምርመራ ሂደት
ውስጥ ጠንካራ የሆነ የወንጀል ምርመራ ስርዓት አለ ሊባል የሚችለው ስለወንጀሉ አፈጻጸም
በሚመለከት በዝርዝር ሊያስረዱ የሚችሉ ማስረጃዎችን ሰብስቦ አጥፊውን ፍርድ ቤት አቅርቦ
ጥፋተኛ ለማስባል የሚያስችል አሳማኝና በቂ ማስረጃ በህግና በስርዓት መሰብሰብ ሲቻል ነው፡፡
በወንጀል ፍትህ አስተዳደር ውስጥ የአንድን የወንጀል ድርጊት መፈጸምና አለመፈጸም፣
የወንጀል ፈጻሚውን ማንነት ለመለየት የሚያስችል አግባብነትና ተቀባይነት ካላቸው ከተለያዩ
የማስረጃ ዓይነቶች ውስጥ ምስክርነት (የሰው ማስረጃ) ዋነኛው ነው፡፡ ስለሆነም ምስክርነት
ከአንድ የወንጀል ድርጊት ጋር በተያያዘ የወንጀል አድራጊውን ሁኔታ በአግባቡ ለዳኛው
በማስረዳትና አጥፊን ከንጹህ በመለየት ሂደት ውስጥ ትልቅ ድርሻ ያለው ነው፡፡ ምክንያቱም
ምስክርነት በወንጀል ጉዳይ ክርክር በሚደረግበት ጊዜ ወንጀሉ መቼ ተፈጸመ፣ የት ተፈጸመ፣
እንዴት ተፈጸመ፣ በምን ተፈጸመ፣ በማን(እነማን) ተፈጸመ፣ በምን ምክንያት ተፈጸመ
የሚሉትን የወንጀል ድርጊቱን ዋና ዋና ማቋቋሚያ ፍሬ ነገሮችና ጭብጦች ለመለየትና በግልጽ
ለማሳየት የሚያስችል በመሆኑ ነው3፡፡
ምስክርነት ከሌሎች ማስረጃዎች አንጻር ሲታይ ምናልባትም ረጅም እድሜ ያስቆጠረና በፍርድ
ቤትም የወንጀሉን አፈጻጸም በአግባቡ በማረጋገጥ በኩል አግባብነት ያለው ማስረጃ ነው4፡፡
በተለይም ምስክርነት እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ታዳጊ ሀገራት በወንጀል ፍትህ ስርዓቱ ውስጥ
ክርክሮችን ለማስረዳት ያለው ድርሻ ከፍተኛ ነው፡፡ ምክንያቱም በሀገራችን ሳይንሳዊ የወንጀል
የምርመራ ዘዴን ተጠቅሞ የቴክኒክ ማስረጃዎችን ለመሰብሰብ ከፍተኛ የሆነ የእውቀት፣
የዘመናዊ መሳሪያ እና የሰለጠነ የሰው ሀይል እጥረት የሚታይ በመሆኑ ነው፡፡ ታዲያ
ምስክርነት አጥፊን ከንጹህ ለመለየት እንዲያስችል በፍርድ ቤት የሚቀርቡ ምስክሮች የስነ-
2
ታጠቅ ታደሰ፣ የማስረጃ ህግ መሰረተ ሀሳቦች፣ አዲስ አበባ ዩ ኒቨርስቲ መጻህፍት ማእከል፣ 1997 ዓ.ም፣ገጽ 1
3
ዝኒ ከማሁገጽ 161-163
4
ዝኒ ከማሁ ገጽ 161-165
ስርዓት ህጉ በሚፈቅደው መሰረት ምስክሮቹ እውነት ለመናገራቸው ቃለ-መሀላ ፈጽመው
ምስክርነታቸውን መስጠት ይኖርባቸዋል፤ ምስክርነታቸውም ስነ-ስርዓት ህጉ በሚፈቅደው
መሰረት የተለያዩ ጥያቄዎችን በማለፍ የተፈተነና ተዓማኒ መሆን ይገባዋል፡፡
ምንም እንኳን ምስክርነት ለወንጀል ክርክር ትልቅ የማስረጃ ምንጭ ሆኖ የሚያገለግል ቢሆንም
በተለይም በአሁኑ ወቅት የምስክር ቃል በባህሪው ብዙ ህጸጾች ያሉበትና ተዓማኒነቱን ሊቀንሱ
የሚችሉ ምክንያቶች እየተስተዋሉ ነው፡፡ ምስክርነት በተፈጥሮው በሰዎች የስሜት ህዋሳት ላይ
ተመስርቶ የሚሰጥና በሰው የማስታወስ ችሎታ ላይ የተመሰረተ ስለሆነ የራሱ ጉድለት ያለበት
ነው፡፡ ስለሆነም የሰው ምስክርነት እንደ ማስረጃ ከመወሰዱ በፊት የተለያዩ ስርዓቶችን ማለፍ
ይኖርበታል፡፡ አንድ ምስክር በፖሊስ ጣቢያ ወይም በፍርድ ቤት ቀርቦ ምስክርነቱን ከመስጠቱ
በፊት ምስክሩ በአካልና በአእምሮ ብቁ መሆን ይኖርበታል፡፡ ይህም ማለት ምስክሩ
የተፈጸመውን ድርጊት ለመረዳት የሚችል መሆኑ፣ ድርጊቱን ተገንዝቦ በማስታወስ
ለሚመለከተው አካል (ለፍርድ ቤት ወይም ለመርማሪ ፖሊስ) እንደገና ለመግለጽ የሚችል
መሆኑ፣ ምስክሩ ቃለ-መሀላ የሚፈጽም (ፍርድ ቤት) እና እውነት በመመስከርና ሀሰት
በመመስከር መካከል ያለውን ልዩነት የሚረዳ መሆን ይገባዋል፣ የምስክሩ የአካልና የአእምሮ
ብቃት የሚቀርብለትን ጥያቄ ለመረዳትና ለመመለስ የሚያስልች መሆኑ መታየት እንዳለበት
ጠቅላላ የማስረጃ ህግ መርህ ያስገነዝባል5፡፡
5
Gary L. wells and Elizabeth A.፣ Eye witness testimony፣ https// public.psych iastate edu/glweslannual review፣ 2003 ገጽ 53
የተወሰደው ሰኔ 15/2010 ዓ.ም
በሀሰት በመደራጀት አላግባብ በሀሰት በመክሰስ /በመመስከር/ እንዲቀጡ ሊያደርጉ ይችላሉ፣
በተመሳሳይ ወንጀል የፈጸሙ ግለሰቦች ለድርጊታቸው ተገቢውን ቅጣት እንዳያገኙ በማሰብ
በሀሰት በመከላከያ ምስክር በመደራጀት ወንጀል የፈጸሙ ሰዎች ነጻ እንዲወጡ ሊያደርጉ
ይችላሉ6፡፡ እንዲሁም ምስክሮች ጉዳዩን በሚመለከተው ፍርድ ቤት ቀርበው ከመመስከራቸው
በፊት በሞት ሊለዩ ይችላሉ፣ በጽኑ ህመም ምክንያት ፍርድ ቤት ቀርበው መመስከር
የማይችሉበት ሁኔታ ያጋጥማል፣ ከሀገር ሊወጡ ይችላሉ፣ ቀደም ሲል ካስመዘገቡት አድራሻ
ሊጠፉ ወይም ሊሰወሩ ይችላሉ፡፡ እነዚህና ሌሎች መሰል ምክንያቶች በሰው ምስክር ላይ
የሚታዩ ጉድለቶች ናቸው፡፡
ታዲያ ምስክርነት እንደዚህ ዓይነት ህጸጾች የሚታዩበት ስለሆነ ችግሩን ለመቀነስ የወንጀል ስነ-
ስርዓት ህጉ የምስክሮች ቃል የሚጣራበትንና የሚፈተንበትን ስርዓት ዘርግቶ እናገኘዋለን፡፡
የምስክሮች ቃል ተዓማኒ እንዲሆን ምስክር በሚሰማበት ወቅት በአግባቡ መፈተን ይኖርበታል፡፡
ማስረጃው የሚፈተነው በዋና ጥያቄ፣ በመስቀለኛ ጥያቄ፣ በመሪ ጥያቄ ወይም በማጣሪያ ጥያቄ
ሊሆን እንደሚችል በወንጀለኛ መቅጫ ስነ-ስርዓት ህጉ ላይ ተመልክቷል፡፡ በመስቀለኛ ጥያቄ
ወይም በመሪ ጥያቄ የምስክር ቃል ሲፈተን የጥያቄው ዋና ዓላማ የተሰጠውን ምስክርነት
ማስተባበልና በፍርድ ቤቱ ዘንድ ተዓማኒ ተደርጎ እንዳይታይ ለማድረግ ነው፡፡ የምስክርነትን
ቃል በመስቀለኛ ጥያቄ ወይም በመሪ ጥያቄ የሚፈተንበትና የሚስተባበልበት ዘዴ
በእንግሊዘኛው “impeachment” ተብሎ የሚታወቅ ነው7፡፡ የምስክሩ ቃልም የሚፈተነው የስነ-
ስርዓት ህጉ ምስክር በሚሰማበት ወቅት በተከራካሪ ወገኖች በኩል የቀረቡ ምሰክሮች
የሚጠየቁበትንና የምስክርነት ቃሉ የሚፈተንበትን ሁኔታ ለማረጋገጥ በተቀመጠው ስርዓት
መሰረት ነው፡፡
አንድ ወንጀል የተፈጸመ መሆኑን መርማሪ ፖሊስ መረጃ በደረሰው ጊዜ ምንም ዓይነት ጊዜ
ሳያጠፋ ወንጀሉን ያስረዳሉ የተባሉ ማስረጃዎችን ሁሉ እንደየአግባብነታቸው መሰብሰብና
መተንተን እንደሚገባው የወንጀለኛ መቅጫ ስነ-ስርዓት ህጉ ያስገነዝባል፡፡ ከሚሰበሰቡት
ማስረጃዎች ውስጥ የምስክር ቃል አንዱና ዋነኛው ሲሆን በወንጀለኛ መቅጫ ስነ-ስርዓት ህጉ
6
ሀብታሙ በቃሉ፣ በአብክመ ፍትህ ቢሮ የደብረ ብርሀን ቋሚ ምድብ ዐቃቤ ህግ ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ፣ ሰኔ 9/2010 ዓ.ም
7
ከላይ በግርጌ ማስታወሻ ቁጥር 4
አንቀጽ 30 ስር መርማሪ ፖሊስ የምስክር ቃል እንዴት መቀበልና መመዝገብ እንዳለበት
ዝርዝር ስርዓቱን የሚያመለክት ድንጋጌ እናገኛለን፡፡ ማስረጃዎችም ተሰብስበው ካለቁ በኋላ
የምርመራ መዝገቡ ጉዳዩን ለማየት ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት ትይዩ የሆነ ስልጣን ላለው
የዐቃቤ ህግ መስሪያ ቤት እንደሚላክና እንደሁኔታው የምርመራ መዝገቡን የሚመለከተው
ዐቃቤ ህግ ክስ የመመስረት፣ ለተጨማሪ ምርመራ የመላክ ወይም የክስ አላቀርበም ውሳኔ
ሊሰጥ እንደሚቸል የስነ-ስርዓት ህጉ ያስገነዝባል8፡፡ የምርመራ መዝገቡም ክስ የሚያስመሰረት
ሆኖ በተገኘ ጊዜና ዐቃቤ ህግ ክስ ከመሰረተ በኋላ ክርከር እንደሚጀምር በክርክር ሂደትም ዐቃቤ
ህግና ተከሳሽም የየራሳቸውን ምስክሮች እንደሚያሰሙ ስነ-ስርዓት ህጉ ያስቀምጣል፡፡ ምስክሮች
በሚሰሙበት ጊዜ ተከራካሪዎቹ ወገኖች ስነ-ስርዓት ህጉ እንዳስቀመጠው እንደ አግባብነቱ የዋና
ጥያቄ፣ የመስቀለኛ ጥያቄና የመሪ ጥያቄ የሚጠይቁበት ስርዓት ተዘርግቷል፡፡ ፍርድ ቤቱም
ማጣሪያ ጥያቄ የሚጠይቅበት ሁኔታ ተመልክቷል፡፡ በተጨማሪም ፍርድ ቤቶች ለትክክለኛ
ፍትህ አሰጣጥ አስፈላጊ ነው ብለው ሲያምኑ በዐቃቤ ህግ ወይም በተከሳሽ የማስረጃ ዝርዝር
ውስጥ ያልተጠቀሱ ምስክሮችን ማስቀረብና መስማት እንደሚችሉ ህግ አውጭው ስልጣን
ሰጥቷቸዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ተከሳሹ ወይም ዐቃቤ ህጉ ሲያመለክቱ የዐቃቤ ህግ
ምስክሮች ለፖሊስ የሰጡትን ቃል ፍርድ ቤቱ ሊመለከተው የሚችልበት እድል እንዳለ
በወንጀለኛ መቅጫ ስነ-ስርዓት ህጉ በቁጥር 145 ስር እንደሚከተለው ተደንግጎ ይገኛል፡፡
(2) ከዚህ በኃላ ለትክክለኛ ፍርድ አሰጣጥ የሚጠቅም መስሎ ከታየው የዚህ ቃል ግልባጭ
ለተከሳሹ እንዲደርሰው አድርጎ በዚህ መሰረት ምስክሩ የሰጠውን ቃል ለማስተባበል ይቻላል፡፡
8
የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት፣ የወንጀለኛ መቅጫ ስነ-ስርዓት ህግ፣ 1954 ዓ.ም፣ አንቀጽ 37፣አንቀጽ 38(ሐ)፣ አንቀጽ 42(1-ሀ) ስር
የተመለከተውን ዝርዝር ድንጋጌዎች ይመልከቱ፡፡
ሲያጋጥም ነው የሚለው ነጥብ ነው፡፡ እንዲሁም በዚሁ ድንጋጌ በንኡስ ቁጥር 2 ስር
በተመለከተው ዓረፍተ ነገር ላይ ለትክክለኛ ፍትህ አሰጣጥ የሚጠቅም በሆነ ጊዜ የምስክሩ(ሮቹ)
ቃል ግልባጭ ለተከሳሹ እንዲደርሰው በማድረግ ዐቃቤ ህግ የምስክሩን ቃል “ለማስተባበል”
ይችላል ተብሎ የተደነገገው ነው፡፡ ከላይ በተገለጸው ድንጋጌ ስር የሚታየው የክርክር መነሻና
በባለሙያዎች ዘንድ የሚታየው የግንዛቤ ልዩነት የሚመነጨው ዐቃቤ ህግ ወይም ተከሳሽ
የዐቃቤ ህግ ምስክር ቀደም ሲል ለፖሊስ የሰጠውን የምስክርነት ቃል ፍርድ ቤቱ
እንዲመለከትላቸው አቤቱታ የሚያቀርቡትና ፍርድ ቤቱም እንደ ማስረጃ የሚወስደው መቼና
በምን ዓይነት መንገድ ነው የሚለው ነው፡፡ ይህን ነጥብ በሚመለከት በክልላችን በሚገኙ ፍርድ
ቤቶች በሚሰሩ ዳኞች፣ ዐቃብያነ ህግና ጠበቆች ዘንድ በዋናነት በሁለት ሊከፈል የሚችል
አረዳድና አተረጓጎም እንዳለ ይስተዋላል፡፡ አንዳንድ ባለሙያዎች እንደሚገልጹትና በተግባርም
ሲሰሩ የሚታየው በወንጀለኛ መቅጫ ስነ-ስርዓት ህግ ቁጥር 145 (1፣2) ስር የተቀመጠው
ድንጋጌ ተፈጻሚ የሚሆነውና ለፖሊስ የተሰጠ የምስክርነትን ቃል ፍርድ ቤት ሊመለከተው
የሚችለው ቀደም ሲል ስለወንጀሉ አፈጻጸምና የወንጀሉን ፈጻሚ ማንነት በሚመለከት
በቀጥታም ይሁን ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ ምስከሩ አውቃለሁ በማለት ለመርማሪ ፖሊስ
ምስክርነቱን የሰጠ ምስክር ክሱን ለማየት ስልጣን ባለው ፍርድ ቤት ፊት ቀርቦ መመስከር
ሳይችል በቀረ ጊዜ ተፈጻሚ የሚደረግ ነው የሚል ነው፡፡ ይህ ማለት ምስክሩ ክርክሩ
በሚሰማበት ጊዜ የዐቃቤ ህግ ምስከር በህይወት ከሌለ፣ ከሀገር ከወጣ፣ ቀደም ሲል
ባስመዘገበው አድራሻ ካልተገኘ ወይም በጽኑ ህመም ምክንያት ፍርድ ቤት ቀርቦ መመስከር
ካልቻለ የዓቃቤ ህግ ምስከር/ሮች/ ባለሰማታቸው /ባለመቅረባቸው/ ክርክሩ መቋረጥ
ስለማይገባው ወይም የዐቃቤ ህግ ምስክሮችን በማፈላለግ ምክንያት ፍትህ እንዳይጓተት ሲባል
ፍርድ ቤቱ ለፖሊስ የተሰጠውን የምስክርነት ቃል ሊመለከተውና በማስረጃነት ተቀብሎ
ከማስረጃ ምዘና ውስጥ በማስገባት ውሳኔ ሊሰጥ የሚችልበትን እድል የሚፈጥር ስነ-ስርዓት
ነው በማለት ያስቀምጣሉ፤ በዚሁም አረዳድ በተግባር ሲሰሩ ይታያል9፡፡ እነዚህ ባለሙያዎች
ለክርክራቸው ማጠናከሪያና ማነጻጸሪያ የሚያደርጉት በወንጀለኛ መቅጫ ስነ-ስርዓት ህግ ቁጥር
144 ስር የተደነገገውን የቀዳሚ ምርመራ ዓላማ ነው፡፡ እንደሚታወቀው በወንጀለኛ መቅጫ ስነ-
ስርዓት ህጉ ላይ በግልጽ እንደተመለከተው ቀዳሚ ምርመራ የሚደረግበት ዋናው ዓላማ ማስረጃ
ጠብቆ ለማቆየት (preservation of evidence) ነው፡፡ በወንጀለኛ መቅጫ ስነ-ስርዓት ህጉ
9
በሰሜን ሽዋ ዞን ፍትህ መምሪያና ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከሚሰሩ ከተወሰኑ የወንጀል ዐቃብያነ ህጎችና ዳኞች ጋር የተደረገ ውይይት
ሰኔ 13፣ 2010 ዓ.ም
ቀዳሚ ምርመራ በአስገዳጅነት እንዲደረግ የተቀመጠው ለከባድ ሰው መግደል ወንጀልና ለከባድ
ውንብድና ወንጀሎች ነው፡፡ በሌሎች ወንጀሎች ዐቃቤ ህግ ቀዳሚ ምርመራ እንዲደረግ ካላዘዘ
በስተቀር ቀዳሚ ምርመራ የሚደረግበት አግባብ እንደማይኖር መገንዘብ ይቻላል፡፡ ታዲያ ከከባድ
ሰው መግደልና ከከባድ ውንብድና ወንጀሎች ውጭ በሆኑ ወንጀሎች ቀዳሚ ምርመራ
ስለማይደረግ የምስክር ቃል የማይጠበቅበት (preservation of evidence) ስለማይኖር የክርክር
ሂደቱ እንዳይቋረጥ ወይም እንዳይጓትት በማሰብ በስነ-ስርዓት ህጉ የተቀየሰ ስልት እስከሌለ
ድረስ በክርክር ሂደቱ ላይ እንቅፋት እንደሚያጋጥም የሚታወቅ ነው፡፡ እንደነዚህ ባለሙያዎች
አረዳድ ለዚህ ችግር መፍትሄ የሚሆን የወንጀለኛ መቅጫ ስነ-ስርዓት ህጉ በአንቀጽ 145 ስር
የተመለከተውን ድንጋጌ ህግ አውጭው ያስቀመጠበት ምክንያት፡፡ ይሄውም ቀዳሚ ምርመራ
እንዲደረግ ህጉ በማያስገድድበት ጊዜና ዓቃቤ ህግም ቀዳሚ ምርመራ እንዲደረግ ባላዘዘበት
ወቅት ምስክሮች ባለመቅረባቸው ምክንያት ክርክሩ እልባት ሳያገኝ መቅረት የለበትም በሚል
እምነት ለፖሊስ የተሰጠ ምስክርነት በቀዳሚ ምርመራ ወቅት እንደተሰጠ ምስክርነት ዓይነት
ተቆጥሮ በፍርድ ቤት እንደ ማስረጃ እንዲወሰድ በማሰብ የተቀረጸ ድንጋጌ ነው10፡፡ እንደነዚህ
ባለሙያዎች አረዳድ ከሆነ ቀዳሚ ምርመራ ባልተደረገባቸው ወንጀሎች ስለወንጀሉ ያስረዳሉ
ተብለው ምስክርነታቸውን ለፖሊስ የሰጡ ምስክሮች ጉዳዩ በሚታይበት ወቅት በሞት
በመለየት፣ በጽኑ ህመም ምክንያት ለመመስከር ብቁ አለመሆን፣ ከሀገር በመውጣት ፍርድ ቤት
አለመቅረብ ወይም ምስክሩ በአድራሻው ባለመገኘት ፍርድ ቤት መቅረብ ካልቻሉና ምስክሮቹ
ቀርበው ባለመመስከራቸው ክርክሩ መቋረጥ ስለማይገባው ህግ አውጭው ይህንን ክፍተት
ለመሙላት በሚል ለመርማሪ ፖሊስ የተሰጠው የምስክርነት ቃል እንደ ማስረጃ ተወስዶ
ማስረጃው እንዲመዘን በማሰብ የተቀመጠ ነው በማለት ሀሳባቸውን ይገልጻሉ11፡፡
10
11
´> TG<
ዝኒ ከማሁ
አውጭውን ሀሳብ ለመረዳት ድንጋጌውን በአግባቡ መረዳት እንደሚገባ ያስቀምጣሉ፡፡ ይሄውም
በአንቀጽ 145 (2) ስር በአማርኛው ቅጂ ላይ እንደተመለከተው “….. ለትክክለኛ ፍርድ አሰጣጥ
የሚጠቅም ሆኖ ከታየው …. ምስክሩ የሰጠውን ቃል ለማስተባበል ይቻላል” በሚል የተቀመጠ
ሲሆን ይሄው ድንጋጌ በእንግሊዘኛው ቅጂ ላይ “… such statement may be used to
impeach the creadit of the witness…” በሚል ተቀምጧል፡፡ ከላይ ከተገለጸው ዓረፍተ
ነገር መረዳት እንደሚቻለው ፖሊስ ላይ የተሰጠውን ምስክርነት ፍርድ ቤቱ የሚመለከተው
ምስክሩ የሰጠውን ቃል ለማስተባበል እንዲቻል እንደሆነ ነው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ ምስክሩ
ጉዳዩን በሚያው ፍርድ ቤት ቀርቦ እንደመሰከረ ያስገነዝባል፡፡ የሚስተባበለውም ቃል ቀደም
ሲል የዐቃቤ ህግ ምስከር በመሆን ፖሊስ ላይ ምስክርነቱን የሰጠ ምስክር ክሱን በሚሰማው
ፍርድ ቤት ቀርቦ እንዲመሰክር ሲጠየቅ ቀድሞ ለመርማሪ ፖሊስ ከሰጠው ቃል የሚቃረን
/አንዳንድ ጊዜም አስጠቂ/ ምስክርነት የሰጠ እንደሆነ አሁን በፍርድ ቤት የተሰጠው ምስክርነት
ተዓማኒነት የሌለው መሆኑን ዐቃቤ ህግ ወይም ተከሳሽ ለማስተባበል እንዲችል በማሰብ
የተቀመጠ እንደሆነ የሚያስገነዘብ ነው በማለት ይከራከራሉ፡፡ ስለሆነም ፖሊስ ላይ የተሰጠ
የምስክርነት ቃል በፍርድ ቤት ተቀባይነት የሚኖረው ፍርድ ቤቱ ምስክሩ ቃሉን ቀይሮ
ምስክርነት የሰጠ መሆኑን ካረጋገጠ በኋላ ምስክርነቱ አስጠቂ የሆነበት ወገን ምሰክርነቱን
ለማስተባበል እንዲችል እድል ለመስጠት በሚል ህግ አውጭው ያስቀመጠው ነው ሲሉ
ክርክራቸውን ያጠናክራሉ፡፡ ይህን መከራከሪያ የሚያቀርቡ ባለሙያዎች እንደሚሉት በወንጀለኛ
መቅጫ ስነ-ስርዓት ህግ ቁጥር 145 ስር በፍርድ ቤት የተሰጠውን ምስክርነት ማስተባበል
የሚችለው ዐቃቤ ህግ ብቻ ሳይሆን ተከሳሽም ሊያስተባብል የሚችልበት ጊዜ እንዳለ
ያስቀምጣሉ፡፡ ይሄውም የዐቃቤ ህግ ምስከር ፖሊስ ላይ የሰጠው ቃል ፍርድ ቤት ቀርቦ
ከሰጠው ቃል ጋር የሚቃረን ከሆነና ፍርድ ቤት ቀርቦ የሰጠው ቃል ተከሳሽን የሚጎዳ ወይም
ለመርማሪ ፖሊስ ከሰጠው የተለየ ከሆነ ተከሳሹ የዐቃቤ ህግ ምስክር ቀደም ሲል ለመርማሪ
ፖሊስ የሰጠው አሁን ፍርድ ቤት በመሰከረው ዓይነት አይደለም በማለት ለፍርድ ቤቱ
በማመልከት የምርመራ መዝገቡ እንዲቀርብለት እንደሚያመለክትና ፍርድ ቤቱም ልዩነት
መኖሩን ከተረዳ ተከሳሹ ምስክሩ የሰጠውን ቃል ማስተባበል እንዲችል መፍቀድ ያለበት
መሆኑን ያመለክታል በማለት ይከራካራሉ12፡፡ ይህንንም ሀሳብ የሚያጠናክሩት በአንቀጽ 145
በአርእስቱ ላይ “በፖሊስ የተሰጠ ቃል በማስረጃነት ሊቀርብ ስለመቻሉ” በሚል የተገለጸው
12
በላቸው ኪዳኑ፣በአብክመ ፍትህ ቢሮ የደብረ ብርሀን ቋሚ ምድብ ዐቃቤ ህግ ሰኔ 10፣2010 ዓ.ም፡፡ ሀብታሙ ትርፌ፣ ሰሜን ሽዋ ዞን ፍትህ
መምሪያ ዐቃቤ ህግ፣ ሰኔ 12፣2010 ዓ.ም
ጥቅል አገላለጽ ዐቃቤ ሀግም ሆነ ተከሳሽ ባመለከቱ ጊዜ ተፈጻሚ መሆኑን ያሳያል፡፡
በተጨማሪም የዚሁ ድንጋጌ 145(1) ስር “ዐቃቤ ህጉ ወይም ተከሳሹ ሲያመለክት በፖሊስ
ምርመራ ጊዜ…..” በማለት የተቀመጠው ሀሳብ ዐቃቤ ህግም ሆነ ተከሳሹ እንደአግባብነቱ
የምርመራ መዝገቡ እንዲቀርብላቸው ሲያመለክቱ ለሁለቱም እድሉ የተሰጠ መሆኑን
የሚያመለክት ነው በሚል ነው፡፡
13
ከላይ በግርጌ ማስታወሻ ቁጥር5፣ አንቀጽ 136(3)
ለማረጋገጥ ነው14፡፡ በዚህም ዓይነት ሂደት ውስጥ ያለፈ ማስረጃ በሌላ ፍርድ ቤት ማስረጃ ሆኖ
ሊቀርብ ቢችል ህጋዊና ስነ-ስርዓት ህጉን የጠበቀ ነው፡፡ በሌላ በኩል ግን ለመርማሪ ፖሊስ
የተሰጠ ቃል ልክ እንደ ቀዳሚ ምርመራ ጥብቅ ስርዓቶችን አልፎ ባልመጣበት ሁኔታ የዐቃቤ
ህግ ምስክሮች ፍርድ ቤት ቀርበው መመስከር ባልቻሉ ጊዜ ለፖሊስ የሰጡትን ምስክርነት
በቀጥታ እንደ ማስረጃ መውሰድ ህግ አውጭው በወ.መ.ስ.ስ.ህ.ጉ 145 ስር ያስቀመጠውን
ዓላማ በአግባቡ ያገናዘበ ዓይደለም፤ምስክሩ ፍርድ ቤት ባልቀረበበት ሁኔታ ለመርማሪ ፖሊስ
የተሰጠው ቃል እውነትነት አጠራጣሪ ከመሆኑም በላይ የተከሳሹን ሰብዓዊና ህገ መንግስታዊ
መብት የሚነፍግ ነው15፡፡ ይህንን ከላይ የተጠቀሰውን ሀሳብ በሚያጠናክር መልኩ የተሻሻለው
የጸረ ሙስና ልዩ የስነ-ስርዓትና የማስረጃ ህግ አዋጅ በአንቀጽ 44 ስር በሚከተለው መልኩ
ተደንግጎ ይገኛል16፡፡
በአማራ ክልል ፍርድ ቤቶች ከወረዳ እስከ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ባሉ የቀጥታም ሆነ የይግባኝ
ክርክሮች ላይ በወንጀለኛ መቅጫ ስነ-ስርዓት ህግ ቁጥር 145 ስር የተደነገገውን ድንጋጌ
ተፈጻሚ በማድረግ በኩል ወጥ የሆነ አሰራር አይታይም17፡፡ በዚህም የተነሳ ለመርማሪ ፖሊስ
የተሰጠን ምስክርነት እንደማስረጃ የሚወሰደው በምን ሀኔታ ነው የሚለውን ጉዳይ በሚመለከት
የተለያዬ አሰራር እንዳለ ባለሙያዎችም ይገልጻሉ፤ መዛግብትም ይጠቁማሉ፡፡ በክልሉ በብዙ
ፍርድ ቤቶች ወይም ችሎቶች በወ.መ.ስ.ስ.ህ.ቁ. 145 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ በሚመለከት
ፍርድ ቤቶች ለፖሊስ የተሰጠን የምስክር ቃል የሚመለከቱትና እንደ ማስረጃ የሚወስዱት
የዐቃቤ ህግ ምስክር/ሮች/ በቂ ተብሎ በሚገመት ምክንያት ማለትም ምስክሩ በህይወት ከሌለ፣
በከፍተኛ የጤና ችግር ምክንያት ምስክርነቱን መስጠት ካልቻለ፣ ምስክሩ ከሀገር ከወጣ ወይም
ምስክሩ በአድራሻው ሊገኝ ካልቻለ ዐቃቤ ህግ ምስክሩ ቀደም ሲል ለፖሊስ የሰጠው ቃል እንደ
ማስረጃ ይያዝልን በማለት ያመለክታል፤ ፍርድ ቤትም ይህንኑ በመቀበል ፖሊስ ላይ ምስክሩ
የሰጠውን የምስክርነት ቃል ኮፒ ተደርጎ ከመዝገቡ ጋር እንዲያያዝ ካደረገ በኋላ ማስረጃ ሚዛን
ውስጥ በማስገባት ውሳኔ ሲሰጥ በስፋት ይታያል18፡፡ ይህንን ሀሳብ በሚደግፍ መልኩ የተወሰኑ
ውሳኔዎችም እንዳሉ መዛግብት ያሳሉ፡፡ ለምሳሌ በከሳሽ የሰሜን ሽዋ ዞን ዓቃቤ ህግ በተከሳሽ
ንጉስ ተክለዮሀንስ መካከል በነበረው ከባድ ሰው መግደል ወንጀል የዓይን ምስክር የነበረው
ግለሰብ በሞት በመለየቱ ምክንያት ዐቃቤ ህግ ምስክሩ ፖሊስ ላይ የሰጠው ቃል እንዲያዝለት
ባመለከተው መሰረት ፍርድ ቤቱ ፖሊስ ላይ የተሰጠውን ቃል ኮፒ ተደርጎ ከመዝገቡ ጋር
እንዲያያዝ አድርጎ ተከሳሽን ጥፋተኛ ለማለት ፖሊስ ላይ የተሰጠው ምስክርነት የማስረጃ ሚዛን
ውስጥ በማስገባት ፍርድ ቤቱ እንደተጠቀመበት የፍርድ ቤቱ መዝገብ ያለመክታል19፡፡ እዚህ
ላይ ልብ ሊባል የሚገባው ነጥብ ምስክሩ ፖሊስ ላይ ቀርቦ የሰጠውን ቃል ከሌሎች የሰው
ምስክሮች ቃል ጋር በማጣመር ፍርድ ቤቱ ሲመዝን የማስረጃውን ክብደትና የማስረዳት አቅም
በተመለከተ ፍርድ ቤቱ እንደየሁኔታው የሚመዝነው መሆኑ ግምት ውስጥ ሊገባ የሚገባው
ነው፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ በከሳሽ የሰሜን ሽዋ ዞን ዐቃቤ ህግ በተከሳሽ እነ አይደፈር
17
ፍቃዱ አንዳርጌ፣ የሰሜን ሽዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ ፣ሰኔ 12/2010 ዓ.ም የተደረገ ቃለ መጠይቅ
18
ሀብታሙ በቃሉና በላቸው ኪዳኑ፣ በአብክመ ፍትህ ቢሮ የክልል ዐቃቤ ህግ ጋር በተደረገ ውይይት በክልሉ ውስጥ በተለያዩ
ዞኖችና ወረዳዎች በሰሩበት አጋጣሚ በጽሁፉ ላይ በተቀመጠው ዓይነት እንደሚሰራ ይጠቁማሉ ቃለ መጠይቁ የተደረገው ሰኔ
10/2010 ዓ.ም
19
የሰሜን ሸዋ ዞን ከ/ፍ/ቤት የወ/መ/ዝ/ቁ. 02-40140 ይመልከቱ፡፡
መታፈሪያ20 መካከል በነበረው ክርክር እንደተመለከተው ዐቃቤ ህግ ምስክሮቹን አሰምቶ ከጨረሰ
በኋላ ለፍርድ ቤቱ አስተያየት አቅርቧል፡፡ ይሄውም ሁለተኛና ሶስተኛ የአቃቤ ህግ ምስክሮች
ፖሊስ ላይ የሰጡትን ምስክርነት ቀይረው የሰጡ ስለሆነ ምርመራውን ላጣራው ፖሊስ የሰጡት
ቃል ይያዝልኝ በማለት አሳስቧል፡፡ በዐቃቤ ህግ አስተያየት ላይ መልስ እንዲሰጥ የተጠየቀው
የተከሳሽ ጠበቃ እንደገለጸው ምስክሮች ለፖሊስ የሰጡት ቃል ለፍርድ ቤት ሊቀርብ የሚችለው
ምስክሩ ከሞተ፣ ከአገር ከወጣ ወይም በማንቻውም ሁኔታ ችሎት ቀርቦ መመስከር ካልቻለ
እንጂ ምስክሩ ቀርቦ በመሰከረበት ሁኔታ ፖለስ ላይ የሰጠው ቃል ይቅረብልኝ በማለት የቀረበው
አስተያየት የስነ-ስርዓት ህጉን ዓላማ ያልተከተለ ስለሆነ ውድቅ ሊደረግ ይገባል በሚል
ተከራክሯል፡፡ ፍርድ ቤቱም በቀረበው የግራ ቀኙ ክርክር ላይ ብይን ሳይሰጥ በዝምታ
እንዳለፈው የፍርድ ቤቱ መዝገብ ያመለክታል፡፡
በሌላ በኩል አንዳንድ ፍርድ ቤቶች ወይም ችሎቶች የዓቃቤ ህግ ምስክር መቅረብ ስላልቻለ
ምስክሩ ፖሊስ ላይ የሰጠውን ቃል ይያዝልን በሚል ዐቃቤ ህግ የሚያቀርበውን ክርክር ሲቀበሉ
አይታይም፡፡ ለምሳሌ በከሳሽ የመርሀቤቴ ወረዳ ዐቃቤ ህግ በተከሳሽ ባዩ ጌታቸው መካከል
በነበረው የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ክርክር የግል ተበዳይ የነበረችው የዓይን ምስክር
በአድራሽዋ ልትገኝ ባለመቻሏና ፍርድ ቤት ቀርባ ባለመመስከሯ ዐቃቤ ህግ ለችሎቱ ለፖሊስ
የሰጠችው ቃል እንዲያዝለት ቢያመለክትም በመጀመሪያ ደረጃ ጉዳዩን ሲመለከት የነበረው
የወረዳው ፍርድ ቤትም ሆነ ክርክሩን በይግባኝ የተመለከተው የሰሜን ሽዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ
ቤትና የሰበር አቤቱታ የቀረበለት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ክርክሩን ሳይቀበሉት ቀርተው
ተከሳሽ በነጻ እንደተሰናበተ መዝገቦቹ ያመለክታሉ21፡፡
20
የሰ/ሽ/ዞን ከ/ፍ/ቤት የወ/መ/ዝ/ቁ. 02-41118 ይመልከቱ
21
የሰሜን ሽዋ ዞን ፍትህ/መ/የወ/ይ/መዝ.ቁ. 20/2010፣ የሰ/ሽ/ዞ/ከ/ፍ/ቤት የወ/መዝ.ቁ 02-16151
ይጠቁማሉ22፡፡ ይህ የባለሙያዎቹ አስተያየትም በክርክሮች (በመዛግብት) ላይ ተፈጻሚ ሲሆን
ይታያል፡፡ ለምሳሌ በከሳሽ ዐቃቤ ህግ በተከሳሽ ወርቅዬ ዘገዬ መካከል በነበረው የውንብድና
ወንጀል የዓቃቤ ህግ ምስክር በሀሰት በመመስከሩ ቀደም ሲል ምስክሩ ለፖሊስ የሰጠው ቃል
እንዲያያዝ ተደርጎ ውሳኔ የተሰጠ መሆኑን የፍርድ ቤቱ መዝገብ ያመለክታል23፡፡ እዚህ ላይ
ትኩረት ሊደረግበት የሚገባው ነጥብ ዐቃቤ ህግ ምስክሬ አስጠቂ ስለሆነብኝ ለመርማሪ ፖሊስ
የሰጠው ቃል ይያዝልኝ በማለት ሲያመለክት ፍርድ ቤቱም የምርመራ መዝገቡን ካስቀረበ በኋላ
አስጠቂ ምስክር ተመስክሮብኛል ያለው ዐቃቤ ህግ መስቀለኛ ጥያቄ ወይም መሪ ጥያቄ
እንዲጠይቅ በማድረግ አስጠቂ የሆነበትን ምስክርነት እንዲያስተባብል ማድረግ ሲገባው ፍርድ
ቤቱ ከምርመራ መዝገቡ ላይ የምስክሩ ቃል ኮፒ ተደርጎ ከመዝገቡ ጋር እንዲያያዝ በማድረግ
ውሳኔ ሲሰጥ ይታያል፡፡ ይህም ከድንጋጌው ዓላማና ሀሳብ ውጭ ነው፡፡ የድንጋጌው ዓላማ
አስጠቂ ምስክር ሲሰጥ ወይም ተከሳሽ የዐቃቤ ህግ ምስክር ፖሊስ ላይ ከሰጠው ቃል ጋር
በሚቃረን መልኩ በፍርድ ቤት መሰከረብኝ በማለት ሲያመለክት በፍርድ ቤት የተሰጠውን ቃል
ለማስተባበል ዐቃቤ ህግ ወይም ተከሳሽ መስቀለኛ ወይም መሪ ጥያቄ እንዲጠይቅ በማሰብ
የተደነገገ ድንጋጌ ነው፡፡ በሌላ በኩል የዐቃቤ ህግ ምስክሮች በፍርድ ቤት ቀርበው ሲመሰክሩ
ሀሰት ስለመሰከሩ ቀደም ሲል ለፖሊስ የሰጡት ቃል ይታይልን በማለት ዐቃቤ ህግ
የሚያቀርበውን መከራካሪያ የማይቀበሉ ችሎቶችም እንዳሉ ይስተዋላል፡፡ ለምሳሌ በከሳሽ
የሰሜን ሽዋ ዞን ፍትህ መምሪያ በተከሳሽ መኮንን በላቸው መካከል በነበረው የሰው መግደል
ወንጀል የወንጀሉን ፈጻሚ በቀጥታ አይቻለሁ በማለት የዓይን ምስክር ሆና የቀረበችው ግለሰብ
ጉዳዩን በሚመለከተው ፍርድ ቤት ቀርባ ስትመሰክር አላየሁም በማለት ቃሏን ቀይራ
የመሰከረች በመሆኑ ዐቃቤ ህግ ለፖሊስ የሰጠችው ምስክርነት ይታይልኝ በማለት አቤቱታ
አቅርቦ ገዳዩን በመጀመሪያ ደረጃ ሰልጣኑ ሲመለከት የቆየው የሰሜን ሽዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ
ቤት ሳይቀበለው ቀርቷል24፡፡ በዚሁ ብይን ቅር በመሰኘትና ተከሳሽም ነጻ በመሰናበቱ አግባብ
አይደለም በማለት ይግባኙን ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ደብረ ብርሀን ቋሚ ችሎት አቅርቦ
የክልሉ ዐቃቤ ህግም የስር ከፍተኛ ፍርድ ቤት የዐቃቤ ህግ ምስክር የነበረችው ለፖሊስ
የሰጠችውን ቃል በመቀየሯ ምክንያት ዐቃቤ ህግ ምስክሯ ለፖሊስ የሰጠችው ቃል ፍርድ ቤቱ
22
ፍቃዱ አንዳርጌ፣ የሰሜን ሽዋዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ ጋር ሀምሌ 2፣ 2010 ዓ.ም የተደረገ ቃለ መጠይቅ እንዲሁም
ከሀብታሙ አዲስ፣ የምእራብ ጎጃም ዞን ፍትህ መምሪያ የባህር ዳር ክላስተር ምድብ የወንጀል የስራ ሂደት አስተባባሪ፣ ሰኔ 15
2010 ዓ.ም የተደረገ ቃለ መጠይቅ
23
የሰ/ሽ/ዞ/ከ/ፍ/ቤት የወ/መዘ/ቁ. 02-39159 ከሳሽ ዐቃቤ ህግ ተከሳሽ ወርቅ ዘገዬ
24
የሰሜን ሽዋ ዞን ከ/ፍ/ቤት የወ/መዝ.ቁ 0236732
ይመልከትልኝ በማለት የተከራከረ ቢሆንም ይግባኝ ሰሚው ፍርድ ቤት በዚህ ረገድ የቀረበውን
ይግባኝ አልተቀበለውም25፡፡ በሌላ በኩል አንዳንድ ጊዜ ተከሳሽ የዐቃቤ ህግ ምስክር የመሰከረው
አላግባብ ነው ፖሊስ ላይ የሰጠው ምስክርነት አሁን ፍርድ ቤት በሰጠው ዓይነት አይደለም
በማለት ሲያመለክት የምርመራ መዝገቡን ፍርድ ቤት አስቀርቦ የሚመለከትበት ጊዜም እንዳለ
ይታያል26፡፡
25
የአብከመ ፍትህ ቢሮ የወ.መዝ.ቁ. 21/2008፣የአብክመ ጠ/ፍ/ቤት የወ/ይ/መዝ.ቁ 02-16806፣
26
በላቸው ኪዳኑ፣ በአብክመ ፍትህ ቢሮ የደብረ ብርሀን ቋሚ ምድብ ዐቃቤ ህግ ሰኔ 11፣2010 ዓ.ም
27
የፌደራል ሰበር ሰሚችሎት የወ/መ/ ቁ. 111498 ቅጽ 9 ይመልከቱ
ተገቢ እንዳልሆነና የስር ፍርድ ቤቶች መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት እንዳልፈጸሙ በመወሰን
የስር ፍርድ ቤቶች የሰጡትን ውሳኔ አጽንቷል፡፡ እዚህ ላይ ሰበር ሰሚ ችሎቱ በዝምታ
ያለፈውና በአግባቡ ሊመለከተው ይገባ የነበረው ጉዳይ ይህ ድንጋጌ አከራካሪ እንደመሆኑ መጠን
ሰበር ሰሚ ችሎቱ ለትርጉም ክፍትና እስካሁን ድረስ ገዢ የሆነ ትርጉም ያላገኘ በመሆኑ ሰበር
ሰሚ ችሎቱ ከተቋቋመለት ወጥ የሆነ የህግ አተረጓጎም እንዲኖር የማድረግ ዓላማ መሰረት
በወ.መ.ስ.ስ.ህ.ቁ 145 ስር የተቀመጠው ለፖሊስ የተሰጠ ምስክርነትን ፍርድ ቤት
የሚመለከተው ለምን ዓላማና እንዴት ነው የሚለውን ትርጉም ሰጥቶበት ማለፍ ይገባው ነበር፡፡
አሁንም ቢሆን የዚህን ድንጋጌ አተረጓጎም በሚመለከት በባለሙያው ዘንድ ወጥ የሆነ አቋም
የማይታይና ብዥታ ያለበት በመሆኑ ሰበር ሰሚ ችሎቱ በህግ የተጣለበትን ሀላፊነት በመወጣት
ወደፊት በድንጋጌው ላይ ተገቢ የሆነ ትርጉም በመስጠት ገዢ የሆነ ውሳኔ ቢሰጥ በበታች
ፍርድ ቤቶች የሚታየውን የተለያዬ አረዳድና አተረጓጎም ለማስቀረት ትልቅ ፋይዳ ይኖረዋል፡፡
4. ማጠቃለያ