Professional Documents
Culture Documents
( )
( )
2
www.tlcfan.org 0
መለከት #2
አስሩ ሕግጋት የእግዚአብሔር ሲሆኑ የቀሩትን ሕግጋትና ትዕዛዛትን በሙሉ የሙሴ ሕጎችና
ትዕዛዛት ናቸው የሚል እምነት አለ። ይህ ፈጽሞ የተሳሳተ አስተሳሰብ ወይም የቃል መረዳት
በቤተክርሲያን ውስጥ ሰርጎ በመግባቱ ቤተክርሲያን ከኢየሱስ ክርስቶስ እንዲሁም ከሐዋርያትና ነብያት
የወረሰችውን ትክክለኛ የትምህርት ጎዳና እንድትስት አድርጓታል። ከእነርሱም መንገድ መነውለላችን
ያመጣብን ችግር በቀላሉ ልንቀርፈው ወደማችለው የቤተክርሲያ ውድቀት ውስጥ ከቶናል። ድል
ከሚነሱት ጻድቃብ መካከል በመሆን ፋንታ ለሰይጣንና ፈተናው እጅ ወደ ሰጡትና ድል ከማይነሱት
አማኞች ጋር እንድንፈረጅ አድርጎናል። አሁን በጊዜው መሰረት ወደ ሆነው ወደ እግዚአብሔር ቃል በቶሎ
ልንመለሰና እያንዳዳችን ቃሉን በቃሉ ብቻ ልንተረጉም ይገባናል። አሁንም ይህንን እንደ ቃሉ ለመረዳት
ለመጀመሪያ ጊዜ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የሙሴ ሕግ ተብሎ ከሰፈረበት ጥቅስ በመነሳት ሌሎቹንም
ቃሎች አስከትለን ሁሉን አብረን እንመለከታለን።
www.tlcfan.org 1
መለከት #2
እንግዲህ ከላይ ባየነው ቃሎች መሰረት የሙሴ ሕግና የሙሴ የሕግ መጽሐፍት እራሱ
የእግዚአብሔር ሕግ እንደሆነ እንመለከታለን። ሙሴ የራሱ የሆነ ምንም ሕግ የለውም። ይህም ማለት
ሙሴ ምንም ሕግን አላወጣም። ሙሴ ራሱ ለሕዝቡ ሲነግራቸው እንዲህ አለ፦
“ትወርሱአት ዘንድ ተሻግራችሁ በምትገቡባት ምድር የምታደርጉአትን ሥርዓትና ፍርድ
አስተምራችሁ ዘንድ እግዚአብሔር (ያሕዌ) በዚያን ጊዜ አዘዘኝ።” ዘዳ.4፥14
ለሰው ልጆች ሁሉ የተሰጠን አንድ ሕግና አንድም አይነት ፍርድ እንደሆነ በቃሉ በግልጽ
እንመለከታለን። ስለዚህ ለእስራኤሎች ሌላ ሕግ ደግሞ ለሌላው ሰው ሌላ ሕግ ነው የሚለውን የተሳሳተ
ሃሳብ በቃሉ መሰረት ከአዕምሯችን ልናስወግደው ይገባል። ስለዚህ በአጠቃላይ የሙሴ ሕግና
የእግዚአብሔር ሕግ የተባለው በእርሱ በኩል ለእስራኤሎች ሁሉ የመጣው ሕግና ትዕዛዛት
ከእግዚአብሔር ከእራሱ የመጣ ሲሆን ለእስራኤሎች ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጆችም ሁሉ እንደሆነ ይህ
በእናንተ ዘንድ የታወቀ ይሁን።
www.tlcfan.org 2
መለከት #2
ሌላው ይህን ከላይ ያለውን ሁለቱን ሃሳብ ጠቅልለን ልናይ የምችልበት ቃል ደግሞ
የሚገኘው በዘሁልቁ ምዕራፍ ሃያ ዘጠኝን ላይ ነው። ይህ ምዕራፍ በሙሉ ብናነበው ሌሎቹን የተሰጡትን
ሕግጋትና ትዕዛዛት የምናገኝበትም ምዕራፍ ነው። በዚህ ምዕራፍ ውስጥ ስለ እግዚአብሔር በዓላት፣ ስለ
መስዋዕትና ስርየት ሕግጋቶች ተጽፎ እናገኛለን። ነገር ግን በዚህ ምዕራፍ መጨረሻ ላይ የተባለውን
በደንብ በትኲረት እንድትመለከቱት እወዳለሁ። ይህ የመጨረሻ ቁጥር ላይ እንደምናየው ሙሴ ለሕዝቡ
የነገረውን ትዕዛዛት ሁሉ ያዘዘው እግዚአብሔር እንደሆነ ያረጋግጥልናል።
“ሙሴም ለእስራኤል ልጆች (ያሕዌ) እግዚአብሔር ሙሴን ያዘዘውን ሁሉ ነገራቸው።” ዘሁ.29፥40
“የእስራኤልም አምላክ (ያሕዌ) እግዚአብሔር በሰጠው በሙሴ ሕግ ፈጣን ጸሐፊ ነበረ
የአምላኩም (የያሕዌ) የእግዚአብሔር እጅ በእርሱ ላይ ነበረችና ንጉሡ የሻውን ሁሉ ሰጠው።”
ዕዝራ.7:፥6
“በመጀመሪያውም ወር በአንደኛው ቀን ከባቢሎን ሊወጣ ጀመረ፥ መልካሚቱም የአምላኩ እጅ
በእርሱ ላይ ነበረችና በአምስተኛ ወር በመጀመሪያው ቀን ወደ ኢየሩሳሌም ደረሰ። ዕዝራም
(የያሕዌን) የእግዚአብሔርን ሕግ ይፈልግና ያደርግ ዘንድ፥ ለእስራኤልም ሥርዓትንና
ፍርድን ያስተምር ዘንድ ልቡን አዘጋጅቶ ነበር።” ዕዝራ.7፥9-10
“ሰባተኛውም ወር በደረሰ ጊዜ የእስራኤል ልጆች በከተሞቻቸው ነበሩ። ሕዝቡም ሁሉ በውኃው
በር ፊት ወዳለው አደባባይ እንደ አንድ ሰው ሆነው ተሰበሰቡ (ያሕዌ) እግዚአብሔርም
ለእስራኤል ያዘዘውን የሙሴን ሕግ መጽሐፍ ያመጣ ዘንድ ጸሐፊውን ዕዝራን ተናገሩት።”
ነህምያ.8፥1
www.tlcfan.org 3
መለከት #2
www.tlcfan.org 4
መለከት #2
“ከዚያ ወራት በኋላ ከእስራኤል ቤት ጋር የምገባው ቃል ኪዳን ይህ ነውና ይላል ጌታ፤ ሕጌን
በልቡናቸው አኖራለሁ በልባቸውም እጽፈዋለሁ፥ እኔም አምላክ እሆንላቸዋለሁ እነርሱም ሕዝብ
ይሆኑልኛል። . . . መንፈስ ቅዱስም ደግሞ ስለዚህ ይመሰክርልናል፤ ከዚያ ወራት በኋላ ከእነርሱ ጋር የምገባው
ኪዳን ይህ ነው ይላል ጌታ፤ በልባቸው ሕጌን አኖራለሁ በልቡናቸውም እጽፈዋለሁ”
ዕብ. 8፥10፣ 10፥15-16፣ ኤር.31፥33
www.tlcfan.org 5
መለከት #2
www.tlcfan.org 6
መለከት #2
እኛስ ዛሬ የኢየሱስን ፍለጋ መከተል አለብንን? ወይስ የራሳችንን አዲስ ሕግና ስርዓት
መፍጠር ያስፈልገናልን? ከእግዚአብሔር ሕግ የምንፈልገውን በመውሰድ ሌላውን መተው አለብን?
መልሱን ለእናንተ ተዋለሁ። ኢየሱስ ግን በጊዜው ለሚከተሉት ሕዝብና ለደቀመዝሙርቱ ያስተማረውን
ትምህርት እንመልከት።
www.tlcfan.org 7
መለከት #2
ኢየሱስ በሙሴ ወንበር የሚለው በሙሴ ሕግጋት የሚለውን የሚተካ ነው። እነዚህ ጻፎችና
ፈሪሳዊያን የሚናገሩት ትክክል የሆነውን ዘላለማዊውን የእግዚአብሔር ሕግ ነው። ችግራቸው
የተናገሩትን አለመኖር፣ የሰበኩትን ሆኖ አለመገኘት ነው። ችግሩ እነርሱ እንጂ የእግዚአብሔር ሕግ
አልነበረም። ኢየሱስ የሚሏችሁን ስሙት ደግሞም እናንተ እንደ እነርሱ አትሁኑ! የሚሏችሁን መስማት
ብቻ ሳይሆን አድርጉትም አላቸው። ስለዚህ በኢየሱስ ትምህርት መሰረት በሙሴ በኩል የመጣውን ሕግ
ሁሉ መታዘዝ አለብን? አዎን አለብን። ይህ ከማንም የመጣ ትምህርት አይደለም። ከእርሱ ከኢየሱስ
ክርስቶስ የመጣ እርሱን እከተላለሁ የሚል ሁሉ ሊኖርበት የተገባ ትምህርት ነው።
ስለዚህ በአጠቃላይ የእግዚአብሔር ሕግ ከሙሴ ሕግ ፈጽሞ የሚለያይ አይደለም።
በታቦቱ ውስጥና ውጭ ያለውም ሁለቱም ሕግጋቶች በጥቅሉ 613ቱ የተጻፉልን ሕግጋቶች ዘላለማዊና
እኩል ክብር ያላቸው ናቸው። ይህ ባይሆን ኖሮ ኢየሱስ ታላላቅ ሕጎች ብሎና እንድንጠብቃቸውና
እንድንታዘዛቸው ባላስተማረንም ነበር። ሙሴ ሁሉ ያደረገው፣ ሁሉን ያስተማረው፣ ሁሉን ያዘዘው
እግዚአብሔር የጻፈውን፣ ያዘዘውን፣ያሳየውን፣ የተገለጠለትንና ያሰማውን ብቻ ነው። ዘጸ.25፥9
የማደሪያው ድንኳን ሶስት ክፍል ሲኖረው ቅድስተ ቅዱሳን ታቦቱ የሚገኝበት ሰፍራ
ነው። ሁለቱ ሕግጋቶ ማለትም በጽጋይም ሆነ በመጽሐፍ የተጻፉት ሕግጋቶች የሚገኙት እዛው ክፍል
ውስጥ ነው። ይሁንና አስተውለን ስንመልከተው ሁለቱም በቅድስተ ቅዱሳን ክፍል ውስጥ የተጠቀለሉና
አንድ የሆኑ ናቸው። ታቦቱም ሆነ ቅድስተ ቅዱሳን በሰው ልጆች ልብና መንፈስ የሚመሰል ነው።
እግዚአብሔር ደግሞ ሁል ጊዜ ሕጉን በቅድስተ ቅዱሳን በውስጥና በውጭ እንዳስቀመጠው ሕጉ
በመንፈሳችንና በነፍሳችን ላይ እንዲቀመጥ ወይም እንዲጻፍ ይፈልጋል።
“እንግዲህ እነዚህን ቃሎች (በታቦቱ ውስጥ) በልባችሁና(መንፈስ) በነፍሳችሁ (ከታቦቱ
ውጭ) አኑሩ እነርሱንም ለምልክት በእጃችሁ ላይ እሰሩአቸው፥ በዓይኖቻችሁም መካከል
እንደክታብ ይሁኑ።” ዘዳ.11፥18
“ነገር ግን ታደርገው ዘንድ ቃሉ በአፍህ( ውጭ)ና በልብህ ውስጥ ለአንተ እጅግ ቅርብ ነው።” ዘዳ.11፥18
“ከእነዚያ ወራት በኋላ ከእስራኤል ቤት ጋር የምገባው ቃል ኪዳን ይህ ነውና፥ ይላል እግዚአብሔር ሕጌን
በልቡናቸው አኖራለሁ፥ በልባቸውም እጽፈዋለሁ እኔም አምላክ እሆናቸዋለሁ እነርሱም ሕዝብ ይሆኑኛል።”
ኤር.31፥33
www.tlcfan.org 8
መለከት #2
“ከሁለተኛውም መጋረጃ ወዲያ ቅድስተ ቅዱሳን የምትባለው ድንኳን ነበረች፥በዚያም ውስጥ የወርቅ
ማዕጠንት ነበረ ሁለንተናዋም በወርቅ የተለበጠች የኪዳን ታቦት፤ በእርስዋም ውስጥ መና ያለባት
የወርቅ መሶብና የበቀለች የአሮን በትር የኪዳኑም ጽላት ነበሩ፥” ዕብ.9፥3-4
“ሐዋርያ ሊሆን የተጠራ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ ጳውሎስ በነቢያቱ አፍ በቅዱሳን መጻሕፍት
አስቀድሞ ተስፋ ለሰጠው ለእግዚአብሔር ወንጌል ተለየ።ይህም ወንጌል በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ
ተወለደ እንደ ቅድስና መንፈስ ግን ከሙታን መነሣት የተነሣ በኃይል የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ስለ
ተገለጠ ስለ ልጁ ነው፤ እርሱም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።በእርሱም ስለ ስሙ በአሕዛብ ሁሉ
መካከል ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንዲገኝ ጸጋንና ሐዋርያነትን ተቀበልን፤በእነርሱም መካከል
የኢየሱስ ክርስቶስ ልትሆኑ የተጠራችሁ እናንተ ደግሞ ናችሁ።” ሮሜ.1፥1-6
www.tlcfan.org 9
መለከት #2
www.tlcfan.org 10
መለከት #2
ፋሲካችንን ኢየሱስ ካመንን በኃላ ወይም ከጸደቅን በኃላ መንፈሳዊ እድገታችን ወይም
መዳናችን እዛጋር አያበቃም። ዘጸ 12 ላይ እንደምንመለከተው ደሙን በእምነት በመቃናቸው ካደረጉ
በኃላ በዚያ አላቆሙም። በጌታ መሆን የጌታ አያደርግም። በቤታቸው ውስጥ የፋሲካውን በግ ስጋ
በእሳት ጠብሰው ማለዳ እስኪሆንላቸው ማለት ብርሃን እስኪበራላቸው ድረስ ጨርሰው በሉት።ዮሐ.6
ይህ ከሞት ካመለጥን ወይም ከዳንን በኃላ ወዲያው የሚቀጥል የእግዚአብሔር ትዕዛዝ የዳኑ ሁሉ ሰዎች
ተግባር ሊሆን የሚገባው ነው። ከዚያም ሕጉን ወደ ምንቀበልበት ያወጣናል። ሆሴ.2፥16
www.tlcfan.org 11
መለከት #2
www.tlcfan.org 12
መለከት #2
www.tlcfan.org 13