Professional Documents
Culture Documents
03.
03.
03.
3
www.tlcfan.org 0
መለከት #3
በዚህ መልኩ ከፋፍለን ሕግጋቱን ማየት እንችላለች። ሌላው ደግሞ ልናውቀው የሚገባው
የእግዚአብሔር ሕግ ትንቢታዊ ነው። ሕጉ ለመጪው ዘመን የሚሆነውንም የሚናገር፣ የሚያስተምርና
የዘመናትን ትንቢታዊ በጥላነት የያዘ ነው። ጥላውና መጋረጃው ተገፎለት ወደ ውስጥ ማየትት የቻለ
ወይም ሕጉን እንዲያሰተውል በጌታ አዕምሮ የተከፈተለት አማኝ ሁሉ እነዚህን ትንቢቶችን ማየት
ይችላል። ነብያት የሚናገሩትንም ትንቢቶች የምንመረምለው በእግዚአብሔር ጣት በተጻፉት እና
በእግዚአብሔር በተሰጡት ሕግጋት ነው። ከእግዚአብሔር ሕግጋት ጋር የማይስማማ ማንኛውም
ትንቢትና ራእይ ፈጽሞ ከእግዚአብሔር አይደለም። የእግዚአብሔር ሕግጋትን ትንቢታዊነት
በትምህርታችን እየገፋን ስንሄድ ግጽ ሆኖ እናየዋለን።
www.tlcfan.org 1
መለከት #3
www.tlcfan.org 2
መለከት #3
www.tlcfan.org 3
መለከት #3
. . . ይናገሩ ይቅረቡም በአንድነትም ይማከሩ፤ ከጥንቱ ይህን ያሳየ ከቀድሞስ የተናገረ ማን ነው?
ያሳየሁም የተናገርሁም እኔ እግዚአብሔር አይደለሁምን? ከእኔም በቀር ሌላ አምላክ የለም፤ እኔ ጻድቅ
አምላክና መድኃኒት ነኝ፥ ከእኔም በቀር ማንም የለም።” ኢሳ.45፥5,21
እግዚአብሔር ንጉስ ስለሆነና ብቸኛ ቤዛችንና አምላክ ስለሆነ የሕጉ ምንጭና የሁሉ ፈጣሪ
እርሱ ብቻ ነው። ከእርሱ በቀር ምንም አምላክ የለም!!!! እግዚአብሔር ደግሞ የለም ካለ የለም ነው።
ሰይጣን መጥቶ አምላክ ነኝ ቢል፣ ሰባኪዎችም መጥተው ሰይጣን አምላክ ነው ቢሉን ፣ ሰው መጥቶ
እኔ አምላክ ነኝ ቢለን። ፈጽሞ ስህተትና እውነት ስላልሆነ በፍጹም አንቀበልም። ከእግዚአብሔር ሌላ
ምንም አምላክ የለም!!!!!!!!።
” እንግዲህ ምን ይሁን? ከጸጋ በታች እንጂ ከሕግ በታች ስላይደለን ኃጢአትን እንሥራን?
አይደለም። ለመታዘዝ ባሪያዎች እንድትሆኑ ራሳችሁን ለምታቀርቡለት፥ (በሲና ተራራ ስር)
ለእርሱ ለምትታዘዙለት ባሪያዎች እንደ ሆናችሁ አታውቁምን? ወይም ለሞት የኃጢአት
ባሪያዎች ወይም ለጽድቅ የመታዘዝ ባሪያዎች ናችሁ። ነገር ግን አስቀድማችሁ የኃጢአት
(ፈርኦን፣ ሰይጣን፣ አለም) ባሪያዎች ከሆናችሁ፥ ለተሰጣችሁለት ለትምህርት ዓይነት (ትዕዛዛት)
ከልባችሁ ስለ ታዘዛችሁ፥ ከኃጢአትም አርነት ወጥታችሁ ለጽድቅ ስለ ተገዛችሁ
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን። ስለ ሥጋችሁ ድካም እንደ ሰው ልማድ እላለሁ። ብልቶቻችሁ
ዓመፃ ሊያደርጉ ለርኵስነትና ለዓመፃ ባሪያዎች አድርጋችሁ እንዳቀረባችሁ፥ እንደዚሁ
ብልቶቻችሁ ሊቀደሱ ለጽድቅ ባሪያዎች አድርጋችሁ አሁን አቅርቡ።” ሮሜ.6፥14-19
www.tlcfan.org 4
መለከት #3
ዮሐንስ በወንጌሉ ስለ ልጅነት ሲናገር እንሆን ዘንድ (to become) ስልጣን እንደተሰጠን
ይነግረናል። ዮሐ.1፥12-13 ጳውሎስ ደግሞ በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ እነርሱ የእግዚአብሔር
ልጆች ናቸው ይለናል። ሮሜ. 8፥14-17 ይህ ጠለቅ ያለ ጥናት የሚፈልግ ክፍል ነው። ይሆኑ ዘንድ ተስፋ
ወደ ፊት የምፈጸም ሂደትን የሚያሳይ ሲሆን ልጆች ናቸው የሚለው የጳውሎስ ቃል ቀደሞ ፍጻሜን
ሙላትን ሆኖ መገኘትን የሚያመለክት ነው። በሁለቱ መካከል ያለው ሂደት ከባርነት ወደ ልጅነት
የምንሰለጥንበት የመንፈሳዊ እድገት ደረጃዎችን ያጠቃልላል።
በባሪያና በልጅ መካከል ትልቅ ልዪነትና የእድገት ክፍተት አለ። ብልቶቻችንን ሊቀደሱ
ለድድቅ ባሪያዎች አድርገን ስናቀርብና ከእግዚአብሔር ፍቃድና ሃሳብ ጋር እንደ ካሌብና ኢያሱ
በምድረበዳ ውስጥ ስንስማማና በመንፈስ እንደተመሩ እኛም ስንመራ እነርሱ ድል ነሺ ልጆቹ እንደሆኑ
እኛም እንዲሁ እንሆናለን። ጽድቃችን የሚጀምረው እኛ የእግዚአብሔር ባሪያዎች በማድረግ ነው። ይህን
ስንል ደግሞ ልጆች አይደለንም ማለትም አይደለም። ነገር ግን ልጅነታችን የሚጀምረው ከባርነት አይነት
ሕይወት ነው ይህም ገና ስላላደግን ሕጻን ስለሆንን ነው። ስለዚህ በዝርዝርና በጥልቀት ማወቅ ከፈለጋቹ
የእግዚአብሔር ልጆች የሚለውን መጽሐፌን ያንብቡ።
” ነገር ግን እላለሁ፥ ወራሹ ሕፃን ሆኖ ባለበት ዘመን ሁሉ፥ ምንም የሁሉ ጌታ ቢሆን
ከቶ ከባሪያ አይለይም፥”ገላ.4፥1
ከባርነት ነጻ የወጡት ልጆቹ ግን ከእርሱ ፍቃድ ጋር ወደ ሙሉ መስማማት ወደ ሚደሩስበት
የእድገት ደረጃ ሲመጡ ሕጉ እራሱ ሕይወታቸውና የማንነታቸው ክፍል ይሆናል። ቃሉ በሕይወታቸው
ባሕሪ ሆኖ ይገለጣል። ይህም ለፍቃዱ ምንም አይነት ተቃውሞ ‘’resistance’’ በልባችን ከሌለ ወደዚህ
ሙላት እንደመጣን በትክክል እናውቃለን።
www.tlcfan.org 5
መለከት #3
www.tlcfan.org 6
መለከት #3
ይሁንና ከአዳማዊው አእምሮ የተነሳ፣ ከስጋም ድካም የተነሳ በሙሴ ዘመንም ትውልዱ
ለእግዚአብሔር ሕግ መታዘዝ አልቻለም። ይልቁንም አብዛኞቹ ዘመናቸውን የጨረሱት በማመጽ
በመጨረሻም እንደ እራሳቸው የሆነ የሰው ንጉስ ሳኦልን በማንገስ ነው። እግዚአብሔርም ስለ እያንዳንዱ
ጥፋታቸው እንደ ሕጉ የሚገባቸውን ያህልና መጠን ቅጣትን ቀጥቷቸው ነበር። ዕብ.12 በዚያ
ሊማሩበት፣ ከእርሱ ሊሰሙበትና በመንፈስ ሊመሩበት በወጡበት ምድረ በዳ ጥጃ ሰርተው እንደ
አዳኛቸው አድርገው በማምለክ የመጀመሪያውን ትዕዛዝ ሕዝቡ ሰብረውታል።
እግዚአብሔር ደግሞ ሕጉን ደግሞ ሲሰጠን እንዲሰበር ሳይሆነ በታቦቱ ውስጥ እንዲቀመጥ
ወይም በልባችን ውስጥ እንዲጻፍ ነው። ይህ በሙሴ ሕይወትና በሕዝቡ መካከል በተፈጠረው ጥላዊ
ትምህርት ለእኛ በግልጽ የተቀመጠልን ነው። ሙሴ የመጀመሪያውን ሕግ ስብሮ በጥጃውና አመድ
በጥብጦ ሕዝቡን አጠጥቷቸዋል። ነገር ግን ለሁለተኛ ጊዜ ይህ አስርቱ ትዕዛዛት በጽላቱ ላይ ሲጻፍ ግን
አልተሰበረም ይልቁኑ በታቦቱ ውስጥ ተቀመጠ። ዛሬም ይህን የመጀመሪያ ትዕዛዝ በመስበር ሕጉን
ልንሰብር አይገባም። ዳግም የተሰጠን በልባችን እንድንይዘው ነው። “ትዕዛዜን በልብህ ሸሽግ” ምሳሌ 7
www.tlcfan.org 7
መለከት #3
ሕዝበ እስራኤልን ከግብጽ ባርነት ነጻ ያወጣውና ሕግ ለሙሴ በሲና ተራራ የሰጠው በአዲስ
ኪዳንም የገለጠው ብቸኛ የሰማይና የምድር ነገስታት ሁሉ ንጉስ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ዘጸ.15፥
2 ፣ ኢሳ.12፥1-3 የመጀመሪያው የእግዚአብሔር ሕግ የሚያሳየንና የሚያመለክተን ይህ ከባርነት ነጻ
ያወጣን ንጉስና አምላካችን አንድ መሆኑ ነው። ይህም አምላክ ለእኛ በአካል የተገለጠው የናዝሬቱ እየሱስ
ክርስቶስ ነው። ለብዙ ሺ አመታት ይህንን በምድር ያሉ ነገስታት ሆኑ የሃይማኖት ሰዎች ሊቀበሉት
አልቻሉም። በዳንኤል ትንቢትና ራእይ እንደተገለጠው ለአውሬዎቹ መንግስታት ሁል ጊዜ ራሱን
ሳይገልጥላቸው ቀርቶ አያውቅም። ነገር ግን እውነተኛውን፣ ብቸኛውን ንጉስ አልተቀበሉትም። ዳዊት
ለጊዜው በአቢሴሎም እንደተገፋና ግዛቱን ለጊዜው ጥሎ እንደሄደ እንደገና በክብር ደግሞ እንደተመለሰ
እንዲሁ ኢየሱስ ክርስቶስም በክብር መመለሱ የማይቀር ነው። ማራናታ!!!!!
www.tlcfan.org 8
መለከት #3
www.tlcfan.org 9
መለከት #3
www.tlcfan.org 10
መለከት #3
www.tlcfan.org 11