Download as doc, pdf, or txt
Download as doc, pdf, or txt
You are on page 1of 4

ጥርስ ከተነቀለ በኋላ መደረግ ያለበት ጥንቃቄ(አጭር መግለጫ)

 ሐኪም ያስነከሶትን ጎዝ ወይም ፋሻ ለ 30 ደቂቃ ነክሶ መያዝ።


 ምራቅ አለመትፋት።
 ለ 24 ሰዓት በማንኛውም አይነት ፈሳሽ አለመጉመጥመጥ።
 ለስለስ ያሉ ምግቦችን ቀዝቀዝ አድርጎ መጠቀም።
 አገጫችንን ወይንም ጉንጫችንን(ጥርሳችን በተነቀለበት በኩል)፤በጨርቅ በተጠቀለለ በረዶ አስደግፎ መያዝ።
 የአፍ ንፅህናዎን መጠበቅ።
 ጥርስ ከተነቀሉ በኋላ ላሉት ሰባተ ተከታታይ ቀናት ሲጋራ ወይም ትንባሆ አለማጨስ። እንዲሁም የለስላሳ
መጠጦችን ና የአልኮል ይዞታ ያላቸውን መጠጦች አለመጠቀም።
 በሐኪም የታዘዘሎትን መድሀኒት በአግባቡ መጠቀምና መጨረስ።
 ጥርሶትን ከተነቀሉ ከ 24 ሰዓት በኋላ በአፍ መጉመጥመጫ ፈሳሽ ለ 10 ቀናት መጠቀም።

ጥርስ ከተነቀለ በኋላ መደረግ ያለበት ጥንቃቄ(ረጅም መግለጫ)

 ሐኪም ያስነከሶትን ጎዝ ወይም ፋሻ ለ 30 ደቂቃ ነክሶ መያዝ አላስፈላጊ የሆነን ደም ፍሰት ይከላከላል። ክተወሰነ
ሰዓት በኋላ ደም የቀላቀለ ምራቅ ይኖራል። ይህንንም መዋጥ እንጂ መትፋት የለቦትም።ከበድ ያሉና አቅምን
የሚጠይቁ የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችን አለማድረግ። ከመጠን ያለፈ የደም ፍሰት በሚኖርበት ሰዓት በጎዝ
ወይም በፋሻ መጥረግና ቦታው ላይ ጎዝ ወይም ፋሻ ለ 30 ደቂቃ ነክሶ መያዝ። ጥጥ መጠቀም የለብንም። ይህንን
ለ 3 ጊዜ ሞክረው ደም ካልቆመ ሐኪሞትን ማማከር ይኖርቦታል።
 ጥርሶትን ከተነቀሉ ለ 24 ሰዓት በማንኛውም አይነት ፈሳሽ መጉመጥመጥ የለቦትም።ይህም የደም መርጋትን
ሒደትን ያስተጓጉላል። በተጨማሪም ያካል እንቅስቃሴን ማሶገድ ይኖርቦታል።
 ለስለስ ያሉ ምግቦችን ቀዝቀዝ አድርጎ መጠቀም ተገቢ ነው።በሚያኝኩበት ጊዜ የተነቀለበትን ተቃራኒ ጎን
ይጠቀሙ።ሞቃት ምግቦችንና ሰውነትን ሊያስቆጣ የሚችል ምግቦችን ያስወግዱ።
 ጥርስ በተነቀለበት አከባቢ ውጭውን የፊታችን ክፍል በጨርቅ በተጠቀለለ በረዶ መያዝ እብጠትን ይከላከላል።
 የአፍ ንፅህናዎን መጠበቅ አላስፈላጊ የሆነን የባክታሪያ እድገትን ይከላከላል።በተለመደው የአፍ ንፅህና አጠባብቅ
በቀን ሶስት ያፅዱ። ጥርስ ከተነቀለበት አከባቢ ልስልስ ብሎ ብሩሽ ያፅዱ። ምግብ ከተጠቀሙ በኋላ አላስፈላጊ
የሆነን ለምን ለመቀነስ አፎትን በደምብ ያፅዱ።
 ጥርስ ከተነቀሉ በኋላ ላሉት ሰባተ ተከታታይ ቀናት ሲጋራ ወይም ትንባሆ አለማጨስ። ማጨስ ብክለትን
ወይም የቁስሉን ቶሎ የመዳን ሒደት ይከላከላል። እንዲሁም ህመም እንድንል ያደርጋል።
 በውስጣቸው የጋዝ ይዘት ያላቸውን መጠጦች ያስወግዱ። እነዚህ መጠጦች የደም መርጋት ሂደትን ያስጓጉለል።
እንዲሁም የረጋውን ደም ከቦታው እንዲለቅ ያደርጋል።
 በሐኪም የታዘዘሎትን ፀረ-ባክቴሪያ መድሀኒት በአግባቡ መጠቀምና መጨረስ ያስፈልጋል። የመድሀኒቱን
መጠንና በምን ያህል ጊዜ ልዩነት መወሰድ እንዳለበት አስተውለው ያንብቡ ወይም ይጠይቁ።
 በሐኪም የታዘዘሎትን ማስታገሻ መድሀኒት በአግባቡ መጠቀም ያስፈልጋል። የመድሀኒቱን መጠንና በምን ያህል
ጊዜ ልዩነት መወሰድ እንዳለበት አስተውለው ያንብቡ ወይም ይጠይቁ።
 ጥርስ ከተነቀሉ ከ 24 ብንል 0.12% chlorhexidine በሚባል የአፍ መጉመጥመጫ ለ 10 ቀናት ይጉመጥመጡ።
0.12%chlorhexidine ,ፀረ-ባክቴሪያ ሲሆን የአፍ ውስጥ ባክቴሪያ በመቀነስ ብክለት እንዳይኖር ያደርጋል።ይህም
የጎንዮሽ ጉዳትን ቀንሶ ለክፋ ችግር እንዳንጋለጥ ያደርጋል።

ይህን አድርግዋል?
ጥያቄ

 ጎዝ ወይም ፋሻውን ለ 30 ደቂቃ ነክሰው ይዘዋል?


 ጥርሶትን ከተነቀሉ በኋላ ለ 24 ሰዓት አልተጉመጥመጡም?
 ምግብ መውሰድ በሚፈልጉበት ሰዓት ለስለስ ያለውን መርጠዋል? ሲጠቀሙስ ቀዝቀዝ አድርገዋል?
 ጥርሶትን ከተነቀሉ በኋላ የውጨኛው ፊትዎትን በጨርቅ በተጠቀለለ በረዶ ይዘዋል?
 የአፍዎትን ንፅህና ባግባቡ እየጠበቁ ነው?
 ጥርሶትን ከተነቀሉ በኋላ ላሉት ሰባት ቀናት ሲጋራ ወይም ትንባሆ ከማጨስ ታግደዋል?
 በውስጣቸው የጋዝ ይዘት ያላቸውን መጠጦች አስወግደዋል?
 በሐኪም የታዘዘሎትን ማስታገሻ መድሀኒት በአግባቡ ተጠቅመዋል?
 በሐኪም የታዘዘሎትን ፀረ-ባክቴሪያ መድሀኒት በመመሪያው መሠረት ወስደዋል?
 ጥርስ ከተነቀሉ ከ 24 በኋላ 0.12% chlorhexidine በሚባል የአፍ መጉመጥመጫ ለ 10 ቀናት ያህል
ተጉሞጥሞጠዋል?
ድህረ ጥርስ ነቀላ ጥንቃቄዎች

ምንም አይነት ድንገተኛ ነገር ቢገጥሞት ወዲያውኑ ሐኪሞትን ያማክሩ

You might also like