Download as docx, pdf, or txt
Download as docx, pdf, or txt
You are on page 1of 13

 መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሐቲት/ትንተና--Biblical Exegesis

 ሐቲት/ትንተና -ምን ማለት ነው?


 Exegesis የሚለው ቃል - የግሪኩ ቃል exegeomai/ ሲሆን
 Exegeomai translates as “to lead out of.” ማለት ነዉ፡፡
 የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎችን በተመለከተ ኤክሰጂሴስ/exegesis/ ማለት
 “ካለው ማውጣት፣
 በቁሙ መፊታት/መተርጎም፣ ወይም
 የመጽሐፉን ክፍል መተንተን/መግለጥ ማለት ነው፡፡

 ሐቲት ደራሲዉ በመን/ቅ ምሪት አንድን የመጽ/ቅዱስ ምንባብ በሚጽፍበት ጊዜ ማለትም


 ያኔ (then) እዚያ (there) ለነበሩት ሰዎች
 ለማስተላለፍ የፈለገዉ አሳብ ምን ነበር? የሚለዉን ጥያቄ ይመልሳል፡፡
 ሐቲት ምንባቡ ለመጀመሪያዎቹ አንባቢያን ምን ፊቺ እንደነበረዉ መረዳት እንዳለብን ሲያሳይ፤
 ለ``hermeneutics``ም ተመሳሳይ እርምጃ በመዉሰድ የአፈታት ጥበብ (ሥነ አፈታት) የሚል ቃል
ተሰጥቶታል፡፡
 በአመዘኙ ሥነ አፈታት ሁለቱንም ተግባራት የሚወክል ነዉ፡፡
 የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ዓላማ ሁለቱንም ተግባራት በሚገባ ከመወጣቱ ላይ ያነጣጠረ ሊሆን ይገባል፡፡
1 መተንተን/ትንተና
2 የየዕለት ተግባር ነው

 ከሌሎች ጋር ስንገናኝ ምን እናደርጋለን?


 ራሳችንን የምንጠይቅባቸው ጥያቄዎች
 ተናጋሪው መናገር የፈለገው ስለምንድን ነው?
 እነዚህ ቃላት ቀጥታ ቃል በቃል (literally) ወይስ
 ምሳሌያዊ (symbolically) ናቸው?

 እነዚህ ቃላት የተገለጡት በምን መልኩ ነው? /expressed


 ቀልድ፣  ጥያቄ፣
 ሰላምታ፣  ሪፖርት…ወዘተ እና ትክክለኛ ትርጉም ለመስጠት ቃላት የተገለጡበትን መንገድ መረዳት
 ታሪክ፣ ትልቅ ፋይዳ አለው፡፡
መልስ መስጠት ያለብኝ? ከሆነ ደግሞ እንዴት ባለ መልኩ ልመልስ?

 ለትክክለኛ ትንተና እና ትርጉም የሚጠቅሙን ጥያቄዎች

1
 መቼ ተፃፈ? - የጊዜ አመልካች  ማን? /ተናጋሪው ማነው/? የሚነገርለትስ?
 ማን ፃፈው? - የጸሐፊውን አመልካች  ምን? ርዕሱ ምንድነው ቅደም ተከተሉስ?
 ለማን ተፃፈ ?- ተደራሲያንን አመልካች  የት? ድርጊቱ እየተከናወነ ያለው የት ነው?
 የት ተፃፈ ? - የቦታ አመልካች  መቼ? ድርጊቱ የተፈፀመው መቼ ነው?
 እንዴት ተፃፈ? - ሁኔታን አመልካች እንዴት? የተደረሲያን ምላሽ እንዴት ነበር?

 ለምን ተፃፈ? - ምክንያትን አመልካች

 ንግግሩ የተደረገበትን አውድ መረዳት አሳብን በትክክል ለመተንተን ያግዘናል፡፡


 መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሐቲት/ትንተናን በተመለከተ በተቻለን መጠን
 ስለ ደራሲው/ጸሐፊው፣
 ጸሐፊው እንዲጽፍ የተነሳሳበትን ምክንያት /የጽሁፉ ዓላማ/፣
 ክፍሉ የተጻፈበትን የመጀመሪያ ቋንቋ፣
 መጽሐፉ የተጻፈበትን ዘመን እና
 በመጽሐፉ የተገለጡት ከባህል ጋር ተዛማጅነት ያላቸው ነገሮች የሚሠጡንን ፍንጮች መመልከት ያሻል፡፡

 ሦስት ዓይነት መጽ/ቅዱሳዊ የትንተና ሥልቶች/መንገዶች እነዚህም፡-


 ሥነ-ጽሁፋዊ ትችት/ምልከታ / Literary criticism/
 ማህበራዊና ታሪካዊ ትችት / Socio-historical criticism/
 ዕይታዊ ትችት / Ideological criticism/

 ሥነ-ጽሁፋዊ ትችት/ምልከታ ጽሁፉን በትክክል እንድንገመግመው ያስችለናል:-


 የጽሁፉን ዓይነት (genre) ገጸ-ባሕሪያትን /characters/
 የጽሁፉ ጭብጥ /plote/ ምሳሌአዊ ንግግሮች /symbolism/
 በሥነ-ጽሁፋዊ ትችት/ምልከታ ጊዜ የሚነሱ ጥያቄዎች የሚከተሉትን ያካትታሉ፡-
 የአጻጻፍ ሥልቱ /genre /ምን ዓይነት ነው?
 ጽሑፉን እንዴት ማጠቃለል እችላለሁ? /summarize/
 ክፍሉ ሊናገር የፈለገው በተለይ ስለምንድን ነው? ዋናው ነገር ምንድን ነው?
 ስለተደጋገሙት ቃላት/ቃሎች ምን ዓይነት መረዳት አለህ?
 የትኞቹ ቃላት ናቸው በተለይ የተተኮረባቸው? ምን ትርጉም አላቸው?
 ምን ዓይነት ምሳሌአዊ ነገሮች ተጠቅሰው ይገኛሉ? እንዴት ነው የተጠቀሙት?
 ጥቅማቸውስ ምን ያህል ነው?
 በክፍሉ የሚገኙቱ ባለታርኮቹ እነማን ናቸው?
 ስለ እነርሱ ምን ታውቃለህ?
 አንዱ ገጸ ባህርይ ከሌሎች ጋር በምን ይገናኛል?
 የክፍሉ ትልቅ መልዕክት ምንድን ነው?

2
 ክፍሉ ለዛሬው ምዕመን ምን ትምህርት ይሠጣል?
 ማህበራዊና ታሪካዊ ትችት/Socio-historical criticism/
 የመጽሐፉ ክፍል በተጻፈበት ዓውድ/ዓለም ውስጥ በመሆን የክፍሉን አሳብ መረዳት እንድንችል ያደርገናል፡፡
 በጊዜ ብዛት የተሸፈነውን/ምሥጢር የሆነውን ባሕላዊውን ዓለም ቆፍረው እንዲደርሱበትና እንዲያገኙ ማህበራዊና
ታሪካዊ ትችት ትልቅ እገዛ ያደርጋል፡፡
 የቀደሙቱ ባለታሪኮች የነበሩበትን

 ትውፊት (traditions)፣ ሐይማኖታዊ ተግበራዎች (religious practices)፣ እና


 ባህል (culture)፣ የመልከዓ-ምድር አቀማመጥ (geography) ማወቅ የመጽ/ቅዱስን ክፍል በትክክል ለመረዳት ከፍተኛ
 ልማዶች (customs)፣ እገዛ ያደርጋል፡፡

ዕይታዊ/ምልከታዊ ትችት መጽ/ቅ ሊተረጉምና ሊተነትን የሚነሳ ሰው ቀድሞ በውስጡ የነበረው


 እይታው፣
 ግምቱ፣
 እምነቱ በትንተናው ላይ ትልቅ ተጽዕኖ አለው፡፡
 የተለያዩ ሰዎች አሳባቸው በነበሩበት ማሕበረሰብ መካከል እንዴት ይገልጡ እንደነበር በመረዳት የተጻፈውን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል
 ሳይዛነፍ ለመተርጎም ብርሃን /illumination/ ይሰጠናል፡፡
 ምልከታችን/እይታችን አፈታታችን ላይ ትልቅ ሚና ይጫወታል፡፡
 የዕይታዊ ግምገማ ጥያቄዎች መካከል የሚከተሉቱ ይገኙበታል፡-
 የዚህ ክፍል መልዕክት በምን ዓይነት መልኩ ነበር በነበረው ማሕበረሰብ ሲተገበር የነበረው?
 በክፍሉ ስለተገለጡቱ አሳቦች የጊዜው ማህበረሰብ ቡድን የነበራቸው እይታ ምን ይመስል ነበር?

 የትንተና እንቅፋቶች /Obstacles to Exegesis


 የሦስተኛ አካል እይታ/ምልከታ  የባህል ክፍተት /the cultural gap/
 የቋንቋ ክፍተት /the language barrier/  የታሪክ ክፍተት /the historical gap/
የትንተና ደንቦች /Exegetical Guidelines በ----------------------------ብርሃን መተርጎም

1 በዓውዱ /interpret in the light of structure


2 በክፍሉ ገጽታ
3 በምንጮች/በመረጃዎች
4 በክፍሉ በሚገኙ የንግግር ዘይቤዎች
5 በምሳሌአዊ አገላለጡ
 (እነዚህን አምስት መርሆች እንደሚከተለው እንመለከታለን)

3
1 በዓውዱ ብርሃን መተርጎም
 ከክፍሉ ውጪ ያለው ዓውድ /external context
 የክፍሉ ዓውድ /internal context
 በዚህ ጊዜ ራስን መጠየቅ የሚገቡ ጥያቄዎች ፡-
 ካለሁበት ባህል ጋር የክፍሉ አሳብ ምን ያህል ይስማማል/ ክፍሉ የሚናገረው ነገር የታወቀ ነውን?
 ሌሎች አንባቢያን እንዴት አድርገው ተርጉመውታል?

o ክፍሉ ካለበት ዓውድና ከሰፊው ዓውድ ጋር እንዴት ይገናኛል


 መሸጋገሪያ ነው /transitional/፣
 የክፍሉ አሳብ ጡዘት ነው /climactic/፣
 ምሳሌአዊ ንግግር ነው /illustrative/፣
 የሚጣረስ የሚመስል አንድ እውነት ይዞአልን /paradoxical/፣ ማዕከል ነው /central/፣ …)?
 በመጽሐፉ ውስጥ ሆነ ከተመሳሳይ መጽሐፎች ጋር ምን አይነት የአሳብ መስማማት አለ?
2 በክፍሉ ገጽታ/አስተዋጽኦ ብርሃን መተርጎም
 በመጽሐፉ ጠቅላላ አከፋፈል ውስጥ ክፍሉን የሚገልጥ ክፍል ይኖራልና በአጽንኦት ተመልከተው
 በእነዚህ ጥያቄዎች ራሳችንን መጠየቅ:-
 አጠቃላይ የመጽሐፉ አከፋፈል ምን ይመስላል?
 ይህ ክፍል ለጠቅላላው አስተዋጽኦ የሚያበረክተው ነገር ምንድን ነው?
3 በምንጮች/በመረጃዎች ብርሃን መተርጎም/ስለምታነብባው ክፍል የሚናገሩ
 ሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎችን መመልከት እና
 ሌሎች በዚህ ክፍል የጻፉአቸውን ጽሁፎች መመልከት ክፍሉን በትክክል ለመረዳት ትልቅ ፋይዳ አላቸው፡፡
 ልንመለከታቸው የሚገቡን ነገሮች:-
 ቀጥተኛ የሆነውን አገላለጥ፣
 በጽሁፋዊ ዘዴው እና በቃላት አጠቃቀም ያሉ ልዩነቶችን መመልከት፣
 በአሳብ ፍሰት ውስጥ ያሉ መቆራረጦችን እና አገላለጡን ይዘት ማጤን፣
 ድግግሞሽ (የቃላት፣ የአሳብ፣ የሐረግ፣ የስም …)repetition
 ወጥ ያልሆኑ ነገሮች /የአሳብ መቆራረጥ /inconsistency
4 በክፍሉ በሚገኙ የንግግር ዘይቤዎች ብርሃን መተርጎም
 የንግግር ዓይነቱ ምን ዓይነት እንደሆነ መመልከት መልዕክቱን ለመረዳት ትልቅ ስፍራ አለው

4
 ልንመለከታቸው የሚገቡን ነገሮች:-
 የመጽሐፉ ክፍል አከራካሪ ነው /argumentative?
 ስላቅ አለው /satirical?
 የሚያዝናና ነገር አለው/አዝናኝ/ entertaining?
 ሥነ-ምግባራዊ /didactic?
 ገላጭ/ምሳሌአዊ/ illustrative?

5 በምሳሌአዊ አገላለጡ ብርሃን መተግርጎም


6 ብዙ ሐይማኖታዊ ጽሁፎች የተለያዩ የንግግር ዛይቤዎችን ይጠቀማሉ፡-
 ንጽጽር፣  አካል ማልበስ /personification፣
 አመሳስሎ መናገር/ምሳሌአዊ /metaphor  መንፈሳዊ ትርጉም መሥጠት /allegory፣
 ስላቅ፣  ቃለ አጋኖ /hyperbole፣
 ቅኔ /irony፣  አስተያየት /suggestion፣ ታሪክ…..

ልንመለከታቸው የሚገቡን ነገሮች:-


 ክፍሉ መተርጎም ያለበት
 በቀጥታ "literally" ነው ወይስ
 በምሳሌ "figuratively"?
 እክፍሉ ውስጥ ጸሐፊ ስለተየበው አሳብ ፍንጭ የሚሠጡ ክፍሎች አሉ? የሚሉ
ናቸዉ፡፡
a. ክፍል ሁለት
7 የመጀመሪያዉ ተግባር; ሐቲት
 የተርጓሚዉ የመጀመሪያ ተግባር ሐቲት ይባላል፡፡
 ሐቲት የተፈለገዉን የመጀመሪያ ፍች ለማግኘት መጽሐፍ ቅዱስን በጥንቃቄና በዘዴ
የማጥናት ተግባር ነዉ፡፡
 ይህ በመሠረታዊነት ታሪካዊ ሥራ ነዉ፡፡
 በመሆኑም ተርጓሚዉ
 የመጽሐፍ ቅዱስን ቃላት የመጀመሪያ ዓላማ ያገኝ ዘንድ
 መጀመሪያዎቹ አድማጮች ቃሉን ለመስማት የሚያደርጉት ጥረት ነዉ፡፡
8 ሁሉም ሰዉ ሐቲት መሥራት ይችላል፡፡
 ጥያቄዉ ጥሩ ሐቲትን መሥራት ትችላለህ ወይ? ማለት ነዉ፡፡
 ለምሳሌ፡-“ኢየሱስ ይህን ሲል…” ወይም “በዚያን ጊዜ…” የሚሉ ዓይነት አገላለጾችን ምን
ያህል ጊዜ ሰምተሃል?
 እነዚህ የሐቲት አገላለጾች ናቸዉ::
 ብዙዉን ጊዜ “በእነርሱ” እና “በእኛ “ መካከል ያሉትን ልዩነቶች ለማብራራት ያገለግላሉ፡፡
ሐቲት ለመሥራት መማር

5
ለጥሩ ሐቲትና በዚያዉም መጽሐፍ ቅዱስን በተሻለ ማስተዋል ለማንበብ ቁልፍ ነገር
 ምንባቡን በጥንቃቄ ማንበብና
 ስለ ምንባቡ ትክክለኛ ጥያቄዎችን መጠየቅ መቻል ነዉ፡፡

አንድ ሰዉ ለእያንዳንዱ መጽ/ቅዱሳዊ ምንባብ ሊጠይቃቸዉ የሚገቡ 2 መሠረታዊ ጥያቄዎች እነዚህም


ከ------- እና-----------ጋር የሚዛመዱ ጥያቄዎች ናቸዉ፡፡

 ከአዉደ ንባቡ
 ከይዘቱ
ከዓዉዳ ንባብ የሚዛመዱ ጥያቄዎች ደግሞ
 ታሪካዊና
 ሥነ ጽሑፋዊ ተብለዉ በሁለት ይካፈላሉ፡፡
1 ታሪካዊ ዓዉዳ ንባብ
ከመጽሐፍ መጽሐፍ የሚለያየዉ ታሪካዊ ዓዉዳ ንባብ ከአያሌ ነገሮች ጋር ይዛመዳል፡፡ ከእነዚህም መካከል

1 የደራሲዉና የአንባቢያኑ ዘመንና ባህል ማለትም ከደራሲዉ ጋር የሚዘመዱ መልክዓምድራዊና


ፖላቲካዊ ሁኔታዎች፣
2 መጽሐፉ፣
3 መልዕክቱ፣
4 መዝሙሩ፣
5 ትንቢቱ፣ ወይም
6 ሌላዉ ሥነጽሑፋዊ ቅርጽ እንድጻፍ ያደረገዉ ሁኔታዎች ይገኙባቸዋል
 እነዚህ ሁሉ አንድን መጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ለመረዳት አስፈላጊዎች ናቸዉ፡
የአሞጽን፣
የሆሴዕንም፣
የኢሳይያስን ግላዊ ሥረ መሠረት፣
የሐጌ ትንቢት ከምርኮ በኋላ መሆኑን ወይም
መጥመቁ ዮሐንስና ኢየሱስ በመጡ ጊዜ አይሁዶች ከሚመጣዉ መሢሕ ምን ይጠብቁ እንደነበር
ወይም
በቆሮንቶስና በፈልጵስዩስ ከተሞች መካከል የነበሩትን ልዩነቶችና እነዚህም ልዩነቶች በየከተሞቹ
በነበሩት አብያተክርስቲያናት እንዴት ተጽእኖ እንደሚያሳድሩ መረዳቱ ከፍተኛ የግንዛቤ ለዉጥ
ያስከትላል፡፡
7 ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረበት ጊዜ ስለነበረዉ ሁኔታ መረዳቱ
 የተናገራቸዉን ምሳሌዎች በአግባቡ እንድንገነዘብ ያስችለናል፡፡
 በማቴ፡20፡1-16 የተጠቀሳዉ ዲናር የሠረተኞች የአንድ ቀን ምንዳ እንደሆነ መረዳቱ ለዉጥ
እንደሚያመጣ ግልጽ ነዉ፡፡
 የመልክዓ ምድሩም አቀማመጥ ራሱ አስፈለጊ ነዉ፡፡
የታሪካዊ ዓዉደ ንባብ ይበልጥ ጠቃሚዉ ጥያቄ
 የእያንዳንዱ መጽ/ቅዱሳዊ መጽሐፍና የተለያዩ ክፍሎቹ የመጻፍ ምክንያትና ዓላማ ነዉ

6
እንዲህ ዓይነቱ ሰነድ እንዲጻፊ ያደረገዉ የዚያን ጊዜ የእስራኤል/የቤ/ክ ሁኔታ ምን ነበር? ለሚሉ ጥያቄዎች
አሳብ ማግኘቱ አስፈላጊ ነዉ፡፡

በእነዚህ ጥያቄዎች ላይ ያገኘኻዉን መልስ ከሌሎች ጋር ለማስተያየት የመጽሐፍ ቅዱስ

 መዝገበ ቃላት ወይም


 መጽሐፉ ለይ የተጻፉዉን ጥሩ ማብራሪያ መመልከት ይቻላል፡፡

ነገር ግን መጀመሪያ የራስን ጥናት ማካሄድን ይኖርብናል፡፡

ሥነ ጽሑፋዊ ዓዉደ ንባብ


 ማለት ቃላት ትርጉም የሚሰጡት በዓረፍተ ነገር ዉስጥ ብቻ ነዉ ማለት ነዉ፡፡
 ይህ በሐቲት ዉስጥ ወሳኝ ተግባር ሲሆን ደግነቱ የግድ “ኤክስፔርቶችን” ማማከር ሳያስፈልግ
ማከናወን ይቻላል፡፡
 የመጽ/ቅ ዓ/ነገሮች ደግሞ ፍቺ የሚሰጡት ከፊታቸዉና ከኋላቸዉ ካሉት ዓ/ነገሮች ጋር በመተባበር
ነዉ፡፡
 በእያንዳንዱ ዓረፍተ ነገርና አንቀጽ ሊጠየቅ የሚገባዉ እጅግ አስፈላጊ የዓዉደ ንባብ ጥያቄ፤ “መልዕክቱ
ምንድነዉ?” የሚል ነዉ፡፡
 የጸሐፊዉን አሳብ ለመከተል መሞከር አለብን፡፡
 ጸሐፊዉ ምን እያለ ነዉ?
 ከዚህ ቦታ ለይ ይህንን ያለዉ ለምንድ ነዉ? ብለን መጠየቅ አለብን፡፡

ይህ ጥያቄ ከአንዱ ሥነ ጽሑፋዊ ቅርጽ ወደ ሌላዉ ስንሄድ የሚለያይ ቢሆንም ሁል ጊዜም ወሰኝ ጥያቄ
ነዉ፡፡

የሐቲት ዓላማ
 መጽሐፉን የጻፈዉ ሰዉ ለማስተላለፍ የፈለገዉን መልዕክት ማግኘት ነዉ፡፡
 አንደኛ ተግባር የይዘት ጥያቄዎች፡-

አንድ ሰዉ ስለ የትኛዉም ምንባብ የሚያነሳቸዉ ጥያቄዎች የሚገኙበት ሁለተኛዉ ምድብ ከጸሐፊዉ


ትክክለኛዉ ይዘት ጋር የሚዛመድ ነዉ፡፡ “ይዘት” ደግሞ ከቃላት ፍች በዓረፍተ ነገሮች መካከል ካሉት ሰዋሰዋዊ
ግንኙነቶችና መዛግብቱ የተለያዩ በሚሆኑባቸዉ ምንባቦች የመጀመሪያ ምንባቡ ከተመረጠበት ሁኔታ ጋር
የሚዛመድ ነዉ፡፡

በተጨማሪም “ታሪካዊ ዓዉደ ንባብ” ከሚለዉ ሥር የተጠቀሱትን ነገሮች ያካቲታል፡፡ ከእነዚህም መካከል

 እንደ ዲናር ፤
 የሰንበት መንገድ ወይም
 “የከፍተኛ ቦታዎች” ፤ወዘተ…ፍቺዎች ለአብነት ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡

በአብዛኛዉ እነዚህ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ የሚቀርቡ የፍቺ ጥያቄዎች ናቸዉ፡፡ ጳዉሎስ በ 2 ኛቆሮ.5፡16
ላይ “ክርስቶስንም በሥጋ እንደሆነ ያወቅነዉ ብንሆን እንኳ አሁን ግን ከእንግዲህ ወዲህ እንደዚህ

7
አናዉቀዉም” ሲል የጻፈዉን በሚያነብበት ጊዜ “በሥጋ” የተባለለት ማን ነዉ? ክርስቶስ ነዉ ወይስ እርሱን
የሚያዉቀዉ ሰዉ? ብሎ መጠየቅ አለበት፡፡

 ጳዉሎስ ክርስቶስን የሚናዉቀዉ “ከዓለማዊ አስተሳሰብ አንጻር አይደለም” ለማለት የፈለገዉ አሳብ
 አሁን ክርስቶስን የምናወቀዉ “በምድራዊ ሕይወቱ አይደለም” ከሚላዉ ፍጹም የተለየ ነዉ፡፡

እንደዚህ ዓይነት ጥያቄዎችን ለመመለስ ከመጽሐፍ ቅዱስ ወጭ ሌላ እገዛ ያስፈልጋል፡፡ እንዲሁም አንድ ሰዉ
ለእንደነዚህ ዓይነት ጥያቄዎች የሚሰጣቸዉ መልሶች ጥራት በሚጠቀሚባቸዉ ምንጮች ጥራት ላይ
ይወሰናል፡፡

 ጥሩ ሐቲታዊ ማብራሪያ ለመጠቀም የምትፈልገዉ እዚህ ላይ ነዉ፡፡


 ነገር ግን በማብራሪያ መጽሐፍ መጠቀሙ አስፈላጊ ቢሆንም የመጨራሻዉ ተግባር መሆኑን መዘንጋት
የለብንም፡፡

መሣሪያዎች፡ ጥሩ ሐቲት ለመሥራት


 ከመጽሐፍ ቅዱስ ዉጭ የሚንጠቀምባቸዉ መሣሪያዎች የሚከተሉት ናቸዉ፡፡
ጥሩ የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት
የመጽሐፍ ቅዱስ ማብራሪያ
በጥሩ ሁኔታ የተተረጎመ መጽሐፍ ቅዱስና
ሌሎች ማብራሪያዎች ናቸዉ፡፡

መጽሐፍ ቅዱስን መጽሐፍ በመጽሐፍ ለማጥናት እነዚህ ወሰኝ መሣሪያዎች ናቸዉ፡


 ሁለተኛዉ ተግባር፤የአፈታት ጥበብ(ሥነ አፈታት)

ምንም እንኳ ሥነ አፈታት የሚለዉ ቃል ሐቲትን ጨምሮ ሁሉንም የትርጉም መስክ የሚያጠቃልል ቢሆንም
ጥንታዊ ምንባቦች ለአሁኑ ዘመን ስለሚኖራቸዉ ተዛምዶ በሚያስረዳ ጠበብ ያለ አገባብም ያገለግላል፡፡
ስለሆነም በዚህ ጽሁፍ ዉስጥ ቃሉን የሚንጠቀመዉ “እዚህ አሁን” መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል? በሚላዉ
አሳብ ዙሪያ የሚነሱትን ጥያቄዎችን ለማስተናገድ ነዉ፡፡

 መጽሐፍ ቅዱስን እንዴት ማጥናት እንደሚቻል ማወቁ አስፈላጊ ነዉ፡፡


 ይህም ወደ ጥሞናዊ ንባብ ይመረናል፡
 ለዚህም ነዉ ተገቢዉ “ሥነአፈታት” ከጠንካራ “ሐቲት “ ይጀምራል የሚባለዉ፡፡

አንድ ሰዉ በእዚህና አሁን የማይጀምርበት ምክንያት ተገቢዉ የአፈታት ጥበብ ቁጥጥር የሚገኘዉ
የመጽ/ቅዱስ ምንባብ በተጻፈበት የመጀመሪያ አሳብ ዉስጥ በመሆኑ ነዉ

 ሰዎች የመጽሐፍ ቅዱስን ቃል እየጠመዘዙ እንዳሻቸዉ ሊተረጎሙት ይችላሉ፡፡


 እንዲህ ዓይነቱ ሥነ አፈታት ሙሉ ለሙሉ ግላዊ ስለሚሆን
 የእገሌ አተረጓጓም ትክክል ነዉ፤
 የእገሌ ግን ትክክል አይደለም ማለት ከማይቻልበት ደረጃ ይደርሳል፡፡

 ሞርሞኖች በ 1 ኛ ቆሮ.15፡29 ላይ ተመሥርተዉ ሙታንን ማጥመቃቸዉ፣ ወይም

8
 የይሖዋ ምስክሮች የክርስቶስን አምላክነት መካዳቸዉ፣ወይም
 በማር 16፡18 ን መሠረት በማድረግ እባብ የሚይዙ ሰዎች፣ወይም
 የብልጽግና ሰባኪዎች በ 3 ኛዮሐ 2 ላይ ተመስርተዉ የሚያስተላልፉት ትም/ት የተዛባ አተረጓጎምን የተከተለ ነዉ

የእያንዳንዳቸዉ ስህተት የተንጸባረቀዉ ስነ አፈታት ላይ ሲሆን ለዚህም ምክንያቱ የአፈታት ጥበባቸዉ በጥሩ
ሐቲት ቁጥጥር ያልተደረገበት መሆኑ ነዉ፡፡

የወይይት ጥያቄ

ሰዎች የመጽሐፍ ቅዱስን ቃል እየጠመዘዙ እንዳሻቸዉ የሚተረጎሙባቸዉ ሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች
የትኞቹ ናቸዉ? ክፍሉን ምን ብላዉ ይተረጉማሉ?

አንድ ሰዉ ዮፍታሔ እንዳደረገዉ የሞኝነት ስለት ተስሎ ልጁን እንዳይገድል (መሳ.11፡29-40) ወይም ሴቶች
ፀጉራቸዉን ከኋላ እንዳያጎፈሩ (በማርቆ.13፡15 “ከሰገነትም ያለ ወደ ቤት አይዉረድ” ስለሚል)
የሚከለክላቸዉ ምንድነዉ?

 በእርግጥ ማንም ሰዉ እንዲህ ዓይነቱን የሞኝነት ተግባር እንዳይፈጽም የጋራ ግንዛቤዉ ማድረግ
ይረደዋል፡፡
 መጽሐፍ ቅዱስ ለራሳችን ምን እንደሚል ለማወቅ እንፈልጋለን፡፡
 ነገር ግን ደስ ያለንን እንድል አድረገን ስናበቃ መንፈስ ቅዱስን “ተጠያቂ” ልናደርገዉ አንችልም፡፡
 የመጀመሪያዉን አሳብ ያስተላለፈዉ እርሱ ነዉና ፡፡
 ስለሆነም መንፈስ ቅዱስ ለእኛ የሚያደርግልን እገዛ የመጀመሪያዉን ፍቺ እንድናገኝ መርዳትና
የተገኘዉን አሳብ ከሁኔታችን ጋር ለማዛመድ በታማኝነት በምንጣጣርበት ጊዜ ከጎናችን መቆም ነዉ፡፡
 አንድ መጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ መጀመሪያ ያላስተላለፈዉን መልዕክት ዛሬ ሊያስተላፍ
አይችልም፡፡
 በሌላ አገላለጽ ለእኛ እንደሚተላለፈዉ እዉነተኛ የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባብ ፍቺ
እግዚአብሔር መጀመሪያ በተናገረበት ጊዜ እንዲተላለፍ የፈለገዉ ነዉ፡፡
 ይህ የመነሻ ነጥብ ነዉ፡፡
 የመጽሐፍ ቅዱስ አሳብ ትክክለኛነት የሚያጸድቀዉ ማን ነዉ?
 በእግዚአብሔር ቦታ የሚወስነዉ ማን ነወ?
 በዚህ ጉዳይ ላይ
 የሮም ካቶሊካዊት ቤ/ክ ይፋዊ አስተምህሮ የምንባብን የተሟሉ ፍቺዎች ሁሉ ይወስናል፡
 ፕሮቴስታንቶች ግን እንዲህ ዓይነት ሥልጣን-አዘል አካል ስሌለለን አንድ ሰዉ የጠለቀ መልዕክት
እንዳገኘ በሚነገርበት ጊዜ በጥንቃቄ ልንይዘዉ ይገባል፡፡
 በተለይም የተጠቀሰዉ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል አሁን ተገኘ የተባለዉን ፍቺ የማይሰጥ ከሆነ ጥብቅ
ጥንቃቄ ማድረጉ ተገቢ ነዉ፡፡
 እጅግ ብዙ ኑፋቄዎች የተከሰቱት በዚህ መንገድ ነዉ፡፡

መሠረታዊ መሣሪያ፡- በጥሩ ሁኔታ የተተረጎመ መጽሐፍ ቅዱስ

66 ቱ የመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፍ በመጀመሪያ በሦስት ቋንቋዎች የተጻፉ ናቸዉ፡፡

9
 በእብራይስጥ
 አረማይክና
 በፅርዕ (በግሪክ)
 በአብዘኛዉ የብሉይ ኪዳን ክፍል በእብራይስጥ፤
 የዳንኤል ግማሽና ከዕዝራ 2 ምንባቦች የዕብራይስጥ እህት ቋንቋ በሆነዉ በአረማይክና
 ጠቅላላዉ አዲስ ኪዳን በፅርዕ (በግሪክ) ተጽፎአል፡፡
መጽሐፍ ቅዱስን ለማንበብና ለማጥናት የሚያስፈልገዉ በተጣራ ሁኔታ ከእነዚህ
የሰነድ ጥያቄ
 የመጽሐፍ ቅዱስ ተርጓሚዉ የመጀመሪያዉ ጭንቀት
 እርሱ የሚጠቀምበት የዕብራይስጥ/የፅርዕ/ግሪክ ቃል ከጸሐፊዉ ብዕር
ከፈለቀዉ/እየተናገረዉ ከሚጽፍ ሰዉ ከወጣዉ የመጀመሪያዉ ቃል ጋር የሚቀራረብ
መሆኑን ማረጋገጥ ነዉ፡፡
ምንም እንኳ በብሉይና አዲስ ኪዳን መካከል የሰነድ ችግሮች የተለያዩ ቢሆኑም መሠረታዊ
ጉዳዮች ተመሳሳይ ናቸዉ፡፡
የመጀመሪያ ሰነዶች በእጃችን የሉም፣

በእጃችን የሚገኙት (ጥንታዊ ትርጉሞችን ጨምሮ ለአሥራ አራት መቶ ዓመታት በተደጋጋሚ


በእጅ ሲገለበጡ የኖሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ቅጂዎች ናቸዉ፣

ምንም እንኳ አብዘኛዎቹ የብሉይም ሆኑ አዲስ ኪዳን መጽሐፍት ሰነዶች ከመካከለኛዉ ዘመን
የኋለኛዉ አጋማሽ ቢመጡና ተመሳሳይነት ቢኖራቸዉም እነዚህ የኋለኞቹ ሰነዶች ከቀደምት
ቅጂዎችና ትርጉሞች በከፍተኛ ደረጃ ይለያሉ፡፡

ስለዚህ ጽሑፍ ዓላማ መረዳት የሚገባቸዉ ሦስት ነገሮች፡-


 ሰነዳዊ ሂስ (textual crirticism) ጥንቃቄ በታከለበት ቁጥጥር የሚሠራ መሆኑ ነዉ፡፡
 ተርጓሚዉ ምንባቦቹን በምመርጥበት ጊዜ ከግምት ዉስጥ የሚያስገባቸዉ ሁለት ዓይነት
መረጃዎች አሉ፡፡ እነዚህም
 ዉጫዊ መረጃ (የሰነዶች ባሕሪና ጥናት) እና
 ዉስጣዊ መረጃ (መጽ/ቅዱስን በእጃቸዉ የሚገለብጡ ሰዎች የሚፈጽሙዋቸዉ ስሕተቶ)
ናቸዉ
 ምሁራን ለእነዚህ መረጃዎች ለእያንዳንዳቸዉ ምን ያህል ክብደት ሊሰጡ
እንደሚገባ የተለያዩ አሳቦችን ያቀርባሉ፡፡
 ዉጫዊ መረጃ የተለየዉን ምንባብ ጥረትና ዕድሜ ከሚደግፉ ሰነዶች ጋር የተያያዘ ነዉ፡
 ይህ ለብሉይ ኪዳን ሙሉ ለሙሉ ለማለት ይቻላል የመካከለኛዉ ዘመን ቅጂዎች በሆኑት
የዕብራይስጥ ሰነዶችና ከዚያ የቀደመ ዕድሜ ባላቸዉ የፅርዕ(የግሪክ)
ትርጉሞች[የሴፕቱዋጄንት(LXX)] አንዱን የመምረጥ ጉዳይ ነዉ፡፡
 ዕብራይስጥ ሰነዶች ከፍተኛ ጥንታዊነትን እንደሚያንጸባርቁና ነገር ግን ብዙዉን ጊዜ
የሴፕቱዋጄንትን እርማት እንደሚጠይቁ የምሁራን ዘገባ ያስረዳል፡፡

ለአዲስ ኪዳን የተሻለ ዉጫዊ መረጃ ግብፅ አገር ነዉ፡፡

10
ጥንታዊዉ መረጃ በሌሎች ጥንታዊ የሮም ግዛቶች ተመሳሳይ የዕድሜ አቻዎች
ሲጠናከር፤መረጃዉ እንደ ወሳኝ ይቆጠራል፡፡
 ዉስጣዊ መረጃ ከጻሐፊዎችና ከገልባጮች ጋር የተያያዘ ነዉ፡፡
 የመጽሐፍ ቅዱስ ተርጓሚዎች
 ሁለት/ከዚያ በለይ የተለዩ ምንባቦች በሚያጋጥሟቸዉ ጊዜ በአብዘኛዉ የትኞቹ
ስህተት እንደሆኑ ያዉቃሉ፡፡
 ለዚህም ምክንያቱ ምሁራን የገልባጮችን ልማዶችና ዝንባሌዎች በጥንቃቄ በማጥናት
ሊያዉቋቸዉ መቻላቸዉ ነዉ፡፡

“ሳይገባዉ” የሚላዉ ቃል በየትኞቹም ጥንታዊና አስተማመኝ የፅርዕ ሰነዶች ዉስጥ


አይገኝም፡፡

በላቲንና በኋለኞቹ የፅርዕ ትርጉሞች ዉስጥ ሊካተት የቻላዉ ከቁጥር 27 ተወስዶ ነዉ፡፡

ሁሉም የታወቁ መዛግብት በቁጥር 27 ለይ ይህንኑ ቃል ተጠቅመዋል፡፡

እዚህ ለይ በአብዛኛዉ ተርጓሚዎች የሚጠቀሙት ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ


የታረሙትን የፅርዕና የዕብራይስጥ ምንባቦች እንደሆነ መገንዘቡ ጠቃሚ ነዉ፡፡

ለአዲስ ኪዳን ይህ ማለት “ምርጥ ምንባብ” የመስኩ ኤክፖርቶች በሆኑት ምሁራን


ቀደም ሲል የተወሰነ ነዉ ማለት ነዉ፡፡

 ምንም እንኳን ሰነዳዊ ሂስ ሳይንስ ቢሆንም እጅግ ብዙ ሰብአዊ ልዩነቶችን ስለሚያካትት


ቀጥተኛ ሳይንስ አይደለም፡፡
 አንዳንድ ጊዜ በተለይም ተርጓሚዎቹ በቡድን የሚሠሩ ከሆነ
 የትኛዉ ልዩ ምንባብ የመጀመሪያ ፤
 የትኛዉ ደግሞ በጽሑፍ ከመገልበጥ የመጣ ስሕተት እንደሆነ ለመወሰን
 የተለያዩ አቋሞችን ይይዛሉ፡፡
 ብዙዉን ጊዜ እንዲህ ዓይነት ሁኔታዎች በሚከሰቱበት ጊዜ
 የአብዘኞቹ ምርጫ በዋናዉ ትርጉም ዉስጥ ሲካተት፤
 የአናሳዎቹ ምርጫ በግርጌ ማሰውታዉሻ እንዲሠፍር ይደረጋል፡፡
ኬ ጄ ቪ የሚላዉ የእንግሊዝኛ መጽሐፍ ቅዱስ በዓለም እጅግ የታወቀ ብቻ ሳይሆን
የእንግሊዝኛ ቋንቋም ሕያዉ መግለጫ ነዉ፡፡
በዚህ መጽሐፍ ቅዱስ ዉስጥ ዘመን የማይሽራቸዉ(ሐረጎች)የእንግሊዝኛ ቋንቋ ሐረጎች
ሰፊራዉ ይገኛሉ፡
ይሁንና በ 1611 ዓ.ም ሥራዉን ያካሄዱት የኬ ጄ ቪ ተርጓሚዎች
 የተጠቀሙባቸዉ የአዲስ ኪዳን መዛግብት ከሺህ ዓመታት በለይ በእጅ
በመገልበጣቸዉ ምክንያት ስሕተቶች የታጨቁባቸዉ ጥንታዊ ሰነዶች ነበሩ፡፡
 ከእነዚህ ስህተቶች ጥቂቶቹ የተወሰኑ ምንባባችን ፍች ቢለዉጡም የዶክተሪን ለዉጥ
አያመጡም፡፡
 ለዚህ ነዉ እንግዲህ መጽሐፍ ቅዱስን ለማጥናት የሚፈልግ ሰዉ ከኬጄቪ በስተቀር
የትኞቹንም ዘመናዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች መጠቀም የሚኖርበት፡፡

11
የቋንቋ ጥያቄ

 ሁለት ዓይነት አሳቦች፤ ማለትም


 ቃላዊና
 ሰዋሰዋዊ ምርጫዎች ወደ ዋናዉ የአተረጓጎም ሳይንስ ይመሩናል፡፡
 ችግሩ ቃላትንና አሳቦችን ከአንዱ ወደ ሌላዉ ቋንቋ የማስተላለፉ ጉዳይ ነዉ፡፡
 ዘመናዊ የአተረጓጎም ንድፈ አሳቦች የሚያካቲታቸዉን ፍሬ ነገሮች ለመረዳት የሚከተሉትን
ሙያዊ (ቴክኒካል) አገላለጾችን መገንዘቡ ጠቃሚ ነዉ፡፡
ሙያዊ (ቴክኒካል) አገላለጾች

 መነሻ ቋንቋ  ታሪካዊ ርቀት


 ተቀባይ ቋንቋ  የአተረጓጎም ቲዎሪ(ንድፈ አሳብ)

መነሻ ቋንቋ፡- ይህ ትርጉም


 አሳቦችን የሚያቀርብልን ቋንቋ ሲሆን ስለ መጽ/ቅ ስንነጋገር ዕብራይስጥ፣አረማይክ/ፅርዕ መሆኑ
ነዉ
ተቀባይ ቋንቋ፡-
 አሳቦች ከመጀመሪያዉ ቋንቋ የሚመለሱበት ሲሆን መጽሐፍ ቅዱስን አስመልክቶ
እንግሊዝኛ፣አማርኛ ወዘተ… ሊሆን ይችላሉ፡፡

ታሪካዊ ርቀት፡- ይህ

 በቃላት
 በሰዋሰዉና
 በፈሊጣዊ አነጋገሮች ረገድ
 በመነሻ (በመጀመሪያ) ቋንቋና
 በተቀባይ ቋንቋ መካከል የሚገኙትን ልዩነቶች የሚያሳይ ነዉ፡፡

የአተረጓጎም ቲዎሪ(ንድፈ አሳብ)፡- ይህ

 በሁለት ቋንቋዎች መካከል ያለዉን ልዩነት ለማጥበብ ምን ያህል ርቆ መሄድ እንደሚቻል


የሚያስረዳ ንድፈ አሳብ ነዉ፡፡
ለምሳሌ፡
 አምፑሉን ለማያቁ ሰዎች አሳቡን ለመግለጽ “ችቦ” የሚል ቃል መጠቀም ይቻላል?/
 አምፑሉን “አምፑል” ብለን በመተርጎም ልዩነቱን አንባቢዉ ለራሱ እንዲፈልግ እናድርግ?
 በአደባባይ መሳሳም ፀያፊ ለሆነባቸዉ ማኅበረሰቦች
 “ቅዱስ አሳሳም” ን “እጅ መጨባበጥ” ብለን እንተርጉመዉ?

እነዚህ ሶስት ቃላት ከሚከተሉት መሠረታዊ የአተረጓጎም እሳቤዎች ጋር እንዴት እንደሚዛመዱ


እናስተዉል፡፡

ቃል በቃል፡-

12
 የመነሻዉ ቋንቋ ቃላትና ሐረጎች ስሜት በሚሰጥ መልኩ በተቀባይ ቋንቋ ዉስጥ ቃል
በቃል እንዲተላለፉ የሚደረግበት አተረጓጎም ነዉ፡፡
 ቃል በቃል ትርጉም ታሪካዊ ርቀቱን እንዳለ ጠብቆ ያሸጋግራዋል፡፡
ነፃ፡-
 የመጀመሪያዉን ትክክለኛ ቃላት ለመጠበቅ ሳይጨነቁ አሳቡን ብቻ ለማስተላለፍ
የሚደረግ ጥረት ነዉ፡፡
 ነፃ ትርጉም በተቻለዉ መጠን ታሪካዊ ርቀትን ለማስወገድ ይጥራል፡፡
 አቻዊ ተዛምዶ፡-
 ይህ የመነሻዉን ቋንቋ ቃላት ፈሊጣዊ አነጋገሮችና ሰዋሰዋዊ መዋቅሮች በተቀባዩ ቋንቋ
አቻዊ አገላለጾች ለመተካት ጥረት የሚደረግበት አተረጓጎም ነዉ፡፡
 እንዲህ ዓይነቱ አተረጓጎም የታሪካዊና ሐቃዊ ጉዳዮችን ታሪካዊ ርቀት እንዳለ ሲጠብቅ የቋንቋ
፣የሰዋሰዉና የስልት ጉዳዮችን ከተቀባይ ቋንቋዉ ጋር ያዛምደዋል፡፡

አንዳንድ ጊዜ ቃል በቃል ወይም ነፃ አተረጓጎሞች ከሚገባዉ በላይ በመለጠጣቸዉ “የሐዋሪያዉ


ጳዉሎስ መልዕክት ወደ ሮሜ ሰዎች” የሚለዉ “ወደ ዋሽንግታን ሰዎች” (!) ተብሎ
ተተርጉሟል፡፡

ሮቤርት ያንግም በ 1862 ባሳተመዉ ቃል በቃል ትርጉሙ (1 ኛቆሮ.5፡1 ን) “በእናንተ መካከል ግልሙትና
እንዳለ ይወራል፤ እንዲህ ዓይነቱ ግልሙትና በአሕዛብ መካከል እንኳ አልተሰማም፤ የአባቱን ሚስት
የወሰደ ሰዉ በእናንተ ዘንድ አለና (!)”ሲል ተተርጉሟል፡፡

8 ዛሬ የምንጠቀምባቸዉ የእንግሊዝኛ መጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች ከታሪካዊ ርቀት አንጻር


የሚከተላዉን ሊመስሉ ይችላሉ፡-
9 ቃል በቃል አቻዊ ተዛምዶ ነፃ
10 ኬጄቺ አርኤስቪ ኤን አር ኤስቪ ኤንአይቪ ጂኤንቪ
ፊሊፕስ ኤልቪ
11 ኤን ኤስቪ ኤንኤቪ ጄቪ(Jerusaleme Bible)
1. ኤንኢቪ
 ከሁሉም የሚሻለዉ የአተረጓጎም ቲዎሪ አቻዊ ተዛምዶ ነዉ፡፡
 ቃል በቃል አተረጓጎም ብዙዉን ጊዜ እንደ ሁለተኛ ምንጭ ጠቃሚ ሲሆን
 ፅርዑ ወይም ዕብራይስጡ ምን ይመስል እንደነበር ለመገንዘብ ያስችላል፡፡
 ነፃ ትርጉምም ስለ ምንባቡ ፍች አስተሳሰብህን ለማንቃት ይረዳል፡፡
 ነገር ግን ለማንበብና ለማጥናት የምንጠቀምበት መሠረታዊ አተረጓጎም እንደ ኤን
አይቪ ዓይነት ሊሆን ይገባል፡፡

13

You might also like