Download as docx, pdf, or txt
Download as docx, pdf, or txt
You are on page 1of 27

የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ

የ 13 ኛ ዙር ድህረ -ምረቃ ዲፕሎማ ፕሮግራም

በወንጀል መከላከል ኦፕሬሽን ዋና መምሪያ በ ቪ አይ ፒ እና ዲ/ጥ/ፖ/መምሪያ ሬጅመንት -1


ሻምበል 1 የተደረገ የ 39 ቀናት የተግባር ልምምድ ሪፖርት

አዘጋጅ፡- ዕ/መኮንን እንድሪስ ተካ


መ/ቁጥር፡- 103/15Aaa

10/01/2016 ዓ.ም
ሰንደፋ ኢትዮጵያ

1
ምስጋና
በመጀመሪያ ለሁለም ነገር ስኬት ላበቃኝ ለዓለማቱ ጌታ ለሆነው ለአላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ምስጋና ይገባው ።በመቀጠል
ለኢ/ፖ/ዩኒቨርሲቲ መምህራን ፣ለመስክ አሰልጣኞቼ ፣ጓደኞቼ እና ለቪ አይ ፒ እና ዲ/ጥ/ፖ/ መምሪያ ሬጅመንት 1 ሻንበል
1 ለሚገኙት አመራርና አባላት ከልብ የመነጨ ምስጋና ላቀርብ እወዳለሁ።

i
የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

ማውጫ

ርዕስ ገፅ
1. መግቢያ.......................................................................................................................................4
2. የተለማመዱበት ቦታ አጠቃላይ መግለጫ/የሰሩበት የፖሊስ ተቋም አደረጃጀት...............................................5
3. በየስራ ክፍል ያለው የፖሊስ አባላት ብዛት...........................................................................................6
4. የተግባር ልምምድ ቦታ አዘውትሮ የሚፈፀሙ የወንጀል አይነቶች በቅደም ተከተል 10
5. የሚፈፀሙ ወንጀሎች መንስኤዎቻቸዉ እና እነዚህ ወንጀሎች ያስከተሉት ችግር...............................................11
5.1 የሚፈፀሙ ወንጀሎች መንስኤዎቻቸው፡...........................................................................................11
5.2 ወንጀሎቹ ያስከተሉት ችግር:........................................................................................................12
6. በልምምድ ወቅት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት........................................................................................13
6.2 በወንጀል መከላከል በቪአይፒ እና ዲፕሎማቲክ መምሪያ በሬጅመንት አንድ በሻምበል አንድ አራት የተከናወኑ
ተግባራት.......................................................................................................................................13
7. በዋና ዋና ተግባራት ክንውን የተገኘው ትምህርት/Lesson/.........................................................................14
7.1 በወንጀል መከላከል መስክ በቪአይፒ እና ዲፕሎማቲክ ፖ/መምሪያ በሬጅመንት አንድ ሻምበል አንድ የተገኘ
ትምህርት፡.....................................................................................................................................14
8. በንድፈ-ሀሳብና በተግባር መካከል ያለው ልዩነት፡.....................................................................................15
9. ህብረተሰቡ በፖሊስ ስራዎች ላይ ያለው ተሳትፎና እገዛ..............................................................................16
10. አባሎች እና አመራሮች ህገ-መንግስቱን እና ሌሎች ህጎችን በማክበርና በማስከበር የፖሊስን ስራ የመፈፀም ብቃት....17
11. የአባሎች እና የአመራሮች ፖሊሳዊ ዲሲፕሊንና ስነ-ምግባር ሁኔታ...............................................................18
12. በልምምድ ወቅት ዕጩ መኮነኑን ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ የመፍትሔ እርምጃዎች......................................19
13. በልምምድ ቦታ የሚታዩ ዋና ዋና ችግሮች..............................................................................................22
14. የመፍትሄ ሀሳቦች /Recommendations/.........................................................................................22
15. ማጠቃለያ....................................................................................................................................24
16. ዋቢ መረጃዎች..............................................................................................................................24

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ ii


የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

የሰንጠረዥና የምስል ማውጫ


ምስል 2.1፡- ቪ አይ ፒ እና ዲ/ጥ/ፖ/ መምሪያ አደረጃጀት.................................................................................6
ሰንጠረዥ 3.1፡- የሻምበሏ የስራ ክፍል የሰው ሃይል ብዛት.................................................................................6
ሰንጠረዥ 3.2፡- የሻምበሏ አባላት የሰው ሃይል በሃላፊነት ደረጃ..........................................................................7
ሰንጠረዥ 3.4፡- የሻምበሏ አባሎች የሰው ሃይል በት/ት ደረጃ............................................................................8
ሰንጠረዥ 3.5፡- የሻምበሏ አባሎች የሰው ሃይል በብሔር ደረጃ..........................................................................8
ሰንጠረዥ 3.6፡- የሻምበሏ አባሎች የሰው ሃይል፡በቅጥር ዘመን...........................................................................9

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ iii


የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

1. መግቢያ
በሀገራችን ኢትዮጵያ የወንጀል አይነቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየዘመነ በመምጣቱ እና የአፈፃፀም ዘዴው ውስብስብ እና
ዘመኑ ባፈራቸው የቴክኖሎጂ መሳሪያዎች በመታገዝ የችግሩን አስከፊነት በመቀነስና ከዘመኑ ጋር የዘመነ የፖሊስ ሃይል
ለማፍራት መንግስት በያዘው እቅድ መሰረት የ 13 ኛ ዙር ድህ-ምረቃ ፕሮግራም ዲፕሎማ ዕጩ መኮነኖችን ተቀብሎ
በማስተማር ላይ ይገኛል ፡፡ይህንን ተከትሎ ከ 1 ዓመት ትምህርት እና ስልጠና በኋላ የተግባር ልምምድ በወንጀል
መከላከል ዋና መምሪያ ቪ አይ ፒ እና ዲ/ጥ/ፖ/መምሪያ ማለትም በወንጀል መከላከል የስራ ዘርፍ በተለያዩ የስራ መስኮች
ለአንድ ወር ከ 9 ቀናት የተግባር ልምምድ እያደረኩ በእለት ተእለት ያከናወንኳቸውን የስራ ክንውን የሚገልፅ ሪፖርት
ነው።

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ 4


የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

2. የተለማመደበት ቦታ አጠቃላይ መግለጫ/የሰሩበት ተቋም አደረጃጀት


ልምምዴን ያደረኩት በወንጀል መከላከል ዋና መምሪያ በቪ አይ ፒ እና ዲ/ጥ/ፖ/ መምሪያ ሲሆን
የመምሪያው ሪጅመንቶች በ 6 ሪጅመንት የተከፋፈለ ነው ። ከ 1-3 ያሉት ቪአይፒ ወይም ደግሞ የአገር
ውስጥ ባለስልጣንን የሚያጅቡ እና የሚጠብቁ ከ 4-6 ደግሞ ዲፕሎማቲክ ወይም ደግሞ የአገር ውጭ
አምባሳደር የሚጠብቁ እና የሚያጅቡ ናቸው ።በመሆኑ እኔም በሬጅመንት 1 ሻንበል 1 ልዩ ቦታው ሀያት
ካምፕ ልምምዴን አከናውኛለሁ። ይህ ሬጅመንት በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 3 ሚሊኒየም አዳራሽ በስተግራ
በኩል አምባሳደር ጀርባ የሚገኝ ሲሆን ይህ ሬጅመንት በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 3 እና ወረዳ 2 ፖሊስ ጣቢያ
ያዋስነዋል። ይህ ሬጅመንት በዋናነት ተልዕኮው ወንጀልን መከላከል ሲሆን በሬጅመንት 1 ሻንበል 1 ቀጠና
ኤምባሲዎችን መጠበቅ፣ ቪ አይ ፒ መኖሪያ ቤት እና ቤተሰቦቻቸውን መጠበቅ እና ማጀብ ፣የቪ አይ ፒ
መውጫና መግቢያ ሲንቀሳቀሱ እጀባ ማድረግ፣ በሻንበሏ የተለዩ የስጋት ቀጠናዎችን 1 ኛ ኤድናሞል
አደባባይ አካባቢ 24 ሰዓት ውጠራ ማድረግ 2 ኛ አዲሱ ስቴዲየም ዙሪያ አከባቢ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር
ድንገተኛ ፍተሻ ማድረግ፣ 3 ኛ ቦሌ ብራስ አካባቢ 24 ሰዓት ፖትሮል ማድረግ እና በአጠቃላይ በተሰጠው
ቀጠና ህብረተሰቡ በሰላም ወጥቶ በሰላም እንዲገባ የህብረተሰቡን ደህንነት እና ህግ የማስከበር ሚና
ተሰጥቶት ተልዕኮውን እያከናወነ ይገኛል።

የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ 5


ምስሌ 2.1፡- የቪ አይ ፒ እና ዲ/ጥ/ ፖሊስ መምሪያ አደረጃጀት

3. በየስራ ክፍለ ያለው የፖሊስ አባላት ብዛት


ሰንጠረዥ 3.1፡- የሻምበሏ የስራ ክፍል የሰው ሃይል ብዛት
የስራ ክፍል መነሻ ወንድ ሴት ድምር
ተ/ቁ
1. 1 ኛ ሻምበል 91 82 9 91

ከነዚህ የሰው ሃይል ዉስጥ 4 ወንድ እና 01 ሴት ከጅ ሲሆን እስረኛ 1 የታገደ 5 በተጨባጭ በስራ ላይ ያለው ወንድ 68 እና
ሴት 7 በድምሩ 75 ናቸው፡፡

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ 6


የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

ሰንጠረዥ 3.2፡- የሻምበሏ አባላት የሰው ሃይል በሃላፊነት ደረጃ


የሃላፊነት ደረጃ ወንድ ሴት ድምር
ተ/ቁ
1. ሻንበል አዛዥ 01 - 01

2. ሻንበል ምክትል 01 - 01
3. ሻንበል አስተዳደር 01 01
4. ሻንበል ግልጋሎት 01 01
5. ሃይል አስተዳደር/ ሃላፊነት 02 02
የሌላቸው/
6. መቶ አዛዥ 04 - 04
7. መቶ ምክትል 03 01 04
8. መቶ አስተዳደር 03 03
9. ጓድ መሪ 09 03 12

10 ጓድ ምክትል 12 12
11 ቲም አዛዥ/ በአሁኑ ያላደጉ/ 08 08
12 ቲም ምክትል 06 01 07
/በነበሩበት/ያላደጉ
13 አባል 31 4 35
ጠ/ ድምር 82 9 91

ሰንጠረዥ 3.3፡- የሻምበሏ አባላት የሰው ሃይል ፡በማዕረግ ደረጃ

ተ/ቁ ማዕረግ ፆታ ድምር


ወንድ ሴት
1. ም/ኮ/ር 01 01

2. ዋ/ኢ/ር 01 01

3. ኢ/ር 01 - 01

4. ም/ኢ/ር 07 07
5. ዋ/ሳጅን 15 15
6. ሳጅን 16 02 18

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ 7


የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም
7. ም/ሳጅን 19 01 20
8. ረ/ሳጅን 10 01 11
9. ኮንስታብል 12 05 17
ጠ/ድምር 82 9 91

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ 8


የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

ሰንጠረዥ 3.4፡- የሻምበሏ አባሎች የሰው ሃይል በት/ት ደረጃ

ተ/ቁ የትምህርት ደረጃ ፆታ ድምር


ወንድ ሴት
1. ማስተርስ ድግሪ - - -
2. የመጀመሪያ ድግሪ 05 - 05
3 ድፕሎማ 13 02 15
4. ሰርተፍኬት 01 01 02
5. 12 ኛ ክፍል 01 - 01
6. 10 ኛ ክፍል 56 06 62
7. 9 ኛ ክፍል 01 - 01
8. 8 ኛ ክፍል 04 04
9. 3 ኛ ክፍል 01 - 01
ጠ/ድምር 82 9 91

ሰንጠረዥ 3.5፡- የሻምበሏ አባሎች የሰው ሃይል በብሔር ደረጃ

ተ/ቁ ብሔር ፆታ ድምር


ወንድ ሴት
1. ትግራይ 04 01 05
2. አፋር 01 - 01
3. አማራ 25 01 26
4. ኦሮሞ 23 02 25
5. ሱማሌ - - -
6. ሽናሻ - - -
7. ማኦ - - -
8. አደሬ - - -
9. ሲዳማ 04 01 05

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ 9


የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

10. ወላይታ 05 - 05
11. ሃድያ 06 01 07
12. ከምባታ 03 - 03
13. ጉራጌ - - -
14. ጋሞ 01 01 02
15. ከፋ 01 01 02
16. ቤንች - - -
17. ኙዌር - - -
18. ዳውሮ 01 - 01
19. ባስኬቶ 01 - 01
20. ኮንታ 03 - 03
21. በርታ - - -

22. ጌድዮ - - -

23. አሪ 02 01 03
24. ስልጤ 01 - 01

25. አገው 01 - 01
ጠ/ድምር 82 9 91

ሰንጠረዥ 3.6፡- የሻምበሏ አባሎች የሰው ሃይል፡በቅጥር ዘመን

ተ/ቁ ቅጥር ዘመን ፆታ ድምር


ወንድ ሴት
1. 1983 ዓ.ም 01 - 01
2. 1997 ዓ.ም 04 - 04
3. 1998 ዓ.ም 03 - 03
4. 1999 ዓ.ም 04 - 04
5. 2000 ዓ.ም - - -
6. 2001 ዓ.ም - - -

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ


10
የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

7. 2002 ዓ.ም 08 - 08
8. 2003 ዓ.ም - - -
9. 2004 ዓ.ም 03 - 03
10. 2005 ዓ.ም 03 - 03
11. 2006 ዓ.ም 03 - 03
12. 2007 ዓ.ም 09 02 11
13. 2008 ዓ.ም 12 01 13
14. 2009 ዓ.ም 04 - 04
15. 2010 ዓ.ም 13 02 15
16. 2011 ዓ.ም - - -
17. 2012 ዓ.ም 05 01 06
18. 2013 ዓ.ም 08 02 10
19. 2014 ዓ.ም 02 01 03
ጠ/ድምር 82 9 91

4. የተግባር ልምምድ ቦታ አዘውትሮ የሚፈፀሙ የወንጀል አይነቶች በቅድም


ተከተል
ወንጀል በማንኛውም ዜጋ ሊይ የሚፈፀም ሲሆን የሚያደርሰው ተፅዕኖ ቀላል የሚባል አይደለም ስለሆነም
ወንጀልን በመከላከል ፖሊስም ሆነ ማህበረሰቡ በጥብቅ መታገል እና በሰላም ወጥቶ በሰላም መግባት እንዲችል ማድረግ
የማንኛዉም ሰዉ ግዴታ ነዉ፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በዋናነት የፀጥታ ሀይሉ የወንጀል አይነትና ድርጊት ሰዓቱንና ቦታውን
ለይቶ ማወቅ ፖሊስን ይመለከታል፡፡ስለሆነም ወንጀል በማንኛውም የሀገሪቱ ክፍል /አከባቢዎች የሚፈፀም ሲሆን የወንጀል
አይነትና ሁኔታ፤ ወንጀል የሚፈፀመው ሰዓት ፤ቦታ እና በመልካዓ ምድር ወይም በዓይነት ሆነ በድርጊት የተለያዩ ናቸው፡፡
በዚህም መሰረት የወንጀል አይነቶች በቅድም ተከተል ሲዘረዘሩ

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ


11
የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

ስድብ፣ዛቻ፣ መደባደብ እና አከባቢን መረበሽ፣የቤተሰብ ግጭት፣ ቀምቶ መሮጥ እና በንብረት ላይ ቀላል


ጉዳት ማድረስ ፣
የነብስ ግድያ፣ የመኪና ዝርፊያ፣ ቤት ሰበራ ስርቆት፣ የንብረት ዝርፊያ፣ አስገድዶ መድፈር ናቸዉ፡፡
ጫት ቤት ፣ ሽሻ ቤት ፣ አብሮ በመመሳሰል ፣ አብሮ በመሆን ፣ ህዝብና ፖሊስ በሌለበት ሰዓት ጠዋት ሰዎቹ
ሲወጡ ተከትሎ ዝሪፊያ ማካሄድ

በዚህ ምክንያት ልምምድ ያደረኩበት አከባቢ አዘዉትሮ የሚፈፀሙ የወንጀል ዓይነቶች :-

 የኪስ የስርቆት ወንጀል፡- ይህ የወንጀል አይነት የሚፈፀመው በብዛት በታክሲ፤ ህዝብ በሚበዛባቸው ገበያ
ቦታዎች፤ አትክልት ገበያዎች፤ የታክሲ ማውረጃዎችና የህዝብ ባስ መጫኛ ቦታዎች፤ ከተሳፋሪዎች በመመሳሰል
ወዘተ የሚፈፀሙ ወንጀልናቸው፡፡

 መደባደብ እና አካባቢን መረበሽ፡- ይህ ወንጀል የሚፈፀመው ከሆቴል ወጥተው በተለያዩ ነገሮች


ያለመግባባት ሁከት መፍጠር፤ መረበሽ ፤ መስከር እርስ በርስ መደባደብ

 ቅሚያ:- ይህ የወንጀል ዓይነት የሚፈፀመው በቀንም ይሁን በማታ የሚፈፀም የወንጀል ዓይነት ሲሆን
በብዛት የሚፈፅሙ በማታ በተለይ ብራስ/ ቦሌ ድልድይ የጎዳና ልጆች በ መምሰል ቅሚያ ያካሂዳሉ ፡፡

 የመኪና እቃ ስረቆት

 የማታለል ወንጀል

 ያልተፈቀደ ቦታ ላይ በመሆን አበባ መሸጥ


5. የሚፈፀሙ ወንጀሎች መንስኤዎቻቸው እና እነዚህ ወንጀሎች ያስከተሉት ችግር
5.1 የሚፈፀሙ ወንጀሎች መንስኤዎቻቸው፡-

 የሰው/ የህዝብ ብዛት መኖር

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ


12
የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

 ስራ አጥነት እና የስራ አጥ ቁጥር መብዛት


 በሱስ መጠመድ
 የኑሮ ዉድነት መኖር
 የገቢ ምንጭ ያለመኖር
 ድህነት
 የመጠጥ ንግድ ቤቶች መብዛት
 የቤተሰብ ማጣት ችግር
 ግለሰቦች የንብረት አያያዝ/እንዝላልነት መኖር
በአከባቢው የሰው መቀራረብ በብዛት ስለሚኖር፤ጎዳና ተዳዳሪዎች ሰለሚበዙ ፤ እንዲሁምቦሌ ብራስ እና ኤድናሞል አደባባይ
በሚባል አከባቢ የሰው ብዛት መኖር እንዲሁም ሆኖ፤ የተሰራውን ድልድይ ለዝናብ እና ለብርድ መጠለያ መጠቀምን
በሚመስል ለወንጀል መከሰት ምቹ ሆኗል ፡፡ እንዱሁም የጉሊት ገቢያ መኖር ለወንጀል መባባስ መንስኤዎች
ሆነዋል፡፡

5.2 ወንጀሎቹ ያስከተሉት ችግር:-


- የህዝብንና የመንግስትን ገቢ ያሳጣል
- በዜጎች እና በንብረት ላይ ጉዳት ያደርሳል
- የኢኮኖሚያዊ ቀውስ ያሰከትላል
- የስነ-ልቦና ጉዳት ያስከትላል
- ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ማስከተል
- በመንግስት ላይ እምነት ማጣት (ህብረተሰቡ በመንግስት ላይ ያለዉን አመኔታ እንዲቀንስ ያደርጋል)
- በፖሊስ ተቋማትን በስራ ማጨናነቅ እና አመርቂ ዉጤት እንዳይመዘገብ ያደርጋል
- ቤተሰብ መበተን እና ህፃናትን ወደ ጎዳና መውጣት ያስከትላል።
- የአካል ጉዳት ያስከትላል።
- በእለት ተዕለት ክንውን ላይ ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዳይሰፍን ያደርጋል
- ስደት መኖር እና የመሳሰሉት ናቸዉ፡፡

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ


13
የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

6. በልምምድ ወቅት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት


6.2 በወንጀል መከላከል በቪ አይ ፒ እና ዲ/ጥ/ ፖሊስ መምሪያ በሬጅመንት አንድ በሻምበል
አንድ የተከናወኑ ተግባራት
 በሻምበሏ የጥበቃ ቀጠና እና ለጥበቃ የሚወጣ የሰው ሀይል በተመለከተ፡

የሻምበሏ የጥበቃ ቀጠና በቋሚነት በአዱስ አበባ በቦሎ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ሃያት ሆስፒታል አካባቢ ሃያት ካንፕ ሲሆን
በስጋት የተያዙ ቀጠናዎች 3 ናቸው። ከነዚህም በተጨማሪ አዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በጥምረት በመሆን አልፎ አልፎ የሚደረግ
የተለያዩ ፍተሻዎች ኤድናሞል አካባቢ ፣ 22 አካባቢ ፣ ዳሽን ባንክ አካባቢ ፣ አዲሱ ስቴዲየም አካባቢ እና ጅብሰም ት/ቤት
አካባቢ ድንገተኛ ፍተሻ ይደረጋል። ከዚህ በተጨማሪም አልፎ አልፎ ቪ አይ ፒ በስራ ጉዳይ ወደ ውጭ ሲወጣና ሲገባ እጀባ
ይካሄዳል።

ተ/ቁ የጥበቃ ቦታ በቀን በሌሊት በ 24 በወር


ሰዓት

1 የሻንበሏ ሃያት ካንፕ ጥበቃ 6 6 12 360

2 ኤድናሞል ውጠራ 6 6 12 360

2 የአካባቢ ፓትሮል 6 6 12 360

በድምሩ 18 18 36 1080 የሰው ሃይል


ተሰማርተዋል

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ


14
የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

7. በዋና ዋና ተግባራት ክንውን የተገኘው ትምህርት/Lesson/


7.1 በወንጀል መከላከል መስክ በቪ አይ ፒ እና ዲ/ጥ/ፖ/መምሪያ በሬጅመንት 1 ሻምበል 1
የተገኘ ትምህርት፡-

 የወንጀል መከላከል ስራ እንዴት እንደሚሰራ እና እንደሚከናወን፤የአከባቢ ደህንነት እና ሰላም ያለውን ጥቅም፣


ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር እንዴት ወንጀልን እነደምንከላከል ማወቅ እና መረዳት ችያለው።
 የሀይል አዛዥ እና የኮሚቴዎች የስራ ድርሻ እንዴት ስራቸውን እንደሚያከናውኑ እና የተሰጣቸውን ኃሊፊነት መሰረት
በማድረግ ስራቸውን እንዴት እንደሚሰሩ እና የተሰጣቸውን የሰው ሀይል እንዴት እንደሚቆጣጠሩ እና እንደሚመሩ፣
እንደሚያስተባብሩ እና እኔ ኃሊፊነት ቢሰጠኝ እንዴት መምራት እና ማስተባበር እንደምችል ማወቅና መረዳት ችያለው፡፡
 የማነቃቃት ወይም የማስተባበር እና የመምራት ስራ ለምን እንደሚጠቅም ተረድቻለው፡፡
 የቪአይቪ እጀባ ስርዓት እንዴት እነደሆነ እና እንዴት እነደሚታጀብ ማወቅ ችያለሁ፡፡
 ፖሊስ ለሀገሪቱ እና ለህዝቡ የሚኖር እና ቁልፍ መሆኑን የበለጠ ለማወቅ ችያለሁ፡፡
 አመራር እና አባላት እንዴት መቀራረብ እና አንድ ላይ መስራት እንዳለባቸዉ ተረድቻለሁ፡፡
 ወንጀልን ለመከልከል ከአጋር አከላት ጋር መስራት አስፈላጊ መሆኑን ተረድቻላሁ፡፡
 በተወሰነ መልኩ ቢሆንም በንድፈ-ሀሳብ እና በተግባር መካከል ያለ ልዩነቶች መኖሩን ተገንዝብያሁ ፤ማለትም
ስለወንጀል መከላከል የንድፈ-ሃሳብ ትምህርት ብወስድም በአንድ አመት ውስጥ ከወሰድኳቸው የትምህርት አይነቶች
እንደ የወንጀል ፍትህ ስራዐት/CJS፣ወንጀል መከላከል ፣ ክሪሚኖሎጂ ወዘተ በዋናነት እነዚህን መሰረት በማድረግ
ልምምዴን ሳጠናክር ልዩነቶች እንዳሉ ተረድቻለሁ ፡፡
 የፖሊስ አባሎች እና አመራሮች ከማህበረሰቡ ጋር ያላቸው ግንኙነት ጤናማ መሆኑ ለወንጀል መከላከል
ጠቃሚ መሆኑን እና የማህበረሰቡ ድጋፍ ወንጀል መከላከል ዉጤታማ ሊያደርግ እንደሚችል ተረድቻለሁ።
 ወንጀል መከላከል የፖሊስ ብቻ ሳይሆን የሁሉም ማህበረሰብ ኃሊፊነት መሆኑን ተገንዝቤያለሁ፡፡

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ


15
የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

 በመጨረሻ የወንጀል መከላከል ዋና አላማው ህብረተሰቡ በሰላም ወጥቶ በሰላም እንዲገባ እና የአንድ ሀገር እድገት እና
ልማት እንዲሁም ብልፅግና እንዲስፋፋ ለማድረግ ወንጀል መከላከል ቁልፍ እና ወሳኝ መሆኑን በዚህ በተግባር ልምምዴ
ተረድቻለሁ፡፡

8. በንድፈ-ሀሳብና በተግባር መካከል ያለው ልዩነት፡


በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቪርሲቲ በንድፈ-ሀሳብ ደረጃ የወሰድኳቸው ትምህርት እና ስልጠናዎች አሁን በተግባር ልምምድ
እየሰራሁ ካለሁበት ሲታይ ክፍተቱ ይህን ያህል የጎላ ባይሆንም በወንጀል መከላከል ስራዎች ላይ እና በዲሲፕሊን ልዩነቶች
እንዳለ ለማየት ችያለሁ፡
፡ ለምሳሌ፡-

 በንድፈ-ሀሳብ ያለው በፖሊስ ስራ ውስጥ ወንጀልን መከላከል፣ወንጀል ሲፈፀም በፖሊሳዊ ህግ መሰረት ህገ- መንግስትን
ማክበርና ማስከበር ሲሆን ነገር ግን በተግባር የሚታየው ወንጀልን ለመከላከል እና ወንጀል ሲፈፀም የህግ ሰንሰለቱን
አለመጠበቅ ይታያል። ለምሳሌ፡- ወንጀል ሲፈፀም ወንጀለኞችን በጉልበት ለማሳመን መሞከር፤ ለምሳሌ አዲስ አበባ
እና ፌ/ል ፖሊስ ጋር በጥምር ስራ ስንሰማራ ተጠርጣሪ ሲያዝ መደብደብ እና መሳደብ በሁለቱም አባላት ላይ የስነ-
ምግባር ችግር ይታያል።
 በንድፈ-ሀሳብ አመራሮች እና እያንዳንዱ የፖሊስ አባሎች ፖሊሳዊ ሰላምታ በፖሊሳዊ ህግ እና ስነ-ስርዓት መሰረት
ሰላምታ መሰጠት አለበት ሲባል ነገር ግን በተግባር ፖሊሳዊ ሰላምታ ያለመስጠት ችግር አለ፡፡
 በንድፈ-ሀሳቡ መሰረት አመራሮች እና አባሎች ለወንጀል መከላከል ስራ ከመውጣታቸው በፊት
ዝግጁነታቸውን ማረጋገጥ አለባቸው ሲባል በተግባር ግን በጥቂት አመራሮች ኦረንቴሽን ወይም ስለ ስራው ገለፃ
ያለመስጠት ሁኔታ ይታያል።
 ፂም-ፀጉር በአግባቡ ያለመስተካከል፣ደንብ ልብስ አሟልቶ ያለመልበስ በአንዳንድ አመራር እና አባሎች ላይ ይታያል።

 አንዳንድ አባሎች ፈቃድ ተሰጥቷቸው ሂደው ቀን አሳልፈው የመምጣት እና ፈቃድ ሳይሰጣቸው የመንቀሳቀስ
ሁኔታ ይታያል።

9. ህብረተሰቡ በፖሊስ ስራዎች ላይ ያለው ተሳትፎና እገዛ


 በተግባር ልምምድ ባደረኩበት ወቅት ህበረተሰቡ በፖሊስ ላይ ያለው አመለካከት በአወንታዊና በአሉታዊ ጎን ይገለፃል፡-

 በአዎንታዊ ጎን፡-የፖሊስ የስራ አድካሚና አሰልች እንደመሆኑ መጠን የአከባቢው ማህበረሰብ ወንጀልን
መከላከል ከፖሊስ ጋር በመቀናጀት ወንጀል የሚፈፀምባቸውን ቦታዎች እና ለወንጀል መንስኤ
የሚሆኑትን ቦታዎችን ያሳዩናል፤እንዱሁም የተለያዩ የወንጀል ድርጊት ሲፈፀምባቸው ፍትህ ለማግኘት
ሲል እኛን በመተማመን እስከ መኖሪያ ካምፕ ድረስ በመምጣት አቤቱታቸውን እና ጥቆማ ያቀርባሉ፡፡

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ


16
የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

 በአለታዊ ጎን፡-ጥቂት ማህብረተሰብ የፖሊስ አገልግሎት ለአካባቢው ሰላም የሚያሰፍን መሆኑን


ሳይረዱ የግል ጥቅም የሚያሳድድ የሚመስላቸው ውስን ግለሰቦች አሉ።

 በወንጀል የሚሰማሩ ግለሰቦች ግን በፖሊስ ላይ አሉታዊ ምልከታ አላቸው፡፡ ለምሳሌ ፖሊስ የህዝብ
አገልጋይ ሳይሆን የመንግስት የፖለቲካ ስራ የሚደግፍና የሚሰራ ነው የሚል አስተሳሰብ ያላቸው ጥቂት
ግለሰቦች አሉ፡፡ በዚህም ምክንያት በወቅቱ በሚታየው በንሮ ውድነት ምክንያት በየመንደሩ በተለያዩ
ሸቀጣሸቀጥ ላይ የዋጋ ጭማሪ ሲከሰት ህዝቡ በመንግስት ላይ በማማረር ፖሊስንም በዛው ተግባር
ማየት ሌላ ህገወጥ ቤቶች ሲፈርሱ ፖሊስንም በፖለቲካ አይን ማየት ሁኔታዎች ይታያል ።

10. አባሎችና አመራሮች ህገ-መንግስቱን እና ሌሎች ህጎችን በ ማክበርና በማስከበር


የፖሊስን ስራ የመፈፀም ብቃት
የፖሊስ አባላት ከስራ አንፃር በሚሰሩት ስራ በቁርጠኝነት፣በታማኝነት፣በቅንነትና በግልፀኝነት አባሎች ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ
የህጉን ሰንሰለት በመጠበቅ አመራሮች አባሎችን በበላይነት በመቆጣጠር ሃሊፊነትስራቸውን በአግባቡ ያከናውናሉ፡፡

አባሎች አመራሮች በሚሰጡት ትዕዛዝ መሰረት በቅንነት፤በግልፀኝነት የተሰጣቸውን ተልዕኮ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ያለምንም
ቅሬታ በአግባቡ የስራ ግዴታቸውን በህገ-መንግስቱ መሰረት ስራቸውን በብቃት እየተወጡ ይገኛሉ፡፡

11. የአባሎች እና የአመራሮች ፖሊሳዊ ዲስፕሊንና ስነ-ምግባር ሁኔታ


 አመራሮች አባሎችን የአለባበስ ሁኔታ ፀጉር፤ፂም፤መለዮ አለባበስ፤እርስ በርስ በጓዳዊ ዝምድና ፣ ፍቅር የተጠናከረ
እንዲሆን በአባሎች የሚታየውን ክፍተቶችን በመለየት እንዲያስተካክሉ ምክር የመስጠት ሁኔታ አለ፡፡
 አንዳንድ አመራሮች የዲስፕሊን ችግር ያለበትን አባል በመለየት ይመክራሉ፣ግንባታ ይሰጣሉ፤በመግባባት
ችግሩን ይፈታሉ፡፡
 አመራሮች ትዕዛዝ በሰጡት መሰረት አባሎች ፖሊሳዊ ዲስፕሊን ጠብቀው የተሰጣቸውን የስራ ድርሻ
በቅንነት፤በታማኝነት ስራቸውን በአግባቡ ያከናውናሉ፡፡
 በስራ ላይ ፖሊሳዊ ስነ-ምግባር ክፍተት ያሳየውን በመለየት እርስ በርሳቸው እና በአመራሩ ፊት በመገምገም
እንዲስተካከሉ እና እንዲታረም ያደርጋሉ፡፡(ይህ የአመራሮች በጠንካራ ጎን የሚገለፅ ነዉ፡፡)

ደካማ ጎን፡-አብዛኛው የሻምበል አመራሮች እና አባሎች ፖሊሳዊ ዲስፕሊን እና ስነ-ምግባር የተሻሉ ቢሆንም በአንዳንድ
አባሎች አልፎ አልፎ የሚታይ የዲስፕሊን ግድፈቶች እንደሚከተለው አስቀምጫቸዋለሁ፡-

 የደንብ ልብስ አሟልተው ያለ መልበስ ችግር

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ


17
የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም
 ወታደራዊ ቁመና ያለ መሰተካከል ችግር
 በካምፕ ውስጥ እርስ በርስ አለመከባበር፤መሰዳደብ እና መደባደብ
 ከስራ ምደብ ቦታ የመቀያየሪያ ሰዓት ሳይደርስ ቦታ ለቆ ወደ ካምፕ መመለስ
 በጥበቃ ቦታ ላይ ሞባይል መነካካት
 በፎሌን ቆጠራ በሰዓቱ ያለመገኘት ፣ለፊሽካ ትርጉም ያለመስጠት

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ


18
የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

12. በልምምድ ወቅት ዕጩ መኮንኖች ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ የመፍትሔ


እርምጃዎች
በዚህ በ 39 ቀናት በተግባር ልምምድ ወቅት ያን ያህል የተጋነነ ችግር ባይገጥመኝም፡አንዳንድ የተወሰኑ ችግሮች
አጋጥሞኛል፡

ተ/ ያጋጠሙ ችግሮች የተወሰዱ መፍትሔዎች


1 የመፀዳጃ ቤት አጠቃቀም ችግር መኖር በሳምንት ሶስት ጊዜ የፅዳት ፕሮግራም አለ በዚያ ልክ


ተፀድቶ እንዲስተካከል ተደርጉዋል

2 በፖሌን ቆጠራ ሰዓት ሚሊተሪ አሙዋልቶ ከፖሌን ቆጠራ በኻላ በተሰጠ አስተያየት እንዲስተካከል
አለመልበስ/ሚሊተሪ ለብሶ ከስክስ አለማድረግ/በሲሊፐር
ተደርጉዋል
መቆጠር

3 የትራንስፖት ችግር መኖር ውጠራም ሆነ ፓትሮል በሻንበላ ፓትሮል መኪና


ያልተመደበ በመሆኑ በእግር በመንቀሳቀስ ሰርቻለሁ፡፡

4 አባሎች በጥበቃ ቦታ ሞባይል መጠቀም/መጎርጎር በግል አስተያየት ሰጥቻለሁ/ ለመምከርም ሞክሬያለሁ ሙሉ


ለሙሉ ባይስተካከልም ከበፊቱ እንዲስተካከል ተደርጉዋል

5 የደንብ ልብስ አሟልቶ አለመልበስ የማስተካከያ ሃሳብ ሰጥቻለሁ

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ


19
የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

6 የፖሊስ ሰላምታ ያለመስጠት በተለያየ ግዜ የተለያዩ ማስተካኪያ ሃሳብ ሰጥቻለሁ፡፡

8 በማህበራዊ ኑሮ ላይ በቂ ምግብና ያለመኖር ተጨማሪ ከኪሴ ገዝቼ ተጠቅመያለሁ፡፡


በጤፍ ውስጥ አሸዋ መኖር

9 በአባሎች እና አመራሮች ፂም እና ፀጉር ያለመስተካከል በየግዜው በመቆጣጠር እንዲስተካከል አድርገናል እና


በፖሌን ሰዓት ፍተሻ እንዲኖር አድረጌያለሁ

10 አመራሮች ማዕረግ አለማድረግ ግምገማ ላይ ተናግሬ ማስተካከል ችያለሁ

11 በአመራር ወይምበኮሚቴ ያለመናበብ በመድረክ ለማስተካከል ሞክረናል

12 በመድረክ ያለመታገል መደባዊ ትግል እንዲያደርጉ እና ችግርን የመፍቻአንዱና ዋነኛው


መሳሪያ እንደሆነ ተነጋግረናል

13 አባሎችለስራ ሲታዘዙ ቶሎ ያለመውጣት በግል እና በስብሰባ እንዲስተካከል ሞክረናል

14 ገምባሌ ከሚሊተሪው በላይ አውጥቶማሰር በስብሰባ ማድረግ እንደለለባቸው ተነጋግረናል

15 ከፍተኛ የሆነ የማብራት መቆራረጥ መኖር አከባቢው የሀብታምሰፈር ስለሆነ በአብዛኛው ጀኔረተር ነው
እሚጠቀሙት እንዲስተካከል ተደጋጋሚግዜ ለሚመለከተው
አካል ብናቀርብምሊስተካከል አልቻለም።

16 የመጠጥ ውሃ ችግር መኖር በግላችን እየገዛን ተጠቅመናል

17 የመዝሙር እና የሙዚቃ ከፍተኛ የጩኸት ድምፅ መኖር በግል እንዲስተካከል ጥረት አድርጊያለሁ

18 ፅዳት ስራ ላይ ሁሉምተነስቶያለማፅዳት ፅዳት የማያፀዱአባሎችላይ አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰድ


እንዳለበት ተወያይተናል

19 የእለት ተዕለት ስራዎችን ሰርቶያለማስመዝገብ የሚሰሩ ስራዎችበሰዓቱ ካልተመዘገቡ ለሪፖርት እንደሚቸገሩ


ተነጋግረናል

20 ሳምንታዊ ጥይት ቆጠራ ላይ በፕሮግራምያለማስቆጠር በፕሮግራሙ መሰረት መቆጠር እንዳለበት ከአመራሮችጋር


ተነጋግረናል

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ


20
የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

13. በልምምድ ቦታ የሚታዩ ዋና ዋና ችግሮች


በዚህ 39 ቀናት ውስጥ የተግባር ልምምድ ባደረኩበት ሻምበል ውስጥ ያየኋቸው ችግሮች የሚከተለት ናቸው ፡፡

 የተሟላ የሰራዊት መኖሪያ ካምፕ አለመኖር ፤በዚህም ምክንያት የመኝታ ቤት የለም


 አባሎች ስራ በሚወጡበት ግዜ ለሻምበሏ የተመደበ ተሽከርካር ያለመኖር እና ለስራ በእግር መሰማራት

 የተሟላ የመፀዳጃና የሻወር ቤት ያለመኖር

 የአባሎች እና አመራሮች የኑሮ ሁኔታ ያለመመቻቸት (ደሞዝ፤ጥቅማ ጥቅም፤በቂ የሆነ ምግብ)

14. የመፍትሄ ሀሳቦች /Recommendations/


ከክፍሉ በዋነኝነት ትኩረት ተሰጥቶት ሊፈቱ የሚገቡ ጉዳዮች ፡-

እንደተቋም ሰራዊቱ የሚኖርበትን ካምፕ በከተማው እስታንዳርድ ልክ መገንባት፣በየስራ ክፍላቸው መስራትና ማሟላት ፣በሻንበል ሁለትና
ከዚያ በላይ ፖትሮሎች እንዲመደቡ ማድረግ፣ዋናውና አንገብጋቢው ጉዳይ የሰራዊቱ ደመወዝ እና የሬሽን ጉዳይ በአፋጣኝ መፍትሄ
የሚፈልጉ ጉዳዮች ናቸው ።

በተጨማሪ በሁሉም ካምፕ የተሟላ የመፀዳጃ ቤቶችንና የግቢውን ቆሻሻ ማስወገጃ በየግዜው በማምጣት ፅዳት ማድረግ አለበት፤ ውሃ፤
መብራትና ሻወር ቤት በመስራት ሰራዊቱ እንዲጠቀሙ እና እንድገለገሉ መደረግ መቻል አለበት፡፡

ተቋሙ የሰራዊቱን የተሽከርካሪ ችግር ለመፍታት ከመንግስትም ሆነ ተቋሙ ቢያንስ በሻምበል ደረጃ አንድ
ፓትሮልና አንድ እስታንድባይ መኪና መመደብ አለበት። እንዱሁም አባሎችን በስራ በሚሰማሩበት ጊዜና ሰዓት
በሚፈለገው ቦታ ላይ በፍጥነት በመድረስ ስራቸውን በቅልጥፍና ማከናወን አለባቸው ።

መንግስትም ሆነ ተቋሙ የፖሊስ አባሎች እና አመራሮች የኑሮ ሁኔታ ማስተካከል አለበት፡፡


ይህ ሲባል አሁን ሀገራችን ካለው ኑሮ ውድነት አንፃር በመንግስት በኩል በሰራዊቱ የሚከፈለው ደሞዝ እና ጥቅማ ጥቅም በጣም ዝቅተኛ ከመሆኑ አንፃር
ለብዙ አባሎችና አመራሮች ለፍልሰት መንስኤ ሆኖዋል፡፡ስለዚህም በአሁኑ ሰዓት ለአንድ አባል የሚከፈለው ደሞዝ አነስተኛ በመሆኑ ሬሽን 1200 ብር
ለምግብና አስገብተው በእጃቸው 1600 ብር አከባቢ ብቻ ነው

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ


21
የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም
ደሞዝ እየተከፈለው መሆኑ እና ለምግብ የሚያስገቡት 1200 በአግባቡ ማስመገብ ባለመቻሉ ምክንያት በአሁኑ ሰዓት
በካምፕ የሚኖሩ አባሎች እና ጠዋት ያለ ዳቦ ወይም ያለ እንጀራ በሳምንት ሶስት ቀን ፍርፍር ብቻ ይበላሉ። እየተመገቡ
ስራ እየሰሩ ይገኛሉ ፡፡ ይህም በተቋሙ ካለ ከፍተኛ አመራሮች እና ከመንግስት በኩል በጣም አሳሳቢ በመሆኑ ትኩረት
ሊሰጥ የሚገባው ጉዳይ ነው፡፡

15. ማጠቃለያ
ይህ የተግባር ልምምድ የተደረገው በፌ/ፖ/ወን/መከ/ኦፕሬሽን ዋ/መምሪያ በቪ አይ ፒ እና ዲ/ጥ/ፖ/መምሪያ ሬጅመንት 1
ሻምበል 1 ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሶስት ነው

የቀጠና ብዛት ሶስት በአጠቃላይ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት በአካባቢው ይገኛሉ። በነዚህ ተቋማት
ወንጀል እንዳይፈጸምባቸው እና የአከባቢው ማህበረሰብ በሰላም ወጥቶ በሰላም እንዲገባ ለማድረግ በቋሚነትና በእግር
እንቅስቃሴ በማድረግ በቀንም ሆነ በሌሊት የጥበቃ ፣ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በጥምረት ድንገተኛ የፍተሻ ስራ ፣ የእጀባ
ስራ እንዲሁም አልፎ አልፎ ድንገተኛ የአሰሳ ስራዎች አሉ። በዚህ የስራ ክፍል ላይ ለወደፊት በስራ ላይ እንዴት መስራት
እንዳለብኝ በተግባርና በተጨባጭ ሁኔታ የተለያዩ ልምዶችን ማወቅና መገንዘብ ችያለሁ።

16. ዋቢ መረጃዎች
1. የግል ማስታወሻ ደብተር ፣የቀን ውሎ ማስረጃ
2. የተመደብኩበት ሻምበል ፅ/ቤት ውስጥ ያለ ዶክመንት እና የተለያዩ ሪፖርቶች

3. የተመደብኩበት ቦታ ያሉ ሻምበል አመራሮች እና ፃፊዎች

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ


22
የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ


23
የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ


24
የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ


25
የተግባር ሌምምዴ ሪፖረት 2015
ዓ.ም

“በጀግንነት መጠበቅ በሰብአዊነት ማገልገል” ገፅ


26

You might also like