Download as docx, pdf, or txt
Download as docx, pdf, or txt
You are on page 1of 54

በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን

የታክስ ህግ ተገዥነት ሥጋት ሥራ አመራር ዳይሬክቶሬት

የጉምሩክ ሥጋት ሥራ አመራር የስልጠና ማኑዋል

በጉምሩክ ፕሮፋይልና ሥጋት ትንተና ቡድን

ግንቦት 2009

ማውጫ
ምዕራፍ አንድ...................................................................................................................................................4
1 ምንጮች /Reference |
1.1. መግቢያ...........................................................................................................................................4
1.2. ዓላማ..............................................................................................................................................6
1.3. ትርጉም...........................................................................................................................................6
1.4. የጉምሩክ ሀላፊነቶች...........................................................................................................................9
1.5. በጉምሩክ ስራ ላይ ያሉ ተጽእኖዎችና ምክንያቶቻቸው...............................................................................10
1.6. የጉምሩክ ሥጋት ሥራ አመራር ዓላማ....................................................................................................10
1.7. ለሥጋት ሥራ አመራር ትገበራ የሚያስፈልጉ ሁኔታዎች...............................................................................11
1.8. የሥጋት ሥራ አመራር መርህ...............................................................................................................11
1.9. የባለስልጣኑ የስጋት ስራ አመራር ፖሊሲ መርሆዎች...................................................................................12
2.1. የስጋት ስራ አመራር አላማዎች.............................................................................................................12
1.10. የስጋት ስራ አመራር ስርዓት ጠቀሜታዎች...........................................................................................13
1.11. የሥጋት ሥራ አመራር ደረጃዎች.......................................................................................................15
ምእራፍ ሁለት................................................................................................................................................17
2.1. የስጋት ስራ አመራር ታሪካዊ ዳራ...............................................................................................................17
2.2. ሥጋት ሥራ አመራር ከአለም አቀፍ አሰራር አንጻር....................................................................................18
2.3. የጉምሩክ ስጋት ስራ አመራር በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን...........................................................18
ምእራፍ ሶሥት................................................................................................................................................20
3.1. የስጋት ስራ አመራር ሂደት ደረጃዎች /Risk Management Process/...............................................................20
I. ማዕቀፍ ማስቀመጥ /Establish the Context/.......................................................................................21
II. ስጋት መለየት /Identifying Risks/...................................................................................................22
III. ስጋትን መተንተን /Analyzes Risk.................................................................................................24
IV. ስጋት መመዘን እና ደረጃ መስጠት /Assess & Prioritize Risks..........................................................28
V. ስጋትን ማስተናገድ/Addreess Risk....................................................................................................29
VI. ክትትልና ግምገማ /Monitor and Review/.....................................................................................31
VII. ግንኙነት እና ምክክር.....................................................................................................................33
ምእራፍ አራት.................................................................................................................................................34
የጉምሩክ ስጋት ስራ አመራር ትግበራ በዋናው መ/ቤት እና በቅ/ጽ/ቤቶች.......................................................................34
በዋናው መ/ቤት የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት.....................................................................................................34
የገቢ እቃ አወጣጥ የሥጋት ሥራ አመራር............................................................................................................38
የስጋት መምረጫ መስፈርቶች/Risk Assesment Criteria/..............................................................................38
የቅ/ጽ/ቤቶች የስጋት ስራ አመራር ቡድን ዋና ዋና ተግባራት.....................................................................................51
የገቢናወጪ ዕቃዎች ትራንዚት የስጋት መምረጫ መስፈርቶች...................................................................................53
2 ምንጮች /Reference |
የገቢ ትራንዚት..........................................................................................................................................53
የወጪ ትራንዚት........................................................................................................................................54
የገቢ መንገደኞች ስጋት መምረጫ መስፈርቶች.......................................................................................................55
ማጠቃለያ......................................................................................................................................................59
ምንጮች /Reference.....................................................................................................................................61

ምዕራፍ አንድ
1.1. መግቢያ
የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዘመናዊ የጉምሩክ አስተዳደርን ለመገንባት ዘርፈ ብዙ ጥረቶችን
እያደረገ ይገኛል፡፡ ከዚህም አንዱና ዋነኛው የጉምሩክ አሠራርን ሙሉ በሙሉ የስጋት ሥራ አመራርን መሠረት
ያደረገ ሆኖ የተቀላጠፈ አገልግሎትና ቁጥጥር የተጣጣመ እንዲሆን ማስቻል ነው፡፡ የስጋት ሥራ አመራር
ዓለም አቀፋዊ ይዘት ያለው የአሠራር ሥርዓት ሲሆን ለህጋዊ ነጋዴዎች የተቀላጠፈ አገልግሎት መስጠት፤
ለህጉ ተገዥ ባልሆኑት ላይ ደግሞ ተገቢውን ቁጥጥር ለማድረግ እና ወደ ህግ ተገዥነት ለማምጣት የሚያስችል

3 ምንጮች /Reference |
ዘመናዊ የአሰራር ዘዴ ነው፡፡ መረጃዎችን ከተለያዩ ምንጮች በመሰብሰብና ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ በመተንተን
ፈጣን አገልግሎት አሰጣጥን ከውጤታማ ቁጥጥር ጋር አጣጥሞ ለመተግበር የሚያስችል ስልት ነው፡፡

እየሰፋ ከመጣው የወጪ ፣ የገቢ እና ፣ የመንገደኞች ለተለያዩ ጉዳዮች ከሀገር ወደ ሀገር የሚደረግ እንቅስቃሴ አንጻር
ሁሉንም የጉምሩክ ስራዎች በመቆጣጠር ማከናወን ካለው ውስን ሃብት /የሰው፣የጊዜ፣ የገንዘብ እና ሌሎች/ እና
ውስብስብነት አንፃር የሚታሰብ አይሆንም፡፡ በዓለም ላይ እየጨመረ ከመጣው የጭነት /Cargo/ እንዲሁም የንግድና
የሰዎች እንቅስቃሴ የተነሳ ሁሉንም ሰዎችና ጭነቶች መቆጣጠር ለጉምሩክ ተቋማት የማይቻል እየሆነ መጥቷል፡፡

በየዕለቱ የጉምሩክና የታክስ ባለሙያዎች የትኛው ድርጅት ፣እቃ ወይም ተጓዥ ላይ ቁጥጥር ማድረግ እንዳለባቸው መለየትና
ማወቅ አለባቸው ለዚህም የሰው ፣ የዕቃና የቴክኖሎጂ አቅርቦት ብቻ ሳይሆን መለየት የሚችሉበት ምክንያት ወይም
መስፈርቶች ያስፈልጋቸዋል፡፡ እነዚህም መለያ ምክንያቶች የሥጋት አመላካቾች /Risk Indicators/ እና የኋላ ልምዶች
/Trends/ ናቸው፡፡ የሥጋት አመላካቶችን እና የኋላ ልምዶችን መጠቀም ትክክለኛ ምርጫ እንድናካሂድ ይረዳናል፡፡ ስጋት
ስራ አመራር ስርዓት ውጤታማ የቁጥጥር እና የተቀላጠፈ የመስተንግዶ ስርዓትን፣ የደንበኞች እርካታ እና ታማኝነትን
በማሳደግ ህገ-ወጥ ንግድን በመቆጣጠር ገቢን ለማሳደግ ተመራጭ የማኔጅመንት ጥበብ ነው፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ ባለስልጣኑ ገቢን በብቃት ለመሰብሰብ፣ ኮንትሮባንድን ለመከላከል እና የህብረተሰቡን ደህንነት
ለመጠበቅ በገቢና ወጪ ዕቃዎች ላይ የሚደረገውን ቁጥጥር ስጋትን መሰረት ባደረገ አኳኋን እንዲፈጸም እየሰራ ይገኛል፡፡
በስጋት ሥራ አመራር ያልተደገፈ አገልግሎት አሰጣጥ ንግድን የማሳለጥ ተግባር ከማስተጓጎሉ ባለፈ ቁጥጥር ሊደረግባቸው
የሚገቡ ስጋቶችን ለይቶ ትኩረት ማድረግ ሲገባው በሁሉም ላይ ቁጥጥር በማድረግ አላስፈላጊ የሆነ መስተጓጎል እንዲሁም
የሃብት ብክነት ያስከትላል፡፡

የጉምሩክ ቁጥጥርን የስጋት ሥራ አመራርን መሰረት ባደረገ መልኩ ተግባራዊ ማድረግ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች ሲኖሩት
በዋናነት ንግድና ኢንቨስትመንትን ለመደገፍ፤ህጋዊ ነጋዴዎችን ለማበረታት እና ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴዎችን
ለመቆጣጠርና ወደ ህጋዊ ስርዓት ለማምጣት ከፍተኛ ሚና አለው፡፡

የስጋት ስራ አመራር የሕግ ተገዥነትን ለማምጣት የሚያግዝ መሳሪያ ብቻ ሳይሆን የተቋሙ ዕቅድ እንዳይሳካ የሚያደርጉ
አሉታዊ ተፅዕኖዎችን ለማስተናገድ የሚረዳ የአመራር እና የአስተዳር ዘዴ ነው፡፡

የስጋት ስራ አመራር በዋናነት በአገልግሎት አሰጣጥ እና በቁጥጥር ስርዓት መካከል ሚዛናዊነትን ለማስጠበቅ የሚጠቅም
ከመሆኑ በተጨማሪ ትኩረት በከፍተኛ የስጋት ቦታዎች ላይ እንዲሆን በማድረግ ውስን የሆነውን የተቋሙን ሀብት
ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመጠቀም የሚያስችል የአሰራር ስርዓት ነው፡፡

የኢትዮጵያ ገቢዎች እና ጉምሩክ ባለስልጣንም ይህንን ውጤታማነት ለማምጣት የስጋት ስራ አመራር ፖሊሲ እና ስትራቴጂ
ቀርፆ እንዲተገበር በማድረግ አበረታች ውጤቶች እየታዩ ነው፡፡ በዚህም ያለውን ውስን የሰው ፤ የማቴሪያልና የፋይናንስ

4 ምንጮች /Reference |
ሀብት ከፍተኛ ስጋት ቦታዎች ላይ በማዋል ህጋዊ ግብር ከፋይን በመለየት ቀልጠፋ አገልግሎት በመስጠት ህጋዊ ባልሆኑት
ላይ ደግሞ ውጤታማ ቁጥጥር በማድረግ የደንበኞችን እርካታ በማምጣት ገቢን በብቃት እንዲሰበሰብ እና የግብር ከፋዮች
የህግ ተገዥነት ደረጃ ከፍ እንዲል እየሰራ ይገኛል፡፡

በአጠቃላይ የሥጋት ሥራ አመራር

 የሰው ልጅ የተፈጥሮ ባሀሪ ተደርጎ ይወሰዳል

 የተሻለ ምርጫ በማድረግ የተሻለ ውሳኔ ለመወሰን ያስችለናል

 የስጋት ሥራ አመራር ዋና ትኩረት ሥጋቶች ከመከሰታቸው በፊት አስቀድሞ መከላከል ወይም


ከተከሰቱ በኀላ የሚያስከተሉት ተጽእኖ ዝቅተኛ እንዲሆን ማስቻል ነው

1.2. ዓላማ
 የዚህ ስልጠና ሰነድ ዓላማ የስጋት ስራ አመራር መርህን የተከተለ የአገልግሎት አሰጣጥ እና የቁጥጥር
ስርዓት እንዲኖር የሚያግዝ ግንዘቤ መስጠት እና የባለስልጣኑ ሠራተኞች የሥጋት ሥራ አመራርን
መሠረት ያደረገ ሥራ በየሥራ ክፍላቸው እንዲያከናውኑ የሚያግዝ ግንዛቤ መፍጠር ነው፤

 ስጋት ስራ አመራር እንዴት ለተቋሙ ግብ ስኬት ጠቃሚ እንደሆነ እና ሳይንሱ የተቋሙን ዕሴት
ለማጎልበት እንዴት እንደሚያግዝ ለማስገንዘብ ነው፤

 በታክስ ሕግ ተገዥነት ስጋት ሥራ አመራር የስራ ክፍል የሚመደቡ ባለሙያዎች ሰነዱን በራሳቸው
በማንበብ እውቀታቸውን ለማሳደግ እና ሥራችውን ሲከናውኑ የአሰራር መርህ እንዲሆናቸው
ለማድረግ ነው፤

1.3. ትርጉም
ስጋት ማለት ፡- eÒƒ TKƒ ¾ ተቋሙ ¯LT እ”ÇÃd" ›K<ታ© የሚፈጠር ማንኛውም አይነት ክስተት TKƒ
’¨<:: ከኢትዮጵያ ገቢዎችን ጉምሩክ ባለስልጣን አንፃር ስጋት ማለት ኰንትሮባንድ፣ ንግድ ማጭበርበር፣
ግብርና ታክስ አለመክፈል ወይም ስወራ፣ የስነ ምግባር ችግር ወዘተ ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡

ስጋት ስራ አመራር ማለት ፡- ስጋቶችን በሳይሳዊ ዘዴ የምንለይበት፣ የምንተነትንበት፣ የምናስተናግድበት እና


የምንገመግምበት አሰራር ሲሆን በዚህም እድሎች /opportunities /የሚለዩበት ሊፈጠሩ የሚችሉ ኪሣራዎች
የምንቀንስበት ወይም የምናስወግድበት ማለት ነው፡፡ eÒƒ Y^ ›S^` Ÿ ታ¡e ›”í` c=ታ à ›S^\ ¾}hK ¨<d’@
እ”Ç=cØ G<’@ታ‹” uTS‰†ƒ ¾ ታ¡e cwdu=¨< S/u?ƒ ¯LT¨<” (Óu<”) እ”Ç=S ታ ¾T>Áe‰M ’¨<::

5 ምንጮች /Reference |
ስጋት ስራ አመራር በአለን ውስን ሀብት ውጤታማ ውሳኔ እንድንወስን የሚረዳን የስራ አመራር ጥበብ
(Management Science) ነው፡፡

የታክስ ሕግ ተገዢነት ማለት ፡- ግብር ከፋይ የሚጠበቅበትን የግብርና ቀረጥ ግዴታዎችን በግብር ታክስ እና
በጉምሩክ ህግ መሰረት በወቅቱ አሳውቆ መክፈል ማለት ሲሆን ይህም ሰፋ ባለ ትርጉሙ ሲገለጽ፡

 ለሀገሪቱ ህጎች እና ለማህበረሰቡ አላማዎች ተገዢ መሆን


 ግብር ከፋዩ የሀገሪቱን የታክስ ህጎች በማክበር በሀገሪቱ ኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ፍትሀዊነት
እንዲሰፍን ማድረግ
 የግብር ከፋይ በፈቃደኝነት ትክክለኛውን የግብር መጠን አስታውቆ መክፈል ማለት ሲሆን የዚህም
መገለጫው
 ግብርን ለመክፈል መመዝገብ እና በግብር ስርአቱ መታቀፍ፣
 ትክክለኛውን መረጃ ለግብር አስገቢው መ/ቤት ማሳወቅ፣
 ለግብር አወሳሰን የሚረዱ የሂሳብ ሰነዶችን በትትክክለኛው ስርአት እና በአግባቡ መያዝ፣
 የሚጠበቅበትን ግብር መጠን በፈቃደኝነት በወቅቱ አስታውቆ መክፈል፣
 በመልካም ስነምግባር መስራትን፣
 በህጋዊ ማኣቀፎች መንቀሳቀስን ነው፡፡

የታክስ ህግ ተገዢ አለመሆን፡ አንድ ግብር ከፋይ በግብር ህጉ የሚጠበቅበትን የግብር እና የቀረጥ ግዴታ
አለመወጣት ማለት ሲሆን እነዚህም ግዴታዎች

የታክስሕግ ተገዥነት

የታክስ ሕግ ተገዥነት ማለት የግብርና ቀረጥ ህጎችን ተቀብሎ ግዴታዎችን በፍቃደኝነትና በታማኝነት
መወጣት ማለት ነው፡፡

ስጋት ምዘና/Risk Assessment/

የስጋት ምዘና/Risk Assessment/ ማለት አጠቃላይ ስጋት የሚለይበት፣ የሚተነተንበት፣ የሚገመገምበትና


ስጋቶች በቅደም ተከተል የሚቀመጡበት ሂደት ነው፡፡

የታክስ ሕግ ተገዥነት ስጋት ስራ አመራር

6 ምንጮች /Reference |
የታክስ ሕግ ተገዥነት ስራ አመራርማለት የታክስ ህግስጋቶችን በስጋት ስራ አመራር መርህ መሰረት መለየት፣
መተንተን፣ ቅደም ተከተል ማስቀመጥናማስተናገድ የሚያስችል ሲሆንግብር ከፋዮችን ወደ ህግ ተገዥነት
ለማምጣት የሚያስችል የአሰራር ሂደት ነው፡፡

የጉምሩክ ትራንዚት፡- ማለት ዕቃዎች ወይም መንገደኞች በጉምሩክ ቁጥጥር ስር ሆኖ ከአንድ የጉምሩክ ጣቢያ
ወደ ሌላ የጉምሩክ ጣቢያ በተፈቀደ መስመር የሚተላለፉበት የጉምሩክ ስነ ሥርዓት ነዉ፡፡

ካርጎ ስካኒንግ ማሽን፡- ማለት ማለት ወደ ሀገር የሚገቡ ወይም ከሀገር የሚወጡ ተሽከርካሪዎች የያዟቸው
ጭነቶች ወይም ከአገር የሚወጡ እና ወደ ሀገር የሚገቡ ጓዞች የሚፈተሹበት የዕቃ መፈተሻ መሳሪያ ነዉ፡፡

ቀይ ስጋት ደረጃ፡- ማለት ከፍተኛ የስጋት ደረጃ ማለት ሲሆን ዕቃዎች ወይም መገደኞች ላይ አካላዊ ፍተሻ እና
የሰነድ ምርመራ እንዲደረግ የሚያችል አመላካች የሥጋት ደረጃ ወይም የማለፊያ መስመር (channel) ነው፡፡

ቢጫ ስጋት ደረጃ፡- ማለት መካከለኛ የስጋት ደረጃ ማለት ሲሆን ሰነድ ምርመራ እንዲደረግ የሚያችል
አመላካች የሥጋት ደረጃ ወይም የማለፊያ መስመር (channel) ነው፡፡

አረንጓዴ ስጋት ደረጃ፡- ማለት ዝቅተኛ የስጋት ደረጃ ማለት ሲሆን በመድረሻ ጣቢያ የደረሱ ዕቃዎች ወይም
መንገደኞች የሰነድና የአካላዊ ፍተሻ ሳይደረግባቸው የገቢ ዕቃ ሰነድ እንደቀረበ ወይም መንገደኛው እንደደረሰ
በመልቀቅ በድህረ- ዕቃ አወጣጥ ኦዲት እና በሌሎች ዕቃ ከተለቀቀ በኋላ ቁጥጥር በሚያደርጉ የህግ ማስከበር
የስራ ክፍሎች ቁጥጥር ሊደረግባቸው የሚችሉ መሆኑን የሚገልጽ መስመር ነው፡፡

ሰማያዊ ስጋት ደረጃ፡- ማለት በዝቅተኛ የስጋት ደረጃ የስጋት ደረጃ የሚመደቡ የተመረጡ የኢኮኖሚ
አንቀሳቃሽ ድርጅቶች(AEO) የሚስተናገዱበት የስጋት ደረጃ ሲሆን በመድረሻ ጣቢያ የደረሱ ዕቃዎች የሰነድና
የአካላዊ ፍተሻ ሳይደረግባቸው የገቢ ዕቃ ሰነድ እንደቀረበ ተለቀው በድህረ- ዕቃ አወጣጥ ኦዲት እና በሌሎች
ዕቃ ከተለቀቀ በኋላ ቁጥጥር በሚያደርጉ የህግ ማስከበር የስራ ክፍሎች ቁጥጥር ሊደረግባቸው የሚችሉ
መሆኑን የሚገልጽ መስመር ነው፡፡

ብርቱካናማ የስጋት ደረጃ፡- ማለት ወደ ሀገር ውስጥ ሊገቡ ወይም ሊወጡ የተዘጋጁ ዕቃዎችን የጫኑ
ተሽከርካሪዎች በከፍተኛ የስጋት ደረጃ ላይ መሆናቸውን የሚገልጽ መስመር (channel) ሲሆን በስካኒንግ
ማሽን/አካላዊ ፍተሻ እንዲደረግባቸው የሚገልጽ መስመር ነው፡፡

ነጭ ስጋት ደረጃ፡- ማለት ወደ ሀገር ውስጥ ሊገቡ ወይም ሊወጡ የተዘጋጁ ዕቃዎችን የጫኑ ተሽከርካሪዎች
በዝቅተኛ የስጋት ደረጃ ላይ መሆናቸውን የሚገልጽ መስመር (channel) ሲሆን በስካኒንግ ማሽን/አካላዊ ፍተሻ
ሳይደረግባቸው እንዲለቀቁ የሚገልጽ መስመር ነው፡፡

7 ምንጮች /Reference |
የልዩ መብት ተጠቃሚ፡ ማለት በየጉምሩክ የልዩ መብት ተጠቃሚዎች የአሰራር ስርአት መሰረት በአሰራር ስርአቱ
መሰረት ተመርጠው የተቀላጠፈ መስተንግዶ እንዲያገኙ የሚደረጉ ድርጅቶች ናቸው፡፡

የተመረጡ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ ድርጅቶች፡ ማለት ማለት በተቀቋሙ የተቀመጠውን መስፈረት አሟልተው
ከተቋሙ ጋር የስምምነት ሰነድ ተፈራርመው የተመረጡ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ በመባል መበቱ የተሰጣቸው
ድርጅቶች ናቸው፡፡፡

የስጋት ስራ አመራር ደረጃ፡ማለት በተደረገ የስጋት ትንታኔ መነሻ ወይም በተቀመጠ የስጋት መስፈርት መሰረት
የአንድን ዕቃ ወይም መንገደኛ የመስተንግዶ መስመር የሚገልጽ ነው፡፡

የስጋት ስራ አመራር ማኑዋል፡ይህ የአሰራር ማኑዋል ነው፡፡

1.4. የጉምሩክ ሀላፊነቶች


 ገቢን በብቃት መሰብሰብ

 ህጋዊ የንግድ ሥርአቱን መደገፍ

 የጉምሩክና ሌሎች ህጎችን ማስፈጸም

 የህብረተሰቡን ደህንነት መጠበቅ

 ሀገር በቀል ኢንዱስተሪውን መጠበቅ እና መደገፍ

 ለኢኮኖሚ ትንበያና ፣ ትንታኔ እና እቅድ የሚያገለግሉ የንግድ መረጃዎችን ማደራጀት፣ማሰራጨት እና


መጠበቅ

 ህገ ወጥ ንግድን እና ኮንትሮባንድን መከላከል

1.5. በጉምሩክ ስራ ላይ ያሉ ተጽእኖዎችና ምክንያቶቻቸው


 በተቀላጠፈ መስተንግዶ እና ቁጥጥር አሰጣጥ ላይ የሚፈጠር ተጽእኖ

 እየጨመረ ያለ ወንጀል፣ ሽብርተኝነት፣ እና ህገ ወጥ እንቅስቃሴ

 ለልማት አስፈላጊ የሆነ ገቢን በወቅቱ ሰብስቦ ለመንግስት ገቢ ማድረግ አለመቻል

 የሀብት ውስንነት/ የሰው፣ የገንዘብ፣ የጊዜ እና ሌሎች ቁሳዊ ሀብቶች ውስንነት

8 ምንጮች /Reference |
 ሁሉንም መቆጣጠር አለመቻል

ተጽእኖዎቹ ለምን ?

 የአለም አቀፍ የንግድ እንቅስቃሴ ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣት

 የሰዎች ከሀገር ወደ ሀገር እንቅስቃሴ እየጨመረ መምጠት

1.6. የጉምሩክ ሥጋት ሥራ አመራር ዓላማ


የጉምሩክ ስጋት ስራ አመራር ዓላማ በጉምሩክ አሰራር ላይ ያሉትን ስጋቶች ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ በመለየት፣
በመተንተን፣ ደረጃ በማውጣት፣ በቅደም ተከተል በማስቀመጥና ትኩረትን በከፍተኛ የስጋት ቦታ ላይ እንዲሆን
በማድረግ፣ የተቀላጠፈ አገልግሎት በመስጠት የታክስ ሕግ ተገዥነት ለማምጣት የሚያስችል የአሰራር ስርዓት
መዘርጋት ነው፡፡ በተሻሻለው የኪዮቶ ስምምነት ላይ በተጠቀሰው መሰረት በአለም ላይ እየጨመረ ካለው
የንግድ እና የሰዎች እንቅስቃሴ አንጻር የጉምሩክ አስተዳደር የተቀላጠፈ መስተንግዶ እና ቁጥጥሩን የተጣጣመ
ለማድረግ የስጋት ስራ አመርርን መተግበር ይጠበቅባቸዋል፡፡

የጉምሩክ ሁለት ዋና ዋና አላማዎች :

 ለንግዱ ማህበረሰብ / በተለይም ለህጋዊው / የተቀላጠፈ መስተንግዶን መስጠት እና

 የህግ ተገዥነትን ማረጋገጥ ናቸው ፡፡

እነዚህን አላማዎች ለማሳካት ከተለመደው የቁጥጥር አስተሳሰብ በመውጣት ሥጋትን መሰረት ያደረገ እና
በሥጋት ሥራ አመራር ላይ የተመሰረተ አሰራርን መተገበር ይገባል፡፡

የተቀላጠፈ ሥጋት
ቀልጣፋ የእቃ
መስተንግዶ ሥራ ህግ ማስከበር
ሀገራዊ እና አለም
አመራር
አወጣጥ ሥርአት የመረጃ አቀፋዊ ደህንነት
ዝቅተኛ ወጪ ልውውጥ የህብረተሰብ ጤና
ከፍተኛ ደረጃ የመረጃ እና እና ደህንነት
የአገልግሎት የስጋት ትንታኔ የተሻለ ገቢ
ማስቻያ
አሰጣጥ አሰባሰብ
የሰው ሀብት ሥራ አመራር፣ ዘመናዊ
ዎች ቴክኖሎጂ፣ የሰው ሀብት ልማት እና ህግ

9 ምንጮች /Reference |
1.7. ለሥጋት ሥራ አመራር ትገበራ የሚያስፈልጉ ሁኔታዎች
 የበላይ አመራሩ እና የአጠቃላይ ሰራተኛወ የአመላካከት ለውጥ
 ስጋት ስራ አመራርን ለሁሉም አካላት ማሳወቅ
 በሥጋት ሥራ አመራር ላይ ለሚሰሩ ባለሞያዎች የተለየ ስልጠና መስጠት
 ፖሊሲ እና ስተራቴጂ
 አደረጃጀት
 የህግ ከለላ
 ከተለያዩ የመረጃ ምንጮች ተሰባስበው የተደራጁ መረጃዎች

1.8. የሥጋት ሥራ አመራር መርህ


ለሥጋት ሥራ አመራር ሥኬታማነት ከዚህ በታች የተዘረዘሩት መርሆች ወሳኝ ናቸው፡-

 የበላይ አመራሩ ድጋፍ እና በባለቤትነት ይዞ መምራት፣


 በየደረጃው የሥጋት ሥራ አመራር አሰራርን እና ጠቀሜታ ማሳወቅ፣
 ከሌሎች የተቀም ሥራ ተለይቶ የሚታይ ሳይሆን በእያንዳነዱ እቅዶቻችን ላይ እና ሌሎች ተግባራት
ላይ እቅድ አድርገን መያዝ ፣
 ሥጋቶች ከመከሰታቸው በፊት አስቀድሞ መከላከል ላይ ትኩረት ማድረግ፣
 በአንድ በተወሰነ የስራ ክፍል ብቻ የሚመራ ሳይሆን ሁሉም በባለቤትነት ሊመራው ይገባል፣
 በውሳኔ አሰጣጥ ላይ ግልጽነትን ይጠይቃል፣
 ሥልጠና /አቅም ግንባታ፣
 ከተጽእኖ ነጻ መሆን እና
 ተከታታይ ክትትል እና ግምገማ

1.9. የባለስልጣኑ የስጋት ስራ አመራር ፖሊሲ መርሆዎች


የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን የተቋሙን የሥጋት ሥራ አመራር ፖሊሲና ስትራቴጂ በ 2002
ዓ.ም በስራ ላይ ያዋለ ሲሆን የሚከተሉት መርሆች አሉት

 ለህጋዊ ግብር ከፋይ የተመቻቸና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ግብር ለመክፈል የሚወስድባቸውን
ወጪ እና ጊዜ በመቀነስ የደንበኞችን እርካታን ማሳደግ፤
 ፈጣን አገልግሎት አሰጣጥን ከውጤታማ ቁጥጥር ጋር አጣጥሞ መተግበር ፤
 ፍትሐዊ አገልግሎት መስጠት፤
 የውስጥ እና የውጭ ስጋቶችን መቀነስ፤
10 ምንጮች /Reference |
 የንግድ ማጭበርበርን እንዲቀንስ ማስቻል፤
 ቁጥጥሩን ለህግ ተገዢ ባልሆኑት ላይ በማድረግ ህገወጥነት እንዲቀንስ ማድረግ፤
 ግልጽ፣ ፍትሐዊ እና ተደራሽ አገልግሎት እንዲሰጥ በማድረግ የውጪ ኢንቨስትመንትን ማበረታታት፤
 የግብር ከፋዩን የህግ ተገዢነትን ማሳደግ፤
 ውስን ሀብትን ከፍተኛ ስጋት ቦታዎች ላይ በማዋል የሀብት አጠቃቀምን ውጤታማ ማድረግ ወ.ዘ.ተ.

2.1. የስጋት ስራ አመራር አላማዎች


 የባለስልጣን መ/ቤቱን የውስጥ እና የውጪ ስጋቶችን በመለየት ስጋትን መተንተን እና ማስተናገድ

 በጉምሩክ እና በታክስ ፈጣን አገልግሎት አሰጣጥ እና ቁጥጥሩ የተጣጣመ እንዲሆን ማስቻል

 የግብር ከፋዮች የህግ ተገዥነት እንዲያድግ በማድረግ በፈቃደኝነት የሚሰበሰበውን ገቢ ከፍ እንዲል


ማስቻል

 የስጋት ስራ አመራር ስርአት በሁሉም የባለስልጣን መ/ቤቱ አሰራር ላይ እንዲተገበር ማድረግ ወ.ዘ.ተ.

1.10. የስጋት ስራ አመራር ስርዓት ጠቀሜታዎች


የጉምሩክ ስጋት ስራ አመራር ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች ሲኖሩት በተለይም ከጉምሩክ ስነ-ስርዓት አፈጻፀም ጋር
ተያይዞ የሚከሰቱ ስጋቶችን በመለየት የስጋት ትንታኔ በመስራት እና የስጋት ደረጃ በማውጣት በከፍተኛ
የስጋት ቦታዎች ላይ ትኩረት እንዲደረግ ለማድረግ ከፍተኛ ሚና አለው፡፡ በተለይም ውስን የሆነው ሀብት
በተገቢው ቦታ ላይ እንዲውል በማድረግ የተጣጣመ የቁጥጥርና የተቀላጠፈ መስተንግዶን ለመስጠት
ይጠቅማል፡፡ የሥጋት ሥራ አመራር ለተቋሙ እና ለንግዱ ማህበረሰብ የሚከተሉት ጥቅሞች አሉት፡-

ለንግዱ ማህበረሰብ

 ለህጋዊ ግብር ከፋይ የተመቻቸ ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ግብር ለመክፈል የሚወስድባቸውን
ወጪ እና ጊዜ ለመቀነስ ይረዳል፣
 ህጋዊ ቁጥጥር እና የተቀላጠፈ አገልግሎት አሰጣጥን በማጣጣም የደንበኞችን እርካታን ለማምጣት
ያስችላል፣
 ፈጣን የእቃ አወጣጥ ሥርአት
 የተቀላጠፈ መስተንግዶ
 የተሻለ የህግ ተገዥነት
 አላስፈላጊ መዘግየቶችን በመቀነስ ወጪውን መቀነስ

11 ምንጮች /Reference |
 ከተቀሙ ጋር የተሻለ ግንኙነት እና መተባበር ይፈጥራል
 በአለም አቀፍ እና በሀገር ውስጥ የንግድ እንቅስቃሴ ላይ ተወዳዳሪ መሆን ያስችለዋል
 የግብር ከፋዩን የህግ ተገዢነትን በማስፋት በፈቀደኝነት የሚከፈለውን ቀረጥና ታክስ በማሻሻል ገቢን
ያሳድጋል ፣
ለተቀሙ
 ትክክለኛ መረጣ እንዲያደርግ ያስችለዋል
 ግልጽ የሆነ የውሳኔ አሰጣጠጥ
 ከንግዱ ማህበረሰብ ጋር የተሻለ ግንኙነት እና መተባበር ይፈጥራል
 ሕግ አክባሪነትን በማበረታታት የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት
 ሕገ ወጥነትን በመቆጣጠር ገቢን በብቃት ለመሰብሰብ
 የሀገር ደህንነትን ለመጠበቅ
 ሕጋዊ ንግድ እና ኢንቨስትመንትን ለመደገፍ
 ስጋትን መሰረት በማድረግ ፍትሃዊ የጉምሩክ መስተንግዶ ለመስጠት
 ኮንትሮባንድ፣ ታክስ ስወራ እና ታክስ ማጭበርበርን ለመቀነስ
 የገምሩክ ዕቃ አወጣጥ ጊዜን እና ወጪን በመቀነስ የተገልጋዮችን እርካታ ለማሳደግ
 የሕግ ተገዥነትን ለማሳደግ
 ÁK”” ውስን ¾c¨<' ¾T‚]ÁM' ¾‚¡•KAÍ= እ“ ¾óÓ”e ሀብትን ከፍተኛ ስጋት ቦታዎች ላይ
በማዋል የሀብት አጠቃቀምን ውጤታማ ያደርጋል ፣
 ክልከላና ገደብ የተደረገባቸውን ዕቃዎች ላይ ቁጥጥር እንዲደረግባቸው በማስቻል የማህበረሰቡን
ደህንነት ያስጠብቃል፣
 ሁሉንም ግብር ከፋይ በእኩል እና ግልጽ በሆነ መስፈርት ለመመዘን ይረዳል፤
 ግልጽ፣ ፍትሐዊ እና ተደራሽ አገልገሎት እንዲሰጥ በማድረግ የውጪ የውጭ ቀጥተኛ
ኢንቨስትመንትን ያበረታታል፤
 ታ¡e e¨^“ ንግድ ማጭበርበር Là ¾}cT\ Ów` ŸóÄ‹” እ”É”KÓ }Óv\U እንዲቀንስ Áe‹K“M ፣
 ቁጥጥሩ ፣ ፍተሻው እና ኦዲት ማድረጉን ለህግ ተገዢ ባልሆኑት ላይ በማድረግ ህገ ወጥነት እንዲቀንስ
ያደርጋል ወ.ዘ.ተ.
 ታ T˜ Ów` Ÿóà ¾’u\ ¨Å IÑ-¨Ø’ƒ ¾SH@dž¨<” H>Ń እ”É”S´” Ã[Ç“M::
 ¾Ów` cwdu=¨< vKVÁ ¾ðKѨ<” S`Ù ¾SY^ƒ }Óv` Ãk`“ ueÒƒ u}S[Ö< Là ¾Se^ƒ vIM
ÃÇw^M'
 u}c\ Y^‹ w³ƒ SK"ƒ Ãk`“ u}c\ Y^‹ Ø^ƒ“ ¨<Ö?ƒ SK"ƒ'

12 ምንጮች /Reference |
1.11. የሥጋት ሥራ አመራር ደረጃዎች

ስትራቴጂያዊ
ሥጋት ሥራ
አመራር
ኦፕሬሽናል
ሥጋት ሥራ
አመራር
ታክቲካል ሥጋት ሥራ
አመራር

ስጋት ሥራ አመራር እንደየ ሥጋት ደረጃው፣ እንደሚያስከትለው ተጽእኖ እና ሥጋቱን ለማስወገድ ወይም
ለመቀነስ እንደሚሳተፉት አካላት በሦስት ደረጃዎች ሊከፈል ይችላል፡-

ስትራቴጂያዊ ሥጋት ሥራ አመራር

ሥጋቶቹ ከተቀሙ አላማ እና ግቦች ጋር በቀጥታ የሚያያዙ እና ከረዥም ጊዜ ሰትራቴጂዎች ጋር የሚያያዙ


እና ከከፍተኛ አመራሩ ጀምሮ በየደረጃው ያሉ አካላትን ተሳትፎ የሚጠይቁ የሥጋት ዓይነቶች አይነቶች
ናቸው፡፡ ለምሳሌ በተቋሙ የአምስት አመት እቅድ ላይ ተጽእኖ የሚፈጥሩ ሥጋቶች፡፡

ኦፕሬሽናል ሥጋት ሥጋት ሥራ አመራር

ሥጋቶቹ ከተቀሙ አላማ እና ግቦች ጋር በቀጥታ የሚያያዙ እና ከመካከለኛ ጊዜ ሰትራቴጂዎች ጋር የሚያያዙ


እና የመካከለኛ አመራሩን እና በየደረጃው ያሉ አካላትን ተሳትፎ የሚጠይቁ የሥጋት ዓይነቶች ናቸው፡፡

ታክቲካል ሥጋት ሥጋት ሥራ አመራር

13 ምንጮች /Reference |
ሥጋቶቹ ከእለት ተእለት ተግባሮቻችን ጋር የሚያያዙ እና በስራ ክፍል እና በባለሞያ ደረጃ ሊፈቱ የሚችሉ
የሥጋት ዓይነቶች ናቸው፡፡

የተቀላጠፈ መስተንግዶ እና ቁጥጥር ንጽጽር

ቁጥጥር የተቀላጠፈ መስተንግዶ


ሥጋት ሥራ አመራር
ባልተተገበረበት ሁኔታ
የሀሳብ ግጭት!!!
የተቀላጠፈ መስተንግዶ እና ቁጥጥሩን የተጣጣመ ማድረግ

 የተጣጣመ የተቀላጠፈ መስተንግዶ እና ቁጥጥርን ተግባራዊ ለማድረግ የስጋት ሥራ አመራር


ሥርአትን መተግበር ወሳኝ እና አስፈላጊ ነው፡፡

ከፍተኛ ቁጥጥር ላይ ያተኮረ ሥርአት የተጣጣመ የተቀላጠፈ መስተንግዶ


Red Tape Approach እና ቁጥጥሩን ሥርአት (Balanced
Approach)

ጥ ዝቅተኛ የተቀላጠፈ መስተንግዶ እና ያልተጣጣመ የተቀላጠፈ መስተንግዶ
ጥር ቁጥጥር ሥርአት እና ቁጥጥር ሥርአት
(Crisis Management) (Laissez Faire Approach)

ዝቅተኛ ከፍተኛ
የተቀላጠፈ መስተንግዶ
14 ምንጮች /Reference |
ምእራፍ ሁለት
2.1. የስጋት ስራ አመራር ታሪካዊ ዳራ

ስጋት/Risk የሚለው ቃል Risque ከሚል የፈረንሳይ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም አደጋ/danger ማለት ነው፡፡
ከዚህም አንጻር ስጋት ማለት አደጋ የመከሰት ዕድል ወይም ሁኔታ ተደርጎ ሊቆጠር ይችላል፡፡ ስጋት ስራ አመራር
እንደ ሳይንስ አዲስ ቢሆንም በሰው የሕይወት ዘይቤ ውስጥ ግን ለረዥም ዘመናት እንደነበረ በዘርፉ የተሰማሩ
አካላት ይጠቁማሉ፡፡ በተለይም ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ከመስፋፋቱ በፊት ስጋት በአማልክት ትዕዛዝ ወይም
ፈቃድ አማካኝነት በሰው ልጆች እና በተፈጥሮ ላይ የሚከሰት አደጋ ተደርጎ ይቆጠር ነበረ፡፡ በመሆኑም ሰዎች
እነዚህን አደጋዎች ቀድመው በማወቅ ለመዘጋጀት ሲሉ የባህላዊ ዕምነት አዋቂዎች፣ ልምዶችን እና
ትውፊቶችን ይጠቀሙ ነበር፡፡ በዚህም ምክንያት በተፈጥሮ እና በሰዎች ሕይወት ላይ የሚከሰቱ አደጋዎቸን
ቀድሞ መከላከል ሳይቻል ረዥም ጊዜያት ተቆጥረዋል፡፡ ዘመናዊ የሆነ የስጋት ስራ አመራር ጥበብ የጀመረው
ከአውሮፓዊያኑ የኢንዱስትሪ አቢዮት በኋላ ሲሆን ከቴክኖሎጂ እድገት ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ አደጋዎችን
ለመከላከል ነበር፡፡ በትላልቅ ግድቦች፣ ድልድዮች፣ በአየር፣ በየብስ እና በባህር ትራንስፖርት፣ በነዳጅ
ማስተላለፊያ መስመሮችና ታንከሮች፣ በባይሎጅካልና ኬሚካል ንጥረ ነገሮች አጠቃቀም እና አያያዝ፣
በፋይናስ እና ንግድ ስራ፤ በፕሮጀክቶች አስተዳደር እና ሌሎች አሰራሮች ላይ ስጋትን ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ
የመከሰት እዱሉና ተጽዕኖው በመተንተን የመቀነስ እና የመከላከል ስራ ትኩረት እያገኘ መጣ፡፡

የስጋት ስራ አመራር በተደራጀ እና በተጠናከረ መልኩ በተለይም በፋይናንስ ተቋሟት አሰራር ውስጥ
የተጀመረው ከሁለተኛው የአለም ጦርነት በኋላ ቢሆንም በታክሰ አስተዳደር ውስጥም ከተጀመረ ጥቂት
የማይባሉ ጊዜያትን አስቆጥሯል፡፡ የታክስ ሕግ ተገዥነት ስጋት ስራ አመራር በታክስ አስተዳደር ስጋትን
በመለየት፣ በመተንተን፣ ቅደም ተከተል በማስቀመጥና ትኩረት በከፍተኛ የስጋት ቦታ ላይ እንዲሆን በማድረግ
የታክስ ሕግ ተገዥነት ለማምጣት የሚያስችል የአሰራር ስርዓት ነው፡፡

2.2. ሥጋት ሥራ አመራር ከአለም አቀፍ አሰራር አንጻር


የአለም የጉምሩኮች ህብረት / WCO የተሻሻለው የኪዮቶ ስምምነት ወሳኝ የጉምሩክ መርሆች ብሎ
ካስቀመጣቸውና ሀገራት እንዲተገብሯቸው ከሚመክራቸው እንዲሁም ድጋፍ ከሚያደርግባቸው ጉዳዮች
ውስጥ አንዱ ሥጋት ሥራ አመራር ሲሆን የአለም የንግድ ድርጅትም በ WTO Agreement on Trade
Facilitation ሰነዱ በአንቀጽ 7.4 ሥጋት ሥራ አመራርን የጉምሩክ አሰራር ወሳኝ መርህ መሆኑን ያስቀምጠል፡፡

15 ምንጮች /Reference |
2.3. የጉምሩክ ስጋት ስራ አመራር በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን

የጉምሩክ ስጋት ስራ አመራር በኢትዮጵያ የተጀመረው በ 1996 ዓ.ም ሲሆን አሰራሩም በደንብ ያልተደራጀ፣
በሲስተም ያልታገዘና የማንዋል አሠራርን ብቻ የተከተለ እንዲሁም በተወሰኑ የጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤቶች ላይ
የሚተገበር ነበር፡፡ በ 2 ዐዐዐ ዓ.ም.ተቋሙ የ BPR ጥናት በማጠናቀቅ ከፍተኛ ለውጥ ያካሄደ ሲሆን ከለውጡ
በኋላ በስጋት ሥራ አመራር የአሰራር ስርዓት ላይ መሻሻል ታይቷል፡፡ ይህም የስጋት ደረጃዎችን ለመጣል
የሚያስችሉ መረጃዎች ከቅ/ጽ/ቤቶች እየተሰበሰቡ እና በማዕከል የስጋት ትንታኔና የስጋት ፕሮፋይል እየተዘጋጀ
በአሰሰኩዳ ሴልክቲቪቲ ማትሪክስ አማካኝነት ስጋት በሲስተም እንዲጣል ማድረግ ተችሏል፡፡ የስጋት
መረጃዎችን በተመለከተ በተበጣጠሰ እና ኋላቀር በሆነ መንገድ ይያዙ የነበረ ሲሆን ለውጡን ተከትሎ የስጋት
መረጃዎች በራስ አቅም እና ጥረት በሲስተም የሚያዙበት አሰራር ተዘርግቶ ለስጋት ስራ አመራር ጠቃሚ የሆኑ
መረጃዎች በ Trader Payers Profile Data Base /TRDP/ የሚያዙበት አሰራር ተፈጥራል፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን
በቅርብ ጊዜያት በገቢ ዕቃዎች መስተንግዶ ላይ ብቻ ሲጣል የነበረው የስጋት ስራ አመራር መሰረቱን በማስፋት
በመንገደኞችና በመንደኞች ጓዝ የጉምሩክ ስነ-ስርዓት አፈጻጸም፣ በትራንዚት ዕቃዎች ስነ-ስርዓት አፈጻጸም
እና በወጪ ዕቃዎች ስነ-ስርዓት አፈጻጸም ላይ መተግበር ተችላል፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ ለውጥች ቢኖሩም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ከመጣው የገቢና ወጪ ንግድ እንቅስቃሴ
አንጻር ለውጡን በተጠናከረ መልኩ ማስቀጠል ያስፈልጋል፡፡ በተለይም በቁጥጥር ላይ ያተኮረ የጉምሩክ ስነ-
ስርዓት አፈጻጸም በተመረጠ መልኩ ስጋት ስራ አመራር መሰረት ባደረገ ሁኔታ ሊከናወን ይገባል፡፡ በዚህም
ምክንያት የኢትዬጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሰልጣን ለተቀላጠፈ የንግድ እቅስቃሴ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር
እንዲሁም ለተገልጋይ ሕብረተሰብ ፍትሐዊ፣ ፈጣን፣ ተገማች እና አመኔታን ያተረፈ የጉምሩክ አገልግሎት
በመስጠትና የጉምሩክ ቁጥጥር በማካሄድ ረገድ የግልጽነትና ተጠያቂነት አሰራርን ለማስፈን በአዲሱ የጉምሩክ
አዋጅ እንቀጽ 6 ከንዑስ (1) እስከ (3) በጉምሩክ አሰራር የስጋት ስራ አመራር መርህን ተግብራል፡፡

የስጋት ስራ አመራር

1/ በባለስልጣኑ የሚሰጥ የጉምሩክ አገልግሎት እና የሚከናወን የቁጥጥር ስርዓት በመረጃ


በተደገፈ መመዘኛ የገቢ፣ የወጪ እና የተላላፊ እቃዎችን የስጋት ደረጃ በመለየት የአገልግሎት
አሰጣጥን እና የቁጥጥር ስርዓቱን ሚዛናዊነት ጠብቆ የሚከናወን ይሆናል::

2/ የዕቃ አወጣጥን፣ ቁጥጥርን፣ የሕግ ተገዥነትን እንዲሁም አገልግሎት አሰጣጥን አስመልክቶ


በባለስልጣኑ የሚከናወኑ ተግባራት እና ባለስልጣኑ የሚወስናቸው ውሳኔዎች የስጋት ስራ
አመራርን መሰረት ያደረጉ ይሆናሉ::

16 ምንጮች /Reference |
3/ ባለስልጣኑ የስጋት ስራ አመራርን መሰረት በማድረግ በተሰጠ አገልግሎት ላይ የታዩ የሕግ
ጥሰቶችን በመለየት ተገቢውን እርምጃ ለመውሰድ ኦዲትን እና ሌሎች የቁጥጥር ስልቶችን
መሠረት ያደረገ ቁጥጥር ተግባራዊ እንዲደረግ ሊወስን ይችላል::

ምእራፍ ሶሥት
3.1. የስጋት ስራ አመራር ሂደት ደረጃዎች /Risk Management Process/
የስጋት ስራ አመራር አላማ የታክስ ስጋቶችን ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ በመለየበት፣ በመተንተን፣ ደረጃ በማውጣት፣
ማስተናገድ ነው፡፡ በመሆኑም የታክስ ሕግ ተገዥነት ስጋት ስራ አመራር የስጋት ስራ አመራር ሂደትን /Risk
Management Process/ተከትሎ የሚከናወን ሲሆን በዚህም ስጋቶችን ለመቀነስ የተወሰዱ እርምጃዎች እና ስልቶች
እየተገመገሙ የተሻለ የሕግ ተገዥነት እንዲፈጠር የሚደረግበት ሂደት ነው፡፡ በየአለም ጉምሩኮች ሕብረት የተዘጋጀው
የስጋት ስራ አመራር መርህ (Guide) የተለያዩ የስጋት ስራ አመራር ደረጃዎች እንዳለው ያስቀምጣል፡፡ እነዚህም የስጋት
ሰራ አመራር ሂደት ደረጃዎች ተመጋጋቢ ሲሆኑ ውጤት ከማምጣታቸው እና ከሕግ ተገዥነት ደረጃ አንጻር ክትትልና
ግምገማ ይደረግባቸዋል፡፡

ሰንጠረዥ 1.የሕግ ተገዥነት ስጋት ስራ አመራር ሂደት ደረጃዎች

17 ምንጮች /Reference |
የስጋት ማዕቀፍ
Communicate and Consult /Establish context

Monitor and Review


ስጋትን መለየት /Identify

ክትትልና ግምገማ
ግንኙነትና ም ክክር

Risks
ስጋትን መተንተን
/analyzes risk
ስጋንትን መመዘን እና
ደረጃ መስጠት /assess &
prioritize risks context
ስጋትን ማስተናገድ/
Addreess risk

የስጋት ስራ አመራር በዋናነት ሰባት ደረጃዎች ያሉት ሲሆን እነሱም፡-

1. ማዕቀፍ ማስቀመጥ /Establish the Context/


2. ስጋት መለየት/Identifying Risks/
3. ስጋትን መተንተን /Analyzes Risk
4. ስጋት መመዘን እና ደረጃ መስጠት /Assess & Prioritize Risks
5. ስጋትን ማስተናገድ/Addreess Risk
6. ክትትልና ግምገማ /Monitor and Review/
7. ግንኙነት እና ምክክር/Communicate and Consult/

I. ማዕቀፍ ማስቀመጥ /Establish the Context/


የስጋት ማዕቀፍ ማስቀመጥ ማለት ተቋሙ ስጋትን ሲያስተዳድር ከግምት ውስጥ ሊያስገባቸው የሚገቡ አጠቃላይ ውጫዊና
ውስጣዊ ሁኔታዎች ናቸው፡፡እነዚህም አጠቃላይ የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ሁኔታዎችን ዳሰሳ ሲሆን
በተጨናሪም የውስጥ ተቋማዊ አደረጃጀት እና ብቃት፣ ቴክኖሎጂ በታክስ አሰባሰብ ስርአት የሚኖረውን
አወንታዊ እና አሉታዊ ተጽእኖ የሚተነትንበት ሂደት ነው፡፡ በተጨማሪም፡-

18 ምንጮች /Reference |
 የስጋት ቦታዎችን መለየት
 ባለድርሻ አካላትን መለየት
 የስጋት መስፈርቶችን ማውጣት / የመለየት
 ተቋሙ ለሥጋት ያለው የመቀበል ዝንባሌ/ Risk Appetiet/ የማስቀመጥ ሥራዎች ይከናወናሉ፡፡
ማእቀፍ ስናስቀምጥ የሚከተሉትን ጉዳዮች ታሳቢ ሊደረጉ ይገባል

i. የህግ ማዕቀፍ

የታክስ ስጋትን ስጋት ስራ አመራር የሚያከናወንበትን የሕግ አግባብ፣ የስጋት መምረጫ መስፈርቶች እና
የስጋት መመዘኛ ዘዴዎችን የሚቀመጥበት ሂደት ነው፡፡

ii. የኢኮኖሚ ማዕቀፍ

የኢኮኖሚ ማዕቀፍ የሚቀመጠው ኢኮኖሚው አጠቃላይ ካመነጨው ምርት ምን ያህሉ ገቢ መሰብሰብ እንደሚችል
ለማወቅ እና ሊሰበሰብ ከሚችለው ገቢ አንጻር ከግብር ከፋዩ ምን ያህሉ እንደተሰበሰበ ለማወቅ ነው፡፡ ይህ
የሚከናወነው የስታትስቲክስ ቀመር በመጠቀም፣ በተለያዩ ጥናቶች፣ መረጃዎች ትንተና መሠረት ቢሆንም
ለስጋት ግብዓት እንዲሆን ግምታዊ መጠኖችን በመውሰድ መሥራት፣ እንደ አስፈላጊነቱ የታክስ ልዩነት(Tax-
Gap) በማስላት ነው፡፡ አጠቃላይ የግብር ዕምቅ አቅም፣ መጠን እና የተሰበሰበ የታክስ መጠን ተመጣጣኝ መሆን
አለመሆን መገምገምን ያካትታል፡፡

iii. የማሕበራዊ ማዕቀፍ

የማሕበራዊ ማዕቀፍ አጠቃላይ የሕብረተሰቡ የትምህርት፣ የጤና፣ ባህልና አኗኗር የሚጠናበት ሁኔታ ሲሆን
የማህበራዊ እድገት ደረጃ በተለይም ከሕዝብ ቁጥር፣ ወደ ስራ ለመሰማራት የደረሰ ምን ያህል ሕብረተሰብ
እንደሚገኝ እና ከዚህ ውስጥ ምን ያህሉ በግብር ህጉ መሰረት ግብሩን በወቅቱ እና የሚጠበቀብትን ያህል
እየከፈለ መሆኑ የሚጠናበት እንዲሁም ሕብረተሰቡ ለግብር ያለው ባህል፣ ግንዛቤ፣ እና አመለካከት
የሚዳሰስበት ሂደት ነው፡፡

iv. የፖለቲካ ማዕቀፍ

የፖለቲካ ማዕቀፍ አጠቃላይ ሀገሪቱ የምትከተለው ፖሊስና ስትራቴጂ፣ የተለያዩ የታክስና ግብር ሕጎች
የሚዳሰሰቡት ሂደት ነው፡፡

19 ምንጮች /Reference |
II. ስጋት መለየት /Identifying Risks/

ስጋት የሚለየው ምን፣ ለምን፣ የት፣ መቼ እና እንዴት እንደ ተከሰተ በማጣራት ሲሆን ለቀጣይ የስጋት ትንታኔ
መሰረት ነው፡፡ ስጋት በሚለይበት ወቅት ቀድመው ሲወሰዱ የነበሩ ዕርምጃዎች፣ ተገልጋዮች፣ ባለድርሻ አካላት
እንዲሁም ጠንካራና ደካማ ጎኖች መለየት አለባቸው፡፡

ሥጋትን ስንለይ የሚከተሉትን ጥያቄዎች ልንጠይቅ ይገባል፡-

 ሥጋቶቻችን ምንድናቸው ?

 የት አካባቢ ይከሰታሉ?
 መቼ ሊከሰት ይችላሉ?
 ለምን ሊከሰቱ ይችላሉ?
 እንዴት ሊከሰቱ ይችላሉ?
 በማን ሊከሰቱ ይችላሉ?
የሥጋት ምንጮች ውስጣዊ እና ውጫዊ ሊሆኑ ይችላሉ

ውስጣዊ

 ኦፕሬሽናል ሥራዎች ፣ ህጎች፣ ደንቦች፣ መመሪያዎች የአሰራር ስርአቶች /Management and


operational activities e.g. policies, procedures etc/
 የስራ ቦታ ደህንነት፣ ጤና /Occupational health and safety e.g. working environment/
 የሰራተኛ ጉዳዮች / የሰራተኛ ብቃት፣ ክህሎት፣ ልምድ፣ጥቅማጥቅም፣ሥልጠና/
ውጫዊ
 ፖለቲካዊ - የመንግስት ፖሊሲ፣
 ቴክኖሎጂ - የቴክኖሎጂ ትግበራ፣አቅም፣ ወ.ዘ.ተ.
 የኢኮኖሚ ሁኔታ- እድገት፣የዋጋ ግሽበት፤የውጭ ምንዛሪ፣ ወ.ዘ.ተ.
 የሀይል፣ የኔትወርክ ወቆራረጥ፣ ወ.ዘ.ተ.
 ወ.ዘ.ተ.
ሥጋትን ለመለየት የሚከተሉትን ዘዴዎች መጠቀም እንችላለን ;
 ሀሳቦችን እንደወረደ በማቅረብ/ Brainstorming
 በቃለመጠይቅ፡- በተደራጀና በባለሞያ በሚደረግ ቃለመጠይቅ በስራው ላይ ላሉ ባመለሞያዎች
በማድረግ፣
 ሰነዶችን በመመርመር

20 ምንጮች /Reference |
 በኢንተለጀንስ ትንታኔ፡- ከተለያዩ ምንጮች የተሰባሰቡ መረጃዎች ላይ ትንታኔ በማድረግና ለቀጣይ
ሥራ ዝግጁ በማድረግ፣
 የፍተሻ ውጤቶችን ሪፖርት በመጠቀም
 የኦዲት ግኝቶችን በመጠቀም

ስጋትን ለመለየት የምንጠቀምባቸው የመረጃ ምንጮች

 አካባቢያዊ ቅኝት ፡ በቅ/ጽ/ቤቶች የሚታዩ ስጋቶችን በየወቅቱ በመገምገም፣ የተለያዩ ሚዲያዎችን


በመቀም፣ የተለያዩ የጥናት ውጤቶችን በመጠቀም እና ከተለያዩ የህግ ማስከበር አካላት መረጃዎችን
በመሰብሰብ ስጋቶችን መለየት ይቻላል
 ህብረተሰቡን ያሳተፈ መረጃን በመጠቀም፡ የንግድ እና የተጠቃሚ ማህበራትን፣ የግብር አማካሪዎችን
እና ሁሉንም ህብረተሰብ በማሳተፍ መረጃዎችን በመሰብሰብ እና በመተንተን ስጋትን መለየት ይቻላል
 አዳዲስ አዋጆች ሲወጡ፡ አዳዲስ የግብር አዋጆች መውጣት አዳዲስ ስጋቶች እንዲፈጠሩ እና የነበሩ
ስጋቶችም እንዲጠፉ ወይም እንዲቀንሱ ያደርጋል ስለዚህ በአዋጆች እና ደንቦች እና መመሪያዎች ላይ
ያሉ ክፍተቶችን እና ስጋቶችን መለየት ይቻላል
 በመረጃ ቴክኖሎጂ መረጃዎችን በመሰብሰብ እና በመተንተን፡ የተቋሙን የመረጃ ቋቶች ማለትም
ከሲግታስ፣ ከአሲኩዳ ++፣ ከትሬደር ሪስክ ዳታ ፕሮፋይል ዳታ ቤዝ፣ ከዋጋ ዳታቤዝ፣ ወ.ዘ.ተ.
መረጃዎችን በመሰብሰብ
 በድንገተኛ ኦዲት፡ በተመረጡ ግብር ከፋዮች ላይ ድንገተኛ ኦዲት እንዲደረግ በማድረግ የስጋት
ቦታዎችን መለየት ይቻላል
 ከጉምሩክ ባለሞያዎች ፡ ባለሞያው ከግብር ከፋዩ ጋር በየወቅቱ የሚገናኝ በመሆኑ አዳዲስ ስጋቶች
የተቀየሩ ስጋቶችን በመለየት የመረጃ ምንጭ ይሆናል፣
 ከኢንተለጀንስ በሚገኙ መረጃዎች

III. ስጋትን መተንተን /Analyzes Risk


ትንተና የሚከናወነው በስጋት ስራ አመራር ፖሊሲና ስትራቴጂ ላይ በተቀመጠው ቀመር መሰረት
ወይም በየወቅቱ የሥጋት ሥራ አመራር ኮሚቴ በሚያጸድቃቸውና ሥራ ላይ በሚውሉ ቀመሮች ስጋት
የመከሰት ዕድልና /Likelihood/ ስጋቱ የሚያስከትለው ተጽኖ /Consequence/ በማስላት ይሆናል፡፡

ሥጋት የመከሰት እድል መግለጫ

የሥጋት የመከሰት እድል ከዚህ በታች ከተመለከቱት አንዱን የመከሰት እድል ሊይዝ ይችላል፤

21 ምንጮች /Reference |
ሥጋት የመከሰት እድል መግለጫ አመላካቾች

የመከሰት እድሉ ከፍተኛ የሆነ/ በአብዛኛው ሁኔታ ሲከሰት የነበረ እና ወደ ብዙ ጊዜ የተከሰተ/ ለምሳሌ በአመት
በእርግጠኝነት የሚከሰት ፊትም የሚከሰት ከሦስት ጊዜ በላይ

የመከሰት እድሉ መካከለኛ አልፎ አልፎ የሚከሰት አልፎ አልፎ የተከሰተ/ ለምሳሌ በ
የሆነ/ ሊከሰት የሚችል ስድስት ወር አንድ ጊዜ

የመከሰት እድሉ ዝቅተኛ የሆነ/ በተለየ ሁኔታ የሚከሰት በረዥም ጊዜ ቆይታ የተከሰተ /
ላይከሰት የሚችል ለምሳሌ በ አመት አንድ ጊዜ

ስጋት የመከሰት ዕድል (likelihood) ሥሌት

ስጋት የመከሰት ዕድል (likelihood) ማለት ቀደም ካሉ መረጃዎች በመነሳት ወደፊት ስጋት የመከሰት
እድሉን የምንለካበት ነው፡፡

ስጋት የመከሰት ዕድል (likelihood) የሚሰላው

ስጋት የመከሰት ዕድል (likelihood) = (ልዩነት የተገኘባቸው ሰነዶች ቁጥር/አጠቃላይ የማስመጣት


ድግግሞሽ)*100

Likelihood = (No. of Offence/No. of Shipment)*100

ማስታወሻ፡ (ቁጥሩ በተወሰነ ጊዜ ሊወሰን ይችላል፣ ለምሳሌ 3 ዓመት)

በስጋት ሥራ አመራር ፖሊሲ መሰረት ስጋት የመከሰት ዕድል/Likelihood/ የመከሰት እድሉ ከፍተኛ ወይም
የመከሰት እድሉ መካከለኛ ወይም የመከሰት እድሉ ዝቅተኛ መሆኑን ለመወሰን ከዚህ በታች የተመለከቱት
ታሳቢ ይደረጋሉ፡-

የመከሰት ዕድል Likelihood% የስጋት ደረጃ/ Risk level

 ≤10%  ዝቅተኛ/ Low

22 ምንጮች /Reference |
 10< x≤ 20%  መካከለኛ/ Medium

 >20%  ከፍተኛ/ High

ሥጋቱ የሚያስከትለው ተጽእኖ መግለጫ

ሥጋቱ ከተከሰተ የሚያሰከትለው ተጽእኖ ከዚህ በታች ከተመለከቱት አንዱን ሊይዝ ይችላል፤

ሥጋቱ የሚያስከትለው መግለጫ አመላካቾች


ተጽእኖ

ከፍተኛ በተቀሙ አላማዎች ላይ ተጽእኖ የሚፈጠር የበላይ አመራሩን ትኩረት እና ተሳትፎ


የሚጠይቁ ሥጋቶች

መካከለኛ ጣጠም ከፍተኛ ያልሆነ ነገር ግን በገቢ ላይ የከፍተኛ እና የመካከለኛ አመራሩን


ተጽእኖ የሚፈጠር

ዝቅተኛ ዝቅተኛ ተጽእኖ የሚፈጠር ባለ አቅም እና ሀብት ሊቀረፍ የሚችል

ሥጋቱ የሚያስከትለው ተጽእኖ (Consequence) ሥሌት

ሥጋቱ የሚያስከትለው ተጽእኖ (Consequence) ማለት ሥጋቱ ከተከሰተ ሊያስከትል የሚችለው


ኢኮኖሚያዊ ተጽእኖ የምንለካበት ነው፡፡

ሥጋቱ የሚያስከትለው ተጽእኖ (Consequence) የሚሰላው

ሥጋቱ የሚያስከትለው ተጽእኖ (Consequence) = (በልዩነት የተሰበሰበ ቀረጥ እና ታከስ / አጠቃላይ


የተከፈለ ቀረጥ እና ታከስ)*100

Consequence = (Additional payment / total tax Paid)*100

23 ምንጮች /Reference |
ማስታወሻ፡ (የገንዘብ መጠኑ በተወሰነ ጊዜ ሊወሰን ይችላል፣ ለምሳሌ 3 ዓመት)

በተመሳሳይ በስጋት ሥራ አመራር ፖሊሲ መሰረት ሥጋቱ ከተከሰተ የሚያሰከትለው ተጽእኖ ከፍተኛ ወይም
መካከለኛ ወይም ዝቅተኛ መሆኑን ለማስላት እና ለመወሰን ከዚህ በታች የተመለከቱት ታሳቢ ይደረጋሉ፡-

ተጽዕኖ/Consequence የስጋት ደረጃ/ Risk level

≤5% ዝቅተኛ/ Low

5>x≤7.5% መካከለኛ/ Medium

>7.5% ከፍተኛ/ High

በመጨረሻም ሥጋት የመከሰት እድል (Likelihood) እና ሥጋቱ የሚያስከትለው የኢኮኖሚ እና ማህበራዊ


ተጽዕኖ (Consequence) ጥምርታ (Matrix) በመስራት በሚከተለው ሰንጠረዥ በተቀመጠው መልኩ
የመጨረሻው የሥጋት ደረጃ ይወሰናል፡፡

የሥጋት ደረጃ 3 በ 3 ጥመርታ

የሥጋት ደረጃዎች
ሥጋቱ የሚያስከትለው ተጽእኖ

ከፍተኛ መካከለኛ ከፍተኛ ከፍተኛ


መካከለኛ ዝቅተኛ መካከለኛ ከፍተኛ
ዝቅተኛ ዝቅተኛ ዝቅተኛ መካከለኛ
ዝቅተኛ መካከለኛ ከፍተኛ
ሥጋት የመከሰት እድል

ከላይ የተገከጹትን ሁኔታዎች በምሳሌ ለማየት

ለምሳሌ፡- የአንድን አስመጭ

 አጠቃላይ የማስመጣት ድግግሞሽ በሰነድ ቁጥር=20 (ቁጥሩ በተወሰነ ጊዜ ሊወሰን ይችላል፣


ለምሳሌ 3 ዓመት)

24 ምንጮች /Reference |
 ልዩነት የተገኘባቸው ሰነዶች ቁጥር= 3
 አጠቃላይ የተከፈለ ቀረጥ እና ታከስ= 2,000,000
 በልዩነት የተሰበሰበ ቀረጥ እና ታከስ= 450,000 ቢሆን

ሥጋት የመከሰት እድል= ልዩነት የተገኘባቸው ሰነዶች ቁጥር X*100

አጠቃላይ የማስመጣት ድግግሞሽ በሰነድ ቁጥር

= 3/20*100=15%= መካከለኛ

ሥጋቱ የሚያስከትለው ተጽዕኖ= አጠቃላይ የተከፈለ ቀረጥ እና ታከስ*100

በልዩነት የተሰበሰበ ቀረጥ እና ታከስ

= 450,000 *100

2,000,000

=22.5%= ከፍተኛ

የመጨረሻው የአስመጭው የስጋት ደረጃ በጥምርታው መሰረት ከፍተኛ ይሆናል ማለት ነው፡፡

IV. ስጋት መመዘን እና ደረጃ መስጠት /Assess & Prioritize Risks


ስጋት የሚመዘነው እና ደረጃ የሚወጣለት በተቀመጡ መስፈርቶች መሰረት ነው፡፡ የስጋት ደረጃ የሚወጣው
ቅድሚያ ተሰጥቶ መስተናገድ ያለበትን ስጋት ለመለየት ሲሆን የተተነተኑ ስጋቶችን በቅደም ተከተል
ማስቀመጥ ያስፈልጋል፡፡ የስጋት ደረጃዎች በተቀመጡ መመዘኛ መስፈርቶች መሰረት ከፍተኛ፣ መካከለኝ እና
ዝቅተኛ እየተባሉ ደረጃ ሊወጣላቸው ይችላል፡፡ የሥጋት ደረጃዎች ሲወጡ የሚከተሉት ጉዳዮች ታሳቢ
ሊደረጉ ይገባል፡-

 የስጋቱ ደረጃ ምን ያህል ነው?

 ቅድሚያ የሚሰጠው ሥጋት ነው?

 ሥጋቱን ለማስተዳደር/ ለማስተናገድ ምን ያህል አቅምና ሀብት አለን?

 የመስተንግዶው ውጤት ምን ሊሆን ይችላል?

25 ምንጮች /Reference |
 ጥቅምና ጉዳትንስ?

ከዚህ ጋር በተያያዘ ሥጋቶችን በየደረጃቸው የምናስቀምጥበት እና የምንከታተልበት መሳሪያችን የስጋት


መዝገብ /risk register/ ይባላል

የሥጋት መዝገብ /a risk register

አላማ ሥጋቶች ሥጋት ሥጋቱ የሥጋት ለሥጋቱ የሥጋቱ


የመከሰት የሚያስከትለው ደረጃ የሚሰጥ ባለቤት
እድል ተጽእኖ ቅድሚያ
ደረጃ

የተቀላጠፈ የተንዛዛ አልፎ ከፍተኛ መካከለኛ 1- ከፍተኛ የጉምሩክ


መስተንግዶ የአሰራር አልፎ ቅድሚያ ስነስርአት
ሥርአት የሚሰጠው የስራ ሂደት

V. ስጋትን ማስተናገድ/Addreess Risk


ስጋቶች ቀደም ተከተል እና ደረጃ ከወጣላቸው በኋላ በየደረጃቸው የመስተንግዶ ስልት እየተዘጋጀላቸው
እንዲሰስተናገዱ ይደረጋል፡፡ እነዚህም የሚከተሉት ናቸው፡-

ሥጋትን ለማስናገድ የሚከተሉትን መንገዶች ልንከተል እንችላለን;-

 ሥጋትን መቀበል

 ስጋትን መቀነስ

 ሥጋትን ማስተላለፍ

 ሥጋትን ማስተዳደር/ ማስተናገድ

ስጋትን መቀበል/Accepting the Risk/

26 ምንጮች /Reference |
ስጋትን መቀበል ስጋትን ለማስተንገድ ከምንጠቀምበት ስልቶች መካከል አንዱ ሲሆን ስጋትን በመቀበል
የምናስተንግደው በተወሰነ የጊዜ ገደብ ውስጥ መፈታት የማይችሉ ስጋቶችን ነው፡፡ ይህም በተወሰነ የጊዜ
ገደብ ውስጥ መፍታት ባለመቻላችን ከተቀበልናቸው ስጋቶች ይልቅ ትኩረታችንን መፍታት በምንችለው እና
በሚገባን ስጋቶች ላይ እንድናደርግ ይረዳናል፡፡ ስጋቶችን ከታች በቀረቡ ዘዴዎች መሰረት ልንቀበላቸው
እንችላለን፡፡

1. ቅድመ ሁኔታዎችን መሰረት በማድረግ


መሟላት የሚገባቸው ቅድመ ሆኔታዎች መሰረት በማድረግ ስጋት መቀበል ይቻላል፡፡ ለምሳሌ
የዋስትና ቦንድ ከቀረብ
2. ጊዜን መሰረት በማድረግ
ስጋቶችን ምክንያታዊ በሆነ መልኩ ጊዜን መሰረት በማድረግ መቀበል እንችላለን፡፡ ነገር ግን ለዘላቂ ጊዜ
እና ሁሉንም ስጋቶች መቀበል ስህተት ነው፡፡
 የስጋት ደረጃው ዝቅተኛ ነው ተብሎ ሲታሰብ ወይም ሥጋቱን ለማስተናገድ በቂ ሀብት ሳይኖር
ሲቀር፡፡ እዚህ ላይ ታሳቢ መደረግ ያለበት የሥጋት ደረጃው ዝቅተኛ ነው ማለት ሥጋቱን መቆጣጠር
አያስፈልግም ወይም አይቻልም ማለት አይደለም

ስጋትን መቀነስ /Reducing the risk/

ምንም እንኳን የተለያዩ የስጋት መስተንግዶ ስልቶችን ብንጠቀም ስጋትን ሙሉ በሙሉ ማስወገድ ላይቻል
ይችላል፡፡ የሚቻለው ስጋት የመከሰት ዕድል እና ስጋቱ የሚስከትለውን ተጽዕኖ መቀነስ ነው፡፡ ስጋትን
የምንቀንሰው ስጋት የመከሰት ዕድል እና ስጋቱ የሚያሳድረውን ተጽዕኖ ዝቅተኛ እንዲሆን በማድረግ ነው፡፡

ስጋት የመከሰት ዕድሉን መቀነስ የሚቻለው

 በማስተማርና በመመካከር
 በመከታተል
 ቅድመ መከላከያ ዘዴዎችን በመጠቀም

ስጋቱ የሚያስከትለው ተጽዕኖ መቀነስ የሚቻለው፡-

1. ቁጥጥር በማድረግ ለምሳሌ ኦዲተ፣ ፍተሻና የመሳሰሉት


2. ተጠባባቂ ዕቅድ በማውጣት

ስጋትን ማስተላለፍ/Transferring the Risk

27 ምንጮች /Reference |
ሥጋቶቹን ከእኛ በተሻለ ሊያስተዳድሩ ለሚችሉ አካላት ማስተላለፍ ተመራጭ በሚሆንበት ወቅት ለምሳሌ
ስጋትን ለሚመለከተው ሶስተኛ ወገን በማስተላለፍ ማስተናገድ ይቻላል፡፡ ለምሳሌ ለተጓዳኝ ተቆጣጣሪ
መስሪያ ቤቶች ስጋቱን በማስተላለፍ በነሱ በኩል ቁጥጥር መደረጉን እያረጋገጡ ማስተናገድ ይቻላል፡፡

ሥጋትን ማስተናገድ / ማስተዳደር

አስፈላጊውን ቁጥጥር በማድረግ ሥጋቱ እንዳደደከሰት ወይም እንዲቀንስ እና ሥጋቱ የሚያስከትለውን


ተጽእኖ መቀነስ ማድረግ፡፡ ለዚህ ከላይ የተገለጹትን መስፈርቶች በመጠቀምና የሥጋት ትንታኔ በማድረግ
የሚከናወን ይሆናል

VI. ክትትልና ግምገማ /Monitor and Review/


ክትትልና ግምገማ የሚያስፈልገው የእያንዳዱ የስጋት ስራ አመራር ሂደት /Risk Management Process/ ደረጃዎች
ውጤታማነት ለመመዘን ሲሆን በዚህም ትክክለኛ እና ውጤታማ የስጋት ምዘና እና የስጋት መስተንግዶ መደረጉን
ለመለካት ነው፡፡ የስጋት ስራ አመራር ሂደቶች ውጤት ከገቢው ዘርፍ አንጻር ክትትልና ግምገማ የሚደረግባቸው የታክስ
ስጋቶችን ለመቀነስ የተወሰዱ እርምጃዎች ምን ያህል ውጤታማ እንደሆኑ እና ምን ያህል የሕግ ተገዝነትን እናዳመጡ
ለማወቅ ነው፡፡ የታክሰ ህግ ተገዥነት ስጋት ስራ አመራር ውጤታማነት የሚለካው የስኬት መጠን/Success Rate እና
የሕግ ተገዥነት መለኪያን/Compliance Measurement በመጠቀም ነው፡፡ ክትትልና ግምገማ የሚካሄደው በእያንዳንዱ
ደረጃ እየተከናወነ የሚሄድ ነው፡፡

የሥጋት ሥራ አመራር ውጤታማነትን እንደሌሎቹ ደረጃዎች በተራ ሳይሆን በየደረጃው / በእያንዳንዱ የስጋት ሥራ
አመራር ሂደት / መከታተል እና መገምገም አስፈላጊ ነው፡፡ ለዚህም የሚከተሉትን መንገዶች ልንከተል እንችላለን -

 አዳዲስ ሊከሰቱ የሚችሉ ሥጋቶች/ የሥጋት አመላካቾች ምንድን ናቸው?


 የመስተንግዶ ስትራቴጂዎቹ ውጤታማነት እንዴት ነበር?
 ታሳቢ የተደረጉ ጉዳዮች ትክክል ነበሩ?
 የተሻለ ውጤታማ ለመሆን ምን ማድረግ አለብን ? እና የመሳሰሉትን በመመዘን ይሆናል፡፡
የስኬት መጠን/Success Rate
የስኬት መጠን/Success Rate/ የሚሰራው በስጋት ትንታኔ መሠረት ቅደም ተከተል ወጥቶላቸው እንዲስተናገዱ
ከተደረጉት ስጋቶች መካከል በምን ያህሉ ላይ ውጤት እንደተገኘ በማስላት ነው፡፡ ለምሳሌ በታክስ ማጭበርበርና ሌሎች
ጥፋቶች ምክንያት ከፍተኛ የስጋት ፕሮፋይል ያላቸው ድርጅቶች ሆነው በከፍተኛ የስጋት ደረጃ እንዲስተናገዱ ከተደረጉ
100 ድርጅቶች መካከል በምን ያህሉ ላይ ግኝት እንደተገኘ በማስላት የስጋት ስራ አመራር ማለትም ስጋት መምረጫ
መስፈርቶች ትክክለኛነት ይገመገማል፡፡ ዝቅተኛ የስኬት መጠን/Success Rate በሚከሰትበት ጊዜ የስጋት ስራ አመራር
ሂደት/Risk Management Process/ ላይ ጥያቄ የሚፈጥር ሲሆን የስጋት መምረጫ መስፈርቶች በመገምገም
ማሻሻያ ማድረግ አስፈላጊ ነው፡፡

የሕግ ተገዥነት መለኪያ/Compliance Measurement


28 ምንጮች /Reference |
ሌላው የታክሰ ህግ ተገዥነት ስጋት ስራ አመራር ውጤታማነት መለኪያ የሕግ ተገዥነት መለኪያን/Compliance
Measurement በመጠቀም ነው፡፡ የሕግ ተገዥነት መለኪያ የስጋት ስራ አመራር ሂደት/Risk Management Process/
ውጤታማነት በተለይም የሕግ ተገዥነትን ከማምጣት እንጻር የታክስ ስጋቶችን ለመቅረፍ የተወሰዱ መስተንግዶዎችን
ለመገምገም የሚስችል መለኪያ ነው፡፡ የሕግ ተገዥነት መለኪያ የሕግ ተገዥነት መጠን /Compliance Rate/ የሚያወጣ
ሲሆን ከተቀባይነት መጠን በላይ የሆነ የሕግ ተገዥነት ደረጃ በሚፈጠርበት ወቅት ለሕግ ተገዢ እንዳይሆን የሚያደርጉ
ምከንያቶች ወይም ባህሪያት ይጠናሉ፡፡ በጥናቱ መሰረት ለእያንዳንዱ ባህሪ ተመጣጣኝ የሆነ የመስተንግዶ
ስትራቴጂዎችን መንደፍ ያስፈልጋል፡፡

የሕግ ተገዥነት ደረጃን መለካት በርካታ ጠቀሜታዎች ሲኖሩት ዋነኛዎቹየስጋት ስራ አመራር በተለይም (Risk
Assessment) ዘዴዎችን በመገምገም ማሻሻያ ለማድረግ፣ የታክስ ህግ ተገዠነት ዕንቅፋቶችን ለመፍታት እና የገቢ
አሰባሰብና የህግ ማስከበር ስራዎችን ለመመዘን ነው፡፡

VII. ግንኙነት እና ምክክር


በተመሳሳይ ግንኙነት እና ምክክር እንደሌሎቹ ደረጃዎች በተራ ሳይሆን በየደረጃው / በእያንዳንዱ የስጋት ሥራ አመራር ሂደት
/ መከናወን ያለበት ሂደት ሲሆን ለዚህም የሚከተሉትን መንገዶች ልንከተል እንችላለን

 በየደረጃው / በእያንዳንዱ የስጋት ሥራ አመራር ሂደት / ከሚመለከታቸው አካላት ጋር መገናኘት እና መመካከር

 ተገቢውን ግብአት በሪፖርት፣ በውይይት እና በመረጃ ማሰባሰብ

29 ምንጮች /Reference |
ምእራፍ አራት
የጉምሩክ ስጋት ስራ አመራር ትግበራ በዋናው መ/ቤት እና በቅ/ጽ/ቤቶች
የሥጋት ሥራ አመራር በዋናው መ/ቤት እና በቅ/ጽ/ቤቶች የተደራጀ ሲሆን በዋናነት በሚከተሉት የጉሩክ
አሰራሮች ላይ በማኑዋል እና በሲስተም ተግባራዊ እየተደረገ ነው፡

1. በትራንዚት
2. በገቢ እቃ አወጣጥ
3. በወጪ እቃ አወጣጥ እና
4. በመንገደኞች

በቅድሚያ በሁለቱ አካላት የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ከዚህ እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

በዋናው መ/ቤት የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት


 የታክስ ህግ ተገዢነት ስጋት ስራ አመራር ፖሊሲ እና ስትራቴጂ በመቅረጽ እንዲተገበር ማድረግ ፤
 የታክስ ህግ ተገዢነት ስጋት ስራ አመራር አሰራር ስርአትን ማኑዋል በመቅረጽ እንዲተገበር ማድረግ ፤
 የገቢና የወጪ ንግድ እንቅስቃሴ እና የታክስ ኦዲት ስራው በስጋት ስራ አመራር ስርአት እንዲሆን
ማድረግ ፤
 የተቋም አቀፍ ስጋት ስራ አመራር / Enterprise Risk Management / አሰራር ስርአት በመቅረጽ
በሁሉም የተቋሙ ስራዎች ላይ እንዲተገበር ማድረግ ፤ በአተገባበሩም ላይ ድጋፍ እና ክትትል ማድረግ፤
 በታክስ ህግ ተገዢነት ስጋት ስራ አመራር አሰራር ዙሪያ ስልጠናዎችን በመስጠት ለሰራተኛው
ማስተዋወቅ፣
 ተከታታይ የአቅም ግንባታ ስራ በመስራት በሙያው የተሰማሩ ሰራተኞች አቅም ማጎልበት ፤
 በስራው አለም አቀፍ ተሞክሮን በመቀመር አዳዲስ አሰራሮችን መተግበር ፤
 ስለ መንገደኞች/ተጓዦች ፣ዕቃዎች ፣ሀገራት ፣አስመጪዎች ፣ላኪዎች ፣የጉምሩክ አስተላላፊዎች
፣የንግድ ዘርፎች /ዓይነቶች/ ወ.ዘ.ተ. መረጃዎችን ከተለያዩ የመረጃ ምንጮች ማለትም ፡-
 ከጉምሩክ ዳታቤዝ /ASYCUDA++/፣
 ከታክስ ዳታቤዝ /SIGTAS/፣

30 ምንጮች /Reference |
 በጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤቶች የተያዙ ሪከርዶች/ /seizure reports፡- ከልዩነት አጣሪ፣ከድንገተኛ ፍተሻ፣ከድህረ
ዕቃ አወጣጥ፣ከኢንተሊጀንስ/
 ከታክስ ቅ/ጽ/ቤቶች / ከግብር አሰባሰብ ፣ ከታክስ ኦዲት ፣ ከኢንተሊጀንስ/
 በአጠቃላይ ከትሬደር ሪስክ ዳታ ፕሮፋይል ዳታቤዝ፣
 ከሌሎች የህግ ማስከበር አካላት ( Law Enforcement)
 መረጃዎችን በመሰብሰብ፣ በመመዘን፣ በማደራጀት እና ትክክለኛነታቸውን በማረጋገጥ ለስጋት
ትንታኔ ጥቅም ላይ ማዋል ፡፡
 የግብር ከፋይ የታማኝነት ፒራሚድ በመስራት በሚቀመጠው የህግ ተገዥነት ደረጃቸው መሰረት
የመስተንግዶ ስትራቴጂ በመቅረጽ እንዲተገበር ማድረግ ፤
 የግብር ከፋይ የሪሰክ ፕሮፋይል ዳታ ቤዝ በማደራጀት የግብር ከፋይ ፕሮፋይል መስራትና ጥቅም ላይ
ማዋል ፤
 የስጋት ስራ አመራር ስርአት በመንገደኞች መስተንግዶ ላይ እንዲተገበር በማድረግ የተቀላጠፈ
አገልግሎት መስጠት ፤
 በታክስ አሰባሰብ እና ጉምሩክ ስነስርአት አፈጻጸም ላይ አዳዲስ የሚከሰቱ ስጋቶችን በየወቅቱ በመለየት
የስጋት መስተንግዶ ስትራቴጂ መንደፍ ፤ መተግበር እንዲሁም ለሚመለከታቸው አካለት ማስተላለፍ ፤
 በተመረጡ የንግድ ዘርፎች ላይ ተሰማርተው የሚገኙ ግብር ከፋዮች ላይ የስጋት ትንተና በመስራት
(campaign ) በማድረግ የግብር ክፍያ አፈጻጸማቸው እንዲሻሻል ማድረግ፤
 የጉምሩክ ስጋት ስራ አመራር ስርአት በአሲኩዳ ++ ሴሌክቲቪቲ ሞጁል በሁሉም ቅ/ጽ/ቤቶች
ተግባራዊ እንዲሆን ማስቻል እንዲሁም ድጋፍ እና ክትትል ማድረግ፤
 የታክስ ስጋት ስራ አመራር ስርአት በሲግታስ ሞጁል በሁሉም ቅ/ጽ/ቤቶች ተግባራዊ እንዲሆን ማስቻል
እንዲሁም ድጋፍ እና ክትትል ማድረግ ፤
 የተጣጣመ የታክስ ስርአት እንዲኖር ለክልሎች ተገቢውን ድጋፍ መስጠት ፤
 የመረጃ ማሰባሰቢያ እና ለሌሎች የሥጋት ሥራ አመራር አገልገሎት የሚሰጡ ሲስተሞችን ከሌሎች
የሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር በቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እና በዋናው መ/ቤት ባሉ
ዳይሬክቶሬቶች እንዲተገበር ማድረግ ፤
 በስጋት ስራ አመራር ፖሊሲ መርህ መሰረት ስጋት የመከሰት እድልን / likelihood / እና ስጋቱ
የሚያስከትለውን ተጽእኖ / consequence / በመስራት ስጋትን መተንተን /Risk Analysis/ እና የስጋት
ደረጃ ማውጠት /Risk scoring/

31 ምንጮች /Reference |
 የስጋት መምረጫ መስፈርቶች ላይ የስጋት ትነታኔ በመስራት እና የስጋት ደረጃ በማውጣት
ሚስጥራዊነቱን በጠበቀ መልኩ በማኑዋል በተደራጀ ሰነድ ለተጠቃሚዎች ማሰራጨት ወይም
በኤሌክተሮኒክስ ዘዴ ወደ ሲስተም /አሲኩዳ ++ እና ሲግታስ/ እንዲካተት በማድረግ በሁሉም
ቅ/ጽቤቶች መተግበር፤
 ከተሰራጩ የስጋት መምረጫ መስፈርቶች እና ፕሮፋይሎች የተገኙ ውጤቶችን በተመለከተ
ከተጠቃሚዎች እና ከሲስተም ግብአት በማሰባሰብ ፣ግብረ መልሱን በማጠናቀር ያስከተሉትን ውጤት
በመገምገም እና በመመዘን ማሻሻያዎችን መስራት
 በመንግስት ልዩ አገልገሎት እዲጠቀሙ የተፈቀደላቸውን አምራች ድርጅቶች በሲስተም በዝቅተኛ
የስጋት ደረጃ እንዲስተናገዱ በማድረግ የተቀላጠፈ አገልግሎት መስጠት
 በዝቅተኛ የሥጋት ደረጃ የሚስተናገዱ መንግስታዊና አለም አቀፍ ድርጅቶችን እና ዲፕሎማቶችን
በመለየት በዝቅተኛ የሥጋት ደረጃ እንዲስተናገዱ ማድረግ
 የስጋት ደረጃቸው ከፍተኛ የሆኑ / የህግ ተገዥን ደረጃቸው ዝቅተኛ የሆኑትን/ ግብር ከፋዮችን እና
አስመጪዎችን ችግራቸውን ወይም ምክንያታቸውን መለየት ወይም በማጥናት፣ እንደ እስፈላጊነቱ
ማስተማር፣ ኦዲት እንዲደረጉ ለኦዲት ክፍሎች መስጠት፣ የከፉትን ደግሞ በኢንተለጀንስ ክትትል
እንዲደረግባቸው ማድረግ
 በተደጋጋሚ በዝቅተኛ የሥጋት ደረጃ ላይ የሚገኙትን / የህግ ተገዥን ደረጃቸው ከፍተኛ የሆኑትን/
ግብር ከፋዮች እና አስመጪዎችን ከየቅ/ጽ/ቤቶቹ በማሰባሰብ አጠቃላይ የዕውቅና መስጫ፣ የማበረታቻ
መድረክ በማዘጋጀት ማበረታታት፣ በየቅ/ጽ/ቤቱ የተቀላጠፈ መስተንግዶ እንዲያገኙ ማስቻል
 ቅ/ጽ/ቤቶችን መደገፍ
በዋናው መ/ቤት የጉምሩክ ስጋት ስራ አመራር የሚያከናውነው ከጉምሩክ ስነ-ስርዓት አፈፃፀም ጋር በተያያዘ
ስጋቶችን በገቢ፣ ወጪና ተላላፊ ዕቃዎች እና መንገደኞች ላይ በመለየትና በመተንተን በኤሌክቶሮኒክ እና
በተለያዩ መንገዶች በወጥነት በአገር አቀፍ ደረጃ (national) ስጋቶቹ እንዲስተናገዱ ማድረግ ነው፡፡ በዋናው
መ/ቤት የጉምሩክ ስጋት ስራ አመራር ከታች የተዘረዘሩትን ተግባራት ያከናውናል፡፡
ከተለያዩ የመረጃ ምንጮች መረጃዎችን ማሰባሰብና ማደራጀት

በጉምሩክ ስነ-ስርዓት አፈፃፀም የሚፈጠሩ ስጋቶችን ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ የስጋት ምዘና/Risk Assessment/
ለማከናወን ጥራት ያለው መረጃ ማሰባሰብና መደራጀት ቀዳሚ ተግባር ነው፡፡ መረጃዎች ከውስጣዊ እና
ውጫዊ አካላት በኤሌክትሮኒክ ዘዴ ወይም በማኑዋል ሊሰበሰብ ይችላል

32 ምንጮች /Reference |
የውስጥ የመረጃ ምንጮች

 ከጉምሩክዳታቤዝ /ASYCUDA++/፣
 ከትሬደር ሪስክ ዳታ ፕሮፋይል ዳታ ቤዝ /በጉምሩክቅ/ጽ/ቤቶች በማኑዋል ከታች ከተጠቀሱ የስራ
ክፍሎች የተያዙ መረጃዎች
 ከልዩነትአጣሪ
 ከድንገተኛ ፍተሻ
 ከድህረ ዕቃ አወጣጥ
 ከኢንተሊጀንስ
 ከመንገደኞች የሥራ ሂደት
የውጪ የመረጃ ምንጮች
 ከሌሎች የህግ ማስከበር አካላት /ከደህንነት፣ፖሊስ፣ወ.ዘ.ተ
 ከሦስተኛ ወገን የመረጃ ምንጭ ለምሳሌ፡-
 ከባንኮች
 ኢንሹራንሶች
 ከአየር መንገዶች
 ከንግድ መርከብ
 ከንግድና ኢንዱስትሪ
 ከኢንተርኔት
 ከአለም አቀፍ ተቋማት ድህረገጽና ዳታቤዝ /WCO - CEN/

የገቢ እቃ አወጣጥ የሥጋት ሥራ አመራር


የሥጋት ሥራ አመራረ ሥርአቱ በገቢ እቃ አወጣጥ ላይ በዋናነት በሲስተም /Automated Risk Management
System/ ሲሆን /ASYCUDA++ Selectivity/ በመጠቀም ተግባራዊ የተደረገ ነው፡፡ የሥጋት ትንታኔውና
ደረጃው በ 8 የስጋት መምረጫ መስፈረቶች እና ተጨምሪ 7 ለተቀላጠፈ መስተንግዶ /facilitation/ እና
ቁጥጥር ሚያግዙ መስፈሮቶች በአጠቃላይ 15 መስፈርቶችን የሚጠቀም ሲሆን እያንዳንዱ መስፈርት በስሩ
ንዑሳን መስፈርቶች አሉት፡፡ እነዚህ መስፈርቶች በማዕከል ተተንትነው የመጨረሻ የተጠናቀቀ የስጋት ደረጃ
በሁሉም ቅ/ጽ/ቤቶች ላይ ተግባራዊ እንዲሆኑ አሲኩዳ ሴሌክቲቪቲ ሪስክ ሞጁል ውስጥ ይካተታል፡፡ በዚህም
ሂደት በየትኛውም የጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት የጉምሩክ ስነ-ስርዓት ለመፈጸም ወደ ጉምሩክ ክልል የሚገቡ የገቢ

33 ምንጮች /Reference |
ዕቃዎች ላይ በሲስተም የስጋት ደረጃዎች እየተጣለ በስጋት ደረጃዎች መሰረት የተሳለጠ አገልግሎት መስጠት
እና ቁጥጥር በማድረግ በቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ለደንበኞች አገልግሎት ይሰጣል፡፡መስፈርቶቹም፡-

የስጋት መምረጫ መስፈርቶች/Risk Assesment Criteria/

1. የአስመጪዎች ፕሮፋይል /Company Profile/


2. የጉምሩክ አስተላላፊዎች ፕሮፋል/Customs Clearing Agents Profile/
3. የዕቃዎች ታሪፍ /Tariff/
4. የዕቃዎች ዋጋ /Value/
5. የዕቃዎች ስሪት ሀገር /Country of Origin/
6. የዕቃዎች ጭነት ሀገር /Country of Consignment/
7. CPC (Customs Procuder Codes)
8. ልዩ ፈቃድ/Special Requirement

ከላይ ከተጠቀሱት በተጨማሪ ከታች እንደሚከተለው የቀረቡት መምረጫ መስፈርቶች አሲኩዳ ሴሌክቲቪቲ
ሪስክ ሞጁል ውስጥ ተካተው የስጋት ደረጃዎችን ለመወሰን ያገለግላሉ፡፡

1. የመንግስት ድርጅቶች /Governement List/


2. ዲፕሎማትና ዓለም አቀፍ አህጉር አቀፍ ድርጅቶች/ Diplomatic and International
OrganizationsList/
3. የልዩ የጉምሩክ አገልግሎት ተጠቃሚ የሆኑ አምራች ድርጅቶች/Manufacturing List/
4. ታማኝ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ ድርጅቶች/Authorized Economic Operators/
5. መኪና/Car list/
6. ጥሬ ዕቃዎች/Raw Material and Yellow List Commodities/
7. የራንደም መረጣ/Random Selection/

ከላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች መሰረት በማድረግ በገቢ ዕቃዎች ላይ ስጋት ዝቅተኛ፣

መካከለኛ እና ከፍተኛ እየተባለ በሲስተም ይጣላል፡፡

አሲኩዳ++ ሴሌክቲቪቲ

የስጋት መምረጫ መስፈርት

 የአስመጪዎችየስጋት ፕሮፋይል
 የጉምሩክ አስተላላፊዎች
የስጋት ፕሮፋል
34 ምንጮች /Reference |
 የዕቃዎች ታሪፍ /Tariff/
 የዕቃዎች ዋጋ / Value/
 የዕቃዎች ስሪት ሀገር
የስጋት ደረጃ የመስተንግዶ ስተራቴጂዎች

ቀይ ፍተሻ እና ሰነድ ምርመራ

ቢጫ ሰነድ ምርመራ

ሰነድ(ፌዝቬት
)
አረንጓዴ መልቀቂያ /PCA Intellegence/

መልቀቂያ /PCA Intellegence/


ሰማያዊ

የስጋት ፕሮፋይል /Risk Profile/

የስጋት ፕሮፋይል ማለት የሥጋት ቴምፕሌት ሲሆን የሥጋት አመላካቾችን /Risk Indicators/ በመጠቀም
ኢላማዎች /Targets ለመምረጥ የምንጠቀምበት ነው፡፡ እነዚህ አመልካቾች የተከሰቱ ወይም ሊከሰቱ የሚችሉ
ሥጋቶችን ይጠቁሙናል፡፡ ፕሮፋይሎች ከፍተኛ ሥጋት ያላቸውን ትራንዛክሽኖች ወይም ክስተቶችን ምንም
ወይም ዝቅተኛ ሥጋት ካላቸው ለመለየት ያስችሉናል፡፡ ይህም ውስን የሆነውን የሰውና የገንዘብ ሀብታችንን
በተገቢው ሁኔታ መጠቀም እንድንችል ይረዳናል፡፡ የስጋት ፕሮፋይል ከታች የተዘረዘሩትን ይዘቶች ያካትታል፡-

 የሥጋት ቦታዎችን (Risk Areas) ለምሳሌ፡-


 ከዕፅ ጋር የተያያዘ ሥጋት
 ከገቢ ጋር የተያያዘ ሥጋት
 ሊከሰቱ የሚችሉ ሥጋቶችን
 የሥጋት አመላካቾችን /risk indicators/ ለምሳሌ፡-
 ድርጅቶችን፣ሰዎችን፣ሀገራትን፣ የዕቃዎች ዓይነትን
 ሊወሰዱ የሚገቡ ዕርምጃዎችን/The counter measures to be taken/፣

35 ምንጮች /Reference |
 ፕሮፋይሉ ለምን ያህል ጊዜ አገልግሎት እንደሚሰጥ፣
 ተገቢውን ሀብት (የሰው፣ የገንዘብ እና ሌሎች አስፈላጊ ነገሮችን)፡፡

የስጋት ፕሮፋይል በተለያዩ ሁኔታዎች ሊዘጋጅ ይችላሉ ለምሳሌ፡-


ሀ. ከተለያዩ ሀገራት ለሚመጡ መንገደኞች /ተጓዦች
ለ. ለዕቃዎች
ሐ. ለሀገራት/ ዕቃዎች ለሚመረቱባቸው ወይም ለሚጫኑባቸው
መ. ጭነት የሚካሄድባቸው የውስጥና የውጭ ወደቦች
ሠ. ለአስመጪዎች
ረ. ለላኪዎች
ሰ. ለጉምሩክ አስተላላፊዎች
ሸ. ለንግድ ዘርፎች /ዓይነቶች/

የስጋት ፕሮፋይል በባህሪው

 በተወሰነ ነገር ላይ ማተኮር /ብዛት ያለው ነገር ሲኖር/፣


 ትክክለኛነት - የሚመሰረቱት በትክክለኛ /ጥሩ/ መረጃ ላይ ነው፣
 ማኔጀብል - በየጊዜው የሚሻሻሉና የሚከለሱ ናቸው ፣
ፕሮፋይል ለማዘጋጀት የምንከተላቸው ደረጀዎች

1. መረጃዎችን ከሁሉም የመረጃ ምንጮቻችን መሰብሰብ


2. የተሰበሰቡ መረጃዎችን መመዘንና ማደራጀት
3. መረጃውን መተንተን
4. የሥጋት ትንታኔ ማካሄድ እና የሥጋት ደረጃ ማውጣት
5. ፕሮፋይሎችን ጥቅም ላይ ማዋል
6. ውጤቶችን መገምገምና መመዘን
7. ግብረ-መልስ ማሰባሰብ
8. ፕሮፋይልን ማሻሻል
9. የተሻሻሉ ፕሮፋይሎችን ጥቅም ላይ ማዋል
መረጃዎችን ከሁሉም የመረጃ ምንጮቻችን መሰብሰብ
የመረጃ ምንጮች

36 ምንጮች /Reference |
 ከጉምሩክ ዳታቤዝ /ASYCUDA++/
 ከታክስ ዳታቤዝ /SIGTAS/
 ከ TPRDP ዳታቤዝ/ በጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤቶች የተያዙ ሪከርዶች/ /seizure reports/
 ከልዩነት አጣሪ
 ከድንገተኛ ፍተሻ
 ከድህረ ዕቃ አወጣጥ
 ከኢንተሊጀንስ
 ከታክስ ቅ/ጽ/ቤቶች
 ከግብር አሰባሰብ
 ከታክስ ኦዲት
 ከኢንተሊጀንስ
 ከሌሎች የህግ ማስከበር አካላት /ከደህንነት፣ፖሊስ፣ ወ.ዘ.ተ
 ከሦስተኛ ወገን የመረጃ ምንጭ
 ከባንኮች
 ኢንሹራንሶች
 ከ ህግ ማስከበር አካላት /ደህንነት
 ከአየር መንገዶች
 ከንግድ መርከብ
 ከንግድና ኢንዱስትሪ
 ከተለያዩ ሰነዶች ለምሳሌ ቢል ኦፍ ሎዲንግ/የማስጫኛ ሰነዶች/ ኤርዌይቢል ኢንቮይስ ወ.ዘ.ተ
 ከኢንተርኔት
 ከአለም አቀፍ ተቋማት ድህረ ገጽና ዳታ ቤዝ /WCO - CEN/
የተሰበሰቡ መረጃዎችን መመዘንና ማደራጀት
 የመረጃውን ትክክለኛነትና ተአማኒነት ማጥራት
 የአንድ መረጃ ጥቅም የሚወሰነው በትክክለኛነቱ፣በጥራቱና በተአማኒነቱ ነው ስለዚህ መረጃው ከትክክለኛና
ከታማኝ ምንጭ ስለመገኘቱ ማረጋገጥ ይኖርብናል፡፡
 የተሰበሰቡ መረጀዎች ፕሮፋይል ሊሰራለት ከታሰበው ድርጅት ዕቃ ወይም ሀገር ጋር ተያያዥ ስለመሆኑ መለየትና
ማጣራት
መረጃውን መተንተን (Analyze the data)
 መረጃውን ስንተነትን የሚከተሉትን ጉዳዮች ልንመለከት እንችላለን፡-
 የጋራ ባህሪያትን መለየት
 ግንኙነቶችን መለየት

37 ምንጮች /Reference |
 የሥጋት አመላካቶችንና ዕውነታዎችን መለየት/Indicators and trends identification/
 ልንከተል የሚገባንን የሥጋት መስተንግዶ ማስቀመጥ/Risk treatment/
የሥጋት ትንታኔ ማካሄድ እና የሥጋት ደረጃ ማውጣት/Risk Analysis and Risk Score
 በሥጋት ሥራ አመራር ፖሊሲና ስትራቴጂ ላይ በተቀመጠው መሰረት የተሰበሰበውን መረጃ መሰረት በማድረግ
የሥጋት ትንታኔ /Risk Analysis/ እንደሚከተለው ይሰራል፡-
 በቅድሚያ ሥጋት የመከሰት እድል / Likelihood እና ሥጋቱ የሚያስከትለው የኢኮኖሚ ተጽእኖ /
Consequence ይሰራል
 በመቀጠል ተሰብስቦ በተተነተነው መረጃ መሰረት የስጋት ደረጃዎችን እንደደረጃቸው በሚከተለው መልኩ
ይቀመጣል

 ቀይ/ከፍተኛ የስጋት ደረጃ

 ቢጫ/ መካከለኛ የስጋት ደረጃ

 አረንጓዴ/ ዝቅተኛ የስጋት ደረጃ

ፕሮፋይሎችን ጥቅም ላይ ማዋል /Establish and Disseminate (activate) the profile/

 ፕሮፋይል ጥቅም ላይ ከመዋሉ በፊት የሚያስከትለው ተፅዕኖ መሞከርና መታየት አለበት፡፡በመቀጠል ፕሮፋይሉ
በሁሉም ቅ/ጽ/ቤቶችና በዋናው መ/ቤት ባሉ ዳይሬክቶሬቶች ጥቅም ላይ ይውላል፡፡

ውጤቶችን መገምገምና መመዘን / Follow up and Evaluate results

 ፕሮፋይሎች ጥቅም ላይ ከዋሉ በኋላ ያስከተሉትን ተጽእኖ ወይም ያስከተሉትን ውጤት በመገምገም እና
በመመዘን ቀጣይ የማሻሻያዎች ስራዎችን ይሰራል፡፡

ግብረ-መልስ ማሰባሰብ (Collect Feedback)

 ፕሮፋይል ጥቅም ላይ ከዋለ በኋላ ከሁሉም ቅ/ጽ/ቤቶችና በዋናው መ/ቤት ካሉ ዳይሬክቶሬቶች ግብረ-መልስ
/ግብዓት/ በማሰባሰብ ቀጣይ ማሻሻያ ማድረግ

ፕሮፋይልን ማሻሻል (update the profile)

 ፕሮፋይሎች የተሰወነ ጊዜ አገለግሎት ከሰጡ በኋላ በሚሰበሰቡ ግብዓቶች /መረጃዎች/ መሰረት መሻሻል አለባቸው
ምክንያቱም፡-
 ሰዎች በየጊዜው አዳዲስ ነገሮችን በመጠቀም የወንጀል ተግባር ስለሚፈፅሙ

38 ምንጮች /Reference |
 የግብር ከፋዮች ባህሪ በየጊዜው ስለሚለዋወጥ
 ፕሮፋይሎች ሁሌም ትክክል ላይሆኑ ስለሚችሉ
 ከተጠቃሚዎች የተለየ ግብዓት /ግብረ-መልስ/ ሲኖር

የአስመጪዎች የስጋት ፕሮፋይል /Company Risk Profile/

የአስመጪዎች የስጋት ፕሮፋል የሚዘጋጀው ከተለያዩ ምንጮች መረጃዎችን በማሰባሰብና በማደራጀት የስጋት ትንታኔ
በመመዘኛ መስፈርቶች መሰረት በማከናወን ሲሆን በዋናነት ስ ጋት የመከሰት ዕድል /Likelihood እና ስጋቱ
የሚያስከትለው ተጽዕኖ /Consequence በማስላት ነው፡፡ስጋት የመከሰት ዕድል /Likelihood ለማስላት አንድ
አስመጪ ወይም የጉምሩክ አስተላላፊ በተወሰነ የጊዜ ገደብ ውስጥ ካቀረባቸው ዕቃዎች ወይም ዲክላራሲዮኖች እንጻር
የጥፋተኝነት ሪከርድ የተገኘባቸውን ፐርሰንቴጅ በማስላት ነው፡፡ እንዱሁም ስ ጋቱ የሚያስከትለው ተጽእኖ
/Consequence/ የሚሰላው አስመጪው በራስ ተነሳሽነት ካቀረበው የገንዘብ መጠን በተጨማሪ መንግስት ሊያጣ
የነበረውን በልዩነት የተከፈለ የገንዘብ መጠን ለአጠቃላይ ለተከፈለ የገንዘብ መጠን ፐርሰንቴጅ በማስላት ሊያደርስ የነበረው
ተጽዕኖ Consequnce በማስቀመጥ ነው፡፡ ይህም ከላይ በምእራፍ ሶስት በቀረበው ቀመር መሰረት የሚሰራ ይሆናል፡፡

ከላይ የተቀመጠው የሥጋት ትንታኔ ዘዴ የሚያገለግለው የአስመጪዎችን፣ የላኪዎችን እና የጉምሩክ


አሰተላላፊዎችን የስጋት ትናታኔ እና የሥጋት ደረጃ ለማውጣት ሲሆን ለሌሎች መምረጫ መስፍርቶች
የሥጋት ትንታኔ እና የሥጋት ደረጃ ለመስራትም ያገለግላል፡፡

የጉምሩክ አስተላላፊዎች የስጋት ፕሮፋይል /Customs Clearing Agents Risk Profile/

የጉምሩክ አስተላላፊውች የስጋት ፕሮፋል አሰራር ከአስመጪዎች የስጋት ፕሮፋይል አሰራር ጋር በተመሳሳይ
መልኩ የሚከናወን ቢሆንም በግብዓትነት ከሚውሉ መረጃዎች ጋር ተያይዞ ልዩነቶች አሉ፡፡ ለጉምሩክ
አስተላላፊዎች የስጋት ፕሮፋይል ግብዓት የሚሆኑ መረጃዎች በዋናነት የሚሰበሰቡት አስተላላፊዎች
የሚፈጽሙት ጥፋት የጉምሩክ አስተላላፊዎች በመመሪያ 64/2003 ዓ.ም በተገለጹ ጉዳዮች ላይ ነው፡፡

የዕቃዎች ታሪፍ /Tariff/

የታሪፍ ስጋት ደረጃ በአምስት ንዑስ-መስፈርቶች ድምር አማካይ ውጤት የሚገኝ ሲሆን እያንዳንዱ ንዑስ-
መስፈርት በስጋት ስያሜና (RisK Assignments) እና በስታቲስቲካል ካልኩሌሽን (statistical calculation)
የሚሠራ ነው፡፡ አምስቱ ንዑስ-መስፈርቶች፡-

I. ጥቅል የቀረጥና ታክስ መጣያ ምጣኔ መሰረት የስጋት ትንተና መስራት (Aggregate
Computation Risk)

39 ምንጮች /Reference |
ይህ ንዑስ-መስፈርት በእያንዳንዱ ዕቃ (HS code) ላይ የሚጣለውን ጥቅል ቀረጥና ታክስ ምጣኔ
መሠረት በማድረግ የሚሰራ ሲሆን የእቃዎችን ታሪፍ ምጠኔ በእያንዳንዱ ኤች ኤስ ድምር መስራት
(Agregate Duty and Tax) በኤች ኤስ የታሪፍ አግርጌት ድምር ስትንዳርድ ዲቬሽን ከርቭ
በመጠቀም ይሰራል፡፡

II. የዕቃዎችን ለገቢ የሚኖራቸውን አስተዋዕፆ (Contribution for Revenue Collection)


ይህ ንዑስ-መስፈርት እያንዳንዱ ዕቃ (HS code) በበጀት አመቱ ለተሰበሰበ ገቢ የነበረው
አስተዋጽኦ በመተንተንና ስታንዳርድ ዲቬሽን ቀመር በመጠቀም የስጋት ደረጃዎች
ይመደባሉ፡፡
III. ስጋት የመፈጠር እድልን እና ስጋቱ የሚያስከትለውን ተጽእኖ (Likelhood and
Consequence)
ስጋት የመከሰት እድል /Likelihood ለማስላት አንድ ዕቃ በተወሰነ የጊዜ ገደብ ውስጥ ምንያህል ጊዜ
ወደ ሀገር እንደገባ እና ወደ ሀገር ከገባበት አጠቃላይ ድምር በምን ያህሉ ላይ የጥፋተኝነት ሪከርድ
እንደተገኘበት በማስላት ነው፡፡ ስጋቱ የሚያስከትለው ተጽእኖ /Consequence የሚሰላው ከዕቃው
በራስ ተነሳሽነት ከተሰበሰበው የገንዘብ መጠን በተጨማሪ መንግስት ሊያጣ የነበረውን በልዩነት የተከፈለ
የገንዘብ መጠን ለአጠቃላይ ለተከፈለ የገንዘብ መጠን ፐርሰንቴጅ በማስላት ሊያደርስ የነበረው ተጽዕኖ
Consequnce በማስቀመጥ ነው፡፡
IV. የዕቃዎች ለታሪፍ አመዳደብ አሻሚ መሆን (Confusing Description)
በሃርሞናይዝድ የእቃዎች መጽሀፍ የተዘረዘሩት የእቃዎች አይነት ውስጥ ለታሪፍ ምደባ
አሻሚ የሆኑትን ለይቶ ስጋት ደረጃ ማስቀመጥ፤ ይህ የሚከናወነው ከዚህ ቀደም
የጉምሩክ ስነስርአት አፈጻጸም ወቅት በሚኖሩን እውቀት በመጠቀም ከቅርንጫፍ
ጽ/ቤቶች እና ከታሪፍና ዋጋ ዳሬክቶሬት መረጃ እና ግብአት በመውሰድ ሲሆን
በእቃዎች የኤችኤስ ዝርዝር ምእራፍ በምእራፍ እየተለየ ከፍተኛ፣ መካከለኛ እና
ዝቅተኛ በማድረግ ስጋቱ ይጣላል፡፡
V. በሃርሞናይድ የዕቃዎች መጽሀፍ በሌሎች ላይ መመደብ (Classification in to
outhers)
በሃርሞናይዝ የዕቃች ታሪፍ መጽሀፍ ላይ በሌሎች ምእራፍ የተመደቡ እቃዎችን
በመለየት ለማጭበርበር ተጋላጭ የሆኑትን በከፍተኛ ስጋት ደረጃ ማስቀመጥ፡፡

የዕቃዎች ዋጋ /Value/

የዕቃዎች ዋጋ ስጋት ደረጃ በሁለት ንዑስ-መስፈርቶች ድምር አማካይ ውጤት መሰረት በስታቲስቲካል
ካልኩሌሽን (statistical calculation) የሚሠራ ነው፡፡

40 ምንጮች /Reference |
1. ዕቃዎች ለጠቅላላ ቀረጥና ታክስ አስባሰብ ያላቸው ድርሻ (contribution to revenue
collection

ይህ ንዑስ መስፈርት በአያንዳንዱ ዕቃ በተወሰነ የጊዜ ገደብ ውሰጥ የተከፈለ ቀረጥና ታክስ
በዓመት ውስጥ ለተሰበሰበው ገቢ ያለው ድርሻ በመቶኛ ተሰልቶ የሚሰራ ነው፡፡ ይህ ተግባር
በቀጣይም ስታንዳርድ ዲቪዮሽንን መሠረት በማድረግ የሚሠራ ሲሆን የስጋት ደረጃውም
ለጠቅላላ ገቢ አሰባሰብ ባላቸው ድርሻ መሠረት የሚጣል ይሆናል፡;

2. የዕቃዎች የመነሻ ዋጋ/minimum value/ እና ማጣቀሻ ዋጋ/reference value/ መሰረት


በማድረግ የስጋት ትንተና ማከናወን
ይህ ንዑስ-መስፈርት ሲሰራ የመነሻ ዋጋ ያለቸው ዕቃዎች በሙሉ ወጥ የሆነ ዋጋ የተሰጣቸው
በመሆኑ በዝቅተኛ የስጋት ደረጃ ላይ ይመደባሉ፡፡ ነገር ግን የማጣቀሻ ዋጋ ያላቸው ዕቃዎች
በተቃራኒው በመካከለኛ የስጋት ደረጃ ላይ ይመደባሉ፡፡ ይህ መስፈርት በቀጣይ አዲሱ የዋጋ
ሥርአት በትክክል በሚሰራበት ወቅት ማስተካከያ የሚደረግበት ይሆናል፡፡

የዕቃዎችስሪት ሀገር /Origin/

የሀገራት ስጋት ትንተና እቃዎች ከተለያዩ ሀገራት በሚመጡበት ጊዜ የሚኖራቸው መጭበርበር ምን ያህል
እንደሆነ ለማወቅ ከዚህ ቀደም ከነበሩ የገቢ መረጃዎችን መሰረት በማድረግ ይሰራል፡፡የስሪት ሀገር ስጋት ደረጃ
በአራት ንዑስ መስፈርቶች መሰረት ይጣላል፡፡

1. (preferential and non-preferential trade agreement risk)


ይህ ንዑስ መስፈርት ሀገራት ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የንግድ ስምምነት መሠረት አድርጐ የስጋት
ስያሜ (Risk Assign) የሚደረግበት ነው፡፡ ይህም አስመጪዎች የቀረጥና ታክስ ቅናሽን ለመጠቀም
የስሪት ሀገራት የማጭበርበር ስጋት ሊፈጥሩ ስለሚችሉ ስጋትን ለመቀነስ የሚረዳ ንዑስ መስፈርት
ነው፡፡
2. ስጋት የመከሰት እና ስጋቱ የሚያሳድረው ተጽዕኖ (likelihood and consequence risk)
ይህ ንዑስ መስፈርት የሚሠራው በመጀመሪያ ስጋት የመከሰት እድል በማስላት ሲሆን በእያንዳንዱ
ሀገር በተወሰነ ጊዜ ውሰጥ ምን ያህል ጊዜ ዕቃዎች ወደ ሀገር እንደገቡ እና በምን ያህሉ ላይ ልዩነት

41 ምንጮች /Reference |
እንደተገኘ በማስላት ነው፡፡ ስጋቱ የሚያስከትለው ተጽዕኖ የሚሰላው ከእያንዳንዱ ሀገር የተሰበሰበ
የቀረጥና ታክስ በልዩነት ከተሰበሰበው እንጻር በማስላት ነው፡፡ በመጨረሻም (consequence and
likelihood combination matrix) በመጠቀም ስጋት የሚጣል ይሆናል፡፡
3. ሀገራት ከዚህ ቀደም ያላቸው ተሞክሮ (Previous Risk knowledge on Countries)
ይህ ንዑስ መስፈርት ሀገራት ከዚህ ቀደም ከሚልኳቸው ዕቃዎች ጋር በተያያዘ ያላቸውን የሕግ
ተገዥነት ተሞክሮ በመለየት የሚጣል ነው፡፡ ይህም በየሀገራት ስጋት በመሰየም (Risk Assignment)
የሚሠራ ይሆናል፡፡
4. የአካላዊ ፍተሻ ውጤት (Examination result Risk)
ይህ ንዑስ መስፈርቱ መረጃዎችን መሠረት በማድረግ በአካላዊ ፍተሻ የሚኙትን ልዩነቶች
በተወሰነ ጊዜ ውስጥ በመለየት ስጋት የሚጣልበት አሰራር ነው፡፡ ይህም የሚጣለው የስሪት ሀገርና
የጭነት ሀገር ተመሳሳይ በሚሆንበት ሁኔታ ላይ ነው፡፡
በመጨረሻም የአራቱን ንዑስ መስፈርቶች ድምር ውጤት ስታንዳርድ ዲቪዮሽንን በመጠቀም ስጋት
የሚጣል ይሆናል፡፡

የዕቃዎች ጭነት ሀገር /Consignment/

ይህ መስፈረት በስሪት ሀገራት ላይ ያሉትን ንዑስ-መስፈርቶች መሉ በሙሉ በመጠቀም የሚጣል የስጋት


መምረጫ መስፊርት ነው፡፡ የአሠራር ሁኔታውም በተመሳሳይ መልኩ በስሪት ሀገራት ባለው መሠረት
የሚከናወን ነው፤የሀገራት ስጋት ትንተና እቃዎች ከተለያዩ ሀገራት በሚመጡበት ጊዜ የሚኖራቸው መጭበርበር
ምን ያህል እንደሆነ ለማወቅ ከዚህ ቀደም ከነበሩ የገቢ መረጃዎችን መሰረት በማድረግ ይሰራል፡፡

የ CPC (Customs Procuder Codes)

የሲፒሲ ኮድ በምድባቸው ማለትም ለንግድ፤ቀርጥ ነጻ ተጠቃሚ ፤ ልዩ ፈቃድ ያላቸው ተጠቃሚ ፤


የኢንቨስትመንት ተጠቃሚ እና ሌሎችኮዶች በመለየት ስጋት ደረጃ የማስቀመጥ ተግባር ይከናወናል
ኢምባሲዎችን፤ አለምአቀፍ ድርጅቶችን ፤አህጉራዊ ድርጅቶችን ያላቸውን ልዩ መብት መሰረት በማድረግ
ለማስተናገድ ያስችላል፡፡

ልዩ ፈቃድ/Special Requirement

ገደብ የተደረገባቸው እቃዎች ወደ ሀገር ውስጥ ከመግባታቸው በፊት የሚመለከታቸው ባለስልጣን መ/ቤቶች
ማረጋገጫ እየሰጡባቸው የሚገቡትን በመለየት ስጋት ደረጃ ማስቀመጥ፡፡ የማህበረሰቡን ደህንነት ከመጠበቅ
አንጻር እቃዎቹን ተከታትሎ ተገቢውን ማስረጃ ቀርቦባቸው ወደ ሀገር እንዲገቡ ስልሚያደርግ አስፈላጊ ነው፡፡

42 ምንጮች /Reference |
በታሪፍ መጽሀፉ ከተዘረዘሩት እቃዎች ልዩ ፈቃድ የሚያስፈልጋቸውን ዝርዝር መለየት በተለዩት መሰረት ስጋት
ደረጃቸውን በመካከለኛ ማስቀመጥ ሌሎችን /ከዚህ ውጪ/ ያሉትን በዝቅተኛ ስጋት ደረጃ ማስቀመጥ፡፡

ተጨማሪ የስጋት መምረጫ መስፈርቶች

 የመንግሰት ድርጅቶች /Governement List/


 ዲፕሎማትና አለም አቀፍ ድርጅቶች/ Diplomatic and International Organizations/
 የልዩ የጉምሩክ አገልግሎት ተጠቃሚ የሆኑ አምራች ድርጅቶች/Manufacturing List/
 ታማኝ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ ድርጅቶች/ Authorized Economic Operators /
 መኪና/ Car list/
 ጥሬ ዕቃዎች/ rawmaterial and Yellow List Commodities/
 የራንደም መረጣ/ Random Selection/

የመንግሰት ድርጅቶች /Governement List/

በስጋት ስራ አመራር አመለካከት የመንግስት ድርጅቶች ማለት የመንግስት ባለበጀት መ/ቤቶች ማለት ሲሆን
መንግስት ከዕቃዎች ግዚ ጋር ተያይዞ የቁጥጥር ስርዓት ያለው እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ
ድርጅቶቹ ለባለስልጣን መ/ቤቱ እንደ አጋር ተደርገው ሊቆጠሩ የሚችሉ በመሆኑ ስጋት የመፈጠር እና ስጋቱ
የሚያስከትለው ተፅእኖ በዝቅተኛ የስጋት ድረጃ ላይ ያስመድባቸዋል፡፡ በተጨማሪም ያለንን ውስን ሀብት
በሌሎች ሥጋቶች ላይ ማዋል ተገቢ ይሆናል፡፡

የዲፕሎማትና አለም አቀፍእና አህጉር አቀፍ ድርጅቶች/ Diplomatic and International Organizations
List/

የበቬና ኮንቬንሽን እና በሌሎች ስምምነቶች ያለመፈተሸ መብት ያላቸው ድርጅቶች በዝቅተኛ የስጋት ድረጃ
ላይ በሲስተም እንዲመደቡ ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ እነዚህ መብት ያላቸው አካለት በዝቅተኛ የሥጋት
ደረጃ ይመደባሉ፡፡

የልዩ የጉምሩክ አገልግሎት ተጠቃሚ የሆኑ አምራች ድርጅቶች/Manufacturing List/

መንግስት ሀገራችን ካለችበት ድህነት በአጭር ጊዜ ተላቃ መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ደረጃ እንድትሰለፍ ለማድረግ የልዩ
የጉምሩክ አገልግሎት አሰራር ዘርግቷል፡፡ ይህም ለሀገራችን ልማት ከፍተኛ ሚና የሚኖራቸውን
የአምራችና የላኪ ዘርፍ እንዲሁም ኢንቨስትመንትና ፕሮጀክቶችን ለመደገፍ በልዩ ሁኔታ የተቀላጠፈ

43 ምንጮች /Reference |
የጉምሩክ አገልግሎት የሚያገኙበት አሰራር ዘርግቷል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ድርጅቶቹ መስፈርቱን
አሟልተው ከሚመለከታቸው አካላት በኩል ሲላኩ በዘርፉ የተሰማሩበት የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር በማጣራት
ቢስተም በዝቅተኛ የስጋት ደረጃ እንዲስተናገዱ የማኑፋክቸሪንግ ሊስት ውስጥ ይካተታሉ፡፡ ከተስተናገዱ
በኋላ በድህረ ዕቃ አወጣጥ እና በኢንተነጀንስ ቁጥጥር ይደረግባቸዋል፡፡

ታማኝ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ ድርጅቶች/Authorized Economic Operators/

የአለም ጉምሩኮች ሕብረት Safe Framework of Standards to Secure and Facilitate Global Trade
እንደሚጠቁመው ታማኘ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ ማለት በአለም አቀፍ ደረጃ ከዕቃዎቸ እንቅስቃሴ ጋር
በተያያዘ የጉምሩክ ወይም ሌሎች ተመሳሳይ ህጎች እንደሚያከብር በጉምሩክ አስተድደር በኩል
ማረጋገጫ የተሰጠው አካል ማለት ነው፡፡ ታማኝ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ/ AEO አሰራር መተግበር ተቋሙ
ከተገልጋዮች ጋር መልካም ግንኙነት/partnerships እንዲፈጥር የሚያግዝ ሲሆን ተቋሙ በተለያዩ
ዘርፎች ለተመደቡ ድርጅቶች ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ሊሰጥ ይችላል፡፡ ለምሳሌ ለአምራችና ላኪዎች፣
አጓጓዝ ድርጅቶች፣ ወኪሎች፣ ወደቦች፣ መጋዘኖች፣ ተርሚናሎች እና ወ.ዘ.ተ፡፡ በዚህ አሰራር ውስጥ
የስጋት ስራ አመራር በጉምሩክ በኩል ለድርጅቶች ታማኘ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽነት ማረጋገጫ
ለመስጠት የሚረዳ መመዘኛ ነው፡፡ ድርጅቶች በራሳቸው ፈቃድ ለታማኘ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽነት
ሲያመለክቱ ባለሥልጣኑ ድርጅቶችን ለመምረጥ እንደ እንድ መስፈርት የድርጅቶችን በጉምሩክ ስነ-
ስርዓት አፈጻጸምና ከግብረ አከፋፈል ጋር ያላቸውን የታማኝነት ደረጃ/የፕሮፋይል የስጋት ደረጃ
ይጠቀማል፡፡

በመሆኑም ለተመረጡ ታማኝ ለሆኑ ቀለል ያለ የዕቃ ዲክላራሲዮን አቀራረብና የዕቃ አወጣጥ ሥነ
ሥርዓት ተፈጻሚ ሲሆን ዕቃዎችን ለመለየት የሚያስፈልጉ ውስን መረጃዎች እስከቀረቡ ድረስ
የተሟላው የዕቃ ዲክላራሲዮን በቀጣይነት እንዲቀርብ በመፍቀድ ዕቃዎቹን በሰማያዊ የስጋት ደረጃ
እተመደቡ ይስተናገዳሉ፡፡ በዚህ ስርዓት የሚገቡ እቃዎች በዝቅተኛ የስጋት ደረጃ ላይ እንዲመደቡ
ያስቻለው የሕግ ተገዥነትን ለማበረታታ ሲሆን በድህረ ዕቃ አወጣጥ ኦዲት በኩል የዕቃ ዲክላራሲዮን
ትክክለኛና ተአማኒነት ያለው መሆኑን እና ሌሎች የጉምሩክ ግዴታዎች መከበራቸውን ማረጋገጥ
ስለሚቻል ነው፡፡

መኪና/ Car list/

መኪና ከሌሎች ዕቃዎች አንጻር በባህሪው የማጭበርበር ድርጊት ሊፈጸምበት የሚችል ዕቃ ነው፡፡ የመኪናን
ቀረጥና ታክስ ለማስላት መኪናው የተመረተበትን ዓመት፣ የመኪናውን ሞዴል እና የመኪናወን ሞተር ቁጥር ከቀረበው ሰነድ
44 ምንጮች /Reference |
ጋር ማመሳከር ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም መኪና እና የመኪናን ሰነድ ባለማመሳከር የሚፈጠረው የስጋት ተፅዕኖ ከፍተኛ
በመሆኑ ሁሉም መኪናዎች በስስተም በከፍተኛ የስጋት ደረጃ ላይ ይመደባሉ፡፡

ጥሬ ዕቃዎች/ Raw Material and Yellow Commodities List/

ጥሬ ዕቃዎች የሚባሉት ለምርት አገልግሎት ግብዓት የሚሆኑ በኢንቨስትመት ማበረታቻ ስርዓት የተካተቱ
የሁለተኛ መደብ ዕቃዎች እና የጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ቅናሽ ያላቸው ዕቃዎች ናቸው፡፡ የመካከለኛ ስጋት
ዕቃዎች /Yellow List Commodities/የሚባሉት ደግሞ ፍተሻ ለማድረግ የጉምሩክ ላብራቶሪ
የሚያስፈልጋቸው በመሆናቸው ምክንያት በተጓዳኝ መ/ቤቶች በኩል ቁጥጥር የሚደረግባቸው የኬሚካልነት
ባህሪ ያላቸው ዕቃዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ዕቃዎችን በተመለከተ የሚፈጠሩ ስጋቶች በዶክመንት ምርመራ
ማስተናገድ የሚቻል በመሆኑ እንዲሁም ስጋቱን ለተጓዳኝ መ/ቤቶች በማስተላለፍ በእነሱ በኩል ቁጥጥር
መደረጉን እያረጋገጡ ለማስተናገድ በማሰብ በሲስተም በመካከለኛ ስጋት ደረጃዎች ላይ እንዲመደቡ
ይደረጋል፡፡

የራንደም መረጣ/Random Selection/

የስጋት ስራ አመራር የራንደም መረጣን አዳዲስ ስጋቶችን በመለየት እንዲስተናገዱ ለማድረግ ስለሚያግዝ
እንደ አንድ የስጋት መምረጫ ምስፈርት ይጠቀማል፡፡ በዚህም ምክንያት በየቀኑ በዝቅተኛ እና መካከለኛ
የስጋት ደረጃዎች ከሚስተናገዱ ሰነዶች መካከል አምስት በመቶ በሲስተም በከፍተኛ የስጋት ደረጃ
እንዲስተናገዱ ያደርጋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የራንደም መረጣ የስጋት መምረጫ መስፈርቶች እና የስጋት
ደረጃዎች ተገማች /predictable/ ሆነው ያልተፈለጉ አሉታዎ ተፅዕኖዎች እንዳይፈጠሩ ለማድረግ
ይጠቅማሉ፡፡

የቅ/ጽ/ቤቶች የስጋት ስራ አመራር ቡድን ዋና ዋና ተግባራት


የጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤቶች ስጋት ስራ አመራር በሲስተም የሚጣሉ የስጋት ደረጃዎች በመከታተል ከቅ/ጽ/ቤቱ
አንጻር የሚፈጠሩ ስጋቶችን ከማስተናገድ በተጨማሪ በተለያዩ ምክንያቶች በሲስተም የስጋት ደረጃዎች
መጣል በማይችሉበት ወቅት በማኑዋል የስጋት ደረጃዎችን እየጣሉ የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት
የተቋቋመ ነው፡፡ በተጨማሪ የሚከተሉትን ተግባራት ያከናውናሉ፡-
 በአሲኩዳ ሰሌክቲቪቲ ሲስተም መሰረት የሚጣሉ ስጋቶችን በቅ/ጽ/ቤቶች ክትትል እና ቁጥጥር
በማድረግ እና በማረጋገጥ ማሰተናገድ እና ግብረ መልስ ለዋናው መ/ቤት መስጠት ፣
 የሲስተም መቆራረጥ እና የስጋት ደረጃ መሻሻያ አስፈላጊ በሆነበት ጊዜ ሁሉ በሲስተም የተጣሉ
ስጋቶች ላይ ማሻሻያ በማድረግ የስጋት ደረጃዎችን በማሻሻል በማኑዋል ማስተናገድ ፣

45 ምንጮች /Reference |
 አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን በተዘጋጁ ሲስተሞች ወይም በማኑዋል መያዝና መጠቀም ለዋናው
መ/ቤትም ማስተላለፍ ፣
 በቅ/ጽቤቱ ዙሪያ ያሉ አዳዲስ ስጋቶችን መለየት፣መተንተን እና ማስተናገድ ለዋናው መ/ቤትም
ማስተላለፍ ፣
 በየጊዜው ሪፖርት ለሚመለከታቸው ክፍሎች እና ለዋናው መ/ቤት ማቅረብ ፣
 የስጋት ስራ አመራር ውጤታማነትን መገምገም እና ግብረ መልስ መስጠት ፣
 የቅ/ጽ/ቤቱን ግብር ከፋዮች በሴክተር እና በደረጃ በመከፋፈል የህግ ተገዥነት ደረጃቸውን ማጥናት
ወይም መለየት የህግ ተገዥነት ደረጃን የሚያሳይ የታማኝነት ባህሪ ደረጃ የሚያሳይ ፒራሚድ
ማዘጋጀት፣
 በህግ ተገዥነት / በታማኝነት ደረጃቸው አይነት ሊተገበሩ የሚገባቸውን የመስተንግዶ ስትራቴጂዎች
መንደፍ ስትራቴጂዎችን አቅዶ ከሚመለከታቸው ክፍሎች ጋር በመተባበር መተግበር ፣
 ለህግ ተገዥ መሆን ለማይፈልገውን እና የከፋውን በመለየት ለቅ/ጽ/ቤቱ ኢንተለጀንስ ክፍል እና
ለዋናው መ/ቤት ማስተላለፍ አስፈላጊው ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድበት ማድረግ ፣
 እንዲሁም ዝቅተኛ የስጋት ደረጃ ላይ ያሉ ግብር ከፋዮችን መደገፍ ቀላልና ቀልጣፋ መስተንግዶ
እንዲያገኙ ማድረግ ፣ እውቅና እንዲሰጥ ለሚመለከተው አካል ማሳወቅ ፣
 TPRDP ላይ የሚገቡ መረጃዎች በሁሉም ክፍሎች በአግባቡ እና በሚፈለገው ጥራት መግባታቸውን
በመከታተል ስለአፈጻጸሙ ለዋናው መ/ቤት ሪፖርት ማድረግ

በአሁኑ ወቅት ከገቢ ዕቃዎች ጉምሩክ ስነ-ስርዓት አፈጻጸም በስተቀር ሌሎቹ ማለትም ትራንዚት ቁጥጥር፣
ወጪ ዕቃዎች፣ መንገደኞች እና የመጋዘንን ቁጥጥር በሲስተም የታገዘ የስጋት ስራ አመራር ባለመኖሩ የማኑዋል
አሰራር መተግበር አስፈላጊ ሆኗል፡፡ በማኑዋል የሚጣሉ የስጋት ደረጃዎች አሰራር እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

የገቢናወጪ ዕቃዎች ትራንዚት የስጋት መምረጫ መስፈርቶች


የገቢ ትራንዚት

የገቢ ዕቃዎች ትራንዚት ላይ የሚደረግ ቁጥጥር ዘመናዊ፣ ቀልጣፋ እና በተመረጠ ሁኔታ በማይሆንበት ጊዜ
ያልተፈለገ የጊዜ እና የሀብት ብክነት በማስከተል ሀገርን ይጎዳል፡፡ ቁጥጥሩን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለማረጋገጥ
በስጋት ስራ አመራር መሰረት ተግባራዊ ለማድረግ ያስፈልጋል፡፡ በትራንዚት ላይ ላሉ ዕቃዎች ስጋት ለመጣል
ከታች የተገለጹት የስጋቶች መምረጫ መስፈርቶች ያስፈልጋሉ

ሀ) የከፍተኛ (ብርቱካናማ) ስጋት ደረጃ አመላካች፤

46 ምንጮች /Reference |
 ከኢተለጀንስና ከተለያዩ አካላት ጥቆማ የሚቀርብባቸው፤
 የተረጋጋ የፖለቲካ ስርዓት ከሌላቸው ሀገራት የተመረቱ ወይም የተጫኑ
 በአደንዛዝ ዕጽዝውውር ከታወቁ ሀገራት የተጫኑ ከሆነ
 በመንገድ ወረቀቱ ላይ ጨረር አመንጪ ዕቃዎች የተገለጹ ከሆኑ፤
 በመንገድ ወረቀቱ (T1) ላይ ሪማርክ የተፃፈ ከሆነ፤
 ኤክሳይዝ ታክስ የተጣለባቸው ዕቃዎች ሲመጡ
 ዕቃዎች ካላቸው ባህሪ አንጻር የማጭበርበር ድርጊት የሚፈጸምባቸው በየወሩ በፍተሻ እና ሰነድ
ምርምራ ሪፖርት የቀረበባቸው፤ /ከ TPRDP ወይም ከሌሎች በሲስተም ወይም በማኑዋል
ከሚገኙ መረጃዎች/፤
 ሶስት እና ከዚያ በላይ የከባድ ጥፋት ሪከርድ ባለባቸው የጉምሩክ ስነ-ስርዓት አስፈጻሚዎች
የሚስተናገዱ ሰነዶች፤ /ከ TPRDP ወይም ከሌሎች በሲስተም ወይም በማኑዋል ከሚገኙ
መረጃዎች/፤
 የልዩ የጉምሩክ አገልግሎት ተጠቃሚዎች እና የታማኝ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሾች (AEO) ዕቃዎች
ከሌሎች ጭነቶች ጋር ተቀላቅለው ሲመጡ፤
 በሚያዙ የጥፋት መረጃ መሰረት በተደጋጋሚ የአገላለጽና የትርፍ ልዩነት የሚገኝባቸው ድርጅቶች
ሲያስመጡ፤ ወይም በተደጋጋሚ የሰነድ ምርመራ፣ የፍተሻ እና የድህረ ዕቃ አወጣጥ ግኝት
የሚገኝባቸው አስመጭዎች የሚያስመጧቸው ዕቃዎች፤ (ከ TPRDP ወይም ከሌሎች በሲስተም
ወይም በማኑዋል በተያዙ መረጃዎች መሰረት)፤
 ከጭነቱ ጋር የማይሄድ የተጋነነ ትራንስፖርት ወጪ፤ (ከዕቃው ጋር ተመጣጣኝ ያልሆኑ
የትራንስፖርት ክፍያዎች መኖሩ ሲረጋገጥ)፤
 ተሽከርካሪው ከሚጠበቅበት ጊዜ በላይ ዘግይቶ ሲደርስና አሳማኝ ምክንያት ካልቀረበ፤
 መኪናው በተነሳበት ሁኔታ የደረሰ ካልሆነና አጠራጣሪ ሁኔታ ሲኖር (ሲሉ የተበጠሰ ከሆነ)
 የንግድ እቃዎች በብትን ጭነቶች ሲመጡ፤
 የሲል ቁጥር ልዩነት ሲኖር፤
 በክፍልፋይ የሚጓጓዙ ጭኖቶች፤

ለ) የዝቅተኛ (ነጭ) ስጋት ደረጃ አመላካች፤

 ትላልቅ ወይም ግዙፍ እቃዎች ሆነው በአይን በማየት ብቻ የሚለዩ (የፋብሪካና የፕሮጀክት
ማሽነሪዎች እና ዕቃዎች)፣
 በመንግስታዊና በመንግስት የልማት ድርጅቶች የሚገቡ ዕቃዎች፣

47 ምንጮች /Reference |
 በትምህርት ተቋማት የሚገቡ የትምህርት መገልገያ መሳርያዎች፤
 በታማኝ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሾች (AEO) የሚገቡ ዕቃዎች፣
 በቬና ኮንቬንሽን እና በሌሎች ስምምነቶች መሰረት ያለመፈተሸ መብት የተሰጣቸው
ሲያስመጡ፣
 በጉምሩክ ልዩ አገልግሎት ተጣቃሚ የሆኑ አምራች ድርጅቶች የሚገቡ፣
 ክፈት ጭነቶች ሲመጡ በማየት ብቻ ማለፍ የሚችሉ ከሆነ፤

የወጪ ትራንዚት

በወጪ ዕቃዎች ላይየሚደረግ ቁጥጥር ስጋትን መሰረት ያደረገ ሆኖ ቁጥጥርና የተቀላጠፈ አገልግሎት አሰጣጡ ሚዛናዊ የሆነ
እንዲሆን ስጋት ስራ አመራር ጠቃሚ ነው፡፡ በተጨማሪ ሀገሪቱ ወደ ውጭ የምትልካቸው ምርቶች ጥራታቸውን ጠብቀው
እንዲወጡ ይረዳል፡፡ ወጪ ዕቃዎች ላይ በማኑዋል ስጋት ለመጣል ከታች የተገለጹት የስጋቶች መምረጫ መስፈርቶች
ያስፈልጋሉ፡፡

ሀ)የዝቅተኛ የስጋት ደረጃ አመላካች፤

 ልዩ መብት ተጠቃሚ አምራች ድርጅቶች የሚልኩዋቸው ዕቃዎች፤


 ታማኝ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ ድርቶች የሚልኳቸው ዕቃዎች፤
 መንግስታዊ እና የመንግሰት የልማት ድርጅቶች የሚልኳቸው ዕቃዎች፤
 አለማቀፍና አህጉር አቀፍ ድርጅቶች፣ ኤምባሲዎች እና ዲፕሎማቶች የሚልኳቸው ዕቃዎች(
ለምሳሌ ተመላሾች)፤

ለ) የመካከለኛ ስጋት ደረጃ አመላካች፤

 የቁም እንስሳት፣
 ጫት፣ቡና፣አበባ፣የቅባት እህሎች፣ ቅመማ ቅመሞች፣
 ቆዳ፣
 ሌሎች የተጓዳኝ መ/ቤቶች ፈቃድ የሚጠየቅባቸው ዕቃዎች፣

ሐ) የከፍተኛ የስጋት ደረጃ አመላካች፤

 ለጥገና ወደ ውጭ የሚላኩ ዕቃዎች፤


 በጊዜያዊነት ገብተው የነበሩት ዕቃዎች ሲመለሱ፤
 ታማኝ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ ድርጅቶች የሚልኳቸው ዕቃዎች አልፎ አልፎ(አምስት በመቶ
እየታዬ)፤
48 ምንጮች /Reference |
 የልዩ የጉምሩክ አገልግሎት ተጠቃሚዎች የሚልኳቸው ዕቃዎች አልፎ አልፎ (አምስት በመቶ
እየታየ)፤
 በተለያዩ ምክንያቶች ወደ መጡበት ሀገር እንዲመለሱ የሚደረጉ ዕቃዎች፤
 ኤክስፖርት በሚያደርጉበት ጊዜ በተደጋጋሚ የፍተሻ ልዩነት በሚገኝባቸው ላኪዎች፤
 ከሶስተኛ ወገን መረጃ ሲገኝ፤
 ከሰነድ መርማሪ ወይም ከተለያዩ የስራ ክፍሎች ዕቃው እንዲፈተሽ ጥያቄ ሲቀርብ፤

የገቢ መንገደኞች ስጋት መምረጫ መስፈርቶች


ወደ አገር በሚገቡ እና በአገሪቱ ውስጥ በሚደረጉበረራዎች የመንገደኞች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ
በመምጣቱ የስጋት ሥራ አመራርን በመንገደኞች እና በዕቃዎች ላይ ተግባራዊ በማድረግ ትኩረቱን በከፍተኛ
የሥጋት ቦታዎች ላይ በማዋል አሰራሩን ዘመናዊ ለማድረግ ያስችላል፡፡ በጉምሩክ አዋጅ 859 አንቀጽ 30 ንዑስ
አንቀጽ 3 ወደ አገር ውስጥ የገባ መንገደኛ ከሚከተሉት የማለፊያ መስመሮች አንዱን መርጦ በማለፍ
ዲክላራሲዮን እንዲያቀርብ ሊፈቀድለት እንደሚችል፤

ሀ) በዋጋ ወይም በብዛት ቀረጥና ታክስ ከማይከፈልበት መጠን በላይ ያልሆኑ


ወይም ክልከላ ወይም ገደብ ያልተደረገባቸውን ዕቃዎች የያዙ መንገደኞች
እንዲጠቀሙበት በአረንጓዴ ምልክት የተለየውን የማለፊያ መስመር፤ ወይም

ለ) በዋጋ ወይም በብዛት ቀረጥና ታክስ ከማይከፈልበት መጠን በላይ የሆኑ ወይም
ክልከላ ወይም ገደብ የተደረገባቸውን ዕቃዎች የያዙ መንገደኞች
እንዲጠቀሙበት በቀይ ምልክት የተለየውን የማለፊያ መስመር፡፡

በመደንገግ በራስ ተነሻሽነት የሕግ ተገዢ እንዲሆኑ የሚያደርግ መስመር እንዲፈጠር አድርጓል፡፡ ነገርግን
በተመረጠ ሁኔታ ስጋት መሰረት አድርጎ በአረንጓዴ ምልክት ከሚያልፉት መካከል ቁጥጥር ለማድረግ
የስጋት መምረጫ መስፈርቶች አስፈላጊ ናቸው፡፡ በዛው አዋጅ ንዑስ አንቀጽ 3 ባለሥልጣኑ
በመንገደኞች ላይ የሚፈጸመውን የጉምሩክ ቁጥጥርና የያዟቸውን ዕቃዎች የመልቀቅ ተግባር
ለማቀላጠፍ አግባብ ካላቸው ሌሎች አካላት ጋር በመተባበር ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁና
በቅድሚያ ሊገኙ የሚችሉ የተሳፋሪዎች መረጃዎች ካሉ እነዚህኑ ሊጠቀም ይችላል፡፡ በመሆኑም
የመንገደኞች ቅድመ መረጃ በመጠቀም እንዲሁም ከታች የተገለጹትን የስጋት መምረጫ መስፈርቶችን
መሰረት በማድረግ ሥጋትን መጣል ይቻላል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ባለሥልጣን መ/ቤቱ የመንገደኞችን

49 ምንጮች /Reference |
የሥጋት ደረጃ ለመወሰን መመሪያ ቁጥር 96/2006 አውጥቶ ተግባራዊ ያደረገ ሲሆን የሚከተሉትን
መስፈርቶች ይጠቀማል፡፡

ሀ)የዝቅተኛ የስጋት ደረጃ አመላካች፤

 በዝቅተኛ ስጋት ደረጃ ላይ ከተመደቡ ሀገራት ለጉብኝት፤ ለአለምአቀፍና አህጉር አቀፍ


ስብሰባዎች ወይም ለኮንፈረስ የሚመጡ፤
 ለነጻ ህክምና አገልግሎት፤ ለሰብአዊ እርዳታ እና የትምህርት አገልግሎት ለመስጠት
የሚመጡ፤
 ዲፕሎማቲክ መብት ያላቸው መንገደኞች፤
 ለጥናትና ምርምር የሚመጡ መንገደኞች፤
 በመንግስታዊ እና በግል ተቋማት ለተለያዩ አገልግሎቶች ተጋብዘው የሚመጡ መንገደኞች፤
 ተመላሽ አትዮጵያውያን፤
 ለመጀመርያ ጊዜ የሚመጡ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ-ኢትዮጵያውያን፤
 የመንግስትና የግል ተቋማት ሰራተኞችና ሃላፊዎች ስልጠና፤ ኮንፈረንስ፤ ዎርክሾፖች ወይም
ሴሚናሮች ተሳትፈው የሚመለሱ፤
 በኢትዮጵያ በኩል ወደሌሎች ሀገሮች ትራንዚት የሚያደርጉ ሆነው ለአጭር ጊዜ የሚቆዩና
ከኤርፖርቶች የማይወጡ ሲሆን፤ (በሀገር ውስጥ ቆይታ የሚያደርጉትን ሳይጨምር)፤

ለ) የከፍተኛ (ቀይ)የስጋት ደረጃ አመላካች፤

 የጉዞው ዓላማ ለንግድ ከሆነ፤


 የማንኛውንም ድርጅት ዕቃ ይዘው የሚመጡ መንገዶኞች (ከድፕሎማቶች ውጭ)፤

50 ምንጮች /Reference |
 ተመላላሽ መንገደኛ(በሦስት ወር አንድ ጊዜና ከዛ በላይ) በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ውጭ
ሀገር ወይም በሀገር ውስጥ የሚመላለስ፤
 ከዚህ በፊት ሪኮርድ የተያዘበት መንገደኛ፤
 የጉዞው መነሻ ሀገራት ከከፍተኛ ስጋት ደረጃ ያላቸው ሀገራት ሲሆን፤
 የተቆጣጣሪ መ/ቤቶች ፈቃድ የሚጠይቅ ዕቃ የያዘ መንገደኛ፤
 ለኤግዚቪሽን ጉዳይ ምርትና አገልግሎት ለማስተዋወቅ እና ለማዘጋጀት የሚመጡ፤
 በግል ጉዳይ ከሀገር ወጥተው የሚመለሱ፤
 ከፍተኛ የስጋት ደረጃ ካላቸው ሀገሮች ተላልፈው (through transit) የሚመጡ፤
 በዝቅተኛ ስጋት ደረጃ እንዲስተናገዱ የተዘረዘሩት ዲፕሎማቲክ መብት ካላቸው መንገደኞች
ውጪ አምስት በመቶ በራንደም መረጣ፤
 የመንገደኛው የትውልድ ሃገር በከፍተኛ ስጋት ደረጃ የሚመደብ ሲሆን
 የመንገደኛው የተለየና ያልተለመደ አካለዊ እንቅስቃሴ ሲያሳይ (ለምሳል መነጫነጭ፤
ያልተለመደ ላብ፤ ቅብጥብጥነት፤ ሚዛን ጠብቆ ያለመሄድ ወዘተ)
 ከሦስተኛ ወገን መረጃ ሲገኝ፤
 መንገደኞች ይዘውት የሚመጡት ጥቅል ከሚመጡበት ዓላማ አንጻር ብዛት ሲኖረው
(ለምሳሌ ለትምህርት ወይም ለስብሰባ ሄዶ ሲመለስ ብዛት ያላቸው ሻንጣዎች
ሲይዝ/ስትይዝ)፤
 በኢትዮጵያ በኩል ወደሌሎች ሀገሮች ትራንዚት የሚያደርጉ መንገደኞች ሆኖው በሀገር
ውስጥ ቆይታ የሚያደርጉ ሲሆን፤
 መንገደኛች ይዘዋቸው በሚመጡ ዕቃዎች ላይ የጥርጣሬ ሪማርክ የተደረገበት፣ ከኢንተለጀንስ
እና ከሌሎች አካለት የጥርጣሬ መረጃ የቀረበበት ሲሆን

51 ምንጮች /Reference |
ማጠቃለያ
የስጋት ስራ አመራር ስጋቶችን በሳይንቲፊክ ዘዴ የምንለይበት፣ የምንተነትንበት፣ የምናስተናግድበት እና የምንገመግምበት
ምርጥ የስራ አመራር ጥበብ ሲሆን በዚህም ዕድሎች የሚለዩበት ሊፈጠሩ የሚችሉ ኪሣራዎች የምንቀንስበት ወይም
የምናስወግድበት እንዲሁም በአለን ውስን ሀብት ውጤታማ ውሳኔ እንድንወስን የሚረዳን የማኔጅመንት ጥበብ ነው፡፡
የስጋት ስራ አመራር ስርዓት በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን እንደአሠራር ከተጀመረ ጥቂት ጊዜያትን ያስቆጠረ
ቢሆንም ከጊዜ ወደ ጊዜ ለውጦችን እያመጣ ይገኛል፡፡ ይህም የስጋት ደረጃዎችን ለመጣል የሚያስችሉ መረጃዎች
ከቅ/ጽ/ቤቶች እየተሰበሰቡ እና በማዕከል የስጋት ትንታኔና የስጋት ፕሮፋይል እየተዘጋጀ በአሰሰኩዳ ሴልክቲቪቲ ማትሪክስ
አማካኝነት ስጋት በሲስተም እንዲጣል ማድረግ ተችሏል፡፡

የስጋት መረጃዎች በራስ አቅም እና ጥረት በሲስተም የሚያዙበት አሰራር ተዘርግቶ ለስጋት ስራ አመራር ጠቃሚ የሆኑ
መረጃዎች በ Tax Payers Profile Data Base የሚያዙበት እና ለተጠቃሚዎች የሚሰራጩበት አሰራር ተፈጥራል፡፡
ከዚህ ጎን ለ ጎን በቅርብ ጊዜያት በገቢ ዕቃዎች መስተንግዶ ላይ ብቻ ሲጣል የነበረው የስጋት ስራ አመራር መሰረቱን
በማስፋት በመንገደኞችና በመንደኞች ጓዝ የጉምሩክ ስነ-ስርዓት አፈጻጸም፣ በትራንዚት ዕቃዎች ስነ-ስርዓት አፈጻጸም እና
በወጪ ዕቃዎች ስነ-ስርዓት አፈጻጸም ላይ መተግበር ተችሏል፡፡

ስጋት ስራ አመራር ለኢትዬጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሰልጣን ውጤታማ ቁጥጥር እና የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት
ምቹ ሁኔታዎችን ይፈጥራል፡፡ ባለስልጣኑም ለተገልጋይ ሕብረተሰብ ፍትሐዊ፣ ፈጣን፣ ተገማች እና አመኔታን ያተረፈ
የጉምሩክ አገልግሎት በመስጠትና የጉምሩክ ቁጥጥር በማካሄድ ረገድ የግልጽነትና ተጠያቂነት አሰራርን ለማስፈን በአዲሱ
የጉምሩክ አዋጅ የስጋት ስራ አመራር መርህን ተግብራል፡፡ ይህም የሕግ ተገዥነት በማሳደግ አገልግሎት አሰጣጡንና
የቁጥጥር ሥርዓቱን ሚዛናዊ ባደረገ ሁኔታ በሚቀመጡ መስፈርቶች መሠረት የተለያየ የሥጋት ደረጃ በማውጣት የሕግ
ተገዢ የሆኑት በዝቅተኛ የስጋት ደረጃ ላይ እየተመደቡ የተቀላጠፈ አገልግሎት የሚያገኙበት እና የሕግ ተገዢ የማይሆኑት
በከፍተኛ የስጋት ደረጃ ላይ እየተመደቡ ጠንካራ ቁጥጥር እየተደረገባቸው እንዲስተናገዱ ይደረጋል፡፡

ስጋት ትንታኔ በዋናው መ/ቤት እና በቅ/ጽ/ቤች በተለያዩ መልኩ ይከናወናል፡፡ በዋናው መ/ቤት ስጋት ስራ አመራር
የሚያከናውነው ከጉምሩክ ስነ-ስርዓት አፈፃፀም ጋር በተያያዘ ስጋቶችን በገቢ፣ ወጪና ተላላፊ ዕቃዎች እና መንገደኞች ላይ
በመለየትና በመተንተን በአገር አቀፍ ደረጃ (national) ስጋቶቹ እንዲስተናገዱ ማድረግ እና መከታተል ነው፡፡ በቅ/ጽ/ቤቶች
ስጋት ስራ አመራር በሲስተም የሚጣሉ የስጋት ደረጃዎች በመከታተል ከቅ/ጽ/ቤቱ አንጻር የሚፈጠሩ ስጋቶችን ለማስተናገድ
እንዲሁም በሲስተም የስጋት ደረጃዎች መጣል በማይቻልበት ወቅት በማኑዋል የስጋት ትንታኔ በማከናወን የስጋት

52 ምንጮች /Reference |
ደረጃዎችን ለመጣል ነው፡፡ በመጨረሻም በዋናው መ/ቤትም ሆነ በቅ/ጽ/ቤቶች የስጋት ስራ አመራር ውጤታማነት
እየተገመገመ በአፈጻጸም ወቅት ያጋጥሙ ችግሮች እና አዳዲስ ስጋቶች እንዲስተናገዱ ማሻሻያዎች ይደረጋሉ፡፡

ምንጮች /Reference
 Awustralia Tax Office, Developing Effective Compliance Stratagey, (2009), “Guide for
Compliance Officers”
 COSO (2004) “Guide to EnterpriseRisk Management Frequently asked Question”
 Plain English ISO 31000 (2009)“Risk Management Dictionary”
 The Organisation for Economic Co-operation and Development (OECD) document on
Compliance Risk Management,(2004) “Managing and Improving Tax Compliance”

53 ምንጮች /Reference |
 WCO Safe Frame Work of Standards, (2012), ‘Secures and Facilitate Global Trade’.
 World Customs Organization, (2003), “Risk Management Guide”.
 በ IMF የተዘጋጀ የስጋት ስራ አመራር ረቂቅ ማኑዋል
 የስጋት ስራ አመራር ፖሊሲ እና እስትራቴጂ
 የታክስ ሕግ ተገዥነት ስጋት ስራ አመራር የስራ መዘርዝር እና ማኑዋል
 የኢትዮጵያ ገ/ጉ/ባለስልጣን የጉምሩክ አዋጅ 589/2007 ዓ.ም

54 ምንጮች /Reference |

You might also like