Professional Documents
Culture Documents
2014
2014
መግቢያ
0
የአዲስ ሚዲያ ኔቶርክ የመዝናኛ ፕሮግራሞችና ስፖርት ክፍል አዝናኝና አስተማሪ ፕሮግራሞችን ዕለት
ከዕለት በማዘጋጀት ለአድማጭ ተመልካች ማቅረቡ ይታወቃል፡፡ በተለይም በተለያዩ ጊዜያት የሚከበሩ
ሀይማኖታዊና ህዝባዊ በዓላትን መሰረት በማድረግ በአራቱም የሀገራችን አቅጣጫዎች በመዘዋወር የተለያዩ
ባህሎችን በማስተዋወቅና በማስቃኘት አዝናኝና አስተማሪ ፕሮግራሞችን በዶክመንተሪ በሪያሊቲ ሾው እና
መድረክ በማዘጋጀት ለህበረተሰቡ እያደረሰ የሚገኝ ሲሆን በዚህም ገንቢ የሆነ ግብረ መልሶችን እያገኘ ይገኛል፡፡
በመሆኑም የ 2014 ዓ.ም የገና ዓልን ምክንያት በማድረግ ወደ ጌዴኦ ዞን መዳረሻውን ሊያደርግ ያሰበ ሲሆን
ለእቅዱ መሳካትም ከጌዴኦ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ጋር በመተባበር በደመቀና በአማረ
ሁኔታ ፕሮግራሙን ለማቅረብ ቅድመ ዝግጅቶች በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
በመሆኑም የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ የመዝናኛ ፕሮግራሞችና ስፖርት ክፍል ለተመልካች እንዲደርሱ
የሚፈለጉ መልዕክቶችን በመቅረጽ ገና ልዩ የበዓል ዝግጅቱን ለማከናወን ይህንን ፕሮፖዛል አዘጋጅቶ
አቅርቧል፡፡
1
አላማ
የዚህ ፕሮፖዛል ዋንኛ አላማ የአዲስ ሚዲያ ኔቶርክ የመዝናኛ ፕሮግራሞችና ስፖርት ክፍል ከጌዴኦ ዞን
መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ጋር በመተባበር
የጌዴኦ ህዝብ በታሪኩ በሀገር ህልውና ቀልድ የማያውቅ ዳርድንበሯንም ለመጠበቅ ቀዳሚ ዘማች
ለነብሱ የማይሳሳ፣ ፈጣሪውን በተለያዩ የእምነቱ ስርዓት መሰረት ለሰላም፣ ለፍቅር፣ ለአንድነት ዘውትር
የሚማፀን እምነቱን ጠባቂ ባህሉን አክባሪ እንደመሆኑ መጠን ከፊታችን የሚመጣውን የገና በዓልም
የጌዴኦ ህዝብ የዘመን መለወጫ የሆነውን (የደራሮን) የአከባበር ሁኔታ መነሻ በማድረግ የሀገርን ሰላምና
ፀጥታ በማስጠበቅና ዳርድንበርን በማስከበሩ ዘመቻ ደጀን ለሆነው የመከላከያ ሰራዊት እየተደረጉ ያሉ
የዞኑን እንቅስቃሴዎች በማሳየት "ደግፍ፣ ጠብቅና ዝመት" በሚል መሪ ቃል የብሔረሰቡን ባህል፣ ወግ፣
ስርዓት፣ ተፈጥሯዊና ሰውሰራሽ መገለጫዎቹን ብሎም የተለያዩ ስርዓቶችን ማሳየትና ማሳወቅ የሚችሉ
ፕሮግራሞችን የሚያስቃኝ ሪያሊቲ ሾው ማዘጋጀት ነው፡፡ የጌዴኦ ዞን የበርካታ ፀጋዎች ባለቤት፣ ባለ አረንጓዴ
ወርቅ ባለቤት (ቡና)፣ መልከዓ ምድራዊ አቀማመጡ ልዩ፣ የገዳ ሥርዓቱ እንደ ዘመናዊ የፖለቲካ ድርጅት አወቃቀር
እና አደረጃጀት ያለው፣ አስደናቂ የመካነ-መቃብርና በርካታ ዝርዝር የአከባቢው መገለጫና መታወቂያ ሀብቶች ባለቤት
ሲሆን በዋናነትም የጌዴኦ አባገዳና የባህል ሽማግሌዎች ሀገር በተለያዩ ምክንያቶች ችግር ሲገጥማት ወቅታዊ ሁኔታውን
ከግምት ውስጥ ያስገቡ የተለያዩ ባህላዊ የፀሎትና የምልጃ የባሌ የገዳ ስርዓትን በመከወን አባቶች አባታዊ ግዴታዎችን
እንደሚወጡ ይታወቃል፡፡
በአሁኑም ወቅት ሀገራችን ኢትዮጵያም ከወትሮው በተለየና በጠነከረ መልኩ ሀገራዊ አንድነትን አጠናክረው
የሚቆሙ ልጆች የምትሻበት ወቅት በመሆኑ ፣ ሁሉም ከያለበት በአንድ ተሰባስቦ ከያለበት አከባቢ
መከላከያውን እንዲግፍ፣ ወደ ግንባር እንዲዘምትና አከባቢህን ነቅቶ እንዲጠብቅ መንግስት በሰጠው አደራ
መሰረት የጌዴኦ ዞንም በተለያዩ ዘርፎች ጠንክሮና ያለ አንዳች ድካም ድጋፉን አጠናክሮ በመቀጠል በስንቅ
ዝግጅቱ፣ በተለያዩ የበጎ አድራጎት ተግባራቱ በመትጋት ኢትዮጵያ ዳር ድንበሯ እንደተከበረ በልጆቿ ታፍራና
ተከብራ ትኖር ዘንድ የበኩሉን ሚና እየተወጣ መሆኑን ለማሳየት
መከላከያውን በመደገፍ፣ ወደ ግንባር በመዝመትና አከባቢያችንን በመጠበቅ ህልውናዋ ተጠብቆ በፅኑ መሰረት
ላይ የፀናች ከባንዳና በክፉ ከሚያያት ሁሉ የፀደዳች የበለፀገች ኢትዮጵያን እንፈጥራለን፡፡
2
- የጌዴኦ ብሔረሰብን የዘመን መለወጫ ስርዓት፣ ታሪክ፣ ቋንቋ፣ ባህልና የተለያዩ ሀይማኖታዊ
ስርዓቶችን የሚያስቃኝ ዘጋቢ ፊልም
- የብሄረሰቡን ባህላዊ አመጋገብ፣ አለባበስ፣ አኗኗር፣ የቤት አሰራረ ጥበብ፣ የሚያስቃኝ ሪያሊቲ ሾው
- ታሪካቸው አስተማሪ የሆኑና ድጋፍ የተደረገላቸው የዘማች ቤተሰቦችን የህይወት ገፅ የሚያስቃኝ
ፕሮግራም በፕሮዳክሽን
ቃለ መጠይቅ
- አባ-ገዳዎች
- የሀገር ሽማግሌዎች
- የዘማች ቤተሰቦች
- የዞኑ ኃላፊዎች
- ባህላዊ የምግብ ዝግጅት በቅደም ተከተል የሚያስረዱ የብሔሩ ተወላጅ እናት
- ህፃናት የአከባቢውን ባህላዊ ዜማዎችና ጨዋተዎች የሚያሳዩ
- የቱሪስት መዳረሻዎችን ገለፃ የሚያደርግ ባለሙያ
በአጠቃላይ አከባቢውን ባህል፣ ወግና ልማድ ብሎም የአባቶች ስርዓት የሚያስቃኙ ርዕሰ ጉዳዮችን የሰነቁ
ዝግጅቶች ይቀርባሉ፡፡
ፕሮግራሙ የሚከናወንበት ቦታ እና ቀን
- ታህሳስ 29/04/14 (ዝግጅቱ ቀደም ብሎ የሚቀረጽ ሲሆን የገና ዕለት ለህዝብ የሚቀርብ ነው)
የቀረፃ ዝግጅት
3
- ለፕሮዳክሽን ዝግጅቱ የሚያስፈልጉትን ዝርዝር ሁኔታዎች ይለያል
- ይህ ምክረ ሃሳብ በዞኑ ተቀባይነት እንዳገኘ የካሜራ ባለሙያ፣ ጋዜጠኛና መኪና ይመድባል
- ባህላዊ ስርዓቶች ሳይበረዙና ሳይከለሱ በተገቢው ጥንቃቄ በመቅረፅ ፕሮግራሙን አየር ላይ
ያውላል፤ (የአየር ሰዓት ያለክፍያ ይሰጣል)
- ዝግጅቱን አስመልክቶ ቀድሞ የፕሮሞሽን ስራ ይሰራል፤
- የቅንጅት ችግር
- የጊዜ እጥረት
የመፍትሄ ሀሳብ
ማጠቃለያ
4
ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ህዝቦች ለዘመናት አብሮነታቸው አንዱ ከሌላው ጋር ያላቸው በጎ መስተጋብር
የማይካድ ሀቅ ሲሆን ሀገርም የበርካታ ብሄር ብሄረሰቦች ድምቀት መታያ ነች፡፡
የጌዴኦ ህዝብም በታሪኩ በሀገር ህልውና ቀልድ የማያውቅ ዳርድንበሯንም ለመጠበቅ ቀዳሚ ዘማች
ለነብሱ የማይሳሳ፣ ፈጣሪውን በተለያዩ የእምነቱ ስርዓት መሰረት ለሰላም፣ ለፍቅር፣ ለአንድነት ዘውትር
የሚማፀን እምነቱን ጠባቂ ባህሉን አክባሪ እንደመሆኑ መጠን ከፊታችን የሚመጣውን የገና በዓልም
የጌዴኦ ህዝብ የዘመን መለወጫ የሆነውን (የደራሮን) የአከባበር ሁኔታ መነሻ በማድረግ የሀገርን ሰላምና
ፀጥታ በማስጠበቅና ዳርድንበርን በማስከበሩ ዘመቻ ደጀን ለሆነው የመከላከያ ሰራዊት እየተደረጉ ያሉ
የዞኑን እንቅስቃሴዎች በማሳየት "ደግፍ፣ ጠብቅና ዝመት" በሚል መሪ ቃል የደመቀና የተወደደ
ብሎም አስተማሪ ፕሮግራሞችን ለማዘጋጀት ታቅዶ የተዘጋጀ ምክረ ሃሳብ ሲሆን ለእቅዳችን መሳካትና
ለፕሮግራሙ ስኬት ሁሉም አካል በመተባበር ለበአሉ ዝግጅት የድርሻውን ሊወጣ ይገባል፡፡