Download as docx, pdf, or txt
Download as docx, pdf, or txt
You are on page 1of 6

የተሽከርካሪ ቴክኒክ ብቃት አፈታተሽ

አሽከርካሪዎች በጉዞ ላይ እና ከጉዞ በኋላ የተሽከርካሪውን ደህንነት ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡ አሽከርካሪዎች


የተሽከርካሪያቸውን የቴክኒክ ሁኔታ ዘወትር በመከታተላቸው የሚከተሉትን ውጤት ማግኘት ይረዳቸዋል፡-
 በብልሽት ምክንያት ጉዞው እንዳይስተጓጎል
 አላስፈላጊ ገንዘብ፣ የጊዜ እና የጉልበት ወጪን መቆጠብ
 በቴክኒክ ብልሽት ምክንያት ሊደርስ የሚችለውን አደጋ መከላከል
 የተሳፊሪዎችን ምቾት እና የንብረታቸውን ደህንነት መጠበቅ
 በአስቸጋሪ ሁኔታ እና ቦታ በብልሽት ምክንያት ተሽከርካሪው እንዳይቆም
የእይታ ምርመራ ማከናወን
አንድ ተሽከርካሪ ከተለያዩ ተንቀሳቃሽ እና የማይንቀሳቀሱ ክፍሎች የተዋቀረ ሲሆን አሽከርካሪዎች በቀላል
ጉዳት ሊያደርሱ የሚችሉ የተሽከርካሪ ክፍሎች ላይ በየጊዜው ፍተሻ በማዴረግ ብልሽትን የመከላከል ተግባር
ማከናወን አስፈሊጊ ነው፡፡ የተሽከርካሪ ክፍሎች ወቅታዊ የሆነ ጥገና ወይም ሰርቪስ በተገቢ ሁኔታ ማድረግ
በአሽከርካሪ ሰርቪስ የሚደረጉ የተሽከርካሪ ክፍልች
 የሞተር ማቀዝቀዣ ውሃ መቀየር፡- የሞተር ውሃ በተሽከርካሪ ክፍሎች ዝገት መፍጠር እና በተለያዩ
ምክንያት ሊቆሽሽ ይችላል፡፡ ስለሆነም አሽከርካሪዎች ሞተር ቀዝቃዛ በሆነበት ጊዜ የውሃ ማፍሰሻ
ክፍልን በመፍታት መቆሸሹን ካረጋገጡ በኋላ ሙለ በሙሉ በማፍሰስ በሌላ ንፁህ ውሃ መተካት
/መሙለላት/ ይገባል፡፡
 የሞተር ዘይት መቀየር፡- የሞተር ዘይት እንደተሽከርካሪ የፈረስ ጉልበት የሚጠቀምበት የዘይት ደረጃ
እና መጠን የሚለያይ በመሆኑ የዘይት ዓይነት፣ መጠንና የሰርቪስ ማድረጊያ ጊዜ በአምራች ድርጅት
የሚወሰን ነው፡፡ አሽከርካሪው የሞተር ዘይት መቀየር ተሽከርካሪ የተጓዘውን ኪ.ሜ በማየትና
በሰርቪስ ማንዋል በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ሰርቪስ ማድረግ ይኖርበታል፡፡ ዘይት መቀየር
በሚያስፈልግበት ጊዜ ሙሉበሙለ ዘይቱ ተንጠፋጥፍ እንዲያልቅ ሞተር ለትንሽ ደቂቃ ማሰራት
የሚያስደልግ ሲሆን ሞተሩ ከጠፋ በኋላ በመቀበያ እቃ ዘይቱን በማፍሰሻ ክፍል በማፍሰስ ለተወሰነ
ሰዓት ተንጠፍጥፍ እንዲያልቅ ከተደረገ በኋላ የማፍሰሻ ፔሊግ በመዝጋት ንፁህ ዘይት መጨመር እና
ዘይቱ ትክክለኛ መጠን ሊይ ስለመሆኑ በዲፒስቲክ ወይም በሉቬሎ አማካኝነት መረጋገጥ አለበት፡፡
የሞተር ዘይት በሚቀየርበት ጊዜ አዲስ የዘይት ፊልትሮ አብሮ መቀየር ያስፈልጋል፡፡ የኃይል
አስተላላፊ ክፍሎች በውስጣቸው የተለያዩ ተንቀሳቃሽ ክፍሎች ስላላቸው ሰበቃን መቀነስ ዘይት
ይጠቅማል፡፡ ስለሆነም አንድ አሽከርካሪ በየጊዜው የዘይት መጠን ትክክለኛ ቦታ ላይ መሆኑን እና
ፈሳሽ አለመኖሩን መፈተሽ የሚያስፈልግ ሲሆን በሰርቪስ ማንዋል አማካኝነት በወቅቱ
የሚጠቀሙበትን ዘይት መቀየር ያስፈልጋል፡፡
 ደረቅ የአየር ማጣሪያ፡- ወደ ሞተር የሚገባውን አየር ከባእድ ነገር በመከላከል ንፁህ አየር ወደ
ማቀጣጠያ ስፍራ በማስገባት የአየር ማጣሪያ ክፍል ከፍተኛ ጥቅም አለው፡፡ ተሽከርካሪ ረዥም ርቀት
በተጓዘ ጊዜና በተለይ አቧራማ መንገድ ላይ በማሽከርከር ወቅት የአየር ማጣሪያ ቀዳዳዎች በቆሻሻ
ይደፈናለረ፡፡ ስሆነም ሞተር በቀዝቃዛና በጠፋበት ወቅት የአየር ማጣሪያ ክፍል በመፍታት በውስጡ
የሚገኘው ወንፊት ግፊት በሆነው ንፋስ ከውስጥ ወደ ውጪ ማጽዳት ያስፈልጋል፡፡ ሆኖም የአየር
ማጣሪያ በሰርቪስ በማንዋለ መሰረት የአገግልግት ጊዜው ካበቃ ወይም ያለ ወቅቱ በጣም ከቆሸሸና
ከተበላሸ በሌላ አዲስ መተካት ያስፈልጋል፡፡
 እርጥብ የአየር ማጣሪያ፡- ይህ የአየር ማጣሪያ በውስጡ ከሽቦ የተሰራ ወንፊት የሚመስል ነገር
ሲኖረው አብዛኛውን ጊዜ የሞተር ዘይት የሚጠቀም ነው፡፡ አሽከርካሪዎች በሰርቪስ ወቅት
ማጣሪያውን በመፍታትና በማጠብ ሙለ በሙለ ከቆሻሻ ከፀዳ በኋላ ዘይት በመጨመር በትክክል
መግጠም አለባቸው፡፡
የኤሌክትሪክ መስመሮች አፈታተሽ
በኤሌክትሪክ ክፍሎች ላይ ሊደርስ የሚችለውን ብልሽት በመከላከል በተሽከርካሪ የተለያዩ የኤሌክትሪክ እና
የመብራት ክፍሎች ላይ ፍተሻ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ በኤሌክትሪክ ክፍሎች ላይ የሚደርሰው ጉዳት ከፍተኛ
ሊሆን ስለሚችል አሽከርካሪዎች በየጊዜው ያለበትን ሁኔታ በመፈተሸ እና ማስተካከያ ስራ በማከናወን
ብልሽትን መከላከል ይኖርባቸዋል፡፡ ስለሆነም በመብራት ክፍሎች፣ ባትሪ መሙያ ክፍሎች፣ በሞተር ማስነሻ
ክፍሎች እና እንዲሁም በማቀጣጠያ ክፍሎች የሚገኙትን የኤሌክትሪክ ክፍሎች አለመላጣቸውን፣
አለመላቀቃቸውን አለመላላታቸውን ማየት ያስፈልጋል፡፡
1. የባትሪ ጫፎች፡- በየጊዜው ማጽዳት እና በጣም አለመጥበቃቸውን አመላላታቸውን በማየት በአግባቡ
ንፅህናውን መጠበቅ እና ማሰር ያስፈልጋል፡፡
2. የመብራት ክፌልች፡- የመብራት ብርጭቆዎች ማፅዳት እና አምፖሎቹ አለመቃጠላቸውን ማየት
እንዲሁም የኤሌክትሪክ ገመዴ ጫፍቹ አለመላላታቸውን መፈተሽ እና መብራቶች ሙለ በሙለ
መስራታቸውን ማረጋገጥ፡፡
3. የሞተር ማስነሻ ክፍሎች፡- የሞተር ማስነሻ ክፍሎች ላይ የሚገኙ የኤሌክትሪክ መስመሮች ማለትም
የዲናሞ፣ የስታርተር ሞተር /ሞቶሪኖ/ እና እንዲሁም የሞተር ማስነሻ ቁልፍን የሚያገናኙ ገመዶች
አለመላጣቸውንና አለመበጠሳቸውን አለመላላታቸውንና ሙቀት ካለው ክፍል አለመጠጋታቸውን
መፈተሸ ያስፈልጋል፡፡
4. ፉውዝ ቦርዴ፡- የኤሌክትሪክ ክፍሎች ላይ የሚደርሰውን አደጋ ለመከላከል እንቻል የተሰራ ሲሆን
ለእያንዳቸው የኤሌክትሪክ ክፍሎች ተመጣጣኝ የአምፒር መጠን ባላቸው ፊውዞች እንዲገናኙ
የተደረጉ ናቸው፡፡ ስለሆነም የኤሌክትሪክ ፊውዝ ቦርድ በትክክለኛው ቦታ ላይ መቀመጡንና በውስጡ
የሚገኙ የተለያዩ መጠን ያላቸው ፊውዞች ከቦታቸው አለመላቀቃቸውን ፍተሻ ማድረግ ይገባል፡፡
ስለሆነም እነዚህ ክፊሎች በኤሌክትሪክ ክፍሎች ላይ የሚደርሰውን አደጋ ለመከላከል ሊበላሹ
ስለሚችሉ አሽከርካሪዎች በጉዟቸው ወቅት ተጠባባቂ ፉውዝ መያዝ የሚገባቸው ሲሆን የተበላሸውን
ፊውዝ ሲቀይሩ በተመሳሳይ አምፒር መሆን ይኖርበታል፡፡
ባ.መ.ዘ.ዉ.ን.ነ. / BLOWAF / ምርመራ
አሽከርካሪው ፍተሻ በሚያደርግበት ወቅት ትኩረት ሊሰጥባቸው ከሚገቡ ክፍሎች መካከል ዋና ዋናዎቹ
ስድስት (6) ሲሆኑ ምዕፃረ-ቃል ባ.መ.ዘ.ዉ.ን.ነ ተብለው ሲጠሩ ትርጉማቸውም እንደሚከተለው ነው፡፡
 ባ (B) - ባትሪ - (Battery)
 መ (L) - መብራት- (Light)
 ዘ (O) - ዘይት- (Oil)
 ወ (W) - ውሃ- (Water)
 ነ (F) - ነዳጅ (Fuel)

መመርመር ፡-የተሽከርካሪ ክፍሎች በሚበሹበት ወቅት እና ያልተለመዱ ባህሪ በሚያጋጥምበት ጊዜ ችግሮችን


ለመጠቆም የሚያስችለ ልዩ ልዩ መሳሪያዎች ተገጥመው የሚገኙ ሲሆን እነዚህ ክፊሎች በማንዋል መሰረት
እንዲስተካከል ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ለምሳሌ በአየር የሚሰራ ፍሬን የተገጠ ያላቸው ተሽከርካሪዎች በቂ ንፋስ
ለለመኖሩን በመብራት ወይም በድምጽ ማስጠንቀቂያ የሚሰጡ በመሆኑ አሽከርካሪዎች መብራት እስኪጠፋ
ድረስ ተሽከርካሪውን ማንቀሳቀስ የለባቸውም፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ የሞተር ዘይት ወይም ውሃ በሚቀንስበት
ወይም በሚጎድልበት ጊዜ ሞተር እንዳይነሳ የሚያደርግ ሲስተም የተገጠመላቸው ተሽከርካሪዎች አለ፡፡
በመሆኑም አሽከርካሪዎች ስለተሽከርካሪያቸው ባህሪ ወይም አሰራር በቂ ግንዛቤ ሊኖራቸው የሚገባ ሲሆን
የሚያጋጥሙ ችግሮችን እና ያልተለመደ ባህሪያትን በመመርመር ፍተሻ ማከናወን ይኖርባቸዋል፡፡
ባትሪ፡- ባትሪ የተሽከርካሪ የኤሌክትሪክ ምንጭ ሲሆን በውስጡ የተጣራ ውሃና የሰልፈሪክ አሲድ ውህድ
ይገኛል፡፡ ስሆነም አሽከርካሪዎች የባትሪ ውሃ አለመጉደልን ማየት ከመጠን ያነሰ ሆኖ ከተገኘ የተጣራ የባትሪ
ውሃ በንፁህ እቃ በመጠቀም መጨመርና ማስተካከል ይኖርባቸዋል፡፡ በተጨማሪም የባትሪ ውሃ የሚፈላ ሆኖ
ከተገኘ ለባለሙያ በማሳየት በወቅቱ ብልሽቱን እንዱስተካከል ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
መብራት፡- በተሽከርካሪ ላይ የተለያየ ዓይነት መብራቶች የሚገኙ ሲሆን በትክክል መስራታቸውን በፍተሻ
ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡ ከነዚህም ውስጥ የግንባር መብራት፣ የጎን መብራት፣ የፍሬቻ መብራት፣ እና የማቆሚያ
መብራት ወ.ዘ.ተ የሚጠቀሱ ሲሆን አሽከርካሪዎች ጉዞ ከመጀመራቸው በፊት በመፈተሸ አለመሰበራቸውን
በትክክል መስራታቸውንና አለመቆሸሻቸውን ማረጋገጥ ይኖርባቸዋል፡፡
ዘይት፡- ዘይት በተሽከርካሪ ተንቀሳቃሽ ክፍሎች፣ በሞተር፣ በኃይል አስተላላፊ ክፍሎችና በመሪ ክፍል ውስጥ
አገልግሎት ላይ የሚውል ሲሆን አገልግሎቱም ሰበቃ እንዲቀንስ በማድረግ ክፍሎች እንዳይጎዳ ያደርጋል፡፡
ስለሆነም ዘይት የሚጠቀሙ የተሽከርካሪ ክፍልች ፍተሻ በማድረግ የዘይት ፈሳሽ አለመኖሩን፣ አለመቆሸሹን
እና አለመጉደሉን እንዱሁም ከባእድ ነገር ጋር አለመቀላቀሉን ማረጋገጥ ተሸከርካሪን ከብልሽት መከላከል
ይቻላሌ፡፡
ውሃ፡- ሞተር ከሚቀዘቅዝበት መንገድች አንዱ በውሃ በመሆኑ በራድያተር ወይም በኤክስፒንሽን ታንከር
ውስጥ ያለውን የውሃ መጠን በመፈተሽ አለመጉደሉን እና አለመቆሸሹን እንዱሁም የሚያንጠባጥብ ክፍል
አለመኖሩን ማረጋገጥ ይገባል፡፡ በፍተሻ የተገኙትን ጉዴለቶች ማስተካከል የሚያስፈልግ ሲሆን ከአሽከርካሪው
አቅም በላይ የሆነውን ለባለሙያ ማሳወቅ ያስፈልጋል፡፡
አየር /ንፊስ/፡- አብዛኛዎቹ መለስተኛ እና ከባዴ ተሽከርካሪዎች ለፍሬን፣ ለፍሪሲዮንና እንዲሁም የተለያዩ
ክፍሎች አየር የሚጠቀሙ በመሆናቸው በእነዚህ ክፍሎች ላይ ፍተሻ በማድረግ ብልሽትን መከላከል
ያስፈልጋል፡፡ አሽከርካሪዎች በንፊስ ወይም በአየር የሚሰራ ፍሬን ያለው ተሽከርካሪ የሚያሽከረክሩ ከሆነ
ሞተሩን በማስነሳት በአየር ማጠራቀሚያ ጋን ውስጥ ያለውን እርጥበት አዘል አየር በማስተንፈሻ ክፍል
አማካኝነት ወደ ውጪ
ነዳጅ፡- በነዳጅ ማጠራቀሚያ ጋን (ሰልቫትዮ) ውስጥ የሚገኘው ነዳጅ ለጉዞ በቂ መሆኑን ማየት እና
የሚያንጠባጥብ ወይም የሚያፈስ ቦታ አለመኖሩን ማረጋገጥ የነዳጅ ክፍሎች በቆሻሻ እንዳይደፈኑ ወይም
እንዳይበላሹ በነዳጅ ማጠራቀሚያ ጋን ውስጥ የሚገኘውን ነዳጅ ከግማሽ በታች አለመሆኑን በነዳጅ መጠን
አመልካች ጌጅ ሁልጊዜ መከታተል፡፡

በማንዋል መሰረት የተሽከርካሪ ብልሽት እና ያልተለመደ ባህሪያት

የጌጅ ንባብ ከስታንዳርድ ጋር ማነፃፀር በዳሽ ቦርዴ ላይ የሚገኙትን የመቆጣጠሪያና ጠቋሚ መሳሪያዎች
በፍተሻ ወቅት የተገኘው ንባብ በማንዋለ ላይ ከተቀመጠው ስታንዳርድ ጋር በማነፃፀር ልዩነቱን በማወቅ
የሚስተካከልበት እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል ለምሳሌ የሞተር ውሃ መጠን በማስተካከል፣ የሞተር ዘይት
መጠን በማስተካከል፣ የሚያፈስ አየር ካለ ፌሳሹን በመዝጋት፣ የተቃጠለ ፉዮዞች ካለ በመቀየር፣ በነዳጅ ጋን
ውስጥ ያለውን የነዳጅ መጠን ሁኔታ በማየትና በማስተካከል፣ ጠቋሚ መብራቶች አለመቃጠላቸውን በማየትና
በመቀየር ሊያጠቃልል ይችላል፡፡
የፍሬን እና የመሪ ሁኔታ አፈታተሽ
ፍሬንና መሪ የተሽከርካሪ ዋና ዋና የመቆጣጠሪያ ክፍሎች በመሆናቸውና ብልሽት በሚያጋጥም ጊዜ
የሚደርሰው ጉድለት (አደጋ) ከፍተኛ ሊሆን ስለሚችል በእነዚህ ክፍሎች ላይ ዘወትር የሚከተሉትን ፍተሻዎች
ማድረግ ይገባል፡፡
የፍሬን ብቃት አፈታተሽ
 የፍሬን ንፋስ አለመጉደልን
 የፍሬን ዘይት አለመጉደልን
 የፍሬን መርገጫ ፔዳል ነፃ እንቅስቃሴ ያለው መሆኑን
 የፍሬን ሸራ አለማለቁን
 የዘይት ፈሳሽ አለመኖሩን
 የአየር /የንፋስ/ ፈሳሽ አለመኖሩን
 የእጅ ፍሬን የሚሰራ መሆኑን
 ተሽከርካሪውን በማንቀሳቀስ የእግር ፍሬን ብቃትን መፈተሸ
 የተሽከርካሪ መሪ ብቃት አፈታተሽ
 በተሽከርካሪ ላይ መሪ በሜካኒካል ወይም በዘይት ኃይል በሚታገዝ ሲስተም በሁለት መንገድ ሊሰራ
የሚችል ሲሆን ከዚህ የሚከተሉትን ፍተሻ በማድረግ ከባድ ብልሽት የመከላከል ተግባር ማከናወን
ይገባል፡፡
 በቂ የመሪ ዘይት መኖሩን ማረጋገጥ
 የሚያንጠባጥብ ወይም የሚያፈስ የዘይት መስመር አለመኖሩን መፈተሽ
 የመሪ አገናኝ ዘንጎች አለመጣመማቸውን መፈተሸ
 የመሪ መገጣጠሚያ ክፍሎች አለመስፋታቸውን መፈተሸ
 የመሪ እንቅስቃሴ አለመጠንከሩን መፈተሸ
 ተሽከርካሪን በማንቀሳቀስ የመሪን እና የፍሬን ብቃት መፈተሽ
 የፍሬን እና የመሪ ክፍሎች ተሽከርካሪ በቆመበት ብቻ ሳይሆን ተሽከርካሪውን በማንቀሳቀስ
ብቃታቸውን መፈተሽ ይገባል፡፡ ሆኖም የፍሬንና የመሪ ሁኔታ ተሽከርካሪውን በማንቀሳቀስ አደጋ
በማያስከትል ሁኔታ መፈተሸ ይኖርበታል፡፡ ስለሆነም የሚከተሉትን ቅድም ተከተል በመጠበቅ ፍሬንና
መሪን ፍተሻ ማድረግ ይቻላል፡፡
 ሜዳማና ከትራፉክ ነፃ የሆነ መንገድ መምረጥ
 በአነስተኛ ፍጥነት የፍሬን ብቃት መፈተሽ
 በመካከለኛ ፍጥነት የፍሬን ብቃት መፈተሸ
 ወደ ቀኝና ወደ ግራ በማዞር የመሪ ብቃት መፈተሽ
 መሪን በመልቀቅ ወደ አንድ አቅጣጫ የሚጎትት አለመሆኑን መፈተሽ

የኃይል አስተላላፊ እና ተሸካሚ ክፍሎች አፈታተሽ


የተሽከርካሪ ኃይል አስተላላፊ ክፍሎች ፍሪሲዮን፣ ጊርቦክ፣ ትራንስሚሲዮን ፕሮፕለርሻፍት
ዱዲፈሬንሺያል፣ አክሰሌ /ሺሚያስ/ ሲሆኑ አወቃቀራቸውና አቀማመጣቸው እንደተሽከርካሪ ሁኔታ ሊለያይ
ይችላል፡፡ በመሆኑም አሽከርካሪዎች ከላይ በተገለጹ ክፍሎች ላይ የሚከተሉትን ፍተሻዎች ማከናወን
አለባቸው፡፡
 የፍሪሲዮን ፔዳል እንቅስቃሴን መፈተሽ
 ማርሽ በቀላል የሚገባና የሚወጣ መሆኑን ማየት
 በቂ የፍሪሲዮን ዘይት መኖሩን ማየት
 ካምቢዮ፣ ሪድታና ዲፈረንሻል በቂ ዘይት መኖሩን ማረጋገጥ
 በኃይል አስተላላፊ ተሸካሚ አካል ላይ ንቅናቄ አለመኖሩን ማየት
 በማሽከርከር ወቅት ያልተለመደ ድምጽና ንቅናቄ አለመኖሩን ማረጋገጥ
 ፕሮፕለር ሻፍት ወይም ትራንስሚስዮን በቂ ግሪስ ያለው መሆኑን
 የሚያፈስ ዘይት አለመኖሩን
 የጎማ ጥርስ ማየትና ብሎኖቹ መጥበቃቸውን ማረጋገጥ
 የጎማ ንፋስ መለካትና አለመጉደሉንም መፈተሽ
ተሸካሚ ክፍሎች በወጣ ገባ መንገድ ላይ ሊገጥም የሚችለውን ንቅናቄ በማለስለስ በተሽከርካሪ ክፍሎችና
በተሽከርካሪ ጭነት ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ይከላከላል፡፡ ስለሆነም አሽከርካሪዎች በተሽከርካሪ ተሸካሚ
ክፍሎች ላይ የሚከተውን ፍተሻ ያደርጋል፡፡
 ባላስትራ አለመሰበሩን
 ጥቅል ሞላ (ኮይል ስፕሪንግ) አለመሰበሩን
 የሾክ አብዞርቨር ዘይት አለማፍሰሱን
 ብሎኖች አለመላላታቸውንና አለመጉደላቸውን
 የተሰበረ ወይም የተሰነጠቀ አለመኖሩን
 በቂ ግሪስ /ማለስለሻ/ ያላቸው መሆኑ
ማንዋል መጠቀም
ማንዋል ስንል ስለተሸከርካሪው መግለጫ የሚሰጡ መፅሀፍት ማለት ነው፡፡ ይህም ማለት

 የተሸከርካሪውን አጠቃላይ ይዘት፣ ክብደት፣ ስፋት፣ ቁመት፣ ሞዴል፣ የጭነት ልክ፣ ሲሲ፣
የሚጠቀመውን ነዳጅ፣ የመሪ ሁኔታ፣ ማርሽ..
 አንዳድ ስርዓት
 ይጥገና ቀን የሚደረግበትን ቀን
 የዳሽቦርድ ምልክቶችን የሚተነትን አሽከርካሪው በቀላሉ እንዲያውቅ ይረዳል
ማንዋሎች ን መለየት እና በትክክለኛ ቦታ መጠቀም እና በውስጡ የተጻፉትን መረዳ የትራፊክ አደጋን
ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋፅኦ አለው፡፡

You might also like