Professional Documents
Culture Documents
የ12 ዓመቷ ታዳጊ ዘውትር በእጇ ቅጠላ ቅጠልና የተለያዩ ዕቃዎች ይዛ በዚህ መንገድ
ታልፋለች:: በአካባቢው ወዳለው የቀበና ወንዝ በመውረድ መጫወት ያስደስታታል:: እናቷ ግን አይለቋትም:: ቢሆንም
እሳቸውን ተደብቃ መሔዷን አላቋረጠችም:: የአዕምሮ
ህመምተኛ ናት:: ይህቺን ልጅ አይቶ የማያዝንላት ሰው የለም:: ቀይ ቆንጆና የደስደስ ያላት ታዳጊ ናት:: የምታወራውን
ነገር አታውቀውም:: እናቷ ዘውትር እያዩዎት ያለቅሱ የነበር ቢሆንም አሁን አሁን የሆነውን በፀጋ ከመቀበል ሌላ አማራጭ
እንደሌላቸው በመገንዘባቸው ዝምታን
መርጠዋል:: ብዙ ጸበል ሞክረው አልተሳካላቸውም::
ይቺን ህፃን የሚወዳት የዚህ ሰፈር ወጣት አለ ቀበና ሰፈር 24 ዓመቱ ነው:: ዘውትር
ከረሜላ ይገዛላታል:: እሷም ትወደዋለች:: ያጫውታታል:: ሣንቲም ይሠጣታል:: ብዙ
ጊዜ ከአይኑ እንድትጠፋ አይፈልግም:: አንድ
ቀን ከመንገድ ሲመለስ ወንዝ አካባቢ ጫወታ ላይ ሳለች ከረሜላ እንደሚገዛላት
ነግሮ ይዟት ወደ ቤቱ መጣ:: በዚህ ወቅት ግን የለመደችውን ከረሜላ አልገዛላትም:: የገባውን ቃል አላከበረም:: ይልቅስ
መጥፎ
ድርጊት ተፈጠረ::
አልጋው ላይ ካስወጣት በኇላ ልብሶቿን አስወልቆ ደፈራት:: ክብረ ንፅህናዋ ተገሰሰ:: አሟታልና ጮኸች:: ከዚያን በኋላ
ግን ከኪሱ ከረሜላ አውጥቶ ሲሰጣት ረሳችው:: ከቤቱ አውጥቶ ወደ ቤቷ ሰደዳት::
ከአንድ ሰዓት በኋላ ቤቱ በሀይል ተደበደበ:: ደነገጠ:: ወጣቶች ናቸው:: አንገቱን ይዘው አወጡት:: ፖሊስ ነበር:: ይዘውት
ሄዱ:: የፈፀመውን ድርጊት አመነ:: ታዳጊዋ ቀሚሷ ላይ ደም ስለታየ እናቷ ምን እንደሆነች ጠይቀዋት ይህ ግለሠብ
ያደረጋትን ነግራቸው ስለ ነበር ነው ለጎረቤት ሁኔታውን አሳውቀው ፖሊስ ጣቢያ የሄዱት:: ይህ ጨዋ መሳይ ወጣት
ለፍትወቱ ጥማት ሲል ህፃን ለዚያውም የአዕምሮ ህመምተኛዋን በመድፈሩ : ይህም በራሱና በማስረጃ በመረጋገጡ ፍርድ
ቤት የ12 ዓመት ፅኑ እስራት አከናንቦ ዘብጥያ ልኮታል:: ዕውን የአዕምሮ ህመምተኛው ከህፃኗና ከርሱ ማነው?
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
+++++++++++++++
የዘናጭ ልጅ ልቅሶ
እናቱ ለአሥራ አምስት ዓመት ልጇ የአክስቱን ሞት እንዴት እንደምትነግረው ተጨንቃለች፡፡ ይህቺ የአባቱ እኅት
የሆነችው የልጁ አክስት ልጅ አልነበራትምና እንደ ልጇ ታየው ነበር፡፡ አብራው ኳስ ታያለች፤ አብራው ትዝናናለች፣
አብራው ታጠናለች፣ አብራው ትዋኛለች፣ አብራው ፊልም ታያለች፣ አብራው ኳስ ትጫወታለች፡፡
እንዲህ የምትሆንለትን አክስቱን ሞቷን ሲሰማ ያብዳል ብላ እናቱ ተጨንቃለች፡፡ እናም ትንቆራጠጣለች፡፡ ከትምህርት
ቤት ሲመጣ መጀመርያ መክሰስ አበላችውና ወደ መኝታ ቤት ወሰደችው፡፡ ከዚያም በሰው ልጅ ሕይወት ውስጥ መኖርና
መሞት ያለ መሆኑን፤ አንዳንድ ጊዜ የምንወዳቸው ሰዎች ሊሞቱ እንደሚችሉ ትነግረው ጀመር፡፡ ልጁ ግራ ገባው፡፡
‹እይውልህ ልጄ› አለች እናቱ ድምጽዋ ሆድዋ ውስጥ ገብቶ ሊጠፋ እየደረሰ፡፡ ‹‹ያች የምትወድህና የምትወዳት አክስትህ
በድንገት ትናንት ማታ ዐረፈች›› አለችው፡፡
‹‹ምን?›› አለና ሶፋው ላይ ተደፍቶ ድምጽ ሳያወጣ አለቀሰ፡፡ ከዚያም ከተደፋበት ተቃንቶ አንገቱን ሰበረና ይነቀንቅ
ጀመር፡፡
እናቱ የሚያደርገውን ሁሉ እንዲሁ ትከታተላለች፡፡ እንደሰማ አገር ይያዝልኝ ይላል፤ በድንጋጤ አቅሉን ይስታል፤ መሬት
ላይ ይፈጠፈጣል፤ ዓባይ ዓባዩን ያነባዋል ብላ ነበር የጠበቀችው፡፡ እንዲህ ቢሆንባት ምን ማድረግ እንደምትችል ነበር
ስትጨነቅ የቆየችው፡፡ አንዳንድ ጎረቤቶቿንም ስትጠራቸው መጥተው እንዲረዷት ተማጽናቸው ነበር፡፡
ሁሉም ግን እንዳሰበችው አልሆነም፡፡
‹‹አንተ፣ ያች እንደዚያ የምታሞላቅቅህ አክስትህ ሞታ እንዲህ ነው የምትሆነው›› አለችው ተናድዳ፡፡
‹‹ምን ሆንኩ?››
‹‹አታለቅስም እንዴ?››
‹‹እያለቀስኩ አይደል እንዴ፤ ዕንባዬን አታይውም››
‹‹ለእርሷ እንደዚህ ነው የምታለቅስላት፤ ማፈሪያ ነህ፡፡ እርሷኮ ላንተ ያልሆነችው የለም፡፡ እንደ ሕጻን አብራህ
ትጫወታለች፤ እንደ ጓደኛ ፊልም ቤት ይዛህ ትገባለች፤ እንደ እናት ትሳሳልሃለች፤ ለእርሷ እንደዚህ ነው የምታለቅሰው››
እናቱ አዝና ሶፋው ላይ ዘርፈጥ ብላ ተቀመጠች፡፡
‹‹ታድያ እንዴት ነው ለርሷ የሚለቀሰው?›› አላት ዕንባውን እየጠረገ፡፡
‹‹እትዬ እትዬ፤ ጉድ አደረግሽኝ፤ ሳትነግሪኝ፤ ምነው ጥለሽኝ ሄድሽ፤ እየተባለ ነዋ››
‹‹እንዴ እማዬ እንዴት ልትነግረኝ ትችላለች? በድንገት ነው የሞተችው አላልሽኝም? ደግሞስ ጥለሽኝ ሄድሽ ማለት ምን
ማለት ነው? እና ይዛኝ እንድትሄድ ፈለግሽ?››
እናቱ አፏን እጇ ላይ ጭናለች፡፡
‹‹አይ የዛሬ ዘመን ልጆች፤ የልቅሶው ወግ እንደዚህ ነው፤ የቅርብ ዘመድ እንዲህ ነው የሚያለቅሰው፤ የሸንኮሬ ልጅ ‹ጥሪኝ
አክስቴ ጥሪኝ› እያለ ጠዋት ሲያለቅስ ባየኸው››
‹‹እንዴ እርሱ ደግሞ ምን ነክቶታል፡፡ ባለፈው ‹ና ግቢውን እናጽዳ› ብላ ስትጠራው ያልመጣውን አሁን የት ነው ጥሪኝ
የሚላት? ውሸታም ነው፡፡ አሁን አንቺ ብትጠራሽ ትሄጃለሽ?››
እናቱ አማተበች፡፡ ‹‹ደረቅ ነህ ልጄ፤ ደረቅ ነህ፤ ነውር ነው፣ በእውነት ነውር ነው እንደዚህ አይባልም፡፡ በዚህ ዓይነት
ለእኔም ጊዜ እንደዚሁ ነው›› ከልቧ አዘነች፡፡ ደግሞም ታያት፡፡ እርሷ ሞታ፤ ልጇ ዝም ሲል፤ ሰው ሁሉ ዓይንህን ላፈር
ሲለው፡፡ ‹አሁን የርሷ ልጅ ይኼ ይሁን› እያለ በዓይኑ አፈር ድሜ ሲያበላው፡፡ ታያት፡፡
‹‹እማዬ ግን አንቺ የምትፈልጊው ካሰብሽው ቦታ የሚደርስልሽ ልጅ ነው ወይስ ስትሞቺ የሚያለቅስልሽ? እኔን ሠራ ነው
ወይስ እንዳለቅስ? ደግሞም ያኔ የምሆነውን ያኔ ነው ማወቅ የሚቻለው፡፡ እኔ ማዘን ያለብኝ ለራሴ ነው ወይስ ለሰው?
ኀዘን እንደ ፊልምና ድራማ ለሕዝብ መታየት አለበት?››
‹‹እርሱማ ልክ ነበርክ ልጄ፤ ግን ሰው ይቀየምሃል፤ ዘመዶቻችን ይቀየሙሃል፡፡ በልቶ ካጅ፣ ወጭት ሰባሪ፣ እጅ ነካሽ
ይሉሃል ልጄ፡፡››
‹‹ይበሉኛ፤ እኔ የት እሰማቸዋለሁ››
‹‹እኔ እሰማለኋ››
‹‹አትስሚያቸዋ፤ ተያቸው››
‹‹እንዴት አድርጌ ልጄ፡፡ የሰው ምላስ መርዝ ነው ይገድላል፡፡ ዱላ ነው ይሰብራል፡፡ እኔ ልጄን በክፉ እንዲያነሡብኝ
አልፈልግም፡፡ የሰው ጥርስ ውስጥ ትገባለህ ልጄ፡፡ ደግሞ እርሷ ናት እንዲህ ያደረገችው ይሉኛል፡፡ የአባትህ ዘመዶች
ይጠምዱኛል፡፡ አንተስ ብትሆን አክስትህ ናት፤ እንዲያ የምትወድህ አክስትህ ናት፤ ምናለ ብታለቅስላት?››
‹‹ቆይ ግን አሁን ማልቀስ ያለብኝ ለእርሷ ነው ለእኔ››
‹‹እንዴት እንዴት?››
‹‹አጉራሼ፤ አልባሼ፤ ጠያቂዬ፤ ሆዴ፤ ደጋፊዬ እያሉ የሚያለቅሱት ለሟቹ አዝነው ነው ወይስ እነርሱ ስለቀረባቸው?
ማረፊያችን ነበርሽ፤ ማን ላመትባል ይጠራናል ብሎ ማልቀስ አሁን ለሟች ነው ለራስ? ቆይ ግን ሰው ስለ ሰው
የሚመሰክረው ሲሞት በልቅሶ ዜማ ብቻ ነው እንዴ?››
‹‹የዛሬ ልጆች መፈላሰም ትወዳላችሁ እንዴው፤ አለቀሰ አላለቀሰም? የሚል እንጂ ለምን አለቀሰ? የሚል ዕድር እስካሁን
የለም፡፡ አቤት እገሌ እንዴት ቢወዳት ነው፤ አቤት እገሌ አለቃቀሱን ስትችልበት ይባላል እንጂ ለራሱ ነው ወይስ ለሟች?
ተብሎ ድንኳን ውስጥ አይጠየቅም፡፡ ይኼው በቀደም አንዱ የነ እትዬ የሰው ሐረግ ድንኳን ገብቶ ለያዥ ለገራዥ
እስኪያስቸግር መሬት እየወደቀ ሲያለቅስ ቆየ፡፡ ሰው ሁሉ ምን ቢዋደዱ ነው እስኪል ድረስ፡፡ ማን ይገላግለው፡፡ ሰውን
ሁሉ ዕንባ በዕንባ አራጨው፡፡ በመጨረሻ በቄስ ተገዝቶ አቆመና ቀና ሲል ሰዎቹንም አያውቃቸውም፤ ፎቶዋን
አያውቀውም፡፡ ለካስ ድንኳን ተሳስቶ ኖሯል፡፡ ይቅርታ ጠይቆ ወጣ አሉ፡፡ እዚያኛውም ሄዶ እንዲሁ ሲያለቅስ ነበረ
አሉ፡፡››
‹‹እና አሁን ይኼ በማያገባውና በማያውቀው ልቅሶ ገብቶ የሚያለቅሰው የፍቅር መግለጫ ነው?››
‹‹ባህሉ ነዋ ልጄ፡፡ መቼም ቢሳሳትም ልቅሶውን ሁላችንም አደነቅንለት፡፡ ወንድ ልጅ እንደዚህ ሲያለቅስ እኔ አይቼ
አላውቅም፡፡ ‹ዘመዶቹ ታድለው› ነው ያልነው፡፡ አስለቃሽም አያስፈልጋቸው፡፡ እኛን እንኳን የረሳነውን ሁሉ እያስታወሰ
አስለቀሰንኮ፡፡››
‹‹እሺ አሁን ምን አድርግ ነው የምትይኝ››
‹‹እንሂድና አንድ ጊዜ ብቻ ሰው እንዲያይህ ‹አጉራሼ አልባሼ› ብለህ ጯጩኸኽ እንገላገል››
‹‹እኔንኮ አላጎረሰችኝም፣ አላለበሰችኝም››
‹‹ይኼ ልጅ ምን ሆኗል ዛሬ፡፡ አብራህ አልነበረም ኳስ የምታየው? ከርሷ ጋር አልነበረም ፊልም የምትገባው? ደውለህ
ለርሷ አልነበረም እገሌ አገባ፤ እገሌ ተሸነፈ ትላት የነበረው? ሶደሬ አልወሰደችህም? ጌም አልጋበዘችህም? ዋና
አላስዋኘችህም? በጣም ታሳዝናለህ፡፡ እንዴት እንደዚህ ትላለህ?›› ተቀየመችው፡፡
‹‹እና ይኼ ማጉረስ ማልበስ ነው? የምጎርሰው ራሴ ነኝ፣ የምለብሰውም ራሴ ነኝ›› አላት፡፡
‹‹ኤዲያ፤ የስምንተኛው ሺ ልጆች፤ አባባሉንም አታውቁትም፡፡ ይህኮ አባባል ነው፡፡በል አሁን ከሄድክ እንሂድ ሰው ጥርስ
ውስጥ እንዳታስገባኝ፡፡ ››
‹‹እኔኮ አልችልበትም፡፡ እንደናንተ ማድረግ አልችልበትም፡፡ እናንተኮ የብዙ ዓመት ልምድ አላችሁ››
‹‹ሆሆይ›› ሳቋ መጣ ‹‹የመሥሪያ ቤት ቅጥር አደረግከው እንዴ ልምድ ምናምን የምትለው፡፡ ከልብ ካለቀሱ እንባ
አይገድም ሲባል አልሰማህም፡፡››
‹‹እሺ ሄጄ ምን ላድርግ?››
‹‹ድንኳን እስክንደርስ ዝም ትላለህ፡፡ ልክ ድንኳኑ አካባቢ ስንደርስ እኔ እጮኻለሁ፣ አንተም እኔን ተከትለህ ትጮህና
‹አልሰማሁም ነበር፤ አልሰማሁም ነበር› እያልክ ኡኡ ትላለህ››
‹‹እንዴ እማዬ ይኼው ሰማሁ አይደል እንዴ፤ ይኼማ ውሸት ነው፡፡››
‹‹ልጄ እኔ እናትህን ስማኝ፤ እንደዚያ ነው የሚባለው፡፡ አባባል ነው፡፡ ደግሞ በገላጋይ ካልሆነ በቀር ልቅሶህን
እንዳታቆም››
‹‹እንዴ ዝም በል እያሉኝ ልቀጥል? እንዲያውም ምክንያት ካገኘሁ ተገላገልኩ››
‹‹እንዲያውም ከቻልክ መሬት ውደቅ››
‹‹እንዴ እማዬ እኔ በረኛ አይደለሁ ለምን መሬት እወድቃለሁ››
‹‹በርህ ይጥፋና ባህል ነው አልኩህ፡፡ ሰው ያደንቅሃል፤ እንዲያውም ትንሽ ተንከባለል››
‹‹እማዬ አሁንስ አበዛሽው፣ ሳቄ ቢመጣስ፡፡ አንቺኮ የድራማ አክት የምታስጠኚኝ ነው የመሰልሽኝ››
‹‹በል ተወው ደግሞ ታዋርደኛለህ›› አለችና ወደ ምኝታ ቤት ገብታ ጋቢና ፎጣ ይዛ መጣች፡፡
‹‹በል እንካ ጋቢውን ትከሻህ ላይ፣ ፎጣውን አንገትህ ላይ አድርግ፡፡ ስታለቅስ በፎጣው ተሸፈን፡፡ ዕንባ እንኳን
ባይመጣብህ የሚያይህ የለም፡፡››
‹‹የልቅሶ ቤት ዩኒፎርም መሆኑ ነው›› አላት፡፡ ‹‹ሆሆ›› አለች አንገቷን እየነቀነቀች፡፡
ሄዱ፡፡ ልቅሶው ቤት በር ላይ ከመድረሳቸው በፊት አንድ ጓደኛው ደወለና የሆነ የእግር ኳስ ውጤት ነገረው፡፡ ውጤቱ
አስደሳች ነበር፡፡ እርሱን እያሰበ ድንኳኑ በር ላይ ሲደርሱ እናቱ ያስጠናችው ነገር ተረሳው፡፡ ጉዱ ፈላ፡፡ መኪናዋን ሲያዩ
ለቀስተኞቹ ተንጋግተው ከድንኳኑ ወጡና ከበቧቸው፡፡ እናት ከመኪናዋ እየጮኸች ወረደች፡፡ ልጁ ግን የሚባለው ነገር
ጠፍቶታል፡፡ ከእናቱ ጎን ሆነና በፎጣው ተሸፍኖ ‹‹እማዬ ምን ነበር ያልሽኝ፤ ስቴፑ ጠፋኝኮ›› አላት፡፡ እናቱ በዓይነ መዓት
አየችውና ጩኸቷን ቀጠለች፡፡
እርሱ ግን በአፉ እየጮኸ በልቡ ስቴፑን አሰበው፡፡ አልመጣለት አለ፡፡ ቀና ሲል የአክስቱን ፎቶ በአንድ አልቃሽ እጅ ላይ
አየው፡፡ ያን ጊዜ የሆነ የኀዘን ስሜት መጣበት፡፡ ልቡ ተንቦጨቦጨ፡፡ ትዝ አለው ነገር ዓለሙ፡፡ እናም ወደራሱ ልቅሶ
ተመለሰ፡፡
‹‹እትዬ እትዬ አይስክሬም ማን ይገዛልኛል፤ ሶደሬ ማን ይወስደኛል፤ ጌም ማን ያጫውተኛል፤ እትዬ እትዬ ኳስ ከማን ጋር
አያለሁ፡፡ ሩኒ ሲያገባ ለማን እነግራለሁ፤ ሮናልዶ ሲስት ከማን ጋር አወራለሁ፤ ሜሲ ሲያገባ ለማን እደውላለሁ፡፡ እትዬ
ደውይልኝ፤ ማን አገባ በይኝ፤ ማን ተጫወተ በይኝ፤ እትዬ፡፡ እትዬ ዛሬኮ ማንቼ ይጫወታል፤ ከማን ጋር አያለሁ፡፡ እትዬ
የዛሬው ጨዋታኮ ወሳኝ ነው›› አስነካው፡፡
ወዲያው አንድ በእርሱ እድሜ ያለ ልጅ ነጠር ነጠር እያለ መጣና በጆሮው ‹‹ማንቼ ተጫውቶ ቅድም ተሸነፈኮ›› አለው፡፡
ይህን ጊዜ መሬት ላይ ወድቆ እየተንከባለለ ‹‹እርምሽን ባትኖሪ ማንቼ ተሸነፈልሽ፤ እርምሽን ባትኖሪ ቫምፐርሲ ሳያገባ
ቀረ፡፡ እርምሽን ባትኖሪ ማንቼ ነጥብ ጣለ፡፡ የፈራሁት ይኼን ነበር፡፡›› ለቀስተኛው ሁሉ ልቅሶውን ቀስ በቀስ እየተወ
እርሱን ያየው ጀመር፡፡ እናቱ ግን ሾልካ የት እንደገባች አልታወቀም፡፡
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
አጫጭር ቀልዶች
አንደኛው ውሸታም፤
“የኔ አባት በርሻው ቦታ ላይ አውሮፕላን የሚያህል ጥቅል
ጐመን አምርቶ አንደኛ ወጣ፡፡
ሁለተኛው ውሸታም፤
“የኔም አባትኮ በጋራዣችን ውስጥ ትልቅ አፍሪካን የሚያህል
ብረት ድስት አምርቶ ተሸለመ፡፡”
አንደኛው ውሸታም፤
“እንዴት! አፍሪካን የሚያህል ብረት ድስት ምን ያደርግላቸዋል?
ብሎ ጠየቀው፡፡
ሁለተኛው ውሸታም፤
“ታዲያ! ያንተ አባት ጥቅል ጐመን በምን ይቀቀላል ሲል
መለሰለት፡፡”
አለቃ ገብረ ሃና ከዕለታት አንድ ቀን መንገድ እሄዳለሁ ብለ ይነሣሉ፡፡ “ማዘንጊያ” ይላሉ ሚስታቸውን “አቤት” ይላሉ
ሚስት “መንገድ ልሄድ አስቤያለሁ” “ወዴት?” “ወደ ቆላ ወርጄ የታመመ ጠይቄ፣ የተጣላ አስታርቄ እመለሳለሁ!”
“እንግዲያው ባዶ ሆድዎን አይሄዱም ቆይ ቁርስ ደርሷል፡፡” “ባዶ ሆዳችንን አደል የተፈጠርን? “ቢሆንም ወንድ ልጅ
የሚገጥመው ስለማይታወቅ ባዶ ሆዱን አይወጣም” “ሴትስ የሚገጥማት ታጣለች ብለሽ ነው? ካልሽ እንግዲህ ቶሎ
አቅርቢልኝና ፀሃዩ ሳይገርር ልነሳ” ወ/ሮ ማዘንጊያ ጉድ ጉድ ብለው ቁርስ አቀረቡና አብረ በልተው ተሰነባብተው ተለያዩ፡፡
አለቃ ቆላ ወርደው የታመመ ጠይቀው የተጣሉትን ሁለት ሰዎች ሊያስ…ታርቁ ግቢያቸው ሲደርሱ ጭራሽ ተጋግለው
ቡጢ ሊቀማመሱ ግራ ቀኝ ሲሉ ያያሉ፡፡ ሰዎቹ አንደኛው የተማረና አዋቂ የሚባል ሰው ነው፡፡ ሌላኛው ምንም ያልተማረ
መሀይም ነው፡፡ መሀይሙ የተማረውን፡ “አንተ ደንቆሮ! ዶሮ ራስ!” ይለዋል፡፡ “አፍህን ዝጋ ነግሬሃለሁ!” ይላል
የተማረው “ደንቆሮ! ደደብ! ቆርቆሮ!” ይላል መሀይሙ፡ “ምንም ልሁን አፍህን ካልዘጋህ ዋጋህን ታገኛለህ!” አለቃ፤
“ተው እንጂ ተው አይሆንም!” ይላሉ ሊገላግ መካከል ገብተው፡፡ መሀይሙ አሁንም “ደንቆሮ! አለቃ፤ ይሄኮ ደደብ ነው!
ይላል፡፡ አለቃ፤ ሁለቱንም በተለያየ አቅጣጫ ገፍተይለያዩዋቸዋል፡፡ ይሄኔ አንድ መንገደኛ ድንገት ይደርሳል፡፡ አለቃ
ያውቃቸዋል፡፡ ወደሳቸው ቀረብ ብሎ፤ አለቃ ምን እያደረጉ ነው?” ሲል ይጠይቃቸዋል፡፡ አለቃም፤ “ስድብ ቦታውን
ስቶብኝ፤ ቦታ ቦታው እየመለስኩ ነው!” አሉ፡፡
የ80 ዓመት አዛውንት ለጠቅላላ የጤና ምርመራ (Checkup) ሆስፒታል ይሄዱና ሃኪማቸው “እንዴት ነው
ጤንነትዎ?” ሲል ይጠይቃቸዋል፡፡
ሽማግሌውም “በጣም ጤና ነኝ —እንደውም የ18 ዓመት ኮረዳ አግብቼልህ አርግዛልኛለች—-ልጅ ላገኝ ነው —
መታደል ነው አይደል?” ይሉታል – ለሃኪሙ፡፡ ሀኪሙ ነገሩ አልተዋጠለትምና ትንሽ ሲያስብ ከቆየ በኋላ “አንድ ታሪክ
አስታወሱኝ” በማለት ይነግራቸዋል፡፡
“አንድ እኔ የማውቀው አደን የሚወድ ሰውዬ ነበር፡፡ በቃ የአደን ነገር ጨርሶ አይሆንለትም፡፡
አንድ ቀን ለአደን ሲወጣ ታዲያ ጠብመንጃውን አነሳሁ ብሎ ዣንጥላውን ይዞ ይወጣል፡፡ ገና ጫካ ውስጥ እንደገባም
ከየት መጣ ሳይባል አንድ የተበሳጨ ድብ ፊትለፊቱ ገጭ ይልበታል፡፡ ከመቀፅበት ዣንጥላውን እንደጠመንጃ አስተካክሎ
ድቡ ላይ ያነጣጥርበትና እጀታውን ይጫነዋል—-ድቡ ወዲያው መሬት ላይ ጠብ ይላል” አላቸው ሃኪሙ፡፡
ሽማግሌውም “ይሄማ ሊሆን አይችልም! ድቡ ላይ የተኮሰው ሌላ ሰው መሆን አለበት!” አሉ – ጮክ ብለው፡፡
ሀኪሙም “የእርስዎም ነገር እኮ እንደዚያ መስሎኝ ነው” አላቸው፡፡
“የባል ኑዛዜ”
ባል ጣዕረ-ሞት ይዞት እያጣጣረ ሳለ ሚስቱን ያስጠራና “እንግዲህ እኔ መሞቴ ነው፤ አንቺ ግን ያለ ባል መቅረት
የለብሽም፤ እንዲያውም ያንን ኩራባቸውን አግቢ” ይላታል። በዚህ አባባል የተናደደችው ሚስት “አንተን ይማርልኝ እንጂ
እኔ አሁን ስለ ባል አላስብም! ደግሞ ባገባስ እንዴት ያንተን ዋነኛ ጠላት ኩራባቸውን አግቢ ትለኛለህ?” ስትል
ትጠይቀዋለች። በዚህ ጊዜ ጣር የያዘው ባል እያቃሰተ መለስ ብሎ “አንቺ ደሞ አይገባሽም እንዴ? ጠላቴ መሆኑንማ መች
አጣሁት? ልክ እንደ እኔ አንገብግበሽ እንድትገድይልኝ ነው እንጂ! አላት ይባላል። ኑዛዜ ይልሃል ይህ ነው! ከእንዲህ
አይነቱ ኑዛዜ ይሰውራችሁ ይሰውረን አሜን አሜን በሉ።
ሚስት፡- “11”
ቢቸግረው አንድዋን ቆንጆ ልጅ ያስቆምና …”ሚስቴ ስለጠፋችብኝ በናትሽ ትንሽ ግዜ አብረሺኝ ሁኚ”…
ጋባዡ……
አንድ ሰውዬ ፊቱ በደስታ ጥርስ በጥርስ ሆኖ መጠጥ ቤት
ውስጥ ይገባና ደብል ውስኪ ያዛል ::
አንድ ሰካራም ሰውየ መንገድ ላይ አጥር ተደግፎ ሽንቱን ይሸናል…ድንገት ዞር ሲል ደንብ አስከባሪ አጠገቡ ቆሞ ደረሰኝ
ቆርጦ ይሰጠዋል፡፡
ሰውየው ፡- ምንድ ነው ?
ደንብ አስከባሪው፡- እዚህ ጋር መሽናት 5 ብር ያስቀጣል
ሰውየው ወንጀለኝነት በተሰማው መንፈስ 5 ብር ከ50 ሳንቲም ይሰጠዋል ፡፡
ደንብ አስከባሪው፡-..ሃምሳ ሳንቲሙ የምንድን ነው ?
ሰውየው፡- ፈስቻለው
“የታሰረበትን ገመድ የፈታ ውሻ ከኔ ስጋ ቤት ስጋ ሰርቆ ቢሄድ የውሻውን ባለቤት የስጋዬን ዋጋ ልጠይቀው እችላለሁ?”
“ያለጥርጥር!”
በማለት እርግጠኛ መልስ ይሰጠዋል::
የስጋ ቤቱ ባለቤትም እምቅ ፈገግታ ፊቱ ላይ እየተነበበ በልቡም “ሰራሁልሽ!” እያለ “ዛሬ ጠዋት ያንተ ውሻ ማሰሪውን
በጥሶ ግማሽ ኪሎ ስጋ ይዞብኝ ሮጧል፡፡
ስለዚህ 20 ብር ልትከፍለኝ ይገባል፡፡” (የስጋው ዋጋ አዲስ በወጣው የመንግስት የዋጋ ተመን መሰረት ነው!)
ጠበቃውም ያለተቃውሞ ከኪሱ 20 ብር አውጥቶ ይሰጠዋል፡፡ የስጋ ቤቱ ባለቤት በጠበቃው ቅንነት እየተገረመ ሊወጣ
ሲል ጠበቃው አስቆመውና አንድ ደረሰኝ ጽፎ…
“የምን መቶ ብር?”
አንዲት ሴት ልጇን ይዛ ባቡር በመሳፈር ላይ እያለች የባቡሩ ሹፌር እንዲህ አይነት አስቀያሚ ልጅ አይቼ አላውቅም
ይላታል እሷም በጣም ትበሳጭና ከባቡሩ መሀል ሄዳ ስቅስቅ ብላ ታለቅሳለች ከዛም ከተሳፋሪዎች አንዱ ለምን
እንደምታለቅስ ይጠይቃታል
ተሳፋሪ – ታድያ ለሱ ነው እንዲህ የምታለቅሽው ሄደሽ ልክ ልኩን አትነግሪውም እስከዛ ጦጣውን ልያዝልሽ ::
አላት ይባላል
ታሪክን የኅሊት
አበበ ቢቂላ ጣሊያን ሮማ ውስጥ ባለው stadio olimpico ውስጥ በባዶ እግሩ ማራቶን ያሸነፈ ጊዜ…
አንድ የተሸነፈ ሯጭ “ለምን በባዶ እግሩ እንዲሮጥ ፈቀዳችሁለት?” “እሱ እኮ ያሸነፈው ሸክም ስለቀለለት ነው” ብሎ ክስ
በማቅረብ ዳኞቹን ሲጠይቃቸው ጊዜ ምን ብለው መለሱለት መሰላችሁ?
.
.
.
.
.
.
“አንተም ሸክም እንዲቅልልህ ከፈለግህ ለምን
ራቁትህን ሮጠህ አታሸንፍም ነበር?”
ሰውዬው ላዳ ታክሲ ተኮናትሮ ከቦሌ እየመጣ ነው፡፡ ሗላ ወንበር ተቀምጦ እየመጣ እያለ የሚያውቀው ሰው ያይና
ታክሲውን እንዲያቆምለት ለሹፌሩ ለመንገር ትከሻውን ነካ ያደርገዋል፡፡ ይሄኔ በቅፅበት ውስጥ ታክሲዋ እንዳልነበረች
ሆነች… ትከሻውን የተነካው ሹፌር በድንጋጤ መጮህ ጀመረ… ታክሲዋን መቆጣጠር አቅቶትም አንዴ ወደ ግራ ከዛ
ወደ ቀኝ ካንገላታት በሗላ በከባዱ እየተነፈሰ እንደምንም የመንገዱ ጥግ ላይ አቆማት፡፡
ወዲያውም “ሰውዬ ያምሃል እንዴ? ምን ነካህ?” እያለ መነጫነጭ ጀመረ፡፡ በሁኔታው የተደናገጠው ተሳፋሪም ይቅርታ
እየጠየቀ ..
“እንደዚህ ትደነግጣለህ ብዬ ፈፅሞ አላሰብኩም ነበር፤ እንድትቆምልኝ ፈልጌ ስለነበር ነው” ብሎ ለማስረዳት ሞከረ::
በመጠኑ የተረጋጋው ሹፌርም “ነገሩስ አንተ አይደለህም ጥፋተኛው፤ ገና ዛሬ ለመጀመርያ ጊዜ ታክሲ ስለያዝኩ ነው
የተደናገጥኩት መሰለኝ…”
በጠጪነቱ የታወቀ የአንድ መሥሪያ ቤት ሠራተኛ ጧት ሥራከመግባቱ በፊት ከቤቱ ጀምሮ ባሉ አንድ አራት መጠጥ
ቤቶች
ጎራ እያለ ፉት ይላል፡፡ ማታም እንዲሁ አትለፍ የተባለ ይመስል የደንቡን ሳያደርስ ቤቱ አይገባም፡፡ ይህ ልምዱ
እንደማያዋጣው በብዙ ሰዎች ከተነገረው በኋላ አንድ ጧት
ለራሱ ቃል ገባ፣ ሳይጠጣ ቢሮው ገብቶ ሳይጠጣ ቤቱ ለመመለስ፡፡ እናም፣ ምሎ እና ተገዝቶ እኒያን መጠጥ ቤቶች ጧት
ላይ እየገላመጠ እና እየረገማቸው አልፎ መሥሪያ ቤቱ
ደረሰ፡፡ በውሳኔው ተደስቶ በሰላም ሲሠራ ከዋለ በኋላ ማታም ወደ ቤቱ ሲመለስ የጧቱኑ ዕርምጃ ወሰደ፡፡ ሳይቀምስ
ውሎ ሳይቀምስ በመግባቱ ተደስቶ፣ ‹‹ጀግና ነኝ! ቆራጥ! ለዚህ
ጀግንነቴ አንድ ጠርሙስ አረቄ ይገባኛል በማለት ወደ አረቄ ቤት በረረና አረፈዋ!
ቁራሽ በሚለምንበት መንደር ‹‹ተቀምጬ›› የሚባል የምግብ ዓይነት ነበርና አንዲት ሴት ወይዘሮ እንጀራ አልጋገረች ኖሮ
‹‹ተማሪ እንጀራ አልጋገርኩምና ተቀምጬ
ልስጥህ?›› ትለዋለች፡፡ ተማሪውም መልሶ ‹‹ኧረ እመይቴ የሚዘክሩኝስ ከሆነ ተኝተውም ቢሆን ቢሰጡኝ አልጠላም››
አላቸው ይባላል፡፡
ባል ለሚስት በሞባይል መልዕክት… “ነገ ለስብሰባ ወደ ክፍለ ሃገር ስለምሄድ ከውስጥ የምለብሳቸውን ልብሶች ቅያሬ
እና ሸሚዝ እንዲሁም ካልሲ በመካከለኛው ሻንጣ አዘጋጂልኝ::”
ትንሽ ቆይቶ እንደገና ሌላ መልዕክት “ውይ ሳልነግርሽ እረስቼው: ባለፈው የተወዳደርኩበትን ቦታ እኮ አለፍኩ:: የደስ ደስ
ያንን የእራት ቀሚስ ገዝቼልሽ እመጣለሁ::”
ባል ከእንደገና በመልክት: “አረ ውሸቴን ነው:: የመጀመሪያውን መልዕክት እንደደረሰሽ ለማረጋገጥ ነው::”
ባል የሰሞኑን የሚስቱ ሁኔታ አልጥምህ ብሎት እንዳይነግራት ትዳራቸውን እንዳያቀዘቅዝ ፈርቶ ሀኪም ለማናገር ፈለገ::
“ዶክተር ሚስቴ የመስማት ችግር ሳይኖርባት አይቀርም:: በግልፅ እንዳልነግራት ደግሞ እንዳታኮርፈኝ ፈራሁ::
” ሀኪሙም ከአምስት ሜትር ርቀት ጀምሮ አንድ ሜትር ርቀት እየቀነስክ አንድ ጥያቄ ጥይቃት እና የችግሩን ክብደት
እንለያለን ብሎ መክሮ ይሸኘዋል::
ባልም እቤት እንደገባ ከአምስት ሜትር ርቀት “ውድ, ዛሬ ምሳ ምንድን ነው?” ብሎ ይጠይቃታል:: ምን መልስ የለም::
ከአራት ሜትር ጥያቄውን ደገመ:: አሁንም መልስ የለም:: ከሶስት ሜትር: ከሁለት ሜትር: ተመሳሳይ ሞከረ:: ምንም
መልስ የለም::
ሚስት “እህ አንተ ሰውዬ ዛሬ ምን ሆነሃል? አሁን እኮ ስትጠይቀኝ ለአምስተኛ ጊዜህ ነው:: ምስር ወጥ አልኩህ አይደል!”
ልጅቷ አምራና ተውባ ከቤት ልትወጣ ስትል አያቷ አስቆሟትና “ ወዴት ልትሄጂ ነው የኔ ልጅ አሏት”
“ እንደዛ ከሆነ ማድረግ ስለሚኖርብሽ ጥንቃቄ ልንገርሽ ቁጭ በይ፡፡ እነዚህ ወጣቶ ወንዶች ተንኮለኞች ናቸው ሊያሳስቱሽ
ይችላሉ፡፡” አሉ አያትየው የወጣትነት ዘመናቸውን በትውስታ እየተመለከቱ፡፡
“አንዴት አያቴ”
“አሺ ……”
“ሲቀጥል ደግሞ ጡቶችሽን እያሻሸ’ ስሜት ውስጥ ሊያስገባሽ ይሞክራል፡፡ ይሄም በጣም ደስ ይላል፡፡ ግን እንደዛ
እንዲያደርግ እንዳትፈቅጅለት፡፡”’
“አሺ ……”
“ሲቀጥል ጣቶቱን በእግሮችሽ መሀል አስገብቶ ሊነካካሽ ይሞክራል፡፡ በእርግጥ ይሄም ጥሩ ስሜት ይፈጥራል፡፡ ሆኖም
ልትፈቅጅለት አይገባም፡፡”
“አሺ ……”
“ ይሄም ሁላ አልበቃ ብሎት አንቺን አስተኝቶ እላይሽ ላይ ሊደሰት ይሞክራል፡፡ ስለዚህ ይሄንንም እንዳትፈቅጅለት
ቤተሰባችንን ያዋርዳል፡፡”
ከዛ ልጅቷ ምክሩን ሁሉ ከሰማች በኋላ ወደ ወንድ ጓደኛዋ ሄደች፡፡ በማግስቱ አድራ ስትመለስ ደረቷን ነፍታ በድል
አድራጊነት ስሜት እያለከለከች ነበር፡፡
“አያቴ መጀመሪያ ላይ ምክሮችሽን ሁሉ ለመተግበር የሚቻለኝን ሁሉ ብሞክርም ተግባራዊ ማድረግ አልቻልኩም ነበር፡፡
“ ምን አደረግሽ ልጄ”
ማን በለጠ?
እንግሊዛዊው፣ አየርላንዳዊውና ስኮትላንዳዊው ጩኸት የበዛበትና በጭስ የታፈነ በርካታ ሰዎች የተሰበሰቡበት መጠጥ
ቤት ውስጥ ተቀምጠዋል፡፡
የእንግሊዙ ተወላጅ ‹‹የአገሬ የእንግሊዝ መጠጥ ቤቶች ምርጦች ናቸው፡፡ አንደ ነገር የጠጣ ሰው ሁለተኛውን በነፃ
ይጋበዛል!›› አለ፡፡ ጠጪዎቹ በመገረም ራሳቸውን ነቀነቁ፡፡
አየርላንዳዊው በበኩሉ፣ ‹‹በኔ አገር አንድ ነገር የወሰደ ሰው ሁለት በነፃ ይጋበዛል›› በማለቱ ጠጪዎቹ ይበልጥ በመደነቅ
አጨበጨቡ፡፡
በመጨረሻ ስኮትላንዳዊው፣ ‹‹የናንተ መዝናኛ ሥፍራዎች ጥሩ ቢሆኑም እንደ ስኮትለንድ ሊሆኑ ግን አይችሉም፡፡
ስኮትላንድ ውስጥ አንድ መለኪያ በሒሳባችሁ ከጠጣችሁ፣
ሦስት በነፃ ትጋበዙና ባክብሮትና በፍቅር ቤታችሁ ድረስ ትሸኛላችሁ!›› አለ፡፡
እንግሊዛዊው በሸቀ፡፡ ‹‹አታጋን እባክህ፤ አሁን የተናገርከው አጋጥሞህ ያውቃል? በዓይንህ በብረቱ አይተሃል?››
በማለትም በቁጣ ጠየቀው፡፡
በድሮ ጊዜ ነው አሉ፡፡ ከብዙዎቹ ጦርነቶች በአንዱ ጊዜ፡፡ እንደተለመደው ሴቶች ለወታደሩ ሁሉ ቆሎ ቆልተው፣ አምሰው
ያሳድራሉ፡፡
በማግስቱ ፤በዘመን ብዛት ቃልም ‹‹እንደሚባልግ›› ያልተረዳ አንዱ የዘመኑ ወታደር ጡሩምባውን ይዞ የሚከተለውን
ለፈፈ፡፡
‹‹አባ እንግዲህ መሞቴ ነው፤ እንደሚያዩት እንኩዋን የሚወረስ የሚላስ የሚቀመስ ተቤት የለም! ያም ቢሆን ለሁለቱ
ልጆቼ ምንም ሳላወርሳቸው አልሞትም፡፡ እዚህ
ከቤቴ በስተግራ ካለው ጎረቤቴ ጋር ያልቋጨሁት ጠብ አለኝ፣እሱን ልጆቼ እንዲጨርሱልኝ ተናዝዣለሁ››
ጊዜን በስላቅ
የሥዕል አስተማሪ ክፍል ውስጥ ይገቡና ለተማሪዎቻቸው የክፍል ሥራ ይሰጣሉ፡፡ መምህሩ ተማሪዎቻቸው ስለው
እንዲያሳዩዋቸው የጠየቁት በሀዲዱ ላይ የሚጓዝ ባቡር ወይም ባቡሩን ከነሀዲዱ ቁጭ እንዲያደርጉላቸው ነው፡፡ ክፍለ
ጊዜው
ከማለቁ በፊት እንዲታረምላችሁ በፍጥነት ሥሩ ይሉና ወደ መቀመጫቸው ያመራሉ፡፡ ቁጭ እንዳሉ እንቅልፍ ሸለብ
ያደርጋቸውና ክፍለ ጊዜው ሊያልቅ 5 ደቂቃ ሲቀረው
ይነቃሉ፡፡ ወዲያውም ተማሪዎቻቸው የሠሩትን በየተራ እየተመለከቱ ሲያርሙላቸው ከተማሪዎቹ መካከል አንደኛው
ሐዲዱን ብቻ ሥሎ ያሳያል፡፡ መምህሩ ሲመለከቱት ባቡሩ
የለም ሀዲዱን ብቻ ይመለከቱና ጥያቄ ያነሳሉ፡፡
መምህሩ፡-ስላችሁ አሳዩኝ ያልኳችሁ በሀዲድ ላይ የሚጓዝ ባቡር ነው፣ አንተ የሣልከው ደግሞ ሀዲዱን ብቻ ነው፤ ባቡሩስ
ሲሉ
ይጠይቃሉ፡፡
ተማሪ፡- አይ ቲቸር እርስዎ እኮ እንቅልፍ ወስዶዎት እያለ ባቡሩ አልፏል፡፡ ለዚህ ነው ሀዲዱን ብቻ የሚመለከቱት
ፍቅር በሒሳብ
በአንዳች ቅጽበት set ነትሽን አድንቄ ቀርቤ ላወራሽ ብፈልግ ስለፍቅርሽ እኔ ለፍቅር negative ነኝ ብለሽ
ብታስደነግጭኝም እኔ ግን ለፍቅር positvie ሳስብም እኔ
radical ውስጥ የገባሁ ነኝ ብትይም ተማመንኩ፡፡ ከcomplex system ላስቀር negative ፍቅርሽን sub set ሆነሽብኝ
ፍጹም ብታስቸግሪኝም በsine መስመር ወደ
አንቺ ብመጣ የአንቺ ምርጫ በcosine መስመር ሆኖ ቢያስከፋኝም ተስፋ ባለመቁረጥ በhorizontal line ወይስ
በsymptote ወደ አንቺ ለመቅረብ አንድ ሐሳብ መጣልኝ፤ ሳሰላስል ድንገት ወስኜ ለራሴ እንደ polynomila በ power
በዝቼ rationalize ሆነ inverse ሆኜ በመምጣት እንዳለብኝ ወሰንኩ አንቺን ፈልጌ፡፡
የምር ግን አስቸጋሪ ነሽ ለፍቅር empty set ነሽ፡፡ በሂሳብ ቀመር በ subtracton ኧረ እባክሽ በmultiplication
ደግሞም በaddition እኔ ልሆንልሽ የፍቅርሽ division:: የፍቅርሽ ውስብስብነት በlimit “x” goes to beta
አለመፈታቱ ቢሆንብኝ ስቃይ በሐሳብ ብዞር በቁጥሮች ጎራ በgraph ዎች መንደር በcircle አደባባይ በquadratic ሰፈር
በcalculus እና በመደመር አንቺ ግን ክፋትሽ አሁንም undifined ነሽ፡፡ ግን solve ማድረጊያው የፍቅርሽ መንገዱ
sequence አይደለም፤ አቤት ክፋቱ እኔ ግን ተስፋ
ባለመቁረጥ logarithm ተጠቅሜ exponentialን አብዝቼ በsolution set ቦታ ሆኜ perimeter ሽን አቅፌ vertical
line ሽን አይቼ upper and lower
bounedሽን አረጋግጩ remainder ሽን በድካም አግኝቼ square root ሳላበዛ ተስፋ አደርጋለሁ እንደማግኝሽ፡፡
በfunction ቦታ ካልተገኘሽ የፍቅር slope ካልገባሽ የ
“x” “y” ዋጋ ካልሆንሽ የምር አሁንም ለፍቅር empty set ነሽ፤ ለፍቅር undefined ነሽ፤ ለፍቅር one over
zero ነሽ፤ ሁሌም ነሽ፡፡
“ምን ተፈጠረ?”
“ልጅ”..
.“የምን ልጅ?”
“የ 15 አመት ልጃችን እኮ አረገዘች”
#ትንሹ ማሙሽ እድሜው ለትምህርት ሲደርስ አባቱ ትምህርት ቤት ይዞት ይሄድና ለተቀበለችው መምህርት እንዲህ
የሚል መስጠንቀቂያ ይነግራታል::
” ይህ ልጅ ቁማር በጣም ነው የሚወደው:: እስከ ዛሬ እንዳየሁት የሚሸነፍ አይነት አይደለም:: ስለዚህ ምንም ነገር
እናሲዝ ቢልሽ እሺ እንዳትይ ብሎ ይነግራታል::
አባት ገና እግሩ ከክፍሉ እንደወጣ ማሙሽ ቲቸሩን ጠርቶ “ቲቸር ከፊትሺ ፈገግታ ተነስቼ: ያረግሺውን ፓንት መገመት
እችላለሁ::”
“እስቲ ገምት?” አለችው:: “ሃምሳ ብር አናሲዝ?” አላት:: ተስማምታ ከክላስ በሁላ ተቃጠሩ:: ክላሱ ሲያልቅ “እስቲ
ግምትህ ምንድን ነው?” ማሙሽ “ነጭ!” አይደለም ብላ ቀሚሱአን ገልባ ስታሳየው ቀይ ነው::
አባት:- “ምን? “
አባት:- “በምን?”
አስተማሪዋ:-“ፓንትሽ ነጭ ነው ብሎ::”
አባት:- “እና ፓንትሽን አሳየሽው?”
አስተማሪዋ :- “አዎ!”
አባት:- “እናቱ አፈር የበላች! ከእኔ ጋር እኮ ክላሱ ከማለቁ በፊት ፓንቱአን አያለሁ ብሎ 100 ብር አሲዞኛል!”
አንድ ሀብታም ሰው ፓርቲ አዘጋጅቶ ብዙ ሰው ጋበዘ:: በፓርቲው መሃል “አንድ ውድድር አለኝ” ብሎ አስታወቀ::
“ውድድሩ እዚህ የዋና ገንዳ ውስጥ አዞዎች አሉ:: በእነዚህ አዞዎች ውስጥ ዋኝቶ በህይወት የወጣ ሰው 3 ፍላጎቶችን
ላሙዋላለት ቃል እገባለሁ::” አለ::
በመጀመሪያ ፍቃደኛ የሆነ ሰው ጠፋ:: በመኅል ግን የሆነ ሰው ዘሎ ገብቶ በፍጥነት መዋኛት ጀመረ:: ምንም አዞ ሳይነካው
በህይወት ወጣ::
ስፍራው የአዕምሮ ህመም ችግር የለባቸው ሰዎች (ወይኔ እርዝመቱ – እብዶች ማለቴ ነው) ሆስፒታል ግቢ ውስጥ ነው፡፡
በግቢው ውስጥ ያሉት እብዶች በጋራ ድምፅ “….13…..13….13…13….” እያሉ ይጮሃሉ፡፡ በዚህ ግዜ ወደ ስራው
ለመሄድጫማውን እንኳን በደምብ ሳያስር ተጣድፎ ከቤቱ የወጣ አንዱ ወሬ ወዳድ ግለሰብ የፈለገው ሰዓት ይርፈድ እንጂ
ይሄንንማ ምን እንደሆነ ማየት አለብኝ ብሎ ወደ ሆስፒታሉ ተጠግቶ ወደ ግቢው ውስጥ ለማየት የሚያስችለውን ቀዳዳ
መፈለግ
ይጀምራል፡፡ ከትንሽ ፍለጋ በኋላ በበሩ ቁልፍ ስር ትንሽዬ ቀዳዳ አግኝቶ ወደ ውስጥ ለማየት አይኖቹን ሲያቁለጨልጭ
ከውስጥ
ካሉት አንዱ እብድ በጣቱ አይኑን ይወጋዋል፡፡
ከተማሪወች መሃል የፕሬዝዳንት ኢሳያስ ልጅ አለ እናም መምህር ጠየቀ”እስኪ ተማሪወች ከበራሪ እንስሳት መካከል ጥቀሱ
“ይላል
ከተማሪወች መሃል እጁን ላወጣው የኢሳያስ ልጅ አንተ ሲባል “ዝሆን” ይላል አስተማሪውም አጨብጭቡለት
ይላል፣ታላቅ ጭብጨባ በመሃል ጭብጨባውን የሰማ ረእስ መምህር ሲመጣ ምንድን ነው ሲል ጉዳዩ ይነገረዋል እናም
ደግማችሁ አጨብጭቡለት ይልና ለመምህሩ”ወንድሜ እኛ ከምንበር ዝሆኑ ቢበር ይሻላል !!!!!አለው ይባላል!!
የሳይንስ ክፍለ ጊዜ ነዉ መምህሩ ‘ሰልፈሪክ አሲድ’ ስለ ሚባለዉ የአሲድ አይነት በማስተማር ናቸዉ: :
”ልጆች አሁን ይህን የወርቅ እንክብል እዚህ አሲድ ዉስጥ ልከተዉ ነዉ እና አሲዱ ወርቁን የሚያበላሸዉ ወይም
የማያበላሸዉ መሆኑን አስቀድሞ ሊነግረኝ የሚችል አለ”
“ለምን”
ለምን ደወልሽው ?
————— —
አንድ ሴት ዉሀ ልትቀዳ ጎንበስ ስትል አንድ ጊዜ ያመልጣትና (Feswan) ድዉ ታደርገዋለች።
“ዉድ ልጄ ፤ ይኸዉልህ አንተ በመታሰርህ ምክንያት በዚህ አመት እርሻ ቦታዉ ላይ ድንች ሳልዘራ ጊዜዉ ሊያልፍብኝ
ነዉ፤ እኔ እንደሆንኩ ከእንግዲህ ደክሜያለሁ፤ምነዉ
በኖርክልኝ ኖሮ” አፍቃሪ አባትህ።
በሚቀጥለዉ ንጋት ላይ የፖሊስ መዓት መጥቶ የድንቹ ማሳ ላይ ፈሰሰ፤ የተቀበሩትን አስክሬኖች ለመፈለግ ሲቆፍሩ
ቢዉሉም ምንም ሊያገኙ አልቻሉም ፡፡ ስለዚህ ገበሬዉን ይቅርታ ጠይቀዉ ሄዱ፡፡ ወዲያዉ ልጁ ለአባቱ እንዲህ የሚል
ሌላ ደብዳቤ ፃፈ፡-
“አባቴ፤ አሁን ድንችህን መዝራት ትችላህ፤ ካለሁበት ችግር አንፃር ላደርግልህ የምችለዉ ነገር ቢኖር ይሄ ብቻ ነዉ”
ብልጥ ለብልጥ
እናት፡- ዮሐንስ እዚያ ኬክ ያስቀመጥኩበት መሳቢያ ውስጥ ጭራቅ መኖሩን አትርሳ፤ እሺ?
የፊደሏ ጣጣ
ጎልማሳው ለሥራ ጉዳይ ካለበት ብርዳማ የአሜሪካ ግዛት ወደ ሌላ ሞቃታማ ግዛት ይጓዛል፡፡ ባለቤቱም በቀጣዩ ቀን
እንደምትመጣ ተነጋግረው ነበር፡፡
ጎልማሳውም ታዲያ የሆቴል ክፍሉ ውስጥ ሆኖ ለባለቤቱ የኢ-ሜይል መልዕክት ይልክላታል፡፡ ሆኖም ግን አድራሻዋን
ሲጽፍ አንዲት ፊደል ይስትና የኢ-ሜይል መልዕክቱ ወደ ባለቤቱ መሄዱ ቀርቶ አቅጣጫውን ስቶ ወደ አንዲት ባለቸው
ወደ ሞቱባቸው ባልቴት ዘንድ ይሄዳል፡፡
“ውድ ባለቤቴ እኔ ደርሻለሁ፡፡ ይገርምሻል፤ እዚህ በጣም ይሞቃል፡፡ ላንቺም ነገ መምጣት ሁሉም ነገር ተዘጋጅቶ
እየጠበቀሽ
ነው! ከልጆችሽ ተለይቶ መምጣቱ እንዳይከብድሽ ! ያንቺው!
የሚል ነበር፡፡
የፍቅር ጣዕም
ያልነገርኩሽ ነገር
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
++++++
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
++++++++
ጣቶችሽ አለንጋ
አቤት ሲያናዝዙ
ካንቺ ጋራ ፍቅር
ብዙ ነው መዘዙ
መግነጢሳዊ ኃይል
ገላሽ እየሳበኝ
ለማምለጥ አልቻልኩም
እንደ ወጥመድ ይዞኝ
ሰብሰብ ብዬ እማስበው
ብዬ ከልቤ ስማከር
ተጨብጨ እማብላላው
ልቤ ልቤን ሲሞግተው….
ያም ሆኖ ነገሬ ከልብ
ያልወጣነውና ለሕዝብ
ከመጠጡ ብዥ ድንብር
ለኔ ከቶ ላታውቁልኝ
ጠር በቀር ላታስቡኝ
ልታጫውተኝ ልትጠይቀኝ
ልታዋየኝ ልታቀርበኝ
ከዘመድ ልትደባልቀኝ
ካገር ልታመሳስለኝ
አዲስ ዘዴ ልታሳየኝ
መጣች ብዬ ሳሳስቃት
ሳጎርሳት ስገባብዛት
ልቤ ፈክቶ ሳደምጣት÷
ምሥጢር የሚያመሳጥራት
አሳስቧት÷ አሰኝቷት
በኔው ሶፋ እያስጠናት
ችግሯን ከተረዳላት
አሰኝቷት÷ አሳስቧት
ነበር ለካ የደከመችው
ከልቤ ጋር ስከራከር
እያልኩ ነው፡፡
ይህ ነው አንዳንዴ እሚያጽናናኝ
በሚያሾፍ እንዳሾፍበት
በሚስቅ እንድስቅበት
በቀን ለሚንበላጠጡ
በሌት ለሚብለጠለጡ ….
በወሬም በማሽቃበጡ
በምሥጢር ሲቀማመጡ
ገቢያችንን ወስደውብን
ስሙን ብቻ በተውልን ….
መልሰው ደሞ ሲያዝኑልን
ለወግ ሲመጻደቁብን ….
ባንደኛው ሲነካከሱ
በሌላው ሲሞጋገሱ
በሦስተኛው ሲነካከሱ
የሥነ-ሥርዓት ደላዳይ
“ከሌባ ሌባ ቢሰርቀው
ምን ይደንቀው” እንደሚባለው
እኔንም የሚያስደንቁኝ
ወኔአችንን ካልበከሉ
ሲያሽቃብጡ ሲያዳልሉ …
ወይ ለንዴት መቀነሻ
ወይ ለበቀል ማስታገሻ
ወይ ለመሃላ ማፍረሻ ….
ልቅሶ ላይ ሆነ አደባባይ
ምንም የማልደብቃቸው
አንዳንዴም ሲቸግራቸው ….
መጦሪያ እሚሆናቸው
ጎጆ ልቀልስላቸው
የግብር ልከፍልላቸው
ጉድ ብለው እያስታወሱ
በገጻቸው እያወሱ
ከንፈር እየተናከሱ
በዓይን እየተጠቃቀሱ
የልጅነቴን ሳይረሱ
እሺ ስል ጉድ-ፈላ ያሉኝ
በዓይን እየተጠቃቀሱ
አሙኝ
ሥጋዬን ከተፉኝ
እያልኩ ነው፡፡ ….
አለነሱም የለኝም ብል
ቢያሙኝ ነውና የባህል ….
እያልኩም ነው፡፡
ተገንጥዬ ተነውሬ
አስጨርሼ ተቸግሬ
…. ማን ይበለኝ÷ ምን ይበለኝ
ስም አጠረው÷ ስም አጠረኝ፡፡
ስም ያጣልኝን አንድዬን
ባላዋለኝ ውል እንዳልውል
ብቻ አንዳንዴ እየረሳሁት
የሐቅ ራብ እንደፈራሁት
እንኳ ቢለው
እያልኩ ነው፡፡
የ አማርኛ ተረት እና ምሳሌ ዝርዝር
ሀ ሳይሉ ጥፈት ውል ሳይዙ ሙግት
ሀ ባሉ ተዝካር በሉ
ሀ ባሉ ደሞዝ በሉ
ሀሜተኛ ነው ከዳተኛ
ሀሜተኛ ያፍራል ሀስተኛ ይረታል
ሀሜት አይቀር ከድሀም ቤት
ሀሜትና ጅራት በስተኋላ ነው
ሀምሌ ቢያባራ በጋ ይመስላል
ሀምሌና ሙሽራ ሳይገለጡ ነው
ሀምሌን በብጣሪ ነሀሴን በእንጥርጣሪ
ሀምሳ ሎሚ ለሀምሳ ሰው ጌጡ ለአንድ ሰው ሸክሙ
ሀረጉን ሲስቡት ዛፉ ይወዛወዛል
ሀረጉን ሳብ ዛፉ እንዲሳሳብ
ሀረግ ለመዳፍ አልጋ ለምንጣፍ
ሀሰተኛ ምስክር ጉልበት ይሰብር
ሀሰተኛ ሲናገር ይታወቃል ስሱ ሲበላ ይታነቃል
ሀሰተኛ ሲናገር ይታወቃል በሶ ሲበሉት ያንቃል
ሀሰተኛ በቃሉ ስደተኛ በቅሉ
ሀሰተኛ ብርቱ ወንጀለኛ
ሀሰተኛ ያወራውን ፈረሰኛ አይመልሰውም
ሀሰተኛን ሲረቱ በወንድም በእህቱ
ሀሰት ስለበዛ እውነት ሆነ ዋዛ
ሀሰት ቢናገሩ ውቃቢ ይርቃል
ሀሰት ነገር ክፉ ገሀነም እሳት ትርፉ
ሀሰት አያቀላ እውነት አያደላ
ሀሰት አያድንም መራቆት መልክ አያሳምርም
ሀሰትና ስንቅ እያደረ ያልቅ
ሀሳቡ ጥልቅ ነገሩ ጥብቅ
ሀሳብ ከውለታ አይቆጠርም
ሀሳብ ከፊት አይፈታ ሙት አይመታ
ሀሳብ ያገናኛል ፍራት ያሸኛኛል
ሀሳብ ያገናኛል ፍርሀት ያሸኛኛል
ሀሳብህን ጨርቅ ያድርገው
ሀሳብና መንገድ ማለቂያ የለውም
ሀስት እያደር ይቀላል እውነት እያደር ይበራል
ሀስት እያደር ይቀላል እውነትና ውሀ እያደር ይጠራል
ሀብታም ለሀብታም ይጠቃቀሱ ድሀ ለድሀ ይለቃቀሱ
ሀብታም ለሰጠ የድሀ ሙርጥ አበጠ
ሀብታም ለሰጠ የድሀ ሙርጥ ያብጣል
ሀብታም ለሰጠ ደሀ ምንጭሩ አበጠ
ሀብታም ለሰጠው ደሀ ይንቀጠቀጣል
ሀብታም ሊሰጥ የደሀ ቂጥ ያብጥ
ሀብታም ሊሰጥ የደሀው ሙርጥ ያብጣል
ሀብታም ሊሰጥ ደሀ ምርጥ ያወጣል
ሀብታም ሲወድቅ ከሰገነት ድሀ ሲወድቅ ከመሬት
ሀብታም በመመጽወቱ ድሀ በጸሎቱ
ሀብታም በከብቱ ድሀ በጉልበቱ
ሀብታም በወርቁ ድሀ በጨርቁ
ሀብታም በገንዘቡ ይኮራል ድሀ በጥበቡ ይከብራል
ሀብታም በገንዘቡ ድሀ በጥበቡ እርስ በርስ ይቃረቡ
ሀብታም ቢሰጥ አበደረ እንጂ አልሰጠም
ሀብታም ቢያብር ድህነትን ያጠፋል
ሀብታም ነው መባል ያኮራል ድሀ ነው መባል ያሳፍራል
ሀብታም እንደሚበላለት ድሀ እንደሚከናወንለት
ሀብታም ያለ ድሀ አይኮራም ድሀ ያለ ሀብታም አይበላም
ሀብታም ገንዘቡን ያስባል ድሀ ቀኑን ይቆጥራል
ሀብት እና እውቀት አይገኝ (ም ) አንድነት
ሀብት የጠዋት ጤዛ ነው
ሀኪም ሲበዛ በሽተኛው ይሞታል
ሀኪም የያዘው ነፍስ ባያድር ይውላል
ሀኪሞች እስኪመካከሩ በሽተኛው ይሞታል
ሀዘንሽ ቅጥ አጣ ከቤትሽ አልወጣ
ሀዘንና ደስታ ጎን ለጎን ናቸው
ሀዘንን የፈራ በደስታ የተጣራ
ሀይለኛ ውሀ አሻቅቦ ይፈሳል
ሀይለኛ ዱቄት ከነፋስ ይጣላል
ሀይማኖቱ ከጅማት ጉልበቱ ከብረት የጠና
ሀይማኖት ከግብር ጸሎት ከፍቅር
ሀይማኖት የሌለው ሰው ልጓም የሌለው ፈረስ ነው
ሀይማኖት ያለ ፍቅር ጸሎት ያለ ግብር
ሀጢአት ለሰሪው ምህረት ለአክባሪው
ሀጢአት ሲደጋገም ጽድቅ ይመስላል
ሀጢአት ሳያበዙ በጊዜ ይጓዙ
ሀጢአት በንስሀ በደል በካሳ
ሀጢአት በንስሀ እድፍ በውሀ
ሀፍረት ያከሳል ያመነምናል
ሁ
ሁለተኛ ደሞ ለዘበኛ ! አሉ
ሁለተኛ ግፌ ጫንቃዬን ተገርፌ ልብሴን መገፈፌ
ሁለተኛ ግፍ ልብሴን ይገፍ ጀርባዬን ይገርፍ
ሁለተኛ ጥፋት ቆሞ ማንቀላፋት
ሁለተኛ ጥፋት ከገበያ ማንቀላፋት
ሁለተኛ ጥፋት ከገበያ ቆሞ ማንቀላፋት
ሁለቱን ወንበዴ በአንድ ዘዴ
ሁለቱን የተመኘ አንዱንም አላገኝ
ሁለቴ ሰላምታ አንዱ ለነገር ነው
ሁለት ሆነው የተናገሩት በመሬት የቀበሩት
ሁለት ሞት መጣ ቢለው አንዱን ግባ በለው አለ
ሁለት ሞግዚት ያለው ህጻን ያለጥርጥር በእሳት ይቃጠላል
ሁለት ቁና ሰጥቼ አንድ ጥንቅል
ሁለት ባላ ትከል አንዱ ሲስበር ባንዱ ተንጠልጠል
ሁለት ባላ ትከል አንዱ ሲነቀል ካንዱ ተንጠልጠል
ሁለት ብልጥ ኑግ አያደቅ
ሁለት አይወዱ ከመነኩሴ አይወልዱ
ሁለት አይወዱ ከመነኮሱ አይወልዱ
ሁለት አይወዱም ከመነኮሱ አይወልዱም
ሁለት አገር አራሽ ለባልንጀራው አውራሽ
ሁለት አፎች ባይናከሱ ይናቀሱ
ሁለት እግር አለኝ ብሎ ሁለት ዛፍ አይወጡም
ሁለት እግር አለኝ ብሎ እሁለት ዛፍ አይወጣም
ሁለት እግር አለኝ ተብሎ ሁለት ዛፍ አይወጣም
ሁለት ወፎች ባይናከሱ ይናቀሱ
ሁለት የተመኘ አንድም አላገኘ
ሁለት የወደደ አንዱን ሳያገኝ ሄደ
ሁለት ጉድጓድ ያላት አይጥ አትሞትም
ሁለት ጊዜ በላህ ተፋህ
ሁለት ጊዜ ተናገርህ ከፋህ
ሁለት ጊዜ ተናግረህ ከፋህ
ሁለት ጊዜ ነው የዶሮ ልደት አንዱ በእንቁላል አንዱ በጫጩት
ሁለት ጊዜ ይፈርዱ ጉድ ይወልዱ
ሁለት ጥፉ ካገር ይጥፉ
ሁሉ ሄደ ተበተነ እህና እኔ ቀረነ አለ ያዘነ
ሁሉ ሄዶ ተበተነ እህና እኔ ቀረነ አለ እያዘነ
ሁሉ ሆነ ቃልቻ ማን ይሸከም ስልቻ
ሁሉ በእጄ ሁሉ በደጄ
ሁሉ ቢናገር ማን ይሰማል
ሁሉ አማረሽን ዲስኮ (disco) አታውጧት
ሁሉ አማረሽን ገበያ አታውጧት
ሁሉ አማረኝን ገበያ አታውጣት
ሁሉ አረሰ ማን ይሸምት
ሁሉ የሚገኝ ከእሱ የሚገኝ የለም ያለእርሱ
ሁሉ ያልፋል እስኪያልፍ ያለፋል
ሁሉ ያልፋል እውነት ብቻ ይተርፋል
ሁሉም ሰው መምሰሉ ባይታይ አመሉ
ሁሉም ሸክሙን ፍቅርም ያዥውን
ሁሉም በየዘመድህ ቢሉት አክንባሎ ጋጥ ገባ
ሁሉም በየዘርህ ቢሉት አከንባሎ ጋጣ ገባ
ሁሉም አካል ነው ግን እንደአይን አይሆንም
ሁሉም ከልኩ አያልፍም
ሁሉም ከኋላው ያገኘዋል እንደስራው
ሁሉም ወንፈሉን ፈታይም ድውሩን
ሁሉም ያልፋል እውነት ብቻ ይተርፋል
ሁሉም ያልፋል የሚኮርጅም ቢሆን
ሁሉም ያልፋል ግን እስኪያልፍ ያለፋል
ሁሉን ለእኔ አትበል
ሁሉን ቢናገሩት ሆድ ባዶ ይቀራል
ሁሉን አውቆ አሳውን እሾህ ከስጋው ለይቶ
ሁል ጊዜ ባሬራ ትበያለሽ ወይ አንዳንድ ጊዜ እንኳ ወጥ አትይሞይ
ሁል ጊዜ ከመደንገጥ አንድ ጊዜ መሸጥ
ሂ
ሂዳ ጉበት ቢነሷት ታናሽ ታላቅ ስደዱልኝ አለች
ሂዳ ጉበት የነሷት ታናሽ ታላቅ ስደዱልኝ አለች
ሂዳ ጉበት ይነሷታል ታናሽ ታላቅ ላኩልኝ አለች
ሂድ አትበለው እንደሚሄድ አርገው
ሂድ አትበለው እንዲሄድ አድርገው
ሂድ ካገር ኑር ካገር
ህ
ህልም ተፈርቶ ሳይተኛ አይታደርም
ህልም አለ ተብሎ ሳይተኛ አይታደርም
ህመሙ ቀርቶ ሞቱን በሰጠኝ
ህመሙ ቀርቶ ሞቱን በተወኝ
ህመሙን የሸሸገ መድሀኒት የለውም
ህመሙን የደበቀ መድሀኒቱም አልታወቀ
ህመሙን የደበቀ መድሀኒት የለውም
ህያዋን ለነገስታት ሙታን ለካህናት ይገብራሉ
ህዳር መማረሪያ ሰኔ መቃጠሪያ
ህግ ይኖራል ተተክሎ ስርአት ይኖራል ተዛውሮ
ሆ
ሆሆሆ ስቄ ልሙት አለ ሰውየው
ሆቴል ቢያብር ገንዘብ ያስገኛል
ሆደ ሰፊ ነገር አሳላፊ
ሆደ ሰፊ ይሻላል ከአኩራፊ
ሆዱ ሲሞላ ፍቅሩ ሌላ
ሆዱ ሲጎድል ሰው ያጋድል
ሆዱ ናረት ሙያው ከጅረት
ሆዱ ወድዶ አፉ ክዶ ክፉ ለምዶ
ሆዱ ፈሪ እግሩ ዳተኛ አዳም ሲዋጋ እርሱ ይተኛ
ሆዱን የወደደ ማእረጉን የጠላ
ሆዱን የወደደ ማእረጉን ይጠላል
ሆዱን ያለ ሆዱን ተወጋ
ሆዳም ሰው እንብርት የለውም
ሆዳም ቢሸከም የበላ ይመስለዋል
ሆዳም ቢፈተፍት የጠገበ ይመስለዋል
ሆዳም ፍቅር አያውቅም
ሆዴ ሆዴ የሚለውን ጌታ ያየዋል አይኔ አይኔ የሚለውን ሰው ያየዋል
ሆዴ በጀርባዬ ቢሆን ገፍቶ ገደል በጣለኝ
ሆዴ ኑር በዘዴ
ሆዴ አታጣላኝ ከዘመዴ
ሆዴን በልቶኝ ጎኔን ቢያኩኝ አይገባኝ
ሆድ ሆዴን የምትል ወፍ አለች ምናለች
ሆድ ለማታ በልቶ ለጠዋት
ሆድ ለባሰው ማጭድ አታውሰው
ሆድ ለባሰው ቢላዋ አታውሰው
ሆድ ለተተባሰው ማጭድ አታውሰው
ሆድ ሲሞላ ራስ ባዶ ይቀራል
ሆድ ሲያር ጥርስ ይስቃል
ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ
ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ጠዋት
ሆድ ባዶ ይጠላል
ሆድ ባዶን ይጠላል
ሆድ እንዳሳዩት ነው
ሆድ ከሁዳድ ይስፋል
ሆድ ካገር ይስፋል
ሆድ ወዶ አፍ ክዶ ክፉ ለምዶ
ሆድ ዘመድ ሳይወድ አፍ እህል ሳይለምድ
ሆድ የሸሸገውን ብቅል ያወጣዋል
ሆድ የኔ ነው ሲሉት ቁርጠት ሆኖ ይገድላል
ሆድ ያበላውን ያመሰገናል
ሆድ ያባውን ብቅል ያወጣዋል
ሆድህን ጎመን ሙላው ጀርባህን ለጠላት አታሳየው
ሆድና ግንባር አይሸሸጉም
ሆድና ግንባር አይሸሸግም
ሆድን በጎመን ቢደልሉት ጉልበት በዳገት ይለግማል
ሆድን በጎመን ቢደልሉት ጉልበት ዳገት ላይ ይለግማል
ተረት ለ
ለሀምሳ ጋን አንድ አሎሎ ይበቃል
ለሀብት መትጋት ሰውነትን ያከሳል ገንዘብን ማሰብ እንቅልፍ ይነሳል
ለሀጥአን የወረደ ለጻድቃን ይተርፋል
ለሁሉም ጊዜ አለው
ለሂያጅ የለውም ወዳጅ
ለህልም ምሳሌ የለውም
ለሆዳም ሰው ማብላት ውቅያኖስን ለመደልደል መቃጣት
ለሆዳም በሬ ገለባ ያዝለታል
ለሆዳም በሬ ጭድ ያዝለታል
ለሆዳም በሬ ቫት ተከፈለ
ለሆዳም በቅሎ ጭድ ያዝለታል
ለሆዴ ጠግቤ በልብሴ አንግቤ
ለሆድ ቁርጠት ብላበት ለራስ ምታት ጩህበት
ለላሙ መንጃ ለሸማው መቅደጃ
ለላሙ መንጃ ለሸማው መከንጃ
ለላም ቀንዷ አይከብዳትም
ለላም ከጥጃዋና ከአላቢዋ ማን ይቀርባታል
ለላም የሳር ለምለም
ለላም ጥጃዋ ለአህያ ውርንጭላዋ
ለሌለው ምን ትለው
ለሌባ ቅሌት ልብሱ ነው
ለልደት ያልሆነ ቀሚስ ይበጣጠስ
ለልጅ ሲሉ ይበሉ ለወዳጅ ሲሉ ይጠሉ
ለልጅ ሲሉ ይበሉ ለወገን ሲሉ ይጠሉ
ለልጅ አይስቁለትም ለውሻ አይሮጡለትም
ለልጅ ከሳቁለት ለውሻ ከሮጡለት
ለልጅ ጥርስህን ለዝንብ ቁስልህን
ለልጅ ጨዋታ ለባለጌ ቧልታ
ለሎሌው ምን ትለው
ለመሀን እምዬ ለአገልጋይ እትዬ ብርቋ ነው
ለመሄድና ለመላወስ አዛዥ ራስ
ለመሄድና ለመመለስ አዛዥ ራስ
ለመሆኑ ሳይሆን እንዴት ይሆናል ቢሆን
ለመማር ክፍል መግባት ለመኮረጅ ካሮት መብላት
ለመማር ክፍል መግባት ለማለፍ ካሮት መብላት
ለመስማት የፈጠንህ ለመናገርና ለቁጣ የዘገየህ ሁን
ለመስማት የፈጠንህ ለመናገር የዘገየህ ሁን
ለመስራት የሚያፍር መብላት አይደፍርም
ለመስራት ያፈረ ለመብላት ደፈረ
ለመስጠት አለመቸኮል ከሰጡም ወዲያ አለመጸጸት
ለመነኩሴ መልካም ሎሌ
ለመታማት መፍራት
ለመከራ ያለው መነኩሴ ዳዊቱን ሸጦ አህያ ይገዛል
ለመከራ የጣፈው ቢነግድ አይተርፈው
ለሙት የለው መብት
ለሚመለከት ለሚያየው ሞት ቅርብ ነው
ለሚስት ያጎርሷል ለተመታ ይክሷል
ለማረም ማን ብሎት ሲሰራው ግን ግድፈት
ለማን አለው ፈጣሪ አለው ጠጅ ለሌለው ውሀ አለው
ለማን ይፈርዱ ለወደዱ አይደለም ለወለዱ
ለማኝ ቢያብድ ስልቻውን አይጥልም
ለማኝ አያማርጥም ማር አይኮመጥጥም
ለማየት የፈለገ አይኑን ይገልጣል
ለማያቅህ ታጠን ብሎሀል ሀሰን
ለማያውቅ ፎገራ ዱሩ ነው
ለማያውቁሽ ታጠኚ
ለማያውቁሽ ታጥበሽ ቅረቢ
ለማይሞት መድሀኒት አለው
ለማይሰጥ ሰው ስጡኝ ማለትን ማን አስተማረው
ለማይሰጥ ሰው ስጡኝን ማን አስተማረው
ለማእበል ወደብ ለነፋስ ገደብ የለውም
ለምሽት መብራት ለመከራ ጊዜ ብልሀት
ለምክንያት ምክንያት አለው
ለምን ላለው ፈጣሪ አለው ጠጅ ለሌለው ውሃ አለው
ለምን ሰርግ ይሄዳል ሰርግ አለ በቤቱ
ለምን ተክዤ አምላክን ይዤ
ለምን ያለው ስልቻውን ጫን ያለው ኮርቻውን
ለምን ያለው ስልቻውን ጫን ያለው ኮርቻውን አያጣም
ለምን ጊዜው ነቀዝሽ
ለምኖ ለማኝ ቆቤን ቀማኝ
ለሞኝ ሰኔ በጋው መስከረም ክረምቱ
ለሞኝ ንገረው ምን ይሰማ ብዬ ለብልህ ንገረው ምን ይሳተው ብዬ
ለሞኝ ከሳቁለት ለውሻ ከሮጡለት
ለሞኝ ጉድጓድ አያሳዩትም ቤት ነው ብሎ ይገባበታል
ለሞፈር ቆራጭ እርፍ አይታየውም በግላጭ
ለረዥም ሰው ልብ እና ልብስ ያጥረዋል
ለረዥም መንገድ አትሩጥበት ለረዥም ነገር አትቸኩልበት
ለራሱ አያውቅ ነዳይ ቅቤ ለመነ ላዋይ
ለራሱ አያውቅ ጠንቋይ መድሀኒቱ ላዋይ
ለራሱ ጥላ ለእግሩ ከለላ
ለራሱ የማይረባ ለሌላም አይረባ
ለራሱ የማይረባ ለሰውም አይረባ
ለራስ ምታት ጩህበት ለሆድ ቁርጠት ብላበት
ለራሱ አያውቅ ሰው አይጠይቅ
ለራስ ሲቆርሱ አያሳንሱ
ለራስ ቢያወሩ ለቅንቅን ይዘሩ
ለራስ ቢያወሩ ለቅንቅን ይዘሩ አለች ዶሮ
ለራስ ከበጁ አይታጡ ደጁ
ለራበው ሰው ቆሎ ለቁልቁለት በቅሎ
ለራበው ባዶ መሶብ ማቅረብ
ለራት የማይተርፍ ዳረጎት
ለርስት ሴቶች ስንኳ ይሞቱበታል
ለሰማይ ምሰሶ የለው ለባእድ ስር የለው
ለሰለባ የመጣ ልብስ ቢጥሉለት አይመለስ
ለሰለባ የመጣ ልብስ ቢጥሉለት አይመለስም
ለሰበበኛ ቂጥ መረቅ አታብዛበት
ለሰባቂ ጆሮህን አትስጠው
ለሰው ልጅ ሲያበሉ ለውሻ ልጅ ያብሉ
ለሰው ልጅ ከሚያበሉ ለውሻ ልጅ ያብሉ
ለሰው ልጅ ከማብላት ለውሻ ልጅ ማብላት
ለሰው ልጅ እውቀት ለጦጣ ብልጠት
ለሰው ሞት አነሰው
ለሰው ሞት አነሰው ውሻውንስ ፈሴ መለሰው አለች ቀበሮ
ለሰው ቢነግሩት ለሰው
ለሰው ቢናገሩ መልሶ ለሰው ጫር ጫር አድርጌ አፈር ላልብሰው
ለሰው ብሎ መሞት አምላክነት ያሻል
ለሰው ብሎ ሲያማ ለኔ ብለህ ስማ
ለሰው ብትል ትጠፋለህ ለእግዜር ብትል ትለማለህ
ለሰው እንግዳ ላገሩ ባዳ
ለሰው እንዴት F አነሰው
ለሰው ከበሬታው ሰው ለወጥ ማጣፈጫው ጨው
ለሰው ጠላቱ ይወጣል ከቤቱ
ለሰው የማይል ሰው ሞትም ሲያንሰው
ለሰው ብሎ ሲያማ ለእኔ ብለህ ስማ
ለሴትና ለጉም አይዘነጉም
ለሰይጣን አትስጠው ስልጣን
ለእሳት ውሀ ለጸጉር ቡሀ
ለሴት ልጅ እስከአርባ ቀን ሞቷን ከዚያ ወዲያ ሀብቷን
ለሴት ምስጢር ማውራት በወንፊት መቅዳት
ለሴት ምክር አይገባትም
ለሴትና ለጉም አይዘነጉም
ለሴት ጠላ ለፈረስ ቆላ
ለስሟ መጠሪያ ቁና ሰፋች
ለስሱ ፍትፍት አሳይቶ እበት ያጎርሷል
ለሸማኔ ማገጃ ስለት ማረጃ
ለሹመት ካልመከሩለት ለጥርስ ካልነከሩለት
ለሹመት ካልመከሩለት ለጥርስ ካልከደኑለት
ለሹመት ያደለው የለማኝ አለቃ ይሆናል
ለሺ ፍልጥ ማሰሪያው ልጥ
ለቀላል ምስጢር መንገር በቀዳዳ ጤፍ መቋጠር
ለቀላል ሰው ምስጢር መንገር በቀዳዳ ጤፍ መቋጠር
ለቀላል ሰው ምስጢር መንገር በቀዳዳ አቁማዳ ጤፍ መቋጠር
ለቀማኛ የለውም እጅ ለበቅሎ የለውም ልጅ
ለቀበጠች አማት ሲሶ በትር አላት
ለቀባሪው አረዱት
ለቀን ቀጠሮ ለሴት ወይዘሮ
ለቀንዳም በሬ ቤት አትከልክለው ቀንዱ ይከልክለው
ለቀንዳም በሬ ቤት አትከልክለው ቀንዱ ይከለክለዋል
ለቁንጫ ለምጽ ያወጣል
ለቁንጫ መላላጫ
ለቂጡ ጨርቅ የለው ቆንጆ ያባብላል
ለቅልብልብ አማት ሲሶ በትር አላት
ለቅሶ ሳለ ከቤት ይሄዳል ጎረቤት
ለቅናት የለውም ጥናት
ለቅዘን እግር አንስተውለት ለውሻ ሮጠውለት
ለቆመ ሰማይ ቅርቡ ነው
ለቆማጣ አንድ ጣት ብርቁ ናት
ለበራ ወለባ ለውሻ ገለባ
ለበጋ ጥጃ ውስ አነሰው ወይ
ለበግ ደጋ ለምቾት አልጋ
ለቡናሽ ቁርስ የለሽ ለነገርሽ ለዛ የለሽ
ለባለጌ ገድሉ ውርደቱ
ለቤት ሳማ ለውጭ ቄጤማ
ለቤት ሳንቃ ለሰው አለቃ
ለቤት ሳንቃ ለነገር ጠበቃ
ለቤት ባላ ለችግር ነጠላ
ለብልህ ንገረው ምን ይስተው ብዬ ለሞኝ ንገረው ምን ይገባው ብዬ
ለብልህ አይነግሩ ለድመት አያበሩ
ለብልህ አይነግሩ ላንበሳ አይመትሩ
ለብልህ አይነግሩ ለንጉስ አይመክሩ
ለብልህ አይነግሩም ለንጉስ አይመክሩም
ለብልህ አይነግሩ ካልጠየቀ በስተቀር
ለተማሪ ቆሎ ለወታደር በቅሎ
ለተሟጋች መዘዘኛ የዳኛ ትእግስተኛ
ለተረታው ያበደረ እሳት ጨመረ
ለተራበ ግብር ለተበደለ ነገር
ለተራበ በግብር ለተበደለ በነገር
ለተራበ ቂጣ ለተጠማ ዋንጫ
ለተሸሸገ ምግብ የተሸሸገ ሆድ አይጠፋለትም
ለተሾመ ይሟገቱለታል ለተሻረ ይመሰክሩበታል
ለተሾመው ይመሰክሩለታል ለተሻረው ይመሰክሩበታል
ለተሾመ ይመሰክሩለታል ለተሻረ ይመሰክሩበታል
ለተቀማጭ ሰማይ ቅርቡ ነው
ለተባባሰው ማጭድ አታውሰው
ለተንኮለኛ ሲሉ ይሰበስባሉ ለቅን ይፈርዳሉ
ለተወገረ የማያዝን እንብርት የለውም
ለትኋን ልጓም ማጉረስ ላፈኛ ሰው መመለስ
ለትኋን ልጓም ማጉረስ ላፈኛ ሰው መመለስ አይቻልም
ለቸኮለ ሰው ዋንጫ አስጨብጠው
ለችግር የፈጠረው ቢነግድ አይተርፈው
ለነገረኛ ሰው ጀርባህን ስጠው
ለነገረኛ ነገር ተውለት ለሆዳም እህል አቅርብለት
ለኔ ነግ በኔ
ለንጉስ የማይገዛ ለእግዚአብሄር አይገዛ
ለንጉስ ያልረዳ ከባህር የማይቀዳ
ለንጉስ ያልረዳ ከባህር ያልቀዳ
ለንፉግ ሰው የገበያ መንገድ ይጠበዋል
ለንፉግ ሰው የገበያ መንገድ ይጠበው
ለአህያ ማር አይጥማትም
ለአምላክ ልንገረው ለማያስቀረው
ለአበባ የለው ገለባ
ለአቤቱታ የለው ይሉኝታ
ለአንበሳ አታበድር ካበደርክ አትጠይቅ
ለአንተ ያለውን እንጀራ ይሻግታል እንጂ ማንም አይበላውም
ለአኩራፊ ምሳው እራት ይሆነዋል
ለአይነ ስውር መስተዋት
ለአይንና ለወዳጅ ጥቂት ይበቃል
ለአይን የሚከፋ ለአፍንጫ ይከረፋ
ለአዋጅ ነጋሪት ለጥጥ ልቃቂት
ለአገሩ እንግዳ ለሰው ባዳ
ለአፈ ግም አፍንጫ ድፍን ያዝለታል
ለአፉ ለከት የለውም
ለአፍታ የለውም ፋታ
ለአፍ ዳገት የለውም
ለእሳት እንጨት ካልነሱት አይጠፋም
ለእሳት እንጨት ካልነፈጉት አይጠፋም
ለእሳት ውሀ ለጸጉር ቡሀ
ለእሳት ፍላት ለጮማ ስባት
ለእበጥ ፍላት ለእንጨት እሳት
ለእባብ እግር የለው ለሞኝ መላ የለው
ለእብለት ስር የለው ለእባብ እግር የለው
ለእብለት ስር የለውም ለእባብ እግር የለውም
ለእበጥ ፍላት ለእንጨት እሳት
ለእኔ እናት ምን ደላት ያም አፈር ያም ድንጋይ ጫነባት
ለእውር ዝማሜ ለመላጣ ጋሜ
ለእጅ ርቆ ለአይን ጠልቆ
ለእግሩ የተጠየፈ ለቂጡ አተረፈ
ለእግር የፈሩት ለቂጥ ይተርፋል
ለእግዚአብሄር የቀነቀነ ለጽድቅ ለጌታ የቀነቀነ ለወርቅ
ለእውነት ማማ ለውሸት ጨለማ
ለከለላ ጥላ ቢርብህ ብላ
ለከሳሽ የለው መላሽ
ለካህን ጥምቀት ለገበሬ ግንቦት
ለክፋት ያደለው አሳዳጊ የበደለው
ለኮ መሳቢያ ወፍጮ ማላሚያ
ለወሬ ሞትሁ
ለወሬ ሞትሁ ለእህል ሰለፍኩ
ለወሬ ወዳጁ ወሬ ለመነኩሴ ጥሬ
ለወሬ የለው ፍሬ
ለወሬ የለው ፍሬ ለአበባ የለው ገለባ
ለወሬ የቸኮለ እናቱን በመንገድ ይረዳል
ለወርቅ ያሉት አንገት ላሽክት
ለወታደር ሰፊ መንደር ለወዲላ መልካም ዱላ
ለወይዘሮ መልካም ዶሮ
ለወደላ መልካም ዱላ
ለወዳጅ የማር ወለላ ለጠላት አሜኬላ
ለወዳጅና ለአይን ትንሽ ይበቃዋል
ለወጡም እዘኑለት ከእንጀራውም ጉረሱለት
ለወጡ ጊዜስ ከደረቁም
ለወጡም እዘኑለት ከደረቁም ብሉለት
ለወጥ የሚሻል ቅልውጥ
ለዋንጫ ቡሽ ለውሀ ጉሽ የለውም
ለዋስ አፍ የለው ለጉንዳን ደም የለው
ለውሻ ምሳ የለው ራት ብቻ
ለውሻ ሞት ፊት አይነጩለትም
ለውሻዬ ያልሁትን ልጄ ቢበላብኝ አልወድም
ለውሽማ ሞት ፊት አይነጩለትም
ለውጡኝ ባይ የሚሻለውን አውቆ
ለዘመዴ ያዝናል ሆዴ
ለዚህ ሆዴ ጠላኝ ዘመዴ
ለዝናም ጌታ ውሀ ነሱ
ለዝናም ጌታ ውሀ ነሱት
ለዝንብ ከትላንት ወዲያም ድሮ ነው
ለይቶ እንደፈፋ አንጓሎ እንዳረፋ
ለይቶት አባ ንጉሷ
ለደህና ሰው ዋጋ አነሰው
ለደህና ሰው ውሸት ለጅብ እሸት
ለደብተራ መቋሚያና ጭራ
ለደደብ ማስረዳት ድንጋይ ቅቤ መቀባት
ለደግ ንጉስ እለት እለት ማልቀስ
ለዳርቻው ሲሳሱ መካከሉን ተነሱ
ለዳርቻው ሲሳሱ ከነመሀሉም ተነሱ
ለዳባ ለባሽ ነገርህን አታበላሽ
ለዳኛ አመልክት እንዲሆን መሰረት
ለዳኛ የነገሩት በርጥብ ያቃጠሉት
ለዳኛ ዳኛ አለው ለአንበሳ ተኩላ አለው
ለድሀ ማን ሰጠው ውሀ
ለድህነት የፈጠረው ቢነግድ አይተርፈው
ለድህነት የፈጠረው ቢነግድ አያተርፍም
ለድሪ ያሉት አንገት ለአሸንክታብ
ለድሪ ያሉት አንገት ላሽክት
ለድካም የጣፈኝ ብነግድ አይተርፈኝ
ለዶሮ ሲነገሩ ምጥማጥ ይሰማል
ለጆሮ ጥርስ ለሆዳም ስስ
ለገላጋይ ደም የለውም
ለገበሬ መልካም በሬ
ለገቢህ ተንገብገብ
ለገና ጨዋታ አይቆጡም ጌታ
ለገደለ ጎፈሬ ላረጋገጠ ወሬ
ለገዳም የረዳ አይጎዳ
ለጉንዳን ደም የለው ለዝንብ ቤት የለው
ለጉንዳን ደም የለው ለገንዘብ ቤት የለው
ለጋስ ቢለግስ አበደረ እንጂ አልሰጠም
ለጋስ ቢለግስ አበደረ እንጂ እንዲያው አልሰጠም
ለእግዜር የተቀናቀነ ጽድቅ ለንጉስ የተቀናቀነ ወርቅ
ለጎበዝ ስጠው ሰንጋ ፈረስ
ለጠላትህ እንደ ዳቦ እስኪገምጥህ አትመቸው
ለጠቢብ አንድ ቃል ይበቃል
ለጠጪ ሰው የመጠጥ ወሬ አውራው
ለጥልና ለዳኛ ያለው ገንዘብ አፋፍ ይቆያል
ለጥርጣሬ ምንጣሬ
ለጥቅም ሲታጠቁ ከጎን ይጠንቀቁ
ለጥቅምት ያልሆነ ቀሚስ ይበጣጠስ
ለውጠኝ ባይ የሚሻለውን አውቆ
ለጨለማ ጊዜ መብራት ለመከራ ጊዜ ብልሀት
ለጨቅጫቃ ሰው ከማበደር ይሻላል በጄ ማደር
ለጭሰኛ መሬት ለሳር ቤት ክብሪት
ለጾም ግድፈት ለበአል ሽረት
ለጾም ግድፈት ለባል ሽረት
ለፈረስህ አንገት ለጋሻህ እንብርት
ለፈሪና ለንፉግ እያደር ይቆጨዋል
ለፈሪ ሜዳ አይነሱም
ለፈሪ ምድር አይበቃውም
ለፈሪ ይበቃል ፍርፋሪ
ለፈሪ ስጠው ፍርፋሪ
ለፋሲካ የተዳረች ሁል ጊዜ የፋሲካ ይመስላታል
ለፍቅር ብተኛት ለጠብ አረገዘች
ለፍቅር የለውም ድውር
ለፍየል ቆላ ለሙክት ባቄላ
ለፍየል ህመም በሬ ማረድ
ለፍየል ስም አውጣ ቢለው ሞት አይደርስ አለው
ሊበሉዋት ያሰብዋትን አሞራ ይሏታል ጂግራ
ሊወጋ የመጣ ጌታዬ ቢሉት አይመለስም
ሊያልፍ ውሀ አደረገኝ ድሀ
ሊያስቡት አይገድም
ሊጣላ የመጣ ሰብብ አያጣም
ላህያ ፈስ አፍንጫ አይዙለትም
ላህያ ማር አይጥማት
ላህያ ያልከበደው ለመጫኛ ከበደው
ላለው ቅንጭብ ያረግዳል
ላለው ይጨመርለታል
ላለፈ አይጸጸቱም ለሚመጣው አይበለጡም
ላለፈው አይጸጸቱም ለሚመጣው አይበለጡም
ላለፈው ክረምት ቤት አይሰራለትም
ላለፈው ክረምት ውሀ ማቆር አይቻልም
ላለፈው ጸሎት ከንቱ ጩኸት
ላሊበላ ሄደሽ ከህንጻው ብትሰፍሪ አይገኝም ጽድቅ አለ ባህሪ
ላሊበላ አደራውን አይበላ
ላሊበላ የቃሉን አይበላ
ላሊበላን ካላጠገቡት ይጮሀል ሎሌም ካልሰጡት ይከዳል
ላላየ ልጅ ዳቦ ፍሪዳው
ላላየው የሚያስገርም ለሰማው የሚያስደንቅ
ላላዩ ልጅ ዳቦ ፍሪዳው
ላላወቀው ፎገራ ዱር ነው
ላመት ልብስ ለእለት ጉርስ
ላሜ ቦራ የልጆቼን ነገር አደራ
ላም ሲበዘበዝ ጭራዋን ያዝ
ላም ቀንዷ አይከብዳትም
ላም በረቱን የሰው ልጅ አባቱን አይረሳም
ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ
ላም አለኝ በሰማይ ወተትዋንም አላይ
ላም አለኝ በሰማይ ገመድ እፈልጋለሁ
ላም እሳት ወለደች እንዳትልሰው ፈጃት እንዳትተወውም ልጅ ሆነባት
ላም ከወንዝ ልጅ ከቦዝ
ላንተ መምከር ጥቁር ድንጋይ ላይ ውሀ ማፍሰስ ነው
ላንቺ ቁምነገርሽ በሶብላ ወጥሽ
ላንቺ ብርቅሽ በሶቢላ ወጥሽ
ላያዘልቅ ጸሎት ለቅስፈት
ላይቀርልኝ እዳ በጊዜ ልሰናዳ
ሌባ ላመሉ ቅድመ እውቅና አገኘ
ሌባ ላመሉ ንግድ ይላል
ሌባ ላመሉ ዳቦ ይልሳል
ሌባ እናት ልጇን አታምንም
ሌባን ሌባ ቢሰርቀው እንዴት ይደንቀው
ልባም ሴት ለባልዋ ዘውድ ናት
ልብስህን በውሀ ገንዘብህን በድሀ
ልብ ካላየ አይን አያይም
ልብ ካላየ አይን አይፈርድም
ልትደርቅ የደረሰች ምንጭ ጭልጭል ትላለች
ልትሰራ ሂዳ ተላጭታ መጣች
ልጅም ከሆነ ይገፋል ድንችም ከሆነ ይጠፋል
ልጅ ለናቷ ምጥ አስተማረች
ልጅ ምን ቢሮጥ አባቱን አይቀድምም
ልጅ ሳለህ አጊጥ ሞል ሳይዘጋ ሸምት
ልጅ ቢያኮርፍ ቁርሱ እራት ይሆናል
ልጅና እሳት ባለቤቱ ያጠፋዋል
ልጅን አሳዳጊ እሳትን ውሀ ያጠፋዋል
ልጅና ወረቀት የያዘውን አይለቅም
ልጅና ጦጣ ውሀ ይጠጣ
ልጅ ያቦካው ለእራት አይሆንም
ልጅ ይወለዳል ከቦዝ ላም ይገዛል ከወንዝ
ልጅ ደረሰ ቤት ፈረሰ
ልግመኛ ባሪያ መጇን ትደብቃለች
ልግመኛ አጋዥ ብታገኝ መጅ ደበቀች
ልግመኛን መምከር ውሀ በወንፊት ማኖር
ልፋት ቢያምርህ መሬት ግዛ ችግር ቢያምርህ ልጅ አብዛ
ልፋ ያለው ሊስትሮ እግር ስር ይውላል
ልፋ ያለው ምረጡኝ አለ
ልፋ ያለው በህልሙ ሲሸከም ያድራል
ልፋ ያለው አንድ እንጨት ያስራል
ልፋ ያለው በሬ ቆዳው ለከበሮ
ልፋ ያለው ቢን ላደንን ይፈልጋል
ልፋ ያለው አንድ እንጨት ያስራል
ሎሌ ለስህተት ጌታ ለምህረት
ሎሌ ሲከብር ጌታውን ይከሳል ሙክት ሲሰባ ሾተሉን ይልሳል
ሎሌ ያገለገለውን ይቆጥራል ጌታ ያስቀየመውን ያስባል
ሎሌና አሞሌ ካዘዙት ይውላል
ሎሚ ካልመጠጡት እምቧይ ነው
ሎሚ ካልመጠጡት እምቧይ ዳቦ ካልገመጡት ድንጋይ
ሎሚና ትርንጎ ሞልቶልህ ባገር እንቧይ ታሸታለህ የድሀ ነገር
ሎሚና ትርንጎ ሞልቶ ባገር እንቧይ ያሸታል አወይ የድሀ ነገር
ሎሚ ቢያብብ ቢኖርና መልካም ሽታ ቢሰጥ መኮምጠጡን አይተውም
ተረት መ
ተረት ሸ
ሸማ ለብሶ ስልቻ በቅሎ ጭኖ ለብቻ
ሸማ ማዋስ ለባላገር በቅሎ ማዋስ ለወታደር
ሸማ በውሀ ሰው በንስሀ
ሸማን በውሀ ሰውነትን በንስሀ
ሸማ በየፈርጁ ይለበሳል
ሸማና ምስጥ ወደ ውስጥ
ሸማኔ በመኑ ጠይብ በከሰሉ
ሸማኔ በድሩ ጠይብ በመንደሩ
ሸማኔ ድውሩን ባለስልጣን ክብሩን
ሸማን ጠምዞ ያሰጧል እህልን አላምጦ ይበሏል
ሸምበቆ በመርዘሙ አይሆንም ምሰሶ
ሸምበቆ በመርዘሙ ምሰሶ አይሆንም
ሸርሙጣ ስታረጅ አቃጣሪ ትሆናለች
ሸርሙጣን የወደደ ልብሱን ጥሎ አበደ
ሸርሙጣን የወደደ ልብሱን ጥሎ ያበደ
ሸኚና ጥላ ቤት አይገባም
ሸኚ ቤት አያደርስም
ሸኝ ቤት አይገባም
ሸክላ ቢጥሉት ገለባ
ሹመት ላወቀው ይከብደዋል ላላወቀው ያሳብደዋል
ሹመት ሲገኝ ዘመድ አይገድም
ሹመት ሺህ ሞት
ሹመት በተርታ ስጋ በገበታ
ሹመት የለመደ ወንዝ ዳር ይወርዳል
ሹመትና ቁመት ከልኩ አያልፍም
ሹመትና ቁመት አይገኝም በምኞት
ሹም ለመነ አዘዘ
ሹም ለሹም ያወርሳል ጉም ተራራ ያለብሳል
ሹም ለሹም ይጎራረሳል ድሀ ለድሀ ይለቃቀሳል
ሹም መክሰስ ወጀድ ማረስ አይቸግርም
ሹም ሲቆጣ ማር ይዞ እደጁ ደስ ሲለው ማር ይዞ እደጁ
ሹም ቢሞት ሀምሳ የሹም ልጅ ቢሞት መቶ ሀምሳ
ሹም ቢሞት ቀባሪው ሀምሳ የሹም ልጅ ቢሞት መቶ ሀምሳ
ሹም ያዛል ቄስ ይናዝዛል
ሹምና ማር እያደር ይከብዳል
ሹምና የጋማ ከብት በጊዜ ይከተት
ሹምና ጥጥ እያደር ይከብዳል
ሹምና ጥጥ እያደር ይከዳል
ሹሩባ ትሰራ ሄዳ ጠጉሩዋን ተላጭታ መጣች
ሹክሹክታ የጠብ ወለምታ
ሺ መት ሺ ሞት
ሺም ታለበ አንድ ያው በገሌ
ሺ በመከረ አንድ በወረወረ
ሺ በመከር አንድ በወረወር
ሺ አውል ሲሞት ሺህ ይሙት
ሺ አውል ከሚሞት ሺ ይሙት
ሺ አውል ኪሞት ሺ ይሙት
ሺ ይሙቱ ሺ አውል አይሙት
ሺ ዝንብ መሶብ አይከፍትም
ሺህ ቢታለብ አንድ በገሌ አለች ድመት
ሺ ቢታለቡ ከገሌ አላልፍም አለች ድመት
ሺ ቢያጩሽ አንድ ያገባሽ
ሺ ያጭሽ አንድ ያገባሽ
ሻማ ራሱ ነዶ ራሱ ብርሀን ይሰጣል
ሻሽ ይደምቃል ማቅ ይሞቃል የሚበጀውን ባለቤቱ ያውቃል
ሻጭ ገዥ ሆኖ ይገምታል
ሽልም እንደሆን ይገፋል ቂጥም እንደሆን ይጠፋል
ሽል ከሆነ ይገፋል ቂጣም ከሆነ ይጠፋል
ሽል እንደሆን ይገፋል ቂጣም እንደሆን ይጠፋል
ሽመልና ዘንግ ቂልና በግ
ሽማግሌ ሳለ ምክር አይጠፋም ጎልማሳ ሳለ ላም አይነዳም
ሽማግሌ በምክሩ አርበኛ በሰናድሩ
ሽማግሌ ካለበት ነገር አይናቅበት
ሽማግሌ ካለበት ነገር አይሰረቅ ጎበዝ ካለበት በትር አይነጠቅ
ሽማግሌ ካልሞተ ስንዴ ካልመረተ
ሽማግሌ ካልሞተ ስንዴ ካልሸተ
ሽማግሌ ይገላግላል የተጠቃ አቤት ይላል
ሽማግሌና ስልቻ ሳይሞሉ አይቆሙም
ሽማግሌና ጅብ በላላባት ይገባል
ሽማግሌን ከምክር ከመለየት ከምግብ መለየት
ሽሮን ሲሸውዷት ፕሮቲን ነሽ አሏት
ሽሽት ከኡኡታ በፊት
ሽበት ምን ታረግ መጣህ ቢሉት እኖር ብዬ አለ
ሽበት እኖር ብዬ መጥቻለሁ አለ
ሽታና ግማት ላልሰማ ማውራት
ሽንብራ መኖር በመከራ
ሽንኩርት አንድም በሉት ገማ ደገሙትም ገማ
ሽንኩርት የባህሪውን ይሸታል
ሾላ በድፍን
ሾተልን ወደ ሰገባህ ቁጣህን ወደ ትእግስት
ሾተልን ወደ አራዊት ቁጣህን ወደ ትእግስት
ሾተልን ወደ አፎት ቁጣን ወደ ትእግስት
ሽሮ ቢደነፋ እንጀራ እስኪቀርብ ነው
ተረት ቀ
ቀለም ሲበጠበጥ ብርእ ሲቀረጥ
ቀለም በቀንድ ውስጥ ጨለማ ነው ሲፃፍ ግን ብርሃን ነው
ቀለም ሲበጠበጥ ብርእ ቅረጹልኝ
ቀለበት ለቆማጣ ሚዶ ለመላጣ
ቀሊል አማት ሲሶ በትር አላት
ቀላጅ የሰይጣን ወዳጅ
ቀላዋጭ ወጥ ያውቃል
ቀልብ የሌለው ውሻ ጠዲቅ አምጡልኝ ይላል
ቀልድና ቅዘን ቤት ያጠፋል
ቀልደኛ አልቅሶ ካልተናገረ የሚያምነው የለም
ቀልደኛ ገበሬ ሲያስቀን አደረ
ቀልደኛ ገበሬ ናይት ክለብ ከፈተ
ቀልደኛ ጎረምሳ እያራ ያፏጫል
ቀልድና ቅዘን ቤት ያበላሻል
ቀሙን ላይቀር ከነጫማቸው
ቀማኛና ሽፍታ ጭለማና ማታ
ቀርቀሬ ወርጄ ማር ስልስ ማር ልከፍል
ቀስ በመቀስ አንቁላል በአግሩይሂዳል
ቀስ እንዳይደፈረስ
ቀስ እንዳይፈስ
ቀስ በቀስ እንቁላል በእግሩ ይሄዳል
ቀስ በቀስ አባይም ዝናብ ይሆናል
ቀበሮ ናት የገጠሩዋ ሚዳቋ ናት የሰፈሩዋ
ቀበሮ የበሬ ቆለጥ ይወድቅልኛል ብላ ስትከተል ዋለች
ቀበቶ ለማፈኛ ሰንሰለት ለማቆራኛ
ቀበኛ ማሰሪያውን በልቶ ያሳጥራል
ቀበኛ ከብት ዋጋውን ያደርስ
ቀባሪ በፈጣሪ
ቀብረው ሲመለሱ እግዜር ይማርዎ
ቀብሮ የሚመለስ የሚመለስ አይመስለውም
ቀኑ የጨለመበት መንገዱ ዘንግ ነው
ቀና ሲታጣ ይመለመላል ጎባጣ
ቀና ቢታጣ ይመለመላል ጎባጣ
ቀናውን ብነግራት ውልግድግዱን አለች
ቀን ስው መስሎ ማታ ጅራት አብቅሎ
ቀን ሲከፋ በግ ይነክሳል
ቀን ሲጥለው ሁሉ ይጠላው
ቀን ሲገለበጥ ውሀ ወደ ላይ ይፈሳል
ቀን ሲደርስ አምባ ይፈርስ
ቀን ሳይቆጥሩ ውሻ ሳይጠሩ ደረሰ በእግሩ
ቀንበር ታርቆ ጣውንት ታርቆ ምን ይሆናል
ቀንበር ታንቆ ጣውንት ታርቆ ምን ይሆናል
ቀን በበቅሎ ማታ በቆሎ
ቀን በቅሎ ማታ ቆሎ
ቀን ቢረዝም ልብ ያደክም
ቀን ቢረዝም ልብ ይደክም
ቀን ቢቆጥሩ ውሻ ቢጠሩ ደረሰ በእግሩ
ቀን ቢቆጥሩ ውሻ ቢጠሩ ይደርሳል በእግሩ
ቀን ባጀብ ሌት በዘብ
ቀን አይጥለው የቀለም ሰረገላ አያሰናክለው
ቀን አይጥለው ጠጅ አያስክረው
ቀን አይጥለው ጠጅ አያሰክረው የለም
ቀን እስኪወጣ ያባቴ ገበሬ ያግባኝ
ቀን እስኪያልፍልሽ ያባትሽ ሎሌ ያግባሽ
ቀን እስኪያልፍ ያለፋል
ቀን እስኪያልፍ ያባቴ ባሪያ ያግባኝ
ቀን እስኪያልፍ ያባቴ ባሪያ ይግዛኝ
ቀን እንደተራዳ ሌት እንደ ግርግዳ
ቀን ከህዝብ ሌት ከጅብ
ቀን ከጣለው ሁሉ ይጥለው
ቀን ካልለቀሙ ሌት አይቅሙ
ቀን ካለቀሙ ሌት አይቅሙ
ቀን የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራል
ቀን የጎደለበት ጠገራ አይጥ ይበላዋል
ቀን ይነዳ እንደ ፍሪዳ
ቀንና ጨርቅ እንደምንም ያልቅ
ቀንና ጨርቅ ያልቃል ብልህ ያውቃል
ቀንዳምን በሬ ቀንድ ቀንዱን
ቀንዱ ሰማይ ጠቀስ ጭራው ምድር አበስ
ቀንድ ካላት ላም ጎዳ ትከፋለች
ቀንድና ጅራት ለዋንጫ አለፉ
ቀንድ እገባበት ጅራት አይቀርም
ቀንድ ውስጥ ገብቶ ጅራት አይቀርም
ቀኝም ሰገሩ ግራም ሰገሩ መገናኛው ኮሩ
ቀድሞ ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ አሁን ምን ያደርጋል ድስት ጥዶ ማልቀስ
ቀድሞ ነበር እንጂ ተራምዶ ማለፍ አሁን ምን ይሆናል ተይዞ መለፍለፍ
ቀይ ምላሱ ጥቁር እራሱ
ቀይ ሰው መልክ አይፈጅም
ቀይ እንደበርበሬ ጥሩ እንደ ብርሌ
ቀዳዳ ያፈሳል ግቢ ያፈርሳል
ቀድሞ ሰኞን አለመሆን ነው
ቀድሞ የሸተውን ወፍ ይበላዋል ቀድሞ የሚናገረውን ሰው ይጠላዋል
ቀድሞ የሸተውን ወፍ ይበላዋል ቀድሞ የተናገረውን ሰው ይጠላዋል
ቀዶ ያለበሰ ቆርሶ ያጎረሰ
ቀጥኜ ቢያየኝ ጅማት ለመነኝ
ቀጥኜ ቢያዩኝ ጅማት ለመኑኝ
ቀጥኜ ቢያዩኝ ሞዴል ነሽ አሉኝ
ቁልቢጥ የላት ቁና አማራት
ቁልቢጥ የላት ድርጎ አማራት
ቁመህ ተከራከር ዙረህ ተመካከር
ቁመህ ተናገር ዙረህ ተመካከር
ቁመቷ ቢያጥር እንደ ድምብላል ውዷ ክፉ ነው ይደበልላል
ቁም እንደአላማ ቁረጥ እንደጫማ
ቁም እንዳላማ ጥልቅ እንደጫማ
ቁም ነገረኛ መምሰል የተለመደ አመል
ቁም ነገር ይዞ ተረት ቂም ይዞ ጸሎት
ቁራ ሲነጣ አህያ ቀንድ ያወጣ
ቁራ ስሙን የጠራ
ቁርበት ምን ያንቋቋሀል ቢሉት ባያድለኝ ነው እንጂ የነጋሪት ወንድም ነበርኩ አለ
ቁርበት ምን ያንጓጓሀል ቢሉት ባያድለኝ ነው እንጂ የነጋሪት ወንድም ነበርኩ አለ
ቁርጥማት ቢያብር አልጋ ላይ ያማቅቃል
ቁርጥ ያጠግባል ተስፋ ያታልላል
ቁቅም ከፈስ ተቆጠረች
ቁና ለመስፈሪያ ብርብራ ለማስከሪያ
ቁንጥጫ ይሻላል ከግልምጫ
ቁንጫ ለትልቅ ሰው ይበረታል ይባላል
ቁንጫ መሄድ ሳትማር መዝለል ትማራለች
ቁንጫ ሞኝ ናት ቀን ትበራለች ተለቃቅማ ታልቃለች
ቁንጫ ውሀ ወረጅ ቢሏት ስፈናጠር የሰው ዶጮ እሰብር አለች
ቁጥቋጦም ሲያድግ ዛፍ ይሆናል
ቁጥቋጦ ሲያድግ ዛፍ ይሆናል
ቁጥቋጦ ያለዛፍ አይሆንም
ቁጩና ብስጩ አልማችሁ ፍጩ
ቁጭትና መረቅ ለጊዜው ይጣፍጣል
ቁጭትና መጠጥ ለጊዜው ይጣፍጥ
ቁፍ ቁፍ አሰኘሽ እንደቄብ ዶሮ ለመከራ ላሳርሽ ኖሮ
ቂል ሲረግሙት የመረቁት ይመስለዋል
ቂል አይሙት እንዲያጫውት
ቂልን ለብቻው ስደበው ራሱን ባደባባይ እንዲሰደብ
ቂልን አንድ ጊዜ ስደበው ሲሰደብ ይኖራል
ቂልን ድንጋይ ተማትቶ ጌታና ሎሌ ተሟግቶ የማይሆን ነው ከቶ
ቂል ከጠገበበት አይወጣም
ቂል ያገኘው ፈሊጥ ውሻ የደፋው ሊጥ
ቂምህን አትርሳ የወደቀን አንሳ
ቂም ይዞ ጸሎት ሳል ይዞ ስርቆት
ቂም ይዞ ጸሎት ጭድ አዝሎ ወዘት
ቂጡን የተወጋ ውሻ እንደልቡ አይጮህም
ቂጡ የቆሰለ ውሻ እንደልቡ አይጮህም
ቂጥ ቢወድል ፈስ አያድን
ቂጥ ቢያብጥ ልብ አይሆንም
ቂጥኛም ከውርዴ ይማከራል
ቂጥኛም ከውርዴ ይውላል
ቂጥ ገልቦ ክንብንብ
ቂም ቂም ያሰኘሽ እንደዶሮ ለካስ ለመከራሽ ላሳርሽ ኖሮ
ቂፍ ቂፍ ያሰኘሽ እንደ ቄብ ዶሮ ለመከራሽ ላሳርሽ ኖሮ
ቃልህ ሳይዘጋ እግርህ ሳይዘረጋ
ቄሱም ዝም መጽሀፉም ዝም
ቄስ ለኑዛዜ ፍቅር ለሚዜ
ቄስ ምን ይሻል ጠላ ነገር ምን ይሻል ችላ
ቄስ ኤርክሶን መምህሩ እናት አያስቀብሩ
ቄስ እበር አረመኔ ከማህበር
ቄስ ካናዘዘው እድሜ ያናዘዘው
ቄስ ካፈረሰ ዲያቆን ከረከሰ
ቄስና ንብ እያዩ እሳት ይገባሉ
ቄስና ንብ እያየ እሳት ይገባል
ቄስ ያዘዘህን አድርግ እንጂ ቄስ ያደረገውን አታድርግ
ቅል ባገሩ ድንጋይ ይሰብራል
ቅል ባገሩ ደንጊያን ይሰብራል
ቅልና ድንጋይ ተማትቶ ሎሌና ጌታ ተሟግቶ
ቅልና ድንጋይ ተማትቶ ሎሌና ጌታ ተሟግቶ የማይሆን ነው ከቶ
ቅልና ድንጋይ ተማትቶ ጌታና ሎሌ ተሟግቶ የማይሆን ነው ከቶ
ቅልውጥ አሳስቦ ይጥላል ዘመቻ
ቅምሙ የበዛበት ወጥ አይፋጅ አይኮመጥጥ
ቅማል እንኳን ካቅሟ ጥብጣብ ታስፈታለች
ቅማል ውሀ ውረጅ ቢሏት ስንዳሰስ ለመቼ ልደርስ ቁንጫ ውሀ ውረጅ ቢሏት ስፈናጠር የሰው ዶጮ እሰብር አሉ
ቅማል በጥፍር ቢድጧት ራስ ደህና አለች
ቅማል ከአካላት ምስጢር ከቤት
ቋንጣና ባለሟል ሳያር አይቀርም
ቅዝምዝም ወዲያ ፍየል ወዲህ
ቅርብ ያለ ጠበል ልጥ ይነከርበታል
ቅርናታም ለቅርናታም ሰንቡሌ ሰንቡሌ ይባባላል
ቅርንጫፉ እንደዛፉ
ቅቤ መዛኝ ድርቅ ያወራል
ቅቤ ሲለግም ወስፌ አይበሳውም
ቅቤ ተነጥሮ ለመብላት ያባት የናት
ቅቤና ቅልጥም ወዴት ግጥምጥም
ቅቤ ይፍሰስ ከገንፎ አይተርፍ
ቅቤ ይፍሰስ ከገንፎ አይለፍ
ቅብጥና ቅልጥ አንድ ላይ ሲሄዱ ቅልጥ ብላ ቀረች ሶራስ ክመንገዱ
ቅል በአገሩ ድንጋይ ይሰብራል
ቅናት ያደርሳል ከሞት
ቅናት ጥናት አያገናኝ ካባት ከናት
ቅናት ጥናት አይገኝም ከናት ካባት
ቅና ያለው በአባቱ ከረባት ይቀናል
ቅና ያለው በናቱ ብልት ይቀናል
ቅን በቅን ከማገልገል ፊት ለፊት ማውደልደል
ቅንቡርስ የት ትሄዳለህ መተማ ትደርሳለህ ልብማ
ቅንነት ለነፍስ መድሀኒት
ቅንድብ ለአይን ጥቅሻ አስተማረች
ቅዝምዝም ሲወረወር ጎንበስ ብለህ አሳልፈው
ቅዠት ተፈርቶ ሳይተኛ አይታደርም
ቆላና ደጋ እመቤትና አልጋ
ቆሎ ለዘር እንዶድ ለድግር አይሆንም
ቆሎን ቢቆረጥሙት እንጂ ቢያሹት አያልቅም
ቆመው የሰቀሉትን ቁጭ ብለው ለማውረድ ይቸግራል
ቆማጣ ቤት አንድ ጣት ብርቅ ናት
ቆማጣ ብለው ያው ቁምጥና ነው ሌላ ምን ይመጣል አለ
ቆማጣን ቆማጣ ካላሉት ገብቶ ይፈተፍታል
ቆሩ መቀበሪያው ያው ፈሩ
ቆሩ በማን ምድር ትለፋ
ቆርሶ ያላጎረሱትን ቀዶ ያላለበሱትን ብላቴና ማዘዝ አይገባም
ቆቅ ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ
ቆንጆና እሸት አይታለፍም
ቆዳ ማንጓጓቱን ስሱ መጓጓቱን
ቆዳ ማንጓጓቱን ስሱ መጓጓቱን አይተውም
ቆዳ ሲወደድ በሬህን እረድ
ቆጥሮ የማይሰጥ ሌባ ቆጥሮ የማይቀበል ሌባ
ትኩስ ቀልዶች
አንድ እብድ በስጋ መሽጫ ሱቅ በር ላይ ቆም ሲል ያየ ስጋ ሻጭ በጭራው ሊያስፈራራው አየሞከረ አትሄድም ከዚህ አንተ
አብድ ብሎ ይጮህበታል :: አብዱም ሳቅ ብሎ <የሞተ ፣እሬሳ ስቅለህ ዝንቡን አሽ , , አሽ ስትል የምትውል አብድስ አንተ
…
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
++++
አንድ በጣም ወፍራም ሴትዮ የእንጦጦን ጋራ በእግራቸው ለመውጣት ይያያዙታል ሲደክማቸው ኋላቸውን ዞር በማለት
እየተመለከቱ በማረፍ ሲጓዙ አንዴ ፈሳቸውን ብው ሲያደርጉ «ጎጃምን ምታ ! ይላሉ አሁንም ወጥተው ወጥተው
ሲደክማቸው ዞር ብለው በማየት ፈሳቸውን ብም ..ብም ..ቡዋ !» ሲያደርጉት «ጎንደርን ምታ !» ይላሉ። በመጨረሻም
ዞር ዞር ብለው በመመልከት ፈሳቸውን «ጣጣጣጣጣ ..ጥጥጥጡዋ » ሲያደርጉት «ትግራይ ላይ ወያኔን ምታ !» ብለው
ዞር ሲሉ አንድ ዱርዬ ተማሪ ከኋላቸው ቆሞ ያዩታል ። ከዚያም «ውይ ! ልጄ የት ነበርክ ?» ሲሉት «ጎጃምም ሲወጋ
እዚሁ ነበርኩ : ጎንደርም ወያኔም ሲወጋ እዚሁ ነበርኩ» ሲላቸው : «ውይ ልጄ ! እናትም የለህ ?» ሲሉት ምን እንዳለ
ታውቂያለሽ ? ቂቂቂቂቂ … «ታዲያ እናት ቢኖረኝ ይታራብኛል እንዴ ብሏቸው አረፈው…..
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
+++++++
ሰውዬው ያንዱን አጥር ያፈርሳል፤ ባለቤቱም ዝም ይላል፡፡ ይቀጥልና ደግሞ ግቢውን ያርስበታል፤ አሁንም ዝም ይላል፡፡
በመጨረሻም በሩን ያርስበታል፣አሁንም ዝም ይላል፡፡ የኼኔም ሚስቱ፣ “አንቱ ሰውዬ ዝምታዎ አልተዋጠልኝም፣ ሰውየው
መጀመርያ አጥርዎን አፈረሰ፣ ዝም አሉ፣ ቀጠለና ግቢዎን አረሰ፣ ዝም አሉ፣ ሰለሰናም በሮን አረሰ አሁንም ዝም አሉ፣ ከዚህ
በኋላ ምንዎን እስኪያርስሎት ነው የሚጠብቁት?” ብትለው፣
“እውነትሽንኮነው” ይልና ሰውየውን፣ “እኔ ምልህ ምንድነው ጉዳይህ፣ በመጀመሪያ አጥሬን አፈረስህ፣ ዝም አልኩህ፤
ቀጥሎ ግቢዬን አረስህ፣ ዝም አልኩህ፤ በመጨረሻም በሬን አረስህ፣ አሁንም ዝም አልኩህ፤ ለመሆኑ ማላውቅ መሰለህ
እንዴ?” ሲለው፣
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
++++++
ባል እቤት ሲገባ ውሽምዬን ያገኘዋል፣ ግብግብም ይያዛሉ፡፡ ባልም መሸነፍ ሲጀምር፣ ሚስቱን፡- “ማነሽ ዕቃዎቹን
ከመንገድ ላይ ዞር ዞር አድርጊያቸው እስቲ” ይላታል፡፡
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
+++++++
ሴትየዋ ዓለም በቃኝ ብለው መነኮሱ፡፡ እናም አንድ ዕለት ጸሎታቸውን አድርሰው ከማደሪያቸው ሲወጡ ሳይፈልጉ
አይናቸው አንድ መልከ መልካም ጎረምሳ ፍየል ተሸክሞ ከጫካ ሲወጣ ያያል፡፡
ፈተና ውስጥም ገቡ፡፡ ስጋቸውና ሩህያቸውም ሙግት ገጠሙ፡፡ ኋላ ላይ ሥጋቸው ድል ነሳ፤ እናም ጎረምሳውን፣
“ና ውረድ” ይሉታል
“ፍየል ተሸክሜያለሁ”
“ፍየሉን አውርደው”
“ጫካ ይገባብኛል”
“በመቀነቴ አቁመው”
ከዚያ በኋላ ያለውን መናገር ጊዜ ማባከን ነው፡፡
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ብርቱካን
እትዬ ብርቱካን !!
ሁሴን !!
አዬ የርሶ ነገር !!
ስኩዋር ጣራ ወጣ ጋዙ ከዛፍ ላይ
እትዬ ብርቱካን !!
እኔኮ የምልህ !!
ሁሴን !!
አልሰሙም እንዴ ርሶ ?
በል እኮ ንገረኝ ኢኮኖሚ ማን ነው ?
ሁሴን !!
ምነው ያኔ ድሮ
ታዲያ ልደትዬ !!
ከምሽቱ ሁለት ሰዓት አካባቢ ነው… ከኦሎምፒያ ወደ አጎና ሲናማ ለመሄድ በመከራ የተገኘች ሚኒ ባስ ውስጥ ለመግባት
ሰዉ ይጋፋል… ምንም እንኳን ታሪፉ 1ብር ከ35 ቢሆንም ረዳቱ “ሁለት፣ ሁለት ብር ነው… ሰምታችኋል!” እያለ
እያስጠነቀቀ በተገኘው ክፍት ቦታ ተሳፋሪውን ይጠቀጥቃል… እንደምንም ብዬ ታክሲው ውስጥ ከገባሁ በኋላ…
የረዳቱን ማስጠንቀቂያ ማንም ቁም ነገሬ አለማለቱ በጣም አስገርሞኝ ለረዳቱና አብሮኝ ለነበረ ጓደኛዬ በሚሰማ ድምፅ…
“ለምን ሲባል!” ብዬ አጉረመረምኩ… ተሟግቼም… “አንተ ከማን ትበልጣለህ…” ተብዬም ለኔና ለጓደኛዬ 2ብር ከ70
ከፈልኩ…
እዛው ታክሲ ውስጥ ሳለን… ጓደኛዬን እንዲህ አልኩት… “ኑሮን ግን ማን እንዳስወደደብን ታውቃለህ?” መልስ
እስኪሰጠኝ አልጠበኩም… ንግግሬን ቀጠልኩ…
“ኑሮን ያስወደድነው እኛው እራሳችን ነን… አንተና እኔ!” ጓደኛዬ ጆሮውን ሰጠኝ… ቀጠልኩ…
“ለምሳሌ… ታክሲ ውስጥ ከተሳፈሩት አንዱ ዶክተር ነው እንበል… ይሄ ዶክተር ክሊኒክ አለውም ብለን እናስብ…
ታዲያ… ባለ ታክሲውና ረዳቱ ስለመሸ ብለው 65ሳንቲም እዚህ ዶክተር ላይ ሲጨምሩበት… ዶክተሩ በተራው ወደ
ክሊኒኩ ይገባና 50ብር የነበረውን የካርድ ማውጫ ዋጋ ከሁለት ሰዓት በኋላ 60ብር ያደርገዋል… ምክንያቱም የታክሲ
ዋጋ ጨምሮበታላ!
ሌላም… የዳቦ ቤት ባለ ቤት የሆነ ግለሰብ እዚህ ታክሲ ውስጥ አለ እንበል… እሱም… ምናልባትም… ከሶስትና አራት
ዳቦ የሚያተርፋትን 65ሳንቲም በትራንስፖርት ላይ ስለተጨመረበት እሷን ለማካካስ ሲል 1ብር የነበረውን ዳቦ 1ብር
ከ10ሳንቲም ያደርገዋል… ምክንያቱም የታክሲ ዋጋ ጨምሮበታላ!
አንዷ ደግሞ እንጀራ ሻጭ ናት እንበል… 2ብር ከ50 ትሸጥ የነበረውን እንጀራ 2ብር ከ75 ታደርገዋለች… ምክንያቱም
የታክሲ ዋጋ ጨምሮባታላ!
እንዲሁም… ሌላኛው ተሳፋሪ ትምህርት ቤት አለው እንበል… ታዲያ ይሄ ግለሰብ… 150ብር የነበረውን ወርሃዊ
የትምህርት ቤት ክፍያ 160ብር ያደርገዋል… ምክንያቱም የታክሲ ዋጋ ጨምሮበታል!
ሌላኛው… ባለ ስጋ ቤት ነው፣ ሌላው… ባለ ወፍጮ ቤት… ሌላው… እህል ነጋዴ… ሌላው… አትክልት ነጋዴ…
ሌላው… ባለ ምግብ ቤት… ሌላው… ጠበቃ… ሌላው… ጥበቃ… ሌላዋ የቤት ሰራተኛ… ሌላም… ሌላም…
ታዲያ ባለታክሲውና ረዳቱ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ሆነው ሳሉ እነሱ በጨመሯት 65 ሳንቲም ምክንያት ህክምና
ይጨምርባቸዋል፣ ዳቦ ይጨምርባቸዋል፣ እንጀራ ይጨምርባቸዋል፣ ስኳር ይጨምርባቸዋል… ሌላም… ሌላም…
ሾፌሩና ረዳቱ ዛሬ ማታ የለኮሷት ትንሽ ክብሪት ሌሊቱን ሙሉ ስትቀጣጠል አምሽታ… አንዱ፣ ለሌላው እያቀበላትና
እየተቀባበላት አድራ በነጋታው ሰደድ እሳት ሆና እነሱኑ ትፈጃቸዋለች፡፡
የሚገርመው ነገር… ባለታክሲው ትርፍ የጫናቸውን ጨምሮ በአጠቃላይ 20 ሰዎችን ጭኗል እንበል… ታዲያ
በ65ሳንቲሟ ተሰልቶ ዛሬ ማታ 13ብር አትረፎ ሊሆን ይችላል… ነገር ግን… በንጋታው… ከላይ ከጠቅስኳቸው፣ እሱ
እራሱ ከሚጠቀማቸው አምስት አገልግሎቶች ብቻ 21ብር ከ35ሳንቲም ተጨማሪ ሊከፍል ግድ ይሆንበታል ማለት ነው፡፡
ወንድሜ ሆይ! ኑሮ ተወደደ እያልክ እያማረርክ ነው? እኔ ግን አንድ ነገር ልንገርህ… ኑሮን ያስወደደው ማንም ሳይሆን…
አንተው እራስህ ነህ!
አንቺ እህቴስ! ኑሮ ንሮብሻል? እንግዲያውስ አንድ ነገር ልምከርሽ… ኑሮሽ የተወደደው አንቺ በወደድሽው ልክ ነው…
አንቺ በመረጥሽውና በፈቀድሽው ልክ… ኑሮሽ የተወደደው ያለ በቂ ምክንያት 70ሳንቲም ሳታንገራግሪ የጨመርሽ ጊዜ
ነው… ኑሮሽ የተወደደው የጋገርሽው እንጀራ ላይ ያለ አግባብ ዋጋ የጨመርሽ ጊዜ ነው… ኑሮሽ የተወደደው የጋገርሽው
አምባሻ ላይ የተጋነነ ዋጋ የጨመርሽ ጊዜ ነው… ኑሮሽ የተወደደው ከጓሮሽ ያበቀልሽው ጎመን ላይ የማይገባ ዋጋ የጫንሽ
ጊዜ ነው…
አንተ ኑሮ የተወደደብህ፣ አንቺ ኑሮ የተወደደብሽ… ያልተረዳኸው፣ ያልተረዳሽው ነገር ቢኖር ህይወት የቅብብሎሽ
ሰንሰለት መሆኗን ነው… ኑሮ የገዢና የሻጭ፣ የአገልግሎት ሰጪና ተቀባይ ቀለበት መሆኗን ነው… ታዲያ! ዛሬ በሌላው
ላይ የወረወረከው ጠጠር ነገ ከሌሎች ጠጠሮች ጋር ተደማምሮ አንተ ላይ ከባድ አለት ሆኖ ይመጣብሃል…
የማትሸከመው ቀንበር ይሆንብሃል… አንገትህን ያስደፋሃል… አንተ ዛሬ የከፈትካት ቀዳዳ ነገ በሌሎች ሰፍታ የአውሬዎች
ሲሳይ ታደርግሃለች… አንተ ዛሬ የፈጠርካት ጠብታ ነገ ጎርፍ ሆና ይዛህ ትሄዳለች…
ታዲያ ያኔ ማን ላይ ልታላክክ ነው? መንግስት ላይ? ባለ ሃብት ላይ? ነጋዴ ላይ? ገበሬ ላይ? እኔ ግን ልምከረህ…
የመንግስትም፣ የነጋዴም፣ የገበሬም፣ የመምህርም፣ የአስተማሪም፣ ስልጣን ሰጪና ነፋጊ አንተ ነህ! ማንም የሚገዛህም ሆነ
የሚሸጥልህ አንተ በሰጠኸው ዋጋና ተመን ልክ ነው፡፡ እሱ ያወጣው ዋጋ ካልተስማማህ እያጉረመረምክ አትግዛ!
ይልቁንም በኢትዮጲያዊ ቆራጥነት ቆፍጠን ብለህ… “አልገዛህም!” በለው ያኔ እሱም የሚገዛው ነገር አለና ብር
ስለሚያስፈልገው አንተ በተመንክለት ዋጋ ይሸጥልሃል…
ምናልባት… ዛሬ የተጣለችብህን ጭማሬ የመግዛት አቅሙ ስላለህ ከመጨቃጨቅ ብለህ ጭማሬዋን ከፍለህ ልትሄድ
ትችላለህ… ነገር ግን ካንተ በታች ያለውን ወንድምህን ደግሞ አስብ!
አንተ ዛሬ ለደካማው ወንድምህ ዘብ ካልቆምክለት፣ ነገ… ትላንት የናቅካት ጭማሪ አንተው ላይ እጥፍ ሆና ስትመጣብህ
ማን ከጎንህ ሊቆም ነው? ስለዚህ… አንድ ነገር ተረዳ… የማንኛውም ነገር አስጨማሪም ጨማሪም አንተ ነህ! ኑሮህን
ያስወደድከው አንተው እራስህ ነህ!
Leave a comment
የለሊት ወጎች
21. August 2014Allgemein
ተወልጄ ያደኩት ከእናቴ ጋር ነው… እናቴም የምትኖረው ከኔና ከእናትና-ልጅ(አረቄ) ጋር ነው… በ ሁለት በ ሁለት
ቤታችን ውስጥ…
ታዲያ… ፍቅር የሚገለፀው ሁሌም በሁለትዮሽ ብቻ ይመስለኛል… ለምሳሌ እኔና እናቴ… ሁለት ብቻ ነን… የአረቄ
ጠርሙሱ ላይ ያሉት እንስሶች… አጋዘን መሰሉኝ… እናትና ልጅ ይሏቸዋል… እነሱም ሁለት ናቸው… እኛ ግድግዳ ላይ
የተሰቀለው የእመቤታችንና የልጇ ምስል… እነሱም ሁለት ናቸው… ከሩቅ ደግሞ… የነዚህን ሁለት ነገሮች ፍቅር ከላይ
ሆነው የሚጠብቁ… ሁለት መልዓክት አሉ… ልክ የእመቤቴና የልጇ ምስል ላይ እንዳሉት…
የሰፈር ልጆች… “አባትህ የት ነው? አባት የለህም እንዴ?” እያሉ ይጠይቁኝና ሊያበሽቁኝ ይሞክራሉ… እኔ ግን
አልበሽቅላቸውም… እንደውም እንደኔና እማዬ ሁለት ባለመሆናቸው አዝን ነበር… ምክንያቱም ሁሉም ጎረቤቶቻችን
ሲጨቃጨቁ… ሲጣሉ… ሲደባደቡ አያለው… እናም እንደኔና እማዬ ሁለት ባለመሆናቸው ነው ብዬ አስባለው… እኔና
እማዬ አንድም ቀን ተጣልተን አናውቅም… ሁለት በ ሁለት ቤታችን ውስጥ ሁልጊዜም ደስ የሚል ፍቅር አለ… ጥልና
ፀብ እራሱ ምን እንደሆነ ያወኩት በጎረቤቶቻችን ምክንያት ነው…
አንዳንድ ጊዜ ቤታችን ከሁለት በ ሁለት ትንሽ ብትሰፋ እኔና እማዬ እራሱ ዝም ብለን የምንጣላ ይመስለኛል… ምንም
እንኳን ሁለት ሰው ባይጣላም…
አባት ግን ምን ይሰራል? አባት ኖሮኝ ባያውቅም… የሌሎች ልጆች አባቶች ሁሌም ሲቆጧቸውና ሲገርፏቸው… ልጆቹም
አባቶቻቸውን ሲፈሩ ነው የማውቀው… አባቶች ልጆችን ብቻ አይደለም የሚቆጡትና የሚገርፉት እናቶችንም ጭምር
ነው… አንዳንድ ጊዜ ሳስበው… ግድ ሆኖባቸው እንጂ… እንደኔና እማዬ እደለኛ ሳይሆኑ ቀርተው እንጂ… የጎረቤት
ልጆችና እናቶች እራሱ አባት ባይኖራቸው የሚመርጡ ይመሰልኛል…
አባቶችም ለክፋትና ለፀብ ብቻ የተፈጠሩ ይመሰልኛል… ለዛም ነው… ጦር ሜዳ የሚልኳቸው… ለምሳሌ እኛ አረቄ
ቤት የሚመጡት ሁሉም አባቶች ናቸው… ታዲያ… ሰክረው ጮክ ብለው ከማውራትና ከመሰዳደብ ውጪ ሌላ ስራ
የላቸውም… ታዲያ አባት ምን ይሰራል? የእመቤቴ ማሪያምና የልጇ ምስል ላይ እራሱ አባት የለም… ስለዚህ ፍቅር
የሚገለፀው በሁለት ነው ብዬ አስባለው…
ሰው ከሁለት በላይ ከሆነ ሁሌም የሚጨቃጨቅ ይመስለኛል… ለምሳሌ የኛ ቤት… ሁለት በ ሁለቷ… አረቄ ጠጪዎች
ሲመጡባት… ወዲያው ቀውጢ ትሆናለች… እኔና እማዬ ለሁለት የዘራንባት ፍቅር ወዲያው በጭቅጭቅና በፀብ
ይደፈርሳል…
እናም… በቃ… ሰው ከሁለት በላይ ሆኖ መኖር የለበትም ብዬ አስባለው… ለዚህም ይመስለኛል የሰውነት ክፍሎቻችን
እራሳቸው በአብዛኛው ሁለት ሁለት ሆነው የተፈጠሩት… ሁለት እጅ… ሁለት እግር… ሁለት ጆሮ… ሁለት አይን…
እንዲሁም… እንደ ነገረኛ ጎረቤታችን… ሁለት ምላስ…