Professional Documents
Culture Documents
Type Text
Type Text
ክፍል አንድ
ምዕራፍ አንድ
[Type text] Page 1
መግቢያ
ክፍል ሁለት
[Type text] Page 4
ምዕራፍ ሁለት
ወጣቶች እና ፈተናዎቻቸው
የወጣቶች ምኞት
በወጣትነት ዘመን አካላት እንደሚደራጁ እና አእምሮአቸው እንደሚዳብር ሁሉ ምኞታቸውም በዓይነት እና
በመጠን እየሰፋ እና እየጨመረ ይሄዳል፡፡ ይህም በአመዛኙ ከመንፈሳዊነት ጋር የሚቃረን እና ሥጋዊ
በመሆኑ ‹‹እኩይ ፍትወት›› ይባላል፡፡ 2 ጢሞ. 2፡22 ‹‹አንተ ግን ከክፉ የጎልማሳነት ምኞት ሽሽ
በንጽሕናም ልብ ጌታን ከሚጠሩ ጋር ጽድቅን እምነትን ፍቅርን ሰላምን አጥብቀህ ተከተል፡፡›› እንዳለ ቅዱስ
ጳውሎስ፡፡ ወጣትነት የሚሠሩበት ዘመን እንጂ የሚመኙበት ዘመን አይደለም፡፡ እኛም ወጣቶች ምኞታችንን
ወደ ጎን በመተው የሥራ ሰዎች ልንሆን ያስፈልጋል፡፡ያለ ሥራ ምኞት የሚደረስበት አይደለም፡፡ ያዕ. 1፡13
ማንም ሲፈተን በእግዚአብሔር እፈተናለሁ አይበል፤ እግዚአብሔር በክፉ አይፈትንምና፤ እርሱ ራሱስ
ማንንም አይፈትንም ነገር ግን እያንዳንዱ በራሱ ምኞት ሲሳብ እና ሲታለል ይፈተናል፡፡ ይህም ምኞት ወደ
ጥፋት የሚስብ የሚጎትት እና የሚያታልል ነው፡፡ ‹‹በገዛ ምኞት ሲሳብ›› ማለት ምኞት ከፍተኛ ጉልበት
እንዳለው ይጠቁማል፡፡በወጣትነት ዘመን ምንም አእምሮ የበሰለ ቢሆን ከዚያ የሚበረታው ግን ምኞት
ነው፡፡ ከወጣቶች እውቀት ይልቅ ምኞታቸው መበርታቱን ለማስረዳት ወጣቶች በዘመነ ኦሪት ይመሰላሉ፡፡
ሕገ ልቡና እንደመሰለው መኖር ሕግ ኦሪት የሰው ባሕርይ በኃጢአት የጎሰቆለ ስለነበር ሕጉን ፈጽመው
ለመጽደቅ አልተቻለም ነበር፡፡ ወጣቶችም እውቀታቸው እየጨመረ ቢመጣም ምኞታቸውም የዚያኑ ያህል
ስለሚበረታና ስለሚስባቸው እውቀታቸውን ተጠቅመው የሚያጽደቃቸውን ጎዳና ለመከተል ይቸገራሉ፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ. 7፡23 ‹‹በብልቶቹ ውስጥ ያለው ይህ የኀጢአት ሕግ (ምኞት) ወደ እርሱ ማረከኝ
ተበረታታብኝ›› ሊቁ አባ ሕርያቆስም በቅዳሴ ማርያም ‹‹ድንግል ሆይ የሚያታልሉ ጎልማሶች ያረጋጉሽ
አይደለም የሰማይ መላእክት ጎበኙሽ እንጂ›› ብሎ ወጣቶች በምኞታቸው ተሸንግለው ሌላውን ለማታለል
እንደሚያባብሉ ይናገራል፡፡
ምኞት በውስጣችን እንዲኖር እና እንዲያድግብን የምንከባከበው ነገር መሆን የለበትም፡፡ ምኞት ተስፋ
አይደለምና፡፡ ጠቢቡ ሶሎሞን በምሳ. 21፡26 ‹‹ኀጥእ ቀኑን ሁሉ ምኞትን ይመኛል፡፡›› ይላል፡፡ምኞት
አስደሳች እና ጣፋጭ ነገር ትመስል ይሆናል ነገር ግን አይደለችም፡፡ ‹‹ምኞት ስሕተት እና ውድቀት ናት
እንጂ ጣፋጭ አይደለችም›› (ቅ/ዮሐንስ አፈወርቅ)፡፡ ምኞትን ማብዛት ልፋትን ወይም ተስፋ መቁረጥን
ማብዛት ነው፡፡ምክንያቱም ምኞትን ለማሳካት ብዙ መድከም ከማስፈለጉም በላይ ብዙ ምኞት ካልተሳካ
የሚያስከትለው ተስፋ መቁረጥም እንደዚሁ ይሆናል፡፡ ብዙ ወጣቶች የሚመኙት ጉዳት የሚያስከትልባቸው
እና ከጥቂት ጊዜ በኋላ በብርቱ የሚያስቀጣቸውን ነገር ነው፡፡የሚገርመው ግን ጓጉተው የሚፈልጉት እንጂ
ሲያገኙት ወዲያው የሚሰለቹት ወይም የሚጸጸቱበት ነው፡፡
ፈጣሪን ሳይጠጉ ምንም ነገር አርኪ እና በቂ መሆን አይችልም፡፡ ስለዚህ መመኘት እና ለማግኘት ብቻ
ሳይሆን አስቀድመን ፈጣሪን መጠጋት ይኖርብናል፡፡ በወጣትነት የሚከሰት ምኞት አንድ ብቻ አይደለም፡፡
ወጣቶች ሁሉም ስለሚያምራቸው በአንድ መርጋት አይሆንላቸውም፡፡ተምሮ በመአረግ መመረቅ፣ አጭቶ
ማግባት፣ ሀብታም ነጋዴ መሆን፣ትልቅ ባለሥልጣን መሆን ተራ ጠብቀው ብታሰቡ የሚሳኩ ይሆናሉ
ካልሆነ ግን ‹‹ሁለት የወደደ አንዱን ሳያገኝ ሄደ›› ይሆንብናል፡፡ ስለዚህ ወጣቶች አንድን ነገር መጀመር
ሳይሆን በእርጋታ ሆኖ እስከ መጨረሻ መፈጸም አለባቸው፡፡ ወጣቶች ምኞቶቻቸው ብዙ ከመሆናቸው
[Type text] Page 5
የተነሳ ሁለት የማይጣጣሙ ነገሮችን የሚመኙበት ጊዜ አለ፡፡ ሙሽራ ሲያዩ ማግባት እና መውለድን
ይመኙና በዚያው ቀን ደግሞ ልቡናቸው በመንፈሳዊ ነገር ተነክቶ መመንኮስ እና መመነን የሚመኙበት ጊዜ
አለ፡፡ ይህ ደግሞ በአንድ ሰው መፈጸም ስለማይቻል መታወክ ነው፡፡ ብንታገሥ ግን ከጊዜ ብዛት ራሱ
ይርቃል፡፡ ማቴ. 7፡25 ‹‹ዝናብም ወረደ ጎርፍም መጣ ነፋስም ነፈሰ ያንንም ቤት ገፋው በዐለት ላይም
ስለተመሠረተ አልወደቀም፡፡›› በዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል፡-
ቤት የወጣትነት ሕይወት ነው፡፡
ነፋስ ነፈሰ ማለት የአጋንንት ፈተና በወጣቱ ላይ ተነሳበት እና ከሴት ርቆ ንጽሕናውን ጠብቆ እንደ
እንጦንስ እና እንደ መቃርስ ለመኖር እንዲመኝ አደረገው ማለት ነው፡፡
ዝናብም ወረደ ማለት ያንኑ ወጣት እንደ እንጦንስ እና መቃርስ መኖር አይቻለኝም ባይሆን እንደ
ኢዮብ እና አብርሐም አግብቼ ልጆች ወልጄ በሕግ ሊኑር አሰኘው ማለት ነው፡፡
ጎርፍም ጎረፈ ማለት በመጨረሻ ተስፋ በመቁረጥ ሁሉንም አልችልም እስኪል ድረስ አደረሰው
ማለት ነው፡፡ዐለት የተባለው ግን የእግዚአብሔር ቃል ነው፡፡ ወጣቶች ከፈቀዱ በእግዚአብሔር ቃል
ላይ መመስረት ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሔር ሕጉ ከውስጣቸው እንዳይጠፋ ማድረግ ይችላሉ፡፡
1 ዮሐ. 2፡14 ‹‹የእግዚአብሔር ቃል በእናንተ ስለሚኖር...›› ፡፡
በቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ አስትምህሮ መሠረት ምእመናን በአምስት መደብ ይመደባሉ፡፡ ይህም መደብ
‹‹ጾታ ምእመናን›› ይባላል፡፡ እነዚህም
ካህናት
መነኮሳት
አዕሩግ (አረጋዊያን)
ወራዙት (ወንድ ወጣቶች)
አንስት ወጣቶች
እነዚህ አምስቱ የጾታ መደቦች በዐብይ ፈተና ይፈተናሉ፡፡
የካህናት ፈተናቸው ትዝኅርት (ትዕቢት)
የመነኮሳት ስስት
የአረጋዊያን ፍቅረ ንዋይ
የወጣቶች ዝሙት
የወጣት ሴት ፈተና ደግሞ ትውዝፍት (የምንዝር ጌጥ)
ዮሐ. 5፡4 (ትርጓሜ) ይህ ማለት ግን ዋና ዋና ፈተናቸውን አንጓሎ መናገር ነው እንጂ እያንዳንዱ ጾታ
ምእመን የሚፈተነው በአንድ ነገር ብቻ ነው ማለት አይደለም፡፡ እነዚህ በር የሚከፍቱ እና ለምእመኑ ረቂቅ
እና ከባድ ስለሆኑ ነው፡፡ ለምሳሌ ካህኑ ሰማያዊ ስልጣን ስላለው ሲተብት ትዕቢተኛ መሆኑን ለራሱ
አያውቅም ሌሎችም እንዲሁ አያስተውሉትም፡፡ ሰውነቱ በደዌ የተጠቃ ሰው ጉንፋን እንኳን
አንደሚያይልበት እንዲሁ በዋና ፈተናው ድል የተደረገ ምእመን ሌሎች ጥቃቅን ፈተናዎች ይረባረቡበታል፡፡
ነገር ግን ዋናውን ፈተና ድል ካደረገ የሚመጡበትን ሌሎች ፈተናዎች በቀላሉ ድል ለማድረግ ይቻለዋል፡፡
ወጣቶች እድሜያቸው እየገፋ በመጣ ቁጥር ወጣትነታቸው ሲያልፍ የወጣትነት ፈተናቸውም አብሮ
ጥያቄ?
ሕጻን ሴት ከእናቷ ይልቅ አባቷን የምትቀርበው ለምን ይመስላችኋል?
ሕጻን ወንድስ ከአባቱ ይልቅ ለእናቱ የሚቀርባት ልምንድነው?
ሠይጣነ ዝሙት አንድን ሰው ያልተፈቀደለትን የሌላን ሰው አካል በዝሙት መንፈስ ለመንካት እንዲመኝ
እንደሚያነሳሳ ሁሉ ሰውዬው የራሱንም ሕዋሳት በዝሙት መንፈስ ሆኖ እንድደባብስ የሚገፋፋበት ጊዜ
አለ፡፡ ሰይጣኑ ሰው የራሱን ሰውነት ያለ ማቋረጥ እንዲያክ፣ እንዲያሻሽ አንዲደባብስ በማድረግ የራሱ
ሰውነት እንዲሸክረውና እንዲኮሰኩሰው በማድረግ ፈተና ያመጣበታል፡፡ መጽሐፈ መነኮሳት እንዲህ ይላል፡፡
‹‹ሰውነቱንም የሚያሻክርበት ጊዜ አለ፣ ያለ ማቋረጥም አንዲያክ ያደርገዋል፡፡ አንተም ስለዚህ በቆምክ ጊዜ
ሕዋሳትህን ትዳብሳለህ፣ ትንጠራራለህ፣ ወይም ትወጣጠራለህ፣ እግርህንም ታፋትላለህ፡፡ ይህ ርኩስ
መንፈስ ለመጀመሪያ ማሳከክ ሲጀምርና ሰውነትህን እንድትደባብስ ሲያደርግ ከሕዋሳቶችህ የሚመርጠው
የለም፡፡›› ይህ ሁሉ ሲሆን ሰውዬው የሰይጣን ፈተና መሆኑን ካልተረዳ እንዲያው እንዳሳከከው ወይም
ሰውነት እንዲቆሸሸ ያስባል፡፡ ገፋ ካለም ወደ ሐኪም ዘንድ ይሄዳል፡፡ ሰውነት በማሳከክ የጀመረው ሰይጣነ
ዝሙት ዓላማውን ከግብ ለማድረስ በዚህ ብቻ አይወስንም፡፡ እንደ መጽሐፈ መነኮሳት ገለጻ ወደ አባለ
ዘሩም ይሄድና ያን ሰው ያለመጠን እንዲያክ ያደርገዋል፡፡ ያንን ሰው በዝሙት ሐሳብ ተስቦ በዚህ መልኩ
ብልቱን እያሻሸ ዘሩን እስኪያፈስ ድረስ ዕረፍት ሳይሰጠው ፈተናውን ያስቀጥላል፡፡
ማስገንዘቢያ፡- ከዚህ አንጻር ማሳጅ እና ፊዚዮ ቴራፒ ዓላማው ከዚህ ጋር የተያየዘ ነው፡፡ ሰይጣነ
ዝሙት ሰው የገዛ ሰውነቱ እንድከብደው በማድረግ እንዲታሽ ያደርጋል፡፡ ለዚህ መፍትሔው
ስግደት፣ ጾም እና ጠበል መጠመቅ ነው፡፡
በዚህ ዓይነት የዝሙት ዝንባሌ ተይዞ ከእንቅልፍ ውጭ ዘር እያወቁ ወደ ውጭ ማፍሰስ ግብረ አውናን
ይባላል፡፡ አውናን የተባለ ሰው ከሚስቱ ጋር ተኝቶ ሳለ ዘሩን ከሚስቱ ማኅፀን ውጭ ያፈሰው ስለ ነበር
ነው፡፡ ዝሙትን ወዶ ክቡር ዘርን የትም ማፍሰስ የአውናን ዘሩን ከማህፀን ውጭ መፍሰስ አንድ ናቸውና፡፡
ዘፍ. 38፡9
ግብረ አውናን ፈጽሞ ተገቢ አይደለም፡፡ ገበሬው ዘሩን በጎተራ አቆይቶ ያለቦታው፣ ያለጊዜው
እንደማይበትነው ሁሉ የሰው ዘር በሰውነት ተጠብቆ መቆየት አለበት ከጋብቻ በኋላ በሩካቤ ጊዜ በመልካሟ
ማሳ በሚስት ማኅፀን መዝራት አንጂ በልዩ ልዩ ምክንያት ሆን ብሎ ዘርን እንደ ጉድፍ ከማኅፀን በአፍአ
ማፍሰስ ከባድ ኃጢአት ነው፡፡
የሰው ዘር ክቡር በመሆኑ ዘራቸውን በሜዳ ከሚያፈሱ ሰዎች ይልቅ ሰው የመሆን እድል የነበራቸው ነገር ግን
በየሜዳ ፈሰው የቀሩት ዘሮች የተሻሉ ናቸው፡፡ ዘር ያፈሰሱ ከሕገ እግዚአብሔር ሲወጡ፤ የፈሰሰው ዘር ግን
ምንም ካለመበደላቸውም ቢወለዱ ኖሮ ጳጳስና ንጉሥ የመሆን ዕድል ሊኖራቸው ስለሚችል ነው፡፡ በዝያን
ጊዜ ዘር ያፈሰሱትን ጊዜ ሳይሰጣቸው እግዚአብሔር ቀስፏል፡፡ ዘፍ. 38፡9-10 (ከመጽሐፍ ቅዱስ ሳያነቡ
አይለፉ)
ትኩረት የሚሹ!!!
ከግብረ አውናን ጋር ተመሳሳይነት ያላቸው በጋብቻ ውስጥ ያሉ በማንኛውም መልኩ ሩካቤ ሲፈጽሙ
ኮንደም መጠቀም አይፈቀድም፡፡ ምክንያቱም እንደ አውናን ዘርን ከማኅፀን ውጭ ማፍሰስ ነውና፡፡ በትዳር
ያሉ ባልና ሚስት ኮንደምን የሚጠቀሙት ወሊድ ለመቆጣጠር ነው፡፡ ነገር ግን በቤተ ክርስቲያናችን
ሥርዓት መሠረት ማንኛውንም ወሊድ መቆጣጠሪያ መንገድ መጠቀም አይቻልም፡፡ ልጆች የእግዚአብሔር
ስጦታዎች እንጂ በእኛ ፎርሙላ የሚገኙ አይደሉም፡፡ ነገር ግን በባልና ሚስት መካከል የሚደረገው ወሲብ
ሥርዓት ያለው መሆን አለበት፡፡
[Type text] Page 16
ክፍል ስድስት
ምዕራፍ ሦስት
ክፍል ሰባት
ምዕራፍ አራት
ለአቅመ ሔዋን የመድረስ ምልክት
ፈጣን የቁመት ማደግና የክብደት መጨመር ከመከሰቱም ሌላ የሽንጥ መርዘም፣ የደረት መጋጠሚያ
መጎድጎድ፡፡ በአንዳንድ ሴቶች ላይ ደግሞ ብጉር በሰውነታቸው በተለይ በፊታቸው ላይ በዝቶ የሚታይ
ሲሆን የፊት ቅርጽም ቀስ በቀስ እየተለወጠ ይሄዳል፡፡ በብብትና የብሽሽት (ኀፍረተ አካል) አካባቢ ጸጉር
መብቀል ጋር ዳሌዎች ይሰፋሉ፡፡ ልጃ ገረዶች የሚኖራቸው ሰፋ ያለ ዳሌ ወሊድን ብቻ ሳይሆን ከወለዱ
በኋላ ሕጻናትን ለማዘልና ለማቀፍ ምቹ ሁኔታን ይፈጥርላቸዋል፡፡ የጡት መጎጥጎጥ ለአቅመ ሔዋን
የመድረስ ጉልህ ምልክት ነው፡፡ አንዲት ኮረዳ የሚኖሩአት ሁለት ጡቶች ልጅ በምትወልድበት ጊዜ ለሕጻኑ
ምግብ የሚሆነውን ወተት ማመንጨት ይጀምራሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ‹‹ጡቷ ሁልጊዜ ታርካህ፣
በፍቅርዋም ሁል ጊዜ ጥገብ›› (ምሳ. 5፡19) ማለቱ ባልዋ የሚደሰተው ጡቶቿን በመሳም፣ በመነካካትና፣
በመዳባበስ ነውና፡፡ ለጡት ማነስ እና መተለቅ የሚያሳስብ አይደለም፡፡ የተፈጠረበትን ዓላማ ስለማያጓድል
ሊጨንቀን አይገባም፡፡ በጡት መያዣ የሚወጥሩ፣ ምናምን የሚወትፉ፣ ቀዶ ጥገና የሚያስደርጉ ሴቶች
አሉና፡፡ ነገር ግን ሠለስቱ ምዕት ‹‹ሌላ መልክ አትሻ(መነቀስ፣ መጠቆር፣ መታከም) በተፈጥሮ ያገኘኸው
ይበቃሃልና›› ብለው አስተምረዋል፡፡
ጡት በቀላሉ ሊጎዳ የሚችል ስለሆነ ከመጨነቃችን የተነሳ የማናውቃቸውን ነገሮች እንደመሰለን መጠቀም
ጉዳት ላይ ሊጥለን ይችላል፡፡ ለጡት ካንሰር መጋለጥ...፣ አንዳንድ ሴቶች ደግሞ በጡታቸው ምክንያት
የወር አባበ
ለአቅመ ሔዋን የደረሱ ሴቶች የሚያሳዩት ሌላው ምልክት የወር አበባ ነው፡፡ የወር አበባ የተለያዩ ስያሜዎች
አሉት፡፡
የሴቶች ልማድ ዘፍ. 18፡11 ልማደ አንስት
በሴቶች የሚደርስ ግዳጅ ዘፍ. 31፡35
የወር አበባ የተባለበት ምክንያት በየወሩ የሚታይ ስለሆነ አበባ መባሉ ፍሬ ለመስጠት የሚችል
እንቡጥ (አበባ) ስለሆነ ነው፡፡
አደፍ ተብሏል
ደመ ጽጌ ይባላል ‹‹የአበባ ደም›› ማለት ነው፡፡ የወንድ ዘር ባለማግኘቱ በደም መልክ ይወጣል፡፡
እስከሚጸንሱት በየወሩ ይታያል፡፡ በእርግዝና ወቅት ይቋረጥና ልጅ ከተወለደ(ች) በኋላ ጤናማ
ሂደቱን ይቀጥላል፡፡ ይህ ወርኃዊ ዑደት የሚጀምርበት፣ የሚቋረጥበት ዕድሜና መታየት ከጀመረበት
እስከሚቋረጥበት ድረስ የሚወስደው ጊዜ ከሰው ወደ ሰው ይለያያል፡
የወር አበባ ሴት ልጅ ፈጣሪ ለመደበላት ዕጥፍ የሕይወት ሚና ማለትም ሚስት እናት ለመሆን መድረሷን
የሚያመለክት በመሆኑ ሳትከፋ በጸጋ ልትቀበለው ይገባታል፡፡ መደንገጥ፣ መፍራት አያስፈልግም፡፡
ምክንያቱም አንዳንድ ሴቶች የወር አበባ ሲታያቸው የሚበሳጩ፣ በመታየቱም የሚከፉ፣ ባይታይ ደስ
የሚላቸው አሉ ነገር ግን ይህ በደል ነው፡፡ ወደ ትዳር ከገቡ በኋላ ባይታይ ግን ልጅ መውለድ የለምና ምን
ያህል ያስከፋ ይሆን? ስለዚህ እናቶች ለልጆቻቸው አስቀድመው በቂ ግንዛቤ ማስጨበጥ አለባቸው፡፡
ልጆችም ለቤተሰቦቻቸው በግልጽ ማማከር ይገባቸዋል፡፡ ዘፍ. 31፡35 ራሔል ‹‹በሴቶች የሚደርስ ግደዳጅ
ደርሶብኛል›› ብላ ለአባቷ እንደ ነገረችው፡፡
ድንግል ማርያም ግን ለ 64 ዓመታት ስትኖር ልማደ አንስት አላገኛትም፡፡ ሌሎችም ሳያዩ የሚያልፉ
ጤናማ ሴቶች የሉም፡፡ ምክንያቱም እሷ ልዩ ናት ከአዳም እና ከሔዋን የውርስ ኃጢአት(Orginal
Sin) ነጻ ስለሆነች ይህ አይመለከታትም፡፡
የወር አበባ መቼቱ አዳምና ሔዋን በኃጢአት ከወደቁ በኋላ ከገነት ውጭ ነው፡፡ በገነት በነበሩበት ጊዜ
ምንም እንኳን በሔዋን ባሕርይ ደመ ጽጌ የነበረ ቢሆንም ደሟ በአፍአ አይታይም ነበር፡፡ በምድር ላይ
ክፍል ስምንት
ምዕራፍ አምስት
ድንግልና
ድንግል የሚለው ቃል ‹‹ተደነገለ፣ ተጠበቀ›› መጠበቅ ማለት እንደ አገባቡም ፍቺው ሊለያይ ይችላል፡፡
ለዕቃ እንደሆነ ገና ከማምረቻ የወጣ፣ ምንም ያልተሠራበት፣ ያላደፈ፣ ያላረጀ፣ ያልተቀላቀለ ማለት ነው፡፡
በዚህ መሠረት እስኪ ለሰው ደግሞ ተጠቀሙ፡፡ ድንግል መሬት ሲባል ደግሞ ለምነቱ እንደተጠበቀ ያለ፣
ለእርሻ ያልዋለ ወይም ያልታረሰ፣ ያልተቆፈረ፣ ዘር ያላረፈበት፣ እንደተፈጠረ ያለ፡፡ ለሰው ስነገር ደግሞ
ወንድ የማታውቅ፣ በጥብቅ፣ ልጃገረድ ወይም ሴትን የማያውቅ ወንድ ማለት ይሆናል፡፡ ዘፍ. 24፡16 ራዕ.
14፡4፡፡ ነገር ግን አንዲትን ሴት ምኅተመ ድንግልና ስላላት ብቻ ሩካቤ አድርጋ አታውቅም ወይም ሩካቤ
ስላደረገች ማኅተመ ድንግልና የላትም ማለት አይቻልም፡፡ የወንዶች ድንግልና እንደ ሴቶች ተጨባጭ ጉልህ
የድንግልና ምልክት ስለሌላቸው ከሴት ጋር ሩካቤ ፈጽመው የማያውቁ ሆነው ሳለ ደናግል አይደሉም
ለማለት አይቻልም፡፡ ሩካቤን ፈጽመው የማያውቁ ሴቶች ስወለዱ ጀምሮ ማኅተመ ድንግልና የሌላቸው
ሊሆኑ ይችላሉ ወይም ከጊዜ በኋላ በከባድ የአካል እንቅስቃሴ፣ በአደጋ፣ በሕክምና ወይም በዕድሜ ብዛት
በአግባብ ለመኖር፡- በድንግልና መኖር አግባብ ነው ዝሙት ግን ግብረ ገብነትን ማጣት ነው፡፡
ድንግልናን ጠብቆ ለመኖር የሚደረገው ትግል ሕጋዊ ሰው ሆኖ መኖርን ያለማምዳል፡፡
ሳይባክኑ ለመኖር፡- ድንግልናውን የጠበቀ ወዲህና ወዲያ አይልም፡፡ ዝሙት ግን መባከን ነው፡፡
ዝሙተኛ ኃጢአቱን ለመደበቅ፣ ከዚህ በኋላ እግዞ,ዚአብሔር ምን ያመጣብኝ ይሆን? በማለትና
ዝሙቱ ቢታወቅ በሌሎች ዘንድ ምን ሊባል እንደሚችል በማሰብ በስጋትና በመባከን ይኖራል፡፡
መዝ. 6፡1-3፣ 1 ቆሮ. 7፡32-33፡፡ በጋብቻ ከመኖር በድንግልና መኖር የበለጠ ከሐሳብ ነጻ
ያደርጋል፡፡ ወጣቶችም በዚህ ሕይወት ለመኖር ከወዲሁ ከእግዚአብሔር ጋር ብነጋገሩ እና
ቢወስኑ እጅግ በሕይወታቸው ተጠቃሚ ይሆናል፡፡
በጌታ ይጸናል፡- ብዙዎች ስለ ፍትወት ብለው ኮረዳና ጎልማሳ ፍለጋ ብዙዎች ሃይማኖታቸውን
አንደተው የሚታወቅ ነው፡፡ ዛሬም የመናፍቃን ትልቁ አጀንዳ የሆነው ሴቶች ረጋፊ የሆነ
መልካቸውን ተጠቅመው ኦርቶዶክስ ወጣቶችን የነጠቁ ብዙ ናቸው፤ ወንዶችም እንዲሁ
እህቶቻችንን፡፡ ለመሆኑ የጋብቻ የመጀመሪያ መስፍርት እኮ ሃይማኖት ነው፡፡ ከዚያ የተረፈ
ገንዘብ፣ መልክ፣ ጎሳ፣ ብሔር፣ ነገድ፣ ቋንቋ፣ የመሳሰሉት የጋብቻ መስፈርት ሊሆኑ አይችሉም፡፡
እግዚአብሔር እና ቅዱሳኑ በእነዚህ መስፈርቶች ውስጥ የሉምና፡፡ ለመሆኑ ላንተ (ላንቺ) የተዳር
[Type text] Page 27
መስፈርትሽ ምንድነው? ባሁኑ ጊዜ የተዳር መስፈርቱ ውጫዊ ነገር ስለሆነ የጋብቻ ክብር
ቀንሷል፡፡ ጋብቻ እኮ የመጀመሪያ ተቋም ነው በዚህ ዓለም ላይ ያለው ሕዝብ ሁሉ የተገኘበት፣
በገነት ውስጥ በእግዚብሔር የተመሠረተ፡፡ 2 ጴጥ.2፡1-2፣ 1 ቆሮ. 7፡37፡፡ ድንግልናን መጠበቅ
ራሱ ትዕግስት እና ጽናት ስለሚጠይቅ ይህን ይለማመዳሉና በእግዚአብሔር ለመጽናት ይረዳል፡፡
ድንግልናን መጠበቅ ታማኝነትን ያረጋግጣል፡- ድንግልናን ጠብቀን እንድንይዘው በአደራ
የተሰጠን የከበረ ንብረት ነው፡፡ ባለአደራ ፈጣሪያችን፣ በሚያስፈልግ ጊዜና ሰዓት ለትዳር
አጋራችን እንድንሰጠው ይጠብቀናል፡፡ ድንግልናውን ያልጠበቀ ግን አደራ በሊታ፣ ታማኝነትም
የጎደለው ይሆናል፡፡ ድንግልና ሳይኖራቸው የተጋቡ ሰዎች ሳይተማመኑ ይኖራሉ፤ ይህ ደግሞ
ለአንድ ትዳር ትልቁ ፈተና ነው፡፡ ምክንያቱም ባልና ሚስት ተማምነው እና ተዋደው ይኖራሉ
እንጂ ተቻችለው አይደለም፡፡ የአንድ ሰው አካል ላይ ያሉ ብልቶች ተግባብተው፣ ተዋደው፣
አንድ ሆነው፣ ተማምነው ይኖራሉ እንጂ ግድ ተቻችለው አይደለም፡፡ ባልና ሚስትም እንዲህ
ናቸው፡፡ ሚስት ለባሏ እግዚአብሔር በአደራ የሰጣትን ድንግልና ስትሰጠው በአደራ ጠባቂነት
እንዲያያት፣ እንዲያምናት፣ እንዲያከብራት፣ እንዲወዳት ያደርገዋል፡፡ ያን ጊዜ ይዋደዳሉ፣
ይከባበራሉ፡፡ ይህን ያደረገ እግዚአብሔር ነው፡፡ ሰው ግን እንደ ተራ ነገር ይቆጥራል፡፡
ድንግልናን መጠበቅ ችሎታ ነው፡፡ ምክንያቱም በውስጡ ጽናት፣ ብርታት፣ ትዕግሥት፣
ታማኝነት አለበትና፡፡
ድንግልናን መጠበቅ መጠንቀቅ ነው፡- ከበሽታ፣ ያለ አግባብ ወይም ሳያገቡ ከመውለድ፣ ክብርና
መልካም ስምን ከማጣት፣ ከመጸጸት ያድናል፡፡ ለወደፊት መንፈሳዊውም ሆነ ሥጋዊ ችግር
ከሚፈጥሩ የኑሮ ጠንቆች ሁሉ መቶ በመቶ ሊሰወር የሚችል መጠንቀቅ ቢኖር ድንግልናን
መጠበቅ ነው፡፡
ልብ ሳይከፈል ፈጣሪን እጅግ አድርጎ ለማስደሰት፡- ባሏንም ታስደስታለች(ከዚህ ይጀምራልና)፡፡
ድንግልናን ካጠፉ በኋላ የሚደረግ ጋብቻ አግብቶ የፈታ ሰው እንደሚፈጽመው እንደ ሁለተኛ
ጋብቻ ይቆጠራል፡፡ስሙም የመዐስባን ጋብቻ መባሉ ለዚህ ነው፡፡ ለመመንኮስ ተስሎ የነበረ ሰው
ቢያገባ የተሳለው ስእለት እንደ መጀመሪያ ጋብቻ ተቆጥሮ የሚፈጽመው ጋብቻ ለሁለተኛ ጊዜ
እንደሚያገባ ሰው እንደሚቆጠርበት ፍትሐ ነገሥት መንፈሳዊ ያስረዳል፡፡ በ 1 ቆሮ. 7፡33-34
‹‹የተጋባች ግን ባሏን እንዴት ደስ እንደምታሰኘው የዓለም ነገር ታስባለች፡፡›› ድንግልናቸውን
አጥተው የተጋቡ ባለትዳሮች ያጡበትን መንገድ በሕሊናቸው ማሰባቸው አይቀርም፡፡ ያንጊዜ
ደግሞ ላሉበት ትዳር ደስተኛ አይሆኑም፡፡ ምንም እንኳን በአካል መዋሐድ ቢችሉም የልቡና
ተዋሕዶ ለመፍጠር ይቸገራሉና ደስታቸው በእጅጉ ይቀንሳል፡፡ እንደዚህ ዓይነት ትዳር የሚመሩ
ሰዎች ብዙ ጊዜ ሰማያዊውን ዋጋ ትተው የዚህን ዓለም ቢዝነስ፣ ኑሮ፣ደስታ ወዘተ ሲያወሩ፣
ሲያስቡ እና ስያደርጉ ይኖራሉ፡፡ የትዳር መስፈርታቸውም ከእነዚህ የራቀ አይደለም፡፡
ድንግልናን መጠበቅ ጋብቻ ሳይዘገይ በጊዜው እንዲፈጸም ይገፋፋል፡- ከጋብቻ በፊት ዝሙት
ከተፈጸመ ለጋብቻ ያለው ውስጣዊ ፍላጎት ይቀንሳል፤ እንደመታሰርም ይቆጥሩታል፡፡ ባሁኑ ጊዜ
የሚታዩ እውነታዎችም ይህን የሚያሳዩ ናቸው፡፡ ብዙ ዓለማዊ ፊልሞችም ከጋብቻ በፊት
ዝሙትን የሚያበረታቱ ስለሆኑ ወጣቱ ሊርቃቸው ይገባል፡፡ ከጋብቻ በፊት የሚደረግ ሩካቤ
የጋብቻ ቀነ ቀጠሮ እንዲራዘም ከማድረጉም በላይ ለመለያየትም በር ከፋች ነው፡፡ ቢጋቡ እንኳን
ግን አንድ ጥያቄ ላንሳ! ከጋብቻ በፊት ድንግልናቸውን ያጡበትን ቀን በደስታ ነው ወይስ በሀዘን ነው
የሚያስቡት?
አጭር ምከር፡- ውድ ወጣት ስፖርት ለምን እንደምትሰራ በትክክል ንገረኝ! ለጤና ወይስ ጡንቻህን
እና ደረትህን ነፍተህ በሰው መሀል ለመሄድ ወይስ ለምን? ብረት በማንሳት ባሳበጥከው ደረትህ
አጭር ምከር፡- ውድ ወጣት ስፖርት ለምን እንደምትሰራ በትክክል ንገረኝ! ለጤና ወይስ ጡንቻህን
እና ደረትህን ነፍተህ በሰው መሀል ለመሄድ ወይስ ለምን? ብረት በማንሳት ባሳበጥከው ደረትህ
አንድ ኃጢአት በየቀኑ እየሰራ እንደሆነ ታውቃለህ? (ርቱዓ ሃይማኖት አንብብ):: የተነፋው
ደረትህን እያዩ በዝሙት የሚወድቁ ሴቶች እንዳሉ አስበህ ታውቃለህ?
ለመሆኑ የትኛው ስፖርት ዓይነት ደጋፊ ነህ እውነት በስፖርቱ መርሐግብር ነው ወይስ በራስህ መርሐግብር
ነው የምትመራው? ግን ምን ተጠቀምክ? እዚያ ያጠፋሀቸውን ሰዓቶችስ፣ ከዚያ ወጥተህ ደግሞ ስለ
ጫወታው ለማውራት ያጠፋኸውን ሰዓት አስብ፣ ምናለበት ያንን ዓለማዊ ትምህርት አንብበህበት እንደ
ቅጣው እጅጉ ሀገር ብታስጠራበት፣ የቤተ ክርስቲያንን ችግር ብትደፍን፣ የብዙ ስፖርተኞችን ስም ከነ
ክለባቸው፣ ደሞዛቸው፣ እድሜያቸው ማወቅን እንደ እውቀት ከምትቆጥር በሀገርህ ያሉ ቅዱሳንን ብታውቅ
ምን አለበት? ይህ የሰይጣን ሴራ ነውን ተወው፡፡
ሲኒማና ቴሌቪዥን
ተንቀሳቃሽ ስዕል ፊልም ይባላል፡፡ በሲኒማ የምናያቸው ነገሮች ተዋሕደውን የኛ አንድ አካል ሊሆኑ
ይችላሉ፡፡ ፊልም ላይ ያየኸውን ለጊዜው ልትጠላው ትችላለህ፡፡ ነገር ግን አንድ ቀን በቅጽበት ማሰብ
ትጀምራለህ፡፡ ሰይጣን ደግሞ ልዩ ልዩ የኃጢአት ሥራዎችን እንድትመለከት በር ይከፍታል፡፡
ወደፊት በምዕራባውያን የሚሠሩ ፊልሞች የሀገራችንን የማይውጥበት ምክንያት የለም፤ አሁንም እያየን
ስለሆነ፡፡ ብዙ ፊልሞች ትዕቢትን፣ የዘር ልዩነትን፣ አድልዎን፣ ጭካኔንና ግፍን፣ ቅንጦትን፣ ግለኝነትን፣ የራስ