Professional Documents
Culture Documents
5 7
5 7
5 7
ዕብ 5፥7-10
"እርሱም በስጋው ወራት ከሞት ሊያድነው ወደሚችል ከብርቱ ጩኸትና ከእንባ ጋር ጸሎትንና
ምልጃን አቀረበ፥ እግዚአብሔርንም ስለ መፍራቱ ተሰማለት፤
መልስ!
1ኛ ~~~ "በስጋው ወራት ይላል" ይህም ማለት በዚህ ምድር የኖረበትን 33 ዓመት ከ3 ወር
የሚያመላክት ነው። ከሞት ከተነሳ በኋላማ ወደ ቀደመ ክብሩ ስለተመለሰ በስጋው ወራት
እንዳወቅነው አሁን አናውቀውም፡፡ ለዚህም ነበር ቅዱስ ጳውሎስ አንዲህ ያለን፡-
" ነፍሴን ደግሞ አነሣት ዘንድ አኖራለሁና ስለዚህ አብ ይወደኛል። እኔ በፈቃዴ አኖራታለሁ
እንጂ ከእኔ ማንም አይወስዳትም። ላኖራት ሥልጣን አለኝ ደግሞም ላነሣት ሥልጣን አለኝ"
የዮሐንስ ወንጌል 10 : 17-18/ ለምን አለ?
" ነፍሴን ደግሞ አነሣት ዘንድ አኖራለሁና ስለዚህ አብ ይወደኛል። " የዮሐንስ ወንጌል 10 :
17
ከቅድስት ድንግል ማሪያም ከስጋዋ ስጋን ከነፍሷም ነፍስን ነስቶ ሰው ሆኖ የመጣው ይህን
የሞት ጽዋ ጠጥቶ በእርሱ ሞት እኛ ህይወትን እንድናገኝ አልነበረምን?
" አሁን ነፍሴ ታውካለች ምንስ እላለሁ? አባት ሆይ፥ ከዚህ ሰዓት አድነኝ። ነገር ግን ስለዚህ
ወደዚህ ሰዓት መጣሁ። "የዮሐንስ ወንጌል 12: 27
፨ ኢየሱስ ክርስቶስ እኮ ሁሉን ማድረግ የሚችል ኃያል አማላክ ነው። ነቢየ እግዚአብሔር
ኢሳያስ እንዲህ ይለናል፦
"ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፤
ስሙም ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥ የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል።
"ትንቢተ ኢሳይያስ 9 :6
ይህ ኃያል ተብሎ የተጠራው ህጻን ከማን የተወለደው ነው? ካልን ከቅድስት ድንግል
ማሪያም የተወለደው ነው።
በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጎአል። መልክና ውበት የለውም፥
ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም።
~~~ "ከዚችም ዓለም ገዦች አንዱ እንኳ ይህን ጥበብ አላወቀም፤ አውቀውስ ቢሆኑ
የክብርን ጌታ ባልሰቀሉትም ነበር"1ኛ.ቆሮ 2 : 8/
ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አለው፦ የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ በሰማያት ያለው አባቴ እንጂ
ሥጋና ደም ይህን አልገለጠልህምና ብፁዕ ነህ።
‹‹ዳሩ ግን እኔ ከአብ ዘንድ የምልክላችሁ አጽናኝ እርሱም ከአብ የሚወጣ የእውነት መንፈስ
በመጣ ጊዜ፥ እርሱ ስለ እኔ ይመሰክራል›› ዮሐ.15፡26
4ኛ--- ዕብ.5፥8 " እግዚአብሔርን ስለመፍራቱ ተሰማለት" ይላል። ይህ ማለት ጸሎቱ "ከሞት
አድነኝ" ያለው ተሰምቶለታል። ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ሞቷል፡፡
ጥቅሱን ስንመለከት ቅኔያዊ ነው። ከላይ ከላይ የሚናገረው ስለኢየሱስ ክርስቶስ ይምሰል
እንጂ በዋነኝነት የሚነግረን ግን ስለአዳም ነው።
ስለዚህ ቅዱስ ጳውሎስ በዕብ. 5፡7-10 የሚነግረን ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ
ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ከቅድስት ድንግለ ማሪያም ከስጋዋ ስጋን ከነፍሷ ነፍስን ነስቶ ሰው
ሆኖ ስለአዳም(የሰው ልጆች) መከራን መቀበሉ፣ በእለተ ሐሙስ በጌቴ ሴማኒ ለ5500
ዓመታት ሲዖል ሆኖ በሞተ ነፍስ ሲሰቃይ የነበረውን የአዳምን ልመና በማስተጋባት ‹‹ ይህቺ
የሞት ጽዋ ከእኔ ትለፍ›› አለ፡፡ አዳምም ከተቀበለው መከራ የተነሳ መታዘዝን ስለተማረ
እግዚአብሔር ልመናውን ሰማው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስም በዕለተ አርብ 9 ሰዓት ላይ በመስቀል
ላይ ሆኖ ‹‹ ተፈፀመ›› ብሎ ነፍሱን ከስጋው በፈቃዱ ለይቶ፣ በስጋው ወደ መቃብር በነፍሱ
ወደ ሲዖል ወርዶ በሲዖል ለነበሩት የምስራችን ሰበከለቸው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ እንዲህ
ይለናልና፡-
ይህ ነው ወንድሜ !!!