Professional Documents
Culture Documents
034956
034956
አክሲዮን ማህበር
ነሐሴ 2012 ዓም
ባህርዳር
መመስረቻ ጽሑፍ
እኛ ከዚህ በታች ስማችን፣ ዜግነታችንና አድራሻችን የተገለፀው መስራቾች በኢትዮጲያ ሕግ፣ በተለይም
በ1952 ዓ.ም በወጣው የንግድ ህግ መሰረት የአክሲዮን ማህበር ለማቋቋም በመወሰን ይህን የመመስረቻ
ጽሁፍ እና ከዚህ ጋር የተያያዘውን የመተዳደሪያ ደንብ አውጥተን የማህበሩን ካፒታል በስማችን አንጻር
የተመለከተውን አክሲዮን ለመግዛት ተስማምተናል።
አንቀጽ አንድ
ተ. ቁ ስም ዜግነት አድራሻ
አንቀጽ ሁለት
የማህበሩ መጠሪያ
አንቀጽ ሶስት
የማህበሩ ዋና መ/ቤትና ቅርንጫፎች
የማህበሩ ዋና መስሪያቤት በአማራ ክልል በባህርዳር ከተማ አስተዳደር ጣና ክፍለ ከተማ በቀበሌ 16 የቤት
ቁጥር አዲስ ነው፡፡ ማህበሩ ቅርንጫፍ ድርጅቶችን በኢትዮጲያ ውስጥና ከኢትዮጲያ ውጭ ሊያቋቁም
ይችላል።
አንቀጽ አራት
የማህበሩ አላማዎች
አንቀጽ አምስት
የማህበሩ ዋና ገንዘብ
1 ዶ/ር እንየው አባተ በላይ 4 10,000 40000 የለም 10000 የለም 30000 የለም
2 ንጉስ ሀይሉ ተገኘ 4 10,000 40000 የለም 10000 የለም 30000 የለም
3 ዶ/ር አዱኛ እውነቱ ማዘንጊያ 4 10,000 40000 የለም 10000 የለም 30000 የለም
4 ዶ/ር ሙሉጎጃም መንግስቱ ዘለቀ 4 10,000 40000 የለም 10000 የለም 30000 የለም
5 ቢልልኝ መንግስቱ ዘለቀ 4 10,000 40000 የለም 10000 የለም 30000 የለም
6 ዶ/ር በእውቀቱ ዘላለም ዘለቀ 4 10,000 40000 የለም 10000 የለም 30000 የለም
8 በእውቀቱ ድረስ መሰሉ 4 10,000 40000 የለም 10000 የለም 30000 የለም
9 አሳቤነህ አለማየሁ ምኑየ 4 10,000 40000 የለም 10000 የለም 30000 የለም
10 ሀብታሙ ጤናው ጥላሁን 4 10,000 40000 የለም 10000 የለም 30000 የለም
11 ደመቀ ብርሀኑ አማረ 4 10,000 40000 የለም 10000 የለም 30000 የለም
12 ትልቅ ታሪኩ አላምነህ 4 10,000 40000 የለም 10000 የለም 30000 የለም
14 እይላቸው አንተነህ ውባለም 4 10,000 40000 የለም 10000 የለም 30000 የለም
15 እንዳለው ምኑየ ቢያድግልኝ 4 10,000 40000 የለም 10000 የለም 30000 የለም
17 ግዛቸው ተፈራ ቀለምወርቅ 4 10,000 40000 የለም 10000 የለም 30000 የለም
18 ላመስግን ባንታምላክ አንተነህ 4 10,000 40000 የለም 10000 የለም 30000 የለም
19 ይበልጣል ትሳሴ ደመቀ 4 10,000 40000 የለም 10000 የለም 30000 የለም
20 አበባው ቁምሌ ደነቀው 4 10000 40000 የለም 10000 የለም 30000 የለም
አንቀጽ ስድስት
አክሲዮኖች
አንቀጽ ስምንት
የሂሳብ አመት
የትርፍ አከፋፈል
1. በየሂሳብ ዓመቱ መጨረሻ የማህበሩን ንብረት እና እዳ የሚያሳይ የሂሳብ ሚዛን /ባላንስ ሺት/
ተዘጋጅቶ ለዳይሬከተሮች ይቀርባል፡፡
2. የማህበሩ አመታዊ የሂሳብ ሁኔታ የሚያሳዩ ሰነዶች፣ ማለትም የሂሳብ ሚዛን /ባላንስ ሽት/ የትርፍና
ኪሳራ መግለጫ የንብረት ቆጠራ፣ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሪፖረት እና የኦዲተሮች ሪፖርት በማህበሩ
መዝገብ ላይ ለተመዘገቡ ባለአክሲዮኖች ቢያንስ ከመደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ቀን ቢያንስ 15
ቀን አስቀድሞ በሬኮማንዴ ይላካል፡
3. ከዚህ በታች ከንዑስ አንቀጽ 4/ሀ እና ለ/ሥር የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በዓመቱ ሂሳብ
መግለጫ ውስጥ እንደተመለከተው የማህበሩ የአመቱ የተጣራ ትርፍ፣ ጠቅላላ ወጪና ዋጋ፣ አላቂ
ለሚሆኑ ነገሮች መተኪያ ገንዘብ /አሞርታይዜሽን፣ አላዋንስ እና ለሌሎች መዋጮዎች ታክስና
ያለፈው ዓመት ግዴታዎች ከተቀነሱ በኋላ የሚታየው የተጣራ ገቢ ነው፡፡
4. ከተጣራው አመታዊ ትርፍ ላይ
ለ/ በጠቅላላ ጉባኤው ውሳኔ የጸደቁ ሌሎች ልዩ የመጠባበቂያ ሂሳቦችና የአሞርታይዜሽን ወጪዎች ከተቀነሱ
በኋላ ተራፊው በተከፈለው የአክሲዮን ድርሻ ልክ ለባለ አክሲዮኖች ይከፋፈላል፡፡
አንቀጽ አስር
የአስተዳደር አካሎች
ለ/ የዳይሬክተሮች ቦርድ
ሐ/ የቁጥጥር ኮሚቴ እና
መ/ ሥራ አስኪያጅ ናቸው፡፡
ጠቅላላ ስብሰባ
1. የባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባዔ ከፍተኛው የስልጣን አካል ነው፡፡ይህም ጉባኤ መደበኛና ድንገተኛ
ስብሰባ በደንቡና በንግድ ሕጉ መሰረት ያካሂዳል።
7. ከንግድ ህጉ ተቃራኒ ካልሆነ በቀር ማንኛዉንም ጉዳይ ላይ ስለማህበሩ ዉሳኔ ማሳለፍ ይችላል፡፡
9. የዳየሬክተሮች ቦርድ በሌላ ጊዜ እንዲሆን ካልወሰነ በቀር የማህበሩ ጠቅላላ ጉባዔ በአመት አንድ ጊዜ
ይካሄዳል፡፡ ሆኖም አመታዊ ጠቅላላ ጉባዔ ስብሰባ በሚደረግበት ጊዜ ጥር ወርን ማለፍ የለበትም፡፡
ድንገተኛ ስብሰባ ግን በማንኛውም ጊዜ ሊጠራ ይችላል፡፡
10. ጠቅላላ ጉባኤ የሚካሄደው ከጠቅላላ አባሉ ከ 50 በመቶ በላይ በስብሰባው መገኘቱን በማረጋገጥ
ይሆናል፡፡ ይህ ካልሆነ ለሁለተኛ ጊዜ ጥሪ እንዲተላለፍ ተደርጎ በሁለተኛው ስብሰባም በተመሳሳይ
መልኩ ከ 50 በመቶ መገኘቱን በማረጋገጥ ውይይቱን መጀመር ይቻላል፡፡ ይህ ካልሆነ ደግሞ
ለሶስተኛ ጊዜ ጥሪ እንዲተላለፍ ተደርጎ በዚህ ስበሰባ በተገኘው የሰው ሀይል ጉባኤውን ማስኬድ
ይቻላል።
11. የጉባኤ ውሳኔዎችን ለማጽደቅ ቆጠራው በአክሲዮን ድምጽ የሚወሰን ሲሆን ማንኛውም ውሳኔ ተፈጻሚ
የሚሆነው ከ 60 በመቶ በላይ ድጋፍ ማግኘት ሲችል ብቻ ነው፡፡ ሆኖም ግን የማህበሩ አባላት ድምጽ
እኩል በሚሆንበት ጊዜ የቦርዱ ፕሬዜዳንት ተጨማሪ የወሳኝነት ድምጽ ይኖረዋል፡፡
12. በውክልና ከጉባኤው የተገኘ ማንኛውም አካል ባለአክሲዮኑ ባለው የአክሲዮን ድርሻ መጠን ድምጽ
የመስጠት መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
13. የተያዙትን አክሲዮኖች ወይም የወከሉትን ቁጥር የሚቆጣጠሩ ከባላአከክሲዮኖች ወይም እንደራሴዎች
መካከል ሁለት ድምጽ ተቀባዮች ይሾማል።
14. ማንኛውም ባለአክሲዮን ወይም እንደራሴ በምስጢር እንዲሆን ካልጠየቀ በቀር ማንኛውም ውሳኔ
ሚተላለፈው በድምጽ ቆጠራ ነው፡፡
15. ጉባዔው በሚከሄድበት ጊዜ የጠቅላላ ጉባዔው አጀንዳ ሊሻሻል ይችላል፡፡ ይህ ሊሆን የሚችለው ግን
እንዲመረጡ የተፈቀደላቸው ይበልጡን /የማጆሪቲ/ የአክሲዮን ድርሻ የያዙት ሲስማሙበት ብቻ ነው፡፡
16. ባለአክሲዮኖች ወደ ስብሰባ ሲመጡ እስከ አከሲዮን ድርሻቸዉ በማህበሩ መዝገብ መመዝገብ አለባቸዉ፡
፡
17. ምልዓተ ጉባዔው /ኮረም/ እና የድምጽ ብልጫ በሚመለከት በ 1952 ዓ.ም.በኢትዮጵያ የንግድ ህግ
ቁጥር 421፣425 እና 428 የተደነገገው ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
የዳይሬክተሮች ቦርድ
1. ማህበሩ የሚተዳደረው በባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባዔ በሚመረጡ ቢያንስ 3 ቢበዛ 12 አባሎች ባሉት
የዳይሬክተሮች ቦርድ ነው፡፡ የቦርዱም የስራ ዘመን ሶስት አመት ነው።
5 ይግዛው ካሴ _______________________________አባል
2. አሳቤነህ አለማየሁ እና
ለ/ በጠቅላላው የባለአክሲዮኖች ስብሰባ ከተወሰነው ሳያልፍ የማህበሩን የንግድ ስራ ለማካሄድ አስፈላጊ የሆኑ
እርምጃዎችን መውሰድ፣
ሠ/ በአገር ውስጥ ከሚገኝ ማንኛውም ባንከ የገንዘብ ድርጅት ወይም ተቋም ለማህበሩ አላማዎች ማከናወኛ
የሚውል ብድር በመያዣ ወይም ያለመያዣ ለመበደር፣ ለመደራደር፣ ለመዋዋልና ለመፈረም፣
ሥራ አመራር
ተቆጣጣሪዎች/ኦዲተሮች/
1. ማህበሩ በዓመት 1 (አንድ ጊዜ) በሚያደርገው ስብሰባ የማህበሩን ኦዲተር ወይም ኦዲተሮች
ይሾማል፡፡የሚሾመው ኦዲተር ወይም ኦዲተሮች በሂሳብ ምርመራ ሥራ የተፈቀደለት ሰው ወይም
ድርጅት ይሆናል፡፡ የእነዚህም ኦዲተሮች ተግባር ስልጣንና ሃላፊነት በህግና በተለይም በንግድ
ህግ ቁጥር 386 እና 460 መሰረት ይሆናል፡፡
የማህበሩ ቆይታ
ማህበሩ የተቋቋመው ላልተወሰነ ጊዜ ሲሆን በንግድ ህግ ቀጥር 495 ሥር በተገለጹት ምክንያቶች የሚፈርስ
ይሆናል፡፡
ተ.ቁ ሙሉ ስም ፊርማ
7 በሀይሉ ቢሰነብት ሞሴ
13 ጌታቸው አበ መዋኸኝ
16 ይግዛው ካሴ ትዝዙ
አንቀጽ አንድ
የባለአክሲዮን መብት፡-
እያንዳንዱ ባለአክሲዮን ፡-
ሐ/ የማህበሩን የተጣራ ትርፍና ማህበሩም ሲፈርም በሚደረገው የሂሳብ ማጣራት ድርሻን የመካፈል
ረ/ አግባብ ባለው ህግ፣ የመመስረቻ ጹሁፍና በዚህ የመተዳደሪያ ደንብ በሚሰጡት መብቶች የመጠቀም
መብት ይኖረዋል፡፡
የባለአክሲዮን ግዴታ
እያንዳንዱ ባለአክሲዮን፡-
ሐ እያንዳንዱ አባል በየወሩ ብር 1000(አንድ ሺህ) የማዋጣት ግዴታ አለበት። አስፈላጊ በሆነ ጊዜ
ሐ. አክሲዮን ማህበሩ በሚያደርገው ወርሃዊ መዋጮ በወቅቱ ተገኝቶ ክፍያውን የመክፈል ግዴታ አለበት
ይህ ካልሆነ ግን ለአንድ ወር ክፍያ መዘግየት በየወሩ የሚከፍለውን 10% ቅጣት ይኖርበታል።ቅጣቱን
እናወርሃዊ ክፍያውን በአንድ ወር ውስጥ ካልከፈለ በወሩ ልክቅጣቱ እየተባዛ ይከፍላል።
አንቀጽ ሁለት
የአክሲዮን ዋጋ /ፕሬሚየም/
አንቀጽ ሶስት
አክሲዮን ስለማስተላለፍ
አክሲዮኑን ለሌላ ማስተላለፍ የተከለከለ አይደለም። ቅድሚያ የሚሰጠው ለአሉት ባለ አክሲዮኖች ይሆናል፡፡
አንቀጽ አራት
1. አክሲዮኖችን በጋራ ባለ አክሲዮኖች ወኪል ይሾማል፡፡ የሾሙትን ሰው ስምና አድራሻም በባለ አክሲዮኖች
መዝገብ ያስመዘግባሉ፡፡ ማህበሩ መጥሪያዎቹን የሚልከው ለዚሁ ለተሾመው ለባለ አክሲዮኖች ተወካይ
ይሆናል፡፡
2. በመያዣም ሆነ በአላባ አከሲዮን ያስያዘው ስው ስምና አድራሻ ያስያዘበትን ምክንያትና መብቱን ጨምሮ
ማስመዝገብ አለበት ማህበሩም ማስጠንቀቂያዎቹን /ኖቲስ/ የሚልከው ለባለ አክሲዮኑና ለመያዣ/አላባ/
ተጠቃሚው ነው፡፡
አንቀጽ አምስት
ስለስራ አስኪያጅ
2. በመዝገቡ ውስጥ ጉድለት/ስህተት/ መኖሩ እንደታወቀ የማህበሩ ስራ አስኪያጅ ይህን ጉድለት በሰላሳ
ቀናት ውስጥ እንዲስተካከል /እንዲታረም/ ያደርጋል፡፡
2. የመክፈያ ጊዜው ካለፈ በኋላ ድርሻውን በወቅቱ ላልከፈለ ባለአክሲዮን ማህበሩ ክፍያው
እንዲደረግ ይጠይቃል፡፡ ባለአክሲዮኑ ደብዳቤ በደረሰው 30 ቀናት ቀን ውስጥ ክፍያውን
ባያጠናቅቅ ማህበሩ ያልተከፈለባቸውን አክሲዮኖች በሃራጅ ለመሽጥ ይችላል፡፡
አንቀጽ ሰባት
ማህበሩ የሚያድላቸው አክሲኖች ጉዳት ቢደርስባቸው፣ ቢበላሹ፣ ቢጠፉ፣ ወይም ቢሰረቁ የዳይሬክተሮች
ቦርድ በሚሰጠው መመሪያ 200 ብር (ሁለት መቶ ብር) ባልበለጠ ክፍያ እንደገና ይታደላል፡፡
አንቀጽ ስምንት
ጉባዔዎች
1. የዳይሬክተሮች ቦርድ በሌላ ጊዜና ቦታ እንዲሆን ካልወሰነ በቀር የማህበሩ ጠቅላላ ጉባዔ በየአመቱ አንድ
ጊዜ በዋናው መስሪያ ቤት ይካሄዳል፡፡ ሆኖም የአመታዊ ጠቅላላ ጉባዔ ስብሰባ በየበጀት አመቱ መጀመሪያ
ሀምሌ ወር ማለፍ የለበትም፡፡ ድንገተኛ ግን በማንኛውም ጊዜ ሊጠራ ይችላል፡፡
3. የመደበኛውም ሆነ ድንገተኛ ጠቅላላ ስብሰባ በምልዓተ ጉባዔ አለመሟላት ምክንያት ሊካሄድ ካልቻለ
ሁለተኛ ጥሪ ስብሰባው ከመካሄዱ 15 ቀናት በፊት ይተላለፋል በሁለተኛው ስብሰባ ጥሪ ምላዕተ ጉባዔ
ካልሞላ ስብሰባው ቀጥሎ ውሳኔዎች ማስተላለፍ ይቻላል፡፡
4. አግባብ ባለው ህግ፣ በመመስረቻ ጹሁፍና በዚህ መተዳደሪያ ደንብ መሰረት በሌላ ጉባኤዎች ይውሳሉ
ከሚባሉ ጉዳዮች በስተቀር አመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ በማንኛውም ጉዳዮች ላይ መወያየትና ውሳኔ ማሳለፍ
ይችላል፡፡
አንቀጽ ዘጠኝ
ስራ አመራሩ /ስራ አስኪያጅ/ የተመዘገቡ በላአክሲዮኖች ወይም ተወካዮቻቸው በጉባዔ እንዲገኙ ተመዝግቦ
ባለው አድራሻቸው በተራ የፖስታ መልዕክት አማካኝነት ጥሪ ያደርግላቸዋል፡፡በተጨማሪም ህጋዊ
ማስታወቂያ ለማውጣት በተፈቀደለት በማህበሩ ዋና መስሪያ ቤት በሚገኙበት ቦታ በማከፋፈል ጋዜጣ
አማካኝነት ጥሪው ሊገለጽ ይችላል፡፡
ቀሪው መልዕከት አግባብ ባለው ህግ፣ የመመስረቻ ጹሁፍና መተዳደሪያ ደንብ የሚጠየቀውን መረጃ
/ኢንፎርሜሽን/ሁሉ ያሟላ መሆን ይኖርበታል፡፡
አንቀጽ አስር
1. በንግድ ህጉ አንቀጽ 403 መሰረት በእያንዳንዱ ጉባዔ ላይ የተገኙትን ማህበርተኞች መቆጣጠሪያ ሰነድ
መያዝ አለበት፡፡
2. በስብሰባ ላይ የተደረጉ ውይይቶችና ክርክሮች በንግድ ህጉ አንቀፅ 411 እና 412 መሠረት በቃለ-
ጉባዔው ተመዝግበው እንዲቀመጡ ይደረጋል፡፡
ማንኛውም ማህበርተኛ በማህበሩ ዋና መስሪያ ቤት በመገኘት ከዚህ ቀጥሎ ያሉትን ሰነዶች በማንኛውም
ጊዜ ለመመርመር ወይም ኮፒዎችን የመውሰድ መብት አለው፡፡ ሊሰጡት የሚችሉ ሰነዶች የሚከተሉት
ናቸው፡፡
2. ያለፉትን ሶስት የሂሳብ ዓመታት በሚመለከት ዳይሬክተሮችና ኦዲተሮች ለጠቅላላ ጉባዔው ያቀረቧቸው
ሪፖርቶች
የእንደራሴነት ስልጣን
3.በጉባዔ የመተካት ውክልና በጹሁፍ ሆኖ ቀን የተጻፈበትና በወካዩ ባለአክሲዮን የተፈረመ መሆን አለበት፡፡
አጀንዳ
ፀሀፊ
የሥራ አመራር
1. በጉባዔዎች ሁሉ ሰብሳቢ የዳይሬክተሮች ቦርድ ፕሬዝዳነት ነው፡፡ እርሱም የሌለ እንደሆነ ከዳይሬክተሮቹ
በስራ ቀደምትነት ያለው /ሲኒየር/ ሰብሳቢ ይሆናል፡፡ ሁለቱም የሌሉ ቢሆን ካሉት ዳይሬክተሮች በስራ
ቀደምትነት ያለው ይሰበስባል፡፡
3. ማንኛውም ባለአክሲዮን ወይም እንደራሴ በምስጢር እንዲሆን ካልጠየቀ በቀር ማንኛውም ውሳኔ
የሚተላለፈው በድምጽ ቆጠራ ነው፡፡
ምልአተ ጉባዔው /ኮረም/ እና የድምጽ ብልጫን በሚመለከት በ 1952 ዓ.ም በወጣው የኢትዮጲየ የንግድ
ህግ ቁጥር 421፣ 425 እና 428 የተደነገገው ተፈጻሚ ይሆናል፡፡
1. የዳይሬክተሮች ቦርድ በህግ፣ በማህበሩ መመስረቻ ጹሁፍ፣ መተዳደሪያ ደንብና በጉባኤው ውሳኔዎች
የተሰጡትን ስልጣንና ግዴታዎች ይፈጽማል
2. የዳይሬክተሮች ቦርድ በተለይም የሚከተሉት ሥልጣንና ግዴታዎች ይኖሩታል፡
ሀ/ የማህበሩን ስራ ይመራል
ለ/ ጠቅላላ ጉባዔው በሚሰጠው መመሪያ መሰረት የማህበሩን አላማ ግቡን የሚመታበትና
የሚሰምርበትን እርምጃወዎች ሁሉ ያከናውናል፡፡
ሐ/ የስራ ኃላፊዎችን ይሾማል፣ ደመወዛቸውን ይተምናል፡፡ ስጦታን ስንብትንና ጡረታን
በሚመለከት ይወስናል፡፡
መ/ የማህበሩን የማይንቀሳቀሱም ሆነ የሚንቀሳቀሱ ንብረቶችን ይገዛል በዚህም እስከ ብር 1
ሚሊዮን ብር ድረስ በቦርዱ ውሳኔ መሰረት ግዥ የሚፈጽም ሆኖ ከብር 1 ሚሊዮንብር በላይ
ለሆነ ግዥ ግን የጠቅላላ አባሉ ውሳኔ መኖር አለበት
ሠ/ የብድርና የመያዣ ውሎችን ይዋዋላል፤ ለማህበሩ ተቀጣሪዎች የቁጠባ ሂሳብ በመክፈት
የተለያዩ እቅዶችን ያዘጋጃል፡፡
ረ/ በኢትዮጲያ ወይም ከኢትዮጲያ ውጭ የማህበሩ ቅርንጫፎች እንዲከፈቱ ይወስናል፡፡
ሸ/ ተገቢ/ጠቃሚ የመሰለውን ሃሳብ፣ የማህበሩን ገንዘብ ኢንቨስት ማድረግን ጨምሮ ለጠቅላላ
ጉባዔው ያቀርባል፡፡
4. ዳይሬክተሮች በማህበሩ ሥራ አስኪያጆችን ወይም ወኪልነት የጋራ ሃላፊነት አለባቸው፡፡
አንቀጽ አስራ ሰባት
1. በተደጋጋሚ መመረጥ ያላቸው መብት እንደተጠበቀ ሆኖ የአስተዳዳሪዎች የስራ ዘመንሶስት አመት ነው፡፡
ሆኖም ተተኪዎች ተመርጠው እስከሚረከቧቸው ድረስ በስራ ይቆያሉ፡፡ የዳይሬክተሮች ምርጫ የሚከናወነው
በሚስጥር ድምጽ አሰጣጥ ስርዓት ነው፡፡
2. አንድ ወይም ከዚያ በላይ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ቢጎድሉት/ቢወጡ/ ቀሪዎች ግማሽ በላይ ከሆኑ
በወጡት ምትክ ከባለአክሲዮኖቹ መካከል መርጠው ይሾማሉ፡፡ ቀሪዎቹ ዳይሬክተሮች ከግማሽ በታች ከሆኑ
የጎደሉትን ለመሙላት ጠቅላላ ጉባዔ ይጠራል፡፡ የተሾመም ካሉ ለአመታዊ ጠቅላላ ጉባዔ ቀርበው ውሳኔ
ይሰጥባቸዋል፡፡ ሹመቱ የፀደቀ እንደሆነ የተተካው ሰው ያቋረጠውን የአገልግሎት ዘመን ይሸፍናል፡፡ ሹመቱ
የጸደቀ እንደ ሆነ የተተካው ሰው ያቋረጠው የአገልግሎት ዘመን ይሽፍናል፡፡ ሹመቱ ተቀባይነት ካላገኘ
ክፍት ቦታው በአመታዊ ጠቅላላ ጉባዔው ይተካል፡፡
አንቀጽ ሃያ
2. ከዓመታዊ ጠቅላላ ጉባዔ በኋላ በሚደረገው የመጀመሪያው የቦርድ ስብሰባ የዳይሬክተሮች ሰብሳቢ
/ፕሬዝዳንት/ ይመረጣሉ፡፡ ሰብሳቢው ለአንድ አመት ወይም የሚተካው ሰው ቦታውን ተረክቦ ስራውን
እስከሚጀምር ድረስ ያገለግላል፡፡ ቦርዱ የሾመውን ሰብሳቢ ሊሽረው ይችላል፡
ሐ/ የማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ በሚያዘው መሰረት ዓመታዊ በጀት፣ የስራ ፕሮግራምና የሂሳብ ሪፖርት
እንዲሁም ሌሎች እንቅስቃሴዎችን ካዘጋጀና ከመረመረ በኋላ ለቦርዱ ያቀርባል፡፡
መ/ ሠራተኛ ይቀጥራል፣ ዕድገት ይሰጣል ያስተዳድራል፣ የደመወዝ ክፍያን የስራ ሁኔታዎችን ይወስናል፡፡
ለዋናው ስራ አስኪያጅ በቀጥታ ተጠሪ የሆኑትን ሃላፊዎች መርጦ እንዲሾሙ ለቦርዱ ያቀርባል፡፡
ሠ/ በዳይሬክተሮች ቦርድ በተፈቀደው የስራ ፕሮግራም መሰረት የማህበሩ የሂሳብ አያያዝ ደንብና ስርዓት
በሚፈቅደው መሰረት ወጭዎችን ያጸድቃል፡፡
ረ/ የማህበሩን አመታዊ ሂሳብ የሚመረምሩ የውጭ ኦዲተሮችን ምርጫና ሹመት በሚመለከት ለቦርዱ
ሃሳብ/ምክር/ ያቀርባል፡፡
ቀ/ የስራ መጓተትን የሚያስቀርና ትርፋማነትን የሚጨምር የተቀላጠፈ የቁጥጥር መዋቅር አሰራር ያዘጋጃል፡፡
3. የዳይሬክተሮች ቦርድ የቅርብ ክትትል በማድረግ የተሰጠውን ስልጣን በከፊል ወይም በሙሉ፣
የማይንቀሳቀስ ንብረት መሸጥንና ማስያዝንም ጨምሮ፣ ለዋናው ስራ አስኪያጅ ውከልና መስጠት ይችላል፡፡
4. ዋናው ስራ አስኪያጅ ወይም እርሱ የሚወክለው ተወካይ በማንኛውም የዳይሬክተሮች ቦርድ ጉባዔ ላይ
ይገኛል፡፡ በውይይቱም ተካፋይ ሊሆን ይችላል፡፡
አንቀጽ ሃያ ሁለት
ስለ ኦዲተሮች
1. ኦዲተሮችና ረዳት ኦዲተሮች በህግ፣ በማህበሩ መመስረቻ ጹሁፍና በመተዳደሪያ ደንቡ የተጠቀሱት
ስልጣንና ግደዴታዎች አሏቸው፡፡
ለ/ የማህበሩን ንብረት፣ ሂሳብ ማመዛዘኛ ትርፍና ኪሳራውንም የሚያሳዩትን መዛግብት ትክክለኝነት ማረጋገጥ
ሐ/ የዳይሬክተሮች ቦርድ የሰጠው ሪፖርት የማህበሩን ትክክለኛ ገጽታ የሚያሳይ መሆኑን ማረጋገጥ፡፡
አንቀጽ ሃያ ሶስት
ስለተጨማሪ ኦዲተሮች
የካፒታሉ ከ ሀያ አምስት በመቶ /25 % ያላነሰ ይዞታ ያላቸው ባለአክሲዮኖች በራሳቸው ወጪ ተጨማሪ
ኦዲተሮች ሊሾሙ ይችላሉ፡፡ የተጨማሪ ኦዲተሮች ሊሾሙ ይችላሉ፡፡ የተጨማሪ ኦዲተሮች ስልጣንና ግዴታ
ቀደም ሲል ከተመረጡት ኦዲተሮች ጋር ተመሳሳይ ይሆናል፡፡ የተጨማሪ ኦዲተሮችን የስራ ዋጋና አበል
በሚመለከት ማህበሩ በከፊል ወይም በሙሉ ይከፍል እንደሆነ ጠቅላላ ጉባዔው ይወሰናል፡፡
አንቀጽ ሃያ አራት
1. ከተጣራ ትርፍ በየዓመቱ 5% ለህጋዊ የመጠባበቂያ ገንዘብ ይነሳል፡፡ ይህም የሚሆነው ህጋው የሆነው
የመጠባበቂያ ገንዘብ የማህበሩን ዋና ገንዘብ 20% እስኪደርስ ነው፡፡
2. ከዳይሬክተሮች ቦርድ ወይም ከማንኛውም ኦዲተር ሃሳብ የቀረበለት እነደሆነ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔው
ተጨማሪ ወይም አማራጭ የመጠባበቂያ ገንዘብ እንዲኖር መወሰን ይችላል።
አንቀጽ ሃያ አምስት
የሂሳብ አያያዝ ስርዓት
1.ማህበሩ በህጉ መሰረት ተቀባይነት ያለዉ የሂሳብ አያያዝ ስርዓት ይኖረዋል፡፡
2.ማህበሩ ሂሳቡን በአመት አንድ ጊዜ መዝጋት ይኖርበታል፡፡
አንቀጽ ሃያ ስድስት
ስለ ትርፍ አደላደልና አከፋፈል
1. የማህበሩ እዳዎችና ወጪዎች ከተቀነሱና እንዲሁም የመጠባበቂያ ገንዘብ ከተነሳ በኋላ ከትርፍ ቀሪ
የሆነውን ገንዘብ ለባለአክሲዮኖች እንዲከፋፈል ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባዔው ውሳኔ ይሰጥበታል፡፡
2.ትርፉም የሚከፋፈለው ባለአክሲዮኖች በከፈሉት ገንዘብ መጠንና በወል በተጠቀሰው የቀደምትነት መብት
መሰረት ነው፡፡
3. የትርፍ ድርሻዎች የሚከፈልበት ቀንና የአከፋፈሉ ሁኔታ በአመታዊ ጠቅላላ ጉባዔ የሚወሰኑ ናቸው፡፡
አንቀጽ ሃያ ሰባት
ስለማህበሩ መፍረስና ሂሳብ ማጣራት
1. ማህበሩ በህግ በተመለከተው እና በጠቅላላ ጉባዔው ውሳኔ መሰረት ይፈርሳል፡፡
2. ማህበሩ እንዲፈርስ ጠቅላላ ጉባዔው በወሰነ ጊዜ ማህበሩ ሶስት ሂሳብ አጣሪዎች ይሾማል፡፡
3. ማህበሩ እንዲፈርስ ትዕዛዝ የተሰጠው በፍርድ ቤት ውሳኔ ሲሆን የዳይሬክተሮች ቦርደ ጠቅላላ ጉባዔውን
ጠርቶ የፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ በተሰጠ --30 ቀን ውስጥ ሶስት ሂሳብ አጣሪዎች ይሾማል፡፡
4.ማንኛውም የማህበሩ አባልም ሆነ ኦዲተር የሂሳብ አጣሪዎችን ሹመት በመቃወም ያመለከተ እንደሆነ
የቀረበው መቃወሚያ በቂ ምክኒያት ያለው ሆኖ ካገኘው ጠቅላላ ጉባዔው ሹመቱን ሊሽረው ወይም
ሊያስቀረው ይችላል፡፡
ሹመቱ በተካሄደት ጊዜ በጠቅላላ ጉባዔው ውሳኔ የተሰጠበት ካልሆነ፣ለሂሳብ አጣሪዎች የሚከፈለው አበል
ማህበሩ በፈረሰበት ጊዜ ለዋናው ስራ አስኪያጅ በሚከፈለው አበል ልክ ነው፡፡
አንቀጽ ሃያ ስምንት
አንቀጽ ሃያ ዘጠኝ
የማጠቃለያ ድንጋጌ
በመመስረቻ ጹሁፉ ወይም በዚህ መተዳደሪያ ደንብ በግልጽ ያልተካተቱ ጉዳዮች በንግድ ህጉ መሰረት
ይወሰናል፡፡
መስራች አባላት፡-
7 በሀይሉ ቢሰነብት ሞሴ
13 ጌታቸው አበ መዋኸኝ
16 ይግዛው ካሴ ትዝዙ