2

You might also like

Download as docx, pdf, or txt
Download as docx, pdf, or txt
You are on page 1of 7

የቀጠና 11 መኖርያ ቤቶች የሰላምና

የትብብር ማህበር
አዲስ አበባ፡ ኢትዮጲያ
ምስረታ
. አድራሻ፡- ን/ስ/ላ/ከ/ከተማ ወረዳ 11 ቀጠና 1
. የምሰረታ ዘመን ፡- መስከረም 3 ቀን 2015 ዓ.ም
. ዘርፍ ፡- ማህበራዊ አገልግሎት

 የአባላት ብዛት -በቤት ቁጥር ብዛት……….የቤት ባለቤቶች


 አደረጃጀት - በአራት(4)
 የገቢ ምንጭ ፡- የአባላት መዋጮ
 ለትርፍ - ያልተቐቐመ
. መግለጫ - ከላይ በተጠቀሱ የመኖርያ ቤት ከሚገኙ አጠቃላይ ነዋሪ
በቅንነትና በዕኩል ተሳትፎ ለጋራ ደህንነት እና አከባቢው ለኑሮ
ምቹ እንዲሆን ለማድረግ በትብብር የተቐቐመው ማህበር ነው፡

አደረጃጀት
ማህበሩ የተቐቐመበትን ዓላማና ዕቅድ ከግብ ለማድረስ እንዲመቸው በተጨማሪም ግልፅና
ቀልጣፋ አገልግሎቱን ለአባላቱ ለማድረስ በአራት(4)መዋቅር በመደራጀት የተመሰረተ ነው፡፡
1 ኛ. የማህበሩ አስተዳደር ክፍል
2 ኛ. የማህበሩ ፋይናንስ ክፍል
3 ኛ. የማህበሩ ንበረት ክፍል
4 ኛ. የማህበሩ ኦዲት ክፍል
ከላይ በዝርዝር በተቀመጠው የማህበሩ የአደረጃጀት ክፍሎች ከአንድ(1)በላይ የስራ ድርሻ
ያላቸው ሲሆኑ፡የተጠቀሱትን የስራ ሐላፊነቶችን የሚያከናውኑት ሰዎች (አመራሮች)
(ኮሚቴዎች)ከባለቤቶቹና በቐሚነት ነዋሪ ከሆኑት የማህበሩ አባላት ውሰጥ በእጩነት
ቀርበው(ተጠቁመው) የተመረጡት ቢቻ ናቸው፡፡
ማህበሩ በአባላቱ አርቃቂነትና በጠቅላላ ጉባኤ በአፀደቀው የመተዳደርያ ደምብ መሰረት
የሚመራ ሲሆን አጠቃላይ የማህበሩ አባላትም፡ሆኑ የማህበሩ ኮሚቴ፡የማህበሩ አባላት
በመሆናቸው ቢቻ፡ግዴታና ውዴታ እንዲሁም መብትና ጥቅም ያላቸው የሆናሉ፡፡

የማህበሩ የአደረጃጀት ክፍል ክንውኖች(ስራዎች)


1 ኛ. የማህበሩ አስተዳደር ፡- የሊቀ መንበርነት
፡- የፀሓፊነት
፡- የመረጃ ስርጪት
፡- የቅጥር ሁኔታን
2 ኛ. የማህበሩ ፋይናንስ ፡- የገንዘብ መዋጮ መሰብሰብ
፡- ክፍያ የመፈፀም
፡- ግዥ የማከናወን

3 ኛ. የማህበሩ ንበረት ክፍል ፡- የመረከብ


፡- የመቆጣጠር
፡- የማሰራጨት
፡- የመሰብሰብ
፡- የመጠየቅ
4 ኛ. የማህበሩ ኦዲት ክፍል ፡- አጠቃላይ የሐብት መጠንን
፡- የመጠየቅ ስራ
፡- የመቆጣጠር ስራ
፡- የማረጋገጥ ስራ
፡- የማሳወቅ(ሪፖርት ማቅረብ)ስራ

የዝህ ማህበር የምስረታ ሰነድና የማህበሩ መተዳደርያ ድንብ፡በሁሉም የማህበሩ አባላት ፍሎጎት
እና ሁኔታ የተሳናዳ ስነድ ሲሆን፡ይህ ማህበር በመተዳደርያ ደንቡ ላይ በግልፅ እንዳስቀመጠው
ለንግድ ስራ ወይም ለትርፍ ያላተቐቐመ እና በሃይማኖታዊም ሆነ በፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ
እንደ ማህበር ምንም አይነት እንቅስቃሴ ማድረግ የማየፍቀድ መሆኑን የደነገገ ሲሆን፡ነገር ግን
ማንኛውም የማህበሩ አባል በነዚህ ጉዳዮች ላይ የመሳተፍ የመጋበዝና የማዘጋጀት መብትን
የማይነፍግ ነው፡፡

ማስታወሻ፡-ይህ የማህበሩ መመስረቻ ሰነድ በማንኛውም ጊዜ የማሻሻልና የመቀየር


መብቱ የአባላቱ ቢቻ ሲሆን፡በጠቅላላ ጉባኤና በድምፅ ብልጫ ይሆናል፡፡

የማህበሩ መተዳደርያ(ህግ) ደንብ


የማህበሩን ዓላማና ዕቅድ ከግብ ለማድረስ እንዲሁም የማህበሩ አባላት በእኩል ተስትፎ
በሚጠበቅባቸው ፍጥነት እንዲጓዙ የሚያደረግ የጋራና የተናጥል (ለጠቅላላ አባላትና ለማህበሩ
አመራር)የሚውል የመተዳደርያ ደንብ አረቂቆ በጠቅላላ ጉበኤ በማፅደቅ ከምስረታው ዕለት
ጀምሮ ስራ ላይ አውሏል፡፡
አንቀፅ አንድ(1) የማህበሩ መተዳደርያ ደንብ በዝርዝር

1. ማንኛውም የማህበሩ አባል ለማህበሩ ዓላማና ህገ ደንብ ተገዥ መሆን አለበት፡፡


2. የማህበሩን ህልውና በሚጠብቁና በሚያረጋግጡ ሁኔታዎች ላይ ከሁሉም አባላቶች ጋር
እኩል ተሳትፎ ማደረግ ይኖረበታል፡፡
3. በማህበሩ አባላት በድምፅ ተመርጠው ማህበሩን ከሚያሰተዳድሩት ኮሚቴዎች
የሚተላለፈውን ትዕዛዝ በተቀመጠው የግዜ ሰሌዳ ውስጥ መፈፀምና ማጠናቀቅ
ጊዴታው ነው፡፡
4. ማንኛውም አባል በአከባቢው የሚፈጠሩትን ሁከቶችን፡የአከባቢ የንፅህና ማጓደልን
እንዲሁም የማንኛውንም የቤት የግንባት ለውጥ በሚደረግበት ወቅት ክትትል
እንዲደረግ መረጃ የመስጥት ጊዴታ አለበት፡፡

5. በአከባቢው የሚኖር የማህበሩ አባል(ባለቤት) በቤቱ ላይ የግንባታ ለውጥ ለማድረግ


ሲፈልግ ከአስር(10)ቀን ቀድም ብሎ ለማህበሩ ኮሚቴ ማሳወቅ ጊዴታ ይኖረበታል፡፡
6. የማህበሩ አባል የሆነ፡የቤት ባለቤት ቤቱን የአከራየ አንደሆነ የአከራይ ተከራይ ውልና
የተከራይን መታወቅያ ኮፒ ለማህበሩ አሰተዳደር በመሰጠት ማሰተዋወቅ ይኖረበታል፡፡
7. የማህበሩ አባል የመኖርያ ቤቱን አከራይቶ በማህበሩ አቅራቢያ የማይገኝ ከሆነ በማህበሩ
ያለውን ተሳትፎና መብት በጊዝያውነት ለተከራይ የማስተላለፍ ጊዴታ ይኖርበታል፡፡
8. የማህበሩ መዋጮ በመጀመርያው በማህበሩ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በተወሰነው የመዋጮ
መጠንና በተቀመጠው ጊዜ ገደብ ውሰጥ የሚፈፀም ይሆናል፡፡
9. ማህበሩ ከአባላቱ የሚሰበስበውን ወረዊ መዋጮን ወር በገባ በመጀመርያው ዕለተ ……
የሚሰበሰበ ይሆናል፡፡
10. በማህበሩ ማንኛውም አባለ በማንኛውም ሁኔታ በአባልነት ከተመዘገበበት አከባቢ ለቆ
ቢሄድ እንዲሁም ለማህበሩ ቢያሳውቅ የሽኝት ዝግጅት ይደረግለታል፡፡
11. በማህበሩ ኮሚቴ ሆኖ ስያገለግል የነበረ አባል በማንኛውም ሁኔታ ማህበሩ ከሚያወቀው
የመኖረያ አድራሻ ለቆ ቢሄድ ወይም ቢያከራይ ለተከራይም ሆነ ለሌላ አካል
የኮሚቴ(አስተዳደራዊ ስራውን) ማሰተለለፍ አይችልም፡፡
12. በማህበሩ አባል መሆን የሚችለው የቤት ባለቤት ቢቻ ሲሆን ተከራይን ግን የቤቱ
ባለቤት በማህበሩ ላይ ያለውን መብትና ግዴታውን ለማህበሩ በፁሑፍ በማሳወቅ
ውክልና ከሰጠው እና ተወካዩ ወይም ተከራዩ ግዴታውን ከተወጣ በማህበሩ እንደ አባል
አስፈላጊውን አገልግት ያገኛል፡፡
13. በማህበሩ የአባል ተወካይ ወይም ተከራይ በሰተቀር ማንኛውም አባል ለማህበሩ
አስተዳደራዊ(ለኮሚቴ) ስራ የመረጣል ይመርጣል
14. በማህበሩ ለአሰተዳደራዊ ስራ የሚመረጥ አባል 51% ድምፅ ያገኝ ቢቻ ይሆናል፡፡
15. በማህበሩ ለአሰተዳደራዊ አገልግሎት በአራት(4)ዓመት ሁለት ጊዜ ምርጫ የሚያካሄድ
ሲሆን የተመረጠው አባል በአንድ ጊዜ ምርጫ ለተከታታይ ሁለት(2)ዓመት ቢቻ
የሚያገለግል ይሆናል፡፡
16. የማህበሩ አባል ለማህበሩ አስተዳደራዊ ስራ ዕጩ ሆኖ መመረጥ የሚችለውና የቀድሞ
ኮሚቴም ከሆነ ለተከታታይ ሁለት(2) ጊዜ ቢቻ ዕቹ ሆኖ ቀርቦ የሚመረጥ ይሆናል፡፡
17. ማህበሩ በዓመት ሁለት(2) ጊዜ ጠቅላላ ጉባዔ ሲያደርግ በዓመት አንድ(1)ጊዜ
በኦዲተርና በሊቀመነበሩ ዓመታዊ ሪፖርት በቃልና በሰነድ የሚቀርብ ይሆናል፡፡
18. ማንኛውም የማህበሩ አባል መደበኛውን መዋጮና ልዩልዩ ትዕዛዞችን የማይፈፅም ከሆነ
በማህበሩ በተቀመጠው የቅጣት ዝርዝር ሁኔታ መሰረት የሚቀጣ ይሆናል፡፡
19. በዚህ ማህበር አባል በመሆን በመህበሩ ሰነድ ለይ ፍርሞ ያፀደቀና የተቀበለ ከሁሉም
አባላት ጋር እኩል መብትና ጊዴታ አለበት፡፡

አንቀፅ ሁለት(2) በማህበሩ አባላት መብት


1. በማህበሩ አባል የሆነ የቤት ባለቤት እንደ አባል ማግኝት ያለበትን ማንኛውንም
አገልግሎት ያገኛል፡፡
2. በማህበሩ ደንብ አንቀፅ አንድ(1) ቁጥር 13 ላይ ከተጠቀሰው ሁኔታ በስተቀር
ለአሰተዳደራዊ(ኮሚቴ)ስራ የመመረጥና የመምረጥ መብት አለው፡፡
3. ሚዘናዊ ያለሆነ እና ቅሬታ የሚፈጥር የማህበሩ አሰተዳደራዊ ስረ ካለ ሁኔታውን
በፁሑፍና በቃል ማቅረብ የችላል፡፡
4.

አንቀፅ ሦስት(3) በማህበሩ የቅጣት ዝርዘር ሁኔታዎች


ተ.ቁ የቅጣት አይነት የመጀመርያ ሁለተኛ ሦስተኛ
1 ኛ. ለማህበሩ ዓላማና ደንብ ተገዢ አለመሆን
2ኛ
አንቀፅ አራት(4)በማህበሩ የኮሚቴው መብት
1.

የማህበሩ አገልግሎት
1. በመንኛውም ሁኔታ የአከባቢውን ሰላምና ፀጥታን ለማስከበር ከህግ አካላት ጋር
በትብብር ይሰራል፡፡
2. የአከባቢውን የፅዳት ሁኔታ በከፍተኛ ደረጃ ይቆጣጠራል፡፡
3. በህግ የተከለከሉ ነገሮች በአከባቢው እንዳይሸጡ እንዳይለወጡ ይከላከላል፡፡
4. የነዋሪው መግብያና መውጫ በቤዝ ማፕ በሚታየው ሁኔታ ስፋታቸውን ጠብቀው
እንዲቀጥሉ አሰፈላጊውን ጥረት ያደርጋል፡፡
5. በማህበሩ አባላት መካከል የሚፍጠሩትን አለመግባባቶችን ለመፍታት ጥረት ያደርጋል፡፡
6. በማንኛውም ሁኔታ ከአባላትም ሆነ ከሌላ አካል በአከባቢውም ሆነ በማህበሩ ላይ
የሚፈፀሙ አሉታዊ ተገባሮችን ይቃወማል፤ቅጣት ያስተላልፋ፤በፍ/ቤት ደረጃ
አቤቱታ(ክስ) ያቀርባል፡፡
7. በማህበሩ አባላት ላይ የተለያዩ ከባድ ሁኔታዎች ሲገጥሙ በመተዳደሪያ ደንቡ ላይ
በተቀመጠው ወጥ አሰራር መሰረት ማህበራዊ ድጋፍ ያደርጋል፡፡
8. የማህበሩን አባላትም ሆነ የአከባቢውን የሳላም ሁኔታን ለማስጠበቅ አሰፈላጊ የሆነውን
ሁሉ ያደርጋል፡፡
9. በመኖሪያዎቹ አከባቢው የ 24 ሰዓት የጥበቃ ሻፋን እንዲኖር ያደርጋል፡፡
10.በማህበሩ አባላት መኖር አከባቢ የተጓደሉ፤የተበለሹ አና ለአደጋ የተጋለጡ መሰረተ
ልማቶች አፋጣኝ መፍቴ እንዲያገኙ አጥብቆ ይሰራል፡፡

You might also like