Download as pdf or txt
Download as pdf or txt
You are on page 1of 27

‫اإلفتراء األحباش على السلف في‬

‫"أن هللا موجود بال مكان"‬


‫”‪“አላህ ያለቦታ አለ‬‬
‫‪አህባሹ በሰለፎች ላይ የቀጠፈው ቅጥፈት‬‬

‫‪ትርጉሙ ፡ ዩሱፍ አሕመድ‬‬


1/25

ከዚህ በኋላ፡ “አላህ ያለቦታ አለ” የሚለውን አመለካከት በርካታ ሰለፎች እንዳጸድቁት አንድ
አህባሽ አረጋግጦ ሲናገር አደመጥኩ፡፡ ይህም ከዓልይ ብን አቢጧሊብ ፣ ከዓልይ ብን አቢጧሊብ
የልጅ ልጅ ከሆነው ዘይኑል ዓቢዲን ዓልይ ብን አልሁሰይን ብን ዓልይ ብን አቢጧሊብ ፣ ከጀዕፈር
አስሷዲቅ -ጀዕፈር ብን ሙሐመድ ዓልይ ብን አልሁሰይን ብን ዓልይ ብን አቢጧሊብ ፣
ከአቡሀኒፋ ፣ ከሻፍዕይ ፣ ከአህመድ ፣ ከጦበሪ… እንደተገኘ ተናግሯል፡፡

➢ በዚህ ላይ አንድ ሰው ምላሽ ለመስጠት ቆሟል ፣ ይሁን እንጅ ምላሹ ደካማ ምላሽ ሆኖ ነው
ያገኘሁት፡፡ ምክያቱም አህባሹ ወዳወሳው ምንጭ በመመለስ አደገኛ የሆነውን ማምታቻ
ለማፍረስ ሙከራ አላደረገም፡፡ ይልቁንም እነዚህ የተወሱት -አቡሀኒፋ ፣ ሻፍዕይ ፣ አህመድ
፣ ጦበሪና ሌሎችም- ትክክለኛው እምነታቸው ከልቅናው ጋር በሚስማማ ሁኔታ የአላህን
ከዓርሽ በላይ መሆን ፣ እርሱ ከሁሉም በላይ መሆኑን የሚያጸድቁ መሆናቸውን
ከማባብራራት ጋር በሱና መሪዎች ላይ የቀጠፈው ቅጥፈቱ እንዲጋለጥ ፣ ማህይምነቱ ይፋ
እንዲሆን አህባሹ ወዳወሳው ምንጭ መመለስ የግድ ይላል፡፡

ማንቂያዎች

ማንቂያ አንድ፡- ስለነዚህ (የሙስሊም) መሪዎች አህባሹ ያወሳው “አላህ ያለቦታ አለ”
የሚለው ቃል በእውቀት ባለቤቶች መጽሐፎች ውስጥ አይታወቅም፡፡ በውስጧ ከሚገኙ
ማህይምነትና ቅጥፈቶች ማብራሪያ ጋር ወደነርሱ የተጠጉ ቃላቶች ለወደፊት ይወሳሉ፡፡

ማንቂያ ሁለት፡- ሐቅ ፈላጊ ሆይ! በአላህ ባህሪያት ዙሪያ ከቁርኣን እና ከሱና ያልጸደቀ ንግግር
ከመናገር ተጠንቀቅ፡፡
2/25
ኢማም ኢብኑ ተይሚያ የሚከተለውን ተናግሯል፡-“ሰለፎች ከአላህ ባህሪያቶች ፣ ከተግባራቶቹ
ከአላህ ይዘው በሚያጸድቁትና በሚያራቁቱት የቁርኣንን እና የሐዲስን ቃላቶች ይጠብቁ ነበር፡፡
በማጽደቅም ይሁን በማራቆት አዲስ የተፈጠረ ቃላትን አያመጡም፡፡ ይልቁንም ማንኛውም
ትክክለኛ ትርጉም በረሡል ‫ ﷺ‬ንግግር ውስጥ የተካተተ ነው፡፡ አዳዲስ የተፈጠሩ ቃላቶች ህግና
ስርዓት የላቸውም፡፡ ሁሉም ሰው በእርሷ የሚፈልገው ትርጉም ፣ ሌላው በሚፈልገው ትርጉም
ተቃራኒ ነው፡፡ “ጅስም” (አካል) ፣ “ጅሐት” (አቅጣጫ) ፣ “ሀይዝ” (ለእርሱ ብቻ
የተከለለ ቦታ) የሚሉት ቃላቶች… እንደምሳሌ ይጠቀሳሉ፡፡” መጅሙዕ አል ፈታዋ፡

በተጨማሪ የሚከተለውን ተናግሯል፡-“የሰለፎችና የሙስሊም መሪዎች በሸሪዓ እና በዓቅል


የታወቁ የሆኑ ትክክለኛ ትርጉሞችን ይጠብቃሉ፡፡ በተጨማሪ ሸሪዓዊ የሆኑ ቃላቶችን ይጠብቃሉ፡፡
ወደርሷ መንገድን ካገኙ በእርሷ ይገልጻሉ፡፡ ቁርኣንና ሱናን በሚቃረን ትክክለኛ ያልሆነ ትርጉም
የተናገረን አካል በእርሱ ላይ ይመልሱበታል፡፡ እውነትና ውሸትን አሻሚ የሆነን አዲስ የተፈጠረ
ቃል የተናገረን ሰው እንደዚሁ ወደቢድዓ ያስጠጉታል፡፡ (እንዲህ ዓይነቱን ሰው) 'ቢድዓን
በቢድዓ ፣ ባጢልን በባጢል ምላሽ የሰጠ' ይሉታል፡፡” ደርኡ ተዓሩድ አል ዓቅል ወንነቅል፡

የቢድዓ ባለቤቶች ከሚናገሯቸው ቃላቶች መካከል “ጅስም” (አካል) ይገኝበታል፡፡


አህለሱናዎችን “ሙጀሲም” (አላህን በአካል ገላጭ) በማለት ይገልጿቸዋል -ምክንያቱም
ያለማጣመም ፣ ያለማራቆት ፣ ያለማመሳሰል የአላህን ባህሪያት ያጸድቃሉና፡፡ በክርክር ጊዜ፡
“ጅስም” ያለው ቃል በማራቆትም ይሁን በማጽደቅ በቁርኣንም ይሁን በሱና አልመጣም ፣
በመሆኑም ይህንን ቃል በአላህ ላይ በጥቅል መናገሩ አዲስ ከተፈጠሩ ቢድዓዎች ነው”
እንላቸዋለን፡፡ “ጅስም” ያለው ቃል ትንታኔ ከሚያስፈልጋቸው ጥቅል ቃላቶች መካከል አንዱ
ነው፡፡

ኢብን ዑሰይሚን የሚከተለውን ተናግረዋል፡- “እናንተ ሙጀሲም ናችሁ” ይላሉ፡፡ “ሙጀሲማ


እንዴት ነው?” ፣ “የሙጀሲማ ትርጉም ምንድን ነው?” ቁርኣንን ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ
3/25
ብታነበው ፣ ከነብዩ ‫ ﷺ‬የመጣውን ሱና ከመጀመሪያው እስከመጨረሻው ብትዳስሰው ፣
በማጽቅም ይሁን በማራቆት በአላህ ቁርኣንም ይሁን በአላህ መልእክተኛ ሐዲስ “ተጅሲም”
የሚለውን ቃል አታገኘውም… አህለሱና ወልጀማዓ (መጓዝ በሚገባቸው ቦታ) በመንገዳቸው ላይ
ይጓዛሉ ፤ በሚቆምበት ቦታ በዝምታ ይቆማሉ፡፡ “ጅስም” የሚለውን 'ከቃሉ አኳያ አናጸድቅም ፣
አናወግዝም' ይላሉ፡፡ ትርጉሙን አስመልክቶ ግን 'ዝርዝር ማብራሪያ እንፈልጋለን ፣ “ጅስም”
ስትል ምን ፈልገህ ነው?' እንለዋለን፡፡ ከእርሱ ጋር በሚስማማ ባህሪ የሚገለጽ ትክክለኛ አካል
ፈልገህ ከሆነ እርሱ ህያው ፣ አዋቂ ፣ ቻይ ከመሆን አልተወገደም ፣ አይወገድም፡፡ ተስማሚ በሆኑ
ሙሉ መገለጫዎች ተገላጭ ነው፡፡ አንዱ ወደሌላው ድጋፍ የሚፈልግ የሰውነት ክፍል እንዳላቸው
አካላት ዓይነት ፈልገህ ከሆነ ይህ ከአላህ ጋር የሚስማማ አይደለም፡፡ በዚህም ትርጉሙን በትክክል
ሐቁን ሰጠነው፡፡ “ጅስም” ያለው ቃል፡ በማጽደቅም ይሁን በማራቆት ምንጊዜም ለእኛ
አይፈቀድልንም፡፡ ነገር ግን ቆም እንላለን፡፡ ብናጸድቅ “(ለማጽደቅህ) ምንድን ነው መረጃህ”
ይለናል፡፡ ብናራቁትም “(ለማራቆትህ) ምንድን ነው መረጃህ” ይለናል፡፡ በዚህ መሰረት ከቃሉ
አኳያ ዝምታ የግድ ነው፡፡ ከትርጉም አኳያ ግን ከዚህ በፊት እንዳብራራነው ዝርዝር ማብራሪያን
እንፈልጋለን፡፡” (አስማኡሏሂ ወሲፋቲሂ ወመውቂፉ አህለሱነቲ ሚንሀ፡ ገጽ/32) ተመልከት

የቢድዓ ባለቤቶች ይህን ጥቅል ቃል የሚናገሩት ፣ አላህን ከጉድለት እናጸዳለን በሚል በጃሂሉ
ማህበረሰብ ላይ ብዥታን ለመፍጠር ነው፡፡ አህለሱናዎች “ሙጀሲም” ፣ “ሙሸቢህ”
(አመሳሳዮች) ናቸው እያሉ ሰዎች ከእነርሱ እንዲርቁ ለማድረግ በአህለሱናዎች ላይ ይቀጥፋሉ፡፡

ኢማም አህመድ “አርረድ ዓለል ጀህምየቲ ወዝዘናዲቃህ” በተባለው መጽሐፋቸው ገጽ/


ላይ የሚከተለውን ተናግረዋል፡-

“እነርሱ መጽሐፉን ተቃራኒ ናቸው ፣ በመጽሐፉ ውስጥ እርስ በርስ ተወዛጋቢ ናቸው ፣
ከመጽሐፉ ለመለየት የተስማሙ ናቸው ፤ በአላህ ላይ ፣ ስለአላህ ፣ በአላህ ቁርኣን ያለእውቀት
ይናገራሉ፡፡ ከንግግር በሙተሻቢህ ይናገራሉ፡፡
4/25
በእነርሱ ላይ በማምታታት ጃሒሎችን ያታልላሉ፡፡ ከአጥማሚዎች ፈተና በአላህ እንጠበቃለን፡፡”

ኢብን ተይሚያህ ከዚህ በፊት የተወሳውን የአህመድን ንግግር ከወሰደ በኋላ የሚከተለውን
ተናገረ፡-

“የቢድዓና የስሜት ባለቤቶች ሙተሻቢህ (ተመሳሳይ) በሆኑ ንግግሮች እንደሚናገሩ ተናገረ፡፡


በእነርሱ ላይ ማምታቻዎችን በመናገር ጃሒሎችን ያታልላሉ፡፡ “ለይሰ ሙተሀይዝ (በተከለለ ቦታ
አይደለም) ፣ ወላ ፊ ጅሐቲን (በሆነ አቅጣጫም አይደለም)” ፤ “(እርሱ) እንደዚህ
አይደለም ፣ እንደዚህ አይደለም” የሚሉትን ንግግራቸው እንደምሳሌ ይጠቀሳል፡፡ እነዚህ በሐቅ
ሊተረጎሙ ወይም በባጢል ሊተረጎሙ የሚችሉ ጥቅል ቃሎች ናቸው ፤ ሙተሻቢህ ናቸው፡፡
አላማቸው አላህ በአንዳንድ ፍጡራኖች ባህሪያት አይነት የታጠረ ከመሆን ለማጥራት በሚል
እነዚህን ቃላቶች ጥቅል በሆነ ሁኔታ በመናገር የማያውቀውን ሙስሊም ህብረተሰብ ብዥታ
ውስጥ ይከታሉ፡፡ የአላህን ባህሪያት በሚያጸድቁ አካላት ላይ “እነርሱ ይህን ይላሉ” ፣ አንዳንድ
ዳኞቻቸው ለመሪዎቻቸው “አላህ የሚገኘው በዚህ ዛውያ (ማዕዘን) ነው” ይላሉ ፣
ከጣዖቶቻቸው አንዳንዶች ደግሞ “አላህ ሰማያትን የሞላ ነው” ይላሉ (በማለት በአህለሱናዎች
ላይ ይቀጥፋሉ)፡፡ በዚህ ምክንያት “ሐሸዊያ” በመባል ይጠራሉ፡፡ የአላህን ባህሪያት በሚያጸድቁ
አካላት ላይ እነዚህን የመሳሰሉ ቅጥፈቶችን ይዋሹባቸዋል፡፡ ከዚያም እውነታውንም ይሁን ሐሰቱን
ለማራቆት የሚያመች ሁኔታ ጥቅል እና የሚያምታታ ቃል ያመጣሉ፡፡ ቃሉን በጥቅል ይናገሩታል፡፡
በዚህም ጃሂሉን ህብረተሰብ ይሸውዱበታል፡፡ ማብራሪያና ትንታኔ ከተደረገበት ደግሞ ሚስጢሩ
ግልጽ ይሆናል፡፡ ሌሊቱ ከቀኑ ግልጽ ይሆናል፡፡ የኢማን እና የእርግጠኝነት ባለቤቶች እያወቁ ሐቅን
ከባጢል ከሚደባልቁ ፣ እውነታውን ከደበቁ የንፍቅና እና የተድሊስ (የማጭበርበር) ባለቤቶች
ይለያሉ፡፡” ቲስዒንያት፡

ሶስተኛው ማንቂያ፡- አሻዒራ እውቀት ፣ ችሎታ ፣ ኢራዳ እና የመሳሰሉ ባሕሪያትን ያጸድቃሉ፡፡


“እናንተ በመዝሐባችሁ መሰረት ሙጀሲም ናችሁ ፣ ምክንያቱም እነዚህ ባህሪያቶች ሁሉ
5/25
ፍጡራን የሚገለጹባቸው ባህሪያት ናቸው፡፡ ካለበለዚያ እናንተ እርስ በርስ የምትቃረኑ ናችሁ”
እንላቸዋለን፡፡ “የተወሰኑ ባህሪያቶችን ካጸደቃችሁ ሁሉንም ባህሪያቶች ልታጸድቁ ግድ
ይላችኋል፡፡ ካለበለዚያ ኢብን አል’ቀይም በኑንያ ኪታቡ እንደተናገረው ሁሉንም አራቁቱ
(እንላቸዋለን)፡፡

‫ واإلثبات في عقل وفي ميزان‬.... ‫فالباب باب واحد في النفي‬

‫ لزم الجميع أو ائت بالفرقان‬...... ‫فمتى أقر ببعض ذلك مثبت‬

‫ فمجسم متناقض ديصاني‬...... ‫ومتى نفى شيئا وأثبت مثله‬


በማራቆትም ይሁን በማጽደቅ

በዓቅልም ይሁን በሚዛን አንድ ብቻ ነው ክፍሉ

አጽዳቂው ፣ (ከፊሉን ትቶ) ከፊሉን ከተቀበለ

ሁሉንም (ማጽደቅ) ይይዘዋል ወይም የለየህበትን አምጣ ይባላል

አንዱን አራቁቶ ፣ የእርሱን ተመሳሳይ ካጸደቀ


እርሱ ነው የተምታታበት ሙጀሲም ፣ እንዲሁም ዲሷንይ

ልክ እንደዚሁ ከቁርኣን ፣ ከሱና እና ሰለፎች ከነበሩበት ጎዳና ያፈነገጠ ፣ ስሜቱን በአቅሉ ላይ


ፈራጅ ያደረገ እና ወደግሪኮች የፍልስፍና እውቀት ፊቱን ያዞረ የተምታታበት ይሆናል፡፡

ኢማም ሻፍዒያ የሚከተለውን ተናግረዋል፡- “በፍልስፍና ሰዎች ላይ የምሰጠው ፍርድ በተምር


ቀንዘል እና በጫማ እንዲደበደቡ ፣ በየጎሳውና ብሔሩ እንዲዞሩ ፣ ይህ ቁርኣንን እና ሱናን ትቶ

“ዲሷንያ” በመባል የሚጠሩት ቡድኖች “ሰነውያ” በመባልም ይጠራሉ፡፡ ዓለም በሁለት አምላክ የሚመራ ነው

ብለው ያምናሉ፡፡ የብርሃን አምላክ እና የጨለማ አምላክ፡፡ ማንኛውም መልካም ነገር ከብርሃን አምላክ የሚመጣ

ነው, ማንኛውም መጥፎ ነገር ደግሞ ከጨለማ አምላክ የሚመጣ ነው ብለው ያምናሉ፡፡
6/25
ወደፍልስፍና የዞረ ሰው ዋጋ ነው እንዲባል ነው” ኢብን ዓበዲልበር ፊ አልኢንቲቃእ፡ ገፅ ኸጢብ ፊ ሸረፊ
አስሃቢል ሐዲስ፡ ገፅ አል ፈታዋ አል ኩብራ ሊብን ተይሚያህ፡

አራተኛው ማንቂያ፡- ሶሃቦች ፣ ታብዒዮች እና እነርሱን የተከተሉ የሱና መሪዎች ከልቅናው ጋር


በሚስማማ ሁኔታ አላህ ከሁሉ በላይ ፣ ከዓርሽም በላይ መሆኑን ተስማምተዋል፡፡

በተለያየ መልኩ አላህ ከሁሉ በላይ መሆኑን ቁርኣን ጠቁሟል፡-


ምሳሌ፡-
﴾‫﴿ َوُه َو الْ َعلِ ُّي الْ َع ِظ ُيم‬
“እርሱም የሁሉ በላይ ታላቅ ነው” አል በቀራህ፡

َ ِ‫اس َم َرب‬
﴾‫ك ْاْل َْعلَى‬ ْ ‫﴿ َسبِ ِح‬
“ከሁሉ በላይ የሆነውን ጌታህን ስም አሞግስ” አል አዕላ፡

﴾ُ‫﴿ َوُه َو الْ َعلِ ُّي الْ َكبِي‬


“እርሱም ከፍተኛው ታላቁ ጌታ ነው፡፡” ሰበእ ፡

እና የመሳሰሉት ናቸው፡፡
“ፈውቂያ” (የአላህ የበላይነት) በግልጽ የተወሳበት ቁርኣናዊ አንቀጾች የሚከተሉት ናቸው፡-
﴾ِ‫﴿فَ ْو َق ِعبَ ِاده‬
“እርሱም ከባሮቹ በላይ ሲሆን” አል አንዓም፡

﴾‫﴿ ََيَافُو َن َرهَّبُم ِمن فَ ْوقِ ِه ْم‬


“ጌታቸውን ከበላያቸው ሲሆን ይፈሩታል፡፡” አን ነሕል፡

ነገሮች ወደርሱ እንደሚዘልቁና እንደሚወጡ የተገለጸበት ቁርኣናዊ አንቀጾች የሚከተሉት


ናቸው፡-
﴾‫ف َسََ ٍة‬ ِ ِ ٍ ِ ‫الر‬ ِ
َ ‫وح إِلَْيه ِِف يَ ْوم َكا َن م ْق َد ُارهُ َخَْس‬
َ ْ‫ني أَل‬ ُ ُّ ‫﴿تَ ْع ُر ُج الْ َم ََلئ َكةُ َو‬
“መላእክቱና መንፈሱም ልኩ አምሳ ሺ ዓመት በሆነ ቀን ውስጥ ወደርሱ ያርጋሉ
(ይወጣሉ)” አል መዓሪጅ ፡
7/25
ِ ِ ِ
ْ َ‫﴿إِلَْيه ي‬
ُ ‫ص َع ُد الْ َكل ُم الطهي‬
﴾‫ب‬
“መልካም ንግግር ወደርሱ ይወጣል” ፋጢር፡

ነገሮች ከእርሱ እንደሚወርዱ በግልጽ የተነገረበት ቁርዓናዊ አንቀጾች የሚከተሉት ናቸው፡-


ِ ‫﴿يُ َدبُِر ْاْل َْمَر ِم َن ال هس َماء إِ ََل ْاْل َْر‬
﴾‫ض‬

“ነገሩን ሁሉ ከሰማይ ወደ ምድር ያዘጋጃል፡፡” አስ ሰጅዳህ፡

﴾‫اَّللِ الْ َع ِزي ِز الْ َعلِي ِم‬


‫اب ِم َن ه‬
ِ َ‫﴿تََ ِزيل الْ ِكت‬
ُ
“የመጽሐፉ መወረድ አሸናፊ ዓዋቂ ከሆነው አላህ ነው፡፡” ጋፊር፡

አላህ ከሰማይ በላይ መሆኑ በግልጽ የተነገረበት ቁርኣናዊ አንቀጽ የሚከተለው ነው፡-
﴾‫ور‬ ِ ِ ‫﴿أَأ َِمَتم همن ِِف ال هسماء أَن ََيْ ِسف بِ ُكم اْلَر‬
ُ ُ‫ض فَإذَا ه َي ََت‬
َ ْ ُ َ َ ُ
“በሰማይ ውስጥ ያለን በእናንተ ላይ ቢደረምስባችሁ ወዲያውም እርሷ የምታረገርግ
ብትሆን ትተማመናላችሁ” አል ሙልክ፡

ዘህብይ የሚከተለውን ተናገረ፡ “አላህ ለእርሷ በተለየ ፣ ከእርሷ በውሰጥ የገባ ሳይሆን ፣
እውቀቱ በሁሉም ቦታ ፣ ከዓርሽ በላይ ፣ ከፍጡሩ ሁሉ በላይ መሆኑን የሚገልጽ መረጃ ቁርኣን ፣
ሱና ፣ የሶሃባ ፣ የታብዕይ ፣ በቅን ጎዳና ላይ ያሉ መሪዎች ኢጅማዕ (ስምምነት) ነው፡፡” ኪታብ
አል ዓርሽ፡

➢ አስደናቂ ታሪክ፡ ኢብን ተይሚያ “ደርእ ተዓሩድ አልዓቅል ወንነቅል” በተባለው ኪታብ
(6/343) የሚከተለውን ተናግሯል ፡ -

“ከአራቋቾች መካከል አንዱ ብርቱ ነገር ካሳሰበው አላህን ሊማጸን ልቡ ወደላይ ያማትራል ፣
ከእኔ ዘንድ ይህን የሚያራቁት ከሸይኾቻቸው መካከል አንድ ሰው ነበር ፣ እርሱ ከእኔ የሆነ ጉዳይ
ፈለገ ፣ ይህን ጉዳይ የማልቃወም መስየ በዚህ መዝሐብ ዙሪያ አናግረው ነበር፡፡ ልቡ
እስከሚጨናነቅ ድረስ የሚፈልገውን ጉዳይ አዘገየሁበት ፣ እጁን እና ራሱን ወደሰማይ በማድረግ
“ያ አሏህ” አለ፡፡ አንተ ይገባሃል እንዴ? እጅህን እና ራስክን ወደላይ ያንጋጠጥክ ፣ አንተ ይህ
8/25
ጉዳይ ይገባሃል እንዴ? ከአንተ በላይ አንድ አካል አለን? አልኩት፡፡ እርሱም “አስተግፊሩሏህ”
አለ፡፡ ለእርሱ ግልጽ የሆነለት ጊዜ ፣ ተፈጥሮውንም የተቃረነ መሆኑ ግልጽ ሲሆንለት ወደዚያ
(ወደሚያስተባብለው ነገር) ተመለሰ፡፡ ይህ አነጋገሩ የተበላሸ መሆኑን ለእርሱ ግልጽ
አደረግኩለት፡፡ ተፈጥሯቸውን ወደሚያረጋግጡ ሙስሊሞች ንግግር ተጸጽቶ ተመለሰ፡፡”

➢ በ ሒጅራው አቆጣጠር የሞተው አሽዓርይ ኢማሙ አልሀረመይን በመባል የሚታወቀው


አቡል መዓሊ አልጁወይንይ ታሪክ ልክ እንደዚሁ ነው፡፡ “ዓርሽ ሳይኖር አላህ ነበር” በማለት
ተናገረ፡፡ “አንተ ኡስታዝ ሆይ! ዓርሽን ከማውሳት እባክህ ተወንና በልቦቻችን ውስጥ የግድ
የምታገኛትን ነገር ንገረን፡፡ ማለትም የሰው ልጅ የግድ ዱዓ በሚያደርግና ወደአላህ በሚተናነስ
ጊዜ በልቡ ውስጥ የእርሱን የበላይነት ይፈልገዋል፡፡” በማለት አቡጀዕፈር አልሐምዳኒ
ተናገረ፡፡ ኣሻዒራው ጁወይንይ በእጁ ራሱን ደበደበ፡፡ “ሀምዳኒ አዋለለኝ ፣ ሀምዳኒ
አዋለለኝ” በማለት ተናገረ፡፡ ኢጅቲማዑ ጁዩሽ አል ኢስላሚያህ፡

“ዓርሽን ከማውሳት ተወን” ያለው ንግግር ፣ የአላህ ከዓርሽ በላይ መሆኑ በቁርኣን ፣ በሱና እና
በዑለሞች ስምምነት (በኢጅማእ) ተረጋግጧል ለማለት ነው፡፡ “ዑሉው” (ልቅ በሆነ ሁኔታ
ከአንድ ነገር በላይ መሆኑ) ግን በተፈጥሮ ግልጽ ነው፡፡ እምቢተኛ ካልሆነ በቀር እርሱን
የሚቃወም የለም፡፡ ኣሻዒራ ፣ አህባሽ ፣ ጀህምያ እና ሌሎች ቡድኖች ግን የሰው ልጅን ተፈጥሮ
ሊቀይሩ ይሞክራሉ፡፡ ከጥመት እና ከሐቅ ከመዘንበል በአላህ እንጠበቃለን፡፡

➢ አላህ ከዓርሽ በላይ ለመሆኑ (ኢስቲዋእ) ከቁርኣናዊ መረጃዎች መካከል የሚከተለው


ይገኝበታል፡
ِِ ِ ِ
ْ ‫ض ِِف ستهة أَ هَّيٍم ثُه‬
﴾ِِ ‫استَ َو َعلَى الْ َع ْر‬ َ ‫﴿إِ هن َربه ُك ُم اَّللُ الهذي َخلَ َق ال هس َم َاوات َواْل َْر‬
“ጌታችሁ ያ ሰማያትንና ምድርን በስድስት ቀኖች ውስጥ የፈጠረ አላህ ነው፡፡ ከዚያም
ከዓርሹ በላይ ሆነ” አልአ ዕራፍ፡

እና ሌሎችም ቦታቸው የሚታወቁ ማስረጃዎች ይገኛሉ፡፡


9/25
የአላህን የበላይነት ከሚገልጹ የተረጋገጡ ሐዲሶች መካከል ባሪያ ለሆነችው ሴት የተናገሩት
ይገኝበታል፡፡

“አላህ የት ነው” በማለት ባሪያዋን ጠየቋት፡፡ እርሷም “ከሰማይ በላይ” በማለት ምላሽ ሰጠች፡፡

“እኔ ማን ነኝ” አሏት ፡፡ እርሷም “አንተ የአላህ መልክተኛ ነህ” በማለት ምላሽ ሰጠች፡፡
ረሡልም ‫“ﷺ‬እርሷ ሙእሚን ነችና ነጻ አድርጋት” በማለት ተናገሩ፡፡ ሙስሊም፡

የአላህ መልእክተኛ ‫ ﷺ‬የሚከተለውን ተናግረዋል፡-


"‫"أال تأمنوني وأنا أمين من في السماء يأتيني خبر السماء صباحا ومساء‬
“አታምኑኝምን? እኔ ከሰማይ በላይ ካለው ታማኝ ነኝ ፣ በማልዳም በምሽትም የሰማይ ዜና
ይመጣልኛል” ቡኻሪ፡ ሙስሊም፡

አላህ ከዓርሽ በላይ ለመሆኑ አቡሁረይራ ከረሡል ‫ ﷺ‬ሰምቶ ያስተላለፈው የተረጋገጠ ትክክለኛ
ሐዲስ ሌላው ማስረጃ ነው፡፡
"‫"لما قضى هللا الخلق كتب في كتابه فهو عنده فوق العرش إن رحمتي غلبت غضبي‬
“አላህ ፍጥረትን እንደፈጠረ ፣ ከዓርሽ በላይ ከእርሱ ዘንድ ከሚገኘው መጽሐፉ ውስጥ 'እዝነቴ
ቁጣየን አሸነፈች' በማለት ጻፈ፡፡” ቡኻሪ፡ ሙስሊም፡

ኢማም ብን አል’ቀይም የሚከተለውን ተናግሯል፡- “ተፈጥሮ ፣ ዓቅሎች ፣ የሸሪዓ ህጎች


ከመሰከሩት ጉዳይ በጣም ግልጽ የሆነው አላህ ከዓለም ሁሉ በላይ መሆኑ ነው፡፡ አላህ በዚህ ላይ
የማይናገሩ ፍጥረቶችን እንኳ ሳይቀር ፍጥረታትን በአጠቃላይ ፈጥሯል፡፡ ይህን የሚቃወም አካል
በአንድ ጎን ሲሆን ፤ ሰላማዊ ተፈጥሮዎች ፣ ቀጥ ያሉ ዓቅሎች እና አጠቃላይ ከሰማይ የወረዱ
መጽሐፎች እና በእርሷም ላይ የተላኩት በሌላ ጎን ናቸው፡፡” አሶዋዒቅ አል ልሙርሰላ ፊር ረዲ ዓለል ጀህምየቲ
ወልሙዓጢላ፡

የሚከተለውን ተናግሯል፡ “ፈጣሪ ከፍጥረቱ የተለየ ለመሆኑና አላህ ከፍጡራኑ ሁሉ በላይ ለመሆኑ
ማስረጃው ዓቅላዊ ፣ ተፈጥሯዊ ሲሆን ስለትርጉሙ አስፈላጊ እውቀት ግዴታ ነው፡፡ ከቁርኣን
10/25
ከሐዲስ የመጡ ማስረጃዎች ደግሞ ወደአንድ ሽ ይቃረባሉ፡፡” አሶዋዒቅ አል ሙርሰላ ፊር ረዲ ዓለል ጀህምየቲ
ወልሙዓጢላ ፡

የአህባሹን ወደሱና መሪዎች የማዛመድ ቅጥፈት ግልጽ ማድረግ

አህባሹ “አላህ ያለ ቦታ አለ” የሚለውን ንግግር ዓልይ ተናግሮታል በማለት ወደርሱ አስጠግቶታል፡፡

እኔም እላለሁ ፡ በ ሒ. ላይ የሞተው ዓብዲልቃሂር ብን ጧሂር አልበግዳድይ “አልፈርቅ


በይነል ፊረቅ” በሚባለው ኪታብ ገጽ የሚከተለውን ተናግሯል፡-

“የምእመናን መሪ የሆነው አልይ የሚከተለውን ተናግሯል፡“አላህ ለአካሉ ቦታ ሳይሆን ፣


ቁድራውን ይፋ ለማድረግ አርሽን ፈጠረ ፤ አሁንም አለ ፡ ቦታ ሳይኖር በእርግጥ ነበረ ፣
ከነበረበት ቦታ አሁንም አለ”፡፡
መልስ፡-

የመጀመሪያው፡ አብዱልቃሂር ታላላቅ ከሚባሉት ዓሻኢራዎች አንዱ ሲሆን የበላይነትን


የሚያራቁት ፣ ኢስቲዋእ እና የአላህን ባህሪያቶች አጣሞ የሚተረጉም ሰው ነው፡፡

ሁለተኛው፡ ልክ እንደ ሙብተዲዖችና የሚያምታቱ ሰዎች ወደ አልይ ብን አቢጧሊብ


የሚያገናኘውን ሰነድ አላወሳም፡፡

ሶስተኛው፡ በአብዱልቃሂር እና በዓልይ ብን አቢጧሊብ መካከል አራት መቶ አመት የሚቀርብ


ልዩነት አለ፡፡ ዓልይ ብን አቢጧሊብ የሞተው በሂጅራው አቆጣጠር አርባ አመት ላይ ነው፡፡

እነዚያ የሌሊት እንጨት ለቃሚዎች ናቸው፡፡ ከእነርሱ ዘንድ የሐዲስ እውቀት ግንዛቤ የላቸውም፡፡
ያለምንም ሰነድ ከአኢማዎች የነቀሉትን ወሬ ፊት ሊዞርለት አይገባም በተለይም በአላህ ባህሪያት
ዙሪያ፡፡

አራተኛው፡ ኢማም ኢብን አል’ቀይም የሚከተለውን ተናገረ፡- ዓድይ ብን ዑመይራ


አልኪንድይ ባስተላለፈው ሐዲስ ዓልይ የአላህ መልእክተኛ ‫ ﷺ‬ከጌታቸው ይዘው ያወሩትን ሐዲስ
11/25
እንደሚከተለው ተናግረዋል፡-
"...‫"وعزتي وجاللي والرتفاعي فوق عرشي‬
“በአሸናፊነቴ ፣ በልቅናዬ ፣ ከዓርሽ በላይ ከፍ በማለቴ…” ኢብን አቢ ሸይባ ዓርሽ በሚባለው ኪታቡ ፣ አቡ
አህመድ አልዓሳል አልመእሪፋ በሚባለው ኪታቡ ዘግቦታል፡፡ ኢጅቲማዑ አል ጁዩሽ አልኢስላምያ በተባለው የኢብን አልቀይም ኪታብ
ጥራዝ ገጽ ላይ ተመልከት፡፡ አልኡሉው ሊል ዓልይ አልገፋር በተባለው የዘህብይ ኪታብ፡ ገጽ ተመልከት፡፡

እኔም የሚከተለውን እላለሁ፡ በሰነዱ ዙሪያ ሊታይ የሚገባው ነገር አለ፡፡ ነገር ግን በአህለሱና
ኪታቦች ታዋቂነት አለው፡፡ አህለሱናዎች ከሰዎች በጣም እውነተኛ ፣ ከፍጠራኖች ሁሉ በጣም
ታማኞች ናቸው፡፡ ያለምንም ልጓም እና ማሰሪያ ወሬን ነቅለው በሚያስተላልፉ የቢድዓ ባለቤቶች
ተቃራኒ የሚነቅሉትን ወሬ ከነሰነዷ ምንጩን ጨምረው ያወሳሉ- አላህ ይዘንላቸው፡፡

ለዚህ ነው ኢማም ዓብደሏህ ኢብን ሙባረክ የሚከተለውን የተናገረው ፡ -

‫أخرجه مسلم في مقدمة صحيحة‬ .‫"اإلسناد من الدين ولوال اإلسناد لقال من شاء ما شاء‬

“ሰነዶች ከዲን ናቸው፡፡ ሰነዶች ባይኖሩ ማንም ሰው የፈለገውን ይናገር ነበር፡፡” ሙስሊም በሶሂህ
ኪታባቸው መግቢያ ላይ ዘግበውታል

ታብዕዩ ኢማም ሙሐመድ ብን ሲሪን የሚከተለውን ተናግሯል፡-“ስለሰነድ አይጠይቁም ነበር ፣


ፊትና የተከሰተ ጊዜ ሰዋችሁን ጥቀሱልን ተባለ ፣ ወደአህለሱና ይመለከታሉ ሐዲሳቸው ይያዛል ፤
ወደቢድዓ ባለቤቶች ይመለከታሉ ሐዲሳቸው አይያዝም፡፡” ሙስሊም በሶሂህ ኪታባቸው መግቢያ ላይ
ዘግበውታል

በማንኛውም ጉዳይህ በተለይም የዝንባሌ ባለቤቶች በሚነቅሉት ወሬ የኢብን ሲሪንን ንግግር


ዘወትር የአይንህ ማረፊያ አድርገው፡፡

➢ አህባሹ “ኢትሀፍ ሳደቱል ሙትቂን” በሚባለው ኪታብ ውስጥ ዘይኑል ዓቢዲን ዓልይ ብን
አልሁሰይን ብን ዓልይ ብን አቢጧሊብ “አላህ ያለ ቦታ አለ” በማለት ተናግሯል የሚል
ንግግር ወደርሱ አስጠግቷል፡፡
12/25
እኔም እላለሁ፡- “ኢትሀፍ ሳደቱል ሙትቂን” በሚባለው ኪታብ የኪታቡ አዘጋጅ
ከዘይኑል ዓቢዲን ይዞ በሰነድ ረጅም ንግግር ተናገረ፡፡ በውስጡ የሚከተለው ንግግር ይገኝበታል ፡ -

"‫"أنت هللا الذي ال تحويك مكان‬


“አንተ አላህ ቦታ የማይዝህ (የማያካብብህ) ነህ”

እኔም የሚከተለውን እላለሁ፡ በውስጡ በርካታ ነገሮች አሉ

አንደኛ፡- በሰነዱ ውስጥ በተከታታይ የማይታወቁ አሉበት፡፡ ጨለማነቱ ከፊሉ በከፊሉ ላይ


የተደራረበ ነው፡፡ ከመሰረቱ ለመረጃነት አይቆምም፡፡

ሁለተኛው፡- “ኢትሀፍ አስሳደቱል ሙትቂን” የተባለው ኪታብ አዘጋጅ ሙርተዷ አዙበይዲ


ሙሐመድ ብን ሙሐመድ በመባል የሚታወቅ ሲሆን የሞተው በ ዓመተ ሒጅራ ነው፡፡
ይህ ሰው እራሱ ግልጽ እንዳደረገው ዓሽአርይ ፣ ሱፍይ ነው፡፡ ከሱና ኡለሞች ነቅሎ ያወራው
ማስረጃ ሊሆን አይችልም፡፡

ይህ የዙበይድይ መጽሐፍ “ኢህያኡ ኡሉሙ ዲን” የተባለው የገዛሊ ኪታብ ማብራሪያ ነው፡፡
“ኢህያኡ ኡሉሙ ዲን” የተባለው ኪታብ ደግሞ በሱፍያ ፣ በቢድዓ ፣ የአላህን ባህሪያት
በማራቆት የተሞላ ኪታብ ነው፡፡

በዚህ በተወሳው ኪታብ ውስጥ “ኢትሀፍ አሳደቱል ሙትቂን” ዙበይዲይ ከነቀለው


በጣም የሚያስገርመው የሚከተለው ንግግር ነው፡-
"‫"أن الكعبة تطوف بالصالحين‬
“ካዕባ ሷሊሆችን ጦዋፍ ያደርጋል” የሚለው ነው፡፡

ይህ የሱፍያ ኹራፋት ነው፡፡ በተወሳው ኪታብ ውስጥ ዙበይድይ በርካታ ቦታ ላይ አህለሱናዎችን


“ሙጀሲማ” በማለት ይገልጻቸዋል፡፡ ለምሳሌ “ኢትሀፍ አስሳዳት አልሙትቂን”
ተመልከት፡፡
13/25
ስለዚህ ይህ ጃሂል አህባሽ ከዚህ ሰው ወሬ መንቀሉ የሚያስገርም አይደለም -ምክንያቱም
“አጡዩሩ ተቀዑ አላ አሽካሊሃ” (ወፎች ከተመሳሳያቸው ያርፋሉ) ፣ “አንነል አርዋሃ ጁኑዱን
ሙጀነዳ ነው” (ነፍሶች የተሰባሰቡ ጀማዓዎች ናቸው) ተብሏልና፡፡

ሶስተኛው፡- ዘይኑል አቢዲን በመባል የሚጠራው ዓልይ ብን አልሁሰይን ብን ዓልይ ብን


ዓቢጧሊብ ከሱና መሪዎች ነው ፡፡ ቡኻሪና ሙስሊም በሶሂህ ኪታቦቻቸው ዘግበውለታል፡፡
በኢስላም ሰነዶች ውስጥ ሐዲሶቹም የታወቁ ናቸው፡፡ የአላህን የበላይነት ፣ እርሱ ከዓርሽ በላይ
መሆኑን የጠቆመበትን ሐዲስ ሙስሊም ዘግቦለታል፡፡

አልይ ብን ሁሰይን ዘይኑል ዓቢዲን የሚከተለውን ተናግሯል፡- ዓብደላህ ብን ዓባስ ከአንሷር


የነብዩ ‫ ﷺ‬ሶሃቦች መካከል አንድ ሰው ነገረኝ በማለት ተናገረ፡፡ እነርሱ ከነብዩ ‫ ﷺ‬ጋር በአንድ
ሌሊት ውስጥ ተቀምጠው ባሉበት አንድ ኮከብ ተወረወረ ፣ አበራ፡፡ ከዚያም የአላህ መልእክተኛ
‫ ﷺ‬የሚከተለውን ነገሯቸው ፡ -

“እንደዚህ አይነት ሲወረወር በጃሂልያ ምንድን ነበር የምትሉት?” በማለት ጠየቋቸው፡፡ “አላህና

መልእክተኛው ያውቃሉ በዚህ ሌሊት ታላቅ ሰው ተወለደ ፣ ታላቅ ሰው ሞተ እንል ነበር፡፡” አሉ፡፡
“እርሷ አንድ ሰው ስለሞተ ወይም ህያው ስለሆነ አትወረወርም ፤ ነገር ግን ስሙ የተባረከና ከፍ
ያለው ጌታችን አንድን ነገር የወሰነ ጊዜ የዓርሽ ተሸካሚዎች እርሱን ከጉድለት ያጠሩታል፡፡ ከዚያም
የሰማይ ባለቤቶች ተከትለው ያጠሩታል ፣ ከእነርሱ ለጥቀው ያሉትም ተስቢሁ ከቅርቢቱ ሰማይ
እስኪደርስ ያጠሩታል፡፡ ከዚያም ከዓርሽ ተሸካሚ ለጥቆ ያሉት ፣ ለዓርሽ ተሸካሚዎች “ጌታችሁ
ምን አለ” በማለት ይጠይቋቸዋል፡፡ ምን እንዳለ ይነግሯቸዋል፡፡ ወሬው ከቅርቢቱ ሰማይ እስኪደርስ
ድረስ ከፊሉ የሰማይ ባለቤት ለከፊሉ ወሬ ይጠይቃል፡፡ ወሬን ጅን ይነጥቃል፣ ይዘውት የመጡትን
ሐቅ በሆነው መልኩ ወደወዳጆቻቸው ይጥላሉ፡፡ ነገር ግን እነርሱ ይቀጥፋሉ ፣ ይጨምራሉ፡፡”
ሙስሊም፡

ዘይኑል ዓቢዲን ያወራው ሐዲስ የአላህን የበላይነት ከዓርሽ በላይ ከፍ ማለቱን ይጠቁማል፡፡
አላህ አንድ ነገር ለመወሰን ሲሻ ወደመላኢካዎች ወህይ ያወርዳል ፣ መጀመሪያ የሚሰሙት
14/25
የዓርሽ ተሸካሚ መላኢካዎች ናቸው፡፡ ከዚያም ተስቢሀቸው ዱንያ ሰማይ ወደሚገኙ መላኢካዎች
እስከሚደርስ የመላኢካዎች ተስቢህ ይከታተላል፡፡

ይህ አላህ የበላይ ለመሆኑ ፣ ከዓርሽ በላይ ከፍ ለማለቱ ግልጽ የሆነ ማስረጃ ነው፡፡ ይህን ሐዲስ
ለእኛ ሰምቶ ያስተላለፈልን ደግሞ የአልይ ብን አቢጧሊብ የልጅ ልጅ የሆነው ዘይኑል አቢዲን
ነው፡፡ ይህ ዘገባ በጣም ትክክለኛ በሚባለው ሶሂህ ሙስሊም ኪታብ ከአህለሱናዎች ዘንድ
ይታወቃል፡፡

➢ አህባሹ በ“ሪሳለቱ ቁሸይሪያ” እንደተገለጸው “አላህ ያለ ቦታ አለ” የሚለውን ንግግር


ወደጀዕፈር አስሷዲቅም አስጠግቶታል፡፡

እኔም የሚከተለውን እላለሁ፡ ጀዕፈር አስሷዲቅ ማለት አቡዓብዲላህ ጀዕፈር ብን ሙሀመድ


ብን ዓልይ ብን አልሁሰይን ብን ዓልይ ብን አቢጧሊብ ነው፡፡ እርሱም ራፊዷዎች “ጀዕፈር ይህን
ተናገረ..” እያሉ በመጽሐፋቸው የሚቀጥፉበት አንዱ የሙስሊሞች መሪ ነው፡፡ እርሱ ግን
ከእነርሱ የጸዳ ነው፡፡

ኢብን ተይሚያ የሚከተለውን ተናግሯል፡- “ጀዕፈር ብን ሙሀመድ ከዲን መሪዎቸ መሆኑ


የአህለሱናዎች ስምምነት ነው፡፡” መንሐጅ አስ ሱና አን ነበውይ፡

ሼይኹል ኢስላም ብን ተይሚያ የሚከተለውን ተናግሯል፡- “በጀዕፈር አስሷዲቅ ላይ እንደተዋሸው


አንድም የተዋሸ የለም፡፡” መንሐጅ አስሱና አን ነበውይ፡

ወደጀዕፈር የተዛመደው ንግግር አገላለጽ፡- ጀእፈር አስሷዲቅ የሚከተለውን ተናገረ፡

“’አላህ በሆነ ነገር ውስጥ ነው ወይም የሆነ ነገር ነው ወይም በሆነ ነገር ላይ ነው፡፡’ ያለ
በእርግጥ አሻረከ፡፡ በሆነ ነገር ላይ ነው ከተባለ የሚሸከሙት ነገር ሆነ ፣ በሆነ ነገር ውስጥ ከሆነ
ተከበበ ማለት ነው ፣ አንድ ነገር ከሆነ አዲስ ነገር ሆነ፡፡” አሪሳለቱ አል ቁሸያህ፡

እኔም የሚከተለውን እላለሁ፡ ይህ ፣ ሊታይ የሚገባው ንግግር ነው


15/25
አንደኛው፡- አልቁሸይሪ ማለት ዓብዱልከሪም ብን ሀዋዚን አልቁሸይሪ በመባል ይታወቃል ፣
የሞተው በሒጅራው አቆጣጠር ላይ ነው፡፡ አሽዓሪ ፣ ሱፊ ነው፡፡ ወደጀዕፈር አስሷዲቅ
የሚወስደውን የሐዲስ ሰነድ አላወሳም፡፡ ጀዕፈር አስሷዲቅ የሞተው በሒጅራው አቆጣጠር
ላይ ነው፡፡ በሁለቱ መካከል ከሶስት መቶ አመት በላይ የሚሆን ልዩነት አለ፡፡ እንዲህ
አይነቱን ደግሞ ቂል የሆነ የጥመት ባለቤት እና ሙብተዲዕ ካልሆነ በቀር ሊደገፉበት አይገባም፡፡

ሁለተኛው፡- የሸይኹል ኢስላም ኢብን ተይሚያ ኪታብ “አልኢስቲቃማ” ሱፍይ በሆነው


ቁሸይሪይ ላይ ምላሽ ሰጧል፡፡

ሶስተኛው፡- ይህ ንግግር በጀዕፈር አስሷዲቅ ላይ የተቀጠፈ ውሸት ነው፡፡ ይህ አህባሽ


ከቁሸይሪይ ፣ ቁሸይሪይ ደግሞ ከጀእፈር አስሷዲቅ ነቅሎ ያወሳውን ንግግር ኢብን ተይሚያ
አውስቶቷል፡፡ ከዚያም ኢብን ተይሚያ የሚከተለውን ተናግሯል፡-

“ይህ ንግግር እና መሰሎቹ የእውቀት ባለቤቶች በጀዕፈር ላይ የተዋሸ ለመሆኑ የተስማሙበት


ነው… በርካታ ውሸቶች በጀዕፈር ለይ ተሰራጭቷል፡፡ ታማኝ ዓሊሞች ከእርሱ የነቀሉት በእርሱ ላይ
ከቀጠፉ አካላት ጋር የተቃረነ መሆኑ ይታወቃል፡፡” አልኢስቲቃማ ፡

➢ አህባሹ “አላህ ያለቦታ አለ” የሚለውን ንግግር ወደአቡሀኒፋ አስጠግቷል ፡-

እኔም የሚከተለውን እላለሁ፡ ኢማም አቡሀኒፋ “ፊቅሁል አክበር” በሚባለው ኪታባቸው አላህ
ከዓርሽ በላይ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ እንዴውም አላህ ከዓርሽ በላይ መሆኑን የማያረጋግጥ
አካል ይከፍራል ብለዋል፡፡

ሸይኹል ኢስላም የሚከተለውን ተናግሯል፡ ከአቡሀኒፋ ባልደረቦች ዘንድ ታዋቂ በሆነው


“ፊቅሁል አክበር” ኪታብ ውስጥ አቡ ሙጢዕ አልሀከም ብን ዓብዲላህ አልበለኺ በሰነድ
የሚከተለውን ተናግሯል ፡- “አቡሀኒፋን ስለፊቅሁል አክበር ጠየቅኩት፡፡” እርሱም “በወንጀል
አንድንም አካል አታክፍር ፣ በእርሱ ምክንያት ከኢማን አንድንም አታራቁት ፣ በመልካም እዘዝ
16/25

፣ ከመጥፎም ከልክል፡፡” በማለት ምላሽ ሰጠኝ፡፡


አቡሀኒፋ ፣ “ጌታዬን በሰማይ ይሁን በምድር አላውቅም” ስለሚሉ ሰዎቸ ተጠየቁ፡፡ “በእርግጥ
ካደ ፣ ምክንያቱም አላህ “ረህማን ከዓርሽ በላይ ሆነ” በማለት ተናግሯል ፣ ዓርሹ ከሰባት
ሰማያት በላይ ነው፡፡” በማለት ምላሽ ሰጡ፡፡ እኔም አልኩ ፡ “እርሱ ከዓርሽ በላይ ነው ፣ ነገር
ግን ዓርሽ ከሰማይ ወይም ከምድር መሆኑን አላውቅም” ካለ፡፡ አልኳቸው፡፡ “እርሱ ካፊር ነው፡፡
ምክንያቱም እርሱ ከሰማይ በላይ መሆኑን ተቃወመ፡፡ አላህ ከዒልይን በላይ ነው፡፡ አላህ ከታች
ሳይሆን ከላይ ሆኖ ነው የሚለመነው፡፡” -በሌላ ቃል- “ሰዎች ጌታየ በሰማይ ይሁን በምድር
አላውቅም” ስለሚሉ ሰዎች አቡሀኒፋን ጠየኳቸው፡፡ “በእርግጥ ከፈረ፡፡ ምክንያቱም አላህ
“ረህማን ከዓርሽ በላይ ነው” ብሎ ተናግሯል፡፡ ዓርሹ ከሰባት ሰማያት በላይ ነው፡፡” በማለት ምላሽ
ሰጡኝ፡፡ “አላህ ከዓርሽ በላይ ነው ፣ ነገር ግን ዓርሽ ከምድር ይሁን ከሰማይ አያውቅም፡፡” ብዩ
ጠየኳቸው፡፡ “በሰማይ በላይ መሆኑን ከተቃወመ በእርግጥ ከፈረ፡፡” በማለት ምላሽ ሰጡኝ፡፡

በዚህ ከባልደረቦቻቸው ዘንድ በሚታወቀው የአቡሀኒፋ የታወቀ ንግግር፡ ጌታዬ በሰማይ ወይም
በምድር አላውቅም የሚል ዋቂፋ (አቋም የለሽ) የኩፍር ብይን ከተሰጠው ጌታውን በሰማይም
አይደለም ወይም በሰማይም በምድርም አይደለም የሚል አስተባባይ እና አራቋች እንዴት ሊሆን
ነው? አቡሀኒፋ ለክህደቱ ማስረጃ ያደረጉት “ረህማን በዓርሽ ላይ ነው” ፣ “ዓርሹ ከሰባት
ሰማያት በላይ ነው” የሚለውን አምላካዊ ቃል ነው፡፡

በዚህም “ረህማን ከዓርሽ በላይ ነው” የሚለው የአላህ ቃል አላህ ከሰማያት በላይ መሆኑን ፣
ከዓርሽ በላይ መሆኑን ፣ አላህ በነፍሱ ከዓርሽ በላይ መሆኑን ይጠቁማል፡፡ ከዚያም “በዓርሽ በ ላይ
ነው ነገር ግን ዓርሽ በሰማይ ይሁን በምድር መሆኑ ተወቁፍ ያደረገ ካፊር እንደሚሆን አያይዞ
ተናገረ፡፡ ምክንያቱም ከሰማይ ላይ መሆኑን ተቃወመ፡፡ ምክንያቱም አላህ ከኢልይን በላይ ነው፡፡
እርሱ የሚለመነው ከታች ሳይሆን ከላይ ሆኖ ነው፡፡ ይህ አቡሀኒፋ አላህ ከሰማይ መሆኑን
የተቃወመ አካል ካፊር መሆኑን በግልጽ የተናገሩበት ነው፡፡ በዚህ ላይ አላህ ከኢልይን በላይ
17/25

መሆኑን ፣ እንዲሁም እርሱ የሚለመነው ከታች ሳይሆን ከላይ እንደሆነ ማስረጃ አድርገዋል፡፡

እነዚህ ሁለት መረጃዎች ተፈጥሯዊ እና ዓቅላዊ ናቸው፡፡ ልቦች አላህ ከላይ እንደሆነ ፣ ከላይ
እንጅ ከታች እንደማይለመን በማረጋገጥ ላይ ተፈጥረዋል፡፡ በዚህ ላይ በሌላ ቃል በግልጽ
የተናገሩበት እንደሚከተለው መጧል፡፡

“ከሰማይ በላይ መሆኑን ከተቃወመ በእርግጥ ከፈረ” ይህን ቃል ከእርሱ ሰነድ ያወራው ሸይኹል
ኢስላም አቡ ኢስማኢል አልአንሷሪ አልሀረዊይ “ኪታቡል ፋሩቅ” በሚባለው መጽሐፍ ነው፡፡
መጅሙዕ አልፈታዋ ፡

➢ አህባሹ “ኢትሀፍ ሳደቱል ሙትቂን” በሚባለው ኪታብ “አላህ ያለቦታ አለ” የሚለውን
ንግግር ወደኢማም አሽሻፍዒይ አስጠግቷል፡፡

እኔም የሚከተለውን እላለሁ ፡ በኢትሀፍ ሳደቱል ሙትቂን ኪታብ አገላለጹ የሚከተለው


ነው ፡ ሻፍዒይ የሚከተለውን ተናገረ ፡ “በእርሱ ላይ ማስረጃው ፣ የላቀው አላህ ቦታ ሳይኖር
ነበረ ፣ በአዘል ቦታን ከመፍጠሩ በፊት በነበረው ባህሪ ላይ ሆኖ ቦታን ፈጠረ ፣ በአካሉ መቀየር
፣ በባህሪው መለወጥ በእርሱ ላይ አይበቃም፡፡”

እኔም የሚከተለውን እላለሁ ፡ ይህ ንግግር ጥናት ይፈልጋል

አንደኛው፡- የ“ኢትሀፍ ሳደቱል ሙትቂን” ባለቤት ሙርተዷ ዙበይድይ ሙሐመድ ብን


ሙሀመድ በሂጅራው አቆጣጠር እንደሞተ ከዚህ በፊት አሳልፈናል፡፡ ከዚህ ቦታ
ያለምንም ሰነድ የሻፍዕይን ንግግር አወሳ፡፡ ኢማም አሽፍዒይ የሞቱ በሂጅራው አቆጣጠር በ
ላይ ነው፡፡ በሁለቱ መካከል ከአንድ ሽ አመት በላይ ልዩነት አለው፡፡ ከአላህ ባህሪያት ጋር
የተያያዘ ወሬ ከእርሱ (ከዙበይዲይ) እንዴት ይያዛል? አፊያን ከአላህ እንጠይቃልን፡፡

ሁለተኛው፡- ሙርተዷ ዙበይድይ አሽአርይ ፣ ሱፊ በመሆኑ ከሱና ኡለሞች ነቅሎ ያስተላለፈው


ማስረጃ ሊሆን አይችልም፡፡ ሰነድ ባይኖር ኖሮ ፣ ማንም ሰው የፈለገውን ይናገር ነበር፡፡
18/25
በርካታ አሻዒሮች እና የፍልስፍና ዑለሞች በሰነድ እውቀትና በሀዲስ ጃሂሎች ናቸው፡፡ በዚህ
ምክንያት ከዚህም ከዚያም ያገኙትን ይነቅላሉ፡፡ ጥንቃቄና ማረጋገጥ የላቸውም፡፡ ስለዚህ ከእነርሱ
ያለውን መጠንቀቅ ግድ ይላል፡፡

ሶስተኛው፡- ኢማሙ ሻፍዒያ መጽሐፎች አሏቸው፡፡ ከእነርሱ መካከል እንደምሳሌ ኡም ፣


አርሪሳላህ ፣ ኢኽቲላፉል ሐዲስ የሚባሉ ኪታቦች ናቸው፡፡ ኢማም ሻፍዕይ ታላላቅ ተማሪዎች
አሏቸው፡፡ የኢማም ሻፍዒይን ዓቂዳ ለማወቅ ወደኢማም አሻፍዕይ እና ወደተማሪዎችም
መጽሐፎች መመለስ ግድ ነው፡፡

አራተኛው፡- ልክ እንደሌሎች የሰለፍ ዑለሞች ከኢማም አሻፍዕይ የተያዘው አላህ ከሁሉም


በላይ ነው ፣ አላህ ከዓርሽ በላይ ነው የሚለው ነው፡፡ ልክ እንደቢድዓ ባለቤቶች የኢስተዋን
ትርጉም እስተውላ አላሉም፡፡

ኢማም ኢብን አልኢማም ዓብዱረህማን ብን አቢሀቲም አርራዚ ፣ አቡሹዓይብ እና አቡሰውር


ከአቡ አብዲላህ ሙሀመድ ኢብን ኢድሪስ አሻፍዕይ ይዘው የሚከተለውን ነገሩን ይላሉ ፡-

“ሱናን በተመለከተ እኔ ያለሁበት ንግግር ፣ በእርሷ ላይ ባልደረቦቻችንንም ተመልክተናል ፣


እናንተ የተመለከታችኋቸው ፣ ከእነርሱ የያዝኩባቸውን -ሱፍያን ፣ ማሊክ እና የመሳሰሉት-
የሐዲሰ ባለቤቶችንም ተመልክታችኋል፡፡ ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ እንደሌለ መመስከር
፣ ሙሀመድ የአላህ መልእክተኛ መሆናቸውን መመስከር ፤ አላህ ከዓርሽ ከሰማይ በላይ መሆኑን
፣ እንደፈለገ ለፍጡራን እንደሚቀርብ ፣ አላሀ ወደቅርቢቱ ሰማይ እንደፈለገ እንደሚወርድ
(ማመን) ነው፡፡”

ይህ ከኢማም ሻፍዒይ ሲሆን ሰነዱ ሶሂህ ነው፡፡ ኢጅቲማኡል ጁዩሽ አልኢስላምይ ፡ ተመልከት

ሻፍዒይ የሚከተለውን ተናገሩ፡-

"‫ وجمع عليه قلوب عباده‬،‫"خالفة أبي بكر رضي هللا عنه حق قضاها هللا في سمائه‬
19/25

“የአቡበክር መሪነት ሀቅ ነው ፣ አላህ ከሰማይ በላይ የወሰነው ነው ፣ በእርሱም ላይ የባሮችን


ልቦናዎች የሰበሰበበት ነው”

አነስ ብን ማሊክ በትክክለኛ ሐዲስ የሙእሚኖች እናት ዘይነብ የሚከተለውን ንግግር በነብዩ
‫ ﷺ‬ሚስቶች ላይ በኩራት ትናገር እንደነበር በሀዲሳቸው አስተላልፈዋል፡፡

"‫"زوجكن أهاليكن وزوجني هللا من فوق سبع سماوات‬

“እናንተን ቤተሰቦቻችሁ ነው የዳሯቹህ ፣ እኔን ግን ከሰባቱ ሰማያት በላይ ያለው አላህ ነው


የዳረኝ” ቡኻሪ፡

ኢብን ተይሚያ የሚከተለውን ተናገረ፡- ይህ(ማለትም አነስ ከዘይነብ ይዞ ያወራው) ልክ


እንደሻፍዕይ ንግግር ነው፡፡ አልፈታዋ አልሀመውያ አልኩብራ ገጽ ተመልከት

(በሰማይ በላይ) በሚለው የሻፍዕይ ንግግር የአላህን የበላይነት ማጽደቅ ነው፡፡ ከልቅናው ጋር
በሚስማማ ሁኔታ የበላይነትን ፣ ከዓርሽ በላይ መሆንን የሚያጸድቅን አካል ዓሻኢራዎች
ያከፍራሉ፡፡ ከአላህ ሰላምን እንለምናለን

ኢማም ሻፍዕይ ካፊር ናቸው? በርካታዎች አሻዒራዎች በመዝሀብ ወደሻፍዒይ ይጠጋሉ፡፡ ነገር
ግን በዓቂዳው ይቃረኑታል፡፡ ከነርሱ መካከል የጥመት ሸይኽ የሆነው ዓብደላህ አልሀረሬ አንዱ
ነው፡፡ የሻፍዕይ መዝሀብ ተከታይ ነኝ ብሎ ይሞግታል፡፡

➢ ኢማም ሻፍዕይ በእርሱ ላይ ማስረጃ ለማድረግ (ነጻ የተደረገችውን) ባሪያ ሀዲስ በመጽሐፉ
ውስጥ አውስቷል፡፡ የአላህ መልእክተኛ “አላህ የት ነው” አሏት፡፡ እርሷም “ከሰማይ በላይ
ነው” አለች…

አሻዒራዎች የባሪያዋን ሐዲስ ሌላ ትርጉም ይሰጡታል ወይም ይህን ቃል ደካማ ያደርጉታል፡፡


የአላህን የበላይነት የሚያጸድቅን አካል ያከፍራሉ፡፡
20/25
➢ ይህ አህባሽ በ ሒጅራው አቆጣጠር ላይ የሞተው የአቡል ፈድል አተሚሚይ አብዱል
ዋሂድ የጻፈውን “ኢእቲቃዱል ኢማም አልሙበጀል” የተባለ መጽሐፍ ማስረጃ በማድረግ
“አላህ ያለቦታ አለ” የሚለውን ወደኢማም አህመድ አስጠግቷል፡፡
እኔም እላለሁ፡ ይህ ንግግር ጥናት ያስፈልገዋል

አንደኛው፡- ሊመለከቱት ዘንድ አምታቲታ የሆነው አህባሽ የኢማም አህመድን አገላለጽ


አላወሳውም፡፡

ሁለተኛው፡- አህባሹ ባወሳው ኪታብ ውስጥ እርሱ ካወሳው ጋር እርስ በበርሱ የሚጋጭ ንግግር
አለው፡፡ እርሱም፡ “አላህ ከተላቀው ዓርሽ በላይ ነው…” ብሎ ይናገር ነበር፡፡ ማለትም -ኢማም
አህመድ፡፡ እንዲሁም (ኢማም አህመድ) የ“ኢስቲዋእን” ትርጉም ዑሉው ፣ እርቲፋእ
“አለል ዓርሽ ኢስተዋ” የሚለውን ደግሞ በእርሱ ላይ የበላይ ሆነ በሚል ተርጉሞታል፡፡ ኢዕቲቃዱ
አልኢማም አልሙበጀል ኢብን ሀንበል፡ ገጽ

አህባሹ ባወሳው ኪታብ ውስጥ ፡ ኢማም አህመድ ለአላህ ሁለት እጆች እንዳሉት ያጸድቃሉ፡፡
እጅ የሚለውን ቃል ሀይል ብሎ የሚተረጉምን አካል አውግዘዋል፡፡ ኢእቲቃዱል አልኢማም አልሙበጀል ኢብን
ሀንበል፡ ገጽ

አሁንም በተወሳው ኪታብ ውስጥ አህመድ የአላህን ንግግር ያጸድቃል፡፡ አጣመው የሚተረጉሙ
አካላትንም ያወግዛል፡፡ ኢዕቲቃዱ ኢማም አልሙበጀል ኢብን ሀንበል፡ ገጽ

ሶሰተኛው፡- የኢማም አህመድ ዓቂዳ የሚወሰደው ከራሱ መጽሐፎች ፣ ከታማኝ ልጆቹ እና ታዋቂ
ሐፊዝ ከሆኑት በዓቂዳቸው ሰላማዊነት በከተማም ይሁን በሰፈር አብረውት ካልተለዩት ባልደረቦቹ
ነው፡፡

ከኢማም አህመድ ታላላቅ ኪታቦቹ መካከል (አርረድ አለል ጀህምያ ወዘናዲቃ) ይገኝበታል፡፡
በዚህ መጽሐፍ ውስጥ (አርረህማን ዓለል አርሽ ኢስተዋ) የሚለውን እና መሰል ቁርኣናዊ
አንቀጾች ጀህም አጣሞ በመተርጎሙ ምለሽ ሰጦታል፡፡ ኢማም አህመድ የአላህን የበላይነት
21/25
የሚጠቁሙ አንቀጾችን እንደሚከተለው አወሳ፡፡ ለምሳሌ፡
﴾‫ف نَ ِذي ِر‬ ِ ِ ِ
َ ‫﴿أ َْم أَمَتُم همن ِِف ال هس َماء أَن يُْرس َل َعلَْي ُك ْم َحاصبًا فَ َستَ ْعلَ ُمو َن َكْي‬
“ወይም በሰማይ ውስጥ ያለን በእናንተ ላይ ጠጠርን ያዘለች ነፋስን ቢልክባችሁ
ትተማማናላችሁ?” አል ሙልክ፡

ِ ِ ِ
ْ َ‫﴿إِلَْيه ي‬
ُ ‫ص َع ُد الْ َكل ُم الطهي‬
﴾‫ب‬
“መልካም ንግግር ወደርሱ ይወጣል” ፋጢር፡

‫ك إِ َه‬ ِ ِ ِ
﴾‫ل‬ َ ‫يسى إِِّن ُمتَ َوف‬
َ ُ‫يك َوَرافع‬ ِ
َ ‫﴿إ ْذ قَ َال اَّللُ ََّي ع‬
“አላህም ባለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡ዒሳ ሆይ! እኔ ወሳጂህ ወደ እኔም አንሺህ ነኝ፡፡”
አል ዒምራን፡

﴾‫﴿بَل هرفَ َعهُ اَّللُ إِلَْي ِه‬


“ይልቁንስ አላህ (ዒሳን) ወደርሱ አነሳው፡፡” አን ኒሳእ፡

﴾‫﴿ ََيَافُو َن َرهَّبُم ِمن فَ ْوقِ ِه ْم‬


“ጌታቸውን ከበላያቸው ሲሆን ይፈሩታል፡፡” አን ነሕል፡

﴾‫﴿ َوُه َو الْ َعلِ ُّي الْ َع ِظ ُيم‬


“እርሱም የሁሉ የበላይ ታላቅ ነው፡፡” አል በቀራ፡

ከዚያም ኢማም አህመድ፡- “ይህ የአላህ ዜና ነው ፤ እርሱ ከሰማይ ላይ እንደሆነ ነገረን፡፡”


አር ረድ አለል ጀህምያ ወዘናዲቃ፡ ገጽ

ኢማም አህመድ የሚከተለውን የአላህ ንግግር አወሳ፡-


ِ ‫﴿وهو اَّلل ِِف ال هسماو‬
ِ ‫ات َوِِف اْل َْر‬
﴾‫ض‬ ََ ُ ََُ
“እርሱም ያ በሰማያትና በምድር (ሊግገዙት የሚገባው) አላህ ነው፡፡” አል አንዓም፡

አህመድ የሚከተለውን ተናገሩ፡ “እርሱ በሰማይ ላለው ሁሉ አምላክ ነው ፤ በምድር ላለው


ሁሉ አምላክ ነው፡፡ እርሱ በዓርሽ ላይ ነው፡፡ ከዓርሽ ውጭ ያለውን ሁሉ እውቀቱ አካቧል፡፡ ከአላህ
እውቀት አንድም ቦታ የሚያገል የለም፡፡ የአላህ እውቀት ከአንድ ቦታ ኑሮ ፣ ከሌላ ቦታ
የማይኖርበት የለም፡፡” አር ረድ ዓለል ጀህምያ ወዘናዲቃ፡ ገጽ
22/25

አህመድ የሚከተለውን ተናገረ፡ “እንሆ እርሱ ከሰባት ሰማያት በላይ እንደሆነ የእውቀት
ባለቤቶች ሁሉ አወቁ፡፡” አር ረድ ዓለል ጀህምያ ወዘናዲቃ፡ ገጽ

በአሽዓርይና በአህባሽ መዝሀብ ኢማም አህመድ ካፊር ናቸው፡፡ ምክንያቱም የቢድዓ ባለቤች
በጎደሎ ዓቅላቸው የሚያራቁቱትን ፣ በልብ ወለዳቸው የሚያጣምሙትን ፣ ከልቅናው ጋር
በሚስማማ ሁኔታ የአላህን የበላይነትና ከዓርሽ በላይ መሆን አጽድቋል ፤ ለአላህ ሁለት እጆችን
አጽድቋል ፤ የአላህን ተናጋሪነት አጽድቋል እንዲሁም ሌሎችንም ባህሪያቶች አጽድቋል፡፡

➢ ኸላል “ኪታቡ ሱና” በሚባለው መጽሐፉ ዩሱፍ ብን ሙሳ ከዓብደላ ብን አህመድ ፣


ዓብደሏህ ደግሞ አባቴ፡ “ጌታችን ከሰባት ሰማያት በላይ ከአርሽ በላይ ከፍጡራኑ በተለየ ፤
እውቀቱ ፣ ቁድራው በሁሉም ቦታ ነው?” ተባለ፡፡ “አዎ ከእውቀቱ አንድም ነገር የሚያገል
የለም፡፡” አለ፡፡

ኸላል የሚከተለውን ተናገረ፡ ዓብዱል መሊክ ብን አብዱል ሁመይድ አልመይሙኒ “አላህ ከዓርሽ
በላይ አይደለም” ስለሚሉ ሰዎች አባአብዲላህ አህመድን ጠየቅሁት፡፡ እርሱም “ንግግራቸው
በሙሉ የሚሽከረከረው በኩፍር ላይ ነው፡፡” አለ ብሎ ነገረኝ፡፡ የኢብን አልቀይም ኢጅቲማኡ አልጁዩሽ

አልኢስላምያ፡ ተመልከት፡፡

እንደዚሁ የሸይኹል ኢስላም ኢብን ተይሚያን ኪታቦች ተመልከት፡፡ ከእነርሱ መካከል “በያን
ተልቢስ አልጀህምያ” እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡

ኸላል ማለት አህመድ ብን ሙሀመድ ብን ሀሩን ብን የዚድ አልኸላል አቡበክር የሚባል ሲሆን የ
“ኪታቡ ሱና” ባለቤት ነው ፤ ሀፊዝ ፣ ፈቂህ ነው፡፡ የሀናቢላዎች ሸይኽ እና ዓሊማቸው ነው፡፡
እርሱ የኢማም አህመድ ብን ሀንበልን እውቀቶች በመሰብሰብ ላይ ትኩረት ከሰጡ ሰዎች
መካከል አንዱ ነበር፡፡ ለእርሷ ሲባል ወደየአገሮች ተጉዟል፡፡ በኢማም አህመድ እውቀቶች
ከሰዎች ሁሉ በጣም አዋቂ ነበር፡፡ ታሪክ አልኢስላም ሊዘህብይ፡ ተመልከት
23/25
(አስሱና ሊልኸላል) የሚባለውን ኪታብ ኢብን ተይሚያ ፣ ኢብን አልቀይም እና ሌሎችም
የኢስላም አኢማዎች ይደገፉበት ነበር፡፡
➢ አህባሹ “አላህ ያለቦታ አለ” የሚለውን ወደኢብን ጀሪር አጦበሪ አስጠግቷል፡፡
እኔም የሚከተለውን እላለሁ፡ ኢብን አልጀሪር አጦበሪ የቋንቋ እና የተፍሲር ኢማም ነው፡፡
ኢስቲዋእን በዑሉው (በበላይነት) እና በኢርቲፋእ (ከፍ በማለት) ተርጉሟል፡፡ ኢስተዋ
“አቅበለ” የሚል ትርጉም አለው ለሚሉ ሰዎች ምላሽ ሰጧል፡፡ የዚህን ሰለፍይ የሆነ ትርጓሜ
በተፍሲር ኪታቡ በተለያዩ ቦታዎች አውስቷል፡፡

አላህ ይዘንለትና (ሱምመ ኢስተዋ ዓለል ዓርሽ) የሚለውን የቁርኣን አንቀጽ “በእርሱ በላይ
ሆነ” በሚል ተርጉሞታል፡፡ ተፍሲር አጦበሪ፡

(አርረህማን ዓለል ዓርሽ ኢስተዋ) የሚለው ንግግሩን በተመለከተ፡ መወሳቱ የላቀው አላህ
የሚከተለውን ይላል፡ “ረህማን ዓለል አርሽ ኢርተፈዓ ፣ ዓላ”፡፡ ተፍሲሩ ጦበሪ፡

ጦበሪ የሚከተለውን ተናገረ፡ (ሁወ መዓኩም አይነማ ኩንቱም)፡ “እናንተ ሰዎች ሆይ!
እናንተን እርሱ በማንኛውም ቦታ ብትሆኑ ይመለከታችኋል፣ ያውቃችኋል፡፡ ስራችሁንም ያውቃል
፣ እንቅስቃሴያችሁንም ፣ መርጊያችሁንም ያውቃል፡፡ እርሱ ከሰባት ሰማያት በላይ ከዓርሽ በላይ
ነው፡፡” ተፍሲር ጦበሪ፡

“ሶሪሁ ሱና” በሚባለው ኪታቡ፡ ገጽ/ ላይ ልክ እንደዚሁ የአላህን ከዓርሽ በላይ መሆን
አጸደቀ፡፡ ይህ ስውር አምታቲታ አህባሽ በሙፈሲሩ ኢብን ጀሪር አጦበሪ ተፍሲር ይስማማል?

ኢብን ጀሪር ሁለት እጆች ለአላህ እንዳሉት ያጸድቃል፡፡ ከልቅናው ጋር በሚስማማ ሁኔታ
ሌሎችንም ባህሪዎች ያጸድቃል፡፡ እርሱ ሙጀሲም ካፊር ነውን?

ማንቂያ፡ ወደአቢል ሀሰን አልአሽዓርይ በበደል እና በወንጀል የተጠጉ አሻዒራዎች ምን ይላሉ?


እርሱ ወደኢማም አህመድ ዓቂዳ ከተመለሰ በኋላ የሚከተለውን ተናግሯል ፡-
24/25
“እንሆ ከፍ ያለው አላህ ከዓርሽ በላይ ፣ ከመሬት ሳይሆን ከሰባት ሰማያት በላይ ነው፡፡ ለዚህ
የሚከተሉት የቁርኣን አንቀጾች ይጠቁማሉ ፡ (አአሚንቱም መን ፊ ሰማኢ አን የኽሲፈ
ቢኩሙል አርዶ) ፤ (ኢለይሂ የስአዱል ከሊሙ…) ፤ (አርረህማን ዓለል ዓርሽ ኢስተዋ)

የቀደር ባለቤቶች እንደሚሉት የአላህ ኢስቲዋእ (የበላይነት) ኢስቲላእ (መሾም)


አይደለም፡፡ ምክንያቱም አላህ በማንኛውም ነገር ላይ ሙስተውሊ ከመሆን (ከመሾም)
አልተወገደም፡፡” ሪሳለቱ ኢላ አህሊ ሱጉር ፡ ገጽ

አቡል ሀሰን አልአሻአርይ የሚከተለውን ተናገረ፡ “አላህ በእርሱ በሚስማማው መልኩ ከአርሽ
በላይ ነው” አልኢባና ዓን ኡሱሊ ዲያና አሽዓርይ ገጽ ፡

የሚከተለውን ተናገረ፡ “ለእርሱ- ሷድ ላይ (ኸለቅቱ ቢየደይየ -በሁለት እጆቸ


ለፈጠርኩት) ፣ ማኢዳ፡ (በል የዳሁ መብሱጦታኒ- ይልቁንም ሁለት እጆቹ የተዘረጉ
ናቸው) በማለት እንደተናገረው- ያለአኳኋን ሁለት እጁች አሉት፡፡” የአቡል ሐሰን አልአሽዓሪ ኢባና አን

ኡሱሊ ዲያና ፡ ገጽ ) ተመልከት፡፡ ታዲያ እርሱን ሙጀሲም ፣ ካፊር ትላለህ?


ሌላው ማንቂያ፡ ወደአሽዓርያ መዛመዱ ብቻ ቢድዓ ነው፡፡

ኢብን ተይሚያ የሚከተለውን ተናገረ፡ “ከእነርሱ መካከል የእርሱን ተቃራኒ ይፋ ሳያደርግ


አሽዓሪይ በመጨረሻ እድሜው ባዘጋጀው በ “ኢባና” ኪታብ የሚናገር ከሆነ ከአህለሱና
ይቆጠራል፡፡ ነገር ግን ወደአሽዓርያ መዛመዱ ብቻ ቢድዓ ነው፡፡” መጅሙእ አልፈታዋ ፡

ወደኋላ የመጡ አሽዓርዮች በኢባና ኪታብ በአጠቃላይ ተቃራኒዎች ናቸው፡፡ የአላህ የበላይነት ፣
ከአርሽ በላይ መሆን ፣ የንግግር ባህሪ ፣ የእጅ እና ሌሎችም ባህሪያቶች ከአላሀ ጋር በሚስማማ
መልኩ ማጽደቅ በኢባና ኪታብ ውስጥ ይገኛል፡፡

ከኢማም አህመድ ሸይኾች ታላቁ እና አንዱ ሐፊዝ የሆነው የዚድ ብን ሀሩን “ጀህምያ
ማን ነው” የሚለው ጥያቄ ቀረበለት፡፡“ረህማን ከዓርሽ በላይ ነው የሚለውን ፣ ተራው ማህበረሰብ
25/25
በልቡ ከሚያረጋግጠው ተቃራኒ ያለ ሰው ጀህምይ ነው” በማለት ምላሽ ሰጧል፡፡ የቡኻሪ ኪታብ ኸልቁ

አፍዓሊል ዒባድ ገጽ ፡ ተመልከት አስሱና የአብደላ ብን አህመድ ኪታብ ፡ ተመልከት

‫وصلى هللا على نبينا محمد وعلى آله وصحبه أجمعين‬


ባህር ዳር በሚገኙ የአህለሱና መሻይኾች የተቀሩ ጠቃሚ ኪታቦች፣ ከሀገር
ውስጥና ከውጭ በሚመጡ መሻይኾች የተሰጡ ኮርሶች፣ ሙሓዶራዎች፣
የጁመዓ ኹጥባ፣ በትክክለኛ ማስረጃ የተደገፉ የተለያዩ ኢስላማዊ መጣጥፎችን
የሚከተለውን የቴሌግራም ሊንክ ጆይን በማድረግ መከታተል ይችላሉ
http://t.me/alateriqilhaq

You might also like