ራስን የማብቃት ሪፖርት

You might also like

Download as docx, pdf, or txt
Download as docx, pdf, or txt
You are on page 1of 5

/

በልደታ ክ ከተማ ወረዳ 3 / /


ሥራ ኢንተርፕራይዝ እና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ ቤት

የማበረሰብ አቀፍ ስራዎች ተጽዕኖ ግምገማ ቡድን

የ 2015 . ዓ ም የራስ ማብቃት ሪፖርት

ነብዩ ገመዳ
(የተቀናጀ የመሰረተ ልማት ባለሞያ)

ጥር፣2016 ዓ.ም
1.መግቢያ
የወረዳ 3 ስራ ዕድል ኢንተርፕራይዝ እና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት በዚህ ዓመት በተሻለ መልኩ የአገልግሎት
አሰጣጥ ስርአትን በመዘርጋት ተግባራትን ስኬታማና እውን ለማድረግ በአመለካከት፣በእውቀትና በክህሎት የበቃ ፈጻሚ
በመሆን ህብረተሰቡን ማገልገል የሙያዬ ግዴታ መሆኑ የሚታወቅ ነዉ፡፡ ስለዚህ እኔም በል/ክ/ከተማ ወረዳ 3 ሥራ
ኢንተርፕራይዝ እና ኢንዱስትሪ ልማት ጽ/ቤት የመሰረተ ልማት ባለሞያ እንደመሆኔ መጠን በ 2015
በጀት አመት ለጽ/ቤቱ ብሎም ለወረዳዉ የበኩሌን ድርሻ በጽናትና በቁርጠኝነት በማበርከት ለ 2016 በጀት
ዓመት ያሉኝን ጠንካራ ጎኖች በማስቀጠል እና ያሉብኝን ክፍተቶች በመሙላት በሙያዬ ህብረተሰቡን
ለማገልገል ይህንን ራስ የማብቃት ሪፖርት እንደሚከተለዉ አቀርባለሁ፡፡

2- የሪፖርቱ ነባራዊ መነሻ


በተያዘዉ በጀት አመት ለጽ/ቤቱ የበኩሌን አስተዋጽኦ በማድረግ የተጀመሩ ስራዎችን ለማስቀጠል ይቻል ዘንድ ያሉኝን
ጥንካሬዎችና ክፍተቶቸን በመለየት ጥንካሬዎቼን የበለጠ በማጎልበት ለማስቀጠልና ክፍተቶቼን በመለየት ለ 2016 በጀት ዓመት
ሊስተካከሉበት የሚችሉበትን ሪፖርት በማዘጋጀት ወደ ተግባር ለመግባት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ነው ፡፡

2.1.ጥንካሬዎች
 ራስን ከሌላዉ ጋር በማለማመድ እና በመግባባት ከስራ ባልደረቦቼ ጋር ጥሩ የሆነ እና ዉጤታማ የሆነ ስራ
መስራት፣
 በሃይል መድረኮችም ሆነ በንዑሳን መድረኮች ላይ ሃሳብን በነፃነት መግለፅ መቻል፣
 ስራዎችን በራሴ በመተማመንና በተገቢው ሁኔታ ተረድቶ ለመስራት ያለኝ ተነሳሽነት
 የተሰማራሁበትን ተግባር በጥራት መስራት ፣ ዕቅድ ማቀድና ሪፖርት ማዘጋጀት
 የጽ/ቤት ንብረት በአግባቡ መያዝ፤መጠቀም፤፤

2.2. ክፍተቶች
 በአንድ አንድ ስራዎች ላይ ባለመናበብ ስሜታዊነት መስተዋሉ
 ሙሉ እቅምን አሟጥጦ አለመጠቀም

3- ዓላማ

3.1.1. በፀረ-ኪራ ይሰብሳቢነት ትግሉ ላይ የጎላ ሚና ያለው ሰራተኛ መሆን፣


3.1.2. ከስሜታዊነትና ከተስፋ ቆራጭነት በመላቀቅ በጽናት እና በቁርጠኝነት የሚሰራ ሰራተኛ
መሆን ፣
3.1.3. ሙሉ አቅምን አሟጥጦ በመጠቀም ህብረተሰቡን ማገልገል፡፡
4- ዋና ዋና እና ዝርዝር ተግባራት

4.2 በፀረ-ኪራይ ሰብሳቢነት ትግሉ ላይ የጎላ ሚና ያለው ሰራተኛ መሆን ፣


 የሚንፀባረቁ የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባራትን መለየት፤
 ለኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር ምንጭ የሆኑ ጉዳዮችን መለየትና መረዳት ፣
 ለኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር ምንጭ ለሆኑት የመቅረፊያ ወይም ማስወገጃ መንገዶችን
መቀየስ ፣
 እነዚህን መንገዶች በመጠቀም የኪራይሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር መታገልና ማስወገድ
 የመጣውን ለውጥ በየጊዜው እየገመገምሁ ዉጤቱንም እየመዘገብኩና እየለካሁ መሄድ

4.3 ከስሜታዊነትና ከተስፋ ቆራጭነት በመላቀቅ በጽናት እና በቁርጠኝነት የሚሰራ ሰራተኛ መሆን

 በስራ ላይ ስሜታዊ የሚያረጉኝንና ተስፋ የሚያስቆርጡኝን ነገሮች በትክክል መለየት ፣


 ተስፋ የሚያስቆርጡኝና ስሜታዊ የሚያደርጉኝን ነገሮች ከሚመለከተው አካል ጋር በመነጋገር
እንዲፈቱ ማድረግ ፣
 በስራ ባልደረቦቼ በአቻ ለቸቻ የቡድን ውይይት እና በግል እንድያግዙኝ በማድረግ የሚሰጡኝን ጠቃሚ
ሀሳቦች በመውሰድ ራስን የማስተካከል ስራ መስራት ፣
 ስሜታዊነትን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ጽሁፎችን በማንበብ ከችግሩ መውጣት ፣
 በመጨረሻም ያመጣሁትን ለውጥ በየጊዜው እየገመገምኩና እየለካሁ መሄድ ፡፡

5.እቅዱን ለማሳካት ያሉ ምቹ ሁኔታዎች

 እቅዱን ለማሳካት ያለኝ ተነሳሽነትና ቁርጠኝነት


 የተሻለ ክህሎትና ልምድ ያላቸው የስራ ባልደረቦች መኖራቸው
 የተለያዩ የመገነባቢያ/መማማሪያ/መድረኮች መኖራቸዉ
7.የአፈፃፀም አቅጣጫ

 ራስን የማብቃት ሪፖርት ማዘጋጀትና በሚመለከተው የቅርብ ሀላፊ ማፀደቅ ፣


 የተቀመጡ ዓላማዎችን ለማሳካት በዝርዝር የተቀመጡ ተግባራትን በጊዜ ሰሌዳ በማስቀመጥ መተግበር
 ራስን ለማብቃት እና በቡድን የመፈጸም አቅም ለማሳደግ የሚረዱ አጋዥ መጽሀፍትን ማንበብ
 የሚሰጡ ስልጠናዎችን በንቃት መሳተፍና መሻሻልን እየገመገሙና እየመዘኑ መሄድ ፣
 በአቻ ለአቻ የውይይት መድረክና ከስራ ባልደረቦቼ የማገኘውን እውቀት በትክክል መጠቀም፣
 በአጠቃላይ ራሴን ለማብቃት ያስቀመጥኳቸውን ተግባራቶች በትክክል በመተግበር እና ቋሚ የግንኙነት
ጊዜ ከቡድን አባላት ጋር በመፍጠር የመጣውን ለውጥ በየጊዜው እየመዘገብኩና እየለካሁ መሄድ ፣

8.የግምገማና የሪፖርት ስርዓት

 በየቀኑ የተከናወኑ ራስን ከማብቃት እና አጠቃላይ የተቋሙን ተልእኮ ከማሳካት አንጻር ተግባራትን
በየቀኑ በግል እየገመገሙና እያዩ መሄድ
 የመጣውን ለውጥ በሳምንት አንድ ጊዜ ከቡድን አባላቶቼ ጋር በ 1 አቻ ለአቻ በጋራ መድረክ መገምገም፣
 ሪፖርት በየወሩና በየሩብ ዓመቱ ለቅርብ ኃላፊ ማቅረብ፣
 ከቅርብ ኃላፊ የሚሰጡ ግብረመልሶችን ተቀብሎ በቶሎ ምላሽ መስጠት፣
 የመጣውን ለውጥ እያረጋገጡ መሄድና በመረጃ አጠናክሮ መያዝ፣
9.ማጠቃለያ

ይህ ሪፖርት ሲቀርብ ያሉኝን ጠንካራ ጎኖቼን የበለጠ አጠናክሬ ለመቀጠልና የሚታዩብኝን ክፍተቶች በመለየት
እና ለቀጣይ ሊሻሻል የሚችልበትን ስልቶች በማወቅ እና በመረዳት የታቀደ ነው ፡፡ስለሆነም በዚህ በጀት አመት
የጽ/ቤቱን እንቅስቃሴ ከዳር ለማድረስ የተጣለብኝን ሙያዊ ሀላፊነት በትክክል ለመወጣት ያስችለኝ ዘንድ
ያለብኝን የክህሎት ክፍተትና የአመለካከት ጉድለት ለመሙላት እንዲያግዘኝ ይህንን የ 2015 በጀት አመት የራስ
ማብቃት ሪፖርት አዘጋጅቻለሁ ፡፡

You might also like