Download as docx, pdf, or txt
Download as docx, pdf, or txt
You are on page 1of 34

መመሪያ ቁጥር-----/2006

የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ከተሞች


የተሻሻለው የሊዝ እና የኪራይ መነሻ ዋጋ
መወሰኛ የአፈፃፀም መመሪያ

ጥር 2006 ዓ/ም
ባሕር-ዳር

በከተሞች የህዝብ ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በመምጣቱ ምክንያት በመሬት አቅርቦት እና ፍላጎት
መካከል ያለው ያለመጣጣም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሰፋ በመምጣቱ ቀጣይነት ያለው መሰረተ ልማት የተሟላለት
የመሬት አቅርቦትን ማረጋገጥ በማስፈለጉ፤

በከተሞች የመሬት ሊዝና ኪራይ መነሻ ዋጋ የመሬት ዝግጅት ወጪ በሊዝ ዘመኑ ውስጥ መመለስ በሚያስችል ታሳቢ በስራ
ላይ ያለውን የመሬት የሊዝና ኪራይ መነሻ ዋጋ በማሻሻል የመሬት አቅርቦቱን ማሳደግ ተገቢ ሆኖ በመገኘቱ፤

0
የመሰረተ ልማት መዘርጊያ እና ሌሎች የመሬት ዝግጅት ወጭዎች ዋጋ ከጊዜ ወደ ጊዜ መጨመር ምክንያት
የመሬት ዋጋ/land value /የጨመረ ሲሆን ከተሞች ይህን መሬትን ለማዘጋጀት የሚወጣ ወጭ ከመሬት ሀብት
በሚገኝ ገቢ መሸፈን እንዳለባቸው ስለታመነበት፤

አሁን በስራ ላይ ያለው የከተሞች የሊዝ ወይም የቦታ ኪራይ መነሻ ዋጋ በ 2005 እና 2006 ዓ.ም ለተለያዩ አገልግሎቶች
በጨረታ በቀረቡ ቦታዎች ላይ ለካሬሜትር ከቀረበው ዝቅተኛና ከፍተኛ ዋጋ ጋር ሲነፃፀር እና ከሌሎች አቻ ክልሎች ሊዝ
ወይም ኪራይ ዋጋ ጋር ሲገናዘብ በጣም አነስተኛ ሆኖ በመገኘቱ፤

በስራ ላይ የነበረው የሊዝ ወይም ኪራይ መነሻ ዋጋ መወሰኛ የአፈፃፀም መመሪያ ለረጅም ጊዜ ሳይከለስ
በመቆየቱ እና የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ ተሻሽሎ በወጣው አዋጅ ቁጥር 721/2004 አንቀጽ 14
ንዑስ አንቀጽ 3 እንዲሁም አዋጁን ለማስፈፀም በወጣው ደንብ ቁጥር 103/2004 አንቀጽ 30
ንዑስ አንቀጽ 1 መሰረት የሊዝ ወይም ኪራይ መነሻ ዋጋ ወቅታዊነቱን እንዲጠብቅ ቢያንስ
በየሁለት አመቱ መከለስ እንዳለበት በመደንገጉ፤

የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ ተሻሽሎ በወጣው አዋጅ ቁጥር 721/2004 አንቀጽ 33 ንዑስ አንቀጽ
2፣ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት አስፈጻሚ አካላት እንደገና ማቋቋሚያና ስልጣንና ተግባራት መወሰኛ አዋጅ ቁጥር
176/2003 አንቀጽ 11 ንዑስ አንቀጽ 1 ፊደል ሠ እና የከተማ ቦታን በሊዝ ለማስተዳደር በወጣዉ የክልሉ
ደንብ ቁጥር 103/2004 አንቀጽ 57 ንዑስ አንቀጽ 2 በተሰጠዉ ስልጣን መሰረት የኢንዱስትሪና ከተማ
ልማት ቢሮ ይህንን መመሪያ አዉጥቷል፡፡

ክፍል አንድ
ጠቅላላ
1. አጭር ርዕስ
ይህ መመሪያ “የተሻሻለው የሊዝ እና የኪራይ መነሻ ዋጋ መወሰኛ የአፈፃፀም መመሪያ
ቁጥር--------/2006” ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል፡፡

2. ትርጓሜ

የቃሉ አገባብ ሌላ ትርጉም የሚያሰጠው ካልሆነ በስተቀር በዚህ መመሪያ ውስጥ፡-


1. “አዋጅ” ማለት የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ የወጣው አዋጅ ቁጥር 721/2004 ዓ.ም ነው፡፡
2. “ደንብ” ማለት የከተማ ቦታን በሊዝ ለማስተዳደር እንደገና ተሻሽሎ የወጣ የክልል መስተዳድር
ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 103/2004 ነው፡፡

1
3. “ሊዝ” ማለት በጊዜ በተገደበ ውል መሰረት የከተማ ቦታ የመጠቀም መብት የሚገኝበት የመሬት
ይዞታ ስሪት ነው፣፡
4. “የሊዝ ዘመን” ማለት በአዋጁ አንቀጽ 18 በተደነገገው መሰረት ለየአገልግሎት አይነቱ የተወሰነው
የይዞታ መጠቀሚያ የጊዜ ጣሪያ ነው፡፡
5. “ኪራይ” ማለት በጊዜ ባልተወሰነ ወይም ባልተገደበ ውል መሰረት የከተማ ቦታ የመጠቀም መብት
የሚገኝበት የመሬት ይዞታ ስሪት ነው፣፡
6. “ከተማ” ማለት ማዘጋጃ ቤት የተቋቋመበት ወይም ሁለት ሺህ ወይም ከዚያ በላይ የህዝብ ቁጥር
ያለውና ከዚህ ውስጥ ሃምሳ በመቶ በላይ የሚሆነው ነዋሪ ከግብርና ውጭ በሆነ ሥራ ላይ
የተሰማራ ሆኖ የሚገኝበት አካባቢ ነው፡፡
7. “የከተሞች ፈርጅ” ማለት በክልሉ ደንብ ቁጥር 65/2001 በተደነገገው መሰረት የክልሉ ከተሞች
ሜትሮፖሊታን፣ መካከለኛ፣ አነስተኛ ከተማ አስተዳደር እንዲሁም የማዘጋጃ ቤት ከተማ መሪ
ማዘጋጃ ቤት፣ ንዑስ ማዘጋጃ ቤትና ታዳጊ ከተማ በሚል የተከፋፈሉበትና የተሰየሙበት ነው፡፡
8. “የከተሞች ደረጃ” ማለት ለክልሉ ከተሞች የቦታ ደረጃ ምደባ አሰጣጥ ብቻ ሲባል በስድስት የከተማ
ደረጃ የተመደቡበት ነው፡፡
9. “የቦታ ደረጃ” ማለት የክልሉ ከተሞች እንደ ከተሞቹ የልማትና እድገት ስትራቴጅካዊ ጠቀሜታ
አንፃር ከአምስት እስከ ሁለት የቦታ ደረጃ የተከፋፈሉበት ነው፡፡
10. “መሰረተ ልማት” ማለት ኢኮኖሚያዊ መሰረተ ልማት (መንገድ፣ ዉሀ፣ መብራት፣ ስልክ፣ ዲች
ድልድይ፤ ግድብ፤ የገበያ ማዕከል፤ ወዘተ) እና አካባቢያዊ መሰረተ ልማት (የደረቅ እና ፈሳሽ ቆሻሻ
ማስወገጃ፤ የብክለት ማከሚያ ስትራክቸሮችን እና ወዘተ) የሚያጠቃልል ነው፡፡
11. "ካሳ" ማለት ለሕዝብ ጥቅም ሲባል እንዲለቀቅ በተፈለገው መሬት ላይ በህጋዊ መንገድ ለሰፈረ ንብረት በዓይነት፣
በገንዘብ ወይም በሁለቱም በካሳ መመሪያ ቁጥር 35/2000 መሰረት የሚፈፀም ክፍያ ነው፡፡
12. “የሊዝ መነሻ ዋጋ” ማለት ዋና ዋና የመሠረተ ልማት አውታሮችን ለመዘርጋት የሚያስፈልጉ
ወጪዎችን ፣ነባር ግንባታዎች ባሉበት አካባቢ የሚነሱ ግንባታዎችንና ንብረቶችን ለማንሳት
የሚያስፈልጉ ወጪዎችን፣ ለተነሺዎች የሚከፈል ካሣን እና ሌሎች አግባብነት ያላቸዉ
መስፈርቶችን መሰረት በማድረግ ለአንድ የሊዝ ዘመን በካሬ ሜትር የሚተመን የመሬት ሊዝ
የጨረታ መነሻ ዋጋ ነው፡፡
13. “በጨረታ መሰረት የተላለፈ ይዞታ ጠቅላላ የሊዝ ክፍያ” ማለት ጠቅላላ የቦታው ስፋት(ካ.ሜ) ሲባዛ
ቦታው ለካሬ ሜትር የተላለፈበት ዋጋ ነው፡፡
14. “በጨረታ መሰረት የተላለፈ የሊዝ ይዞታ ዓመታዊ ክፍያ” ማለት ቅድሚያ የሊዝ ክፍያ
መጠን ከጠቅላላ የሊዝ ክፍያ መጠን ላይ ተቀንሶ የሚገኘው ጠቅላላ ቀሪ ክፍያ በሊዝ ውሉ
ላይ ለተቀመጠው የክፍያ ማጠናቀቂያ ጊዜ ተካፍሎ የሚገኘው የገንዘብ መጠን ነው፡፡

2
15. “በሊዝ ምደባ መሰረት የተላለፈ ይዞታ ጠቅላላ ክፍያ” ማለት ለአገልግሎት ዓይነቱ ለካሬ ሜትር
የተቀመጠው የሊዝ መነሻ ዋጋ ሲባዛ በቦታው ጠቅላላ ስፋት ይሆናል፡፡
16. “በሊዝ ምደባ መሰረት የተላለፈ የሊዝ ይዞታ ዓመታዊ ክፍያ” ማለት ለአገልግሎት ዓይነቱ ለካሬ
ሜትር የተቀመጠው የሊዝ መነሻ ዋጋ ሲባዛ በቦታው ጠቅላላ ስፋት የሚገኘው ውጤት
ሲካፈል በሊዝ ውሉ ላይ ለተቀመጠው የክፍያ ማጠናቀቂያ ጊዜ የሚገኘው የገንዘብ መጠን
ነው፡፡
17. “የሊዝ ወይም የኪራይ ጨረታ ዋጋ” ማለት የነጻ ገበያ ስርዓትን በመከተል መሬትን ለልማት
የሚፈልግ ተጫራች በነጻ ዉድድር የሊዝ መነሻ ዋጋዉን መሰረት በማድረግ በጨረታ ላይ ለቀረበ
አንድ ካሬ ሜትር ቦታ የሰጠዉ እና ጨረታዉን ያሸነፈበት ከፍተኛ የሊዝ ወይም ኪራይ ዋጋ ነዉ፡፡
18. “የጨረታ ከፍተኛ ዋጋ” ማለት በአንድ የጨረታ ሂደት ለአንድ ቦታ ከተወዳዳሪዎች ለቦታዉ የተሰጠ
ከፍተኛ የመሬት ሊዝ ወይም ኪራይ ዋጋ ሆኖ አሸናፊው መሬቱን ተረክቦ ውል የተፈራረመበት ዋጋ
ነው፡፡
19. “የኪራይ መነሻ ዋጋ” ማለት በሊዝ ከተሞች በሚገኙ ነባር ይዞታዎች እና ወደ ሊዝ ስርዓት ባልገቡ
ከተሞች ላይ ለአንድ ዓመት ተነጥሎ የሚተመን በካሬ ሜትር የቦታ ስፋት ታሳቢ የሚደረግ የኪራይ
ጨረታ መነሻ ዋጋ ነው፡፡
20. “በምደባ የተላለፈ ይዞታ ዓመታዊ የቦታ ኪራይ ዋጋ” ማለት ለአገልግሎት ዓይነቱ ለካሬ ሜትር
የተቀመጠው የኪራይ መነሻ ዋጋ ሲባዛ በቦታው ጠቅላላ ስፋት ይሆናል፡፡
21. “በጨረታ መሰረት የተላለፈ ይዞታ ዓመታዊ የኪራይ ክፍያ ” ማለት የቦታው ጠቅላላ ስፋት
(ካ.ሜ) ሲባዛ ቦታው በጨረታ ለካሬ ሜትር የተላለፈበት ዋጋ ነው፡፡
22. ማንኛውም በወንድ ጾታ የተገለጸው የሴትንም ይጨምራል፡፡

3. የተፈጻሚነት ወሰን
ይህ መመሪያ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ውስጥ የሊዝ ወይም ኪራይ መነሻ ዋጋና የቦታ ደረጃ
በተወሰነላቸው እና በቀጣይም በሚወሰንላቸው ሁሉም የክልሉ ከተሞች ላይ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡

3
ክፍል ሁለት

የከተማ ቦታ ሊዝ ወይም ኪራይ መሰረታዊ ድንጋጌዎች

4. የሊዝ ወይም ኪራይ መነሻ ዋጋን ወቅታዊ የማድረግ መርሆዎች


1. የከተማ መሬት ልማትና ማኔጅመንት ፖሊሲና ስትራቴጅዎች እንዲሁም የአዋጁንና ደንቡን
ተግባራዊነት የሚያረጋግጥ መሆን ይኖርበታል፡፡
2. የከተሞችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ የእድገት ደረጃ መሰረት ያደረገና የነዋሪዎችን ፍትሃዊ
ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ መሆን አለበት፡፡
3. በደንቡ አንቀጽ 29 ንዑስ አንቀጽ 2 በተገለፀው መሰረት ለመሬት ዝግጅት ሲባል የተፈፀመ
የካሳ ክፍያ፣የመሰረተ ልማት ዝርጋታ፣የቦታ ዝግጅት እና ሌሎች አስተዳደራዊ ወጭዎችን
መሰረት ያደረገ መሆን አለበት፡፡
4. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ ከተሞች መሬትን ለማዘጋጀት
የሚያወጡትን ወጭ መሸፈን የሚያስችል ገቢ የሚያስገኝ መሆን አለበት፡፡

5. የከተሞች ፈርጅ አወሳሰንና የከተማ ቦታ ደረጃ አሰጣጥ

1. የከተሞች ፈርጅ አወሳሰንና ደረጃ ሽግግር በደንብ ቁጥር 65/2001 መሰረት የሚወሰን
ይሆናል፡፡
2. የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 አገላለጽ እንደተጠበቀ ሆኖ ለከተማ ቦታ ደረጃ አሰጣጥና
ለሊዝ መነሻ ዋጋ ሲባል የክልሉ ከተሞች ከደረጃ 1 እስከ 6 ድረስ ተለይተው
ተመድበዋል፡፡ዝርዝሩን በዚህ መመሪያ አባሪ-3 ላይ መመልከት ይቻላል፡፡
3. የከተማ ፈርጅ ደረጃ ወይም ስያሜ ሽግግር የሚያደርጉ ከተሞች ሽግግር ላደረጉበት የከተማ ፈርጅ
የተቀመጠውን የከተማና ቦታ ደረጃ እንዲሁም የሊዝ ወይም ኪራይ መነሻ ዋጋ በመጠቀም
ተግባራዊ ያደርጋሉ፡፡

6. የሊዝ ዘመን

1. የክልሉ ከተሞች በአዋጁ አንቀጽ 18 ንዑስ አንቀጽ 1 እና በደንቡ አንቀጽ 49 ስር በተመለከቱት


ድንጋጌዎች መሰረት ተፈፃሚ ያደርጋሉ፡፡
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ በሊዝ ስርዓት በማይተዳደሩ ከተሞች
በጨረታና በምደባ ለተጠቃሚ የሚተላለፉ ቦታዎች ከተሞቹ ወደ ሊዝ ስርዓት እስከሚገቡ ድረስ
ወይም ይዞታዎቹ ወደ ሊዝ ስሪት እስካልተሸጋገሩ ድረስ የጊዜ ገደብ አይኖራቸውም፡፡

4
7. የከተሞች የሊዝ ሽግግር
1. የክልሉ ሁሉም ከተሞች የሊዝ ሽግግር መርሀ ግብር በክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት በሚጸድቀው የድርጊት
መርሀ ግብር መሰረት በአዋጁ አንቀጽ 5 ንዑስ አንቀጽ 4 ላይ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ተፈጻሚ
የሚያደርጉ ይሆናል፡፡
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ ወደ ሊዝ ስርዓት ያልገቡ ከተሞች ወደ ሊዝ
እስከሚሸጋገሩ ድረስ በዚህ መመሪያ ላይ በቦታ ደረጃና በአገልግሎት ዓይነት የተቀመጠውን የቦታ ኪራይ
ዋጋ የሚጠቀሙ ይሆናል፡፡
3. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 2 የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ ከተሞቹ ወደሊዝ ስርዓት ሲሸጋገሩ በዚህ
መመሪያ በከተማና ቦታ ደረጃ የተቀመጠውን የሊዝ መነሻ ዋጋ ተግባራዊ የሚያደርጉ ይሆናል፡፡

8. የሊዝና የቦታ ኪራይ ክፍያ አፈጻጸም


1. የሊዝ ክፍያ አፈጻጸም በደንቡ አንቀጽ 32 እና ደንቡን ለማስፈፀም በወጣው የሊዝ የአፈጻጸም መመሪያ
ቁጥር 1/2005 አንቀጽ 42 እና 43 መሰረት የሚፈጸም ይሆናል፡፡
2. በአዋጁ እና ደንቡ የችሮታ ጊዜ ለተፈቀደላቸው ዘርፎች ዓመታዊና የሊዝ ወለድ ክፍያ የሚጀምረው
የችሮታ ጊዜው ከተጠናቀቀ በኋላ ይሆናል፡፡
3. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 2 የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ ግለሰቦች ወይም ድርጅቶች የችሮታ ጊዜ
ወስደው ወይም ለመውሰድ ፈቃደኛ ባለመሆን በችሮታ ጊዜው ውስጥ ክፍያ መክፈል ከጀመሩ ወለድ
የሚታሰብ ይሆናል፡፡
4. በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ 2 እና 3 የተጠቀሰው ቢኖርም በኪራይ ስሪት የተያዘ ቦታ ክፍያ በየዓመቱ
የሚፈጸም በመሆኑ ወለድ የሚታሰብበት አይሆንም፡፡
5. በአዋጁ አንቀጽ 20 ንዑስ አንቀጽ 5 እና 6 እንዲሁም በደንቡ አንቀጽ 33 መሰረት ወቅቱን ጠብቆ ዓመታዊ
የሊዝ ክፍያውን የማይፈጽም ባለይዞታ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በዘገዩ የብድር ክፍያዎች ላይ በሚጥለው
የቅጣት ተመን መሰረት ቅጣት የሚከፍል ይሆናል፡፡
6. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 4 የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ ዓመታዊ የቦታ ኪራያቸውን በወቅቱ
የማይከፍሉ ተጠቃሚዎች የአመታዊ ክፍያውን 25 በመቶ ቅጣት በየአመቱ የሚከፍሉ ይሆናል፡፡
7. አዋጁ ተግባራዊ ከሆነ በኋላ በጨረታ ለተጠቃሚዎች የተላለፉ ቦታዎች ዓመታዊ የቦታ ኪራይ ክፍያ በዚህ
መመሪያ ከተሻሻለው የዋጋ ተመን በታች ከሆነ የኪራይ ውሉ እንዲቀየር በማድረግ በዚህ መመሪያ
በተቀመጠው የኪራይ ተመን መሰረት እንዲከፍሉ ይደረጋል፡፡

9. የሊዝ ወይም ቦታ ኪራይ መነሻ ዋጋን ስለማሻሻል


1. በደንቡ አንቀጽ 30 ንዑስ አንቀጽ 2 ላይ በተደነገገው መሰረት የሊዝ መነሻ ዋጋ ወቅታዊነቱ ተጠብቆ እንዲሄድ
ቢያንስ በየሁለት ዓመቱ የሚሻሻል ይሆናል፡፡

5
2. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ የማይሻሻልበት ሁኔታ ሲያጋጥም ወይም
አስፈላጊና አሳማኝ ባልሆነበት ጊዜ በስራ ላይ ያለው መመሪያ አግባብ ያለው አካል ቀርቦ የመመሪያው
ተፈፃሚነት እንዲቀጥል ውሳኔ ማግኘት ይኖርበታል፡፡
3. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ የቦታ ኪራይ ዋጋ ማሻሻያ ጥናት ከአራት ዓመት
መብለጥ የለበትም፡፡
4. ሁሉም የከተማ አስተዳደሮች የሊዝና ቦታ ኪራይ መነሻ ዋጋ የማሻሻያ ጥናት በማጥናት ወይም በማስጠናት ጥናቱ
ለቢሮው ቀርቦ ከተገመገመ በኋላ በምክር ቤታቸው በኩል አስጸድቀው ተግባራዊ ማድረግ ይችላሉ፡፡
5. ለሁሉም ማዘጋጃ ቤትና ታዳጊ ከተሞች በዞን ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት መምሪያዎች በኩል የሊዝና ቦታ ኪራይ
መነሻ ዋጋ ማሻሻያ እየተጠና በቢሮው የሚፀድቅ ይሆናል፡፡

ክፍል ሶስት
የአስፈጻሚ አካላት ማንነት፣ ተግባር እና ኃላፊነት
10. የአስፈጻሚ አካላት ማንነት
የከተሞች የተሻሻለ የሊዝ እና የኪራይ መነሻ ዋጋ መመሪያን በተሟላ አኳኋን ተፈጻሚ ለማድረግ ከዚህ

የሚከተሉት አካላት ከፍተኛ ተግባራት እና ኃላፊነት አለባቸው፡፡

1. የኢንዱስትሪና ከተማ ልማት ቢሮ፣


2. የዞን ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት መምሪያዎች፣
3. የከተማ አስተዳደሮች እና
4. ማዘጋጃ ቤት ከተሞች፡፡

11. የቢሮው እና የዞን ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት መምሪያዎች ተግባርና ኃላፊነት


1. ቢሮው፡-
ሀ. በክልሉ የሚገኙ ከተሞችን የሊዝ ወይም የኪራይ መነሻ ዋጋ መመሪያ አፈጻጸምን በበላይነት ይመራል፤
ለ. የከተማ አስተዳደሮች የሊዝና ቦታ ኪራይ መነሻ ዋጋ የማሻሻያ ጥናት በማጥናት ወይም በማስጠናት
ያቀረቡለትን ጥናቶች በመገምገምና አስፈላጊውን ማስተካከያ በማድረግ በየምክር ቤቶቻቸው
እንዲያስጸድቁ እገዛ ያደርጋል፤
ሐ. በማዘጋጃ ቤትና ታዳጊ ከተሞች በየዞን ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት መምሪያዎች ተጠንቶ የቀረበለትን
የሊዝና ቦታ ኪራይ መነሻ ዋጋ ገምግሞ የማጽደቅ፤
መ. የሚመለከታቸውን አካላት በአፈፃፀም መመሪያው ላይ ግልፅ ግንዛቤ የማስያዝ፣ የመመሪያውን ተግባራዊነት
የመከታተልና የመደገፍ፤
ሠ. በመመሪያው አፈፃፀም ዙሪያ ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት መፍትሔ የማስቀመጥ እና

6
ረ. የከተማ ቦታ ዋጋ ወቅታዊነት እንዲረጋገጥ ተገቢውን የአሰራርና የአቅም ግንባታ ስራ የማከናወን
ተግባርና ኃላፊነቶች ይኖርበታል፡፡
2. የኢንዱስትሪና ከተማ ልማት መምሪያዎች፡-

ሀ. የከተሞቻቸውን የሊዝና የኪራይ መነሻ ዋጋ ማሻሻያ ለማድረግ በጋራ ጥናት የማድረግ፤


ለ. በመምሪያዎቻቸው የተጠናው የሊዝ ወይም የኪራይ መነሻ ዋጋ ተገምግሞና አስፈላጊው ማስተካከያ
ተደርጎበት በቢሮው በኩል እንዲፀድቅ የማድረግ፤
ሐ. የሚመለከታቸውን አካላት በአፈፃፀም መመሪያው ላይ ግልፅ ግንዛቤ የማስያዝ ፣የመመሪያውን
ተግባራዊነት የመከታተልና የመደገፍ፤
መ. በመመሪያው አፈፃፀም ዙሪያ ያጋጠሙ ችግሮችን በመለየት መፍትሔ የማስቀመጥ እና
ሠ. የከተማ ቦታ ዋጋ ወቅታዊነት እንዲረጋገጥ ተገቢውን የአሰራርና የአቅም ግንባታ ስራ የማከናወን
ተግባርና ኃላፊነቶች ይኖርባቸዋል፡፡
3. ከተማ አስተዳደርና ማዘጋጃ ቤት ከተሞች፡-
ሀ. ለነዋሪዎቻቸው የተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎችንና መድረኮችን በመጠቀም በተሻሻለው የሊዝ ወይም
የኪራይ መነሻ ዋጋ መመሪያ ላይ ለህዝብ ይፋ የማድረግና ግንዛቤ የመፍጠር፤
ለ. በከተማው ውስጥ የሚገኙ የሊዝና ነባር ይዞታዎችን ብዛት ለይቶ በተደራጀ ሁኔታ ፋይሎችን
የመያዝና ለቦታ ሊዝ ወይም ኪራይ ክፍያ ሰብሳቢ አካላት በማሳወቅ መረጃ የመስጠት፤
ሐ. የሊዝ ወይም የኪራይ ይዞታዎች ክፍያ አሰባሰብን የመከታተል፣ የመደገፍ እና ወቅቱን ጠብቀው
በማይከፍሉት ላይ እርምጃ የመውሰድ እና
መ. የከተማ ቦታ ገቢ አሰባሰብን በተመለከተ ከከተማውና ወረዳው ገቢዎች ጽ/ቤት ጋርበቅንጅት
የመስራት ተግባርና ሀላፊነት ይኖርባቸዋል፡፡

ክፍል አራት
ልዩ ልዩ ድንጋጌዎች
12. ወደ ሶስተኛ ወገን የሚተላለፉ ይዞታዎችን በተመለከተ
1. ይዞታው ቀደም ሲል የሊዝ ይዞታ ከሆነ ወደ ሶስተኛ ወገን ሲተላለፍ ሁለተኛ ወደሊዝ ስለማይገባ ይዞታው
የተላለፈለት ሰው የአገልግሎት እና ሌሎች የሚጠበቅበትን ክፍያ የሚከፍል ሆኖ የአገልግሎት ለውጥ እስካልተደረገ
ድረስ ቀደም ሲል ይዞታው ወደ ሶስተኛ ወገን ከመተላለፉ በፊት ሲከፈል የነበረውን አመታዊ የሊዝ ክፍያ የሚከፍል
ይሆናል፡፡

7
2. በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ 1 ላይ የተጠቀሰው እንደተጠበቀ ሆኖ የሊዝ ይዞታው ወደ ሶስተኛ ወገን
ሲተላለፍ የአገልግሎት ለውጥ ካለ አመታዊ የሊዝ ክፍያው የቦታው ስፋት ሲባዛ የአገልግሎቱ አካባቢያዊ
የጨረታ ዋጋ ሲካፈል በሊዝ ውሉ ላይ የተቀመጠው ቀሪ የሊዝ ክፍያ ማጠናቀቂያ ጊዜ ይሆናል፡፡
3. በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ 1 የተጠቀሰው ቢኖርም ነባር ይዞታ ከውርስ በስተቀር ወደ ሶስተኛ ወገን ሲተላለፍ
ቀደም ሲል ሲከፈል የነበረው ዓመታዊ የቦታ ኪራይ ቀሪ ሆኖ ወቅታዊ የቦታው የሊዝ መነሻ ዋጋ በቦታዉ ጠቅላላ
ስፋት ከተባዛ በኋላ የሚገኘዉ የገንዘብ መጠን በሊዝ ውሉ ላይ በተቀመጠው የመክፈያ ጊዜ ተካፍሎ የሚገኘው
ውጤት በየዓመቱ ሚከፈል ይሆናል፡፡
4. በዚህ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ 3 መሰረት የሊዝ ውል የፈፀመው ባለይዞታ የሊዝ ቅድሚያ ክፍያ እንዲፈጽም
ባይገደድም ይህንኑ የመክፈል ፍላጎት ካለው ከጠቅላላው የሊዝ ክፍያ የሚታሰብ ቅድሚያ ክፍያ አግባብ ላለው አካል
የመፈጸም መብት ይኖረዋል፡፡
5. በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 4 መሰረት ባለመብቱ የቅድሚያ ክፍያ በመፈጸም የችሮታ ጊዜ እንዲሰጠው ጥያቄውን
በጽሁፍ ካቀረበ እንደ አገልግሎቱ አይነት የችሮታ ጊዜ የሚፈቀድለት ይሆናል፡፡

13. የሊዝ ወይም ኪራይ ወለድን በተመለከተ


1. “የሊዝ ወለድ” ማለት በየዓመቱ በሚከፈለው ቀሪ የሊዝ ክፍያ ላይ የሚታሰብ ሆኖ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
የማበደሪያ ተመን መሠረት በየአመቱ ሚከፈል ይሆናል፡፡
2. የዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 1 ድንጋጌ ቢኖርም ነባር የከተማ ይዞታዎች ወይም ወደ ሊዝ ባልገቡ ከተሞች ላይ
ለሚከፈል የኪራይ ክፍያ ወለድ የሚታሰብ አይሆንም፡፡

14. የሊዝ ክፍያ ማጠናቀቂያ ጊዜ የሌለው ውል ባጋጠመ ጊዜ ስለሚወሰድ


እርምጃ

በሊዝ ውሉ ላይ የሊዝ ክፍያ ማጠናቀቂያ ጊዜው ያልተቀመጠበት ሁኔታ ሲያጋጥም በደንቡ አንቀጽ 32 ንዑስ
አንቀጽ 3 ላይ ለአገልግሎቱ የተቀመጠው የክፍያ ማጠናቀቂያ ጊዜ ተፈፃሚ የሚደረግ ይሆናል፡፡

15. የመተባበር ግዴታ


1. ማንኛውም ሰው ይህንን መመሪያ ለማስፈፀም በሚደረግ እንቅስቃሴ ትብብር እንዲያደርግ ሲጠየቅ የመተባበር
ግዴታ አለበት፡፡
2. በዚህ መመሪያ ውስጥ የተጠቀሱት አስፈፃሚ አካላት ግዴታቸውን ካልተወጡ አግባብ ባለው ህግ ተጠያቂ
ይሆናሉ ፡፡

8
16. የተሻሩና ተፈጻሚነት የማይኖራቸው ህጎች
1. የሊዝ መነሻ ዋጋ መወሰኛ መመሪያ ቁጥር 23/1998 እና ነባር የከተማ ቦታ የኪራይ
ተመን መወሰኛ መመሪያ ቁጥር 24/1998 በዚህ መመሪያ ተሽረዋል፣
2. ከዚህ መመሪያ ጋር የሚቃረን ማናቸውም ሌላ መመሪያ ወይም የተለመደ አሰራር በዚህ መመሪያ ውስጥ
በተሸፈኑ ጉዳዮች ላይ ተፈፃሚነት አይኖረውም፡፡

17. መመሪያው የሚፀናበት ጊዜ

ይህ መመሪያ በኢንዱስተሪና ከተማ ልማት ቢሮ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ የጸና ይሆናል፡፡

9
አባሪ-1 የተሻሻለው የክልሉ ከተሞች የሊዝ መነሻ ዋጋ፡-
ሰንጠረዥ 4፡- የከተማ ቦታ የሊዝ መነሻ ዋጋ በ አ ገ ል ግ ሎ ት አ ይ ነ ት ፣ በከተማና በቦታ ደረጃ፣
( ብር/ካሬ ሜትር)

የሊዝ መነሻ ዋጋ በአገልግሎት አይነት


(ብር × 1 ካ.ሜ)
መኖርያ ንግድ ማህበራዊ ኢንዱስትሪ በልዩ ጨረታ የመንግስት ቢሮዎችና
ለሚስተናገዱ የልማት
ቦታዎች በጨረታ ደርጅቶች፣የበጎ
ለሚተላለፍ አድራጎት
የከተማ
ተ.ቁ የቦታ ደረጃ ድርጅቶች/NGOs፣የ
ደረጃ የከተማ ግብርና
ሀይማኖት ተቋማት

1 1 1 525 1280 760 560 585 200

2 425 1005 690.7 476 463 190


3 325 795 621.4 392 314 180
4 225 615 552.1 308 184 170
5 115 455 482.8 224 85 160
2 2 1 308 893 552 476 330 190
2 262 758 482.7 404 183 180
3 222 665 413.4 332 150 170
4 188 614 344.1 260 89 160

0
5 160 605 275 188 65 150
3 3 1 222 758 351 384 204 180
2 189 665 298 327 138 170
3 161 614 253 270 84 160
4 138 605 208 213 65 150
5 120 590 163 156 45 140
4 4 1 189 665 298 327 115 160
2 161 614 253 270 95 150
3 138 605 208 213 61 140
4 120 590 163 156 50 130
5 5 1 161 614 253 270 95 140
2 138 605 208 213 61 130
3 120 590 163 156 50 120
6 6 1 138 605 208 213 61 130
2 120 590 163 156 50 100

ማሳሰቢያ፡-ለኢንዱስትሪ የቦታ አገልግሎት የተቀመጠው የሊዝ መነሻ ዋጋ በኢንዱስትሪ መንደርነት ለተከለለ/ለሚከለሉ/ አገልግሎት ውጭ ላሉ ዘርፎች
የሚያገለግል ነው፡፡

አባሪ-2. የተሻሻለው የኪራይ ተመን፡-

1
ሰንጠረዥ 5፡- የከተማ ቦታ የኪራይ ተመን መነሻ ዋጋ በ አ ገ ል ግ ሎ ት አ ይ ነ ት ፣ በከተማና በቦታ ደረጃ
( ብር/ካሬ ሜትር)

የኪራይ መነሻ ዋጋ በአገልግሎት አይነት


(ብር × 1 ካ.ሜ)
በጨረታ ለሚተላለፍ የመንግስት ቢሮዎችና
የልማት ደርጅቶች፣የበጎ
የከተማ መኖርያ ንግድ ማህበራዊ ኢንዱስትሪ የከተማ ግብርና
ተ.ቁ የቦታ ደረጃ አድራጎት
ደረጃ
ድርጅቶች/NGOs፣የሀይ
ማኖት ተቋማት

1 1 1 1.45 3.2 2.7 1.89

2 1.04 2.7 2.2 1.69


3 0.82 2.2 1.7 1.49
4 0.79 1.7 1.2 1.29
5 0.65 1.2 0.7 1.09
2 2 1 1.04 2.7 2.2 1.69
2 0.82 2.2 1.7 1.49
3 0.79 1.7 1.2 1.29
4 0.67 1.20 0.7 1.09
5 0.55 0.95 0.45 0.89
3 3 1 0.82 2.2 1.7 1.49

2
2 0.79 1.7 1.2 1.29
3 0.67 1.2 0.7 1.09
4 0.55 0.95 0.45 0.89
5 0.49 0.825 0.325 0.69
4 4 1 0.79 1.7 1.2 1.29
2 0.67 1.2 0.7 1.09
3 0.55 0.95 0.45 0.89
4 0.49 0.825 0.325 0.69
5 5 1 0.67 1.2 0.7 1.09

2 0.55 0.95 0.45 0.89


3 0.49 0.825 0.325 0.69
6 6 1 0.55 0.95 0.45 0.89
2 0.49 0.825 0.325 0.69
ማሳሰቢያ፡-ለኢንዱስትሪ የቦታ አገልግሎት የተቀመጠው የሊዝ መነሻ ዋጋ በኢንዱስትሪ መንደርነት ለተከለለ/ለሚከለሉ/ አገልግሎት ውጭ ላሉ ዘርፎች
የሚያገለግል ነው፡፡

3
አባሪ-3. የክልሉ ከተሞች ዝርዝር በዞንና በከተሞች ደረጃ
ተ.ቁ የከተማው ስም ከተማው ለቦታ ምደባ የተሰጠ የከተማ ደረጃ ከተማው ምርመራ
የሚገኝበት ዞን የሚኖረው ቦታ
ስም ደረጃ ፈርጅ ደረጃ ብዛት

1 ባህርዳር ምዕ/ጎጃም 1 ሜትሮፖሊታን ከተማ 5

2 ደሴ ደ/ወሎ 1 ሜትሮ ፖሊታን ከተማ 5

3 ጎንደር ሰ/ጎንደር 1 ሜትሮ ፖሊታን ከተማ 5

4 ደ/ማርቆስ ምስ/ጎጃም 2 መካከለኛ ከተማ 5

5 ደ/ብርሃን ሰ/ሸዋ 2 መካከለኛ ከተማ 5

6 ኮምቦልቻ ደ/ወሎ 2 መካከለኛ ከተማ 5

7 ወልዲያ ሰ/ወሎ 2 መካከለኛ ከተማ 5

8 ደ/ታቦር ደ/ጎንደር 2 መካከለኛ ከተማ 5

9 ላሊበላ ሰ/ወሎ 2 መካከለኛ ከተማ 5

10 ደባርቅ ሰ/ጎንደር 2 መካከለኛ ከተማ 5

11 ፍ/ሰላም ምዕ/ጎጃም 2 አነስተኛ ከተማ 5

12 ሰቆጣ ዋግህምራ 2 አነስተኛ ከተማ 5

13 እንጂባራ አዊ 2 አነስተኛ ከተማ 5

14 ከሚሴ ኦሮሚያ 2 አነስተኛ ከተማ 5

15 ሞጣ 3 አነስተኛ ከተማ 5

16 ዳንግላ 3 አነስተኛ ከተማ 5

17 ቻግኒ 3 አነስተኛ ከተማ 5

18 ቡሬ 3 አነስተኛ ከተማ 5

4
19 ቆቦ 3 አነስተኛ ከተማ 5

20 ወረታ 3 አነስተኛ ከተማ 5

21 አዲስ ዘመን 3 አነስተኛ ከተማ 5

22 ደጀን 3 አነስተኛ ከተማ 5

23 ባቲ 3 አነስተኛ ከተማ 5

24 ሃይቅ 3 አነስተኛ ከተማ 5

25 መሃልሜዳ 3 አነስተኛ ከተማ 5

26 ገንዳ ውሃ 3 አነስተኛ ከተማ 5

27 አይከል 3 አነስተኛ ከተማ 5

28 መርሣ 3 አነስተኛ ከተማ 5

29 ነፋስ መውጫ 3 አነስተኛ ከተማ 5

30 መካነ-እየሱስ 3 አነስተኛ ከተማ 5

31 ሸዋ ሮቢት 3 አነስተኛ ከተማ 5

32 አጣየ 3 አነስተኛ ከተማ 5

33 አለም ከተማ 3 አነስተኛ ከተማ 5

34 መራዊ 3 አነስተኛ ከተማ 5

35 ደንበጫ 3 አነስተኛ ከተማ 5

36 አዴት 3 አነስተኛ ከተማ 5

37 ከሚሴ 3 አነስተኛ ከተማ 5

38 መካነ-ሰላም 3 አነስተኛ ከተማ 5

39 አዲአርቃይ ሰ/ጎንደር 3 መሪ ማ/ቤት 4

5
40 መካነ ብርሃን “ 3 መሪ ማ/ቤት 4

41 ዳባት “ 3 መሪ ማ/ቤት 4

42 አብርሀ ጃራ “ 3 መሪ ማ/ቤት 4

43 አብደራፊ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

44 ትክልድንጋይ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

45 አምባ ጊዮርጊስ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

46 ማክሰኝት “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

47 ቆላ ድባ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

48 መተ/ዩሀንስ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

49 ሻሁራ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

50 አርባያ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

51 ዙሀሙሲት “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

52 ሳንጃ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

53 ደልጊ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4 15

54 እብናት ደ/ጎንደር “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

55 ክምር ድንጋይ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

56 አርብ ገበያ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

57 ወገዳ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

58 ሀሙሲት “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

59 አንበሳሜ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

60 አንዳ ቤት “ 4 መሪ ማ/ቤት 4 7

6
61 ሙጃ ሰ/ወሎ 4 መሪ ማ/ቤት 4

62 ፍላቂት ገረገራ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

63 ኮን “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

64 ሃራ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

65 ኩርባ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

66 አይና “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

67 ጋሸና “ 4 መሪ ማ/ቤት 4 7

68 ሳልመኔ ደ/ ወሎ 4 መሪ ማ/ቤት 4

69 ሃርቡ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

70 ኩታበር “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

71 ውጫሌ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

72 ቢስቲማ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

73 ደጎሎ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

74 ወረኢሉ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

75 መዲና “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

76 አቀስታ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

77 አጅባር “ 4 መሪ ማ/ቤት 4
78 ማሻ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4
79 ማህደረ ሰላም “ 4 መሪ ማ/ቤት 4
(ወግዲ)
80 ከላላ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4
81 ሳይንት አጅባር “ 4 መሪ ማ/ቤት 4
82 ወገል ጤና “ 4 መሪ ማ/ቤት 4
83 ወይንአምባ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

84 ደንሳ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4 17

7
85 ጫጫ ሰ/ሸዋ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

86 ጊና አገር “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

87 ጎረቤላ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

88 ሾላ ገበያ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

89 መተህብላ 4 መሪ ማ/ቤት 4

90 መኮይ 4 መሪ ማ/ቤት 4

91 ማጀቴ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

92 ራቤል “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

93 ሞላሌ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

94 እነዋሪ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

95 አረርቲ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

96 መራኛ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

97 ደነባ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

98 ደብረ ሲና “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

99 ሰላድንጋይ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

100 ለሚ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

101 ዘመሮ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

102 ወገሬ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4 18

103 አማኑኤል ምስ/ ጎጃም 4 መሪ ማ/ቤት 4

104 ኤልያስ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

8
105 ዲጐጽዮን “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

106 ሎማሜ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

107 የጁቤ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

108 ቁይ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

109 ደብረወርቅ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

110 ግንደወይን “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

111 መርጡ ለማሪያም “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

112 የዕጽ ውሃ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

113 ሮብ ገበያ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

114 አምበር “ 4 መሪ ማ/ቤት 4 12

115 ዘጌ ምዕ/ጎጃም 4 መሪ ማ/ቤት 4

116 ዱርቤቴ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

117 ግሽ አባይ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

118 ቁጭ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

119 ሽንዲ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

120 ጅጋ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

121 ገብዘማሪያም “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

122 ፈረስ ቤት “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

123 አዲስ አለም “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

124 ሊበን “ 4 መሪ ማ/ቤት 4 10

125 አምደወርቅ ዋግ ኸምራ 4 መሪ ማ/ቤት 4

9
126 ፅፅቃ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

127 ሽፍሩ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

128 ኒሯቅ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

129 መሽሃ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

130 አስከተማ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4 6

131 ቅላጅ አዊ 4 መሪ ማ/ቤት 4

132 ግምጃ ቤት “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

133 አዲስቅዳም “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

134 ቲሊሊ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

135 ፈንድቃ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4 5

136 ጨፍሮቢት ኦሮሚያ 4 መሪ ማ/ቤት 4

137 ሰንበቴ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4

138 ቦራ “ 4 መሪ ማ/ቤት 4 3

139 ጉኋላ ሰ/ጎንደር 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

140 ጯሂት “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

141 ጎርጎራ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

142 ኮኪት “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

143 ቱመት “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

144 ሽንፍ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

145 መሻህ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

146 ዛሪማ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

10
147 ገለጉ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

148 ነጋዴ ባህር “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

149 ሰራባ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

150 ቅራቅር “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

151 ሶሮቃ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

152 አሸሬ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

153 ማሰሮ ደንብ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

154 ፀዳ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

155 እንፍራዝ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

156 አፀደ ማሪያም “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

157 ድኩሉ አርባ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

158 ጨው ድባ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

159 ገደብየ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

160 አይምባ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

161 ወቅን “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 23

162 ቆማ ደ/ጎንደር 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

163 ልጫ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

164 አርብ ገበያ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

165 ጎብጎብ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

166 ሣሊ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

167 ጃራገዶ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

11
168 አዳዳ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

169 ሙጃ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

170 አለም በር “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

171 ይፋግ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

172 አምቦ ሜዳ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

173 ጋሳይ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3 12

174 ሮቢት ሰ/ ወሎ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

175 ጎብዩ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3


176 ውርጌሳ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

177 ሲሪንቃ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

178 ጊራና “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

179 ደብረ ፀሃይ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3 6


(ኩል መስክ)
180 ቦኮክሳ ደ/ ወሎ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

181 ተንታ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3 2

182 ኮቱ ሰ/ ሸዋ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

183 አልዩ አምባ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

184 ካራቆሬ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

185 ጀውሃ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

186 ፌጥራ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

187 ጅሁር “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

188 ባልጪ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

189 መዘዞ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3 8

12
190 ወይን ውሃ ምስ/ ጎጃም 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

191 የትመን “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

192 ዲማ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

193 ፈለገ ብርሃን “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

194 ቀራንዮ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

195 ሰዴ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

196 ደብረ እየሱስ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3 7

197 ጢስ አባይ ምዕ/ ጎጃም 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

198 ወተት አባይ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

199 ማንኩሳ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

200 ዋድ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

201 ቁንዝላ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

202 ይሰማላ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

203 ገነት አቦ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3 7

204 ፃታ ዋግ ኸምራ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

205 ሐሙሲት “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

206 ከሳ አዊ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

207 ቅዳማጃ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

208 መንታ ውሃ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

209 ጥርጊ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

210 አዘና “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

13
211 እሁዲት “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

212 ጫራ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

213 ጊሳ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

214 ፋግታ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3 9

215 ጭረቲ ኦሮሚያ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

216 በጤ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

217 ባለጪ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

218 ወለዲ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3

219 ሀረዋ “ 5 ንኡስ ማዘጋጃ ቤት 3 5

220 መቃ ሰሜን 6 ታዳጊ ከተማ 3


ጎንደር
221 ቴዎድሮስ ከተማ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

222 ዱባባ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

223 አርባ ፀጓር “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

224 ደጎማ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

225 ድልይብዛ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

226 ደንገል በር “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

227 ሙሴ ባምብ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

228 ወይኖች “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

229 ሮቢት “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

230 ጫንጨቅ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

231 በሆና “ 6 ታዳጊ ከተማ

14
232 ጭን ድባ “ 6 ታዳጊ ከተማ

233 እርጎየ “ 6 ታዳጊ ከተማ

234 አዲስ አለም “ 6 ታዳጊ ከተማ 15

235 ጅብ አስራ ደቡበ ጎንደር 6 ታዳጊ ከተማ

236 አጋጥ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

237 ቅዳሜ ገበያ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

238 ማዕድ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

239 ቤተልሔም “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

240 ኤፍራታ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

241 አቄቶ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

242 ቆጥ መንደር “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

243 የኳሳ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

244 ምክሬ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

245 ማክሰኝት “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

246 ፀደይ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

247 ዚቦ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

248 አጃ ፋሲለደስ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

249 ሰላማያ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

250 ቋሊላ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

251 አጊላ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

252 ኒቋራ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

15
253 ገላማጠቢያ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

254 ወለላ ባህር “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

255 ሃገረ ገነት “ 6 ታዳጊ ከተማ 21

256 ብልባላ ሰሜን ወሎ 6 ታዳጊ ከተማ

257 ተኩለሽ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

258 ቦረን “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

259 ቃሊም “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

260 አራዶም 6 ታዳጊ ከተማ

261 በቅሎ ማነቂያ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

262 አግሪት “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

263 ደብረ ዘቢጥ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

264 ሀሙሲት “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

265 ስታይሽ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

266 ድፕኮ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

267 አርቢት “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

268 ሻሪያ ገነት “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

269 ሣንቃ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

270 ዶሮግብር “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

271 አሁንተገኝ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2 16

272 ጉጉፍቱ ደቡብ ወሎ 6 ታዳጊ ከተማ 2

273 ደጋጋ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

16
274 ጦሳ ፈላና “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

275 ገርባ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

276 ደጋን “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

277 አንቻሮ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

278 አዳሜበል “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

279 አዳሜ ቀጠጥያ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

280 አላንሻ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

281 ቁንዴ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

282 ሙሜድ ገትራ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

283 ልጎት “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

284 አባቦራ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

285 ካታሪ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

286 ቢላው “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

887 ባሶሚሌ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

288 ሱሉላ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

289 ጦሳ በሉማ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

290 ሮቢት “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

291 ጀርሳ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

292 ሳህ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

293 ጉዴሳ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

294 ዳዮ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

17
295 ፍጅ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

296 ሸለፋፍ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

297 ቀይ አፈር “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

298 ካቤ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

299 ሰኞ ገበያ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

300 ገላቴ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

301 ቱሉአውሉያ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

302 ጭሮ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

303 አምባማሪያም “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

304 ለሰበር “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

305 የኮሶ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

306 ገዙራ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

307 አደጉየ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

308 ደብረዘይት “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

309 ባከፍታ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

310 ጎርጎጅ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

311 አብዮ ጎርባ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

312 ለሚ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

313 ሰዬ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

314 ልጓማ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

315 ቲርቲር “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

18
316 አቤት ውሃ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

317 ደገር “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

318 እዋ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

319 የጎሌ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

320 አባፍሬት “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

321 ወርቅ ማውጫ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

322 አለገታ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

323 ቆተት “ 6 ታዳጊ ከተማ 2 52

324 ጐዶ በረት ሰሜን ሸዋ 6 ታዳጊ ከተማ 2

325 ጐርጐ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

326 አባያ አጥር “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

327 የለን “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

328 አምቦ ውሃ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

329 ሲያደብርና ዋዩ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

330 ሬማ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

331 አርማኒያ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

332 ሳሲት “ 6 ታዳጊ ከተማ 2 9

333 ሃሙሲት ምስ/ጎጃም 6 ታዳጊ ከተማ 2

334 ደጋ ሰኝን “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

335 ግራ ቅዳምን “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

336 ጎይ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

19
337 ጃቢ ገነት “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

338 ደጅባ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

339 ዋብር “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

340 ወጀል “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

341 ኮርክ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

342 የላምገጅ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

343 የትኖራ /ጢቅ/ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

344 የቀቢሃና “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

345 መንግስቶ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

346 ወይራ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

347 ገደብ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

348 መጣያ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

349 ተንጉማ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

350 ጌትስማኔ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

351 ጨሞ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

352 ገንቦሬ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

353 እነጉዴ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

354 እነጎሽ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

355 ሀገረ ሰላም “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

356 አስተሪዮ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

357 ከርነዋሪ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

20
358 ዲቦ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

359 ሰኞ ገበያ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

360 መርገጭ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

361 ፍንድቅ ብየ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

362 ጃማ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

363 ጉዳልማ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

364 የቦቅላ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

365 ቸርተከል “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

366 ፈንድቃ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

367 አባሊባኖር “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

368 ማይ አንገታም “ 6 ታዳጊ ከተማ 2 36

369 መሸንቲ ምዕ/ጎጃም 6 ታዳጊ ከተማ 2

370 ቅንባባ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

371 ደብረ መዌ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

372 አግታ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

373 ብራቃታ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

374 ዳጊ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

375 ላሊበላ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

376 አዲስ አለም “ 6 ታዳጊ ከተማ 2


ጎንጅ
377 አሹዳ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

378 ጣህመ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

21
379 አጉት “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

380 ሰንቶም “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

381 ወገዳድ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

382 አዲስ አለም “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

383 የጨረቃ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

384 ገረገራ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

385 ዋሸራ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

386 ጭንባ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2 18

387 ፀመራ ዋግ 6 ታዳጊ ከተማ 2

388 “ 6 ታዳጊ ከተማ 2


ዛሮታ
389 ስሬል “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

390 ቀውዝባ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

391 ጭላ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2 5

392 ዲንካራ አዊ 6 ታዳጊ ከተማ 2

393 “ 6 ታዳጊ ከተማ 2


አካናጅፊ
394 “ 6 ታዳጊ ከተማ 2
ጉባላ
395 አምብቂ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

396 “ 6 ታዳጊ ከተማ 2


ይማሊ
397 “ 6 ታዳጊ ከተማ 2
አህቲ
398 “ 6 ታዳጊ ከተማ 2
ጆሞራ
399 አምበላ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

22
400 “ 6 ታዳጊ ከተማ 2
መሰላ
401 “ 6 ታዳጊ ከተማ 2
ችጓሊ
402 ደቅ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

403 “ 6 ታዳጊ ከተማ 2


ወርቅ
ሜዳ
404 ኮፕተሌ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

405 “ 6 ታዳጊ ከተማ 2


ማምቡሉ

406 “ 6 ታዳጊ ከተማ 2 15
ፊልፊል
407 ገረቢ ኦሮሚያ 6 ታዳጊ ከተማ 2

408 ጎዳ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

409 ሽክላ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2

410 ቱቼ “ 6 ታዳጊ ከተማ 2 4

23

You might also like