Download as pdf or txt
Download as pdf or txt
You are on page 1of 28

====እንዲሁም ሁሉ በደኅና ወደ ምድር ደረሱ። የሐዋ.ሥ.

27፡44====
======በነጋም ጊዜ ምድሩን አላወቁትም። =======
የቀጠለ……..
 መግቢያ
 ወንጌላዊ ቅዱስ ሉቃስ ስለ ወንጌል እስረኛ የሆነዉን የቅዱስ ጳዉሎስን ጉዞ በደንብ ገልጿል። ያሳያል።
 በጉዞው ምን እንደገጠማቸው፦
• የጳዉሎስን ምንነት
• የእሰረኞቹን
• የመሪዎቹን ሁኔታ በደንብ ገልጿል።
• እስረኖቹ በመቶ አለቃ በሚመሩ ወታደሮች ይጠበቁ ነበር።
• ቅዱስ ጳዉሎስ እንደ እስረኛ ሳይሆን እንደ የክርስቶስ ወንጌል ሰባኪ ነበር
• ጉዞው በመከራ የተመላ ቢሆንም፣ ወንጌልን ለማስተማር ጥሩ አጋጣሚ ነበር
ጉዞው ፦
 ከቂሳርያ ወደ ማይራ 1-5
 ከማይራ/ ሙራ/ ወደ መልካም ወደብ 6-8
 ከመልካም ወደብ ወደ ማልታ 9-44

========ይህንም በተናገረ ጊዜ ንጉሡና አገረ ገዢው በርኒቄም ከእነርሱም ጋር የተቀመጡት


ተነሡ፥ ፈቀቅ ብለውም እርስ በርሳቸው ተነጋገሩ። ========

 አግሪጳም ፊስጦስን ይህ ሰው ወደ ቄሳር ይግባኝ ባይል ነጻ ይወጣ ነበር አለው።


=========የዚህ ጉዞ ዋና ዓላማ አለው፦ ==በአይሁዶች ወንጌልን አልቀበል ባይነት፣ ለአረማዉያን
የእምነት በር ሊከፈት ወደ ነገስታቱ አደባባይ ወደ ሆነችው ሮም ወንጌልን ለመስበክ፣ ለክርስቶስ ምስክር
ለመሆን ነው። ========

 ዳግመኛም እንደ ፍርዱ እንዴት እንደ ፈረዱ ተመልከት፤ “አንተ ከራስህ ጋር ነህ” ካሉ በኋላ ለሞት
ብቻ ሳይሆን ለእስራትም ያልተገባ ነው ብለው ነጻ አወጡት፤ በእርግጥም ሊፈቱት ይወዱ ነበር።

 ሙሉ በሙሉ፣ ወደ ቄሳር ይግባኝ ባይል ኖሮ ይፈቱት ነበር።


 ጌታም "ከዓመፀኞች ጋር ተቆጥሯል" (ማር. 15፡28) ።

 ይልቁንም ጳዉሎስ:- ነገር ግን ልክ ጌታ ከእነርሱ ጋር በምግባራቸው/ በድርጊታቸው እንዳልተካፈላቸው፣ እንዳልተስተፈ፣


ጳውሎስም እንዲሁ ከግብራቸው አልተሳተፈም።

 ቅዱስ ጳዉሎስም ከእነዚያ ጋር / ከእስረኞቹ ጋር/ አብሮ ታሰረ/ አብሮ ለፍርድ ወደ ሮም ሄደ/ ተባበረ
እንጂ በክፉ ድርጊታቸው አልተባበረም።
 በዚህም ድንቅ ነገር ይታያል።

የጳዉሎስ ጉዞ ወደ ሮም
የቀጠለ………….
ጉዞው ተወሰነ፦
 "ወደ ኢጣሊያም በመርከብ እንድንሄድ በተቈረጠ ጊዜ፥ ጳውሎስንና ሌሎች እስረኞችን ከአውግስጦስ
ጭፍራ ለነበረው ዩልዮስ ለሚሉት ለአንድ የመቶ አለቃ አሳልፈው ሰጧቸው።
 የጳውሎስ ጉደኞች፦
 ቅዱስ ሉቃስ፡
 ጳዉሎስ ወደ ኢየሩሳሌም ሲሄድ አብሮት ነበር።
 በቂሳርያ ጳዉሎስ ሲታሰርም በቂሳርያ ይኖር ነበር
 ቅዱስ ጳዉሎስ ወደ ሮም ለፍርድ ሲስሄድ አብሮት ነው የተጓዘው።
 አርስጥሮኮስ፦ ተሰሎንቄያውም አብሮቸው ነበር። ከቅዱስ ጳዉሎስ ጋር ወደ ኢየሩሳሌም አብሮ መጥቷል። የሐዋ.ሥ
19፡29 ወደ ሮም አብሯቸው ተጉዘ።

=====ሁለቱም በጳዉሎስ መታሰር አላፈሩም። የታሰረው ስለ ወንጌል ነውና። ነገር ግን አብረው እርሱ የሚቀበልዉን መከራ፣ በጉዞው
የሚመጣዉን ፈተና ለመቀበል የወሰኑ እዉነተኛ ጉደኛ፣ ደቀመዝሙር ናቸው። ህይወታቸዉን ለእሱ፣ ለስብከት አገልግሎት፣ ክርስቶስን
በአህዛብ ፊት ለመመስከር አሳልፈው የሰጡ ናቸው።=========

 አርስጥሮኮስ ከጳውሎስ ጋር ምን ያህል ርቀት እንደሄደ ተመልከት። አርስጥሮኮስ በዚህ ጉዞ መኖሩ/መገኘቱ ለመልካም ነገር
እና ለአላማ ነው። ምክነያቱም የጳዉሎስን የሌሎችንም ስለ ክርስቶስ መከራ መቀበላቸዉን የሁሉንም ዘገባ ወደ መቄዶንያ ሰዎች
ይወስዳልና።

 ጉዞው የጀመረው፦ ከቂሳርያ ነው። ከደቡብ ጠርሴስ ወደብ ማለት ነው። ወደ አድራሚጢስ መርከብ ገብተን በእስያ ዳር
ለመጓዝ ተነሳን።
የቀጠለ………….

 በማግሥቱም በሲዶና ደረስን” አለ። ( ምዕ. 27፡1–3።)

 ሲዶና ለመጀመርያ ጊዜ የደረሱባት ወደብ ናት። በፊንቄ የምትገኝ ናት።


 ከቂሳርያ 17 ማይል ናት። 24 ሰአት ነው የፈጀባቸው።

 ምንም እንኳ ብዙ ተቃዋሚዎች ጳዉልስ ቢኖሩትም፣ እግዚ አብሄር መልካም ሰው፣


የሚደግፈው ሰው አላሳጣዉም።

 የሀገረ ገዢው ፊልክስም አልጨከነበትም። “የመቶ አለቃዉንም ጳዉሎስን ሲጠብቅ እንዲያደላለት፣


ከወዳጆቹም ማንም ሲያገለግለው ወይም ወድ እርሱ ሲመጣ እንዳይከለክልበት አዘዘው። ሐዋ.ሥ 24፡23”
 የመቶ አለቃዉም አልጨከነበትም። የቅዱስ ጵዉሎስን ጉዳይ ያዉቃልና። በንጉስ አግሪጳ ፊት የመለሰዉንም
መልስ ያዉቃል። ንጉሱም ምን እንዳለ ያዉቃል።
 ሀዋርያው ጳዉሎስ በብዙ ቦታ/ ከተማ/ ሀገር/ ብዙ ጉደኞች፣ ወዳጆች አሉት።
 ምንም እንኳ ጳውሎስ በአለቃው ስር ያለ እስረኛ ቢሆንም፣ ነገር ግን እንደ እዉነተኛ ወዳጆች ነበሩ።

 ይህ ሰው/ መቶ አለቃው ስልጣን አለው በእስረኞቹ ላይ ግን ስልጣኑን ያለ አግባብ አላዋለዉም።


አስተዋይ የነበረ አለቃ ነበር።

 ዮልዮስም ጳውሎስን አክብሮታል።


 ወደ ወዳጆቹ ይሄድ ዘንድ ፈቀደለት።
 ዮልዮስ ለጳውሎስ ነፃነት ሰጠው።
 ቸርነት አደረግለት ይኸዉም ቅዱስ ጳዉሎስ ርዳታቸዉን ይቀበል ዘንድ
ወደ ወዳጆችቹእንዲሄድ ነው።
የቀጠለ…………
===========ከዚያም ተነስተን ነፋሱ ፊት ለፊት ነበርና፣ በቆጵሮስ ሥር ተጓዝን፤ ምክንያቱም ነፋሱ ተቃራኒ
ነበርና። ( ቁ. 4 )==========
 በድጋሜ ሌላ ፈተናዎች፦ እንደገና ተቃራኒ ነፋሶች ገጥሟቸው
 የበልግ ወቅት ሰሜን ምዕራብ ነፋስ በሜድትራሊያን ባህር የሚነፍስበት ወቅት ነው።
 ስለዚህ አቅጣጫ ቀይረው ብቆጵሮስ ጥግ ጥጉን ተገን አድረግው ተጓዙ። ይህም ከነፋሱ ለመሸሽ ነው።
 በኪልቅያና በጵንፍልያ አጠግብ ከተሻገሩ በኋላ በሉቅያ ወደ አለ ወደ ሙራ ደርሱ።

 ነፋሱ ትክክለኛ ነፋስ ቢሆን ኖሮ፣ በቀጥታ ይጓዙ ነበር። ቆጵሮስን በስተቀኝ አድርገው ይሄዱ
ነበር።
 ነገር ግን ነፋሱ ትክክለኛ ነፋስ አይደለምና በነፋሱ ተጽዕኖ/ አስገዳጅነት ወደ ተለያየ አቅጣጫ ተጓዙ።
በዚህም ቆጵሮስን በስተግራ አለፏት።

 የመርከቡ ሰራተኞች ቀጥታ በባህሩ ለመሄድ አልቻሉም። ነገር ግን በምዕራብ ነፋስ ተጽዕኖ
በኪልቅያና በጵንፍልያ አጠግብ ከተሻገሩ በኋላ በሉቅያ ወደ አለ ወደ ሙራ ደርሱ።

 ማጠቃልያ፦
 የቅዱሳን ሕይወት በጠቅላላው እንዴት መከራ የበዛበት ህይወት እንደሆን ተመልከት:፡
 ከእስር ቤት ወደ ሌላ ፈተና ገቡ።
 ግን በመርከብ እና በማዕበል ዉስጥ ወደቁ።

 ሙራ፦ በግሪክ የሉቅያ ከተማ ናት። ትልቅ/ ዝነኛ የወደብ ከተማ ናት። ትላልቅ መርከቦችን
የምትስተናግድ ናት። በተለይ ከእስክንድርያ ወደ ሮም ስንዴ የሚያጓጉዙ መርከቦች
ይበዙባታል።
የቀጠለ…………
 ጉዞ ከሙራ ወደ መልካም ወደብ

 በዚያም የመቶ አለቃው ወደ ኢጣሊያ የሚሄድ የእስክንድርያ መርከብ አገኘ። በውስጧም አኖረን። (ቁ. 5፣6።)
 ከከባዱ ነፍስ ለማምለጥ
 ለመርከቧም ደህንነት
 ቆጵሮስን ተገን አድርገው ተጉዙ። ይህዉም አደገኛዉን ነፋስ ለመሸሽ ነው።

 ቀኒዶስ ከሙራ 130 ማይል ይርቃል። በምዕራብ ሙራ የሚገኝ ወደብ ነው። ጉዟቸውም ጥግ
ጥጉን ነው። ሲጓዙም በጭንቅ በዝግታ ነብር።
 በዝግታ የሚጉዙበት ምክነያት በሰሜን ምዕራብ ነፋስ ምክነያት ነው። ይህ ነፍስ ጉዞው
በጭንቅ እንዲሆን አድርጓል።
 ስለዚህም የቀርጤስን ከተማ ተገን አድርገው በሰልሙና አንጻር ሄዱ።
 ለልስያ ከተማ ወደቀረበች ወደ መልካም ወደብ ደርሱ።

 ነገር ግን ሁልጊዜ በምድር አጠግብ ባለው ባህር ይጓዙ ነበር።


 ጉዞ ከመልካም ወደብ ወደ ማልታ
 ብዙ ጊዜ ካለፈ በኋላ የጦም ወራት አሁን ዓልፎ ስለ ነበር በመርከብ ለመሄድ
አሁን የሚያስፈራ ነበርና። ቁ.9
 የጦም ወራት አሁን ዓልፎ ስለ ነበር።
 ወቅቱ የመጉዣ ሰአት አይደለም።
 የጥቅምት ወር መጀመርያ ነው።
 ከተሞክሮ አንጻር በዚያን ጊዜ በመርከብ መጓዝ ትልቅ አደጋ
አለው።
የቀጠለ…………
 ጉዟቸውን ሲጀምሩ አደገኛው የመርከብ ጉዞ ጊዜ ከመጀመሩ በፊት መድረሻቸው ላይ ለመድረስ ተስፋ
ማድረጋቸው ግልጽ ነው። ነገር ግን ይህ እውን ሊሆን አልቻለም።

 ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ይህ ጾም የአይሁድ ጾም ሲሆን፣ ታላቁ ‘የሥርየት ቀን’ እንደሆነ ያምናል (ዘሌ.
23፡27)።
 በሰባተኛው ወር በአሥረኛው ቀን (በመስከረም መጨረሻ አካባቢ) የበልግ ወራትን ተከትሎ፣ ያለው ወር ለመርከብ
ጉዞ አደገኛ በሚሆንበት ጊዜ ነው።

==============ከበዓለ ሃምሳ በኋላ ብዙ ጊዜ ከዚያ ተነሥተው ነበርና፥ ወደ


ቀርጤስ ዳርቻም እስኪደርሱ ድረስ ክረምት አጋማሽ ነበረ።===========
 “ጳውሎስም ሊመክራቸው ተነሳና፣ እንዲህም አላቸው።
=======================ጌቶች፣ ይህ ጉዞ በጭነት እና በመርከቧ ላይ ብቻ ሳይሆን በህይወታችንም
ላይ ጉዳት እና ብዙ ጥፋት እንደሚደርስ ተረድቻለሁ።ቁ.10============

 ጳውሎስ መደበኛ እስረኛ አልነበረም።


 ገር ግን የመርከብ ልምድ ያለው ካፒቴን ነው።
 በተለይም የመርከብ ስብርባሪዎችን በተመለከተ (2ቆሮ. 11.25-26)።፣
 ነገር ግን የአየር ገዥ የሆነው ዲያብሎስ፦
 ሰዎቹ ምክሩን እንዳይሰሙ የሁሉንም ጆሮ አስዘጋ።
 በጳውሎስ ላይ አዳዲስ ችግሮችን ለመጨመር ፈለገ።
 ቅዱስ ጳውሎስ በባሕር ጉዞ ብዙ ልምድ ነበረው፣ በመከራው መካከል፣ የመርከብ መሰባበር እንዳጋጠመው
ጠቅሷል። (2ቆሮ. 11.25)።
የቀጠለ…………

 ከዚህ በተጨማሪ ሐዋርያው መንፈስ ቅዱስ እንዳናገረው ማንም ሊክደው አይችልም። በመርከቡ ጉዞ ላይ ምን
እንደሚገጥማቸው ማለት ነው።
 ስንዴዉንም ሮም ትፈልገዋለች።

 የመቶ አለቃው ግን ጳውሎስ ከተናገረው ይልቅ የመርከቡን ባለቤትና የመርከቡን መሪ አመነ። ቁ.11
 ምክነያቱም፦
 ብዙ ልምድ አላቸው በማለት ነው።
 ከጳዉሎስ ይልቅ ለመርከባቸው እና ለደህነታቸው ያስባሉ ያዉቃሉ ብሎ ነው።
 በዚህ ምክነያት መቶ አለቃው አመነ። ምንም እንኳ ለጳዉሎስ ርህራሄ እና አድናቆት፣ ክብር ቢኖረውም።
ነገር ግን ምክሩን አልተቀበለም።

=============ወደቡም በክረምት ይከርሙበት ዘንድ የማይጠቅም ስለ ሆነ፥ የሚበዙት ሰዎች


ደግሞ ወደ ፊንቄ ለመድረስ በዚያም ለመቆየት ወደዚያ እንዲሄዱ መከሩ። ቁ.12-==========
 መልካም ወደብ፦
 ለክረምቱ ተስማሚ አልነበረም።
 ፍንቄ ዉስጥ ወዳለው የቀርጤስ ወደብ ለመሄድ መርጠዋል።
 በደቡብ ምዕራብና በሰሜን ምዕራብ በኩል ትገኛለች።
 የደቡብም ነፋስ በቀስታ በነፈሰ ጊዜ ዓላማቸውን እንዳገኙ መሰላቸውና ከዚያ ተነሥተው ወደ
ቀርጤስ ሄዱ። ቁ.13
 ነገር ግን በፊት ይነፍስ የነበረው የምዕራብ ነፋስ እንደገና መጣ።
 ይህ ነፍስ ደግሞ አደገኛና መርከቧን ወደ ተቃራኒ የሚነዳት ነበር።
 ያ ቀስ ብሎ የነፈሰው የደቡብ ነፍስ ተስፋ አድርገው ነበር።
 ድንገት ያ አስቸጋሪው ነፍስ ተለዉጦ መልካሙ ነፋስ መጣ። ግን ጊዜያዊ ነበር።
 ወዲያዉኑ በአስቸጋሪዉ በሰሜን ምዕራቡ ነፋስ ተተካ።
የቀጠለ…………

 ብዙም ሳይቆይ አውራቅሊስ የሚሉት ዐውሎ ነፋስ በላያቸው ተነሣ። ቁ.14


 ድንገት አስቻጋሪው ነፋስ ዉስጥ ገቡ።
 ቅዱስ ጳውሎስ እንደ ነቢዩ ዮናስ ችግር ገጠመው።
 ነገር ግን ዮናስ ከጌታ ፊት ሲሸሽ ነው።
 ጳውሎስ ግን ለጌታ መመስከር ነው።
 ዮናስ ለአህዛብ ለመስበክ ፈቃደኛ ባለመሆኑ ነው።
 ጳውሎስ ግን በአህዛብ ፊት ስለ ጌታ ክርስቶስ ለመመስከር ነው።

===============መርከቢቱም በነፋሱ በተያዘች ጊዜ ወደ ነፋሱን ተቁቋማ ወደ አሰቡበት መሄድ


አቃታት፥ ከዚያ ለቀነው በነፋስ ተነዳን።” (በነፋሱ “ተነዱ።”) (ቁ. 15)============
 በዛ ኃይለኛ አውሎ ነፋስ የተያዘችው መርከብ እንደ አሻንጉሊት ሆነች።
 ሰራተኞቹ በመጨረሻ መቆጣጠር መሞከራቸውን አቆሙ።
 ከዛም ሕይወታቸውን ምህረት ለሌለው ንፋስ አሳልፈው ሰጡ።
 ሐዋርያው ጳውሎስ ግን፦ በመርከቧ ዉስጥ ላሉት ሁሉ በየስማቸው ጉዳዩን በእግዚአብሔር እጅ አሳልፎ
ሰጠ።
 ሁሉም በዘላለማዊ ክንዶች እንደተያዙ አምኗል።

 " ቄዳ ወደ ምትባል ደሴትን ተገን አድርገን መርከባኡን ለመቆጣጠር ቻልን።


 ቄዳ፦ ከቀርጤስ በስተደቡብ ምዕራብ 20 ማይል ርቀት ላይ የምትገኝ ትንሽ ደሴት።

 "እኛም በዐውሎ ነፋስ ስለ ተናወጥን በማግስቱ መርከቡ ጭነት ወደ ባህር ይጥሉ ነበር።" (የሐዋ. ሥራ 27:18)
 በማግስቱ እቃውን በተለይም እህሉን ወደ ባህር መጣል ጀመሩ።
 ሀብት እንደማያድናቸው ተረድተዋል።
 ነገር ግን ይህ በህይወታችን መርከብ ላይ ያለዉን ከባድ ሸክም ያሳያል።
 ይህም ሸክም በዚህ ዓለም ውኃ ውስጥ ልንጥለው የሚገባ ነው።
የቀጠለ…………

 ጠቢቡ ሰሎሞን “ሀብት ለባለቤቱ የተቆጠበች መከራው ናት።” ሀብት ጉዳት ነው። (መክ. 5፡13)።
 የዚህ ዓለም ሰዎች ጊዜያዊ ሕይወታቸውን ለማዳን ያገኙትን/ያጠራቀሙትን/ በዉድ ዋጋ የገዙትን ሁሉ በቀላሉ እንዴት
እንደሚጥሉ አስገራሚ ነው።
 ለዘለአለማዊ ሕይወታቸው ሲሉ ከሱ ትንሽ ክፍል ለድሆች እና ለችግረኛ ወንድሞቻቸው ለመስጠት በጣም ይከብዳቸዋል።
 ዘላለማዊነትን ከክብ የሚጠባበቅ ሁሉ በዓለማዊ ጉዳዮች አይጠመድም።
 የሚበልጥና ለዘወትር የሚኖር ገንዘብ በሰማይ ለራሳችሁ እንዳላችሁ አውቃችኋል” (ዕብ. 10፡34)።

 ማንኛውም ምክንያታዊ ሰው ህይወቱን ለማዳን በመርከቧ ላይ ያለውን ሁሉ ያጠፋል፣ ይጥላል።


 ብዙዎች ለጊዜያዊ ነገሮች ሲሉ የእምነታቸውን መርከብ እና በጎ ሕሊናቸውን ለማጥፋት ይመርጣሉ።

 የዚያች መርከብ መርከበኞች እንዳደረጉት፦ እኛም በዚህ ዓለም ማዕበል መካከል ሆነን ከባድ ሸክማችንን
ለማቅለል፣ በአየር ላይ እንደምትበር ወፍ ቀላል ለመሆን ቆርጠን መነሳት አለብን።
 እንደ ፈርዖንና ወታደሮቹ እንዳንሆን። “ በግዙፍ በዉቅያኖስ/ ባህር ውስጥ እንደ እርሳስ ሰመጠን እንዳንቀር ማለት
ነው። " (ዘፀ. 15.10)

 በሦስተኛውም ቀን የመርከቡን ዕቃ በእጃችን ጣልን።

============ብዙ ቀንም ፀሐይና ከዋክብት አላየንም፥ ትንሽም ማዕበል


በመጣብን ጊዜ፥ ወደፊት እንድናለን ብለን የነበረን ተስፋ ጠፋ።================

 ሁኔታውን የከፋ ያደረገው ደግሞ ጨለማው ነው።


 ጨለማው በላያቸው ላይ በመውደቁ ለብዙ ቀናት ሌሊትና ቀን መለየት አለቻሉም።
 በዚህም ምክነያት ያሉብትን ቦታና አቅጣጫ ማወቅ አልቻሉም።
 ስለዚህ ወደ ደኅንነት (የዕረፍት ወደብ/ መሬት) የሚወስደውን ትክክለኛ መንገድ
መወሰን አልቻሉም።
የቀጠለ…………
 የጽድቅ ፀሐይ የሆነውን ጌታ ክርስቶስን የምታይበትን ዓይኗን/ብርሃኗን/ ያጣችን ነፍስ መንገዷ
እንዲህ ነው።
 በብርሃኑ አትደሰትም። “የቀን ሴት ልጅ” አትሆንም።
 እንደ አንጸባራቂ ከዋክብት የሆኑትን እውነተኛቹን የእግዚአብሔር ልጆች እይታ/ብርሃን/ ሲያጣ፣
በፊታቸው ፈለጋቸውን/ መሪነታቸውን ለመከተል የእምነት አርአያ/ ምሳሌ የሚሆነው ሲጠፋ
ጨለማዉ ከባድ ነው።
 ሰው፦
 በመንፈስ ቅዱስ ብርሃንነት፦
 የነፍሱ እውነታ/ ማንነት፣
 ያለበትን ሁኔታ/ቦታ ሳይረዳ፣
 የአዳኙን ብርሃን / የክርስቶስን የማዳን ሥራ ሳያይ ሲቀር፣
 የቤተክርስቲያንን ውበት፣
 የቅዱሳን ታላቅነት፣ ድንቅ ነገር ሲያጣ፣ ህይወቱ አደጋ ዉስጥ ይሆናል። ያለበት
ሁኔታ በጣም አደገኛ ይሆናል።

 ያ አደገኛ ሁኔታ የሰራተኞቹን/ የመርከበኞቹን አስተሳሰብ/ ህሊና አጠፋው።


 ውጫዊው ጨለማ የዉስጣቸዉን ማንነት አጥፊው፣ ውስጣቸዉን ጨለማ አደረገው፣ ተስፋ ቆረጡ።
 “እንድናለን የሚለው ተስፋ ሁሉ በመጨረሻ ተሟጠጠ።” (ሐዋ. 27፡20)።
 በዚህ ዓለም ውስጥ የሰውን ሕይወት የሚያጠፋው በጣም አደገኛ ጠላት ወደ ነፍሳቸው ገባ።
 በተስፋ መቁረጥ ዘላለማዊነቱን ያጣል።
 ተስፋ መቁረጥ ወደ ዉስጥ ሲገባ፣ ያ ሰው በሁሉም ሐጢያቶች ዙሪያዉን ይከበባል። ይታጀባል።
 ስለዚህም አጋንንት በልቡ ዉስጥ የሚቀመጡበትን ዙፋን አገኙ።

==============ሳይበሉ ብዙ ቀን ከቆዩ በኋላ፣ ጳውሎስ በመካከላቸው ቆሞ እንዲህ አለ፦ እናንተ


ሰዎች ሆይ ፦ ሰምታችሁኝ በሆነ ኖሮ፣ ከቀርጤስም እንዳትነሱ፥ ይህንም ጕዳትና መከራ ባለገኛችሁ ነበር።
( ቁ. 21 )================
የቀጠለ…………

 በእነዚያ አስጨናቂ ሁኔታዎች ውስጥ የኃይለኛውን ንፋስ ተፅእኖ ለመገደብ ሸራዎቹን ወደ ታች አወረዱ እና የ
1000 ቶን ጭነት መርከቧን ማቅለል ጀመሩ ።
 ይኸዉም መርከቧ በኃይለኛ ማዕበል ግርፋት እንዳትፈርስ ነው።
 በሦስተኛው ቀን የመርከቧን መያዣ በገዛ እጃቸው ወደ ባህሩ ላይ ጣሉት።
 መርከቧ ውሃ መሞላት ስትጀምር፣ በብስጭት በየቦታው እየሮጡ እርስ በእርሳቸው እየተጣደፉ በከፍተኛ ድምፅ ጮሁ።
 በዚህ ላይም ደግሞ ፦
 ቀዝቃዛው ንፋስ፣
 ከባድ ዝናብ
 ድቅድቅ ጨለማ መከራቸውን ከፍ አደረገው።

================በዚያም አስፈሪ ድባብ ውስጥ ሐዋርያው ጳውሎስ ወደ አምላኩ እየጾመ እየጸለየ ከእርሱ
ጋር በመርከብ ለሚሄዱት ሁሉ ሊፈጽምለት የገባውን አምላካዊ ቃል ኪዳን እውን ለማድረግ በቄሳር ፊት ቆሞ
ለጌታውና ለአዳኙ ይመሰክር ዘንድ ተልእኮውን ይፈጽም ዘንድ በመካከላቸው ነው ።
=====================
 አንዳንዶች በዚህ ጾም ውስጥ ሁሉም ተሳትፈዋል ብለው ያምናሉ። ግን የጾሙት በአምልኮ ሥርዓት
ሳይሆን ከመከራና ከመራራነት የተነሣ ነው። እራሳቸውን እና መርከቧን ለማዳን አድካሚ ችግር ዉስጥ
ስለሆኑ ነው።
 በዚህ ምክነያት በመብልና በመጠጥ አልጠመዱም።

 ቅዱስ ጳዉሎስ መጀምሪያ ላይ ምክሩ አልሰማ ስላሉት ወቀሳቸው።


 ስለ ደህንነታቸው ከእግዚ አብሔር ቃል ኪዳን ተሰቶኛል ሲላቸው እርሱን መስማት ጀመሩ።
===========ዛሬም፦=="ጳውሎስ አሁንም ከእኛ ጋር ይጓዛልና፥ ነገር ግን በዚያን ጊዜ እንደታሰረው ሳይታሰር፣ አሁንም
ይመክረናል።=============
============ጳውሎስን እንታዘዘው፡ በዐውሎ ነፋስ ውስጥ ብንሆን፥ በእርግጠኝነት ከአደጋዎች ነፃ
እንወጣለን።===============
================= ያለ ምግብ አሥራ አራት ቀን ብንቆይም፥ የመዳን ተስፋችን ቢጠፋም፥ በጨለማና በጭጋግ ዉስጥ
ብንሆንም፥ ትእዛዝውን በመፈጸም ከአደጋው እናመልጣለን።=======
የቀጠለ…………
 ዓለሙ ሁሉ መርከብ እንደሆነ እናስብ፦
 በዚህም መርከብ ዉስጥ፦
 ክፉ አድራጊዎች
 ምግባር የሌላቸው፥
 ገዢዎች /አለቆች፥
 ጠበቃዎች/ዘቦች፥
 ጻድቃን፦ ምሳሌ ጳውሎስም፣ ሉቃስ፣ አርስጦኮሮስ ነበሩ፥
 እስረኞች፥
 በኃጢአታቸው የታሰሩ ሰዎች አሉበት።

========ጳውሎስ ያዘዘንን ብናደርግ ከነእስራታችን አንጠፋም።===========


==ከእስራታቸው ተፈትተዋል፤ እግዚአብሔር እኛን ደግሞ ለእርሱ ይሰጠናል። ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ

============“አሁንም አይዞአችሁ እላችኋለሁ፤ ከመርከቡ በቀር በመካከላችሁ የማንም ነፍስ አይጠፋምና


አይዞአችሁ።ቁ.22==============

 የእግዚአብሔር መልአክ በዚች ሌሊት በአጠገቤ ቆሞ ነበርና።


 ጳውሎስ ሆይ፥ አትፍራ፥ አትፍራ፣ አንተ ወደ ቄሳር ፊት ትቀርባለህ፤ እነሆም እግዚአብሔር ከአንተ ጋር የሚሄዱትን
ሁሉ ሰጥቶሃል።
 ስለዚህ፣ ጌቶች፣ አይዞአችሁ፣ እንደ ተባለልኝም እንዲሆን እግዚአብሔርን አምናለሁና።
============ይህ የምስራች ከእርሱ የመጣ ሳይሆን መለኮታዊ ስጦታ ነው። በመከራው መራራ
መካከል ጳውሎስ ከእነርሱ እንደ አንዱ ሆኖ እየጾመ እየሠራ ነበር፣ ዕቃውን ወደ ባህር ጥሎ መርከቧን
ለማዳን የተቻለውን ሁሉ አድርጓል።===================
የቀጠለ…………

=============አሁን ግን መለኮታዊውን የተስፋ ቃል ተቀብሎ በመካከላቸው ቆሞ


ከታሳሪዎቹ እንደ አንዱ ሳይሆን አስደሳች የምስራች የሚናገር መልካም ጉባኤ ሆኖ ነበር።
ከእነርሱም የተስፋ መቁረጥን መንፈስ አርቆ የተስፋን መንፈስ ከሰማይም መጽናኛን
አመጣላቸው።======================

 ነገር ግን በአንድ ደሴት ላይ ማረፍ አለብን። (ቁ. 22-26።)


 ሁለት ነገሮችንም ተንብዮአል። ሁለቱም በደሴት ላይ ማረፍ እንዳለባቸው እና መርከቡ ቢጠፋም
በውስጡ ያሉት ይድኑ ዘንድ ነው።
 ስለ ትንበያ ሳይሆን ስለ ትንቢት ተናግሯል ።
 እና "ወደ ቄሳር ፊት መቅረብ አለበት። ”

 ነገር ግን፣ ሁሉን ሰጠህ የሚለው ይህ በትዕቢት አይደለም ነገር ግን በታንኳ የሚሄዱትን ሊረዳቸው
ፈልጎ ነው እንጂ፤ ከእርሱ ጋር እንደ ታሰሩ እንዲሰማቸው አይደለምና።
 ነገር ግን የተናገረውን ያምኑ ዘንድ ነው።
 "እግዚአብሔር ሰጠህ" እነርሱ አልሰሙህምና በእውነት ሞት ይገባቸዋል፤ ነገር ግን ይህ የተደረገው
ለአንተ ከቸርነቱ የተነሣ ነው።

 “ነገር ግን አሥራ አራተኛው ሌሊት በአድርያ ወደ ላይና ወደ ታች ስንነዳ፥ መርከበኞች በመንፈቀ ሌሊት
ጊዜ ወደ አገር የቀረቡ መሰላቸው። ልኩ፥ ሀያ ጫማም አገኘው። ጥቂትም ወደ ፊት ሄዱ፥
ደግመውም ለኩ፥ አሥራ አምስትም ስብ ሆኖ አገኙት።
የቀጠለ…………

 በዓለት ላይ እንዳይወድቁ ፈርተው ከኋላው አራት መልሕቆች ጣሉ ቀኑንም ተመኙ።


 መርከበኞችም ከመርከቡ ሊሸሹ ሲሉ ታንኳይቱን ወደ ባሕር ካወረዱ በኋላ ከግንባሩ መልሕቅ እንደሚጥሉ መስለው፥
 ጳውሎስ ለመቶ አለቃውና ለጭፍሮቹ፣ እነዚህ በመርከቡ ውስጥ ካልኖሩ ልትድኑ አትችሉም።

 ከዚያም ወታደሮቹ የጀልባዋን ገመድ ቈርጠው እንድትወድቅ ተዉአት። ( ቁ. 27–32 )

 መርከበኞቹ ግን በተነገረው ነገር ስላላመኑ ሊያመልጡ ፈልገው ነበር፤


 የመቶ አለቃው ግን ጳውሎስን አመነ።
 እነዚህ ቢሸሹ ትድኑ ዘንድ አትችሉም ይላልና።
 እንዲገድባቸው ትንቢቱም በምድር ላይ እንዳይወድቅ ነው እንጂ ስለዚህ አይደለም አለ።
 በቤተክርስቲያን ውስጥ በጳውሎስ ባህሪ መረጋጋት እንዴት እንደተማሩ፣ ከአደጋዎች መካከል እንዴት
እንዳዳናቸው ተመልከት።
 ይህም የሆነው፣ እውነትን ከመረመሩ በኋላ እንዲታመን ጳውሎስ አለመታዘዛቸው በጊዜያዊ ሥርዓት ነው፡
 በዳግመኛም ሥጋ እንዲወስዱ አዘዛቸው፥ እንዳዘዛቸውም አደረጉ።
 አውሎ ነፋሱ ምንም እንዳልጎዳቸው ይልቁንም ለነፍሳቸው የሚጠቅም መሆኑን በቃል ሳይሆን በተግባር ለማሳመን
አንዳንዶቹን አስቀድሞ ይወስዳል።\

 “ቀኑም ሲደርስ ጳውሎስ ምግብ ይበሉ ዘንድ ሁሉን ለመነአቸው እንዲህም አላቸው፡- “እናንተ ከቀራችሁበት ምንም
ሳትቀምሱ በጾማችሁ ዛሬ አሥራ አራተኛው ቀን ነው። (ቁጥር 33)
 (ለ) አንተስ ትላለህ፣ ምንም ሳይበሉ እንዴት ሄዱ?

 እንዴትስ ተሸከሙት? ፍርሃታቸው ያዛቸው፣ እና የምግብ ፍላጎት ውስጥ እንዲወድቁ አልፈቀደላቸውም ፣ እነሱ
፣ በጣም ከባድ አደጋ ላይ ስለሆኑ ነው።

 (ረ) ነገር ግን ለምግብ ምንም ደንታ አልነበራቸውም።


የቀጠለ…………

Note.
==============እየዬም ሲዳላ ነው።
እንዲሉ።
(=========በዛ ሰኣት ከመከራው ከሞት
እንዴት እንዳን እንጂ ምግብ ትዝ አላላቸውም።)

 "ስለዚህ መብል ትበሉ ዘንድ እለምናችኋለሁ፤


 ይህ ለጤንነታችሁ ነውና፥
 ከእናንተም ከማንኛችሁም ራስ አንድ እንኳ ፀጉር አይወድቅም። ይህንም ብሎ እንጀራ አንሥቶ በሁሉ ፊት እግዚአብሔርን
አመሰገነ ቆርሶም ይበላ ጀመር።

 በዚያን ጊዜ ሁሉም ደስ አላቸው ሥጋንም ያዙ፤” (ቁ. 34-36) ሕይወታቸው ስለመዳኑ ምንም ጥያቄ እንደሌለው በማየቱ።

 (መ) “እኛ ሁላችን በመርከቡ ውስጥ ሁለት መቶ ሰባ ስድስት ነፍሳት ነበርን።

 በልተውም ከበሉ በኋላ መርከቢቱን አቃለሉት፥ ስንዴውንም ወደ ባሕር ጣሉት።


 በነጋም ጊዜ ምድሪቱን አላወቁም።
 ነገር ግን ቢቻላቸውስ መርከቡን ሊወጉት አሰቡ፥ ከባሕርም ጋር ያለውን ወንዝ አገኙ።

 መልሕቆቹንም በወሰዱ ጊዜ፣ ራሳቸውን ወደ ባሕሩ አሳልፈው ሰጡ፣ እናም የመሪዎቹን ማሰሪያ ፈቱ፣ እናም ዋናውን ሸራውን
ለነፋስ አንስተው ወደ ባሕሩ ዳርቻ ሄዱ። ( ቁ. 37–41 )
የቀጠለ…………
 መሪዎቹን ለነፋስ ሰጥተው "ወደ ባሕሩ ዳርቻ ሄዱ" ብዙ ጊዜ እንደዚህ አያደርጉትምና።

 እነሱ ተሸክመው ነበር ፣ ማጭበርበሪያውን ፣ ማለትም ሸራውን በማላቀቅ።

 ሁለቱም ባሕር በተገናኙበት ስፍራ ወድቀው መርከቢቱን ከገደሉ በኋላ።

 ፊተኛውም ተጣብቆ ሳይንቀሳቀስ ቀረ፥ ዳሩ ግን በማዕበል ግፍ ተሰበረ።

 ኃይለኛ ነፋስ በሚኖርበት ጊዜ, ይህ መዘዝ ነው, የኋለኛው ክፍል (የማዕበሉን) ይሸከማል።

(ሀ) “ወታደሮቹም እስረኞቹን አንዳቸውም ዋኝተው እንዳያመልጡ ይገድሏቸው ነበር። (ቁጥር 42)
 ዳግመኛም ዲያቢሎስ ትንቢቱን ሊያደናቅፍ ሞከረ፣ እና አንዳንዶቹን ሊገድሉ አሰቡ፣ ነገር ግን የመቶ
አለቃው አልፈቀደላቸውም፣ ምናልባትም ጳዉሎስ ያድነው እንደሆን ስላመነ።
 የመቶ አለቃው ከጳዉሎስ ጋር ይህን ያክል ይወደው ነበር።
=================ጳውሎስም “ይህ ጉዞ ከጉዳትና ከመጥፋት ጋር እንደሚሆን
አይቻለሁ” ብሏል። (ቁጥር 10)==================
 የቅዱስ ጳውሎስ አገላለጽ ምን ያህል የማይታሰብ/የማይገመት መሆኑን ተመልከት።
 ትንቢት የሚናገር እንዳይመስል፥ ነገር ግን እንደ ግምት ይናገር ዘንድ፥ "አለሁ" ይላል።
 ሲጀምር ይህን ተናግሮ ቢሆን ኖሮ አይቀበሉትም ነበርና።
 እንዲያውም በዚህ በቀደመው አጋጣሚ ትንቢት ተናግሯል።
 በኋላ እንዳደረገው እና (እዚያ) እንዳለው“የማመልከውን አምላክ” እየመራቸው ነው ይላል።

 ታዲያ እንዴት ነው በሕይወት ማንም “እንዳማይጠፉ” የተናገረው?”


 እንደዚያ ይሆን ነበር ነገር ግን እግዚአብሔር በውስጧ አዳናቸው።
 እንደ ገጠማቸው የተፈጥሮ ሁኔታ መሰረት ቢሆን ኖሮ ጠፍተው ነበር፣ ነገር ግን እግዚ አብሔር ተፈጥሮን ከለከለው።
የቀጠለ…………
 ከዚያም የተናገረው ከግምት እንዳልሆነ ለማሳየት የመርከቡ አለቃ በተቃራኒ ተናግሯል (ቁ. 11)።
 የመርከብ መሪ ግን በጉዳዩ ላይ ልምድ ያለው ሰው ነበር፡፡ ሙያው ነውና።

 እስካሁን ድረስ የጳውሎስ ምክር ተቀባይነት አላገኘም።


 ግምታዊ እንደሆነ ነበር የተረዱት።
 ከዚህም በላይ ቦታው ይህንኑ (መምህሩ የተናገረው) “አለመሆን” የሚል ሐሳብ አቅርቧል።
 እናም ከጳውሎስ ይልቅ “ብዙዎቹ የያሰቡት” የገመቱት (ቁ.12) ግልጽ ነበር።
 ከዚያም፣ኃይለኛ አውሎ ነፋሱ (የተከሰተ።)ጥልቅ ጨለማ መጣ።
 እና የማይረሳው ነገር፣ ዕቃው ደግሞ ይሰበራል፣ እና እህሉ ወደ ውጭ ይጣላል።
 ሁሉም በራሳቸው ሥልጣን እንደሌላቸው ሆኑ፣ ከዚህ በኋላ ሀፍረተ ቢስ ሆኑ።
 በዚህ ምክንያት መርከቧ ወደ ቁርጥራጭ ትሄዳለች, እናም ነፍሶቻቸው በጥብቅ ታስረዋል።
 ከዚህም በላይ አውሎ ነፋሱም ሆነ ጨለማው የሰራው ችሎት እንዲያገኝ አስተዋጽኦ አድርጓል።
 ስለዚህ የመቶ አለቃው ባዘዘው ጊዜ እንዴት እንዳደረገ ተመልከት፤ ስለዚህም ታንኳይቱን እንኳ ትቶ
አጠፋት።
 መርከበኞቹም ትእዛዙን ገና ባያደርጉ፥ በኋላ ግን እንዲሁ ያደርጋሉ፤ በእውነት ይህ ቸልተኛ ሰው ነውና።
 “ጌቶች ሆይ፣ ልትሰሙኝ በነበራችሁ ነበር።” ወዘተ (ቁ. 21)
 አንድ ሰው በአደጋው መካከል ሲጮህ ጥሩ አቀባበል አይኖረውም።
 ከክፉው የበለጠ ምን እንዳለ በነገራቸውና ከዚያም መልካሙን ሲተነብይ እርሱ ተቀባይነት አለው።
 ስለዚህም በመጀመሪያ ያጠቃቸዋል፣ “እንዲድኑም የነበረው ተስፋ ሁሉ ሲጠፋ። ማንም እንዳይናገር።
 ምንም አልመጣለትም።ፍርሃታቸውም ይመሰክራል።
 ከዚህም በላይ ቦታው የሚሞክር ነው፣ ምክንያቱም በአድሪያቲክ ውስጥ ነበር፣ እና ከዚያም ረዥም መታቀባቸው፣
 በሞት መካከል ነበሩ።
 ምንም ሳይበሉ ሲሄዱ አሥራ አራተኛው ቀን ነበር።
 “ስለዚህ፣ ሥጋ እንድትወስድ እለምንሃለሁ፡ አለ። ይህ ለጤንነትህ ነውና” (ቁ. 34)፣ በረሃብ እንዳትጠፉ ትበላላችሁ።
 ይህ ሁሉ ከሆነ በኋላ ማመስገኑ ብርታት እንዳደረጋቸው አስተውሉ።
 ይህም እነርሱ እንደሚድኑ የተረጋገጠ አእምሮ አሳይቷልና።
 (ለ) “ከዚያም ሁሉም ደስተኞች ነበሩ። ሥጋም ወሰዱ። (ቁጥር 36)
የቀጠለ…………
 እና እሱ ብቻ አይደለም ፣ ነገር ግን ከአሁን ወዲያ አሳባቸውን ሁሉ በጳውሎስ ላይ ጣሉት።
 እህሉንም እስኪያጥሉ ድረስ (ቁ. 37)፤ እጅግ ብዙ ነበርና።
 (ሀ) ሁለት መቶ ሰባ ስድስት ነፍሳት (ቁ. 38)፡ መብል ከየት አገኙ?
 (ሐ) እንደ ወንዶች ድርሻቸውን እንዴት እንደሚወጡ እና ጳውሎስ እንዴት እንዳልከለከላቸው ተመልከት።

===========ነገር ግን አንዳንዶች፡- መርከቧን ለምን አላዳናትም ይላሉ?=====

===========ምን ያህል ከታላቅ አደጋ እንዳመለጡ ያስተውሉ ዘንድ ነው።

 ነገሩ ሁሉ የተከናወነው በሰው እርዳታ ሳይሆን ከመርከብ ላይ ወጥተው በየራሳቸው


በእግዚአብሔር እጅ ነበር የዳኑት።

==============ስለዚህ ጻድቃን በዐውሎ ነፋስ ወይም በባሕር ላይ ወይም በጥልቁ


ውስጥ ቢሆኑም እንኳ አይፈሩም። ==============
============ነገር ግን ከራሳቸው ጋር አብረው ሌሎችን ያድናሉ።=========

==========መርከቧ በአደጋና በስቃይ ላይ ወድቃ ሳለ እስረኞችም ስለ ጳውሎስ ከዳኑ፥


ቅዱስ ሰው በቤት ውስጥ ማግኘት ምን ያክል ጥቅም እንዳለው አስቡ።==========

 እኛን ደግሞ የሚያጠቁን ብዙ ዐውሎ ነፋሶች አሉ።


 እኛን የሚያጠቃን አውሎ ነፋስም ከእነዚህ ይልቅ የከበደ ነው።
የቀጠለ…………
 ነገር ግን ቅዱሳን ሰዎች እንዳደረጉት (በመርከቡ ላይ) እንደታዘዙት ብንታዘዝ፣ ያዘዙትን
ብንፈጽም ፦
 መዳንም ሊሰጠን ይችላል።
 መከራውን ማለፍ እንችላለን።
 ወደ እረፍት ወደባችን (ወደ እረፍት መሬት) እንደርሳለን።
 በማዕበል የሚናወጠዉን የህይወት ጉዞ እናመልጣለን።

 እነዚህ ሰዎች በቀላሉ የዳኑ አይደሉምና።


 ነገር ግን ራሳቸው ለሌሎች ሰዎች እምነት አስተዋጽኦ አድርገዋል።

 ቅዱሱ ሰው/ ጳዉሎስ/ ቢታሰርም፣ ነጻ ከወጡት ይልቅ የሚበልጥ


ሥራን ሰርቷል።
 ይህ እንዴት እንደነበረ እንመልከት።

 ነፃው የሆነው/ የእስረኞቹ አለቃ/ መቶ አለቃው /ዮልዮስ ታሰሪውን እስረኛ ፈለገ።


 በሙያው አንተ የተባለው የመርከቡ ካብቴን/ፓይለቱ እውነተኛውን አብራሪ
/መሪ/ ጳዉሎስን ፈልጎ ነበር።
 ቅዱስ ጳዉሎስ ግን የምድራዊቷ መርከብ ካብቴን ሳይሆን የቤተ ክርስቲያን ካፒቴን
ነበር።
 ያ ቺ ቤተ ክርስቲያን ምንም ሳትሆን (ጸጉራቸው እንኳ እንደ ማይጠፋ) ወደ እረፍት
ወደቧ ደረሰች። (captian paul)
 የባህሩ (የዚህ ዓለም) መርከብ ካፕቴን ግን እንኳን መርከቧን ራሱንም ማትረፍ
አልቻለም። መርከቡም ተሰባበረች።
የቀጠለ…………

 ነገር ግን የዓለም ሁሉ ቤተ ክርስቲያን፣ የባሕርም ጌታ ከሆነው ከእርሱ ተመራች።


 (መምራት፣) በሰው ጥበብ ሳይሆን በመንፈስ ቅዱስ ጥበብ ነው።

 በዚህ መርከብ/ ዓለም/ ውስጥ ብዙ የመርከብ ስባሪዎች/ መናወጥ፣ ብዙ ማዕበሎች፣ የክፋት


መናፍስት አሉ።

 ከዉስጥ “ጠብ፣ ክርክር አለ”፣ ከውጭም ፍርሃት አለ። (2ቆሮ7፡5) ስለዚህ እርሱ/ጳውሎስ/ እውነተኛ
አብራሪ ነበር።
 መላ ሕይወታችንን ተመልከት፡-
 የእኛም ሕይወት ልክ እንደዚህ ነው። (እንዲህ ዓይነት ጉዞ ነበረ)።
 በአንድ ወቅት በደግነት፣ በሌላ ጊዜ በዐውሎ ነፋስ እንናወጣለን።
 አንዳንድ ጊዜ ከራሳችን ምክር፣ አንዳንዴ ከሥራ ፈትነት፣ ቁጥር ወደሌለው ክፋት ውስጥ
እንወድቃለን።
 ጳውሎስን ባለመስማት፣ እርሱ ወደ አልመራን ወደ ሌላ መሄድ ስንፈልግ ይህ ይከሰታል።
 ጳውሎስ ያን ጊዜ እንደ ታሰረ ሳይሆን አሁን ከእኛ ጋር በመርከብ እየተጓዘ ነው።

 አሁንም በዚህ ባህር ላይ ለሚጓዙ/ በዚህ ዓለም/ ሁሉ “ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። እያለ ይመክረናል።

 እኔ ከሄድሁ በኋላ ጨካኞች ተኩላዎች ይገባባችኋልና” (ሐዋ. 29)።


 “በመጨረሻው ዘመን፦
 ዘመን የሚያስጨንቅ ዘመን ይመጣል፤
 ሰዎችም ራሳቸውን የሚወዱ፣
 ገንዘብ የሚወዱ፣
 ጉረኞች ይሆናሉ። (2ኛ ጢሞ. 2.)
==========ይህ ከሁሉም አውሎ ነፋሶች/ ማዕበሎች የበለጠ ከባድ ነው።========
የቀጠለ…………

 ስለዚህ ባዘዘን መሰረት እንኑር፡


 በእምነት፣ በአስተማማኝ ቦታ በወደቡ እንኑር(በመልካም ወደብ)።

 በውስጣችን ያለውን ፓይለት/ ካፒቴን/ ማለትም የራሳችንን ምክንያት


ከመስማት ይልቅ እርሱን እንስማው።
 ወዲያው አንሁን፣እሱ የሚጠቁመውን ብቻ እናድርግ።
 የመርከቡ ባለቤት የሚለንን ሳይሆን፤ ጳውሎስን ሐሳብ እንተግብር።

 ቅዱስ ጳዉሎስ በብዙ ማዕበላትን አልፏልና።

 ልማድ/experience፦
 በልምድ አንማር (በእኛ ወጪ) ነገር ግን ከተሞክሮ በፊት “ጉዳት እና
ኪሳራን እናስወግድ”።
 የመቶ አለቃው ግን ጳውሎስ ከተናገረው ይልቅ የመርከብ መሪውንና
የመርከቡን ባለቤት ያምን ነበር። ሐዋ.ሥ. 27፡11
 የመርከቡ መሪ እና የመርከቡ ባለቤት የቅዱስ ጳዉሎስን ምክር
አልሰማ ብለው በራሳቸው ተሞክሮ እና ልምድ ተጉዘው ትልቅ ኪሳራ ዉስጥ
ገቡ።
 የራሳቸዉንም ህይወት እስከ ማጣት ደረሰ።
 “ሀብታሞች ሊሆኑ የሚወዱ ወደ ፈተና ይወድቃሉ” የሚለውን ስሙ። (1 ጢሞ.6፡9.)
የቀጠለ…………
================እንግዲህ እንታዘዘው፣ ያለበለዚያ ምክሩን ስላልተቀበሉ
የደረሰባቸውን ተመልከት።===============
 ዳግመኛም በሌላ ቦታ የመርከብ መሰበር መንስኤ የሆነውን ተናገረ።
 “በእምነት ረገድ መርከብ /ዓለምን/ የሰበረ (ያሸነፈ) ማን ነው?” ብሏል።
 አንተ ግን በተማርህበትና በተረዳህበት ነገር ጸንተህ ኑር። (1ኛ ጢሞ. 19.)
 ለጳውሎስ እንታዘዝዉ፡ በዐውሎ ነፋስ መካከል ብንሆንም ከአደጋው በእርግጥ ነፃ እንወጣለን።

 ያለ ምግብ አሥራ አራት ቀን ብንቆይም


 የመዳን/ የመትረፍ ተስፋ ባይኖረንም፣
 በጨለማና በጭጋግ ውስጥ ብንሆንም፥
 ትዕዛዙን በመፈጸም፣ከአደጋዎች ነፃ እንወጣለን።
 ዓለሙ ሁሉ መርከብ እንደሆነ እናስብ፦
 በዚህም መርከብ ዉስጥ፦
 ክፉ አድራጊዎች
 ምግባር የሌላቸው፥
 ገዢዎች /አለቆች፥
 ጠበቃዎች/ዘቦች፥
 ጻድቃን፦ ምሳሌ ጳውሎስም፣ ሉቃስ፣ አርስጦኮሮስ ነበሩ፥
 እስረኞች፥
 በኃጢአታቸው የታሰሩ ሰዎች አሉበት።

========ጳውሎስ ያዘዘንን ብናደርግ ከነእስራታችን አንጠፋም።===========


============ከእስራታቸው ተፈትተዋል፤ እግዚአብሔር እኛን ደግሞ ለእርሱ ይሰጠናል።====
የቀጠለ…………

 ኃጢአትና ምኞት ከባድ እስራት እንደሆኑ አታስብምን?፦


 የታሰሩት እጆቻችን ብቻ አይደሉምና፥
 መላው ሰውነታችን ነው እንጂ።
 ንገረኝ፣ ብዙ ገንዘብ ያለው ሰው ሳይጠቀምበት ወይም ለሌላ ሰው ሳይሰጠው፣ ግን
በአጠገቡ አድርጎ ይጠብቀዋል።
 ይህ ሰው በመከራ ዉስጥ አይደለምን? ከእስረኛ ሁሉ ይልቅ በጽኑ የታሰረ አይደለምን?

 በድጋሜ ፣ አንድ ሰው ራሱን ለፍትህ አሳልፎ ሲሰጥ፣ እርሱ ደግሞ በሌላ እስራት የታሰረ
አይደለምን?
 ራሱን ለእይታዎች (ጊዜዎች) ሲሰጥስ?

 እነዚህ ከእስራት ሁሉ ይልቅ ጨካኞች አይደሉምን?

 ራስን ምክንያታዊ ላልሆነ ምኞትና ፍቅር አሳልፎ መስጠትስ ምንድነው?


 እነዚህን እስራት የሚቆርጥላችሁ ማን ነው?
የቀጠለ…………
 ከዚህ እስራት እንዲፈቱ የእግዚአብሔር እርዳታ ያስፈልጋል።

 ነገር ግን ሁለቱም እስራት እና አውሎ ነፋሶች ሲሆኑ፣ የአደጋው መጠን ምን


ያህል ትልቅ እንደሆነ አስቡ።

 ከመካከላቸው ለመጥፋት የማይበቃው ማን ነው?

 ረሃቡ፣
 አውሎ ነፋሱ፣
 የተሳፈሩ ሰዎች ክፋት፣
 የወቅቱ አለመመጣጠን፣ ተፈጥሮዊ ወቅት፣ ዝናቡ፣ ብርዱ፣
ማዕበሉ፣ ጨለማው?
 ነገር ግን ከዚህ በተጻራሪ፣ የቅዱስ ጳውሎስ ክብረ ተገለጠ።
የቀጠለ…………
 አሁን/ ዛሬም እንደዚያህ ነው፡-
 ቅዱሳንን በአጠገባችን እንዲቆሙ እንለምን፣ የዚህ ዓለም ማዕበልም አይመጣም፣ አያሸንፈንም።
 ይልቁንም አውሎ ነፋሱ ቢመጣም፣ ታላቅ መረጋጋት፣ ጸጥታ እና ነጻነት ከመከራ ዉስጥ ይሆናል።
 ምሳሌ፦ ያች መበለት ቅዱስ ወዳጅ ነበራት።
 ቅዱስ ወዳጅ ስለ ነበራት ልጅዋ ከሞት ዳነ።
 ልጇን ደግሞ በሕይወት ተቀበለችው። (1ኛ ነገሥት 17:17.)...
 የቅዱሳን ባሉበት ቦታ መከራ፣ ህመም አይኖርም፥ መከራ፣ ስቃይ ከመጣብን እኛን ለመፈተሽ
እና ለታላቁ የእግዚአብሔር ክብር ለመብቃት ነው።

 የቤትህን ወለል በእንደዚህ ዓይነት እግሮች እንዲረግጥ ተለማመድ፥ ክፉ መንፈስም በዚያ


አይረግጥም።

 የጣፈጠ መዓዛ/ ሽታ ባለበት ስፍራ መጥፎ ጠረን ስፍራ አያገኝምና።


 ስለዚህ ቅዱስ ቅባት/ሽታ ባለበት በዚያ ርኩስ መንፈስ የለም።

 በመልካም መዓዛ/ ሽታ/ አጠገብ ያለ ሰው ደስ ይሰኛታል፣ ይማርካል፣ነፍስንም ያድሳል።


 እሾህ ባለበት አውሬ አለ፤ እንግዳ ተቀባይነት ባለበት እሾህ የለም፤
 ምጽዋት በገባችበት ጊዜ ከማንኛውም ማጭድ ይልቅ በትጋት እሾህን ታጠፋለች ከእሳትም ይልቅ
በኃይል።
የቀጠለ…………

 አትፍራ፥ ቀበሮዎች አንበሶችን እንደሚፈሩ። (ክፉ ሰው) የቅዱሳንን መንገድ ይፈራል። “ጻድቅ
እንደ አንበሳ ደፋር ነው” ይላልና። (ምሳ. 28፡1
 1) እነዚያን አንበሶች ወደ ቤታችን እናምጣቸው፥ አራዊትም ሁሉ ይሸሻሉ።
 አንበሶች ማገሳት አያስፈልጋቸውም፣ ነገር ግን በቀላሉ ድምፃቸውን ሲያሰሙ ሌላው አራዊት
ይሸሻል።
 አራዊትን ለማባረር አንበሳ ያን ያህል ጩኸት ማሰማት አይጠበቅበትም፤ ትንሽ ድምጽ ሲያሰማ/
ሲያጉረመርም ይፈራሉ።
 ልክ እንደዚሁ የጻድቅ ጸሎት ክፉ መናፍስት እንዲሸሹ ያደርጋል።

 ምን አልባት እንደዚህ ያሉ ሰዎች አሁን የት ይገኛሉ ብላችሁ ትጠይቁ ይሆናል?

 ካመንን፣ ከፈለግናቸው፣ ከመከራው/ ከህመሙ/ መሳተፍ ከቻልን፣ በሁሉም ቦታ ይገኛሉ።


 የት ተመለከትካቸው? ንገረን?
 ይህን ተግባር መቼ በእጃችን እናደርጋለን?
 መቼ ነው የራሳችን ሥራ የምናድርገው?
 ከመከራው/ ከህመሙ መሳተፍ ካልቻልክ አታገኘዉም፣ አንተ ካልፈልክ በተአምር አይሆንም።
 ማቴ 7፡7 ፈልጉ ታገኛላችሁ ተብሏልና።
 በበርሃ የሚኖሩትን ጠይቋቸው። ከወርቅና እና ከብር ርቀው የሚኖሩትን።
 ቅዱሳን በመላው ዓለም፣ በየቦታዉ ይገኛሉ።

 ወደ ቤትህ መጥተው መቀበል ባትችል እንኳ። አንተ ወደ እነሱ ሂድ። ከእነሱ ጋር ኑር። በማደሪያቸውም እደር።
 በዚያዉም ትደሰታለህ፣ በረከትም ታገኛለህ።
 ታላቁ ነገር ከቅዱሳን በረከት ማግኘት ነውና። በቅዱሳን መባረክ ነዉና።
 የቅዱሳን ጸሎታቸው ከእግዚአብሔር ምህረት ያስገኝልናል።

You might also like