Download as doc, pdf, or txt
Download as doc, pdf, or txt
You are on page 1of 8

እንደ ሕጉ ልማድ ያደርጉለት ዘንድ ሕጻኑን ጌታ ኢየሱስን #በአስገቡት ጊዜ እርሱ ደግሞ ተቀብሎ አቀፈው::

#እግዚአብሔርንም እየባረከ እንዲህ አለ:-'#ጌታ ሆይ! አሁን እንደ ቃልህ ባሪያህን በሰላም# ታሰናብተዋለህ:: ዓይኖቼ
በሰዎች ሁሉ ፊት #ያዘጋጀኸውን ማዳንህን አይተዋልና:: ይህም ለአሕዛብ ሁሉን የሚገልጥ ብርሃን: #ለሕዝብሕም
ለእስራኤል ክብር ነው::' #ዮሴፍና እናቱም ስለ እርሱ በተባለው #ነገር ይደነቁ ነበር:: "[ሉቃ. 2:27]

#እንኳን_አደረሳቹሁ_የእምየ_ተዋሕዶ_ልጆች

የካታት (፰)ታስበው ለሚውሉ #ቅድስተ #ቅዱስን

#በዓለ #ስምዖን🙏🕯

#ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደ በስምንተኛው ቀን (ጥር ፮ ቀን) በኦሪቱ ሕግ መሠረት ሥርዓተ
ግዝረትን ፈጽሟል በተወለደ በዐርባኛ ቀኑ (የካቲት ፰ ቀን) ደግሞ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቷል (ጌታችንመድኀኒታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ ከተወለደበት ከታኅሣሥ ፳፱ቀን ጀምረን ስንቈጥር የካቲት ፰ /፵ቀን ነው ፡፡)

በኦሪቱ ሥርዓትም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እና ጠባቂዋ ጻድቁ ዮሴፍ ለመሥዋዕት የሚቀርቡ
#እንስሳትን ይዘው ጌታችንን በዚህች ዕለት ወደ ቤተ #መቅደስ ወሰዱት ፡፡

በዚያም ክርስቶስ ኢየሱስን ሳያይ #እንደማይሞት የተነገረው ስምዖን የሚባል ሰው ነበር ይህስ እንደምንነው ? ቢሉ
የኦሪት መጻሕፍትን ከዕብራይስጥ ወደ ጽርዕ (ግሪክ) ቋንቋ እንዲተረጕሙ ከታዘዙ ሰብዓ ሰዎች (ሊቃናት) መካከል
አንዱ ነቢዩ ስምዖን ነበር ።

ይህ ነቢይ ትንቢተ ኢሳይያስ ደረሰውና እየተረጐመ ሳለ ‹‹እነሆ ድንግል #ትፀንሳለች፤ ወንድ ልጅንም ትወልዳለች
ስሙንም ዐማኑኤል ትለዋለች » ከሚለው ኀይለ ቃል በደረሰ ጊዜ በቀጥታ ቢተረጕመው ንጉሡ እንደማይቀበለው
በማሰቡ፤ እርሱም ‹‹ይህ እንዴት ሊኾን ይችላል?›› ብሎ በመጠራጠሩ #ድንግል›› የሚለውን ቃል ወለት›› (#ሴት
ልጅ) ብሎ ተረጐመው፡፡

ተኝቶ በነቃ ጊዜም #ወለት›› የሚለው ቃል ተፍቆ #ድንግል›› ተብሎ ተጽፎ አገኘና እርሱም ‹‹ድንግል››ን ፍቆ
‹‹ወለት›› ብሎ ይጽፋል ዳግመኛም ለሁለተኛና ጊዜ ተኝቶ ሲነቃ ቃሉ እንደ ነበረ ኾኖ ያገኘዋል ፡፡

ለሦስተኛ ጊዜ ቃሉን እፍቃለሁ ሲልም የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦ ‹‹የተጠራጠርኸውን፣ ከድንግል የሚወለደው
ክርስቶስን #እስከምታየውና እስከምትታቀፈው ድረስ #ሞትን_አትቀምስም፤ብሎታል፡፡

#መሲሑን ሳታይ አትሞት የተባለው ነቢዩ ስምዖን አርጅቶ ከአልጋ ተጣብቆ ለሦስት መቶ ዓመታት ያህል ከኖረ በኋላ
ትንቢቱ ተፈጽሞ፣ ዘመኑ ደርሶ ክርስቶስ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በተወለደ #በ፵ ቀን ወደ ቤተ
መቅደስ እስከ በገባበት ዕለት መንፈስ ቅዱስ አነሳሥቶ ወደ ምኵራብ ወሰደው፡፡

በዚያም ጌታችንን #ከእመቤታችን ተቀብሎ ለመታቀፍ ታድሏል። የምትጠብቀው ሕፃን ይህ ነው›› ብሎ


እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በነገረው ጊዜም ታውረው የነበሩ ዓይኖቹ ተገልጠዋል፤ ሰውነቱም ታደሷል፡፡

ነቢዩም #የእግዚአብሔርን #ማዳን በዓይኑ በማየቱ፣ ከደዌው በመፈወሱ እና ከእርጅናው በመታደሱ በአጠቃላይ
በተደረገለት ድንቅ #ተአምር ዅሉ በመደሰቱ እግዚአብሔርን አመስግኗል፡፡
አቤቱ ባሪያህን ዛሬ አሰናብተኝ፤ ዓይኖቼ ማዳንህን አይተዋልና ፤ በሚለው ትንቢታዊ መዝሙሩም #የእግዚአብሔርን
ማዳን በዓይኔ ስላየሁ #እንግዲህስ ልረፍ በማለት ሞቱን #ተማጽኗል፡፡

🥀ወስብሐት ለእግዚአብሔር ❤🍃

ተዋሕዶን እንወቅ።:
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

❖ እንኳን አደረሳችሁ ❖

✝✝" በዓለ ስምዖን "✝✝

✝ ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን ጌታ በተወለደ በ 40 ቀኑ ራሱ የሠራውን ሕግ ይፈፅም ዘንድ ወደ ቤተ መቅደስ


ገብቷል። እንደ ሥርዓቱም እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምና አገልጋዩዋ ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ የርግብ ግልገሎችና ዋኖስ
አቅርበዋል። ለ 284 ዓመታት የአዳኙን (የመሢሁን) መምጣት ይጠብቅ የነበረው አረጋዊው ስምዖን በዚህች ዕለት
ስላየውና ስለታቀፈው ዕለቱ በዓለ ስምዖን ይባላል። (ሉቃ. 2፥ 22) ከዘጠኙ የጌታ ንዑሳን በዓላት አንዱ ነው። ይሕስ
እንደ ምን ነው ቢሉ ከዓለም ፍጥረት በ 5,200 ዓመታት (ማለትም ከክርስቶስ ልደት 300 ዓመታት በፊት) በጥሊሞስ
የሚሉት ንጉሥ በግሪክ ነገሠ። በጊዜውም በኃይለኝነቱ ሁሉን አስገብሮት ነበርና "ዓለሙን እንደ ሰም አቅልጬ፥ እንደ
ገል ቀጥቅጬ ገዛሁት። ምን የቀረኝ ነገር አለ?" ሲል ተናገረ። ባሮቹም "አንድ ነገር ቀርቶሃል። በምድረ እሥራኤል
ጥበብን የተሞሉ 46 መጻሕፍት አሉ። እነርሱን አስተርጉም" አሉት። ያን ጊዜ እሥራኤላውያንን አስገብሯቸው ነበርና
46 ቱን የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ከ 72 ምሑራን (ተርጉዋሚዎች) ጋር እንዲያመጡለት አዛዦቹን ላከ። እነርሱም
46 ቱን መጻሕፍተ ብሉይ ኪዳን ከ 72 ምሑራን ጋር አመጡለት።

✝አይሁድ ክፋተኞች መሆናቸውን ሰምቷልና 36 ድንኩዋን አዘጋጅቶ፥ ጥንድ ጥንድ ሆነው እንዲሠሩ፥ ሲተረጉሙ
እንዳይመካከሩ 36 ጠባቂዎችን ሾመባቸው። ይህ ነገር ለጊዜው ከንጉሡ ቢመስልም ጥበቡ ግን ከእግዚአብሔር ነው።
ምክንያቱም በጊዜ ሒደት መጻሕፍተ ብሉያት በአደጋ እንደሚጠፉ ያውቃልና ሳይበረዙ ለሐዲስ ኪዳን ክርስቲያኖች
ለእኛ እንዲደርሱ ነው። ስለዚህም ከክርስቶስ ልደት 284 ዓመት በፊት 46 ቱም ሁሉም መጻሕፍት (ብሉያት)
ከእብራይስጥ ወደ ጽርዕ ልሳን በ 70 ው ሊቃናት አማካኝነት ተተረጐሙ። (በእርግጥ ከዚያ አስቀድሞ መጻሕፍት
(ብሉያት) ወደ ሃገራችን መምጣቸውና ወደ ግዕዝ ልሳን መተርጐማቸውን ሳንዘነጋ ማለት ነው) ወደ ዋናው ጉዳያችን
ስንመለስ ከ 70 ው ሊቃናት መካከል በእድሜው አረጋዊ የሆነ (እንደ ትውፊቱ ከሆነ 216 ዓመት የሆነው) ስምዖን
የሚሉት ምሑረ ኦሪት ነበር። በፈቃደ እግዚአብሔር ለእርሱ መጽሐፈ ትንቢተ ኢሳይያስ ደርሶት እየተረጐመ
ምዕራፍ 7 ላይ ደረሰ።

✝ቁጥር 7 ላይ ሲደርስ ግን "ናሁ ድንግል ትጸንስ፥ ወትወልድ ወልደ" የሚል አይቶ "አሁን እንኳን የአሕዛብ ንጉሥ
የእሥራኤልስ ቢሆን ድንግል በድንግልና ጸንሳ ትወልዳለች ብለው እንዴት ያምነኛል !" ሲል አሰበ። "በዚያውስ ላይ
ኢሳይያስ በምናሴ የተገደለው ስለዚህ አይደል!" ብሎ ቃሉን ሊለውጠው ወሰነ። አመሻሽ ላይም 'ድንግል' የሚለውን
'ወለት-ሴት ልጅ' ብሎ ቀየረው። እርሱ ሲያንቀላፋ ቅዱስ መልአክ ወርዶ 'ድንግል' ብሎ አስተካከለው። ከእንቅልፉ
ሲነቃ ግራ ተጋብቶ እንደ ገና ፍቆ ቀየረው። አሁንም መልአኩ 'ድንግል' ሲል ቀየረበት። 3 ጊዜ እንዲህ ከሆነ በኋላ ግን
መልአኩ ተገልጦ ገሰጸው። በዚያውም ላይ "ይህችን ድንግልና መሲሑን ልጇን ሳታየውና ሳትታቀፈው ሞትን
አታይም" ብሎት ተሰወረው። አረጋዊ ስምዖን ከዚያች ዕለት በኋላ የመድኅን ክርስቶስን መምጣት ሲጠብቅ ለ 284
ዓመታት የአልጋ ቁራኛ ሁኖ ኖረ። አካሉም አለቀ።

✝ለስም አጠራሩ ስግደት የሚገባው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው በሆነበት በዚያ ሰሞን እመቤታችን ቅድስት
ድንግል ማርያምና ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ ወደ ቤተ መቅደስ ወጡ። ሕግን የሠራ ጌታ እርሱ 'ፈጻሜ ሕግ' ይባል ዘንድ
የርግብ ግልገሎችን (ዋኖሶችን) ይዘው በተወለደ በ 40 ቀኑ ወደ ቤተ መቅደስ አስገቡት። በዚህች ቀንም ቅዱስ መልአክ
መጥቶ ቅዱስ ስምዖንን ከአልጋው ቀሰቀሰው። ተስፋ የሚያደርገው አዳኙ (መሲሑ) እንደ መጣም ነገረው። ይህን
ጊዜ አረጋዊው አካሉ ታድሶ እንደ 30 ዓመት ወጣት እመር ብሎ ከአልጋው ተነሳ። እንደ በቅሎ እየሠገረም ወደ
መቅደስ ወጣ። በዚያ መሲሑን (ፈጣሪውን) ሲመለከት እንደ እንቦሳ ዘለለ። ቀረብ ብሎም ሕጻን ጌታን ከድንግል እናቱ
እጅ ተቀበለው። ከደስታው ብዛት የተነሳም "ይእዜ ትስዕሮ ለገብርከ፥ በሰላም እግዚኦ በከመ አዘዝከ - አቤቱ ባሪያህን
እንደ ቃልህ በሰላም አሰናብተው" ሲል ጸለየ። ትንቢትንም ተናገረ። በዚያችው ዕለትም ዐርፎ ተቀበረ።

✝"✝ ሐና ነቢይት ✝"✝

✝ዳግመኛ በዚህች ቀን አረጋዊቷን ነቢይት ቅድስት ሐናን እናስባለን። ይህች ቅድስት ትውልዷ ከነገደ አሴር ሲሆን
አባቷ ፋኑኤል ይባላል። በትውፊት ትምሕርት ሐና የተዳረችው በልጅነቷ (በ 12 /15/ ዓመቷ) ነው። ለ 7 ዓመታት
ከልጅነት ባሏ ጋር ኖራ ዕድሜዋ 19 (22) ሲደርስ ሞተባት። እንደ እሥራኤል ልማድ ሌላ እንድታገባ ብትጠየቅም
'እንቢ' ብላ መበለት ሆነች። ራሷንም ለእግዚአብሔር አሳልፋ ሰጠች። በቤተ መቅደስም ለ 84 ዓመታት ለፈጣሪዋ
ተገዛች። ፈጽማ ትጸልይና ትጾም ነበርና በእነዚህ ሁሉ ዓመታት ውጪውን አልተመለከተችም። ለእርሷ 103 (106)
ዓመት ሲሆን መድኃኒታችን ተወለደ። በዚህች ቀን ወደ ቤተ መቅደስ ሲገባ ተመልክታም ጌታን ባረከች። ደስ
እያላትም ትንቢትን ተናገረች። ወደ ቤቷ ገብታም ነፍሷን ሰጠች። (ሉቃ. 2፥ 36-38)

❖አረጋዊ ስምዖንን ከድካም አልጋ ያነሳ አምላከ ቅዱሳን እኛንም ድካመ ነፍስን ከሚያመጣ የበደል ምኝታ በቸርነቱ
ያንሳን። ቸሩ መድኃኒታችን ተርፎ ከሚቀረው ዘመን ዕድሜ ለንስሃ፥ ዘመን ለፍሥሐ አይንሳን። ከቅዱሳኑ በረከትም
አይለየን።

✞የካቲት 8 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት


1.ቅዱስ ስምዖን አረጋዊ
2.ቅድስት ሐና ነቢይት (የፋኑኤል ልጅ)
3.ቅድስት ዓመተ ክርስቶስ እግዝእት
4.አባ ኤልያስ ገዳማዊ (በትህትና ያጌጠ ቅዱስ ሰው)

✝ ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ሙሴ ሊቀ ነቢያት
2.ኪሩቤል (አርባዕቱ እንስሳ)
3.አባ ብሶይ (ቢሾይ)
4.አቡነ ኪሮስ
5.አባ ሳሙኤል ዘደብረ ቀልሞን
6.ቅዱስ ማትያስ ሐዋርያ (ከ 12 ቱ ሐዋርያት)

✝✝"✝ እንደ ሕጉ ልማድ ያደርጉለት ዘንድ ሕጻኑን ጌታ ኢየሱስን በአስገቡት ጊዜ እርሱ ደግሞ ተቀብሎ አቀፈው።
እግዚአብሔርንም እየባረከ እንዲህ አለ፤ 'ጌታ ሆይ! አሁን እንደ ቃልህ ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ። ዓይኖቼ
በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ማዳንህን አይተዋልና። ይህም ለአሕዛብ ሁሉን የሚገልጥ ብርሃን፥ ለሕዝብሕም
ለእስራኤል ክብር ነው። ' ዮሴፍና እናቱም ስለ እርሱ በተባለው ነገር ይደነቁ ነበር። ✝"✝ (ሉቃ. 2፥ 27)

[በመምህር ዮርዳኖስ አበበ]


✝✝✝ወስብሐት ለእግዚአብሔር✝✝✝
✝✝✝ወለወላዲቱ ድንግል✝✝✝
✝✝✝ወለመስቀሉ ክቡር ይቆየን✝✝✝

. ዓ ይ ኖ ቼ፡ማ ዳ ን ህ ን፡አ ይ ተ ዋ ል ና
༺◉❖═───◉●◉◉●◉────═❖◉༻
በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በየዓመቱ #የካቲት_8 ቀን ከሚከበሩ በዓላት መካከል የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ ወደ ቤተ መቅደስ መግባት፣ የነቢዩ ስምዖን ልደት (መታደስ) እና የነቢዪት ሐና ዕረፍት በስፋት ይነገራል ፡፡

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደ በስምንተኛው ቀን (ጥር 6 ቀን) በኦሪቱ ሕግ መሠረት ሥርዓተ
ግዝረትን ፈጽሟል በተወለደ በዐርባኛ ቀኑ (የካቲት 8 ቀን) ደግሞ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቷል (ጌታችንና መድኀኒታችን
ኢየሱስ ክርስቶስ ከተወለደበት ከታኅሣሥ 29 ቀን ጀምረን ስንቈጥር የካቲት 8 ዐርባኛው ቀን ነው፡፡)

በኦሪቱ ሥርዓትም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እና ጠባቂዋ ጻድቁ ዮሴፍ ለመሥዋዕት የሚቀርቡ
እንስሳትን ይዘው ጌታችንን በዚህች ዕለት ወደ ቤተ መቅደስ ወሰዱት፡፡

በዚያም ክርስቶስ ኢየሱስን ሳያይ እንደማይሞት የተነገረው ስምዖን የሚባል ሰው ነበር ይህስ እንደምንነው ? ቢሉ
የኦሪት መጻሕፍትን ከዕብራይስጥ ወደ ጽርዕ (ግሪክ) ቋንቋ እንዲተረጕሙ ከታዘዙ ሰብዓ ሰዎች (ሊቃናት) መካከል
አንዱ ነቢዩ ስምዖን ነበር ።

ይህ ነቢይ ትንቢተ ኢሳይያስ ደረሰውና እየተረጐመ ሳለ ‹‹እነሆ ድንግል ትፀንሳለች፤ ወንድ ልጅንም ትወልዳለች
ስሙንም ዐማኑኤል ትለዋለች » ከሚለው ኀይለ ቃል በደረሰ ጊዜ በቀጥታ ቢተረጕመው ንጉሡ እንደማይቀበለው
በማሰቡ፤ እርሱም ‹‹ይህ እንዴት ሊኾን ይችላል?›› ብሎ በመጠራጠሩ ‹‹ድንግል›› የሚለውን ቃል ‹‹ወለት››
(ሴት ልጅ) ብሎ ተረጐመው፡፡

ተኝቶ በነቃ ጊዜም ‹‹ወለት›› የሚለው ቃል ተፍቆ ‹‹ድንግል›› ተብሎ ተጽፎ አገኘና እርሱም ‹‹ድንግል››ን ፍቆ
‹‹ወለት›› ብሎ ይጽፋል ዳግመኛም ለሁለተኛና ጊዜ ተኝቶ ሲነቃ ቃሉ እንደ ነበረ ኾኖ ያገኘዋል ፡፡

ለሦስተኛ ጊዜ ቃሉን እፍቃለሁ ሲልም የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦ ‹‹የተጠራጠርኸውን፣ ከድንግል የሚወለደው
ክርስቶስን እስከምታየውና እስከምትታቀፈው ድረስ ሞትን አትቀምስም፤›› ብሎታል፡፡

‹‹መሲሑን ሳታይ አትሞትም›› የተባለው ነቢዩ ስምዖን አርጅቶ ከአልጋ ተጣብቆ ለሦስት መቶ ዓመታት ያህል
ከኖረ በኋላ ትንቢቱ ተፈጽሞ፣ ዘመኑ ደርሶ ክርስቶስ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በተወለደ በዐርባኛው
ቀን ወደ ቤተ መቅደስ እስከ በገባበት ዕለት መንፈስ ቅዱስ አነሳሥቶ ወደ ምኵራብ ወሰደው፡፡

በዚያም ጌታችንን ከእመቤታችን ተቀብሎ ለመታቀፍ ታድሏል። ‹‹የምትጠብቀው ሕፃን ይህ ነው›› ብሎ


እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በነገረው ጊዜም ታውረው የነበሩ ዓይኖቹ ተገልጠዋል፤ ሰውነቱም ታደሷል፡፡

ነቢዩም የእግዚአብሔርን ማዳን በዓይኑ በማየቱ፣ ከደዌው በመፈወሱ እና ከእርጅናው በመታደሱ በአጠቃላይ
በተደረገለት ድንቅ ተአምር ዅሉ በመደሰቱ እግዚአብሔርን አመስግኗል፡፡

‹‹አቤቱ ባሪያህን ዛሬ አሰናብተኝ፤ ዓይኖቼ ማዳንህን አይተዋልና ፤ » በሚለው ትንቢታዊ መዝሙሩም


‹‹የእግዚአብሔርን ማዳን በዓይኔ ስላየሁ እንግዲህስ ልረፍ›› በማለት ሞቱን ተማጽኗል፡፡
በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶም የክርስቶስን የዓለም ቤዛነትና ክርስቶስ በሥጋው በሚቀበለው መከራ እመቤታችን መራራ
ኀዘን እንደሚደርስባት፤ እንደዚሁም ጌታችን ለሚያምኑበት ድኅነትን፣ ለሚክዱት ደግሞ ሞትን የሚያመጣ አምላክ
እንደ ኾነ የሚያስገነዝብ ትንቢት ተናግሯል፡፡

የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ለነቢዩ ስምዖን የተደረገለትን ታላቅ ሥራ ሲያደንቁ እንዲህ ይገልጹታል፤ ‹‹የማኅሌት
መዝሙርን በማዘጋጀት እያከበርሁትና እያደነቅሁት ከሱራፌል ክብር ለሚበልጠው ለስምዖን ክብር ሰላም እላለሁ፡፡
እርሱ መለኮትን በእጁ ታቅፏል፤ እሳቱንም ዳሷልና እቅፎቹን እጅ እነሳለሁ፤ እጆቹንም እስማለሁ።››

የሊቁ ስምዖን አረጋዊ በረከት እና ምልጃ አይለየን!

+ #እርቃንን_አለመሸፈን +

መልካም ስላልሆነው አለባበስ "ሊቁ ዲዲሞስ" ከአዳምና ሔዋን በቅጠል እርቃናቸውን ከመሸፈናቸው ጋር በማያያዝ
ጣፍጭ ፍቺ ይሰጠናል አንዲህ ይላል ፦ ‹‹ አዳምና ሔዋን የበለስን ቅጠል ማገልደማቸው ኃጢአታቸውን ቀላል
ለማድረግ ለመደበቅ የሚያደርጉትን ትግል የሚያሳይ ነው።›› አኹን ኹላችንም ለሰራነው ኃጢአት የምንሰጠው
ሽፍን ቀለል ያለ አይደለምን? በማለት ሊቁ ይጠይቃል። በእርግጥ አኹን ኹላችንም ብንኾን አእምሯችን
በኃጢአታችን ምክንያት ስለታወረብን ከፍ አድርገን ማልቀስ ንስሐ መግባት ሲገባን "ችግር የለውም ቀላል ነው"
በሚል በሸታ ሕሊናችን ቆስሎ ከገባንበት የኃጢአት ጉድጓድ መውጣት አቅቶን ስንቅበዘበዝ እንታያለን። ያልሰራነው
የኃጢአት ስራ የለም ኾኖም ነገሮችን በሙሉ ቅጣት እንደማይገባቸው ተራ ክስተት አድርገን ለራሳችን ራሳችንን
እያሳመንን እንገኛለን።

ምን አለበት ዘና የሚያደርጉ ልብሶችን ብንለብስ? ለምን ታጨናንቁናላቹሁ? መንገዱ ሁሉ ጠባብ አድርጋቹሁ


አትወጥሩን። አንዳንድ እኅቶች ደግሞ “ወንድሞች የእኛ አለባበስ እያዩ ስለተሰናከሉ እኛ ምን አገባን ! እነርሱ
እራሳቸውን መቆጣጠር አለባቸው! በእነርሱ ጥፋት እኛ ልንጠየቅ አይገባንም እንዲህ አትልበሱ እያላቹሁ ቀላሉን ነገር
አታካብዱብን።” ይላሉ። ይህ ሁሉ የኃጢአት ደጋግሞ ከመብላት የተነሳ በሕይወታችን ውስጥ የሚገኝ ያለ ፈተና
ነው።

ድኅነት ተራ ነገር አይደለም፤ በብዙ መከራና ጭንቅ የሚገኝ የማያልቅ ፀጋ እንጂ። እኅቴ ሆይ! ለወንድምሽ መሰናክል
ምክንያት ትኾኚ ዘንድ እንዴት መረጥሽ? የራስሽን ፈቃድ ከምትወጂ የክርስቶስን ፍቃድ ብትወጂስ አይሻልሽምን ?
ስለወንድምሽ ብለሽ ብቻ ሳይኾን ስለ አምላክሽ ብለሽ ኃጢአትሽን ቀላል አድርገሽ አታስቢ፥ ይልቁንም ከልብሽ
በድርጊትሽ ተጸጽተሽ ክርስቶስን ይምርሽ ዘንድ ጠይቂ። (መጽሔተ ወራዙት ዘኦርቶዶክስ ዲያቆን ዮሐንስ ጌታቸው
ገጽ-86)

#ይህን_ቃል_አስታውሱ! “ከነዚህ ከታናናሾች አንዱን ከማሰናከል ይልቅ የወፍጮ ድንጋይ በዐንገቱ ታስሮ ወደባሕር
ቢጣል ይሻለው ነበር።” [ማቴ. 18፥6፤ ማር. 9፥42፤ ሉቃ. 17፥2]
##########
ተሰናባቹ ሽማግሌ

| ጃንደረባው ሚድያ | የካቲት 2016 ዓ.ም.|

✍🏽 ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ እንደጻፉት


በሕይወት መጨረሻ፤ በዘመን ፍጻሜ ላይ የተመኙትን ማግኘት እጅግ ደስ የሚያሰኝ ነገር ነው። የሰው ልጅ መንገድ
በፍለጋ የተሞላ ነው። አንዳንዱ የተመኘውን አግኝቶ ደስ ብሎት ወደ መቃብር ይወርዳል፤ አንዳንዱም ወደ ተመኘው
ዓለም ሲገሰግስ ሞት ያደናቅፈውና በምኞቱ ሳለ ነፍሱን ይነጠቃል።
በጌታ የልደት ዘመን ከነበሩትና በቅዱስ ወንጌል ስማቸው ከተመዘገቡት ሰዎች መካከል ድንቅ ነገር የተመኘ ምኞቱም
የተከናወነችለት ስምዖን የሚባል ሰው አለ። በዚህ ስም የሚጠሩ ብዙ ሰዎች ስላሉ ከእነዚያ ለመለየት ስምዖን አረጋዊ
ተብሎ ይጠራል። ኢየሱስ ክርስቶስ በምድር ሲመላለስ በነበረ ጊዜ ብዙ ስምዖኖች አግኝተውታል። ለምጻሙ ስምዖን
ማቴ 26፥6፣ ፈሪሳዊው ስምዖን ሉቃ 7፥40፣ ጴጥሮስ የተባለው ስምዖን ዮሐ 1፥42፣ እና ሌሎችም ማቴ 10፥4።
እነዚህ ሁሉም ስማቸው እንጅ ግብራቸው የተለያየ ነው። እነዚህ ሁሉም አንድ የሚያመሳስል ታሪክ ያላቸው ሲሆኑ
እሱም ጌታን ማየታቸው ነው። ሕይወት ግዙፍ አካል ኖሯት በሰዎች መካከል ስትመላለስ ማየት እጅግ ደስ የሚያሰኝ
ነገርም አይደል? በሰማይ ላይ የሚታዩት ፀሐይ እና ጨረቃ ሥጋ ለብሰው ብታገኟቸው አትገረሙም? ሚካኤልና
ገብርኤል ቤታችሁ መጥተው እንግዳ ቢሆኑላችሁስ ዜናውን ለሰው ሁሉ በደስታ አታወሩም ? መልሳችሁ አዎ ከሆነ
ለእነዚህ ሰዎች ከዚህ የሚበልጥ ነገር እንደተደረገላቸው አስተውሉ።
መላእክትን የሾመ፣ ፀሐይና ጨረቃን በማያረጅ ብርሃን የሸለመ እግዚአብሔር በሥጋ በመካከላቸው ሲመላለስ አዩት።
ከዚህ የሚበልጥ ምን አለ?
ከእነዚህ መካከል አንዳንዶቹ በሕይወት አጋጣሚ እንዲህ ያለውን መልካም ነገር ተቀብለዋል እንጅ አስበውበት
የተቀበሉት ስጦታ አይደለም። አንዳንዶቹ ግን የልባቸው ምኞት ይህች ነበረች − ክርስቶስን ማየት። ስምዖን አረጋዊ
ረዥም ዓመታትን በምድር ላይ የዘገየው ክርስቶስን ጥበቃ ነው። በዘመኑ ብዙ ነገር ሲከናወን አይቷል፤ ገናናው የጽርዕ
መንግሥት ዓለምን አሸንፎ ሲገዛ አይቷል። የጽርዕ መንግሥት ወድቆ የሮማ መንግሥት ሲቋቋምም ነበረ።
ከእስክንድር እስከ ቄሣር ብዙ ነገሮችን ተመልክቷል። የእሱ ፍለጋ ግን ገና አልተቋጨም። ስንቱን አየው? እስራኤል
ቀድሞ ለባቢሎን ሲሰግዱ፣ በኋላም ለግሪክ ሲያጎበድዱ፣ ቀጠሉና ለሮም ሲያደገድጉ አይቷል እሱ ግን ከቆመበት
የሃይማኖት መድረክ አልወረደም።
ነፍሱ የቃተተችለት ፍለጋ ገና አልተጠናቀቀም። ዘመን ሲለወጥ ሀሳቡን አልለወጠም። ንጉሥ ሲቀየር ተስፋው
አልተቀየረም። ግሪክ ወድቃ ሮም ስትተካ የእሱ ተስፋ አሁንም ባለበት ነው። የእግዚአብሔርን መምጣት ተስፋ
ያደርጋል። የመጡትም ሆነ ያለፉት ተሰፋውን አልፈጸሙለትምና ተስፋውን የሚፈጽምለት ይፈልጋል። የተሾሙትም
ሆነ የተሻሩት ከተስፋው ፈቀቅ አላደረጉትም። አሁንም ክርስቶስን ፍለጋ። እሱ የሚያርፈው የወገኖቹን የእስራኤልን
የመጽናናት ዘመን ሲመጣ ሲያይ ብቻ ነው። መንፈስ ቅዱስ ያደረበት ሰው ፍለጋ ይህ ነውና።
ዛሬ ለዚያ ሰው ምኞቱ ትፈጸምለት ዘንድ ወደ ቤተ መቅደስ በመንፈስ ወጣ። ሊያየው የተመኘው ክርስቶስም በዚያ
ቀን ወደ ቤተ መቅደስ የሚገባበት ቀን ነበረ። አገኘው፤ አየው፤ አቀፈው።
ሰምታችሁኛል ወገኖቼ? ስምዖን የእስራኤልን መድኃኒት አቀፈው እያልኋችሁ እኮ ነው። ዳንኤል ከረዥም ተራራ
የሰው እጅ ሳይነካው ተፈንቅሎ ሲወርድ ያየውን ድንጋይ ስምዖን በዐይኖቹ አየው ዳን 2፥34። ሙሴ በሲና ተራራ ላይ
ከሐመልማል ጋር ተዋሕዶ ያየውን የእሳት ነበልባል በክንዶቹ ታቀፈው ዘፀ 3፥2። አዳም በገነት መካከል ሲመላለስ
ሰምቶት የፈራውን ስምዖን ሳይፈራ ዳሰሰው ዘፍ 3፥10።
እንደ አዳም የሚናዘዝ፤ እንደ ቃኤል የሚቅበዘበዝ ሰው አልነበረምና ተስፋ ያደረገውን ክርስቶስን በዕቅፉ ይዞ
ምስጋናውን ቀጠለ። ቅዱስ ወንጌል እንደ ተናገረ እግዚአብሔርን እያመሰገነ እንዲህ አለ። “ጌታ ሆይ እንደ ቃልህ ዛሬ
ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ፤ዓይኖቼ በሰው ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ማዳንህን አይተዋልና” ሉቃ 2፥29−32
እያለ ምስጋናውንም ልመናውንም አቀረበ። የአንዳንድ ሰው ታሪክ በአንድ ቀን ተጀምሮ በአንድ ቀን የሚፈጸም ነው።
አንዳንዱ ሰው አንድ ቀን ብቻ ኖሮ የሚሞት ነው። ይህች ቀን ለዚህ ሰው እንዲሁ ናት። ከዚህች ቀን አስቀድሞም ሆነ
በኋላ በወንጌል ለመጻ’ፍ የሚያበቃ ታሪክ የለውም። ከኖረባቸው ቀናት መካከል ያለዚህች ቀን የኖረበት ቀን የለም።
ሊሎቹ ቀናት ይህችን ቀን ሲፈልግ የቆየባቸው ቀናት ስለሆኑ አይቆጠሩም። ዕድሜው አንድ ቀን ናት − ግን በቂ ናት።
ለዚህም ነው “ዛሬ ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ” ብሎ መለመኑ።
ሽማግሌው ስምዖን ስንብት ለመነ። ከሦስት መቶ ዓመት በላይ የቆየባትን ዓለም ሊሰናበታት ለመነ። ወዳጆቼን
ልሰናበት፣ ሀብቴን ንብረቴን ላስተናብር አላለም። እንደ ዮፍታሔ ልጅ ለድንግልናው፣ እንደ ዳዊትም ለሽምግልናው
ዕድሜ አልለመነም መሳ 11፥37፣ መዝ 102፥24። “አሰናብተኝ” አለ።
ምን ያደርጋል ዕድሜ፣ ምን ሊያደርግ መቆየት ሰው የሕይወቱን ግብ ካደረሰ። እነዚያ ሁሉ ዘመናት ከዚህች ቀን
አይበልጡም። በእነዚያ ሁሉ ዓመታት ያየው ነገር ሁሉ ዛሬ ያየውን አያኽሉም። ይሄ ሰው አንድ ዘመን ላይ በገናናው
ንጉሥ በበጥሊሞስ ቤተ መንግሥት በጥበባቸው ከተመረጡት ሰዎች መካከል ነበረ። ይሄ ሰው በምቹ የቤተ መንግሥት
ሰገነቶች የተመላለሰባቸው ቀናት በሕይወቱ ውስጥ አልፈዋል። እንዲህ ያለ የስንብት ልመና ሲያቀርብ አልተሰማም።
በንጉሥ ድንኳን ማደር፣ ከልዑላን ጋር መኖር እንደዚህች ቀን ያለ ደስታን እንደማያስገኝ ያውቀው ነበርና።
ዛሬ ግን ከዚህ የሚበልጥ ቀን እንደማይመጣ ያውቃልና አሰናብተኝ ብሎ ለመነ። ከዚህ በኋላ የሚመጣውን የሔሮድስን
ቀን ሳያይ ሊሞት ተመኘ።
የገሊላ አውራጃ በደም የምትሞላበት በእናቶቻቸው ዕቅፍ ያሉ ሕጻናት አንገት የሚቀላበት ዘመን ሳይደርስ መሞት
አማረው። አስጨናቂው ዘመን ሳይመጣ “ድምፅ በራማ ተሰማ ለቅሶና ብዙ ዋይታ ራሔል ስለ ልጆቿ አለቀሰች
መጽናናትም አልወደደችም የሉምና” የተባለው ቃል ሳይፈጸም መሄድ ፈለገ ማቴ 2፥18። የሚመጡት ዐመታት
የኢየሩሳሌም ቆነጃጅት በአደባባይ ደረታቸውን እየደቁ የሚያለቅሱባቸው ዘመናት ናቸው። የጽዮን ቆነጃጅት
በኢየሩሳሌም ተሰብስበው ሙሾ ያወጣሉ የሚሰማቸው ግን የለም፤ ከዚህ የሙሾ ጉባኤ መካፈል አልፈለገምና ዛሬ
አሰናብተኝ አለ።
በሚመጡት ቀናት በከተማ ሁከት ያስነሣውን በርባንን አስፈትተው ከሞት ማሠሪያ የፈታቸውን ኢየሱስን ስቀልልን
የሚል ትውልድ ይነሣል፤ ይህን ክፉ ትውልድ ሳያይ ሊሞት ወደደ። እንዴት በአንድ ዘመን ከቤተ ክህነትም ከቤተ
መንግሥትም ፍርድ ጎደለ፣ ድሀ ተበደለ የሚል ይጠፋል ? ከዚህ ቀንስ አታድርሰኝ ብሎ በጌታ ፊት ማንም ያላቀረበውን
ልመና አቀረበ − “ዛሬ ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ”።
ክርስቶሳውያን ወገኖቼ ሆይ! ከሕይወት የሚሻል ሞት አለ። ነቢዩ ዳዊት “ምሕረትህ ከሕይወት ይሻላል” መዝ
63፥3 ያለው እንዲህ ያለውን ሞት ነው። ከመኖርም የሚበልጥ አለመኖር አለ። ይልቁንም በሰማዩ መንግሥት
ለሹመት የምታበቃንን ቀን ካገኘናት ከዚያ በኋላ ያለው ቀን አይጠቅመንም። ወደ እግዚአብሔር የተመለስንበት፣
ንስሐ የገባንበት፣ ንስሐ በመግባታችን በሰማይ መላእክት ዘንድ ሰለኛ ታላቅ ደስታ የተደረገበት፣ ሥጋውን ደሙን
የተቀበልንበት ያ ቀን ለእኛ የአረጋዊው ስምዖነ ቀን ነው። ከኖርንበት ዓለም ለመሰናበት የመልቀቂያ ደብዳቤ ማቅረብ
ያለብን በዚህ ቀን ነው። ይህን ቀን ከቀናቶቻችሁ መካከል ፈልጉት።
ለጠፉ በጎች ግን ከዛሬ ነገ ይሻላቸዋልና “ዛሬ ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ” ብለው ስንብት ሊጠይቁ አይገባም።
ዓይኖቻቸው ማዳኑን ማየት ያለባቸው በምድር ሳሉ እንጅ በሰማይ አይደለም። የእግዚአብሔርን ምሕረት በምድር
እንጅ በሰማይ አናየውም። ይቅርታውን በምድር እንጅ በሰማይ አናገኘውም። ከካህናት እጅ ያልተቀበልናትን
የእግዚአብሔር መንግሥት ከሰማይ መላእክት እጅ የምንቀበል የሚመስለው ካለ ተሳስቷል። መንግሥተ ሰማያትን
በምድር ሳለ ያልተቀበላት በሰማይ አያገኛትም። በምድር ሳለ የመምህራንን ቃል የሚንቅ ሰው በሰማይ ያለ
የእግዚአብሔርን ድምጽ እንደማይሰማ ጌታ በቅዱስ ወንጌል አስጠንቅቋል ሉቃ 10፥16 የወጣንያን ጸሎት “አቤቱ
በእኩሌታ ዘመኔ አትውሰደኝ” መዝ 102፥24 ነው። የፍጹማን ጸሎት ግን ይህ ነው “ጌታ ሆይ እንደ ቃልህ ዛሬ
ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ” ሉቃ 2፥29
ማስታወሻ :- ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መልአክ የአራቱ ጉባኤያት መምህርና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት የሊቃውንት
ጉባኤ ሰብሳቢ ሲሆን የመጻሕፍት ደራሲም ናቸው:: ሊቅ ሊቃውንት የጃንደረባው ሚዲያ ዐምደኛ ሲሆኑ
ጽሑፎቻቸው ዘወትር ሰኞ የሚነበቡ ይሆናል::

https://janderebaw.org/ተሰናባቹ-ሽማግሌ/
#######
ወበጽባህ አሌሊ ገይሰ ኀበ ቤተ ክርስቲያን
❤በጥዋት ተነስተህ ወደቤተ ክርስቲያን ሂድ

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የምታገኘው በቤተ መቅደስ ውስጥ ነውና በጧት ከመኝታህ ተነስተህ ወደቤተ ክርስቲያን
ገስግስ

✍የ 300 ዓመት እድሜ ባለጸገው ስምዖን ጌታችንን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመቅደሱ ውስጥ አግኝቶ
አቅፎታል

✍የ 106 ዓመት እድሜ ባለጸጋዋ ሀና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመቅደሱ አግኝተዋለች


✍እመቤታችንና ሽማግሌው ዮሴፍ ጌታችን ሲፈልጉት መቅደሱ ውስጥ ከሊቃውንቱ ጋር አግኝተውታል

✍መካኒቱ ሀና በመቅደሱ ፊት ቁማ ጸልያ ጸሎቷ ተሰምቶ ሰሙኤልን ያህል ልጅ ወልዳለች

✍ካህኑ ዘካርያስ ያረጀችው ሚስቱ ኤልሳቤጥ ጸንሳ እንደምትዎልድ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል የነገረው በቤተ መቅደሱ
ውስጥ ነው

✍እመቤታችን ድንግል ማርያም ሰማያዊ ምግብ እና ሰማያዊ መጠጥ መልአኩ ያመጣላት በቤተ መቅደሱ ስትኖር ነው

✍ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ሐርና ወርቁን እያስማመች በቤተ መቅደሱ ስትፈትል አምላኳን እንድትዎልድ
መልአኩ አብስሯታል

✍እግሩ ሽባ ሁኖበት በቤተ መቅደሱ በር ወድቆ ሲለምን የነበረው ሰው ጴጥሮስና ዮሐንስ ለጸሎት ወደመቅደሱ
ሲሔዱ አግኝተው ፈውሰውታል

*ፈውስ ለማግኘት
*አዲስ ብስራት ለመስማት
*ሰማያዊ ምግብ ለማግኘት
*የጸለይከውን ጸሎት ለመሰማት
*ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ለማግኘት
በጧት ተነስተህ ወደቤተ ክርስቲያን ሂድ
ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ እንዳለው ደዊት ወደቤተ ክርስቲያን በመሄድህ ደስ ይበልህ
መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ

You might also like