Professional Documents
Culture Documents
Language Policy Edited
Language Policy Edited
Language Policy Edited
ክፍልአንድ
መግቢያ
1. የፖሊሲው ራዕይ
የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦች ሕዝቦች ቋንቋዎቻቸው በልጽገው
ለኹልአቀፍ ልማት ተጠቃሚነት የሚበቁበት፤ በሕዝቦች መካከል መከባበር፣
ብሔራዊ መግባባትና አንድነት የጎለበተበት ዲሞክራሲያዊ ሕብረተሰብ
ተፈጥሮ ማየት።
2. የፖሊሲው አስፈላጊነት
3
5) ለሳይንስና ቴክኖሎጂ ሥርፀትና ለዘመናዊ ኑሮ ማራመጃ ኹሉም ቋንቋዎች ብቁ
እንዲሆኑ የሚጎለብቱበትን ማዕቀፍ መፍጠር ስለሚያስፈልግ፤
4. የፖሊሲው ዓላማዎች
አጠቃላይ ዓላማዎች
1/ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገመንግስት
የተረጋገጡትን የቋንቋ መብቶች በተሟላ ሁኔታ በተግባር ለመተርጎም
እንዲቻል አስፈላጊ መዋቅሮችንና ተቋማትን፣ እንዲሁም የአፈጻጸም
ሥርዓትን መዘርጋት፤
2/ ልሳነብዙነትን በማበረታታት፣ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን በማጎልበትና አንድ
ማኅበረ-ፖለቲካዊ ኅብረተሰብን በመገንባት፣ እንዲሁም ሀገሪቱ ከአጎራባች
አገሮች ጋር ያላትን ትብብርና ትስስር በማሳደግ ረገድ ትልቅ ፋያዳ ያላቸው
ቋንቋዎች በፌዴራል መንግሥት ደረጃ የሚኖራቸውን ሚና ለማጠናከር
የሚያስችል የፖሊሲ ማዕቀፍ መፍጠር፤
ዝርዝር ዓላማዎች
1/ ትኩረት ያላገኙ ወይም የመጥፋት አደጋ የተደቀነባቸው ቋንቋዎች
ሥርዓታዊና ተቋማዊ እንክብካቤ የሚያኙበትንና ቋንቋዎቹ
የያዟቸው ባህላዊ ዕሴቶችና ዕውቀቶች ለየትውልዱ
የሚተላለፉበትን ኹኔታ ማመቻቸት፤
2/ የኢትዮጵያን የምልክት ቋንቋ ጨምሮ፣ የቋንቋና የሥርዓተ
ጽሕፈት ሀብታችንና ቅርሶቻችንን በምርምር፣በትምህርትና
በቴክኖሎጂ በመታገዝ መጠበቅ፣ ማልማትና ለሀገራዊ ልማት
መጠቀም፣
5
3/ የቋንቋ ልማት ለዜጎች ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ብቁ
ተሳትፎ የሚያገልግልበትን፣ ለሕዝቦች መቀራረብና አንድነት፤
እንዲኹም ዜጎች ኑሮዋቸውን ለመምራት የሚያስፈልጋቸውን
መረጃ የማግኘት ዕድል የሚያሰፋበትን ስልት መቀየስ፤
4/ የቋንቋ ልማት ሀገራዊ፤ ቀጠናዊ፤ አህጉራዊና እና አለምአቀፋዊ
ትስስርን ለማሳለጥና ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ተጨማሪ የስራ
ቋንቋዎችን ማካተት፤
5/ በቋንቋ ጥናት መስክ የተሰማሩ ተመራማሪዎች ለቋንቋ ልማት
የተሻለ አስተዋጽኦ የሚያደርጉበትን የተቀናጀ አሠራር ማስፈን፤
6/ ስለቋንቋዎችና ዘዬዎቻቸው ማበልጸግ አስፈላጊነት በተመለከተ
በተወሰኑ የሕብረተሰቡ ክፍሎች ውስጥ ያለውን የተዛባ አመለካከት
ለማስተካከል የተጠናከረ የግንዛቤ ማዳበርያ ሥራ የሚካሄድበትን
ስልት መቀየስ፤
7/ ጥንታዊ የኢትዮጵያ የጽሑፍ ቋንቋዎች በሀገሪቱ ውስጥ በጥልቀት
የሚጠኑበትንና ለባህልና ለቋንቋ ልማት የበለጠ አስተዋጽኦ
የሚያደርጉበትን፤ በእነዚህ ቋንቋዎች ውስጥ የሚገኘው ሀገር በቀል
ዕውቀት ለሕዝብ ተደራሽ የሚሆንበትን ኹኔታ ማመቻቸት፤
8/ ኢትዮጵያ ለኹሉም ቋንቋዎች እኩል ዕውቅና በመስጠትና
ልሳነብዙነትን በማበረታታት፣ ቋንቋዎች የጽሕፈት፣ የመንግሥታዊ
ሥራና የትምህርት መስጫ እንዲኹም የትምህርት ቋንቋ ማድረግ
የሚያስችሉ ሁኔታዎችን ማመቻቸት፡፡
ክፍል ኹለት
የፖሊሲው የትኩረት አቅጣጫዎችና ማስፈጸሚያ ስልትዎች
7
1/ ማንኛውም ሕዝባዊ አገልግሎት የሚሰጥ ድርጅት ለአካባቢው
ብሔር፣ ብሔረሰብና ሕዝብ ከተረጋገጡ የቋንቋ መብቶች ጋር
በሚጣጣም መልክ የመጠቀም መብት አለው፡፡
ስትራተጂዎች
6. የሥራ ቋንቋ
10
2/ ማንኛውም በኤሌክትሮኒክ የመገናኛ ብዙኃን (ቴሌቨዥን፣
ሬዲዮእናድረ ገጽ) አማካይነት ለመረጃ ማሰራጫ የሚውል ቋንቋ
ሥርዓተ ጽሕፈት እንዲኖረው ይደረጋል።
3/ ማንኛውም በኢትዮጵያ ውስጥ ለመሥራት ፈቃድ ያለው
የመገናኛ ብዙኃን በሀገርኛ ቋንቋ በሚያሰራጨው ፕሮግራም
ወይም የሚያትመው ዓምድ ውስጥ ሀገርኛ አቻ ቃላት ወይም
ሐረግ እንዲጠቀም፤ የአንድን ብሔር፣ ብሔረሰብና ሕዝብ ባህልና
ማንነት፣ ክብር በሚጠብቅ መልኩ እንዲሆን፤ የማዕረግ ስምን
በአግባቡ እንዲጠቀም፤ የአካባቢውን ባህላዊ የአክብሮትና
የጨዋነት የቋንቋ ሥነ ምግባር የተከተለ እንዲሆን ይደረጋል።
4/ ማንኛውም በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኝ የመዝናኛ ኢንዱስትሪ
ድርጅት በቃል፣ በጽሑፍ፣ በምስልና በትዕይንት መልክ
በሀገርኛቋንቋዎች የሚያቀርበው የኢንዱስትሪ ውጤት ወይም
ማስታወቂያ የአካባቢውን ባህላዊ የአክብሮትና የጨዋነት የቋንቋ
ሥነ ምግባር የተከተለ እንዲሆን ይደረጋል።
ስትራተጂዎችች
1/ የመገናኛ ብዙኃንና የመዝናኛ ኢንዱስትሪ የቋንቋ አጠቃቀም
የምልክት ቋንቋን ጨምሮ ልሳነብዙነትን የሚያራምድ እንዲሆን
አግባብ ያለው ሥርዓት ይዘረጋል።
2/ በመገናኛ ብዙኃንና በመዝናኛ ኢንዱስትሪ ዘርፎች ለተሰማሩ
ባለሙያዎች ስለቋንቋ አጠቃቀም ሥነምግባር አጫጭር ሥልጠና
የሚሰጥበት ስልት ይቀየሳል።
3/ በሥነምግባራዊ የቋንቋ አጠቃቀም ረገድ የግንዛቤ ማዳበሪያ
ሁነቶች፣ የውይይት መድረኮች፣ የመገናኛ ብዙኃን ዝግጅቶች፣
በራሪ ወረቀቶችና ሌሎች የመረጃ ምንጮች ተዘጋጅተው
ለተጠቃሚዎች በስፋት እንዲሰራጩ ይደረጋል።
4/ የመገናኛ ብዙኃንና የመዝናኛ ኢንዱስትሪ ባለሙያዎች የቋንቋ
አጠቃቀም የሚመራበት የሙያ ደንብ እና የሥነ ምግባር
መመሪያ (ፕሮፌሽናል ኮድ) ተዘጋጅቶ በሥራ ላይ ይውላል።
5/ የመገናኛ ብዙኃንና የመዝናኛ ኢንዱስትሪ የፈቃድ አሰጣጥና
ዕድሳት የቋንቋ አጠቃቀም ሥነምግባርን ባገናዘበ መልኩ ይኾናል፤
ለዚሁም ማስፈፀሚያ አስፈላጊው የአሠራር ሥርዓትና ሕግ
ይዘጋጃል።
8. ቋንቋና ትምህርት
1/ ማንኛውም የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰብ ሕዝብ ቋንቋውን
ለትምህርት አገልግሎት የማዋል መብቱ የተረጋገጠ ሲሆን
ቋንቋው በትምህርት ሥርዓቱ ውስጥ ሲካተት የቋንቋ መብትን
ከትምሀርት ጥራት ጋር ባገናዘበ መልኩ ይኾናል።
11
2/ የትምህርት ሥርዓቱ እያንዳንዱ ተማሪ ከአፍ መፍቻ ቋንቋው
በተጨማሪ አንድ ሌላ የፌዴራል ን የሚማርበትን ሥርዓተ
ትምህርት በመንደፍ ልሳነብዙነትን በኺደት ተግባራዊ ያደርጋል።
3/ ኢትዮጵያ ለሳይንስና ቴክኖሎጂ ሽግግር እና ከሌሎች ሀገሮች
ጋር ለሚኖራት የውጭ ግንኙነት አገልግሎት በማስፈጸሚያ
ስልታዊ ፍላጎቷ መሠረት የተመረጡ ዓለም አቀፍ ቋንቋዎች
በትምህርት ሥርዓቱ ውስጥ እንዲካተቱ ይደረጋል።
4/ በአገር አቀፍ ደረጃ የሚያስፈልገውን የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርና ግንኙነት
ለማጎልበት የፌዴራሉ ቋንቋዎች የአካባቢ መስተዳድሩንና የትምህርት
ቤቱን አቅም፣ እንዲሁም የአካባቢውን ኅብረተሰብ የቋንቋ አጠቃቀምና
ፍላጎት ባገናዘበ መልኩ በትምህርትነት ይሰጣሉ።
5/ ብሔሮች ብሔረቦችሕዝቦች አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረጉ
በራሳቸው ቋንቋ ወይም በብሄራዊ ክልላዊና በአገርአቀፍ
ሥርጭታቸውና በተናጋሪ ብዛታቸው መሠረት በሚመርጡት
ቋንቋ ሊማሩ ይችላሉ።
ስትራተጂዎች
1/ የክልል መስተዳድሮች ከክልሉ የሥራ ቋንቋ ውጪ ያሉ ሌሎች የፌዴራሉ
መንግሥት የሥራ ቋንቋዎች እንደየአካባቢው ኅብረተሰብ ምርጫ እና
አቅምን ባገናዘበ ኹኔታ በትምህርትነት ወይም በትምህርት
መስጫነት በነሱ ቁጥጥር ሥር ባሉት የትምህርት ተቋማት እንዲሰጡ
አስፈላጊውን ዝግጅትና አቅርቦት ያሟላሉ፡፡
2/ የማንኛውም ብሔር፣ ብሔረሰብ ሕዝብ ቋንቋ ለትምህርት መስጫም
ሆነ እንደ አንድ የትምህርት ዓይነት ተመርጦ በተለያየ
የትምህርት ዕርከን ሥርዓተ ትምህርት ውስጥ ከመካተቱ
አስቀድሞ ለቋንቋው የሚስማማ ሥርዓተ ጽሕፈት፣ የቋንቋው
የሰዋስው ሥርዓት ጥናት፣እንዲኹም የመማሪያና የማስተማሪያ
መጻሕፍት፣ ደጋፊ የንባብ ጽሑፎችና በቋንቋው የሠለጠኑ በቂ
መምህራን መኖራቸው ይረጋገጣል።
3/ በትምህርት መስጫ ቋንቋ ልዩነት ምክንያት የትምህርት ጥራት
መጓደል እንዳይከሠት፣ በኹሉም ክልላዊ መስተዳድሮች የየዕርከኑ
ሥርዓተ ትምህርት አቀራረጽና የአተገባበሩም ኺደት
ተመጣጣኝና ሀገር አቀፍ የጥራት ደረጃን የሚያሟላ መሆኑን
ለማረጋገጥ የክትትል፣ የግምገማና የባለድርሻ አካላት የምክክር
ሥርዓት ይዘረጋል።
4/ በአንድ ክልል ውስጥ ከክልሉ የትምህርት መስጫ ቋንቋ ውጭ
በሌላ አፍ መፍቻ ወይም የጋራ መግባቢያ ቋንቋ ትምህርት
እንዲሰጥ ከአካባቢው ብሔር፣ ብሔረሰብ ሕዝብ ሲቀርብ
በሕገመንግስቱ በተቀመጡለሚነሳጥያቄ የቋንቋ ድንጋጌዎች
መሰረት የሚስተናገድ ይሆናል፡፡
12
5/ የአንድ ብሔር፣ ብሔረሰብ ሕዝብ ተማሪዎች ከአፍ መፍቻቸው
ወይም ከመረጡት የአካባቢው የጋራ መግባቢያ ቋንቋ በተጨማሪ
አንድ የፌዴራል መንግሥት የሥራ ቋንቋ እንደ አንድ የትምህርት
ዓይነት በተጠናከረ መልክ እንዲማሩት ይደረጋል።
6/ የአፀደ ሕፃናት እና የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት የትምህርት
መስጫ ቋንቋ የተማሪዎቹ አፍ መፍቻ ቋንቋ ይኾናል።
7/ የአንድ ብሔር፣ ብሔረሰብ ሕዝብ ተማሪዎች ከአፍ መፍቻቸው
ወይም ከመረጡት የአካባቢው የጋራ መግባቢያ ቋንቋ በተጨማሪ
የፌዴራል መንግሥቱን የሥራ ቋንቋ እንደ አንድ የትምህርት
ዓይነት በተጠናከረ መልክ እንዲማሩት ይደረጋል።
8/ የጎልማሶች ተግባራዊ ትምህርት የትምህርት መስጫ ቋንቋ
በተቻለ መጠን የጎልማሶቹ አፍ መፍቻ ቋንቋ ይኾናል። ይሁን
እንጂ የጎልማሶቹ ምርጫ ትምህርቱ በሌላ በደንብ በሚረዱት
የጋራ መግባቢያ ን እንዲሰጥ ከሆነ ዓቅም እስከፈቀደ ድረስ
ትምህርቱ በመረጡት ቋንቋ እንዲሰጥ ኹኔታዎች ይመቻቻሉ።
9/ የኹለተኛ ደረጃ ትምህርት፣ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና
የከፍተኛ ትምህርት የማስተማሪያ ቋንቋ ከእንግሊዝኛ ወደ
የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች ሕዝቦች ቋንቋ/ዎች እንደየ
ቋንቋዎቹ የእድገት ደረጃ እየታየ በአማራጭነት የሚሸጋገርበት
የጊዜ ሰሌዳና ስትራተጂ ይዘጋጃል።
10/ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ለተለያየ ተግባራዊ አግልገሎት
የሚያስፈልገውን የቋንቋ ክህሎት በሚያስጨብጥ መልኩ
ተጠናክሮ በማንኛውም የትምህርት ዕርከን ባለ ሥርዓተ
ትምህርት ውስጥ እንደ አንድ የትምህርት ዓይነት ተካትቶ
እንዲሰጥ ይደረጋል።
11/ ከእንግሊዝኛ በተጨማሪ የሀገሪቱን ማስፈጸሚያ ስልትያዊ
ፍላጎት መሠረት በማድረግ ከሚመረጡ ሌሎች ዓለም አቀፍ
ቋንቋዎች መካከል ቢያንስ አንድ ሌላ ቋንቋ መርጠው
ተማሪዎች ከተወሰነ የትምህርት ዕርከን ጀምሮ መማር
በሚያስችላቸው ኹኔታ ሥርዓተ ትምህርቱ ይዘጋጃል።
12/ በኹለተኛ ሀገርኛ ቋንቋ እና በውጭ ቋንቋ ትምህርትነት
የተመረጡት ቋንቋዎች በሥርዓተ ትምህርቱ ውስጥ
የሚጀምሩበት የክፍል ደረጃ በሀገሪቱ ውስጥ ተመሳሳይ እንዲሆን
ይደረጋል።
13/ የብሔሮችብሔረሰቦችሕዝቦች የቋንቋ መምህራን ሥልጠና
ዘመናዊና ውጤታማ የቋንቋ ማስተማሪያ ዘዴዎችን ያካተተ
መሆኑ፣ መምህራኑ የሚሠለጥኑበት ቋንቋ ለትምህርት ዕርከኑ
ከተወሰነው የትምህርት መስጫ ወይም በትምህርትነት
ከተመረጠው ቋንቋ ጋር ተመሳሳይ መሆኑ፣እንዲኹም
የሠልጣኞቹ መምህራን ቁጥር በየትምህርት ዕርከኑ ካለው
13
ፍላጎት ጋር የተጣጣመ መሆኑ እና ለትምህርት ደረጃው
ተመጣጣኝ የሆነ የሙያ ብቃት ያላቸው መሆኑ ይረጋገጣል።
9. ሥርዓተ ጽሕፈት
ማስፈጸሚያ ስልቶች
1/ በልሳነብዙ ክልል ውስጥ በአካባቢው ለሚነገር ጽሑፍ-አልባ ቋንቋ
በዕቅድና በቋንቋው ሥነድምፅ ጥናት ላይ ተመሥርቶ ሥርዓተ
ጽሕፈት እንዲዘጋጅለት ይደረጋል።
2/ በአገልግሎት ላይ የዋሉትን የኢትዮጵያ ሥርዓተ ጽሕፈቶች
ደረጃና መደበኛነት ለመጠበቅ በተለይ መንግሥታዊ ተቋማት፣
የትምህርት ተቋማትና መገናኛ ብዙኃን ልዩ ኃላፊነት
ይኖርባቸዋል።ይኽን ለማስፈጸምም የክትትል ሥርዓት ይዘረጋል።
3/ ለማንኛውም ቋንቋ ሥርዓተ ጽሕፈት ቀረጻ ወይም የማሻሻል
ሥራ እንደ ምንጭ እንዲያገለግል አንድ ማዕከላዊ የፊደላት ቋት
ይደራጃል፤ በየጊዜው ይዳብራል፤ ለተጠቃሚዎችም ተደራሽ
እንዲሆን ይደረጋል።
4/ የቋንቋዎቹን ተናገሪ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች ሕዝቦችባሳተፈ
መንገድ ዝምድና እና ከፍተኛ የሥነድምፅ ተመሳሳይነት ባላቸው
ቋንቋዎች ወይም ዘዬዎች መካከል ያሉትን መጠነኛ ልዩነቶች
በማቻቻል ሥርዓተ ጽሕፈታቸው እንዲጣጣም ይደረጋል።
5/ ለትምህርት ወይም ለሥራ ቋንቋነት አገልግሎት ላልዋሉና
ሥርዓተ ጽሕፈት ለሌላቸው ቋንቋዎች ለሥርዓተ ጽሕፈት
ቀረጻ መሠረት የሚሆነውን ፊደል የክልሉ ምክር ቤት
በቋንቋዎቹ ሥነድምፅ ጥናት ላይ ተመሥርቶ ያፀድቃል።
በአግልግሎት ላይ ያለውን ፊደልም ሆነ ሥርዓተ ጽሕፈት
የማሻሻል ሐሳብ ለምክር ቤቱ በየዕርከኑ የሚገኘው አግባብ
ያለው የሥነልሳን ባለሙያዎች አካል ያቀርባል።
10. የአደባባይ ቋንቋ አጠቃቀም
የአደባባይ የቋንቋ አጠቃቀም ሕገ መንግሥታዊ መብቶችንና የሀገሪቱን
ባህሎች በሚያከብር፤ እንዲኹም ኢትዮጵያዊ ማንነትንና በራስ
መተማመንን በሚያንፀባርቅ መልክ እንዲመራ ይደረጋል።
ማስፈጸሚያ ስልቶች
1/ በማንኛውም መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት
መሥሪያ ቤት ውስጥ የሚደረግ የንግግርም ሆነ የጽሑፍ
ግንኙነት፣እንዲኹም የውስጥ ሰሌዳ ማስታወቂያ ሰብእናን ያከበረ
እና ትሕትናን የተላበሰ ይኾናል።
14
2/ በውጭ ሀገር የሚገኝ የኢትዮጵያ ውክልና ያለው ማንኛውም
ድርጅት፤ የየብስ፣ የባሕርና የአየር መጓጓዣ መለያ ስም (በዓለም
አቀፍ አሠራር አስገዳጅ ምክንያት ከሌለ በስተቀር) መጀመሪያ
የፌዴራሉ መንግሥት በመረጠው አንድ የፌዴራል የሥራ ቋንቋ
በጉልህ ይጻፋል፤ እንደ አስፈሊጊነቱ ከሀገርኛው ስም ግርጌ ወይም
ቀጥሎ አግባብ ባለው ሌላ ቋንቋ ይጻፋል።
3/ ማንኛውም ዓይነት በአደባባይ ላይ የሚቀርብ ሕዝባዊ
መልእክትም ሆነ የንግድ ማስታወቂያ የሚጻፍበት የአካባቢውን
ቋንቋ በማስቀደምና በማጉላት የሚጻፍና በይዘቱም ከአካባቢው
ባህልና ሥነ ምግባር ጋር የሚጣጣም ይኾናል።
4/ ማንኛውም በዓለም አቀፍ መደበኛ መድረክ ላይ ንግግር
የሚያደርግ ማንኛውም የኢትዮጵያ መንግሥት ተወካይ አስገዳጅ
ኹኔታ ከሌለ በስተቀር የፌዴራል መንግሥት የሥራ ቋንቋ
ከሆኑት በአንዱ ሐሳቡን ያቀርባል።
15
ትምህርታዊ ዘዴዎች የተጠናከረና ተከታታይ የግንዛቤ ማዳበሪያ
ሥራዎች ይሠራሉ።
ማስፈጸሚያ ስልቶች
1/ የኢትዮጵያ የምልክት ቋንቋን ጨምሮ የትርጉምና
የአስተርጓሚነት ሥራዎች ራሳቸውን የቻሉ የሙያ መስኮች
መሆናቸውን በመገንዘብ መንግሥት በነዚህ መስኮች ለሚሠለጥኑ
ባለሙያዎች በየደረጃው የሥልጠና መርሐ ግብር ተዘጋጅቶ
በሥራ ላይ የሚውልበትን ስልት ይቀይሳል።
2/ የኢትዮጵያ የምልክት ቋንቋን ጨምሮ በትርጉምና
በአስተርጓሚነት ሥራ ለመሰማራት የሚፈልጉ ባለሙያዎች ወደ
መደበኛ ሥራ ከመሠማራታቸው በፊት በመስኩ ሙያዊ የብቃት
ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት እንዲያገኙ ይደረጋል።
3/ በመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ውስጥ ለሚሠሩ የኢትዮጵያ
የምልክት ቋንቋ፣ የትርጉምና የአስተርጓሚነት ባለሙያዎች
የሙያ መደብና ደረጃ ይወጣል።
ማስፈጸሚያ ስልቶች
1/ የቋንቋዎች፣ ሀገር በቀል ዕውቀቶችና ነገረ ወጎች (ፎክሎር)የስነዳ
ሥርዓት፣ የድርጊት መርሐ ግብርና ዕቅድ በከፍተኛ ትምህርት
ተቋማት፣ በጥናትና ምርምር ተቋማትና አግባብ ባላቸው ሌሎች
16
የመንግሥት አካላት ይነደፋል፤ ይኽን ለማስፈጸም የሚያስፈልገውን
ተቋማዊ ዓቅም መንግሥት በየደረጃው በኺደት ይፈጥራል።
2/ የግልና መንግሥታዊ ያልኾኑ ድርጅቶች እንዲኹም ሌሎች የልማት
አጋሮች፣ በቋንቋዎች፣ ሀገር በቀል ዕውቀቶችና ነገረ ወጎች (ፎክሎር)
የስነዳ ተግባራት የሚሳተፉበት ማዕቀፍና ሥርዓት ይዘጋጃል።
3/ በቋንቋዎች፣ ሀገር በቀል ዕውቀቶችና ነገረ ወጎች (ፎክሎር) ስነዳ
የተሰበሰቡ መረጃዎች ለምርምር፣ ለትምህርትና ለልማት ዕቅድ
ተደራሽ በሚሆኑበት ስልት የሚከማቹበት ማዕከል በየዕርከኑ
ይደራጃል።
4/ በመጥፋት ላይ ያሉ ቋንቋዎች የሚሰነዱበት፤ የሚጠበቁበትና
የሚያንሰራሩበት ኹኔታ ይመቻቻል፤
17
ክፍል ሦስት
19
17. የፖሊሲው አስፈጻሚ አካላት
1/ የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግሥት የባህልና
ቱሪዝም ሚኒስቴር የቋንቋ ፖሊሲው ዋና አስፈጻሚ ይኾናል።
2/ የሚመለከታቸው መንግሥታዊ ተቋማትና የመስተዳድር ዕርከኖች
ፖሊሲውን በየደረጃው ያስፈጽማሉ።
3/ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ ማህበራት፣ የሀይማኖት ተቋማት እና
ሌሎች አጋር አካላት ፖሊሲውን በየዘርፋቸው ያስፈጽማሉ።
አባሪ
የቃላት እና ሐረጋት ፍች
በዚኽ የቋንቋ ፖሊሲ ውስጥ የተገለጹት ጽንሰ ሐሳቦች አገባብ ከዚህ በሚከተሉት
ፍችዎች መሠረት ነው።
1/ “የቋንቋ ፖሊሲ” ማለት አንድ መንግሥት ወይም ሥልጣን የተሰጠው አካል
በሚመራው ሀገር ወይም ተቋም ውስጥ የሚነገሩት ቋንቋዎች እንዴት
በጥቅም ላይ እንደሚውሉ፣ እንደሚጠበቁ፣ እና እንደሚለሙ በሕግ ወይም
በሌላ አግባብ የሚያመለክት አጠቃላይ መርሕና መመሪያ።
21
2/ “የቋንቋ መብት” ማለትአንድ ግለሰብ ወይም ብሔር፣ ብሔረሰብ
ወይምሕዝብ አፍ በፈታበት ወይም በደንብ አውቀዋለሁ በሚለው ሌላ ቋንቋ
የመጠቀም፣ የመማር፣ አገልግሎት የማግኘት፣ ቋንቋውን የመጠበቅና
የማልማት መብት።
3/ “የቋንቋ ዕቀዳ”ማለትበሀገሪቱ ወይም በክልሉ ውስጥ የሚገኙትን ቋንቋዎች
እና ዘዬዎች ማጥናት፣ መሰነድና ማልማት፤ በጥናት ውጤቱ ላይ
ተመሥርቶቋንቋዎቹ እና ዘዬዎቹ ለልዩ ልዩ አገልግሎት የሚውሉበትን
ስልትና ደረጃ መቀየስ።
4/ “የቋንቋ ልማት”ማለትቋንቋ ለዘመናዊ ኑሮ፣ኹለገብ እድገትና ሥልጣኔ ብቁ
መግለጫና መግባቢያ እንዲሆን፣ በመዛግብተ ቃላት፣ በሙያዊ የስያሜ ቃላት፣
በሰዋስው፣ በሥርዓተ ጽሕፈት፣ በሥነጽሑፍ፣ ወዘተ፣ እንዲበለጽግ
የማድረግ፣ እነዚህም የሚሰራጩበትን የተለያዩ ዘዴዎች የመለየት፣
የማስፈጸምና የቋንቋውን አጠቃላይ እድገት በዕቅድ የመምራት ተግባር።
5/ “የቋንቋ ስነዳ”ማለትበመጥፋት ላይ ያለን ቋንቋ በውስጡ ከያዛቸው ባህላዊ
ዕሴቶች ጋር በዘመኑ ቴክኖሎጂ በመታገዝ ለትውልድ እንዳለ የሚተላለፍበት
የምዝገባ ሥርዓት ነው።
6/ “የሥራ ቋንቋ”ማለትአንድ መንግሥት ወይም መስተዳድር በሚያስተዳድረው
አካባቢ ለልዩ ልዩ መንግሥታዊ ሥራ የሚመርጠውና የሚገለገልበት ቋንቋ።
7/ “የጋራ መግባቢያ ቋንቋ”ማለትየተለያዩ ቋንቋዎችን የሚናገሩ የአንድ ሀገር
ወይም አካባቢ ሕዝቦች እርስ በርስ የሚግባቡበት ሰፊ ሥርጭት ያለውና
አብዛኛውን ሕዝብ ሊያግባባ የሚችል ቋንቋ።
8/ “የተናጋሪዎቹ ቁጥር አነስተኛ የሆነ ቋንቋ”ማለትበአንድ ልሳነብዙ ሀገር
ውስጥ ከሌሎች ቋንቋዎች ተናጋሪዎች ብዛት አንጻር ሲታይ ቁጥሩ አነስተኛ
የሆነ ተናጋሪዎች ያሉት ቋንቋ።
9/ “የአፍ መፍቻ ቋንቋ”ማለትአንድ ሰው መጀመሪያ የለመደውና ሐሳቡንና
ፍላጎቱን በደንብ የሚገልጽበት፤ ከሌሎች ጋር የሚግባባበት አንደበታዊ
እና/ወይም ምልክታዊ ቋንቋ።
10/ “ኹለተኛ ቋንቋ”ማለት አንድ ሰው አፍ ከፈታበት ቋንቋ ቀጥሎ የሚለምደው
ወይም የሚማረው ቋንቋ።
11/ “ሀገርኛ ቋንቋ”ማለትበአንድ የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰብ ወይም ሕዝብ
ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተላለፈ የሚነገር ቋንቋ።
12/ “ለመጥፋት አደጋ የተጋለጠ ቋንቋ”ማለት በልዩ ልዩ ምክንያት አብዛኞቹን
አፈ-ፈት ተናጋሪዎቹን እያጣ በመሄዱ ከአገልግሎት ውጪ በመሆን ላይ
ያለ ቋንቋ።
13/ “የትምህርት መስጫ ቋንቋ”ማለት በማንኛውም የትምህርት ዕርከን ላይ
የተለያዩ የትምህርት ዓይነቶችን ለማስተማርያነት የሚያገለግል ቋንቋ።
22
14/ “በትምህርትነት የሚሰጥ ቋንቋ”ማለት በማንኛውም የትምህርት ዕርከን
እንደ አንድ የትምህርት ዓይነት ተማሪዎች የሚማሩት ቋንቋ።
15/ “የትምህርት መስጫ ቋንቋ ሽግግር”ማለትበማንኛውም የትምህርት ዕርከን
ላይ ለማስተማሪያነት የሚያገለግልን ቋንቋ በሚቀጥለው ዕርከን ላይ
ለሚሰጠው ትምህርት በሌላ የማስተማሪያ ቋንቋ የመተካት ተግባር ወይም
ኺደት።
16/ “ቋንቋና ዘዬ”ማለትዘዬ የአንድ ቋንቋ አካባቢያዊ ወይም ማኅበራዊ ገጽታ፤
ቋንቋ ደግሞ የአንድ ወይም ከአንድ በላይ የሆኑ ዘዬዎች ድምር ውጤት
ወይም ውሁድ መግባቢያ።
17/ “ዘዬዎችን የማጣጣም ሥራ”ማለትሥርዓተ ጽሕፈታዊ የድምፅ አወካከልን፣
የቃላት ትርጉምን እና የአጠቃቀም ዐውድን በማመሳሰል የየዘዬዎቹን
ተናጋሪዎች ወደ ተሻለ የመግባባት ደረጃ እንዲደርሱ የማድረግ ሥራ።
18/ “የቋንቋ መደበኛነት”ማለትበአንድ ቋንቋ ልዩ ልዩ ዘዬዎች ውስጥ የሚታዩ
መጠነኛ የድምፅ፣ የምዕላድ፣ የቃላት፣ የትርጉም፣ የአወቃቀር የመሳሰሉ
ልዩነቶችን በማስማማት አንድ ወጥ የሆነ ቋንቋን ወይም ዘዬን በዋናነት
ማስተዋወቅና ማስለመድ።
19/ “ልሳነ ዋህድነት”ማለትየአንድ ግለሰብ ወይም ብሔር፣ ብሔረሰብ ወይም
ሕዝብ አፍ በፈታበት አንድ ቋንቋ ብቻ የመግባባት ችሎታ።
20/ “ልሳነክልኤነት”ማለትየአንድ ግለሰብ ወይም ብሔር፣ ብሔረሰብወይም
ሕዝብአፍ በፈታበት ቋንቋ እና በአንድ ሌላ ቋንቋ የመግባባት ችሎታ።
21/ “ልሳነብዙነት”ማለትየአንድ ግለሰብ ወይም ብሔር፣ብሔረሰብ ወይም ሕዝብ
አፍ ከፈታበት ቋንቋ በተጨማሪ ከአንድ በላይ በሆኑ ሌሎች ቋንቋዎች
የመግባባት ችሎታ።
22/ “ሥርዓተ ጽሕፈት”ማለትአንድ የንግግር ብቻ የነበረ ቋንቋ የጽሑፍ ቋንቋ
እንዲሆን ለማድረግ ሲፈለግ የሚዘጋጅለት የምልክት (የፊደል) ገበታና
መደበኛ የአጻጻፍ ሥርዓት።
23/ “ነገረ ወግ (ፎክሎር)”ማለት አንድ ሕዝብ ካለፈው የወረሰው፣ ራሱም
የሚኖረውና ፈጥሮም የሚያስተላልፈው ወጉ፣ ልማዱ፣ ትውፊቱ፣ዕሴቱ፣
እምነቱ፣ ሥነቃሉ፣ አኳኋኑ የመሳሰሉት፤ በአጠቃላይ በሐዘን፣ በደስታና
በሥራ ወቅት የመንፈሳዊና የቁሳዊ ሕይወቱ ባህላዊ መገለጫው።
24/ “ሕዝባዊአገልግሎት”ማለትየግብርናኤክስቴንሽን፣ የፍትሕ፣ የንጹህ ውሃ፣
የጤና፣ የትምህርት፣ የመሳሰሉት አገልግሎቶች።
25/ “ሕዝባዊ መልእክት”ማለትበመንግሥታዊና መንግሥታዊ ባልሆኑ
ተቋማት ለሕዝብ ማንቂያ እና ትምህርት እንዲሰጡ ታስበው በሚዘጋጁ
የአደባባይ ሰሌዳዎች (ቢል ቦርዶች) የሚተላለፉ መረጃዎችና እና
ሌሎችማስታወቂያዎች።
23
24