Download as docx, pdf, or txt
Download as docx, pdf, or txt
You are on page 1of 6

ምእራፍ አራት

4 የኢትዮጵያ ቤ/ከ ቅድም ፍሬምናጦስ


4.1 አፂ ባዜን የኢትዮጵያውያን በጌታ ልደት መገኘት (ሰብአ ሰገል)
ክርስትናና ቤተክርሰቲያን የተወለዱት ወይም የተመሠረቱት በፍልስጥኤም ምድር ነው፡፡ እስራኤል ከግብፅ ከወጡ በ 1644
ዘመን አውግስጦስ ቄሣር በሮም ሄሮድስ በገሊላ ባዜን በኢትዮጵያ ነግሦ ሳለ አኪንም በኢትዮጵያ ሊቀ ካህናት ሆኖ ሳለ ያን ጊዜ ጌታችን
መድኃኒታቸን ኢየሱስ ክርስቶስ የይሁዳ እፃ በምትሆን በቤተልሔም በድንግልና በንጽሐ ሥጋ፣ በንጽሀ ነፍስ ድንግል ከምትሆን
ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በሥጋ ተወለደ፡፡ ባዜን የሚለው ስም በኋላ ዘመን የኢትዮጵያ አውራጃዎች ከነበሩት ውስጥ
የሐማሴን ክፍል ከሆነው ሀገር የአንድ ነገድ የአንድ A ውራጃ ስም መጠሪያ ሆኗል፡፡ ወረዳውም የሚገኘው ከሐማሴን በስተምእራብ
ተከዜ በሚወስደው በኋላ ዘመን ከጎንደር መንግሥት አድያም ሰገድ ኢያሱ ዘምተውበት የነበረው ክፍል ነው፡፡ የባዜን ነገድና አውራጃ
ኩናማ ነው የሚል ግምት የሚሰጡም አሉ፡፡ ጌታችን ሲወለድ ትንቢት የተነገረላቸው ሱባኤ የተቆጠረላቸው ሰብአ ሰገል (የጥበብ ሰዎች)
ነገሥታት ከኮቡን በምሥራቅ አይተን ልንሰግድለት መጥተናልና የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወደ የት ነው? እያሉ ከኢየሩሳሌም ከተማ
ገቡ፡፡ ማቴ 2÷1 ከደቂቀ ነቢያት አንዱ ሚክያስ “ወተንሥህ ሰባቱ ኖሎት ወስምንቱ ሰራዊት” “ሰባቱ እረኞቹ ስምንቱ አለቆች
ይነሡበታል” ጊዜው ኢትዮጵያና ፋርስ የግዛት ወሰን ኩታ ገጠምነት በነበራቸው ጊዜ በመሆኑ አብረዋቸው የሄዱት ነገሥታት መኳንንት
ብዙዎች ናቸው፡፡ ነገር ግን እጅ መንሻ ለማቅረብ በረከት ልደቱን ለመሳተፍ እግዚአብሔር የቀጠራቸው በትንቢት የጠራቸው የወርቅ
የእጣን የከርቤ ባለቤቶች መሊኩ (ሚሊቸር)፣ ማንቱሲራ፣ በዲዳስፋር ናቸው፡፡ ማቴዎስ በወንጌሉ “ከምሥራቅ የመጡ” ያለው ከጥንት
ዘመን ጀምሮ ከኢትዮጵያ በስተምስራቅ ያለው ሀገር (እስከ ሕንድ) ምሥራቅ እየተባለ ይጠራ ስለነበረ ነው፡፡ መዝ 71÷10፣ ኢሳ 8÷6፣
ሚክ 5÷5 ንጉሥ ሄሮድስና ኢየሩሳሌም ሰልፋቸውን ብዛታቸውን ቅልጥፍናቸውን አይተው ጥያቄያቸውንም ሰምተው
ደነገጡ፤ተደናበሩ፡፡ ንጉሡ ሄሮድስ ካህናቱን ለብቻቸው ጠርቶ ስለ ክርስቶስ የተናገረውን ትንቢት ጠይቆ ከተረዳ በኋላ ያገኛቸሁት
እንደሆነ እኔም መጥቼ እንድሰግድለት ተመልሳችሁ ንገሩኝ ሲል በጥብቅ አደራ ለመናቸው፡፡ ይህ ቃል ክርስቶስ ንጉሥ ብቻ ሳይሆን
ነገሥታት የሚሰግዱለት ንጉሠ ነገሥት መሆኑን ስለሚያስረዳ ለሰብአ ሰገል ታላቅ የሃይማት ምስክር ሆነላቸው፡፡ ከዚህ በኋላ ሰብአ ሰገል
በኮከብ እየተመሩ በሄሮድስና በካህናት ምስክርነት ልባቸውን እያጠናከሩ ሃይማኖታቸውን እየመሰከሩ ወደ ቤተልሔም ደረሱ፡፡
ከምሥራቅ እስከ ቤተልሔም የመራቸው ኮከብ በዘኁልቁ 24÷17 “አየዋለሁ አሁን ግን አይደለም እመለከተዋለሁ በቅርብ ግን
አይደለም ከያእቆብ ኮከብ ይወጣል” ተብሎ የተጻፈውን በመተርጎምና የኢሳይያስን ቃል በመጥቀስ “እነሆ እግዚ አብሔር አምላካችሁ
እነሆ ንጉሣችሁ” በማለት ጠቅሶ ኮከቡን አሳያቸው አመለከታቸው፡፡ ወደ ቤትም በገቡ ጊዜ በኮከብ እንደ አዩት አ ርአያ ከ እናቱ
ከድንግል ማርያም ጋር ሕፃኑን አገኙት፡፡ ከዚህ በኋላ ሳጥናቸውን ከፍተው ኮረጃቸውን (ቦርሳቸውን) ፈተው ወርቅ፣ እጣን፣ ከርቤ እጅ
መንሻ አቀረቡለት፡፡ ምክንያቱም ወርቅ ስለ ንጉሠ ነገሥትነቱ፣ እጣን ስለ አምላክነቱ፣ ከርቤ ስለሞቱ ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ ኢየሩሳሌም
መጻሕፍት መምህራን እያሏት ኖሎት መላእክት ነቢያት እየመሰከሩለት ወደ እርሷ የመጣውን ንጉሥ ሳታውቀው ሳታየው ሳትለየው
ኢትዮጵያ በብዙ ሺ ምእራፍ ኪሎ ሜትር የሚገመት መንገድ ሄዳ እጅ መንሻውን በማቅረብ በረከተ ልደቱን በመሳተፏ ለመንፈስ ትንቢት
በመታዘዝ ከእግዚአብሔር ጋር ያላትን ፍቅር በግልጽ አሳይታለች፡፡ ሉቃ 2÷1-21 ሰብአ ሰገል እጅ መንሻውን ካቀረቡ በኋላ ወደ
ሄሮድስ እንዳይመለሱ የእግዚአብሔር መልአክ በሕልም ስለነገራቸው የፈለጉትን አግኝተው የተመኙትን አይተው መስማት በማየት
ተለውጦላቸው ሃይማኖታቸውን አጽንተው ደስ እያላቸው በሌላ መንገድ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ በአርባ ቀን ወደ ቤታቸው ደረሱ፡፡
እነዚሁም አርባ ቀኖች የእስራኤል ምድር ርስት እስኪገቡ በምድረ በዳ ለፈጸሟቸው አርባ ዘመናት ምሳሌዎች እንደሆነ (ዘኁ 14÷33-
34) ከክርስቶስ ልደት በኋላ ኢትዮጵያ ዜና ጥምቀትን ሳትሰማ ለቆየችባቸው አርባ ዘመናት ምሳሌዎች ሆኑ፡፡ ሰብአ ሰገል ከሄዱ በኋላ
ሄሮድስ እንደ ተሳለቁበት ባየ ጊዜ እጅግ ተቆጣ ከሰብአ ሰገልም በተረዳው የዘመን ቁጥር ልክ ከዓመት እስከ ሁለት ዓመትና ዓመት
ተመንፈቅ እድሜ ያላቸውን ሕፃናት በማስገደሉ ከመከራው ጽናት ከግፍ ብዛት የተነሳ ከወላጆቹ የሚመነጨው የለቅሶ የዋይታ ድምጽ
ኤርምያስ እንደተናገረ እስከ ራማ ተሰማ፡፡ ማቴ 2÷16-18፣ ዘፍ 35÷19፣ ኤር 31÷15

4.2 የእመቤታችን ስደት በኢትዮጵያ


ንጉሥ ሄሮድስ በቅንዓት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ለመግደል በተነሳ ጊዜ “ልጄን ከግብጽ ጠራሁት” ሆሴ 11÷1
የተባለው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ እመቤታችን ድንግል ማርያም ከተወዳጅ ልጇ ጋር የፀሐይ ሐሩር በሚጸናበት አሸዋው እንደረመጥ
በሚፈጅበት የሌሊት ቁር እንደ ሰይፍ የሚቆርጥበት በምድረ በዳ ወደ ምድረ ግብፅ ስደትን ጀመረች፡፡ የእመቤታቸን ስደት ወደ
ኢትዮጵያም ጭምር ነበር፡፡ ይህንንም ትንቢት የተናገረው ነቢዩ እንባቆም ነው “እግዚአብሔር ከቴማን ቅዱሱም ከፋራን ተራራ ይመጣል
ክብሩም ሰማያትን ከድኗል ፍለጋውም ለዘለዓለም ነው የኢትዮጵያ ድንኳኖች ሲጨነቁ አየሁ” ብሏል
የፋራን ተራራ የተባለችው እመቤታችን
ከሦስቱ ቅዱስ አንዱ ቅዱስ ኢየሱስ ክርስቶስ
ሳይከፍት ወደ ማኅፀኗ ገብቶ ሳይከፍት ወጥቷልና
ከፋራን ተራራ ይመጣል የተባለው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው
ድንኳኑ ደግሞ የስደተኞቹ ማረፊያ ነው በመሆኑም “ የኢትዮጵያ ድንኳኖች ሲጨነቁ አየሁ” በሚለው አረፍተ ነገር
የእመቤታችን ስደት ወደ ኢትዮጵያ እንደሆነ የሚመለከት ነው፡፡ ዕን 3÷3-7 በዚያን ዘመን ግብፃውያን ጣኦትን አምላክያን ስለነበሩ
እመቤታችንን በስደትዋ ወቅት በሐዘን ላይ ሐዘን በችግር ላይ ችግር ፈጠሩባት እንጂ አላስተናገድዋትም፡፡ በዚህም የተነሳ ፈለገ ግዮንን
(ዓባይን) ተከትላ ወደ ኢትዮጵያ መምጣትዋን የታሪክ የሥነ-ቅርስ ስያሜ ማስረጃዎች ይገልጣሉ፡፡
እመቤታችን የአባይን ወንዝ ተከትላ ወደ ደቡብ ከወረደች በኋላ የመረብን ወንዝ በመያዝ ወደ ምሥራቅ አመራች፡፡
በመጀመሪያ ያረፈችውም በምእራብ ኤርትራ በሚገኝ “ሲሃት” በተባለ ቦታ ነው፡፡ ከዚያ ተነስታ ወደ ሐማሴን በመሄድ አስቀድሞ ደብረ
ዳሞን በኋላም የአክሱምን ከተማ ባረከች፡፡ ከአክሱም ተነስታ ወደ ደቡብ በመጓዝ በተከዜ በረሃ በደብረ አባይ በኩል አድርጋ ዋልድባ ላይ
አረፈች፡፡ ኢትዮጵያውያን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ልዩ ፍቅር አላቸው፡፡ ለኢትዮጵያ ምእመናን እመቤታችን የልብ
ፍቅራቸው፣ የ አንደበታቸው ጣእም ናት፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያውያን ወዳጆቿ በተረታቸው፣በምሳሌ ንግግራቸው፣ በእንቆቅልሻቸው፣
በእንካ ሰላምታቸው፣ በቃል ግጥማቸው ስሟን ሳይጠቅሱ አያልፉም፡፡ ለምሳሌ፡- የማርያም ግርዝ፣ ማርያም የሳመችው (ማርያም
ስምሽ)፣ የማርያም ጠላት፣ የማርያም ራት፣ ማርያም ትልካለች፣ የማርያም አራስ፣ ማርያም ወርዳላች፣ እንኳን ማርያም ማረችሽ፣ ማርያም
ታኑራችሁ፣ ማርያም ቆማለች፣ ማርያም በሽልም ታውጣሽ … የሚሉትን ሳይጠቀሱ አያልፉም፡፡ በእመቤታችን ስም ዝክር በመዘከር
አቅመደካሞችንና ድሆችንና መንገደኞችን ጠርተው እንዲበሉና እንዲጠጡ ያደርጋሉ፡፡ ይህም ትውፊት እመቤታችን ወደ ኢትዮጵያ
በመጣች ጊዜ ኢትዮጵያዊያን አባቶችና እናቶች ያደረጉላትን መስተንግዶ በማሰብ ነው፡፡ ኢትዮጵያዊያን “ድንግል ማርያም እሙ ወእምነ
ንግሥተ ጽዮን ወኢትዮጵያ” የሚለውን ቃል ዓርማ ሰጥተው እናታቸውን እመቤታቸው ብቻ ሳትሆን ሰማያዊት ንግሥታቸው ጭምር
መሆኗን ለራሳቸው በሃይማኖት ለዓለም በይፋ ያረጋግጣሉ፡፡ እመቤታችን በዋልድባ ገዳም የሚገኝው ዋሻ ውስጥ ለጥቂት ቀናት
ከተቀመጠች በኋላ ከዋልድባ ወጥታ ወደ ምሥራቅ በመጓዝ ዛሬ ግብጣይት በሚለው በጎንደር ክፍለ ሃገር በአስቴር ወረዳ አካባቢ
በሚገኝው መንደር ተቀመጠች፡፡ በዚያ መንደር የነበሩ ሰዎችም እንግዳ ተቀባዮች ስለነበሩ ቤታቸውን ለቀው ምንጣፋቸውን አንጥፈው
የሚበላ የሚጠጣ አቅርበው አስተናግደዋታል፡፡ ቦታዋ ግብጣይት የተባለችው የእመቤታችን ከግብጽ ወጥታ ማረፏን ለማሰብ ነው፡፡
ከዚህ በኋላ ወደ ሰሜን ጣና ጎርጎራ በመሄድ ከጣና ቂርቆስ አካባቢ ደረሰች፡፡ በዚያን ዘመን የነበረው ንጉሥ ባዜን በእንግድነት ተቀብሎ
ከቤቶቹ አንዱን ለቅቆ አስተናግዷታል በሌሊትም በራእይ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል በቤቱ ያስተናገዳቸው አምላክንና እናቱን መሆኑን
ነገረው፡፡ እንግዶቹን ሊያዩ ከተሰበሰቡት የአካባቢ ሰዎችም መካከል ብዙ ድውያን ተፈወሱ፡፡ ይህን ድንቅ ተዓምር ያዩ ሁሉ እጅ
መንሻውን ይዘው እየመጡ የደስታቸው ተካፋይ መሆናቸውን በጣና ቂርቆስ የሚኖሩ አባቶችና ምእመናን ያረፈበትን ቦታ ጭምር እያሳዩ
እስከ ዛሬ ድረስ ይናገሩታል፡፡ እመቤታችን በጣና ቂርቆስ ለሦስት ወራት ያህል ተቀምጣለች ሀገራችን ኢትዮጵያ ለእመቤታችን አስራት
ሀገር ሆኖ የተሰጠቸው ከዚህን ጊዜ ነው፡፡ ልጇ የኢትዮጵያን ተራሮች ባርኮ ወንዞቿን ቀድሶ የእህል በረከት የሚወርድባት ወተትና ማር
የሚፈስባት ሀገር ትሁን ብሎ ለእመቤታችን የአስራት ሀገር አድርጎ ቃል ኪዳን ሰጥቷታል፡፡ ከዚህ በኋላ በቅዱስ ዑራኤል መሪነት ጣና
ቂርቆስን ለቃ ከሰሎሜና ከዮሴፍ ጋር ወደ ላእላይ ግብጽ ሄደች፡፡ በዚያም የሄሮድስን መሞት መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል አበሰራት።

4.3 ኢትዮጵያውያን በበዓለ ሃምሳና በኢየሩሳሌም


የሐዲስ ኪዳን ቤተክርስቲያን በጽርሐ ጽዮን በመንፈስ ቅዱስ መውረድ (በበዓለ ሃምሳ) ስትመሠረትና የመንፈስ ቅዱስን ድንቅ
ሥራ ተመልክተው በአንድ ቀን ካመኑት 3 ሺህ የተለያዩ አገር ሰዎች መካከል ኢትዮጵያዊያንም ነበሩ፡፡ ቅዱስ ሉቃስ ያልጠቀሳቸው
ቁጥራቸው ከሌሎች አገራት ከመጡት አንፃር አነስተኛ ስለነበር መሆኑን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በደርሳኑ ገልጾአል።

4.4 ንግሥት እንደኬ(ጌርዳት) እና ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ (ባኮስ)


ከጥንት ዘመን ጀምሮ ኢትዮጵያውያን እንደ እስራኤላውያን የኦሪትን በዓላት ለማክበር በየዓመቱ ለበዓለ ፋስካ ወደ ኢየሩሳሌም
ይመላለሱ ነበር የንግሥት ሕንደኬ የገንዘብ ሚኒስቴር ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ በዓለ ሀምሳን /በዓለ ሰዊትን/ አክብሮ ወደ ሀገሩ ሲመለስ
በሠረገላ ላይ ሆኖ የነቢዩ ኢሳይያስን መጽሐፍ ያነብ ነበር ‹‹የጌታም መልአክ ፊልጶስን ተነስተህ በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ
ወደሚያወርደው ምድረ በዳ ወደ ሆነ መንገድ ሂድ አለው፡፡ተነስቶም ሄደ፡፡ እነሆም ሕንደኬ የተባለች የኢትዮጵያ ንግሥት አዛዥና
ጃንደረባ የነበረ በገንዘብዋም ላይ የሠለጠነ አንድ የኢትዮጵያ ሰው ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ነበርና ሲመለስም በሠረገላ ተቀምጦ
የነቢዩን የኢሳይያስን መጽሐፍ ያነብ ነበር፡፡›› /የሐዋ 8÷26-28/ ዲያቆኑ ቅዱስ ፊልጶስ ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ መጽሐፍ ሲያነብ
የነበረው ቃለ ትንቢት በኢየሱስ ክርስቶስ መፈጸሙን ከመነሻ እስከ መድረሻ ዘርዝሮ ወንጌልን ሰበከለት ጃንደረባውም በራሱ ፈቃድ
‹‹እነሆ ውኃ እልዳልጠመቅ የሚከለክለኝ ምንድን ነው›› አለው ፊልጶስም ‹‹በፍጹም ልብህ ብታምን ተፈቅዶአል›› ሲለው ‹‹ኢየሱስ
ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ አምናለሁ›› በማለት እምነቱን መስከሮ ተጠመቀ፡፡ /ሐዋ 8÷37/ ጃንደረባው ተጠምቆ በ 35
ዓ.ም. ወደ ሀገሩ ከተመለሰ በኋላ አስቀድማ ንግሥት ሕንደኬ በኋላም የቤተመንግሥቱ ሰዎች ዜና ክርስትናን ተቀብለዋል፡፡ በሐገሩም
ክርስትና /ወንጌል/ ሰበከ ለዚህም፣ ማስረጃ የጥንት የቤተክርስቲያን አባቶችና የታሪክ ጸሐፊዎች ገልጸውታል ለምሳሌ (የሊዮን/ፈረንሳይ/
ጳጳስ የነበረው ቅዱስ ሄሬኔዎስ ‹‹ጃንደረባው ለወገኖቹ ሐዋርያ ሆነ›› ሲል በተመሳሳይም የቤተክርስቲያን ታሪክ አባት የሚባለው
አውሳብዮስ ዘቂሣርያ /260-340 ዓ.ም./ የነበረ፡፡ ‹‹ከቤተ እስራኤል ውጭ የአካላዊ ቃልን ምሥጢር በመቀበል /በማመን
ኢትዮጵያዊው ጃንደረባ የመጀመሪያው ነው፡፡ በዓለም የወንጌል ፍሬ በመሆንና ወደ አገሩም ተመልሶ በማስተማር በዓለም ላይ
የመጀመሪያው ነው በዚህም ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች ተብሎ የተነገረው ትንቢት ፍጻሜውን አገኘ›› ብሏል፡፡

4.5 የሐዋርያት ስብከት በኢትዮጵያ


በ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የክርስትና እምነት ዜና የተሰማውና የተሰበከው ኢትጵያውያን ያመኑም የተጠመቁትም በ ኢትዮጵያዊው
ጃንደረባ አማካይነት መሆኑ አይካድም ከ እርሱም ቀጥሎ ቅዱሳን ሐዋርያት መጥተው ወንጌልን እንደሰበኩ በበርካታ የታሪክና
የቤተክርስቲያን አባቶች ምስክርነት ተረጋግጧል፡፡

ለምሳሌ፡-

 ሩፋኖስና ሶቅራጥሰ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ ወንጌል የሰበከ ቅዱስ ማቴዎስ እንደሆነ ገልጿል፡፡
 ከ 317- 419 ዓ.ም. የነበረ የላቲን ቤተክርስቲያን አባት ጀሮም የኢትዮጵያ ሐዋርያ ቅዱስ እንድርያስ ነው ይላል፡፡
 ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ደግሞ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ሐዋርያ ቅዱስ ቶማስ ነው ይላል፡፡
 ዜና ማርቆስ መጽሐፍ ላይ በርተሎሜዎስና እንድርያስ መጥተዋል፡፡
 አውሳብዮስ በሁለተኛው መጽሐፍ እንደገለጸው የሐዋርያት ሥራ 8-26 መሠረት አድርጎ ጃንዳረባው ለወገኖቹ ሐዋርያ ሆነ
ብሏል፡፡
በርካታ ሐዋርያት ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ቢያስተምሩም ተልእኳቸው ዓለምን ዞረው ለማስተማር ስለሆነ ኢትዮጵያም የዓለም
አንዷ አካል ስለሆነችና ለክርስትና መዲና ለኢየሩሳሌም ቅርብ ስለሆነች ኢትዮጵያ መጥተው ያስተማሩ ሐዋርያ ቁጥር በዛ ሊባል
አይችልም ነገር ግን እዚህ ላይ ልንገነዘብ የሚገባን የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ወንጌል ሰባኪ ጃንደረባው ባኮስ መሆኑን ነው፡፡ ኢትዮጵያ
በጃንደረባው አማካይነት ክርስትናን በ 34 ዓ.ም. የተቀበለች ብትሆንም በሲኖዶስ ሕግ የጵጵስና መንበር የተሰጣት ግን በ 328/330
ዓ.ም. ቅዱስ ፍሬምናጦስ የኤጲስ ቆጶስነት ሥልጣን በተሰጠው ጊዜ /በአራተኛው ምእተ ዓመት/ ነው፡፡

4.6 ክርስትና ቶሎ እንዲገባ አስተዋጽኦ ያደረጉ ነገሮች


1. የብሉይ ኪዳን ሥርዓት መኖር
2. ከመካከለኛው ምስራቅ ጋር የነበረው ግንኙነት
3. የጃንደረባው ጉዞ
4. በዓለ ሃምሳን ያከበሩ ኢትዮጵያውያን
5. ቅዱሳን ሐዋርያት
6. ክርስትና ቅድሚያ ነገስታት ጋር መሰበኩ

ምእራፍ አምስት

የኢትዮጵያ ቤ/ከ ጊዜ ፍሬምናጦስ


5.1 ቅዱስን ነገስታት አብርሃ ወአጽብሃ (ኢዛና እና ሳይዛና)
የመጀመሪያዎቹ ኢትዮጵያውያን ክርስቲያን ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሐ ወንደሟሟቾች የሆኑ በፍቅር ኢትዮጵያን የመሩ
መንፈሳውያን ነገሥታት ነበሩ የመጀመሪያ ስማቸው አይዛናና ሳይዛና ሲሆን 330 ዓ.ም. በፍሬምናጦስ ከተጠመቁ በኋላ በክርስትና
ስማቸው አብርሃ ወአጽብሐ ተብለው መጠራት ጀመሩ፡፡ እነዚህ ሁለት መንፈሳዊያን ነገሥታት ሥልጣነ መንግሥቱን ከእናታቸው
ከተረከቡ በኋላ ከአባ ሠላማ ጋር በመተባበር ብዙ መንፈሳዊ ሥራዎችን ፈጽመዋል፡፡
ከሠሯቸው መንፈሳዊ ሥራዎች፦
 ሕዝቡን ከአምልኮተ ጣኦት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር ወደ ክርስትና መልሰዋል
 የክርስትና እምነት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሃይማኖት እንዲሆን በ 350 ዓ.ም. በይፋ አውጀዋል፡፡
 በርካታ አብያተ ክርስቲያናትን ሠርተዋል ጥንታውያን የኦሪት ምኩራቦችን ወደ ቤተክርስቲያን እንዲቀየሩ አድርገዋል፡፡
ካሠሯቸው አብያተ ክርስቲያናት መካከል ፡- በአክሱም ለመጀመሪያ ጊዜ ባለ 12 መቅደስ ባለ 5 ክፍልና ባለ 72 አእማደ በጽዮን
ማርያም ስም ቤተክርስቲያን አሠርተዋል፡፡ በወሎ አማራ ሳይንት ተድባበ ማርያም፣ በጎጃም መርጦ ለማርያምና ጣና ቂርቆስ፣
በምእራብ ሸዋ ጎሐ ጽዮን ቅድስት ማርያምን ጨምሮ በአጠቃላይ ከ 154 ቤት ክርስቲያን በላይ አንፀዋል፡፡
 ሁለቱ ነገሥታት ግዛታቸውን አስፋፍተው እስከ ኬንያ የመን ሱማሌና ሱዳንን / አንድ አድርገው ከመግዛታቸው በተጨማሪ
በእነዚህ ሀገሮች ሁሉ ወንጌል እንዲስፋፋ አድርገዋል፡፡
 በወቅቱ በፖለቲካ እና በዲፕሎማሲ ሥርዓት ግንኙነት ተጠቅመው በኢየሩሳሌም የሚገኘውን ዴር ሱልጣን ገዳምና ቦታ መመለስ
ጥያቄ በማቅረብ ተፈፃሚነት እንዲያገኝ አድርገዋል፡፡
 የአርዮሳውያን የክህደት ትምህርት ወደ ኢትዮጵያ እንዳይገባ በመከላከል የእምነታቸውን ጽናት ያስመሰከሩ አርበኞች ናቸው፡፡
በአጠቃላይ አብርሃና አጽብሃ ለሀገሪቱና ለቤተክርስቲያኒቱ ያበረከቱትን የላቀ አስተዋጽዎ በመዘከር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ
ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱሳን ብላ ትጠራቸዋለች በስማቸውም አብርሃ አጽብሃ ተብሎ የታነጸ የውቅር ቤተክርስቲያን በትግራይ
ሀገረ ስብከት በውቅሮ አካባቢ ላይ ይገኛል የኢ/ቤ/ክ የእረፍት በዓላቸውን በየዓመቱ ጥቅምት አራት(4) ቀን ታስባቸዋለች።

ምእራፍ ስድስት
ብሔረ ምላዳቸው ከውጪ ሆኖ ወደ ኢትዮጵያ የመጡ ቅዱሳን
6.1 የሶርያው ፍሬምናጦስ
በ 300 ዓ.ም አካባቢ ሜሮጵስዮስ የተባለ ነጋዴ ፍሬምናጦስንና ኤዴስዮስ/ ሲደራኮስ/ ከተባሉ ወጣቶች ጋር በመሆን ከጢሮስ
ወደ ሕንድ በጀልባ ያመራል ሁሉም ክርስቲያኖች ነበሩ በጉዟቸው ወቅት በአፍሪካ ጠረፍ ቀይ ባሕር አካባቢ ሲደርሱም በአካባቢው
ለመናፈስ፤ ውሃ ለመጠጣት፤ አገር ለማየት ጀልባቸውን ከወደቡ አስጠግተው ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት ሲሉ በአካባቢው ያሉ ሽፍቶች
በጀልባይቱና በተሳፋሪዎች ላይ አደጋ ጥለው እቃቸውን ዘረፏቸው፡፡ ሜሮጵዮስንና የጀልባይቱንም ቀዛፊዎች እዚያው ገደሉዋቸው እንደ
አጋጣሚ ሆኖ ሁለቱ ወጣቶች ብቻ ከመገደል አምልጠው በዛፍ ሥር ሲጸልዩ ሲያለቅሱ መጽሐፍ ሲያነቡ ተገኙ፡፡ ወጣቶቹንም ከማረኩ
በኋላ በዘመኑ ለነበረው ንጉሥ ኢዛና በጦር የማረክናቸው ናቸው ብለው ሰጡት፡፡ ቅዱስ ፍሬምናጦስ በአክሱም ቤተመንግሥት ለንጉሥ
ኢዛና (ታዜር) ልጆች ለአይዛናና ሳይዛና የሞግዚትነትና የአስተማሪነት ሥራ ተሰጠው ወንድሙ ኤዲስዮስን በአክሱም ቤተ መንግሥት
የግምጃ ቤት ኃላፊ አደረገው፡፡ ወጣቶቹ በአክሱም ቤተ መንግሥት ተወዳጅነትና ታማኝነት አገኙ፡፡ ንጉሡ ኢዛና ለሞት በተቃረበ ጊዜም
ልጆቹ አድገው ዙፋኑን ለመያዝ እስኪበቁ ድረስ መንግሥቱን በሞግዚትነት እንድትይዝ ለንግሥት ሶፍያ አደራ ሰጣት እናታቸው ንግሥት
ኦሕየዊ /ሶፍያ/ ሥልጣኑን በሞግዚትነት ተረከበች ፍሬምናጦስም ሁለቱን የንጉሥ ልጆች ወንጌል በማስተማር እናቲቱንም በአስተዳደር
እየረዷት ለ 3 ዓመታት ያህል ከንግሥት ኦሕየዊ ጋር በፍቅር ኑረዋል፡፡ የንግሥቲቱን ቃል በማክበርም በቤተመንግሥት ውስጥ
በአማካሪነት ሲያገለግሏት ቆይተዋል፡፡ ፍሬምናጦስ ለአይዛናና ሳይዛናን በተጨማሪም ለአክሱም ባለሥልጣናትና ለሀገሩ ተወላጆች
በይበልጥ ክርስትና በማስተማር አጠናከረ በወቅቱ ኢትዮጵያ ሃይማኖት ብቻ እንጂ ክህነት፣ ቁርባንና የመሳሰሉት የክርስቲያን ሥርዓት
አልነበራትም አይዛናና ሳይዛና አድገው ያባታቸውን ሥልጣን እንደተረከቡ፡፡ ኤዲስዮስ ወደ ሐገሩ ጢሮስ ተመለሰ በዚያም ካህን ሆነ፡፡
ይህንን በኢትዮጵያ ያሳለፈውን ጊዜ በጢሮስ ከሩፋኖስ ጋር ተገናኝተው እንደነገረውና ሩፋኖስም በመጽሐፉ መግቢያ ላይ ጽፎት ይገኛል፡፡
አይዛናና ሳይዛናም በትረ መንግሥቱን ከእናታቸው ተረክበው ከጨበጡ በኋላ ቀደም ብሎ በጃንደረባው የተሰበከውን ክርስትና
የሚጠናከርበትን መንገድ ያስተካክሉ ጀመር፡፡ በዚህ መሰረትም ጳጳስ ያመጣላቸው ዘንድ ፍሬምናጦስን ወደ እስክንድርያ ላኩት፡፡
ፍሬምናጦስ ስለ ጵጵስና ጉዳይ ለመነጋገር በቅርብ ወዳለች እስክንድርያ ቤተክርስቲያን ጋር እንዲወያይ ከአክሱም ነገሥታት ተልኮ ሄደ፡፡
ፍሬምናጦስም በእስክንድርያ ያሉትን፤ የእስክንድርያ የቤተክርስቲያን ባለሥልጣናት አላገኘም ምክንያቱም የደረሰበት ጊዜ በ 325 ዓ.ም.
ስለነበር የኒቅያ ጉባኤ የእስክንድርያ ሃይማኖት አባቶች አርዮስን ለማውገዝ ወደ ኒቅያ ተጉዘው ነበርና፡፡ ቅዱስ ፍሬምናጦስ እስኪመለሱ
ድረስ ለአንድ ዓመት በእስክንድርያ ቆይቷል፡፡ በዚህ ጊዜም የእስክንድርያ ቤተክርስቲያን ሃይማኖትንና የሃይማኖት ሥርአትን ጉዳዩ
የበለጠ እስኪጠናና እስኪሾም ድረስ ከ 2 ዓመት በላይ ሲቀመጥ የበለጠ አጥንቷል፡፡ ቅዱስ ፍሬምናጦስ እስክንድርያ ቤተክርስቲያን
ሹመቱን በመጠባበቅ ላይ እያለ በ 328 ዓ.ም. 19 ኛው የእስክንድርያ ፓትርያርክ እለ እስክንድሮስ አርፎ በምትኩ በእስክንድርያ መንበር
ቅዱስ አትናቴዎስ ተተካ፡፡
በዚህ ጊዜ ፍሬምናጦስ የተላከበትን ጉዳይ ለቅዱስ አትናቴዎስ አቀረበ ፓትርያርክ አትናቴዎስም በጉዳዩ ተደስቶ ለኢትዮጵያ
ክርስቲያኖች ቋንቋቸውንና ባህላቸውን የሚያውቅ ሌላ ባለመገኘቱ ራሱን ቅዱስ ፍሬምናጦስን ‹‹ጳጳስ ዘአክሱም ወዘኩሉ ኢትዮጵያ ብሎ
በቅብአትና በአንብሮተ እጅ ሹሞ ላከው አትናቴዎስም የእስክንድርያ 20 ኛው ሊቀ ጳጳስ ነው፡፡ ፍሬምናጦስ ጵጵስናውን ተቀብሎ
ከተመለሰ በኋላ በኢትዮጵያ የክርስትናን ሥርዓት አስፋፍቶ ሰበከ የክህነትና የቁርባንንም ሕግ አጠናከረ፡፡ በመላ ኢትዮጵያ ወንጌል
እንዲዳርስ ቀሳውስትና ዲያቆናትን ሾመ ከዘመዶቹ ጋር በደስታ ከመኖር ይልቅ ከመንፈሳዊ ልጆቹ ኢትዮጵያውያን መኖርንም መረጠ
በይበልጥ ስለተቀበለው ደስታ በኢትዮጵያ ሙሉ የክርስትና ትምህርት ሥርዓተ ቤተክርስቲንን ያለምንም ችግር አስተላልፎአል፡፡
አባ ሰላማ /ፍሬምናጦስ/ ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን በዘመኑ ያከናወናቸው መንፈሳዊ ተግባራት
1. ስብከተ ወንጌልን ቀንና ሌሊት በትጋት ሰበከ
2. ካህናትና ዲያቆናትን ሾመ (ቀሳውስትንና ዲያቆናትን ሾመ)
3. የክህነትና የቁርባን ሥርዓት እንዲጀመር አድርጓል
4. የመጀመሪያውን መንፈሳዊ ትምህርት ቤት አቋቁሟል፡፡
5. ማኅበረ ጽዮን ሰማያዊ የምትባለውን የመጀመሪያ መንፈሳዊ የጽዮን ማኅበር በ 347 ዓ.ም. አቋቁሟል፡፡
6. በርካታ አብያተ ክርስቲያናት እንዲታነጹ አድርጓል፡፡
7. ቅዱሳት መጻሕፍትን ከሱርስት ከእብራይስጥና ከጽርእ ወደ ግእዝ ቋንቋ መልሶ ጽፏል
ቅዱስ ፍሬምናጦስ እነዚህን እና ሌሎችንም ዓበይት መንፈሳዊ ተግባራት በእግዚአብሔር አጋዥነት ከ 330 – 350 ዓ.ም. ድረስ
ቀንና ሌሊት የተደከመበትን የክርስትናን እምነትን በሀገሪቱ ብሔራዊ ሃይማኖት እንዲሆን በ 350 ዓ.ም. አሳውጇል። ብሔራዊ ሃይማኖት
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት እስከ 1966 ዓ.ም. ድረስ የመንግሥት ሃይማኖት ሆኗል፡፡ ፍሬምናጦስ የኢትዮጵያ
ቤተክርስቲያንን ከዚህ ያደረሰ ባለውለታ አባት ነው፡፡ በወቅቱም ይህ ሁሉ ድካሙ ታስቦለት በነገሥታቱ በአብርሃ አጽብሐ እና በአክሱም
ምሁራን /ከሣቴ ብርሃን የሚል/ የማእርግ ቅጽል ስም ተሰጥቶታል፡፡ ትርጓሜውም ብርሃንን የገለጠ ማለት ነው፡፡ ፍሬምናጦስ አባ ሠላማ
ይህንን የመሳሰለ ሐዋርያዊ ተጋድሎውን ፈጽሞ አርፏል ቅድስት ቤተክርስቲያንም የቅዱሳት ማእርግ ሰጥታ በዓለ እረፍቱን ሐምሌ 26
በየዓመቱ ታከብራለች፡፡

6.2 አባ ሊባኖስ
ከዘጠኙ ቅዱሳን መምጣት በፊት ጻድቃን በመባል የሚታወቁ አበው ወደ አገራችን መጥተው በሰሜን ኢትዮጵያ በኤርትራ
ክፍለ ሀገር ይኖሩ የነበሩ ናቸው፡፡ እነዚህ ጻድቃን በልዩ ልዩ ሥፍራ በተለይም በቡድን ተከፋፍለው በአምባዎች ላይ ከሚገኙ ዋሻዎች
ሥፍራ ተሠማርተው ሐዋርያዊ ተልእኮዋቸውን ይፈጽሙ ነበር፡፡ የሚበሉትም ቅጠልና ፍራፍሬ ነበር የሰፈሩባቸውም ቦታዎች ለመግለጽ
መጠራ፣ ሐረሳ፣ መንጉጢን፣ አውዓ፣ ከዲህ፣ ደብረሳህል ወዘተ ናቸው፡፡ ከእነዚህም መካከል አባ ሊባኖስ የተባሉትና ከደረቅ አለት ላይ
ጠበል በማፍለቅ የሚታወቁት በቀደምትነት የሚታወሱትና በስማቸው ገደማትና አብያተ ክርስቲያናት የተመሠረተላቸው ናቸው፡፡
በአጠቃላይ ጻድቃን ለ 30 ዓመታት ያህል ብዙ ገቢረ ተአምራት ሲሰሩ ወንጌልን ሲያስተምሩ ኖረዋል፡፡ በዓላቸውም የመታሰቢያ ቀናቸው
ጥቅምት 19 ቀን ይከበራል፡፡ ኣባ ሊባኖስ /መጣዐ/ ከዘጠኙ ቅዱሳን በቀደምትነት የሚታወቁ አባ ሊባኖስ ሌላ ስማቸው አባ መጣእ
በመባል ይታወቃል፡፡ የታናሽ እስያ ሰው ናቸው፡፡ በመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ጥሪ ወደ A ባ ጳኩሚስ ዘንድ ሄደው ምንኩስናን
ተቀብለዋል፡፡ ከዚያም ወደ ኢትዮጵያ መጥተው በጾም ተጠምደው ገዳም ሠርተው ተአምራት እየፈጸሙ እስከ እለተ ሞታቸው
ቆይተዋል፡፡ የመሠረቱት ገዳም አካለ ጉዛይ ኤርትራ ክፍለ ሀገር ሕሞ ከሚባል ቦታ ነው፡፡ በላስታ ቅዱስ ላሊበላ ካሳነጿቸው አብያተ
ክርስቲያናት አንዱ በአባ ሊባኖስ ስም ነው፡፡ መታሰቢቸው ህዳር 3 ቀንና፣ ጥር 3 ቀን ይከበራል፡፡

6.3 ተሰዓቱ ቅዱሳን ወደ ኢትዮጵያ


ቅዱሳን ሲል የተቀደሱ የተመሰገኑ የተባረኩ የተለዩ ማለት ነው፡፡ ብዙ ክርስቲያኖች መምህራን በሌላ ዓለም ስቃይ ሲጸናባቸው
ጥግ ለመሻት የሚመጡት ወደ ኢትዮጵያ ነበር፡፡ ዘጠኙ ቅዱሳን በመባል የሚታወቁት በሁለተኛው የኢትዮጵያ ጳጳስ በአባ ሚናስ ጊዜ
በንጉሥ አልዓሜዳ ዘመነ መንግሥት በ 5 ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ማለቂያ በ 480/481 ዓ.ም. ወደ አገራችን ገቡ፡፡ ቅዱሳኑ የመጡት
ከሮም ቪዛንታይን፣ ታንሽ እስያ፣ ሶርያ ግዛት አካባቢዎች ሲሆን የመጡበትም ምክንያት በጉባኤ ኤፌሶን የተወገዘውን ኋላም በ 451 ዓ.ም.
በጉባኤ ኬልቄዶን የሁለት ባሕርይ ትምህርትን አንቀበልም በማለታቸው በቤዛንታይን ነገሥታት ስቃይ መከራ ስለበዛባቸው ነው፡፡ 9 ኙ
ቅዱሳን የእምነት መሰሎቻቸው ወደሚኖሩበት ቅድስት አገር ኢትዮጵያ ሲመጡም የተለመደው አብርሃማዊ የእንግዳ አቀባበል
ተደርጎላቸዋል፡፡ ስለ ተሰዓቱ ቅዱሳን ወደ ኢትዮጵያ አገባብ ሁለት ዓይነት ምንጮች ይገኛሉ፡፡
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ሲገልጽ፡፡ ቅዱሳኑ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ነገሥታት መኳንንትና ካህናትን አስከትለው መጽሐፍትንም
ይዘው መጥተዋል፡፡ የአመጣጣቸው ሁኔታ አስፈሪ ስለነበር አገር ለመውረር የመጡ መስለዋአቸው ኢትዮጵያውያን ደንግጠው ነበር፡፡
ነገር ግን በእጃቸው የተለያዩ ተአምራቶችን ለማየት ስለቻሉ ለመንፈሳዊ ተልእኮ መምጣታቸውን ተረዱ ተሰዓቱ ቅዱሳን ያሳዩ አቸውን
ተአምራት ሲገልጹም፡-

 በእራፊ የእሳት ፍም የቋጠሩ


 ጠዋት ዘርተው ለሠርክ ቅዳሴ ማድረሳቸውን
 በወንፊት ውኃ ተሸክመው መሄዳቸውንና
 አሥር የእጅና እግር ጣቶች እንደ ፀሐይ ያበሩ መኖራቸውን አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ገልጸዋል፡፡ ይሄ የመጀመሪያው
ስለ ገባባቸው ሁኔታ የሚልጽ ሲሆን ሌላው
 ሁለተኛው ምንጭ ደግሞ አቡነ A ረጋዊ ብቻቸውን ቀደም ብለው መጥተው የኢትዮጵያውያንን ደግነትና ታማኝነት
ስለተረዱ ተመልሰው ሄደው ለ 8 ቱ ቅዱሳን በመግለጣቸው ምክንያት አብረዋቸው መጡ የሚለው አባበል ነው፡፡
ያም ሆነ ይህ ቅዱሳኑ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣታቸው ወንጌል የበለጠ እንደተስፋፋ የታመነ ነው፡፡ እነርሱም
ኢትዮጵያን እንደ ተወለዱበት ሀገር ቆጥረው በርካታ መንፈሳዊ ተግባራትን አከናውነዋል፡፡ እስከ ዛሬ ድረስ
በስማቸው የሚጠሩ ገዳማትን መሥርተዋል፡፡ ከዘጠኙ ቅዱሳን መካከል ሁለቱ ወደ አገራችን ከገቡ በኋላ እስከ ዛሬ
ድረስ የሚታወቁት በኢትዮጵያውያኑ በወጣላቸው ስም ነው፡፡ እነዚህም ቀድሞ ዘሚካኤል የሚባሉት አቡነ አረጋዊና
ቀድሞ ይሥሐቅ ይባሉ የነበሩት አባ ገሪማ ናቸው፡፡ አቡነ አረጋዊ በትሕትናቸው አባ ገሪማ ደግሞ በገቢረ
ተአምራታቸው አዲስ ስም በኢትዮጵያውያን እንዳወጣላቸው ይነገራል፡፡ የእነዚህ የቅዱሳን ስም የመጡበት ሀገር
የመሠረቱትን ገዳምና የመታሰቢያ እለታቸው በሚከተለው ሠንጠረዥ ተጠቃሎ ቀርቧል፡
 ተሰዓቱ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ያከናወኑአቸው ሐዋርያዊ ተግባራት
 የተሰዓቱ ቅዱሳን ሐዋርያዊ ተግባር በኢትዮጵያ በ አራት ነገሥታት ዘመነ መንግሥት ያጠቃለለ ሲሆን ይህም በ
አልዓሜዳ 8 ዓመት፣ በታዜና 12 ዓመት፣ በካሌብ 30 ዓመት፣ በገ/መስቀል ዘመነ መንግሥት 7 ዓመት በድምሩ
ለ 59 ዓመታት ያህል ሐዋርያዊ ተልኳቸውን ተወጥተዋል፡፡ ተሰዓቱ ቅዱሳን ከሀገራቸው እንደመጡ በዘመኑ
የኢትዮጵያ ርእሰ ከተማ በነበረችው በአክሱም ለስብከተ ወንጌል የሚያበቃቸውን ለሥራቸው በር ከፋች የሆነውን
ቋንቋ ጠንቅቀው ካወቁ በኋላ የሕዝበ ክርስቲያኑን ሕይወት ለውጠዋል አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫም ሲገልጽ ‹‹ምድር
በኪደተ እግራቸው ተቀደሰች ከቦታ ቦታ በመንቀሳቀሳቸው የተለያዩ ቦታዎችም ታደሱ የትምህርታቸው መዓዛም
በአካባቢው ሁሉ ፈሰሰ በማለት ተናግረዋል››፡፡ የተሰዓቱ ቅዱሳንን መልካም ሥራዎች በብዛት መዘርዘር ይቻላል፡፡
ነገር ግን ከዋና ዋናዎቹ መካከል የሚከተሉትን ነጥቦች እንመለከታለን፡፡
 በሰሜን ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ በትግራይና በአካባቢው ወንጌልን አስፋፍተዋል ብዙ ኢትዮጵያውያንን ከጨለማ
ወደ ብርሃን መልሰዋል
 የምንኩስናና ገዳማዊ ሥርዓት በአባ እንጦስና በአባ መቃርስ ሥርዓት እንዲለመድ አድርገዋል
 በስማቸው የሚጠሩትንና ሌሎችንም ገዳማት መሥርተዋል ከእነዚህም መካከል በ አቡነ አረጋዊ የተመሠረተው
የደብረ ዳሞ ገዳም በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ነው
 የአቡነ ሰላማን ፈለግ በመከተል መጻሕፍትን ተርጉመዋል ለምሳሌ ፡- መጽሐፍ ቅዱስን፣ ቄርሎስ ዘእስክንድርያና
ዮሐንስ አፈወርቅን መጽሐፈ መነኮሳት፣ መጽሐፈ ኪዳን፣ የአባ እንጦንዮስ የሕይወት ታሪክ ይገኙባቸዋል፡፡
ስለዚህም ዘጠኙ ቅዱሳን ለግእዝ ሥነ ጽሑፍ እድገትና መስፋፋት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አበርክተዋል፡፡
 ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን አይን የሆኑ ደቀ መዛሙርትን አፍርተዋል፡፡ ተሰዓቱ ቅዱሳን ወደ ሀገራችን መጥተው
ስለሠሩአቸው መንፈሳውያን ተግባራትና ስብከተ ወንጌል በማስፋፋታቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
ቤተክርስቲያን የቅድስናቸውን አውደ ሰጥታ ዓመት በዓላቸውን ታከብራለች፡፡
የቅዱሳኑ በረከት በሁላችን ይደርብን አሜን፡፡

You might also like