21

You might also like

Download as pdf or txt
Download as pdf or txt
You are on page 1of 3

የቦሌ አየር አንባ ነጋዴዎች አንድነት ኃ/የተ/ የግል ማህበር የአባላት

የስምምነት ውል፣
ስምምነት የተደረገበት ቦታ፡-በማህበሩ ጽ/ቤት
የስብበሳው ቀን፡-መጋቢት 8 ቀን 2015 ዓ.ም
የስብሰባው ሰዓት፡-ከ4:00 እስከ 6:00 ሰአት
በስምምነቱ ላይ የተገኙ ባለ አክሲዮኖች ፦
1/ አቶ ነብዩ ገ/ክርስቶስ ገ/ማሪያም
2/ አቶ ይስማ አስራት ለገሰ
3/ አቶ ገ/ወልድ ዘመቻ ሱፉ
4/ አቶ መሐመድ ሁሴን ሟርሼ
5/ አቶ ተባረክ የሱፍ አህመድ
6/ ወ/ሮ ፀሀይነሽ ይማም የሱፍ
7/ ወ/ሮ አረጋሽ ሙሴ ጎጆ
8/ አቶ አ/መኑር ሁሴን ሟርሼ
9/ አቶ ቦጋለ ብሩ አገዘ
10/ አቶ አማኑኤል ቶሎሳ ጨዋቃ
11/ አቶ ዳውድ ሁሴን ሟርሼ
የስብሰባው አጀንዳ፡-ስምምነትን በተመለከተ ፦
እኛ በስብሰባው ላይ የተገኘነው የማህበሩ አባላት በፍ/ሕ/ ቁጥር 1731/1679/2005/2266 መሠረት እና
በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 274 እና በተከታዮቹ ድንጋጌዎች መሰረት ከዚህ በታች በዝርዝር በተጠቀሱት ጉዳዮች
ላይ ወደንና ፈቅደን የስምምነት ዉሉ ተዋውለናል ፡፡
እኛ ተስማሚዎች ቀደም ሲል ከሳሽና ተከሳሽ ሆነን በማህበሩ አጠቃላይ የስራ ሁኔታ ላይ ክስ ተመስርቶ
ከስር ከፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር 134461 የካቲት 14 ቀን 2008ዓ /ም በተሠጠው
ውሣኔ ፣ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር 160248 በቀን 17/4/2010 በሠጠው
ውሣኔ ፣ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር 212204 በቀን 03/09/2010 ዓ/ም በሰጠው
ውሣኔ እና የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 164008 ጥር 13/2012 ዓ/ም
በሠጠው ውሳኔ መነሻነት የቀድሞ ከሳሾች የቦሌ አየር አንባ ነጋዴዎች አንድነት ኃ/የተ/ የግል ማህበር አባላት
ናቸው ብሎ የወሰኑ ስለሆነ በእነዚህ ውሳኔዎች መሰረት ለመፈፀም እና የማህበሩ አባላት ብዛትና የአክሲዮን
ድርሻ መጠን ወደ ነበረበት ለመመለስ የማህበሩ አባላቶች በሙሉ ሰፊ ውይይት ካደረግን በኋላ ስለ አፈፃፀሙ
ከፍርድ ቤት ውጪ በስምምነት የጨረስን ሲሆን የስምምነታችን ዝርዝር ውሳኔዎች ከዚህ በታች አቅርበና ፦
1ኛ/ ከላይ ስማችን የተገለፀው አባላት በማህበሩ ውስጥ ያለን የአክሲዮን ድርሻ መጠን እኩል መሆኑ
የተስማማን ሲሆን በስምምነቱ መሰረት ከአሁን በፊት በሚያዚያ 15 /2010 ዓ/ም በሰባቱ አባላት ስም
የፀደቀው የማሻሻያ ቃለ ጉባኤ በአዲስ መልክ ተሻሽሎ እንዲፀድቅ እና በመጀመሪያው ቃለ ጉባኤ የተገለፁት
የአባላት ብዛት እንዲስተካከል እና ወደ ነበረበት እንዲመለስና እንዲሁም በሰባቱ አባላት ስም የፀደቀው
የካፒታል መጠን ከላይ ከ1- 11 የተገለፁት የማህበሩ አባላት እኩል ድርሻ እንዲሆንና ተስተካክሎ እንዲፀድቅ
በማለት በሙሉ ድምፅ ተስማምተናል ። በስምምነቱ መሠረትም የማህበሩ የአንድ አክሲዮን ዋና ብር 1000
/አንድ ሺህ ብር/ እንዲሆን እና የእያንዳንዱ አባላት የአክሲዮን ድርሻ መጠን 1916 /አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ
አስራ ስድስት/ ሆኖ በስማችን እንዲመዘገብና የማህበሩ አባላት የአክሲዮን ድርሻ ወደ ነበረበት ተስተካክሎ
እንዲፀድቅ በማለት በሙሉ ድምፅ ተስማምተናል ፡፡ በተጨማሪም በስምምነታችን መሰረት አዲሱ የማህበሩ
አባላት የአክሲዮን ድርሻ ድልድል በአዲስ ቃለ ጉባኤ ተዘጋጅቶ በሚመለከታቸው መስሪያ ቤት አቅርበን
ለማፅደቅ ተስማምተናል ። በመጨረሻም በዚህ ስምምነት መሰረት አዲሱ የማህበሩ አባላት ብዛት እና
የአክሲዮን ድርሻ ድልድል ከዚህ እንደ ሚከተለው ተስተካክለዋል ።
ተ.ቁ የባለአክሲዮኖች ስም የአክሲዮን የአንዱ አክሲዮን ጠቅላላ ዋጋ
ብዛት ዋጋ

1 አቶ ነብዩ ገ/ክርስቶስ ገ/ማሪያም 1916 1000 1,916,000


2 አቶ ይስማ አስራት ለገሰ 1916 1000 1,916,000
3 አቶ ገ/ወልድ ዘመቻ ሱፉ 1916 1000 1,916,000
4 አቶ መሐመድ ሁሴን ሟርሼ 1916 1000 1,916,000
5 አቶ ተባረክ የሱፍ አህመድ 1916 1000 1,916,000
6 ወ/ሮ ፀሀይነሽ ይማም የሱፍ 1916 1000 1,916,000
7 ወ/ሮ አረጋሽ ሙሴ ጎጆ 1916 1000 1,916,000
8 አቶ አ/መኑር ሁሴን ሟርሼ 1916 1000 1,916,000
9 አቶ ቦጋለ ብሩ አገዘ 1916 1000 1,916,000
10 አቶ አማኑኤል ቶሎሳ ጨዋቃ 1916 1000 1,916,000
11 አቶ ዳውድ ሁሴን ሟርሼ 1916 1000 1,916,000
12 አቶ አልታዬ በቀለ 24 1000 24,000
ድምር 21,100 1000 21,100,000
2ኛ/ ሁላችንም የማህበሩ አባላት በማህበሩ ላይ የሚመጣ ማንኛውንም የእዳ ተጠያቂነት በእኩል ኃላፊነት
ለመውሰድ ተስማምተናል ፡፡
3ኛ/ ሁላችንም የማህበሩ አባላት በህንጻው ላይ የሚገኘውን ማንኛውንም ጥቅማ ጥቅም እኩል ድርሻ ያለን
መሆኑን ተስማምተናል ፡፡
4ኛ/ የማህበሩ የወደፊት ስራዎችን በተመለከተ ሁሉም አባላቶች በመግባባትና በመነጋገር ማህበሩ አላማው
እንዲያሳካ አንድ ላይ ለመስራት እና በአባላቶች መካከል የሚፈጠር አለመግባባት ቢኖር እንኳን በሶስተኛ
ወገን ከመታየቱ በፊት በማህበሩ ሙሉ አባላት በቅድሚያ እንዲታይና ችግሮቹ ለመፍታት ስምምነት
አድርገናል ፡፡
5ኛ/ እስከ ዛሬ ድረስ በተለያዩ ፍርድ ቤቶች ይታዩ የነበሩ አቤቱዎች በሙሉ መቅረፍና ለመፍታት እንዲሁም
ሁሉንም የማህበሩ አባላቶች ፍትሐዊ ተጠቃሚ የሚሆኑበት አሰራር ተከትሎ ስራዎች ለመስራት እና ማህበሩ
ለላቀ እድገት እንዲደርስ ሁሉም አባላት የተቻለውን ሁሉ ለመፈጸም ተስማምተናል ፡፡
6ኛ/ ሁላችንም ተስማሚዎች ቀደም ሲል ከሳሽ እና ተከሳሽ በማለት ለክርክር መነሻ የሆኑትን ጉዳዮች ላይ
የተስማማን በመሆኑና በዚህ ስምምነት ባለቁ ጉዳዮች ላይ ዳግም ሌላ ክስ ላንመሰርት በዚህ ውል ግዴታ
ገብተን ስምምነት ፈጽመናል ፡፡
7ኛ/ የማህበሩ የመመስረቻ ጽሁፍ አንቀጽ አንድ እና አንቀጽ አምስት ስር የተደነገጉት የማህበሩ አባላት
ብዛት እና የአክሲዮን ድርሻ ድልድል መጠን በዚህ የስምምነት ውል መሠረት እንዲሻሻል እና ማሻሻያው
በቃለ ጉባኤ ተዘጋጅቶ በሚመለከታቸው መስሪያ ቤቶች አቅርቦ ለማፅደቅ ተስማምተናል ።
የተስማሚዎች ስም ፊርማ
1/ አቶ ነብዩ ገ/ክርስቶስ ገ/ማሪያም ………………………
2/ አቶ ይስማ አስራት ለገሰ ………………………
3/ አቶ ገ/ወልድ ዘመቻ ሱፉ …….…………………
4/ አቶ መሐመድ ሁሴን ሟርሼ ....………….…………
5/ አቶ ተባረክ የሱፍ አህመድ …………………………
6/ ወ/ሮ ፀሀይነሽ ይማም የሱፍ …………………………
7/ ወ/ሮ አረጋሽ ሙሴ ጎጆ …………………………
8/ አቶ አ/መኑር ሁሴን ሟርሼ …………………………
9/ አቶ ቦጋለ ብሩ አገዘ …………………………
10/ አቶ አማኑኤል ቶሎሳ ጨዋቃ …………………………
11/ አቶ ዳውድ ሁሴን ሟርሼ …………………………

You might also like