Professional Documents
Culture Documents
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
ሐ) ትዕግስት
ጥናት ከብዙ ሰዎች ጋር የሚያገናኝ ስራ ነው፡፡ ስለሆነም በተገቢው መልኩ ትዕግስትን ገንዘብ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡
መ) ወኔ
አንድን ሰው በአንድ ነገር ላይ በባለቤትነት እንዲጨነቅ ለማድረግና መፍትሄም ለማምጣት እንዲረዳው ብርቱ ወኔ ወይም ተቆርቋሪነት
(ተነሳሽነት) ሲኖረው ነው፡፡ በቤተክርስቲያን ያሉ አጠቃላይ የችግሮችዋን መንስዔዎች ስንመለከት ወኔ ከማጣት ወይም ተቆርቋሪ ካለመሆን
የሚመነጩ ናቸው፡፡
በርካታ የጥናት ዓይነቶች ቢኖሩም ለሰንበት ት/ቤታችን የትምህርት አገልግሎት የሚከተሉትን ብቻ አንመለከታለን፡፡
- ታሪካዊ (ጥናት) ምርምር ያለፈን ታሪክ በተመለከተ ምዝገባ፤ክትትልና ትንተና የሚከናውንበት የጥናት ዓይነት ነው፡፡
- ታሪካዊ የሚያሰኘው ባለፈ ታሪክ ላይ ተመስርቶ ክትትልና ትንተና ስለሚያደርግ ነው፡፡
-ይህ ዓይነቱ ጥናት ተጨባጭ መደምደሚያ ላይ ለመድረስ መረጃዎችን በጥንቃቄ መሰብሰብና መተንተን የሚተኮርበት ጉዳይ ነው፡፡
2
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
1.6.2 ገላጭ ጥናት(ምርምር) (Descriptive Research)
3
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
ክፍል ሁለት
4
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
5
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
በአጠቃላይ መላምት በጥናት ሊረጋገጥ የሚችል እውነትን የያዘ ሃሳብ ማለት ነው፡፡
ሁሉም ሀሳብ መላምት ሊሆን አይችልም፡፡
ለምሳሌ፡- “ሁሉም ኢትዮጵያዊ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ቢሆን”
ይህ ዐረፍተ ነገር ምኞት ወይም ጥሩ አስተያየት ሥለሚሆን እንደመላምት ተቀምጦ ሊረጋገጥ የሚችል ነገር
አይደለም፡፡
የጥሩ መላምት ምሳሌ፡-
“ሁሉም ኢትዮጵያዊ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታይ ያልሆነው ስብከተ ወንጌልን በሰፊው ባለማካሄድ ነው፡፡”
የዚህም መላምት ትክክለኛ መሆን አለመሆን ወደፊት በሃደት ከጥናቱ ውጤት የሚገኝ ይሆናል፡፡
ለመላምት መነሻ የሚሆኑ ሀሳቦች የሚገኘት፡-
ከህብረተሰቡ የቀን ተቀን ውሎ
ከልምድ
የጋራ ከሆነ አስተሳሰብ ወይም አመለካከት
ካለፈ ጥናት
ከተለያዩ ንድፈ ሀሳብ ወዘተ
6
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
መላምት መሠራት ያለበት መረጃ ከመሰብሰብ በፊት መሆን አለበት፡፡
መረጃ ከተሰበሰበ በኋላ ከሆነ መላምቱ ባላሰብነው ወይም በተቃራኒ መልኩ ሊረጋገጥ ይችላል፡፡
ሀ. የጥናቱ ዓይነት
ለጥናቱ የምንጠቀምበት የጥናት ዓይነት ምን ዓይነት እንደሆነ የምትገልፅበትና የመረጥንበትንም ምክንያትም
የምናብራራበት ክፍል ነው፡፡
ለ. የጥቅል ስብስብ ተጠያቂዎች ዓይነትና መጠን
በጥናቱ የምንጠቀምባቸው የጥቅል ስብስብ ተጠያቂ ዓይነቶች እነማን እንደሆኑ የምንገልፅበትና የአጠቃላይ
ተጠያቂዎች መጠንም ምን ያህል እንደሆነ የማናሰፍረው በዚህ ነው፡፡
ሐ. የናሙና ዓይነትና መጠን (የአወሳሰድ ዘዴ)
ለጥናታችን ምን ዓይነት ናሙና እንደመረጥን፣ የናሙናው መጠን ምን ያህል እንደሆነ፣ ናሙናውን እንዴት
እንደወሰድንና ናሙናውን የመረጥንበትን ምክንያት ምን እንደሆነ የምንገልፅበት ክፍል ነው፡፡
መ. የመረጃ አሰባሰብ
በጥናታችን ወስጥ የምንጠቀምባቸውን የመረጃ ምንጭ ዓይነቶችን የምንገልፅበጽ ክፍል ነው፡፡
ሠ. የመጠየቁ ይዘት
ለጥናታችን የምንጠቀመውን መጠይቅ የመጠየቁም ይዘት ምን እንደሚመስል የምንገልፅበት ክፍል ነው፡፡(ማለትም
ሥለ ዝግና ክፍት የመጠይቅ ዓይነቶች እንዴት እንደምንጠቀም የምንገልፀው በዚህ ውስጥ ነው፡፡)
7
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
ከተለያዩ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎች የተሰበሰቡ መረጃዎች ከተዛማጅ ጽሁፎች ጋር በማዛመድ በዚህ ክፍል ውስጥ
እየተተነተኑ ይቀርባሉ፡፡
8
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
በመጀመሪያ ጥናቱ ያተኮረበትን ችግርንና የጥንቱን መደምደሚያ አጠቃላይ ይዘት በዝርዝር የሚፃፍበትን መግቢያን
ማዘጋጀት ፡፡
ጠንካራና ደካማ ጎኖች የሚገለፁበት ግኝቶችን ከመረጃ ትንታኔ በመውሰድ በአጭር በአጭሩ እያጠቃለሉ መጥቀስ፡፡
በመቀጠልም ከግተኝቶች መረጃ በመነሳት ማጠቃለያ ማዘጋጀት፡፡
በመጨረሻም የማጠቃለያ ነጥቦችን መሠረት በማድረግ ለወደፊቱ ጥንቃቄ እንዲደረግ የሚመከርበትን፣ ትኩረት
እንዲደረግ የሚጠቆምበትንና እርምጃ እንዲወስድ ማሳሰቢያ የሚሰጥበትን የመፍትሐየ ሀሳብ ማዘጋጀት ይሆናል፡፡
9
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
ክፍል ሦስት
3. የመረጃ አሰባሰብ
ጥናት ለማካሄድ አስተማማኝ መረጃዎችን መሰብሰብ አስፈላጊ ነው፡፡
ማንኛውም አጥኚ መረጃን ለመሰብሰብ አንድ ወይም ከዚያ በላይ የመረጃ አሰባሰብ ዘዴዎችና ይጠቀማል፡፡
በዚህ ዐበይት ርዕስ ውስጥ
የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴዎችን ለማብራራት ይሞክራል፡፡
የመረጃ መሰብሰቢያ መሣሪያዎች ጠንካራና ደካማ ጎኖቸቻቸው ይገልፃል፡፡
አንድ አጥኚ አንድ የመረጃ መሰብሰቢያ ዘዴ ከመጠቀሙ በፊት ምን ምን ሁኔታዎችን ማጤን እንዳለበት ይረዳል፡፡
10
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
በቂ ንሙን የባለው ተአማኚነት ያለው ጥቅል ስብስብ ወገኖችን መወከል የሚቻል ነው፡፡
ትንሽ ናሙና የሚያስፈልገው አንድ ዓይነት አባል ለሆኑ ጥልቅ ስብስብ ወገኖች ሲሆን ትልቅ ናሙና የሚያስፈልገው
ደግሞ የተለያዩ አባላት በአንድ ጥልቅ ስብስብ ወገኖች ውስጥ ሲገኙ(ሲኖሩ) ነው፡፡
11
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
ለምሳሌ፡- አጥኚው በኢትዮጵያ የሚገኙ የ 8 ኛ ክፍል ተማሪዎች ያገኙትን የሒሳብ ትምህርት ውጤት ማወቅ ሲያስፈልገው በተናጠል
አባላትን በማውጣት ናሙና መውሰድ ያስቸግረዋል፡፡ ስለዚህም በኢትዮጵያ የሚገኙ የ 8 ኛ ክፍል ተማሪዎች በክልል፣
በዞን፣ በወረዳ ትምህርት ቤት የተቦደኑ ስለሆኑ አጥኚው ሰው ክልሎችን፣ ዞኖችን ወይም ወረዳዎችን እንደ አንድ
ቡድን ወስዶ ናሙናውን ማዘጋጀት ይችላል ማለት ነው፡፡
12
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
ሁሉም ወረዳዎችን ይዘረዝሩና ከተዘረዘሩት ውስጥ 100 ወረዳዎች ባየሽ ይመረጣል፡፡ ከነዚህም ወረዳዎች ውስጥ
700 ነጋዴዎችን እንደ ናሙና ይወሰዳል ማለት ነው፡፡
ጠንካራ ጎኖች፡-
ውስብስብ አለመሆኑ
ብዙ ወጪ አለመጠየቁ
በቂ መረጃ ያላቸውን አባላት መምረጥ ስለሚቻል ጊዜን መቆጠብ ያስችላል፡፡
13
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
3.3.1. የጽሑፍ መጠይቅ
ይህ ዘዴ ለመረጃ ማጠናከሪያ ስልት ሆኖ ብዙውን ጊዜ ያገለግላል፡፡
ሰዎችን በግንባር ለማግኘት በማይቻልበት ሁኔታና አስቸጋሪ ሆኖ ሲገኝ መጠየቁን በጽሑፍ አዘጋጅቶ እንዲሞሉ
በማድረግ አስተያየታቸውን ለመሰብሰብ የምንጠቀምበት ዘዴ ነው፡፡
የዚህ ስልት ዋና ጥቅሙ መጠይቁን ለብዙ ሰዎች አሰራጭቶ መረጃ መሰብሰብ ያስችለናል፡፡
በጽሑፋዊ መጠይቅ ውስጥ የሚሰፍሩ ጥያቄዎች በሁለት ዓይነት መልኩ ሊቀርቡ ይችላሉ፡፡
14
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
3.3.1.5. የጽሑፍ መጠይቅ መሙያ(መመለሻ) ቅጽ
ሀ/ የክፍት ጥያቄዎች መመለሻ
ለክፍት ጥያቄዎች መመለሻ መላሹ የሚሞላበት ክፍት ቦታ ይኖረዋል፡፡ አጥኘው ይህን ክፍት ቦታ የሚተወውም
መልስን ለመስጠት የሚፈጀውን የቦታ መጠን በቂ ነው ብሎ በሚገምተው ልክ ይሆናል፡፡
ሌላው የአመላለስ ቅርፅ ደግሞ በደረጃ መመለስ ሲሆን ይኸውም ነጥቦችን በመዘርዘር መላሾች በመልስ ቦታው
ላይ ደረጃ እንዲሰጡአቸው ማድረግ ነው፡፡
ለምሳሌ፡- እባክዎ ከዚህ በታች የገጠር ገዳማትን ህልውና ለመጠበቅ ከተዘረዘሩት የገንዘብ ምንጮች የምንጭነታቸውን መጠን
ደረጃ በመስጠት ያስቀምጧቸው፡፡(1 ኛ, 2 ኛ, ወዘተ በማለት)
....................... በምዕመናን የማሰባሰብ ዕርዳታ
........................ በመነኮሳት የልማት እንቅስቅሴ
........................ በብድር
........................ በልመና
........................ በገዳሙ አነስተኛ እንቅስቃሴ
........................ በገዳሙ ቋሚ ንብረት
15
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
........................ ባጠቃላይ ቤተክህነት የበጀት ድጎማ
የሚጠይቅ ጥያቄዎች ከተጻፉና በቅደም ተከተል ከተቀመጡ በኋላ ቀሪው ተግባር የመግቢያ ፅሁፍ ማዘጋጀት
ነው፡፡
ይህም በመጠይቅ አዘገጃጀት ላይ ዋናው ክፍል ነው፡፡
ምክንያቱም የጥናቱን ምንነት ስለሚገልፅ የመላሾቹንም ትብብር ስለሚጠይቅ ነው፡፡
የመግቢያ ፅሁፍ አጠር ብሎ በጥሩ ሁኔታ መዘጋጀት አለበት፡፡
የመግቢያ ፅሁፍ የሚፃፈው፡-
አጥኚውን የሚደግፈው ድርጅት ሙሉ ስሙን በመፃፍ ይጀምራል
የጥናቱን አላማና አስፈላጊነት
መረጃዎችን ማን እንዲሰበስብ
ጥናቱ ለምን እንዲካሄድ
መረጃው እንዴት ጥቅም ላይ እንደሚውል
ማን መረጃው ማየት እንደሚችል
የመላሾች ምሥጢር የተጠበቀ መሆኑን
ሥም መፃፍ የማያስፈልግ መሆኑን
የመላሾችን ትብብር ማመስገን
የመጠይቁ መመለሻ ጊዜው ቀኑን፣ ወሩንና ዓመተምረቱን ማስቀመጥ
ካስፈለገ የአጥኚውን አዳራሽ መፃፍ ወዘተ.
3.3.1.9. የጽሑፍ መጠይቅ ቅድመ ሥርጭት
መጠይቁ ወደ ተፈላጊ መላሾች ከመሰራጨቱ በፊት ጥያቄዎቹ በሚገባ መዘጋጀታቸውን ማረጋገጥ፡፡
አሻሚ፣ አስፈላጊ ያልሆኑና ወዘተ ዓይነት ጥያቄዎችን በማየት የማስተካከል ሥራ መሥራትና ለሥርጭት
ማዘጋጀት፡፡
3.3.1.10. የጽሑፍ መጠየቅ ደካማ ጎን
ያልተማሩና ልጆችን በመጠይቁ ልንጠቀምባቸው አንችልም፡፡
ከተሰራጩት መጠይቆች መካከል የሚመለሰው መጠይቅ ከ 40 – 50 በመቶ ስለማይበልጥ የመረጃዉን ታማኝነት
ይቀንሰዋል፡፡
አንዳንድ ጊዜ መልስ ሰጪዎች ምስጢራዊ ጥያቄዎችን በጽሑፍ መመለስ ላይወዱ ይችላሉ፡፡
ያልተሟላ መልስ የሰጠን ወይም ገደብ የሌለው መልስ የሰጠን መላሽ ማረጋገጫ የለም፡፡
3.3.2. የመርሐግብር መጠይቅ
መርሐግብር መጠይቅን መልስ ለማስሞላት ለዚህ ተግባር የተመረጡና እንዴት እንደሚሞላ በሰለጠኑ መላሾች
የሚከናወን ይሆናል፡፡
የመጠይቁ አሠረጫጨትና አመላለስ ከሌሎች መጠይቆች የተለየ ነው፡፡
ይህ መጠይቅ ከጽሑፍ መጠይቅ የሚለይበት ነጥቦች፡-
17
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
መጠይቁ አብዛኛውን ጊዜ ለመላሾች የሚላከው ፖስታ ነው፡፡
በዚህ ዓይነት መጠይቅ መረጃ መሰብሰብ የበለጠ ውድ ነው፡፡
በዚህ ዓይነት የመሰብሰቢያ ዘዴ መጠይቆች በብዛት ይመልሳሉ፡፡
በመርሐግብር መጠይቅ የመረጃ አሰባሰብ ዘዴ የመላሾች ማንነት ይታወቃል፡፡
በመርሐግብር መጠይቅ መላሾች ቃል ከገቡበት ጊዜ የበለጠ ፈጥነውመልሱን ሞልተው ይመልሳሉ፡፡
(ስለዚህም መረጃን በፍጥነት መሰብሰብ ይቻላል)
መጠይቅ ማስሞላት የሚቻለው መላሾች የተማሩና ተባባሪ ሲሆኑ ብቻ ነው፡፡
የመርሐግብር መጠይቅ ዘዴ በብዛት ናሙና ማሠራጨት ከባድ ነው፡፡
በመርሐግብር መጠይቅ አሞላል አጠቃላይ የተጠናቀቁና በትክክል የተሞሉ መጠይቆች ይመለሳሉ፡፡
መርሐግብር መጠይቅ ማለት ለጥናቱ ተግባር በተመረጡና በሰለጠኑ መላሾች የሚሞላ ነው፡፡
አሰረጫጨቱም ከጽሑር መጠይቅ የሚለይ ነው፡፡
3.3.3. ቃለ መጠይቅ
ቃለ መጠይቅ የመግባት ወይም የግንኙነት ሂደት ሲሆን ቃለ መጠይቅ የሚያደርግለት ሰው ፊትለፊት በቃል
ወይም በስልክ መረጃ የሚሰጥበት ስልት ነው፡፡የነዚህን መረጃ የመስጫ ስልቶች ግለሰባዊ ቃለመጠይቅና የስልክ
ቃለመጠይቅ ተብለው ይታወቃሉ፡፡
በግለሰባዊ ቃል መጠይቅ ስልት ቃለ መጠይቅ አድራጊው ቃል ሰጪውን ፊትለፊት በማግኘት ይጠይቀዋል፡፡
በታዳጊ ሀገሮች የስልክ ቃለ መጠይቅ ስልት ብዙ ጊዜ ተግባራዊ አይሆንም፡፡
ቃለ መጠይቅ አዘጋጆች
የሚፈለገውን መረጃ ለማግኘት ይቻል ዘንድ መጠይቅ በጥንቃቄ ማዘጋጀት አስፈላጊ ነው፡፡
ቃለ መጠይቅ አድራጊዎችንም በመመልመል ለሚሰበሰበው የመረጃ ዓይነትና በመረጃ አሰጣጡ አካሄዱላይ ማተኮር አለበት፡፡
18
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
በቃለ መጠይቅ አድራጊውና በቃል ሰጪው መካከል ብዙ ክፍተት መኖር የለበትም፡፡
ሁለቱም በተቻለ መጠን በአንድ እድሜ ክልልና ከአንድ ፆታና የኑሮ ደረጃ ቢሆኑ ይመርጣል፡፡
የቃል ሰጪው ትኩረት በቃለ መጠይቅ አድራጊው አለባበስ ላይ እንዳይሆን የጠያቂዎች አለባበስ የተለመደ መሆን አለበት፡፡
ቃለ መጠይቅ አዘጋገብ
ቀጠሮ ከመያዙ በፊት ከባለሥልጣናት በኩል ያሉ እንቅፋቶች መወገዳቸውን ማረጋገጥ፡፡ ደብዳቤም መያዝ ጥሩ ነው፡፡
ለቃል ሰጪውም የሚመች ጊዜ መመረጥ አለበት፡፡
ጠንካራ ጎን(ጥቅሙ)
የበለጠና ጠለቅ ያለ መረጃ ሊገኝ ይችላል፡፡
ቃለ መጠይቅ አድራጊዎች በራሳቸው ክህሎት ቃል ሰጪዎች መልስ ከመስጠት እንዳይቆጠቡ ያደርጋል፡፡
ጥያቄን እንደገና የማጠናቀር ዕድል አለ፡፡
በዚህ ዘዴ ግለሰባዊ መረጃዎች በቀላሉ ይገኛሉ፡፡
የተጠያቂዎቹን የቋንቋ ችሎታ፣ መጠንና የትምህርት ደረጃ ከግምት ውስጥ ያስገባ በማድረግ የጥያቄው በሌላ በኩል
የመተርጎም ሁኔታን መቀነስ ይቻላል፡፡
ደካማ ጎን (ጉዳቱ)
በቃለ መጠይቅ አድራጊዎችና በቃል ሰጪዎች መካከል አድሏዊነት ሊንፀባረቅ ይችላል፡፡
አንዳንድ ግለሰቦችን በዚህ ዘዴ ለማግኘት አዳጋች ስለሚሆን መረጃ አሰባሰቡንበቂ እያደረገውም፡፡
መላሾችቃ፤ መጠይቁን አስደሳች ለማድረግ የማይጨበጥ መረጃ እስከመስጠት ሊደርሱ ይችላሉ፡፡
19
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
3.4. ሁለተኛ ደረጃ መረጃ መሰብሰቢያ
ሁለተኛ ደረጃ የምንላቸው በሌላ ሰው ከዚህ በፊት የተሰበሰቡና የተተነተኑ መረጃዎች ሆነው ምንጮቹ የታተሙ
ወይም ያልታተሙ ጽሑፎች ሊሆኑ ይችላሉ፡፡
ጥቅሞቹ፡-
ጊዜና ገንዘብን ይቆጥባል
20
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
21
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
ክፍል አራት
ምሥጋና፣ መክሰት አርዕስት (የአርዕስት ማውጫ)፣ የሠንጠረዥ ማውጫና ምህፃረ ቃላት እነዚህን በተመለከተ በክፍል ሁለት ላይ
በቀረበው መሠረት በቅደም ተከተላቸው በየገፅ በየገፃቸው ይሰፍራሉ፡፡ ገፃቸውም የሮማን ቁጥርን በመጠቀም ይገለፃሉ፡፡ እንጂ
ከዋናው ጽሑፍ ጋር ተጠቃሎ የገጽ ጽሑፍ አይሰጣቸውም፡፡
በመቀጠልም በክፍል ሁለት ትምህርታችን ውስጥ በንዑስ ክፍል 2.2.2. ላይ በሰፈረው መሠረት በቅደም ተከተላቸው በዝርዝር
ይገለፃሉ፣
የመጀመሪያ አባሪ መረጃዎች ካጠናቀቁ በኋላ በአዲስ ገፅ ላይ ምዕራፍ አንድ በሚል ከሥሩ ዓበይት ርዕስ የሆነው የጥናቱ
ዕቅድ ይቀመጣል፡፡
22
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
- ምዕራፍ አንድ ሙሉ ለሙሉ ተብራርቶ ካለቀ በኋላ የሚቀጥለው ምዕራፍ ሁለት ነው፡፡ በአዲስ ገጽ ላይ ይጀምራል፡፡
- ስለዚህም ምዕራፍ ሁለት በሚል ከሥሩ ዓበይት ርዕስ የሆነው የተዛማጅ ጽሑፎች ዳሰሳ ይቀመጣል፡፡
- የራሱ የሆነ መግቢያ ይኖረዋል፡፡ /መጠኑም ቢበዛ ግማሽ ገፅ ሆኖ በአንድ አንቀጽ ይገለፃል፡፡/
- በዚህ ዓበይት ርዕስ ውስጥ ከርዕሱ ጋር ተዛማጅነት ያላቸው ቀደምት ሥራዎች የሚዳሰሱበት ምዕራፍ ነው፡፡
- የተዛማጅ ጽሑፎች ዳሰሳ ሲዘጋጅ በትንሹ ከሥምንት/8/ ያላነሱ ከጥናቱ ጋር ተዛማጅነት ያላቸው ጽሑፎችን መጠቀም
የግድ ይላል፡፡
- ይህንን ምዕራፍ ስናዘጋጅ ከተለያዩ ተዛማጅ ጽሑፎች የምናገኛቸውን ሀሳቦች ማለትም ከጥናታችን ጋር ተያያዥነት
ያላቸውን ማለት ነው እነዚህን ሀሳቦች ስናሰፍር በየአዲስ መስመሩ መጀመሪያም ይሁን ጨረሻ ላይ በቅንፍ ውስጥ የደራሲው
ሙሉ ስም፣ ፅሑፍ የተገኘበት ገፅ አና ደራሲው ያሳተመበት ዓ.ም. የግድ መሥፈር ይኖርበታል፡፡ /ምሳሌ፡- ዲ/ን ዳንኤል
ክብረት፣ ገፅ 20-21፣ 2006 ዓ.ም./
- የምዕራፍ ሁለት አጠቃላይ ሀሳብ ከተጠናቀቀ በኋላ ምዕራፍ ሦስት በሚል ከሥሩ ዓበይት ርዕስ የሆነው የመረጃ ትንታኔ
ይቀመጠጣል፡፡
- የዚህ ምዕራፍ ይዘትም፡-
1. 3.1. በሚል ንዑስ ርዕስ የመረጃ ምንጮች፣ የአሰባሰብ ሁኔታው እና የትንታኔው ዘዴ አጠቃላይ ምልከታ በሚል መግቢያ
ይኖረዋል፡፡
- በዚህ ንዑስ ርዕስ ውስጥም ከጥናቱ ርዕስ ጀምሮ ዓላማውን በመግለፅ እንዲሁም መረጃ ለመሰብሰብ
የተጠቀምንባቸውን የመረጃ ምንጮች እና በተጨማሪም ለተጠቃሚዎች የተበተነው የመጠይቅ ብዛት ተገልፆ
የአሰባሰብ ሁኔታውም በመቶኛ ይገለጣል፡፡ በመጨረሻም የመረጃ አተናተን ዘዴው እንዴት ሊሆን እንደሚችል
በአጭሩ የሚገለፅበት ንዑስ ክፍል ነው፡፡
2. 3.2. በሚለው ንዑስ ክፍል ውስጥም ከመጠይቅ የተገኙ የመረጃዎች ትንታኔ በሚል ርዕስ ተጠቅመን ሁለት ሌሎች
ርዕሶችን እንገልፅበታለን፡፡
- 3.2.1. በሚል ንዑስ ርዕስ የመላሾች የግል ማህደር መግለፅ ይኖርብናል፡፡
- 3.2.2. በሚል ንዑስ ርዕስ ውስጥም ተጠያቂዎች በጥናቱ ርዕስ ዙሪያ በመጠይቁ መሠረት የተሰጡ ምላሾች በሚል
ወደ ጥያቄዎች መልሶቻቸው እንገባለን፡፡
- ጥያቄዎቹንና መልሶቻቸውን መሠረት በማድረግ ሰንጠረዥን በመጠቀም በመቶኛ በመግለፅና በመተንተን
እያንዳንዱን ጥያቄ በዚህ መልክ እየሰራ እንሄዳለን፡፡
ምሳሌ፡-
23
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
1. መግቢያ(Introduction)
- ምዕራፍ አራት 4.1. በሚል ንዑስ ርዕስ መግቢያ ይኖረዋል፡፡
- የመግቢያው ይዘትም፡-
- የምዕራፍ ይዘት መሠረት ያደረገው ምዕራፈ ሦስትን የመረጃ ትንታኔ መሠረት ያደረገ መሆኑን መግለፅ፣
- ከትንታኔው ውስጥ የተገኙትን መልሶች በጠንካራና ደካማ ጐናቸው በመለየት በግኝት ውስጥ ማስፈር፣ ከግኝቱም በመነሳት
የማጠቃለያና የመፍትሔ ሀሳብ እንደሚዘጋጅ ማስገንዘብ፡፡
2. ግኝቶች (Findings)
- ግኝቶች የሚባሉት ከመረጃ ትንታኔ ከመላሾች የተገኙ ጠንካራና ደካማ ጐኖችን(አስተያየቶችን) ማለት ነው፡፡
- እነዚህ ዓኝቶችም 4.2 በሚል ንዑስ ርዕስ ግኝቶች በማለት ይሰወራል፡፡
- የተገኙትንም ጠንካራና ደካማ ጐኖች፡-
ጠንካሮቹን ጐኖች(አስተያየቶችን)ጠንካራ ጐኖች በሚል ርዕስ ውስጥ ማስፈር፣
ደካማ ጐኖችን(አስተያየቶችን)ደካማ ጐኖች በሚል ርዕስ ውስጥ ማስፈር፡፡
3. ማጠቃለያ(Conclusion)
- አንድ ጥናት ያተኮረበት ችግር እንዴት ሊፈታ እንደሚችልና በምን ዓይነት መንገድ ሊጠቃለል እንደሚችል የሚገለፅበት ክፍል
ነው፡፡
- ማጠቃለያ የጥናታዊ ሥራ ግብ መግለጫ ስለሆነ ዝግጅቱ ጥንቃቄ ይጠይቃል፡፡
- በግኝቶች ውስጥ የሰፈሩትን የጠንካራና የደካማ ጐኖችን ተጨባጭ መረጃዎችን መሠረት ባደረገ የማጠቃለያ ሥራ ይሠራል፡፡
4. የመፍትሔ ሀሳብ(Recommendation)
24
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
- በማጠቃለያው ላይ የተነሱትን ነጥቦች መሠረት በማድረግ ለወደፊቱ ጥንቃቄ እንዲደረግ የሚመከርበትን፣ ትኩረት እንዲደረግ
የሚጠቆምበትን እና እርምጃ እንዲወሰድ ማሳሰቢያ የሚሰጥበትን ሀሳቦች በመጥቀስ የመፍትሔ ሀሳብ ማዘጋጀት
ይጠበቅብናል፡፡
- ዋቢ መጽሐፍት የምንላቸው ጥናቱ በተካሄደበት ጊዜ ሃብ ለማስተካከልና ጥናታዊ ጽሁፉን ፈፃሜ ላይ ለማድረስ አገልግሎት
የሰጡ መጽሐፎች፣ መዛግብተ ቃላት፣ አውደ ጥናቶች፣ መጽሔቶች፣ ጋዞጦች፣ ሰነዶችና ማስታወሻዎች ወዘተ…
የመሳሰሉትን ያጠቃልላሉ፡፡ እነዚህም በዝርዝር የአደራደር ሥርዓት ይዘው በጥናታዊ ጽሑፍ መጨረሻ ላይ ይቀርባሉ፡፡
የአደራደሩን ሥርዓት በጥልቀት በምሳሌ ከማሳየታችን በፊት ስለአደራደሩ ሥርዓት አጠቃላይ መርህ በአጭሩ እንደሚከተለው
ይቀርባል፡፡
1. ዋቢ ጽሑፎች በፊደል ተራ ቅደመ ተከተል መደርደር ይኖርባቸዋል፡፡ ስለዚህ የደራሲው ሥም በተጠቀሰበት ሥራ ውስጥ የደራሲው
ሥም የመጀመሪያ ፊደል፤ የደራሲው ሥም ባልተገለፀበት ሁኔታ ደግሞ የርዕሱ የመጀመሪያ ፊደል ለአደራደሩ ተቀዳሚ ሆኖ ያገለግላል፡፡
2. ዋቢ ጽሑፎች በፊደል ተራ ቅደም ተከተል ሲደረደሩ በአንድ ደራሲ የተፃፉ ቁጥራቸው በርካታ መጽሐፍት ሲያጋጥሙ አሮጌውን ሥራ
በማስቀደም በኀትመት ዘመናቸው ወይም በርዕሳቸው ፊደል ቅደም ተከተል መደርደር ይገባል፡፡
3. በአደራደሩ ሂደት የአውሮፖዊ ስም ሲያጋጥም የመጨረሻው (የቤተሰብ ሥም) በቅድሚያ የወሰድና የሥሙ የመጀመሪያ ፊደል
ለአደራደሩ ቀዳሚ ይሆናል፡፡ ሆኖም በአህፅሮት ማስፈር አይፈቀድም፡፡
4. በሁለት አውሮፖዊያን ደራሲያን የተጻፈ ከሆነ የመጀመሪያው ደራሲ ሥም ከላይ በ3 በተቀመጠው ሥርዓት መሠረት ይቀርባል፡፡
የሁለተኛው ደራሲ ሥም ገን እንዳለ ይፃፋል (የቤተሰብ ሥም አይቀድምም)፡፡
5. ጽሑፉ በሶስትና ከዚያ በላይ ደራሲያን የተፃፈ ከሆነ የመጀመሪያው ደራሲ ሥም መውሰድና በ3 በተጠቀሰው መሠረት ማስቀመጥ
የሚለውን አፅርዎት ማስከተል፡፡ ደራሲያኑ ኢትዮጵያዊያን ከሆኑ ደግሞ እገሌና ሌሎች ብሎ ማመልከት ይቻላል፡፡
6. የመዘርዝሩም አፃፃፍ በስተግራ በኩል ካለው ህዳግ የተነሣው የመጀመሪያ መስመር በስተቀኝ ካለው ህዳግ መግቻ ላይ ያበቃል፡፡ ተከታታዩ
መስመር ግን የመጀመሪያው መስመር ከደመረበት አምስት ፊደል ቦታ ገባ ብሎ መጀመር አለበት፡፡
8. በዋቢ ጽሑፎች አደራደር ሂደት የደራሲ ሥም፣ ዓመተ ምሕረት፣ ርዕስ ወዘተ… ቅደም ተከተለ አንድ ወጥ አይደለም ይህም የሆነበት
የተለያዩ የአደራደር ሥልቶች(ሥርዓቶች) ስላሉ ነው፡፡
25
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
ምሳሌ፡- ኢትዮጵያዊ ደራሲ
1. የሀርቫርድ ሥርዓት
ሀዲስ ዓለማየሁ፡፡(1980)የልምዣት፡፡ አዲስ አበባ፣ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት፡፡
2. የAPA ሥርዓት
ሀዲስ ዓለማየሁ፡፡ (1980)የልምዣት፡፡ አዲስ አበባ፣ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት፡፡
3. የMLA ሥርዓት
ሀዲስ ዓለማየሁ፡፡ የልምዣት፡፡ አዲስ አበባ፣ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት፣(1980)
ከዚህ ቀጥለው የሚቀርቡት ምሳሌዎች በተለይ በአንደኛው ደረጃ ላይ የተጠቀሰውነ የአሰፋፈር ሥልት መሠረት ያደርጋሉ፡፡
Megrath, H. (1998) All about Food. Great Britain: Oxford University Press.
26
ጥናትና ምርምር
ጥናትና ምርምር
ኢትዮጵያዊያን ደራሲያን
ሥዩም ተፈሪና አየለው ሺበሺ (1982)አጭር የምርምር ዘዴ፡፡ አዲስ አበባ፣ ኩራዝ አሳታሚ ድርጅት፡፡
አውሮፖዊያን ደራሲያን
ደራሲዎች፡- Frank Kerecks and Robley Winfrey Kereck,F, and Robley, W (1951) Report Preparation: The lwoa State
College Press.
የደራሲዎች፡- መሥፍን ሀብተማርያም፣ አዳምረታ፣ አበራ ለማ፣ ገበየሁ አየለ፣ ሰለሞን ለማ፣
ሙሉነህ መንግሥቱ
መሥፍን ሀብተማርያምና ሌሎች (1977)አባደፋርና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች፡፡ አዲስ አበባ፣ ኩራዝ አሳታሚዎች
ድርጅት
- ዋቢ መጽሐፍት፣ የጽሑፍ መጠይቅ፣ የቃለ መጠይቅ/ካለ/ እና የመረካከቢያ ሰነድ ሲሆኑ እነዚህም በቅደም ተከተላቸው
የሮማን አሀዝ በመጠቀም በተለያዩ ገፆች ላይ ይሰፍራሉ፡፡ እንጀ ከዋናው ጽሑፍ ጋር ተጠቃሎ የገፅ ጽሑፍ አይሰጣቸውም፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
27
ጥናትና ምርምር